መረጃ ዘመደመር
1.01K subscribers
48K photos
1.81K videos
14 files
15.8K links
Download Telegram
ዩክሬን 600 ድሮኖችን በሩሲያ ላይ አዘነበች።

ዩክሬን ዛሬ ለሊት ወደ 600 የሚጠጉ ድሮኖችን በመተኮስ በሞስኮ እና በዙሪያዋ ላይ መጠነ ሰፊ የአየር ጥቃት ሰነዘረች። 

በጥቃቱ በፖዶልስክ እና በዶሞዴዶቮ የሚገኙ የሎጂስቲክስ መጋዘኖች (የሩሲያው ትልቅ የኦንላይን ገበያ ዋይልድቤሪስን ጨምሮ) በእሳት ተቃጥለዋል።

​የሞስኮ ከንቲባ ሰርጌ ሶቢያኒን ድርጊቱን በቅርብ ጊዜያት ከተሰነዘሩት ትልልቅ ጥቃቶች አንዱ ሲሉ የገለጹት ሲሆን፣ የሩሲያ ባለስልጣናት በመቶዎች የሚቆጠሩ ድሮኖችን መጣላቸውን አስታውቀዋል።

በተመሳሳይ ሌሊት ሩሲያ በዩክሬን ላይ በሰነዘረችው የአየር ጥቃት ቢያንስ አምስት ሰዎች የተገደሉ ሲሆን፣ ይህም በሁለቱ ወገኖች መካከል ያለውን የረጅም ርቀት ጥቃት አዲስ ከፍተኛ ደረጃ ላይ አድርሶታል።
"የተጀመረው ሀገራዊ ምክክር ባህል ሆኖ መቀጠል አለበት" ዶክተር ብርሃኑ ሌንጂሶ

"በኢትዮጵያ እየተካሔደ ያለው ሀገራዊ ምክክር ቀጣይነት ኖሮት ውይይት እንደ ባህል መወሰድ አለበት" ሲሉ ዶክተር ብርሃኑ ሌንጂሶ ተናግረዋል።

“ብሔርተኝነት” የተሰኘው መጽሐፍ ደራሲ እና ፖለቲከኛው ዶክተር ብርሃኑ ከአሐዱ መድረክ ጋር በነበራቸው ቆይታ፣ በምክክሩ ከሚታዩ ችግሮች ትምህርት በመውሰድ ሂደቱን የተሻለ አሳታፊ እና ገለልተኛ ማድረግ እንደሚገባ ተናግረዋል።

በተጨማሪም፤ ሀገር የሚገነባው “በምክክር” እንደሆነ እና ዜጎች ጠንካራ ሀገር መገንባት የሚችሉት “በስምምነት ብቻ” መሆኑን አንስተዋል።

ሰላማዊ መንገድን በመከተል ሀገር መገንባት የሚፈልጉ የፖለቲካ ኃይሎች በምክክሩ መሳተፍ እንዳለባቸው ጠቁመው፣ የፖለቲካ ልሂቃን ድርድር እንደሚያስፈልግም ገልጸዋል።

"ሀገራዊ ምክክር በኢትዮጵያ ጉዳይ ያገባኛል የሚልን ሁሉ ማካተት እንዳለበት" የሚል ሐሳብ ያነሱት ዶክተር ብርሃኑ የችግሩ ዋና መንስኤ ህዝቡ ሳይሆን የፖለቲካ ልሂቃን በመሆናው፤ ዜጎች በራሳቸው መንገድ በምክክር ሂደቱ በመሳተፍ ችግሮቹን መፍታት እንደሚገባቸው አሳስበዋል፡፡
በ2009 ዓ.ም በቀን 20 ሺህ ሜትር ኪዩብ ብቻ የነበረው ፍሳሽ የማጣራት አቅማችን የዛሬውን ጨምሮ ወደ 253 ሺህ ሜትር ኪዩብ በላይ ያሳደግን ሲሆን፣ እንዲሁም በ2011 ዓ.ም በቀን 525 ሺህ ሜትር ኪዩብ ብቻ የነበረዉን የንፁህ መጠጥ ዉሃ የማምረት አቅማችን አሁን ላይ ወደ 910 ሺህ ሜትር ኪዩብ ማሳደግ ችለናል፡፡

በተለይ ዛሬ የመረቅናቸዉ ደግሞ የማምረት አቅምን ከማሳደግ ባሻገር አለም የደረሰበትን እጅግ የረቀቁ ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም በዘላቂነት ፈርቀዳጅ ሚና አላቸዉ።

አዲስ አበባ እንደ ስሟ ውብ፣ አዲስ ፥ ጽዱ፣ ጤናማ፣ አረንጓዴ በማድረግ እና አገልግሎትን የሚያሳልጡ ዘመናዊ መሰረተ ልማቶችን ከዛሬ አልፎ ለትውልድ የምታሸጋግር ከተማ ለማድረግ የጀመርነው ግብ ተጠናክሮ ይቀጥላል ።

ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን ይባርክ

ክብርት ከንቲባ ወ/ሮ Adanech Abiebie- አዳነች አቤቤ
ምክክር ያስፈለገው እኮ የሀሳብ ልዩነት ስላለ ነው ። ልዩነት ደግሞ ተፈጥሯዊ እንጂ ወንጀል አይደለም። ልክ አይመርጡም ሲሉ እንደመረጥነዉ÷ አይተክሉም ሲሉ እንደተከልነዉ÷ አይወያዩም ሲሉ እየተወያየን ነው ።

ኢትዮጵያ እየመከረች ነው !
Solomon Dibaba ያስቀመጣት አጭር ግን ግልፅና ግዙፍ የጋራ መልዕክት

ከ OBN Afaan Oromoo እስከ AMN-Addis Media Network የደመቀ ጉዞ ማለት ይኼ ነው
በአሜሪካየ5 ዓመት ሕፃን ላይ የግብረ ሥጋ ድፍረት ፈጽሞ ህይወቷን ያጠፋው ወንጀለኛ በገዳይ መድኃኒት መርፌ ተገደለ።

በአሜሪካ አላባማ ግዛት፣ ካማሪ ሆላንድ የተባለች የ5 ዓመት ሕጻን ልጅ ላይ የግብረ ሥጋ ድፍረት ፈጽሞ ሕጿኗን በመግደሉ የተፈረደበት ጄረሚ ትሬማይን ዊሊያምስ የተባለ የ42 ዓመት ጎልማሳ ባለፈው በሞት ተቀጥቷል።

ካማሪ በ2021 ከጆርጂያ ኮሎምበስ ከተማ ከቤቷ ከጠፋች በኋላ ምርመራው ወደ አላባማ ፊኒክስ ሲቲ ተስፋፋ። ፖሊስ ዊሊያምስ በሚኖርበት ቤት ፍተሻ ሲያካሂድ የሕፃኗ እቃዎች ተገኝተዋል፤ በመጨረሻም አስክሬኗ ከሕንፃው ምድር ቤት ተገኝቷል።

በምርመራው መሠረት ሕፃኗ ከመገደሏ በፊት ታስራ የግብረ ሥጋ ድፍረት ተፈጽሞባት ነበር፤ በመጨረሻም በመታነቅ ሕይወቷን አጥታለች። በዊሊያምስ ስልክ ላይም ጥቃቱን የሚያሳዩ ቪዲዮዎች መገኘታቸው በፍርድ ሂደቱ ተገልጿል።

ዊሊያምስ እ.ኤ.አ በ2024 የሞት ፍርድ የተፈረደበት ሲሆን ጥፋተኛ መሆኑን አምኖ የይግባኝ ሂደቶችን ለመተው በመምረጡ የተፋጠነ የሞት ፍርድ ተፈጽሞበታል። በዚህም ባለፈው ሳምንት ሀሙስ ዕለት በገዳይ መድኃኒት መርፌ ተገድሏል።

የአላባማ ጠቅላይ አቃቤ ሕግ ቢሮ እንደገለጸው፣ ዊሊያምስ ከዚህ በፊትም በሌሎች ሕፃናት ላይ ጾታዊ ጥቃት መፈጸሙን መናዘዙ ተገልጿል።

የዊሊያምስ ግድያ በተፈጸመበት በዚያው ሀሙስ ቀን በኦክላሆማ እና ቴነሲ ግዛቶችም ሁለት ሌሎች የሞት ፍርዶች ተፈጽመዋል።

በኦክላሆማ 70 ዓመቱ ካርሎስ ኩዌስታ-ሮድሪጌዝ እ.ኤ.አ 2003 ባለቤቱን ኦሊምፒያ ፊሸር በመግደሉ ሞት ተፈርዶበር ተገድሏል። የሞት ፍርዱ ከመፈጸሙ በፊት ከ20 ዓመታት በላይ ዘብጥያ ተወርውሯል።

በቴነሲ ደግሞ 66 ዓመቱ አንቶኒ ዳረል ሂንስ እ.ኤ.አ በ1985 ካትሪን ጄን ጄንኪንሰን የተባለች የ54 ዓመት የሞቴል ሠራተኛ በመግደሉ ተገድሏል። የሞት ቅጣቱ የተፈጸመው ወንጀሉ ከተፈጸመ ከ40 ዓመታት በኋላ ነው። ግለሰቡ ላለፉት 40 ዓመታት በእስር ቆይቷል።

በአሜሪካ ኦክላሆማ፣ ቴነሲ እና አላባማ በአንድ ቀን ሶስት የሞት ቅጣቶችን ተፈጽመዋል። ይህ በአሜሪካ ከረጅም ዓመታት በኋላ በአንድ ቀን ሶስት ግዛቶች የሞት ቅጣት ሲፈጽሙ የታየ ክስተት ሆኗል።

ለመጨረሻ ጊዜ ሶስት የአሜሪካ ግዛቶች በአንድ ቀን የሞት ቅጣት የፈጸሙት እ.ኤ.አ ጥር 7 ቀን 2010 ነበር። የ2026ቱ ክስተት ከ16 ዓመታት በኋላ የተደገመ ነው።

ሶስቱ የሞት ቅጣቶች በግዛቶቹ በተናጠል የተወሰኑ እንጂ በአንድ ላይ እንዲፈጸሙ ተቀናጅተው አልነበረም።
"ሻዕቢያ ኤርትራን ወጣት አልባ ያደረገ ስር የሌለው የደረቀ እንጨት ማለት ነው" - የቀድሞው ህወሃት መስራች አረጋዊ በርሔ (ዶ/ር)
"ጊዜው የኢትዮጵያ ነው" - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
በማህበራዊ ሚዲያ አንዲት ታዳጊ ስትደበደብ የሚያሳይ ቪዲዮን በተመለከተ ፖሊስ አስፈላጊውን ምርመራ ማጣራቱን አስታወቀ፡፡

ፈርዶስ መሃመድ ፣ ኤደን ዳዊት እና ሃኒ ሁሴን የተባሉ ታዳጊ ተማሪዎች በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 4 አለም ባንክ አካባቢ ጓደኛቸውን ሲደበድቧት የሚያሳይ አሳዛኝ ቪዲዮ በማህበራዊ ሚዲያ መሰራጨቱን ተከትሎ ድርጊቱን የፈፀሙት ግለሰቦች  በህግ እንዲጠየቁ ህብረተሰቡ አስተያየት እየሰጠ መሆኑ ይታወቃል፡፡

ድርጊቱ ጥቅምት 14 ቀን 2018 መፈፀሙን  የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አስታውቆ ቪዲዮው በማህበራዊ ሚዲያ ከመሰራጨቱ ከወራት በፊት ወንጀሉን የፈፀሙትን ሦስት ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር በማዋል ምርመራ ማጣራቱን ፖሊስ ገልጿል፡፡ 

በወንጀሉ የተጠረጠሩት ሦስት ተማሪዎች ፍርድ ቤት ቀርበው በጊዜ ቀጠሮ ታስረው ፖሊስ አስፈላጊውን ማስረጃ በማሰባሰብ የምርመራ መዝገቡን  አጠናቆ መዝገቡን ለሚመለከተው የፍትህ አካል መላኩን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል፡፡ 

ልጅቷ ስትደበደብ የሚያሳየው ቪዲዩ መለቀቁ በልጅቷም ሆነ በቤተሰቧ ላይ  አሉታዊ  ጫና የሚያሳድር በመሆኑ ቪዲዮውን የለቀቀውን አካል ለማረጋገጥ ፖሊስ ሦስቱን ተጠርጣሪዎች በድጋሚ  በቁጥጥር ስር አውሎ ተጨማሪ  ምርመራ እያጣራ መሆኑን ገልጿል፡፡
ህብረተሰቡ ድርጊቱን በማውገዝ ወንጀሉን የፈፀሙ ሰዎች በህግ መጠየቅ እንዳለባቸው ያሳየውን  መቆርቆር የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አድንቋል፡፡


የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ