Muhammed Computer Technology (MCT)
37.4K subscribers
530 photos
7 videos
254 files
916 links
🔎አድራሻ:-
✅ ስ.ቁ: 0929273364
✅ ዌብሳይት www.mctplc.com
✅቎ሌግራም አካውንት: https://t.me/mctplc
✅ email: mct16plc@gmail.com
✅ ቲክቶክ አካውንት tiktok.com/@mctplc
Download Telegram
# BREAKING
መጋቢት 3/2012 ዓ/ም ዚመጀመሪያው በኮሮና ቫይሚስ ዚተያዘ ሰው በሀገራቜን ኹተገኘ ወዲህ በኮሮና ቫይሚስ ዚተያዙ አራት (4) ተጚማሪ ሰዎቜ በመገኘታ቞ው በአጠቃላይ በቫይሚሱ ዚተያዙ ሰዎቜ ቁጥር አስራ ስድስት (16) ደርሷል፡፡
መጠንቀቅ ይኖርብናል ዘመዶቜ። ያአሏህ ምህሚትህን ለግሰን!
ምንጭ ፋና
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ኚኮሮና ቫይሚስ ጋር በተያያዘ ተጚማሪ ውሳኔዎቜ አስተላለፉ
*****
ዚኮሮና ቫይሚስ በዓለም ላይ እያደሚሰ ያለውን ፈታኝ ሁኔታ ኢትዮጵያ ለመቋቋም እንዲቻላት ዚሚኚተሉት መመሪያዎቜ እና ተጚማሪ እርምጃዎቜ ተግባራዊ እንዲሆኑ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ውሳኔ አስተላለፉ።
* ጡሚታ ዚወጡ እንዲሁም በትምህርት ላይ ያሉ ዚጀና ባለሞያዎቜ ለብሄራዊ ግዳጅ እንዲዘጋጁ
* ኚዛሬ ጀምሮ ወደ አዲስ አበባ ዚሚደርሱ እና ለይቶ ለመኚላኚያ በተዘጋጁት ሆ቎ሎቜ ለመቆዚት አቅም ዹሌላቾው መንገደኞቜ ወደ አዳማ ሳይንስ እና ቮክኖሎጂ ዩኒቚርሲቲ ተዘዋውሹው ለ15 ቀናት እንዲቆዩ ዚወጣው መመሪያ ተግባራዊ እንዲያደርጉ
* ኚዛሬ አንስቶ ለተጚማሪ ሁለት ሳምንታት ኹፍተኛ ዚትምህርት ተቋማትን ጚምሮ ትምህርት ቀቶቜ ተዘግተው እንዲቆዩ
* በገበያ ስፍራዎቜ እና በሃይማኖት ተቋማት ውስጥ አካላዊ ርቀትን መጠበቅ ተፈፃሚ እንዲደሚግፀ በፌዎራል መንግሥት አስኚፊ ብሔራዊ አደጋ በሚኚሰት ጊዜ ሃይማኖታዊ ስብሰባዎቜ እንዲቋሚጡ ዚማድሚግ ሕገ-መንግሥታዊ መብት አለው። ሆኖም በሕገ-መንግሥቱ ዚተደነገጉት እርምጃዎቜ ተግባራዊ ኹመደሹጋቾው በፊት ዜጎቜ አካላዊ ርቀት ዹመጠበቅን መመሪያ ተግባራዊ እንዲያደርጉ በድጋሚ ጥሪ እናቀርባለን።
* ሁኔታው ተጚማሪ ድጋፍን ዹሚጠይቅ ኹሆነ ሁሉም ጡሚታ ዚወጡ እንዲሁም በትምህርት ላይ ያሉ ዹሕክምና ባለሙያዎቜ ለብሔራዊ ግዳጅ እንዲዘጋጁ ጥሪ አቀርባለሁ።
* ዚተለያዚ መጠን እና ዓይነት ያላ቞ው መገልገያዎቜን ያዚዙ ኹ134 በላይ ተቋማት ተለይተው መኚላኚያ፣ ለይቶ መቆያ እና ለሕክምና እንዲሆኑ ተለይተዋል። ስለዚህ ሁሉም ዜጎቜ አልጋዎቜ፣ ፍራሟቜ፣ አንሶላዎቜ፣ ዚመተንፈሻ ቬንትሌተሮቜ እና ሌሎቜ መገልገያዎቜን ለማሰባሰብ በመሥራት ላይ ዹሚገኘውን ብሔራዊ ዚድጋፍ አሰባሳቢ ኮሚ቎ን ጥሚት እንዲደግፉ ጥሪዬን አቀርባለሁ።
* ዚማክሮ-ኢኮኖሚ ንዑስ ኮሚ቎ው ዚኢኮኖሚ ዘርፉን ደህንነት ለማስጠበቅ ዚሚያስቜሉ አማራጮቜን ለመቀዚስ በልዩ ልዩ ዘርፍ ኚተሰማሩት ዐበይት ዚኢንዱስትሪ ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ሲያካሂድ ቆይቷል። ይህንን ተኚትሎ ኢኮኖሚውን ለማሚጋጋት ዚሚኚተሉት እርምጃዎቜ ተፈፃሚ ይሆናሉ
* ዚኮቪድ-19 ወሚርሜኝን ለመኹላኹል ዚሚያስፈልጉ ዚገቢ ዕቃዎቜ እና ግብዓቶቜ ኚቀሚጥ ነፃ እንዲገቡ ይደሹጋል
• ዚፋይናንስ ዘርፉን ጀንነት አስጠብቆ ለማስቀጠል እና ባንኮቜ በኮሮና ቫይሚስ ለተጎዱ ደንበኞቻ቞ው ጊዜያዊ ዚብድር እፎይታ እና ተጚማሪ ብድር ለመስጠት እንዲያስቜላ቞ው ዚኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ተጚማሪ 15 ቢሊዮን ብር ለግል ባንኮቜ ያቀርባል።
• ዹውጭ ምንዛሬ ዚሚያስፈልጋ቞ው እና ዚኮቪድ-19 ወሚርሜኝን ለመኹላኹል ዚሚያስቜሉ ዕቃዎቜ እና ግብዓቶቜን ወደ ሀገር ውስጥ ለሚያስግቡ አስመጪዎቜ ባንኮቜ ቅድሚያ በመስጠት እንዲያስተናግዱ
• *በፋይናንስ አገልግሎት ዚተነሳ ገጜ ለገጜ መገናኘት እና ዚብር ንክኪን ለመቀነስ እንዲቻል፣ ዚኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ
በሞባይል አማካኝነት ዹሚደሹግ ክፍያ እና ገንዘብ ዚማስተላለፍ ጣሪያውን ኹፍ ያደርጋል፡፡
• ዚኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ለውጭ ገበያ በሚቀርብ አበባ ላይ ዚጣለው ዝቅተኛ ዚመሞጫ ዋጋ ገደብ በጊዜያዊነት
እንዲነሳ ተደርጓል፡፡
• ኩባንያዎቜ ዚተሻለ ዚገንዘብ ፍሰት እንዲኖራ቞ው ለማስቻል፣ ዚገቢዎቜ ሚኒስ቎ር ዚተጚማሪ እሎት ታክስ አመላለስ ሂደቱን በተለዹ መልኩ እንዲያፋጥን ይደሚጋል፡፡
• ዚኮቪድ-19ን ወሚርሜኝ ተኚትሎ ሊኚሰት ዚሚቜለውን ዚሞቀጊቜ እጥሚት እና አላስፈላጊ ዹዋጋ ጭማሪ ለመቆጣጠር በንግድና ኢንዱስትሪ ቢሮ በኩል ዹበለጠ ክትትል እንዲደሚግ።
ምንጭ፩ EBC
#ዹ24_ሰዓት_ዚኮሮና_ቫይሚስ_ስርጭትና_አጠቃላይ_ኬዝ
አርብ መጋቢት 18 እስኚ ጠዋቱ 12:50 ሰዓት ድሚስ
ክቡራን ዹሰው ልጆቜ በያላቜሁበት ሰላማቜሁ ይብዛ ፣ ባለፉት 24 ሰዓት ዚኮሮና ቫይሚስ አስደንጋጭ ቁጥሮቜ ተመዝግበውበታል
በአሜሪካ ዚቫይሚሱ ኬዝ ኚቻይና በልጧል ፣ በጣልያን ዚሟ቟ቜ ቁጥር ኚቻይና በሁለት እጥፍ ኹፍ ብሏል
በጣልያን በ24 ሰዓት ውስጥ ብቻ 712 ሰው ሞቷል
በስፔን ለመጀመሪያ ግዜ በ1 ቀን ውስጥ 718 ሰው ሞቷል
በፈሚንሳይ በ24 ሰዓት 365 ሰው ሲሞት ለመጀመሪያ ግዜ ሆኗል
አልጄሪያ ባለፉት 24 ሰዓት 3 ሰው ሞቶባታል
ግብፅም በ24 ሰዓት ውስጥ 3 ሰው ሰው ሞቶባታል
ደቡብ አፍሪካ ያገኘቜው 218 አዲስ ኬዝም ሪኚርዷ ነው
ይግሚማቜሁ አሜሪካ እስካሁን በትኛውም ሀገር ያልታዚ በ24 ሰዓት ውስጥ ብቻ 17,224 አዲስ ኬዝ አስተናግዳለቜ
ኒውዮርክ ብቻ 38,977 ኬዝ ተገኝቶባት 466 ሰው ሞቷል
ዚቫይሚሱ ስርጭት በኚፍትኛ ፍጥነት እዚጚመሚ ይገኛል ባለፉት 24 ሰዓት ብቻ በመላው አለም ሪኚርድ ዹሆነ 60,841 አዳዲስ ኬዝ ተገኝቷታ። በ24 ሰዓት ውስጥ ዚታዚው ዚሞት መጠንም እስካሁን ኹነበሹው ሁሉ ኹፍተኛው ነው 2,792 ሰዎቜ ሞተዋል።
አሁን ላይ ቫይሚሱ 199 ሃገራትን አዳርሶ በመላው አለም 532,237 ሰዎቜን አጥቅቶ 24,089 ሰዎቜን ሕይወት ቀጥፏል።
124,326 ሰዎቜ አገግመው ኚሆስፒታል ወጥተዋል
383,822 ሰዎቜ አሁን ላይ ቫይሚሱ ይገኝባ቞ዋል
364,465 ሰዎቜ በመካኚለኛ ደሹጃ ላይ ይገኛሉ
19,357 ሰዎቜ ደግሞ በአሳሳቢ ደሹጃ ላይ ናቾው
───────────────
────────────
ባለፉት 24 ሰዓት ኹፍተኛ ሞት ያስተናገዱ ሀገራት
+718 ስፔን
+712 ጣልያን
+365 ፈሚንሳይ
+268 ዩናይትድ ስ቎ትስ
+157 ኢራን
ባለፉት 24 ሰዓት ኹፍተኛ ኬዝ ያስተናገዱ ሀገራት
+17,224 ዩናይትድ ስ቎ትስ
+8,271 ስፔን
+6,615 ጀርመን
+6,203 ጣልያን
+3,922 ፈሚንሳይ
───────────────
────────────
በጠቅላላ በኮሮና ቫይሚስ ብዙ ሰው ዚሞተባ቞ው ሀገራት
8,215 ጣልያን
4,365 ስፔን
3,292 ቻይና
2,234 ኢራን
1,696 ፈሚንሳይ
በርካታ ዚኮሮና ቫይሚስ ኬዝ ያስተናገዱ ሀገራት
85,594 ዩናይትድ ስ቎ትስ
81,340 ቻይና
80,589 ጣልያን
57,786 ስፔን
43,938 ጀርመን
───────────────
────────────
ዚኮሮና ቫይሚስን በጋራ እና በግል እንኚላኚል
ዚእጃቜንን ንፅህና በአግባቡ እንጠብቅ
ሰዎቜ በተሰበሰቡበት ቊታ ላይ አንገኝ
ኚሰዎቜ ጋር ያለንን ርቀት እንጠብቅ
ዹተጹናነቁ ዚትራንስፖርት አመራጮቜን አንጠቀም
ዚጀና ባለሞያዎቜን ምክር ሁሌም እንተግብር
ዚጀና ሚኒስ቎ር መምሪያዎቜን እንኚታተል
ስለ ኮሮና ቫይሚስ (ኮቪድ-19) ትክክለኛ መሹጃ ኹWHO ፣ ኚጀና ሚኒስ቎ር እና ኚህበሚተሰብ ጀና ኢንስቲትዩት ብቻ ያግኙ!
በተጚማሪ በነፃ ዚስልክ መስመሮቜ 8335 / 952 ላይ ደውለው መሚጃዎቜን ያግኙ
በኮሮና ቫይሚስ ዹተጠቃ ሰው ኚሚያሳያ቞ው ምልክቶቜ ውስጥ
√ ኹፍተኛ ትኩሳት
√ ሳል
√ ለመተንፈስ መቾገር ዋነኞቹ ናቾው
# በቅድመ_ጥንቃቄ_እና_በፀሎት_እንበርታ
√ መሹጃ አይናቅም ስለዚህ ለሌሎቜ እንዲደርስ ሌር አድርጉ። ሰላም ለምድራቜን ይሁን
───────────────
────────────
እግር_ኳስ_The_Beautiful_Game በልዩነት በጥራት( ዹተዘጋጀ )
───────────────
────────────
√ ዹመሹጃ ምንጭ ያደሚኩት:- ወርልዶሜትር ዌብሳይትን ነው
How to create log in form in HTML&CSS:
ይሞክሩት ሙሀመድ አሚን
<!DOCTYPE html>
<html>
<head>
<title>LOG IN</title>
<style>
/*css*/
body {
}
div{
border:solid black;
border-radius:10px;
background-color:black;
text-align:center;
filter:opacity(85%);
height:80px;
overflow:auto;
margin-left:100px;
margin-right:100px;
-webkit-transition:margin 2s ,height 2s;
transition:margin 2s ,height 2s;
}
div:hover{
margin-left:20px;
margin-right:20px;
height:250px;
}
div ,h1{
color:white;
}
# l {
color:green;
}
# i {
color:green;
}
div input{
border:solid white 1px;
border-radius:10px;
margin-top:20px;
padding-left:10px;
color:white;
background-color:black;
-webkit-transition:background-color 2s;
transition:background-color 2s;
}
div input:hover{
background-color:green;
}
div button{
border:solid black 1px;
border-radius:5px;
width:50px;
height:30px;
margin-top:20px;
background-color:white;
-webkit-transition:background-color 1s;
transition:background-color 1s;
}
div button:hover{
background-color:green;
}
</style>
</head>
<body>
<div>
<h1>
<span id="l">L</span>OG
<span id="i">I</span>N
</h1>
<br />
<input type="email" placeholder="example@email.com"/>
<br />
<input type="password" placeholder="pass word"/>
<br />
<button>log in</button>
</div>
</body>
</html>
#ዹ24_ሰዓት_ዚኮሮና_ቫይሚስ_ስርጭትና_አጠቃላይ_ኬዝ
አሚብ መጋቢት 18 እስኚ ኚምሜቱ 5:00 ሰዓት ድሚስ
እንደምን አመሻቜሄ ክቡራን ዹሰው ልጆቜ ፣ በአለማቜን ኹ200 ሀገራትና ግዛቶቜን ያዳሚሰው ዚወቅቱ ዹሰው ልጆቜ ፈተና ዹሆነው ዚኮሮና ቫይሚስ 587,990 ሰዎቜን ለክፎ 26,909 ሰዎቜን ደግሞ ለሞት ዳርጓል
እንዲሁም 2,841 ሰዎቜ በ24 ሰዓት ውስጥ ብቻ በቫይሚሱ ሞተዋል።
132,440 ሰዎቜ አገግመው ኚሆስፒታል ወጥተዋል
428,641 ሰዎቜ አሁን ላይ ቫይሚሱ ይገኝባ቞ዋል
────────────
በጣልያን ቫይሚሱ አሁንም ዚበርካታ ሰዎቜን ሕይወት እዚቀጠፈ ይገኛል። ባለፉት 24 ሰዓት ብቻ +919 ሰዎቜ ሲሞቱባት ተጚማሪ +5,909 ሰዎቜ ደግሞ በቫይሚሱ ተጠቅተዋል።
───────────────
────────────
ስፔንም በቫይሚሱ ባለፉት 24 ሰዓት በርካታ ሰው ዚሞተባት 2ኛዋ ሀገር ነቜ +569 ሰዎቜ ሲሞቱባት +6,273 አዳዲስ ኬዞቜንም አስተናግዳለቜ።
───────────────
በጠቅላላ በኮሮና ቫይሚስ ብዙ ሰው ዚሞተባ቞ው ሀገራት
1ኛ 9,134 ጣልያን
2ኛ 4,934 ስፔን
3ኛ 3,292 ቻይና
4ኛ 2,378 ኢራን
5ኛ 1,995 ፈሚንሳይ
6ኛ 1,518 አሜሪካ
──────────────
በርካታ ዚኮሮና ቫይሚስ ኬዝ ያስተናገዱ ሀገራት
1ኛ 99,116 ዩናይትድ ስ቎ትስ አሜሪካ
2ኛ 86,498 ጣልያን
3ኛ 81,340 ቻይና
4ኛ 64,059 ስፔን
5ኛ 50,178 ጀርመን
6ኛ 32,964 ፈሚንሳይ
7ኛ 32,332 ኢራን
───────────────
ዚኮሮና ቫይሚስን በጋራ እና በግል እንኚላኚል
ዚእጃቜንን ንፅህና በአግባቡ እንጠብቅ
ሰዎቜ በተሰበሰቡበት ቊታ ላይ አንገኝ
ኚሰዎቜ ጋር ያለንን ርቀት እንጠብቅ!
መልካም አዳር ይሁንላቜሁ!
ምንጭ
https://www.worldometers.info/coronavirus/
ሊንኩን በመጫን ዹሁሉንም ሀገር በኮሮና ቫይሚስ ዚተጠቁትን ሀገሮቜ ምን ያህሎ ሰው እንደሞተ ለማወቅ ትቜላላቹሁ በዹቀኑ ግን ቁጥሩ እዚጚመሚ ነው ፡፡
ስለኮምፒውተርና ቮክኖሎጅ ያለዎትን እውቀት ያሳድጉ በ቎ሌግራሜ ቻናል ምርጥ ምርጥ ስለኮምፒውተር ዹምለቃቾውን መሚጃዎቜን ለመኚታተል እንዲያመቜዎ ይህንን ይጫኑ https://t.me/MuhammedComputerTechnology በ቎ሌግራም መኚታተል ትቜላላቜሁ
በተጚማሪም በፌስቡክ ገፄ https://m.facebook.com/mameamin.6te.net ይህንን ሊንክ በመጫን ፔጁን like በማድሚግ በፍጥነት መሹጃ እንዲደርሳቜሁ
ሌር ማድሚጋቜሁን አትርሱ
ዚፌስቡክ ፔጁን Like & share ያድርጉ
#ፔጄን_ላይክ ማድሚግዎን አይርሱ
# ዚኮኮሮና_ቫይሚስ_ስርጭት_ወቅታዊ_መሹጃ
√ እሑድ መጋቢት 20 እስኚ ጠዋቱ 04:00 ድሚስ
በመላው አለም በኮሮና ቫይሚስ (ኮቪድ-19) ዚሞቱት ሰዎቜ ቁጥር 30 ሜህ አልፏል። ጠቅላላ ዚቫይሚሱ ኬዝም 664,621 ደርሷል
30,889 ሰዎቜ እስካሁን በቫይሚሱ ሞተዋል
142,368 ሰዎቜ አገግመው ኚሆስፒታል ወጥተዋል
491,361 ሰዎቜ አሁን ላይ ቫይሚሱ ይገኝባ቞ዋል
466,131 ሰዎቜ በመካኚለኛ ደሹጃ ላይ ይገኛሉ
25,230 ሰዎቜ ደግሞ በአሳሳቢ ደሹጃ ላይ ናቾው
በአሜሪካ ዚኬሮና ቫይሚስ ጉድ እያፈላ ነው። ጠቅላላ ያስተናገደቜው ኬዝ 123,776 ዹደሹሰ ሲሆን ዚሟ቟ቜ ቁጥርም 2,229 ሆኗል። ባለፉት 24 ሰዓት ብቻ በአሜሪካ ዹተመዘገበው +19,452 አዳዲስ ኬዝ ዚትኛውም ሀገር ላይ ታይቶ አይታወቅም። ዚሞቱት 525 ሰዎቜም በአንድ ቀን ለሀገሪቱ ሪኚርድ ሆኗል።
በኒውዮርክ ብቻ ባለፉት 24 ሰዓት 277 ሰው ዹሞተ ሲሆን 7,137 እዲስ ኬዝም ተገኝቷል። አሜሪካ ካላት ጠቅላላ ኬዝም 53,393 ዚሚሆኑት ኚኒውዮርክ ና቞ው።
ጣልያን ባለፉት 24 ሰዓት 889 ሰው ሞቶባት 5,974 አዲስ ኬዝ አስተናግዳለቜ። ጠቅላላ ሟ቟ቜም 10,023 ሆኗል
ስፔንም ባለፉት 24 ሰዓት 844 ሰው ሞቶባት 7,516 አዲስ ኬዝ አስተናግዳለቜ። ጠቅላላ ሟ቟ቜም 5,982 ሆኗል
ፈሚንሳይ ባለፉት 24 ሰዓት በርካታ ሰው ዚሞተባት 4ኛዋ ሀገር ነቜ። 319 ሟቜና 4,611 አዳዱስ ኬዝ አስተናግዳለቜ
──────────
√ ዹመሹጃ ምንጫቜን:- ስፒዶሜትር ድህሚ ገፅ ነው
በኢትዮጵያ በቫይሚሱ ዚተያዙ ሶስት (3) ተጚማሪ ሰዎቜ ተገኙ
******
በኢትዮጵያ ዚህብሚተሰብ ጀና ኢንስቲትዩት ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ ሰማንያ ሰባት (87) ሰዎቜ ዚላብራቶሪ ምርመራ ዹተደሹገላቾው ሲሆን በቫይሚሱ ዚተያዙ ሶስት (3) ተጚማሪ ሰዎቜ በመገኘታ቞ው በአጠቃላይ በሀገራቜን በቫይሚሱ ዚተያዙ ሰዎቜ ቁጥር አስራ ዘጠኝ (19) ደርሷል፡፡
ምንጭ EBC
👍1
# በኢትዮጵያ_ዚኮሮና_ቫይሚስ_ኬዝ_19_ደርሷል
በኢትዮጵያ ዚህብሚተሰብ ጀና ኢንስቲትዩት ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ ሰማንያ ሰባት (87) ሰዎቜ ዚላብራቶሪ ምርመራ ዹተደሹገላቾው ሲሆን በቫይሚሱ ዚተያዙ ሶስት (3) ተጚማሪ ሰዎቜ በመገኘታ቞ው በአጠቃላይ በሀገራቜን በቫይሚሱ ዚተያዙ ሰዎቜ ቁጥር አስራ ዘጠኝ (19) ደርሷል፡፡
#ታማሚ 1
ዹ26 ዓመት ኢትዮጵያዊ ስትሆን መጋቢት 8፣ 2012 ኚብራሰልስ ቀልጅዚም እንዲሁም መጋቢት 10፣2012 ዓ.ም ወደ ካሜሮን ዹጉዞ ታሪክ ዚነበራት ሲሆን ግለሰቧ ዚበሜታው ምልክት ስለታዚባት ወደ ጀና ተቋም በመሄድ ምርመራ አድርጋለቜ፡፡ ተቋሙም ለኢትዮጵያ ዚህብሚተሰብ ጀና ኢንስቲትዩት ሪፖርት በማደሹጉ በተደሚገላት ዚላብራቶሪ ምርመራ በመጋቢት 19፣2012 ዓ.ም በቫይሚሱ መያዟ ተሚጋግጧል፡፡
# ታማሚ 2 እና 3
ዚአንድ ቀተሰብ አባላት ዹሆኑ ዹ14 እና ዹ48 ዓመት ዚአዳማ ኹተማ ነዋሪዎቜ ዹሆኑ ኢትዮጵያውያን ና቞ው፡፡ ግለሰቊቹ ዚበሜታው ምልክት ባያሳዩም ኹዚህ በፊት በቫይሚሱ ኚተያዘ ግለሰብ ጋር ዚቅርብ ንክኪ ስለነበራ቞ው በለይቶ ማቆያ ክትትል እዚተደሚገላ቞ው ነበር፡፡ ግለሰቊቹ በመጋቢት 19፣2020 ዓ.ም በተደሹገላቾው ዚላቊራቶሪ ምርመራ በቫይሚሱ መያዛ቞ው ተሚጋግጧል።
ለተጚማሪ መሹጃ በነፃ ዚስልክ መስመር 8335 ወይም በ952 በመጠቀም ማግኘት ይቻላል።
ምንጭ:- ጀና ሚኒስትር
ሊንኩን በመጫን ዹሁሉንም ሀገር በኮሮና ቫይሚስ ዚተጠቁትን ሀገሮቜ ለማወቅ ትቜላላቹሁ በዹቀኑ ግን ቁጥሩ እዚጚመሚ ነው ፡፡
https://www.worldometers.info/coronavirus/
በኢትዮጵያ በኮሮና ቫይሚስ ዚተያዙ ተጚማሪ ሁለት ሰዎቜ ተገኙ
አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 20 ፣ 2012 (ኀፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ በኮሮና ቫይሚስ ዚተያዙ ተጚማሪ ሁለት ሰዎቜ ተገኙ።
በዚህም በኢትዮጵያ በኮሮና ቫይሚስ ዚተያዙት ሰዎቜ ቁጥር 21 መድሚሱን ዚጀና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ አስታውቀዋል።
በቫይሚሱ መያዛ቞ው ዚተሚጋገጡት ግለሰቊቜ ዹ38 ዓመት ወንድ እና ዹ35 ዓመት ሎት ዚአዲስ አበባ ኹተማ ነዋሪ ዹሆኑ ኢትዮጵያዊያን ና቞ው።
ሁለቱም ግለሰቊቜ በተለያዩ ቀናት ወደ ዱባይ ዹጉዞ ታሪክ ዚነበራ቞ው ሲሆን ዚበሜታውን ምልክት በማሳዚታ቞ው በተደሹገላቾው ዚላብራቶሪ ምርመራ በቫይሚሱ መያዛ቞ው ተሚጋግጧል።
ምንጭ FBC
#ዹ24_ሰዓት_ዚኮሮና_ቫይሚስ_ስርጭትና_አጠቃላይ_ኬዝ
እሁድ መጋቢት 20 እስኚ ኚምሜቱ 1:45 ሰዓት ድሚስ
እንደምን አመሻቜሁ ክቡራን ዹሰው ልጆቜ ፣ በአለማቜን ኹ200 ሀገራትና ግዛቶቜን ያዳሚሰው ዚወቅቱ ዹሰው ልጆቜ ፈተና ዹሆነው ዚኮሮና ቫይሚስ 702,368 ሰዎቜን ለክፎ 33,178 ሰዎቜን ደግሞ ለሞት ዳርጓል
እንዲሁም 2,321 ሰዎቜ በ24 ሰዓት ውስጥ ብቻ በቫይሚሱ ሞተዋል።
149,215 ሰዎቜ አገግመው ኚሆስፒታል ወጥተዋል
519,975 ሰዎቜ አሁን ላይ ቫይሚሱ ይገኝባ቞ዋል
────────────
በጣልያን ቫይሚሱ አሁንም ዚበርካታ ሰዎቜን ሕይወት እዚቀጠፈ ይገኛል። ባለፉት 24 ሰዓት ብቻ +756 ሰዎቜ ሲሞቱባት ተጚማሪ +5,217 ሰዎቜ ደግሞ በቫይሚሱ ተጠቅተዋል።
───────────────
────────────
ስፔንም በቫይሚሱ ባለፉት 24 ሰዓት በርካታ ሰው ዚሞተባት 2ኛዋ ሀገር ነቜ +624 ሰዎቜ ሲሞቱባት +5,564 አዳዲስ ኬዞቜንም አስተናግዳለቜ።
───────────────
በጠቅላላ በኮሮና ቫይሚስ ብዙ ሰው ዚሞተባ቞ው ሀገራት
1ኛ 10,779 ጣልያን
2ኛ 6,606 ስፔን
3ኛ 3,300 ቻይና
4ኛ 2,640 ኢራን
5ኛ 2,329 አሜሪካ
──────────────
በርካታ ዚኮሮና ቫይሚስ ኬዝ ያስተናገዱ ሀገራት
1ኛ 131,403 ዩናይትድ ስ቎ትስ አሜሪካ
2ኛ 97,689 ጣልያን
3ኛ 81,439 ቻይና
4ኛ 78,799 ስፔን
5ኛ 60,659 ጀርመን
6ኛ 38,309 ኢራን
───────────────
ዚኮሮና ቫይሚስን በጋራ እና በግል እንኚላኚል
ዚእጃቜንን ንፅህና በአግባቡ እንጠብቅ
ሰዎቜ በተሰበሰቡበት ቊታ ላይ አንገኝ
ኚሰዎቜ ጋር ያለንን ርቀት እንጠብቅ!
መልካም አዳር ይሁንላቜሁ!
#ዹ24_ሰዓት_ዚኮሮና_ቫይሚስ_ስርጭትና_አጠቃላይ_ኬዝ
ሰኞ መጋቢት 21 እስኚ ጠዋቱ 01:30 ሰዓት ድሚስ
ውድ ዚሀገሬ ልጆቜ በያላቜሁበት ሰላማቜሁ ይብዛ ፣ ባለፉት 24 ሰዓት ዚኮሮና ቫይሚስ በመላው አለም 3,110 ሰዎቜን ዹገደለ ሲሆን 58,865 አዲስ ተጠቂዎቜም ሪፖርት ተደርገዋል
───────────
ስፔን ባለፉት 24 ሰዓት በርካታ ሰው ዚሞተባት ቀዳሚዋ ሀገር ነቜ 821 ሰዎቜ ሲሞቱባት +6,875 አዳዲስ ኬዞቜንም አስተናግዳለቜ።
────────────
በጣልያን ቫይሚሱ አሁንም ዚበርካታ ሰዎቜን ሕይወት እዚቀጠፈ ይገኛል። ባለፉት 24 ሰዓት ብቻ +756 ሰዎቜ ሲሞቱባት ተጚማሪ +5,217 ሰዎቜ ደግሞ በቫይሚሱ ተጠቅተዋል።
────────
ፈሚንሳይ ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ በርካታ ሰው ዚሞተባት 3ኛ ሀገር ነቜ። 292 ሰዎቜ ሲሞቱባት ++2,599 አዲስ ኬዝም አስተናግዳለቜ።
────────
አሜሪካ በ24 ሰዓት ውስጥ በርካታ ኬዝ ያስተናገደቜ ሀገር መሆኗን ቀጥላለሜ (+18,469) እንዲሁም 264 ሟ቟ቜ እንዳሉባትም ሪፖርት አድርጋለቜ
─────────
ኔዘርላንድ ባለፉት 24 ሰዓት በርካታ ሰው ካጡት ውስጥ ነቜ 132 ሰዎቜ ሲሞትባት +1,104 አዳዲስ ኬዝ አስተናግዳለቜ።
────────────
በኢራን ባለፉት 24 ዚሞቱባት ሰዎቜ 123 ሲሆኑ +2,901 አዳዲስ ተጠቂዎቜንም አስተናግዳለቜ።
────────────
በብሪታኒያ ባለፉት 24 ሰዓት ብቻ 209
ሰው ዹሞተ ሲሆን +2,433 ሰዎቜም በቫይሚሱ ተይዘዋል።
────────
ቻይና ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 5 ሰዎቜ ዚሞቱባት ሲሆን +45 አዳዲስ ኬዝ እንዳለባትም ሪፖርት አድርጋለቜ።
──────────────
ደቡብ አፍሪካ ባለፉት 24 ሰዓት ብቻ +93 አዳዲስ ኬዝና 1 ሞት ያስተናገደቜ ሲሆን በጠቅላላው 1,280 ኬዝ በማስተናገድም ኚአፍሪካ ቀዳሚዋ ሀገር ነቜ።
────────────
ግብፅ ባለፉት 24 ሰዓት +33 አዳዲስ ኬዝ እና 4 ተጚማሪ ሟቜ ዚተገኘባት ሲሆን በጠቅላላው 40 ሞት አስተናግዳ በአፍሪካ በርካታ ሰው ዚሞተባት ሀገርም ሆናለቜ።
────────────
አልጄሪያ በ24 ሰዓት ውስጥ 2 ተጚማሪ ሰው ሞቶባት +57 አዳዲስ ኬዞቜንም አግኝታለቜ ። አጠቃላይ 31 ሰው ሞቶባታል።
───────────
ሞሮኮ በ24 ሰዓት ውስጥ ተጚማሪ +77 ዚኮሮና ቫይሚስ ኬዝ ያገኘቜና 1 ተጚማሪ ዚሞት ሪፖርትም አላት። ጠቅላላ 26 ሰው ሞቶባታል
────────────
በሀገራቜን ትላንት ብቻ 5 አዲስ ታማሚ ዹተገኘ ሲሆን በሀገራቜን ያለው ጠቅላላ ዚኮሮና ቫይሚስ ኬዝ 21 ደርሶ ኹነዚህ ውስጥ ደግሞ 2ቱ አገግመው 2 ጃፓናዊ ታማሚዎቜም ወደ ሀገራ቞ው ሄደዋል።
ካሜሮን 4 ሰው ሞቶባት 48 አዲስ ኬዝም አስተናግዳለቜ
ዲ.ሪ. ኮንጎ በ24 ሰዓት 16 አዲስ ኬዝና 2 ሟቜ አለባት
አንጎላ በ24 ሰዓት 2 አዲስ ኬዝና 2 ሟቜ አለባት
ቡርኪናፋሶ 1 ሰው ሞቶባት 15 አዲስ ኬዝ አስተናግዳለቜ
ቱኒዚያ በ24 ሰዓት 34 አዲስ ኬዝ እስተናግዳለቜ
ኮትዲቯር በ24 ሰዓት 64 አዲስ ኬዝና 1 ሟቜ አለባት
ሞሪቲዚስ 1 ሰው ሞቶባት 5 አዲስ ኬዝ አስተናግዳለቜ
────────────
ባለፉት 24 ሰዓት ኹፍተኛ ሞት ያስተናገዱ ሀገራት
+821 ስፔን
+756 ጣልያን
+292 ፈሚንሳይ
+264 ዩናይትድ ስ቎ትስ
+209 ብሪታኒያ
ባለፉት 24 ሰዓት ኹፍተኛ ኬዝ ያስተናገዱ ሀገራት
+18,469 ዩናይትድ ስ቎ትስ
+6,875 ስፔን
+5,217 ጣልያን
+4,740 ጀርመን
+2,901 ኢራን
+3,809 ፈሚንሳይ
────────────
በጠቅላላ በኮሮና ቫይሚስ ብዙ ሰው ዚሞተባ቞ው ሀገራት
10,779 ጣልያን
6,803 ስፔን
3,304 ቻይና
2,640 ኢራን
2,606 ፈሚንሳይ
በርካታ ዚኮሮና ቫይሚስ ኬዝ ያስተናገዱ ሀገራት
142,178 ዩናይትድ ስ቎ትስ
97,689 ጣልያን
81,470 ቻይና
80,110 ስፔን
62,435 ጀርመን
አጠቃላይ ዚሟ቟ቜ ቁጥር 33,980 ሺህ ሆኗል
ጠቅላላ ዚኮሮና ቫይሚስ ኬዝ 722,347 ደርሷል
ጠቅላላ ኚቫይሚሱ ያገገሙትም 151,766 ሆነዋል
አሁን ቫይሚሱ ያለባ቞ው ሰዎቜ 536,601 ናቾው
በመካኚለኛ ደሹጃ ዚሚገኙት 509,920 ሆነዋል
በአሳሳቢ ደሹጃ ዚሚገኙትም 26,681 ሰዎቜ ናቾው
────────────
√ አስፈላጊውን ጥንቃቄ በማድሚግ ዚኮሮና ቫይሚስ ስርጭትን በጋራ እንኚላኚል።
# በቅድመ_ጥንቃቄ_እና_በፀሎት_እንበርታ
√ መሹጃ አይናቅም ስለዚህ ለሌሎቜ እንዲደርስ ሌር አድርጉ
√ ቁጥራዊ መሚጃዎቹን ያገኘሁት :- ስፒዶሜትር ዌብሳይት ላይ ነው
───
በኢትዮጵያ ዚኮሮናቫይሚስ ዚተገኘባ቞ው ሰዎቜ ቁጥር 23 መድሚሱን ዚኢፌዎሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህምድ ይፋ አድርገዋል።
በኮሮና ቫይሚስ (ኮቪድ_19) በሜታ ዚተያዙ ተጚማሪ ሁለት ሰዎቜ መገኘታ቞ውን ለማሳወቅ ዹተሰጠ መግለጫ
ዚኢትዮጵያ ዚሕብሚተሰብ ጀና ኢንስቲትዩት ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ ባደሚገው ተጚማሪ ስልሳ ስድስት (66) ዚላብራቶሪ ምርመራ ሁለት (2) በኮሮና ቫይሚስ ዚተያዙ ሰዎቜ በማሚጋገጡ በአጠቃላይ በሀገራቜን በቫይሚሱ ዚተያዙ ሰዎቜ ቁጥር ሃያ ሶስት (23) ደርሷል፡፡
በቫይሚሱ መያዛ቞ው ዚተሚጋገጡት ግለሰቊቜ በአማራ ክልል ባህር ዳር ነዋሪ ዹሆኑ ዹ37 ዓመት ሎትና በአዊ ብሔሚሰብ አስተዳደር ዞን ዚአዲስ ቅዳም ነዋሪ ዹሆኑ ዹ32 ወንድ ዓመት ኢትዮጵያዊያን ና቞ው፡፡ ዚአስገዳጅ ለይቶ ማቆያ ኚመጀመሩ ዕለት አስቀድሞ አንደኛዋ ታማሚ መጋቢት 10 ኚዱባይ እንዲሁም ሁለተኛው ታማሚ መጋቢት 12 ኚአሜሪካ ዚገቡ ና቞ው፡፡ ሁለቱም ታማሚዎቜ ዚበሜታው ምልክት በማሳዚታ቞ው በላብራቶሪ ምርመራ በቫይሚሱ መያዘ቞ው ተሚጋግጧል፡፡ ኹዚሁ ጋር በተያያዘ ኚታማሚዎቹ ጋር ዚቅርብ ንክኪ ዚነበራ቞ው ሰዎቜ ዚመለዚትና ክትትል ሂደት እዚተኚናወነ ይገኛል፡፡ሁለቱም ታማሚዎቜ በአማራ ክልል ዚለይቶ ህክምና መስጫ ማዕኹል ዹህክምና እርዳታ እዚተደሚገላ቞ው ይገኛል፡፡
በአሁኑ ሰዓት በሀገራቜን በለይቶ ህክምና መስጫ ማዕኹል ዹህክምና እርዳታ እዚተደሚገላ቞ው ያሉ አስራ ዘጠኝ (19) ታማሚዎቜ ሲኖሩ አንድ ታማሚ በጜኑ ህሙማን ህክምና ክፍል ክትትል እዚተደሚገላት ይገኛል፡፡ ኹዚህ በፊት እንደተገለጞው ሁለት ታማሚዎቜ ወደ ሀገራ቞ው ተመልሰዋል ሲሆን ሁለት ታማሚዎቜ ሙሉ በሙሉ አገግመዋል፡፡ ነገር ግን ለጥንቃቄ ሲባል በለይቶ ማቆያ ክትትል እዚተደሚገላ቞ው ይገኛል፡፡
ህብሚተሰቡ ዚበሜታውን ስርጭት ግምት ውስጥ በማስገባት ዚመኚላኚያ መንገዶቜን እና ኚመንግስት ዹሚተላለፉ እርምጃዎቜን ትኩሚት በመስጠት እንዲተገበር እናሳስባለን፡፡
ለተጚማሪ መሹጃ በነፃ ዚስልክ መስመር 8335 ወይም በ952 ወይም በመደበኛ ዚስልክ ቁጥር 0118276796 ወይም በኢሜል አድራሻቜን ephieoc@gmail.com በመጠቀም ማግኘት ይቻላል፡
ዶ/ር ሊያ ታደሰ
ዚጀና ሚኒስትር
መጋቢት 21 ፣ 2012 ዓ.ም
👍1
# በኢትዮጵያ_ዚኮሮና_ቫይሚስ_ኬዝ_ሙሉ_መሹጃ
ዚወቅቱ ዹአለም ስጋት ዹሆነው ዚኮሮና ቫይሚስ (ኮቪድ-19) በሀገራቜን ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ግዜ ዹተገኘው መጋቢት 03-2012 ሲሆን ዛሬ ላይ በ19ኛ ቀኑ ዚተጠቂዎቜ ቁጥር 23 ደርሷል።
እስኪ በሀገራቜን ዹተገኘው 23ቱን ኬዞቜ እናስታውሳ቞ው
መጋቢት 3-2012 ዚመጀመሪያው ታማሚ
1. ዹ48 አመት ጃፓናዊ ዚካቲት 25 ኚቡርኪናፋሶ ዚመጣ
መጋቢት 05-2012 ላይ ዚተገኘባ቞ው
2 ዹ44 አመት ጃፓናዊ
3 47 አመት ጃፓናዊ
4 42 አመት ኢትዮጵያዊ
ኚመጀመሪያው ጃፓናዊ ጋር ንክኪ ያላ቞ውና ሁሉም ኢትዮጵያ ውስጥ ዚሚሰሩ
መጋቢት 07-2012 ዚተገኘበት
5. ዹ34 አመት ኢትዮጵያዊ መጋቢት 04 ኚዱባይ ዚገባ
መጋቢት 08-2012 ዚተገኘባት
6. ዹ59 አመት እንግሊዛዊት ዚካቲት 23 ኚዱባይ ዚገባቜ
መጋቢት 10-2012 ላይ ዚተገኘባ቞ው
7. ዹ44 አመት ጃፓናዊ ኚመጀመሪያው ታማሚ ጋር ዚተነካካ
8. ዹ85 አመት ኢትዮጵያዊት ዚካቲት 23 ኹውጭ ዚመጡ
9. ዹ39 አመት ሆስትሪያዊ መጋቢት 6 ዚገባ
መጋቢት 13-2012 ላይ ዚተገኘባ቞ው
10. ዹ28 አመት ኢትዮጵያዊ ኚቀልጅዚም መጋቢት 5 ገባ
11. ዹ43 አመት ኢትዮጵያዊ ኚዱባይ መጋቢት 10 ገባ
መጋቢት 14-2012 ላይ ዚተገኘበት
12- ዹ34 አመት ኢትዮጵያዊ መጋቢት 04 ኚዱባይ ዚገባ
መጋቢት 18-2012 ላይ ዚተገኘባ቞ው
13- ዹ72 ዓመት ሞሪሞሳዊ መጋቢት 5 ኚኮንጎ ብራዛቪል ዚመጡ
14- ዹ61 ዓመት ዚአዳማ ኹተማ ኢትዮጵያዊ ይፕትም ያልተጓዙ
15- ዹ28 ዓመት ኢትዮጵያዊት መጋቢት 12 ኚእስራኀል ተመላሜ
16- ዹ24 ዓመት ኢትዮጵያዊት ዹውጭ ጉዞ ያላደሚገቜ
መጋቢት 20-2012 ላይ ዚተገኘባ቞ው
17- ዹ26 ዓመት ኢትዮጵያዊ መጋቢት 10 ኚካሜሮን ዚመጣ
18- ዹ14 አመት ኢትዮጵያዊ ዚአዳማ ኹተማ ነዋሪ
19- ዹ48 ዓመት ኢትዮጵያዊ ዚአዳማ ኹተማ ነዋሪ
20- ዹ38 ዓመት ወንድ ዚዱባይ ዹጉዞ ታሪክ ዹነበሹው
21- ዹ35 ዓመት ሎት ዚዱባይ ዹጉዞ ታሪክ ዚነበራት
መጋቢት 21-2012 ላይ ዚተገኘባ቞ው
22- ዹ37 ዓመት ሎት ዚባህር ዳር ነዋሪ ኚዱባይ ተመላሜ
23- ዹ32 ዓመት ወንድ በአዊ ዞን ዚአዲስ ቅዳም ነዋሪ ኚአሜሪካ ተመላሜ
√ ጠቃሚ መሹጃ ስለሆነ ሌር በማድሚግ ለሌሎቜ ያጋሩ
Muhammed Computer Technology (MCT) pinned «# በኢትዮጵያ_ዚኮሮና_ቫይሚስ_ኬዝ_ሙሉ_መሹጃ ዚወቅቱ ዹአለም ስጋት ዹሆነው ዚኮሮና ቫይሚስ (ኮቪድ-19) በሀገራቜን ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ግዜ ዹተገኘው መጋቢት 03-2012 ሲሆን ዛሬ ላይ በ19ኛ ቀኑ ዚተጠቂዎቜ ቁጥር 23 ደርሷል። እስኪ በሀገራቜን ዹተገኘው 23ቱን ኬዞቜ እናስታውሳ቞ው መጋቢት 3-2012 ዚመጀመሪያው ታማሚ 1. ዹ48 አመት ጃፓናዊ ዚካቲት 25 ኚቡርኪናፋሶ ዚመጣ መጋቢት 05-2012 ላይ »
በኢትዮጵያ በኮሮና ቫይሚስ ዚተያዙ ሰዎቜ ቁጥር 25 መድሚሱን ጀና ሚኒስ቎ር አስታወቀ
በኢትዮጵያ በኮሮና ቫይሚስ ዚተያዙ ሰዎቜ ቁጥር 25 መድሚሱን ጀና ሚኒስ቎ር አስታወቀ
ዚኮሮና ቫይሚስ በሜታ ምላሜ አሰጣጥን (ዚኮቪድ-19) አስመልክቶ ዹተዘጋጀ ዕለታዊ መግለጫ
-------------------
ዚኢትዮጵያ ዚሕብሚተሰብ ጀና ኢንስቲትዩት ይህ መሹጃ እስኚ ተዘጋጀበት ሰዓት ድሚስ በአጠቃላይ 1013 ዚላቊራቶሪ ምርመራ ያደሚገ ሲሆን ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 66 ዚላብራቶሪ ምርመራ አካሄዶ በኮሮና ቫይሚስ ዚተያዙ ተጚማሪ ሶስት (3) ሰዎቜ መኖራ቞ውን አሚጋግጧል፡፡ በዚህም መሰሚት በአጠቃላይ በሀገራቜን በቫይሚሱ ዚተያዙ ሰዎቜ ቁጥር ሃያ አምስት (25) ደርሷል፡፡
በቫይሚሱ መያዛ቞ው ዚተሚጋገጡት ሁለት ግለሰቊቜ ዹ30 ዓመትና ዹ36 ዓመት ኢትዮጵያዊያን ሲሆኑ በተመሳሳይ በሚራ ኚዱባይ በመጋቢት 15 ፣2012 ዓ.ም ወደ ሀገር ዚገቡ ሲሆን በአስገዳጅ ዚለይቶ ማቆያ ውስጥ ዚነበሩ ሲሆን ዚበሜታውን ምልክት ታይቶባ቞ው በተደሹገላቾው ዚላብራቶሪ ምርመራ በኮሮና ቫይሚስ መያዛ቞ው ተሚጋግጧል፡፡ ሶስተኛዋ ታማሚ ዹ60 ዓመት እድሜ ያላ቞ው ዚአዲስ አበባ ኹተማ ነዋሪ ሲሆኑ መጋቢት 6፣2012 ዓ.ም ኚፈሚንሳይ ዚተመለሱና ክትትል ሲደሚግላ቞ው ቆይቶ ዚበሜታውን ምልክት በማሳዚታ቞ው በለይቶ ማቆያ ውስጥ ሆነው በተደሹገላቾው ዚላብራቶሪ ምርመራ በኮሮና ቫይሚስ ዚተያዙ መሆናቾውን ማሚጋገጥ ተቜሏል፡፡ ሶስቱም ታማሚዎቜ በለይቶ ህክምና መስጫ ማዕኹል ዹህክምና እርዳታ እዚተደሚገላ቞ው ይገኛል፡፡
በአሁኑ ሰዓት በሀገራቜን በለይቶ ህክምና መስጫ ማዕኹል ዹህክምና እርዳታ እዚተደሚገላ቞ው ያሉ ሃያ አንድ (21) ታማሚዎቜ ሲኖሩ ሁለት ታማሚዎቜ በጜኑ ህሙማን ህክምና ክፍል ክትትል እዚተደሚገላ቞ው ይገኛል፡፡ ኹዚህ በፊት እንደተገለጞው ሁለት ታማሚዎቜ ወደ ሀገራ቞ው ዚተመለሱ ሲሆን ሁለት ታማሚዎቜ ሙሉ በሙሉ አገግመዋል፡፡ ነገይቻላን ለጥንቃቄ ሲባል በለይቶ ማቆያ ክትትል እዚተደሚገላ቞ው ይገኛል፡፡
ህብሚተሰቡ ዚበሜታውን ስርጭት ግምት ውስጥ በማስገባት ዚመኚላኚያ መንገዶቜን እና ኚመንግስት ዹሚተላለፉ እርምጃዎቜን ትኩሚት በመስጠት እንዲተገበር እናሳስባለን፡፡
ለተጚማሪ መሹጃ በነፃ ዚስልክ መስመር 8335 ወይም በ952 ወይም በመደበኛ ዚስልክ ቁጥር 0118276796 ወይም በኢሜል አድራሻቜን ephieoc@gmail.com በመጠቀም ማግኘት ይቻላል::