Estifanos Getahun
1.06K subscribers
47.8K photos
1.79K videos
14 files
15.8K links
Download Telegram
የሁለት ሰዎችን ህይወት አጥፍቶ የተሰወረን ተጠርጣሪ በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያጣራ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አስታወቀ፡፡

የወንጀል ድርጊቱ የተፈጸመው ህዳር 04 እና 05 ቀን 2018 ዓ/ም በጉለሌ ክ/ከተማ ወረዳ 06 ልዩ ቦታው 23 ቀበሌ መዝናናኛ ክበብ አካባቢ ነው፡፡

ተከሳሽ እሱ ያውቃል ቢያዝን ከባለቤቱ ከወ/ሮ ሐመልማል አለምነህ ጋር በትዳር ተጣምረው መኖር ከጀመሩ አራት ወራትን አስቆጥረዋል፡፡

ተከሳሽ ከባለቤቱ ጋር በኪራይ ከሚኖሩበት ቤት ህዳር 04 ቀን 2018 ዓ/ም ከጠዋቱ 4፡00 ሠዓት ሲሆን ከሌላ ወንድ ጋር ስልክ ትደዋወያለሽ በሚል ቂም በቀል በመነሳሳት ሟችን አንገቷን በማነቅ ህይወቷ እንዲያልፍ በማድረግ በር ዘግቶባት ከአካባቢው ለጊዜው ይሰወራል፡፡

ተከሳሹ በዚሁ ብቻ አላባቃም ከአንድ ቀን በኋላ ህዳር 05 ቀን 2018 ዓ/ም ባለቤቱን ከገደለበት መኖሪያ ግቢ ተመልሶ በመምጣት ከእዚህ ቀደም ከባለቤቱ ጋር በሚፈጠረው ፀብ ያሸማግል የነበረን አለባቸው አየለ የተባለን ጎረቤቱን በሟች ባለቤቱ ይጠረጥረው ነበርና መሳሪያ በመተኮስ በስምንት ጥይት ህይወቱ እንዲያልፍ በማድረግ ከአካባቢው ሊሰወርም ችሏል፡፡

የወንጀሉ መፈፀም መረጃ የደረሰው የአዲስ አበባ ፖሊስ የወንጀል ምርመራና ክትትል ክፍሉ የወንጀል ስፍራው ላይ በመገኘት የሟች አለባቸው አየለን አስከሬን በማንሳትና ከአካባቢው በሰበሰበው መረጃ መነሻነት የሟች መኖሪያ ቤት ሲከፈት የሐመልማል አለምነህ አስከሬን ሊገኝም ችሏል፡፡

ፖሊስ ከወንጀሉ መፈፀም በመነሳት ተገቢውን የሰውና የኤሌክትሮኒክስ መረጃዎችን በመከታተል ተጠርጣሪውን ህዳር 18 ቀን 2018 ዓ/ም ከአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ሰሜን ሸዋ ዞን ሞላሌ ከተማ ከተደበቀበት መኖሪያ ቤት የግድያ ወንጀሉን ከፈፀመበት መሳሪያ ጋር በቁጥጥር ስር ሊያውልም ችሏል፡፡
"ሚናን ለይቶ ለመፍትሔ መቆም ሰላምን ያረጋግጣል" ምክትል ርእሰ መሥተዳድር አብዱ ሁሴን (ዶ.ር)
#Baay’isuu: Muuxannoowwan gaggaarii fi milkaahinoota argaman karaa qindaa’een babal’isuu;
በአንድ መድረክ አራት ሽልማቶችን ያሸነፈው የኢትዮጵያ አየር መንገድ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአፍሪካ አየር መንገዶች ማህበር (AFRAA) 57ኛ አመታዊ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ በአራት ዘርፎች አሸናፊ ሆኗል።

ማህበሩ በአንጎላ ሉዋንዳ ባዘጋጀው ዓመታዊ የእውቅና መድረክ ላይ ነው ለኢትዮጵያ አየር መንገድ ሽልማቶቹን ያበረከተው።  

በዚህም አየር መንገዱ በዓለም አቀፍ ስራዎች ትርፋማነት የ2024 ምርጥ አየር መንገድ እውቅናን ሲያገኝ፤ አፍሪካን በአየር ትራንስፖርት በማገናኘት የላቀ አገልግሎት በመስጠትም ማሸነፍ ችሏል፡፡

አየር መንገዱ ለአፍሪካ አቪዬሽን ኢንዱስትሪ እድገት ላበረከተው ከፍተኛ አስተዋጽኦ፤ የላቀ አገልግሎት በመስጠት ዘርፍም አሸንፏል።

እንዲሁም የአፍሪካ ህብረት በአህጉሪቱ ነፃ የአየር ትራንስፖርት እውን ለማድረግ ለያዘው ፕሮጀክት የላቀ አስተዋጽኦ በማድረጉም አየር መንገዱ ተሸላሚ መሆን ችሏል።

በአፍሪካ ከ60 በላይ በዓለም ከ145 በላይ መዳረሻዎች ያሉት የኢትዮጵያ አየር መንገድ፤ አፍሪካን በአየር ትራንስፖርት በመገናኘት የአንበሳውን ድርሻ ይዟል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ያገኘው እውቅና የፓን አፍሪካን እሴቶች መጠናከር የሰጠውን ትኩረት ከማሳየቱም በላይ የተቋሙ ሰራተኞች ቁርጠኝነትና ትጋት ውጤት መሆኑን የአየር መንገዱ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ መሥፍን ጣሰው ገልፀዋል።

አየር መንገዱ ለቀጠናዊ ትስስርና እንዲሁም ለዘርፉ እድገት እያደረገ ያለውን አስተዋፅኦ አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አስታውቋልአስታውቋል።