በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል፣ በሚዛን አማን ማረሚያ ቤት በእስር ላይ የነበሩ 27 ደቡብ ሱዳናውያን ወጣቶች ተፈትተው ወደ ሀገራቸው መመለሳቸውን የሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ገለጸ።
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል፣ በሚዛን አማን ማረሚያ ቤት በእስር ላይ የነበሩ 27 ደቡብ ሱዳናውያን ወጣቶች ተፈትተው ወደ ሀገራቸው መመለሳቸውን የሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ገለጸ።
አርብቶ አደሮቹ ወጣቶች በኢትዮጵያ መቼ በቁጥጥር ስር እንደዋሉ ባይገለጽም፤ የደቡብ ሱዳን መገናኛ ብዙኃን አንድ ዓመት ገደማ በእስር ሳይቆዩ እንዳልቀረ ዘግበዋል።
ወጣቶቹን ወደ ሀገራቸው የመመለሱ ሂደት በስኬት መጠናቀቁ የተገለጸው፤ የደቡብ ሱዳን ውጭ ጉዳይ እና ዓለም አቀፍ ትብብር ሚኒስትር መንደይ ሰማያ ከኢትዮጵያ አቻቸው ዶ/ር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ ጋር በጉዳዩ ላይ ያደረጉትን የስልክ ውይይት በማስመልከት በዛሬው ዕለት በተሰራጨ መግለጫ ነው።
የደቡብ ሱዳን መንግስት 27 የታጠቁ አርብቶ አደሮች፤ በኢትዮጵያ በእስር ላይ እንደሚገኙ ያረጋገጠው ባለፈው መስከረም ወር አጋማሽ ነበር።
የደቡብ ሱዳን ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ቃል አቀባይ አፑክ አዩኤል ማየን በወቅቱ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ፤ ከምስራቅ ኢኳቶሪያ ግዛት 27 ወጣቶች “በድንገት” ሁለቱ ሀገራት የሚዋሰኑትን ዓለም አቀፍ ድንበር እንዳቋረጡ ተናግረው ነበር።
ከ1,100 ኪሎ ሜትር በላይ የሚረዝመውን የኢትዮጵያ እና የደቡብ ሱዳን ድንበር እየተሻገሩ የሚፈጸሙ ጥቃቶች፤ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ስብሰባዎች ጭምር በየጊዜው ጥያቄ ሲያስነሳ ቆይቷል።
ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል በተጨማሪ በጋምቤላ በኩል ድንበር የሚሻገሩ የደቡብ ሱዳን ታጣቂዎች፤ ግድያ፣ የህጻናት አፈና እና የቀንድ ከብቶች ዝርፊያ እንደሚፈጽሙ ክልሉ በተደጋጋሚ ባወጣቸው መግለጫዎች ማስታወቁ አይዘነጋም።
ምንጭ ኢትዮጵያን ኢንሳይደር
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል፣ በሚዛን አማን ማረሚያ ቤት በእስር ላይ የነበሩ 27 ደቡብ ሱዳናውያን ወጣቶች ተፈትተው ወደ ሀገራቸው መመለሳቸውን የሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ገለጸ።
አርብቶ አደሮቹ ወጣቶች በኢትዮጵያ መቼ በቁጥጥር ስር እንደዋሉ ባይገለጽም፤ የደቡብ ሱዳን መገናኛ ብዙኃን አንድ ዓመት ገደማ በእስር ሳይቆዩ እንዳልቀረ ዘግበዋል።
ወጣቶቹን ወደ ሀገራቸው የመመለሱ ሂደት በስኬት መጠናቀቁ የተገለጸው፤ የደቡብ ሱዳን ውጭ ጉዳይ እና ዓለም አቀፍ ትብብር ሚኒስትር መንደይ ሰማያ ከኢትዮጵያ አቻቸው ዶ/ር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ ጋር በጉዳዩ ላይ ያደረጉትን የስልክ ውይይት በማስመልከት በዛሬው ዕለት በተሰራጨ መግለጫ ነው።
የደቡብ ሱዳን መንግስት 27 የታጠቁ አርብቶ አደሮች፤ በኢትዮጵያ በእስር ላይ እንደሚገኙ ያረጋገጠው ባለፈው መስከረም ወር አጋማሽ ነበር።
የደቡብ ሱዳን ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ቃል አቀባይ አፑክ አዩኤል ማየን በወቅቱ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ፤ ከምስራቅ ኢኳቶሪያ ግዛት 27 ወጣቶች “በድንገት” ሁለቱ ሀገራት የሚዋሰኑትን ዓለም አቀፍ ድንበር እንዳቋረጡ ተናግረው ነበር።
ከ1,100 ኪሎ ሜትር በላይ የሚረዝመውን የኢትዮጵያ እና የደቡብ ሱዳን ድንበር እየተሻገሩ የሚፈጸሙ ጥቃቶች፤ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ስብሰባዎች ጭምር በየጊዜው ጥያቄ ሲያስነሳ ቆይቷል።
ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል በተጨማሪ በጋምቤላ በኩል ድንበር የሚሻገሩ የደቡብ ሱዳን ታጣቂዎች፤ ግድያ፣ የህጻናት አፈና እና የቀንድ ከብቶች ዝርፊያ እንደሚፈጽሙ ክልሉ በተደጋጋሚ ባወጣቸው መግለጫዎች ማስታወቁ አይዘነጋም።
ምንጭ ኢትዮጵያን ኢንሳይደር
Forwarded from Abiy Ahmed Ali 🇪🇹
የኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲቲዩት ዋና ጽሕፈት ቤቱን ቀድሞ ከነበረበት በመለወጥ መሃል ከተማ ወደ ቀድሞው የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ሕንፃ አዛውሯል። በአንድ አመት ጊዜ ውስጥ አስደናቂ የግንባታ ለውጥ እና ዘመናዊ የመሥሪያ ሥፍራ ጥበብን በማሳየት ለሠራተኞቹ እጅግ ምቹ የሆነ ስፍራንም መፍጠር ችሏል። ተቋሙ በአምስት አመታት ጊዜ ውስጥ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ሕይወታችንን በፍጥነት በመቅረጽ ውስጥ ያለውን ስፍራ በሚያንፀባርቅ እና ሀገራችንም በዚህ አለምአቀፍ የቴክኖሎጂ ውድድር በንቁነት መሳተፏን በሚያረጋግጥ መንገድ ከፍታ ላይ ደርሷል። ኢንስቲቲዩቱ በጤና፣ በግብርና፣ በአገልግሎት ዘርፍ እያደረገ ያለው የመሪነት አስተዋፅኦውን እየተወጣ ሲሆን በክላውድ ኮምፒውቲንግ፣ ትላልቅ የመረጃ ቋቶች፣ የመረጃ ፍለጋ፣ ሮቦቲክስ እና ኢመርሲቭ ቴክኖሎጂዎች አቅሙን በማጎልበት ላይ ይገኛል።
በቅርቡ የተጀመረው የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ስታርት አፕ መዐከል ደግሞ ይኽንን ከባቢ የበለጠ ያጠናክረዋል። ዜጎች ሀሳብ ብቻ ይዘው በመምጣት ፕሮቶታይፕ ለመፍጠር፣ ለማባዛት ብሎም ከግሉ ዘርፍ ኢንቬስተሮች ጋር እንዲገናኙ እድል ያመቻቻል። እስከ አሁን 200 ሀሳብ ፈጣሪዎች በዚህ እድል ተጠቅመዋል።
በቅርቡ የተጀመረው የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ስታርት አፕ መዐከል ደግሞ ይኽንን ከባቢ የበለጠ ያጠናክረዋል። ዜጎች ሀሳብ ብቻ ይዘው በመምጣት ፕሮቶታይፕ ለመፍጠር፣ ለማባዛት ብሎም ከግሉ ዘርፍ ኢንቬስተሮች ጋር እንዲገናኙ እድል ያመቻቻል። እስከ አሁን 200 ሀሳብ ፈጣሪዎች በዚህ እድል ተጠቅመዋል።
Forwarded from Abiy Ahmed Ali 🇪🇹
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
በኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ያየሁት ነገር፤ ሰው የጠራ ራዕይ ካለው ፣ በከፍተኛ ዲሲፕሊን የሚሠራ ከሆነ አንድን ነገር ባየው ልክ ማሳካት እንደሚችል ፤ ኢትዮጵያ ብቃት ያላት ሀገር እንደሆነች ነው።
ብንፈልግም ባንፈልግም ራሳችንን በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ሂደት ውስጥ ማስገባት ካልቻልን ደረጃው የትም ቦታ ይሁን እንደ ሀገር እንደ ከዚህ ቀደሙ ከትላልቅ ሪቮልሽኖች ወደ ኋላ እንቀራለን - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)