Estifanos Getahun
1.06K subscribers
47.8K photos
1.79K videos
14 files
15.8K links
Download Telegram
ከአዲስ አበባ የግብር አሰባሰብና የገቢዎች አገልግሎት አሰጣጥ ጋር በተያያዘ ለሚኖር ማንኛዉም አይነት ቅሬታ መፍታት የሚያስችል አዲስ አሰራር በከንቲባ ፅ/ቤት ስር ተዋቅሯል ።

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የገቢዎች ቢሮ ስር የተዘረጋዉ የቅሬታ አፈታት ስርዓት እንደተጠበቀ ሆኖ ባዛ ያልረካ ግብር ከፋይ ከንቲባ ፅ/ቤት ማንኛዉንም አይነት ከገቢ አሰባሰብ ፣ ከሰራተኞች ስነምግባር እና አገልግሎት አሰጣጥ ጋር የሚነሱ የግብር ከፋዮች ቅሬታዎችን ለመፍታት ዘወትር ሐሙስ ኃላፊዎች በተገኙበት የሚደመጥ እና ተጣርቶ ምላሽ የሚሰጥበትን አሰራር ዘርግቷል ።

ሁልጊዜም የአገልግሎት አሰጣጡን ለማሻሻል የሚተጋዉ እና ህዝብን አዳምጦ ምላሽ መስጠትን የትኩረት ማእከሉ ያደረገዉ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በከንቲባ ፅ/ቤት በሚስጥር ጥቆማ የሚሰጥበትን ነፃ የጥሪ ማእከል 9977 ፣ የሚስጥር ሳጥንን ጨምሮ በተጨባጭ ቅሬታዉን በአካል ለበላይ አመራር ማቅረብ የሚችልበትን አሰራር የፊታችን ሐሙስ ጀምሮ ወደ ተግባር ይገባል ።

በመሆኑም ከመጪዉ ሐሙስ ህዳር 25/2018 ጀምሮ ጠዋት ከ 2 ሰአት እስከ 7 ሰአት ድረስ ከገቢዎች ጋር ብቻ የተያያዘን ቅሬታ አመራሩ ተቀብሎ የሚስተናግድ መሆኑን በመረዳት በከንቲባ ፅ/ቤት ተጨባጭ ቅሬታ ያላችሁ ማቅረብ የምትችሉ መሆኑን የከተማዉ አስተዳደር ያሳዉቃል ።

አስተዳደራችን ለቀልጣፋ እና ፍትኃዊ አገልግሎት ይተጋል !
2
Addis Ababa

The New Global Smart City

🇪🇹🎉🇪🇹🎉🇪🇹🎉🇪🇹🎉
የህንፃዎች የቀለም ኮድ  በስታንዳርዱ መሠረት እየተተገበረ እንደሆነ ተገለፀ

በኮሪደር ልማት መንገዶች ላይ የሚገኙ በስታንዳርዱ መሠረት  ቀለም የቀቡ ÷አጥር ያጠሩ÷ መብራቶች የሰቀሉ ነዋሪዎች በአጠቃላይ 11.3 ቢሊየን ብር በላይ  ወጪ እንዳደረጉ ሰምተናል።

የህንፃዎች የቀለም ኮድ ስታንዳርድ ከማስጠበቅ ጋር በተያያዘ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የግንባታ ፍቃድ እና ቁጥጥር ባለስልጣን እየሰራሁ እገኛለሁ ብሏል።

የባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ዋና ዳይሬክተር ህይወት ሳሙኤል  የግንባታ ፍቃድ እና ቁጥጥር ባለስልጣን የህንፃዎችን የቀለም ኮዶች ስታንዳርድ ማዘጋጀቱን ነግረዉናል።

የህንፃ ባለቤቶች ህንፃዎችን ቀለም ለመቀባት ይህንን ስታንዳርድ ከባለስልጣን መስሪያ ቤቱ የሚሰጣቸዉ ብቻ  መሆኑንም ዳይሬክተሯ አያይዘዉ ገልፀዋል።

ለከተማዋ የሚስማሙ 13 አይነት ቀለማት  መለየታቸዉ ከዚህ ቀደም ተነግሯል።

ይህም ግንባታው ተጠናቆ አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኝ ህንጻ ከተማ አስተዳደሩ በሚያወጣው የአፈጻጸም እርከን አቅጣጫ የቀለም ዲዛይኑን የሚተገብር ይሆናል።

ኮሪደር ልማት ባለፈባቸዉ አካባቢዎች ያሉ ግራ እና ቀኝ  ቤቶች እድሳት የተደረገባቸዉ እና በስታንዳርዱ መሠረት  ቀለም የተቀቡ መሆኑን  የባለስልጣኑ ዳይሬክተር ተናግረዋል።

እስካሁን ባለዉ መረጃ በኮሪደር መንገዶች ላይ የሚገኙ ነዋሪዎች በስታንዳርዱ መሠረት  ቀለም የቀቡ ÷አጥር ያጠሩ÷ መብራቶች የሰቀሉ ነዋሪዎች በአጠቃላይ 11.3 ቢሊየን ብር በላይ  ወጪ ያደረጉ መሆኑን ሰምተናል።

ከተማዋ በህንጻዎች የራሷ የሆነ ስታንዳርድ እና በቀለም የሚገለጽ ብራንድ እንዲኖራት የአረንረጓዴ ልማት የአርባን ዲዛይን ቅርጽ ይዞ እንዲለማ ማድረግ እንደሚኖርበት ባለስልጣኑ በመመሪያው አስቀምጧል።
2
“አንድ አማፂ ስልጣን የያዘበትን እለት ማክበር ነውር ነው” - ሌተናል ጄኔራል ይልማ መርዳሳ የኢትዮጵያ አየር ኃይል ዋና አዛዥ
ስድስቱ 100 % እንዲሳኩ የሚጠበቁ ተግባራት 🎉🎉🎉
ኢትዮጵያ ከ22 ዓመት በኋላ ለአፍሪካ ዋንጫ አለፈች

ከ17 ዓመት በታች የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ኬንያን በማሸነፍ ለአፍሪካ ዋንጫ ማለፉን አረጋግጧል።

ዛሬ በአበበ ቢቂላ ስታዲየም በተደረገው የደረጃ ጨዋታ የኢትዮጵያ ወጣት ቡድን የኬንያ አቻውን 3 ለ 0 በማሸነፍ ነው ከሁለት አስርት ዓመታት በኋላ ወደ አፍሪካ ዋንጫ የተመለሰው።

ዳዊት ካሳው ቢኒያም አብርሃ እና ብሩክ እይላቸው የኢትዮጵያን ግቦች አስቆጥረዋል።

ወጣቱ አጥቂ ዳዊት ካሳው በአጠቃላይ ስምንት ግቦችን በማስቆጠር  ውድድሩን አጠናቋል።

በኢትዮጵያ አስተናጋጅነት ሲካሄድ የቆየው ከ17 ዓመት በታች የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ የሴካፋ ውድድር ዛሬ ፍጻሜውን የሚያገኝ ሲሆን ዩጋንዳ እና ታንዛኒያ ለዋንጫ የሚጫወቱ ይሆናል
1
እንኳን ደስ አለን!

በእግር ኳስ ስፖርት የጀመርነው ፕሮጀክት ፍሬ በማፍራት ላይ ነው። ዛሬ በመዲናችን አዲስ አበባ ሲካሄድ በነበረው የምስራቅና መካከለኛው አፍሪካ አገራት ከ17 ዓመት በታች ውድድር፣ ብሔራዊ ቡድባችን የኬንያ አቻውን 3 ለ 0 በሆነ ውጤት በመርታት ከ 22 ዓመታት በኋላ ለአፍሪካ ዋንጫ ማለፍ ችሏል። ይህ ድል የእግር ኳስ ስፖርት ወዳድ ለሆነው ህዝባችን የዘመናት ቁጭት በቅርቡ መልስ እንደሚያገኝ ያሳየ ነው።

ቀይ ቀበሮዎቹ ያስመዘገቡት ውጤት ለዘርፉ የሰጠነው ትኩረት ውጤት እያፈራ መሆኑን ማሳያ ነው።

በራሴና በከተማ አስተዳደሩ ስም መላው የቡድኑ አባላትን፣ የኢትዮዽያን ሕዝብ እንኳን ደስ አላችሁ ለማለት እወዳለሁ።

ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ሕዝቦቿን ይባርክ!

via - ክብርት ከንቲባ አዴ አዳነች አቤቤ