ምክክር ያስፈለገው እኮ የሀሳብ ልዩነት ስላለ ነው ። ልዩነት ደግሞ ተፈጥሯዊ እንጂ ወንጀል አይደለም። ልክ አይመርጡም ሲሉ እንደመረጥነዉ÷ አይተክሉም ሲሉ እንደተከልነዉ÷ አይወያዩም ሲሉ እየተወያየን ነው ።
ኢትዮጵያ እየመከረች ነው !
Solomon Dibaba ያስቀመጣት አጭር ግን ግልፅና ግዙፍ የጋራ መልዕክት
ከ OBN Afaan Oromoo እስከ AMN-Addis Media Network የደመቀ ጉዞ ማለት ይኼ ነው
ኢትዮጵያ እየመከረች ነው !
Solomon Dibaba ያስቀመጣት አጭር ግን ግልፅና ግዙፍ የጋራ መልዕክት
ከ OBN Afaan Oromoo እስከ AMN-Addis Media Network የደመቀ ጉዞ ማለት ይኼ ነው
በአሜሪካየ5 ዓመት ሕፃን ላይ የግብረ ሥጋ ድፍረት ፈጽሞ ህይወቷን ያጠፋው ወንጀለኛ በገዳይ መድኃኒት መርፌ ተገደለ።
በአሜሪካ አላባማ ግዛት፣ ካማሪ ሆላንድ የተባለች የ5 ዓመት ሕጻን ልጅ ላይ የግብረ ሥጋ ድፍረት ፈጽሞ ሕጿኗን በመግደሉ የተፈረደበት ጄረሚ ትሬማይን ዊሊያምስ የተባለ የ42 ዓመት ጎልማሳ ባለፈው በሞት ተቀጥቷል።
ካማሪ በ2021 ከጆርጂያ ኮሎምበስ ከተማ ከቤቷ ከጠፋች በኋላ ምርመራው ወደ አላባማ ፊኒክስ ሲቲ ተስፋፋ። ፖሊስ ዊሊያምስ በሚኖርበት ቤት ፍተሻ ሲያካሂድ የሕፃኗ እቃዎች ተገኝተዋል፤ በመጨረሻም አስክሬኗ ከሕንፃው ምድር ቤት ተገኝቷል።
በምርመራው መሠረት ሕፃኗ ከመገደሏ በፊት ታስራ የግብረ ሥጋ ድፍረት ተፈጽሞባት ነበር፤ በመጨረሻም በመታነቅ ሕይወቷን አጥታለች። በዊሊያምስ ስልክ ላይም ጥቃቱን የሚያሳዩ ቪዲዮዎች መገኘታቸው በፍርድ ሂደቱ ተገልጿል።
ዊሊያምስ እ.ኤ.አ በ2024 የሞት ፍርድ የተፈረደበት ሲሆን ጥፋተኛ መሆኑን አምኖ የይግባኝ ሂደቶችን ለመተው በመምረጡ የተፋጠነ የሞት ፍርድ ተፈጽሞበታል። በዚህም ባለፈው ሳምንት ሀሙስ ዕለት በገዳይ መድኃኒት መርፌ ተገድሏል።
የአላባማ ጠቅላይ አቃቤ ሕግ ቢሮ እንደገለጸው፣ ዊሊያምስ ከዚህ በፊትም በሌሎች ሕፃናት ላይ ጾታዊ ጥቃት መፈጸሙን መናዘዙ ተገልጿል።
የዊሊያምስ ግድያ በተፈጸመበት በዚያው ሀሙስ ቀን በኦክላሆማ እና ቴነሲ ግዛቶችም ሁለት ሌሎች የሞት ፍርዶች ተፈጽመዋል።
በኦክላሆማ 70 ዓመቱ ካርሎስ ኩዌስታ-ሮድሪጌዝ እ.ኤ.አ 2003 ባለቤቱን ኦሊምፒያ ፊሸር በመግደሉ ሞት ተፈርዶበር ተገድሏል። የሞት ፍርዱ ከመፈጸሙ በፊት ከ20 ዓመታት በላይ ዘብጥያ ተወርውሯል።
በቴነሲ ደግሞ 66 ዓመቱ አንቶኒ ዳረል ሂንስ እ.ኤ.አ በ1985 ካትሪን ጄን ጄንኪንሰን የተባለች የ54 ዓመት የሞቴል ሠራተኛ በመግደሉ ተገድሏል። የሞት ቅጣቱ የተፈጸመው ወንጀሉ ከተፈጸመ ከ40 ዓመታት በኋላ ነው። ግለሰቡ ላለፉት 40 ዓመታት በእስር ቆይቷል።
በአሜሪካ ኦክላሆማ፣ ቴነሲ እና አላባማ በአንድ ቀን ሶስት የሞት ቅጣቶችን ተፈጽመዋል። ይህ በአሜሪካ ከረጅም ዓመታት በኋላ በአንድ ቀን ሶስት ግዛቶች የሞት ቅጣት ሲፈጽሙ የታየ ክስተት ሆኗል።
ለመጨረሻ ጊዜ ሶስት የአሜሪካ ግዛቶች በአንድ ቀን የሞት ቅጣት የፈጸሙት እ.ኤ.አ ጥር 7 ቀን 2010 ነበር። የ2026ቱ ክስተት ከ16 ዓመታት በኋላ የተደገመ ነው።
ሶስቱ የሞት ቅጣቶች በግዛቶቹ በተናጠል የተወሰኑ እንጂ በአንድ ላይ እንዲፈጸሙ ተቀናጅተው አልነበረም።
በአሜሪካ አላባማ ግዛት፣ ካማሪ ሆላንድ የተባለች የ5 ዓመት ሕጻን ልጅ ላይ የግብረ ሥጋ ድፍረት ፈጽሞ ሕጿኗን በመግደሉ የተፈረደበት ጄረሚ ትሬማይን ዊሊያምስ የተባለ የ42 ዓመት ጎልማሳ ባለፈው በሞት ተቀጥቷል።
ካማሪ በ2021 ከጆርጂያ ኮሎምበስ ከተማ ከቤቷ ከጠፋች በኋላ ምርመራው ወደ አላባማ ፊኒክስ ሲቲ ተስፋፋ። ፖሊስ ዊሊያምስ በሚኖርበት ቤት ፍተሻ ሲያካሂድ የሕፃኗ እቃዎች ተገኝተዋል፤ በመጨረሻም አስክሬኗ ከሕንፃው ምድር ቤት ተገኝቷል።
በምርመራው መሠረት ሕፃኗ ከመገደሏ በፊት ታስራ የግብረ ሥጋ ድፍረት ተፈጽሞባት ነበር፤ በመጨረሻም በመታነቅ ሕይወቷን አጥታለች። በዊሊያምስ ስልክ ላይም ጥቃቱን የሚያሳዩ ቪዲዮዎች መገኘታቸው በፍርድ ሂደቱ ተገልጿል።
ዊሊያምስ እ.ኤ.አ በ2024 የሞት ፍርድ የተፈረደበት ሲሆን ጥፋተኛ መሆኑን አምኖ የይግባኝ ሂደቶችን ለመተው በመምረጡ የተፋጠነ የሞት ፍርድ ተፈጽሞበታል። በዚህም ባለፈው ሳምንት ሀሙስ ዕለት በገዳይ መድኃኒት መርፌ ተገድሏል።
የአላባማ ጠቅላይ አቃቤ ሕግ ቢሮ እንደገለጸው፣ ዊሊያምስ ከዚህ በፊትም በሌሎች ሕፃናት ላይ ጾታዊ ጥቃት መፈጸሙን መናዘዙ ተገልጿል።
የዊሊያምስ ግድያ በተፈጸመበት በዚያው ሀሙስ ቀን በኦክላሆማ እና ቴነሲ ግዛቶችም ሁለት ሌሎች የሞት ፍርዶች ተፈጽመዋል።
በኦክላሆማ 70 ዓመቱ ካርሎስ ኩዌስታ-ሮድሪጌዝ እ.ኤ.አ 2003 ባለቤቱን ኦሊምፒያ ፊሸር በመግደሉ ሞት ተፈርዶበር ተገድሏል። የሞት ፍርዱ ከመፈጸሙ በፊት ከ20 ዓመታት በላይ ዘብጥያ ተወርውሯል።
በቴነሲ ደግሞ 66 ዓመቱ አንቶኒ ዳረል ሂንስ እ.ኤ.አ በ1985 ካትሪን ጄን ጄንኪንሰን የተባለች የ54 ዓመት የሞቴል ሠራተኛ በመግደሉ ተገድሏል። የሞት ቅጣቱ የተፈጸመው ወንጀሉ ከተፈጸመ ከ40 ዓመታት በኋላ ነው። ግለሰቡ ላለፉት 40 ዓመታት በእስር ቆይቷል።
በአሜሪካ ኦክላሆማ፣ ቴነሲ እና አላባማ በአንድ ቀን ሶስት የሞት ቅጣቶችን ተፈጽመዋል። ይህ በአሜሪካ ከረጅም ዓመታት በኋላ በአንድ ቀን ሶስት ግዛቶች የሞት ቅጣት ሲፈጽሙ የታየ ክስተት ሆኗል።
ለመጨረሻ ጊዜ ሶስት የአሜሪካ ግዛቶች በአንድ ቀን የሞት ቅጣት የፈጸሙት እ.ኤ.አ ጥር 7 ቀን 2010 ነበር። የ2026ቱ ክስተት ከ16 ዓመታት በኋላ የተደገመ ነው።
ሶስቱ የሞት ቅጣቶች በግዛቶቹ በተናጠል የተወሰኑ እንጂ በአንድ ላይ እንዲፈጸሙ ተቀናጅተው አልነበረም።
"ሻዕቢያ ኤርትራን ወጣት አልባ ያደረገ ስር የሌለው የደረቀ እንጨት ማለት ነው" - የቀድሞው ህወሃት መስራች አረጋዊ በርሔ (ዶ/ር)
በማህበራዊ ሚዲያ አንዲት ታዳጊ ስትደበደብ የሚያሳይ ቪዲዮን በተመለከተ ፖሊስ አስፈላጊውን ምርመራ ማጣራቱን አስታወቀ፡፡
ፈርዶስ መሃመድ ፣ ኤደን ዳዊት እና ሃኒ ሁሴን የተባሉ ታዳጊ ተማሪዎች በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 4 አለም ባንክ አካባቢ ጓደኛቸውን ሲደበድቧት የሚያሳይ አሳዛኝ ቪዲዮ በማህበራዊ ሚዲያ መሰራጨቱን ተከትሎ ድርጊቱን የፈፀሙት ግለሰቦች በህግ እንዲጠየቁ ህብረተሰቡ አስተያየት እየሰጠ መሆኑ ይታወቃል፡፡
ድርጊቱ ጥቅምት 14 ቀን 2018 መፈፀሙን የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አስታውቆ ቪዲዮው በማህበራዊ ሚዲያ ከመሰራጨቱ ከወራት በፊት ወንጀሉን የፈፀሙትን ሦስት ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር በማዋል ምርመራ ማጣራቱን ፖሊስ ገልጿል፡፡
በወንጀሉ የተጠረጠሩት ሦስት ተማሪዎች ፍርድ ቤት ቀርበው በጊዜ ቀጠሮ ታስረው ፖሊስ አስፈላጊውን ማስረጃ በማሰባሰብ የምርመራ መዝገቡን አጠናቆ መዝገቡን ለሚመለከተው የፍትህ አካል መላኩን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል፡፡
ልጅቷ ስትደበደብ የሚያሳየው ቪዲዩ መለቀቁ በልጅቷም ሆነ በቤተሰቧ ላይ አሉታዊ ጫና የሚያሳድር በመሆኑ ቪዲዮውን የለቀቀውን አካል ለማረጋገጥ ፖሊስ ሦስቱን ተጠርጣሪዎች በድጋሚ በቁጥጥር ስር አውሎ ተጨማሪ ምርመራ እያጣራ መሆኑን ገልጿል፡፡
ህብረተሰቡ ድርጊቱን በማውገዝ ወንጀሉን የፈፀሙ ሰዎች በህግ መጠየቅ እንዳለባቸው ያሳየውን መቆርቆር የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አድንቋል፡፡
የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ
ፈርዶስ መሃመድ ፣ ኤደን ዳዊት እና ሃኒ ሁሴን የተባሉ ታዳጊ ተማሪዎች በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 4 አለም ባንክ አካባቢ ጓደኛቸውን ሲደበድቧት የሚያሳይ አሳዛኝ ቪዲዮ በማህበራዊ ሚዲያ መሰራጨቱን ተከትሎ ድርጊቱን የፈፀሙት ግለሰቦች በህግ እንዲጠየቁ ህብረተሰቡ አስተያየት እየሰጠ መሆኑ ይታወቃል፡፡
ድርጊቱ ጥቅምት 14 ቀን 2018 መፈፀሙን የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አስታውቆ ቪዲዮው በማህበራዊ ሚዲያ ከመሰራጨቱ ከወራት በፊት ወንጀሉን የፈፀሙትን ሦስት ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር በማዋል ምርመራ ማጣራቱን ፖሊስ ገልጿል፡፡
በወንጀሉ የተጠረጠሩት ሦስት ተማሪዎች ፍርድ ቤት ቀርበው በጊዜ ቀጠሮ ታስረው ፖሊስ አስፈላጊውን ማስረጃ በማሰባሰብ የምርመራ መዝገቡን አጠናቆ መዝገቡን ለሚመለከተው የፍትህ አካል መላኩን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል፡፡
ልጅቷ ስትደበደብ የሚያሳየው ቪዲዩ መለቀቁ በልጅቷም ሆነ በቤተሰቧ ላይ አሉታዊ ጫና የሚያሳድር በመሆኑ ቪዲዮውን የለቀቀውን አካል ለማረጋገጥ ፖሊስ ሦስቱን ተጠርጣሪዎች በድጋሚ በቁጥጥር ስር አውሎ ተጨማሪ ምርመራ እያጣራ መሆኑን ገልጿል፡፡
ህብረተሰቡ ድርጊቱን በማውገዝ ወንጀሉን የፈፀሙ ሰዎች በህግ መጠየቅ እንዳለባቸው ያሳየውን መቆርቆር የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አድንቋል፡፡
የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ
“አዲስ አበባ ከ5 ሚሎዮን በላይ ህዝብ የሚኖርባት፤ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ መኪኖች ያሉባት ከተማ ነች፡፡ የዛሬ ሶስት እና አራት አመት ገደማ ብዙ ፓርኪንግ ካመኖሩ የተነሳ አስፓልቱ የመኪና ማቆሚያም ነው፣ መንቀሳቀሻም ነው የእግረኛም መሄጃ ከመሆኑ የተነሳ ለአደጋ ሲያጋልጥ ነበር፡፡” - ክቡር ጠቅላይ ሚኒስተር አብይ አህመድ (ደ/ር)
ዛሬስ ምን ለውጥ ተገኘ? ከዘገባው ይከታተሉ
ዛሬስ ምን ለውጥ ተገኘ? ከዘገባው ይከታተሉ
WOW Dr. Birhanu M Lenjiso
አጭር ግን ተሻጋሪ ሃሳብ፣
ግልፅ ደግሞም እጅግ ጠቃሚ ንግግር
እናመሠግናለን ዶ/ር ብርሃኑ ሌንጂሶ
አጭር ግን ተሻጋሪ ሃሳብ፣
ግልፅ ደግሞም እጅግ ጠቃሚ ንግግር
እናመሠግናለን ዶ/ር ብርሃኑ ሌንጂሶ
#ታግዷል❗️
ከ2.2 ቢሊዮን ብር በላይ ጥሬ ገንዘብ፣ ዋጋቸው ከ220 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመቱ አክሲዮኖች፣ ከ5 ሚሊዮን ካሬ ሜትር በላይ መሬት፣ ከ200 በላይ ቤቶች፣ ከ300 በላይ ተሽከርካሪዎች እና 69 ከባድ ማሽነሪዎች…
በኢትዮጵያ በታክስና ግብር ስወራ፣ በሙስና፣ በሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር፣ በኦንላይን ማጭበርበር እና ከሌሎች ከባድ ወንጀሎች ጋር ግንኙነት አለው የተባለ በቢሊየን ብር የሚቆጠር ንብረት መታገዱን የፌደራል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ አስታውቋል።
በ2018 ዓ.ም ብቻ በተከናወነ የምርመራና የሕግ ማስከበር ሥራ፣ በ544 የክስ መዝገቦች ሥር የተካተቱ በርካታ ሀብቶች ታግደው የሕግ ሂደታቸውን በመጠባበቅ ላይ ይገኛሉ ተብሏል።
በዚህም መሠረት ከ2.2 ቢሊዮን ብር በላይ ጥሬ ገንዘብ፣ ዋጋቸው ከ220 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመቱ አክሲዮኖች፣ ከ5 ሚሊዮን ካሬ ሜትር በላይ መሬት፣ ከ200 በላይ ቤቶች፣ ከ300 በላይ ተሽከርካሪዎች እና 69 ከባድ ማሽነሪዎች በቁጥጥር ሥር እንዲውሉና እንዲታገዱ መደረጉን ሸገር አኤፍ አኤም ዘግቧል።
ሥራ ላይ ከዋለ ከአንድ ዓመት በላይ የሆነው አዋጁ የሕገ-ወጥ ሀብት ምንጭን በጥብቅ በመመርመርና በማረጋገጥ፣ ንብረቱ ለመንግሥትና ለሕዝብ ጥቅም የሚወረስበትን ግልጽ ሕጋዊ አሰራር ዘርግቷል።
ሕጉ በጸደቀበት ወቅት እስከ 10 ዓመት ወደ ኋላ ተመልሶ ተጠያቂነት እንዲኖር መፍቀዱ በበርካቶች ዘንድ ከፍተኛ ክርክር አስነስቶ እንደነበር ይታወሳል።
በተለመደው የሕግ አሰራር አንድ ንብረት በሕገ-ወጥ መንገድ መገኘቱን ማስረዳት ያለበት ከሳሽ አካል ቢሆንም፤ በዚህ አዋጅ መሠረት ግን «ሀብቴ በሕጋዊ መንገድ የተገኘ ነው» ብሎ የማሳመንና የማስረዳት ሸክሙ ሙሉ በሙሉ የተከሳሹ ነው።
አዋጁ የታወቀ የገቢ ምንጭ ያላቸው ሰዎች ከሚያገኙት ገቢ ጋር ያልተመጣጠነና የተጋነነ የሀብት ልዩነት ሲገኝባቸው ወይም ምክንያታዊ ጥርጣሬ ሲኖር ምርመራ እንዲደረግባቸው ይደነግጋል።
በተመሳሳይ የታወቀ የገቢ ምንጭ የሌላቸው ግለሰቦች ያፈሩትን ሀብት እንዴትና በምን መንገድ እንዳጠራቀሙት ማስረዳት ካልቻሉ፣ ምርመራ ተካሂዶ ክስ በመመሥረት ንብረቱ እንዲወረስ ያዝል።
በጠቅላይ ዐቃቤ-ሕግ የሀብት ማስመለስ ዳይሬክቶሬት ምክትል ዳይሬክተር አቶ ሰለሞን ኃይሌ የአዋጁ ዋና ዓላማ በሕገ-ወጥ መንገድ የተገኘን ሀብት መለየት፣ መመርመር፣ ማገድና የፍርድ ቤት ሂደቱ ሲጠናቀቅ ደግሞ ሙሉ በሙሉ መውረስ እንደሆነ አስረድተዋል።
በ2018 ዓ.ም የታገዱት ጥሬ ገንዘቦች፣ አክሲዮኖች፣ መሬቶችና ሌሎች ንብረቶች ከጀርባቸው ትላልቅ የኢኮኖሚና የማህበራዊ ወንጀሎች ያሉባቸው እንደሆኑ የጠቆሙት ምክትል ዳይሬክተሩ፣ የወንጀል ጉዳዮቹ በሕግ ሂደት ውሳኔ ሲያገኙ የውርስ አቤቱታው በይፋ እንደሚቀጥል አብራርተዋል።
የሀብት ማስመለስ አዋጁ ትግበራ ወደፊትም ተጠናክሮ ይቀጥላል የተባለ ሲሆን፣ ሰሞኑንም የሀገሪቱን የፋይናንስ ሥርዓት የሚያናጉ ተግባራት ላይ የተሰማሩ ናቸው ተብለው የተጠረጠሩ 169 ግለሰቦች እንዲሁም በገቢዎችና ጉምሩክ ዘርፍ የተጠረጠሩ 109 ግለሰቦች ተለይተዋል።
ከእነዚህም መካከል እስካሁን 91 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሥር ውለው ምርመራ እየተካሄደባቸው መሆኑን የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ማስታወቁንም ነው ዘገባው ያመላከተው።
ከ2.2 ቢሊዮን ብር በላይ ጥሬ ገንዘብ፣ ዋጋቸው ከ220 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመቱ አክሲዮኖች፣ ከ5 ሚሊዮን ካሬ ሜትር በላይ መሬት፣ ከ200 በላይ ቤቶች፣ ከ300 በላይ ተሽከርካሪዎች እና 69 ከባድ ማሽነሪዎች…
በኢትዮጵያ በታክስና ግብር ስወራ፣ በሙስና፣ በሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር፣ በኦንላይን ማጭበርበር እና ከሌሎች ከባድ ወንጀሎች ጋር ግንኙነት አለው የተባለ በቢሊየን ብር የሚቆጠር ንብረት መታገዱን የፌደራል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ አስታውቋል።
በ2018 ዓ.ም ብቻ በተከናወነ የምርመራና የሕግ ማስከበር ሥራ፣ በ544 የክስ መዝገቦች ሥር የተካተቱ በርካታ ሀብቶች ታግደው የሕግ ሂደታቸውን በመጠባበቅ ላይ ይገኛሉ ተብሏል።
በዚህም መሠረት ከ2.2 ቢሊዮን ብር በላይ ጥሬ ገንዘብ፣ ዋጋቸው ከ220 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመቱ አክሲዮኖች፣ ከ5 ሚሊዮን ካሬ ሜትር በላይ መሬት፣ ከ200 በላይ ቤቶች፣ ከ300 በላይ ተሽከርካሪዎች እና 69 ከባድ ማሽነሪዎች በቁጥጥር ሥር እንዲውሉና እንዲታገዱ መደረጉን ሸገር አኤፍ አኤም ዘግቧል።
ሥራ ላይ ከዋለ ከአንድ ዓመት በላይ የሆነው አዋጁ የሕገ-ወጥ ሀብት ምንጭን በጥብቅ በመመርመርና በማረጋገጥ፣ ንብረቱ ለመንግሥትና ለሕዝብ ጥቅም የሚወረስበትን ግልጽ ሕጋዊ አሰራር ዘርግቷል።
ሕጉ በጸደቀበት ወቅት እስከ 10 ዓመት ወደ ኋላ ተመልሶ ተጠያቂነት እንዲኖር መፍቀዱ በበርካቶች ዘንድ ከፍተኛ ክርክር አስነስቶ እንደነበር ይታወሳል።
በተለመደው የሕግ አሰራር አንድ ንብረት በሕገ-ወጥ መንገድ መገኘቱን ማስረዳት ያለበት ከሳሽ አካል ቢሆንም፤ በዚህ አዋጅ መሠረት ግን «ሀብቴ በሕጋዊ መንገድ የተገኘ ነው» ብሎ የማሳመንና የማስረዳት ሸክሙ ሙሉ በሙሉ የተከሳሹ ነው።
አዋጁ የታወቀ የገቢ ምንጭ ያላቸው ሰዎች ከሚያገኙት ገቢ ጋር ያልተመጣጠነና የተጋነነ የሀብት ልዩነት ሲገኝባቸው ወይም ምክንያታዊ ጥርጣሬ ሲኖር ምርመራ እንዲደረግባቸው ይደነግጋል።
በተመሳሳይ የታወቀ የገቢ ምንጭ የሌላቸው ግለሰቦች ያፈሩትን ሀብት እንዴትና በምን መንገድ እንዳጠራቀሙት ማስረዳት ካልቻሉ፣ ምርመራ ተካሂዶ ክስ በመመሥረት ንብረቱ እንዲወረስ ያዝል።
በጠቅላይ ዐቃቤ-ሕግ የሀብት ማስመለስ ዳይሬክቶሬት ምክትል ዳይሬክተር አቶ ሰለሞን ኃይሌ የአዋጁ ዋና ዓላማ በሕገ-ወጥ መንገድ የተገኘን ሀብት መለየት፣ መመርመር፣ ማገድና የፍርድ ቤት ሂደቱ ሲጠናቀቅ ደግሞ ሙሉ በሙሉ መውረስ እንደሆነ አስረድተዋል።
በ2018 ዓ.ም የታገዱት ጥሬ ገንዘቦች፣ አክሲዮኖች፣ መሬቶችና ሌሎች ንብረቶች ከጀርባቸው ትላልቅ የኢኮኖሚና የማህበራዊ ወንጀሎች ያሉባቸው እንደሆኑ የጠቆሙት ምክትል ዳይሬክተሩ፣ የወንጀል ጉዳዮቹ በሕግ ሂደት ውሳኔ ሲያገኙ የውርስ አቤቱታው በይፋ እንደሚቀጥል አብራርተዋል።
የሀብት ማስመለስ አዋጁ ትግበራ ወደፊትም ተጠናክሮ ይቀጥላል የተባለ ሲሆን፣ ሰሞኑንም የሀገሪቱን የፋይናንስ ሥርዓት የሚያናጉ ተግባራት ላይ የተሰማሩ ናቸው ተብለው የተጠረጠሩ 169 ግለሰቦች እንዲሁም በገቢዎችና ጉምሩክ ዘርፍ የተጠረጠሩ 109 ግለሰቦች ተለይተዋል።
ከእነዚህም መካከል እስካሁን 91 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሥር ውለው ምርመራ እየተካሄደባቸው መሆኑን የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ማስታወቁንም ነው ዘገባው ያመላከተው።
👍1
"እኛ ኢትዮጵያውያን ሕብረ ብሔራዊነትን በማጠናከር በገዥ ትርክት ተሸምነን ተቋማዊ ለውጥን እያጠናከርንና ብሔራዊ ጥቅማችንን እያሳካን ሁለንተናዊ ብልጽግናን ማረጋገጥ አለብን" - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
በአሁኑ ወቅት የሚታየውን የዝናብ ሁኔታ ተከትሎ የጎርፍ አደጋ ሊከሰት ስለሚችል ጥንቃቄዎችን አድርጉ ሲል የአዲስ አበባ የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አሳሰበ፡፡
ኮሚሽኑ የጥንቃቄ መልእክቱን በማህበራዊ ትስስር ገጹ ያጋራ ሲሆን ህብረተሰቡ በአሁኑ ወቅት የሚታየውን የዝናብ ሁኔታ ተከትሎ የጎርፍ አደጋ ሊከሰት ስለሚችል ጥንቃቄ ያድርግ ሲል አሳስቧል፡፡በዚህም በወንዝ ዳርቻና ዝቅተኛ ቦታዎች ላይ የሚገኙ ነዋሪዎች የውኃው መጠን ከመጨመሩ በፊት ጥንቃቄ ያድርጉ ብሏል።
በሉላ በኩልም የውኃ መውረጃዎችን መፈተሸ፣ በቤት ዙሪያ ያሉ ቦዮች በቆሻሻ አለመደፈናቸውን ማረጋገጥ እና የልጆችን ውሎ መጠበቅ አስፈላጊ መሆኑ ተጠቁሟል።
ዝናብ በሚዘንብበት ወቅት ልጆች ከቤት እንዳይወጡና ወደ ዋና ዋና የጎርፍ መውረጃዎች እንዳይጠጉ መቆጣጠር ይገባል ተብሏል፡፡
አደገኛ የጎርፍ ምልክት በሚታይበት ወቅት በአደጋ ጊዜ ስልክ 939 ላይ በመደወል ያሳውቁ ሲል ኮሚሽኑ አሳስባል።
ኮሚሽኑ የጥንቃቄ መልእክቱን በማህበራዊ ትስስር ገጹ ያጋራ ሲሆን ህብረተሰቡ በአሁኑ ወቅት የሚታየውን የዝናብ ሁኔታ ተከትሎ የጎርፍ አደጋ ሊከሰት ስለሚችል ጥንቃቄ ያድርግ ሲል አሳስቧል፡፡በዚህም በወንዝ ዳርቻና ዝቅተኛ ቦታዎች ላይ የሚገኙ ነዋሪዎች የውኃው መጠን ከመጨመሩ በፊት ጥንቃቄ ያድርጉ ብሏል።
በሉላ በኩልም የውኃ መውረጃዎችን መፈተሸ፣ በቤት ዙሪያ ያሉ ቦዮች በቆሻሻ አለመደፈናቸውን ማረጋገጥ እና የልጆችን ውሎ መጠበቅ አስፈላጊ መሆኑ ተጠቁሟል።
ዝናብ በሚዘንብበት ወቅት ልጆች ከቤት እንዳይወጡና ወደ ዋና ዋና የጎርፍ መውረጃዎች እንዳይጠጉ መቆጣጠር ይገባል ተብሏል፡፡
አደገኛ የጎርፍ ምልክት በሚታይበት ወቅት በአደጋ ጊዜ ስልክ 939 ላይ በመደወል ያሳውቁ ሲል ኮሚሽኑ አሳስባል።
👍1