“በጦርነት ተጀምሮ በጦርነት ያለቀ ታሪክ የለም ፤ ሕዝቡም ውጊያውን ከዚህ በላይ መሸከም አይችልም” - ካፒቴን ማስረሻ ሰጤ
የተደበቀው_አስፈሪ_እውነት!
የ “TikTok Creative Award” (ሽልማት)አደገኛ ደወል!
✍️ ዶ/ር በረከት አማኑኤል
ከሰሞኑ የተከናወነው የ “TikTok Creative Award” ደማቅ አልባሳት ቅንጦትና አፍራሽ ተግባራት የታዩበት ሊያሳየን ያልቻለው አንድ አስፈሪ እውነት የሀገራችንን የወደፊት አቅጣጫ የሚወስን ነው።
ጥያቄው፡- እየሸለምን ያለነው ሀገር ገንቢዎችን ወይስ ጊዜ ገዳዮችን? የሚለው ነው። ከበለፀጉት ሀገራት ተሞክሮ አንፃር ሲታይ፣ የዘንድሮው ሽልማት ለወጣቱ ያስተላለፈው መልእክት እጅግ አደገኛ ነው።
Has to be banned!!
#ለምን?
1. የቻይናን ጥበብ ወይስ የቻይናን ቆሻሻ? (The Double Standard) የቲክቶክ ባለቤት የሆነችው ቻይና፣ ዓለምን በቴክኖሎጂ የተቆጣጠረችው በመጨፈር አይደለም።
ቻይና ለገዛ ወጣቶቿ የምትፈቅደው የቲክቶክ ቅጂ (Douyin)፣ ከ14 ዓመት በታች ለሆኑ ህፃናት የሚያሳየው የሳይንስ ሙከራዎችን፣ የሮቦቲክስ ፈጠራዎችን እና የአገር ፍቅር ታሪኮችን ብቻ ነው።
#ለምን?
ምክንያቱም “ነገን የሚረከበው ትውልድ ጭንቅላት በዕውቀት እንጂ መደንዘዝ የለበትም” ብለው ስለሚያምኑ ወደኛ ሲመጣ ግን ነገሩ ተገላቢጦሽ ነው።
ሽልማታችን የሳይንስ፣ የቴክኖሎጂ፣ የመፅሀፍ እና የበጎ አድራጎት ስራዎችን ወደ ዳር ገፍቶ “ቀልድን”የጀግንነት ማማ ላይ ሰቀለ። ቻይና ለልጆቿ የዕውቀት ወተት ስትግት፣ እኛ ለልጆቻችን በመዝናኛ የተለወሰ መርዝ እየሰጠን ይሆን? ይህንን ቆም ብለን ልንጠይቅ ልንመረምር ይገባል።
2. “Creative” gፈጠራ) ወይስ “Viral” (ማነጋገሪያ)? ቃላትን በትክክል እንጠቀም። “ፈጠራ” (Creativity) ማለት የህዝብን ችግር የሚፈታ፣ አዲስ እሴት የሚጨምር እና ትውልድን የሚያሻግር ስራ ነው።
ስልክን አገላብጦ በመቅረጽ በሺዎች የሚቆጠሩ “ላይክ”ማግኘት ታዋቂነት (Popularity) እንጂ ፈጠራ (Creativity) ሊሆን አይችልም።
ባደጉት ሀገራት ሽልማት የሚሰጠው ለይዘት ጥራት እና ለሚያመጣው ለውጥ ነው።
እኛ ጋር ግን መስፈርቱ የቁጥር ጨዋታ ሆነ። ሳይንስን፣ ህክምናን እና ትምህርትን የሚያስተላልፉ ቻናሎች እንደ ሁለተኛ ሲታዩ፣ ቀላል መዝናኛዎች የክብር ዙፋን ላይ ተቀምጠዋል። እውቀት በ “ላይክ”ብዛት አይለካም፤ እውነትም በ “ሼር” ብዛት አይረጋገጥም።
3. ለወጣቱ የተላለፈው አደገኛ መልእክት (The Wrong Role Models) አንድ ወጣት ይህንን ሽልማት ሲመለከት አእምሮው ውስጥ የሚቀረፀው ምንድን ነው?
"ለካ ክብር ለማግኘት ተምሮ ዲግሪ መያዝ፣ ሌሊት ተቀን ለሀገር የሚጠቅም ምርምር ማድረግ ወይም መፅሀፍ መጻፍ አይጠበቅብኝም።"
"ለካ አቋራጭ መንገድ አለ! ስልኬ ላይ ብጨፍር፣ በቅጽበት 'የዓመቱ ምርጥ' ተብዬ እሸለማለሁ።"
ይህ አስተሳሰብ የስራ ባህልን (Work ethic) የሚገድል መርዝ ነው። አሜሪካን፣ ጃፓንን እና ጀርመንን የገነቡት ፊታቸው በላብ የረጠበ ኢንጂነሮች ሐኪሞች ሙህራኖች ና ገበሬዎች እንጂ፣ ካሜራ ፊት የሚሽሞነሞኑ አይደሉም።
ወጣቱን ትምህርት እና የሥራ ጎዳና አውጥተን፣ ወደ አቋራጭ መንገድ እየገፋነው ነዉ አገርንም ጭምር!
4. የባህል ወረራ በሽልማት ስም
ሽልማቱ ላይ የታየው የአለባበስ እና የቅንጦት ትርኢት፣ የኢትዮጵያን ወጣት ማንነት የሚወክል ነበር? ወይስ የሆሊውድን "Red Carpet" ለመኮረጅ ?
#Dr.BEREKET EMMANUEL
MD, Author
Founder @influential youth Ethiopia CEO
የ “TikTok Creative Award” (ሽልማት)አደገኛ ደወል!
✍️ ዶ/ር በረከት አማኑኤል
ከሰሞኑ የተከናወነው የ “TikTok Creative Award” ደማቅ አልባሳት ቅንጦትና አፍራሽ ተግባራት የታዩበት ሊያሳየን ያልቻለው አንድ አስፈሪ እውነት የሀገራችንን የወደፊት አቅጣጫ የሚወስን ነው።
ጥያቄው፡- እየሸለምን ያለነው ሀገር ገንቢዎችን ወይስ ጊዜ ገዳዮችን? የሚለው ነው። ከበለፀጉት ሀገራት ተሞክሮ አንፃር ሲታይ፣ የዘንድሮው ሽልማት ለወጣቱ ያስተላለፈው መልእክት እጅግ አደገኛ ነው።
Has to be banned!!
#ለምን?
1. የቻይናን ጥበብ ወይስ የቻይናን ቆሻሻ? (The Double Standard) የቲክቶክ ባለቤት የሆነችው ቻይና፣ ዓለምን በቴክኖሎጂ የተቆጣጠረችው በመጨፈር አይደለም።
ቻይና ለገዛ ወጣቶቿ የምትፈቅደው የቲክቶክ ቅጂ (Douyin)፣ ከ14 ዓመት በታች ለሆኑ ህፃናት የሚያሳየው የሳይንስ ሙከራዎችን፣ የሮቦቲክስ ፈጠራዎችን እና የአገር ፍቅር ታሪኮችን ብቻ ነው።
#ለምን?
ምክንያቱም “ነገን የሚረከበው ትውልድ ጭንቅላት በዕውቀት እንጂ መደንዘዝ የለበትም” ብለው ስለሚያምኑ ወደኛ ሲመጣ ግን ነገሩ ተገላቢጦሽ ነው።
ሽልማታችን የሳይንስ፣ የቴክኖሎጂ፣ የመፅሀፍ እና የበጎ አድራጎት ስራዎችን ወደ ዳር ገፍቶ “ቀልድን”የጀግንነት ማማ ላይ ሰቀለ። ቻይና ለልጆቿ የዕውቀት ወተት ስትግት፣ እኛ ለልጆቻችን በመዝናኛ የተለወሰ መርዝ እየሰጠን ይሆን? ይህንን ቆም ብለን ልንጠይቅ ልንመረምር ይገባል።
2. “Creative” gፈጠራ) ወይስ “Viral” (ማነጋገሪያ)? ቃላትን በትክክል እንጠቀም። “ፈጠራ” (Creativity) ማለት የህዝብን ችግር የሚፈታ፣ አዲስ እሴት የሚጨምር እና ትውልድን የሚያሻግር ስራ ነው።
ስልክን አገላብጦ በመቅረጽ በሺዎች የሚቆጠሩ “ላይክ”ማግኘት ታዋቂነት (Popularity) እንጂ ፈጠራ (Creativity) ሊሆን አይችልም።
ባደጉት ሀገራት ሽልማት የሚሰጠው ለይዘት ጥራት እና ለሚያመጣው ለውጥ ነው።
እኛ ጋር ግን መስፈርቱ የቁጥር ጨዋታ ሆነ። ሳይንስን፣ ህክምናን እና ትምህርትን የሚያስተላልፉ ቻናሎች እንደ ሁለተኛ ሲታዩ፣ ቀላል መዝናኛዎች የክብር ዙፋን ላይ ተቀምጠዋል። እውቀት በ “ላይክ”ብዛት አይለካም፤ እውነትም በ “ሼር” ብዛት አይረጋገጥም።
3. ለወጣቱ የተላለፈው አደገኛ መልእክት (The Wrong Role Models) አንድ ወጣት ይህንን ሽልማት ሲመለከት አእምሮው ውስጥ የሚቀረፀው ምንድን ነው?
"ለካ ክብር ለማግኘት ተምሮ ዲግሪ መያዝ፣ ሌሊት ተቀን ለሀገር የሚጠቅም ምርምር ማድረግ ወይም መፅሀፍ መጻፍ አይጠበቅብኝም።"
"ለካ አቋራጭ መንገድ አለ! ስልኬ ላይ ብጨፍር፣ በቅጽበት 'የዓመቱ ምርጥ' ተብዬ እሸለማለሁ።"
ይህ አስተሳሰብ የስራ ባህልን (Work ethic) የሚገድል መርዝ ነው። አሜሪካን፣ ጃፓንን እና ጀርመንን የገነቡት ፊታቸው በላብ የረጠበ ኢንጂነሮች ሐኪሞች ሙህራኖች ና ገበሬዎች እንጂ፣ ካሜራ ፊት የሚሽሞነሞኑ አይደሉም።
ወጣቱን ትምህርት እና የሥራ ጎዳና አውጥተን፣ ወደ አቋራጭ መንገድ እየገፋነው ነዉ አገርንም ጭምር!
4. የባህል ወረራ በሽልማት ስም
ሽልማቱ ላይ የታየው የአለባበስ እና የቅንጦት ትርኢት፣ የኢትዮጵያን ወጣት ማንነት የሚወክል ነበር? ወይስ የሆሊውድን "Red Carpet" ለመኮረጅ ?
#Dr.BEREKET EMMANUEL
MD, Author
Founder @influential youth Ethiopia CEO
❤2