"መሳል መልካም ነው ብረትን ያሰላዋልና፤ መጽሐፍም መልካም ነው ልብን ያበራዋልና፡፡ መጽሐፍ መነጽር ነው፣ ለሚመለከተው ሰው ከሩቅ ያሳያልና"
መጽሐፈ ጨዋታ መንፈሳዊ፡፡
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem_bot
መጽሐፈ ጨዋታ መንፈሳዊ፡፡
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem_bot
👍1
#ወንድምህን_አትናቀው
@Mgetem
ወዳጄ ሆይ! ክርስቲያን ነህን?እንኪያስ በፍጹም ወንድምህን አትናቀው። እህትህን አትናቃት። ምንም ይኹን ምን ሰውን አትናቅ። ይህ የምትንቀው ወንድም በተለይ ክርስቲያን ከኾነ ክርስቶስን እየሰደብከው እንደ ኾነ አስተውል።"እንዴት?" ያልከኝ እንደ ኾነ ይህ የምትንቀው ወንድምህ የክርስቶስ ሕዋስ ኾኗል። የክርስቶስ ሕዋስ ከኾነ ደግሞ እርሱን ናቀከው ማለት ክርስቶስን ናከው ማለት ነው። ወንድምህን የምትንቅ ከኾነም በጲላጦስ አደባባይ ጌታን ከገረፉት ዕራቆቱን ከሰቀሉት ሐሞትና ከርቤን ቀላቅለው ካጠጡት በፊቱ ላይም ከተፉት ሰዎች በምንም አትተናነስም። ስለዚህ ወንድምህን ከመናቅ ተጠንቀቅ።
📌ሼር
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem_bot
@Mgetem
ወዳጄ ሆይ! ክርስቲያን ነህን?እንኪያስ በፍጹም ወንድምህን አትናቀው። እህትህን አትናቃት። ምንም ይኹን ምን ሰውን አትናቅ። ይህ የምትንቀው ወንድም በተለይ ክርስቲያን ከኾነ ክርስቶስን እየሰደብከው እንደ ኾነ አስተውል።"እንዴት?" ያልከኝ እንደ ኾነ ይህ የምትንቀው ወንድምህ የክርስቶስ ሕዋስ ኾኗል። የክርስቶስ ሕዋስ ከኾነ ደግሞ እርሱን ናቀከው ማለት ክርስቶስን ናከው ማለት ነው። ወንድምህን የምትንቅ ከኾነም በጲላጦስ አደባባይ ጌታን ከገረፉት ዕራቆቱን ከሰቀሉት ሐሞትና ከርቤን ቀላቅለው ካጠጡት በፊቱ ላይም ከተፉት ሰዎች በምንም አትተናነስም። ስለዚህ ወንድምህን ከመናቅ ተጠንቀቅ።
📌ሼር
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem_bot
❤4👍3
#እሳት_ውሀ_ሲሆን
እሳት ቢንቀለቀል ነበልባል ቢያበራ
ዲኑ ውሀ ሆኖል በመላኩ ስራ
ብንገባ ከሳቱ ወጥተናል በግርማ
የሚያድነን መላክ መጥቶልን ከራማ
ዛሬም እሳት ቢነድ ገብርኤል ብለናል
እሳት ውሀ ሲሆን ዱራ ሜዳ አይተናል
@Mgetem
@Mgetem_bot
@Yohannes_mariyam
እሳት ቢንቀለቀል ነበልባል ቢያበራ
ዲኑ ውሀ ሆኖል በመላኩ ስራ
ብንገባ ከሳቱ ወጥተናል በግርማ
የሚያድነን መላክ መጥቶልን ከራማ
ዛሬም እሳት ቢነድ ገብርኤል ብለናል
እሳት ውሀ ሲሆን ዱራ ሜዳ አይተናል
@Mgetem
@Mgetem_bot
@Yohannes_mariyam
✝✝እንጠይቅ ታምሯን✝✝
🔖🔖🔖🔖🔖🔖🔖
፦ዮሐ ፦2 ፥1-11
፦ሉቃ ፦1 ፥ --
እንጠይቅ ስለሷ እውነታው ያልገባችሁ
ከምትናገሩ እንደመጣላችሁ
አበዉን እንጠይቅ ይንገሩን ባካችሁ ።
ብዙ አባቶች አሉ የለበሱ ፍቅሯን እነሱን እንጠይቅ የንገሩን ታምሯን ።
ታምራቱዋን ያየው የተደረገለት
ዶኪማስ ይመስክር ይናገር ስለ እውነት ፦
በዛ በሰረጉ ቤት ቃና ዘገሊላ
ሰርገኛዉ ታድሞ ሲጠጣ ሲበላ ፦
ድንገት በመሀከል ወይኑ በመጥፋቱ
ዶኪማስ ተጨንቆ ሲርድ ሰዉነቱ
የነበረው ደስታ ሁሉም ሲሆን ከንቱ
መቋቋም አቅቶት ሲዝል ጉልበቱ
ተዋረድኩኝ ብሎ ሲታየዉ ሽንፈቱ
እማምላክ አንብባ ጭንቀቱን ከፊቱ ።
እሩህሩህ ናትና እናቴ አዛኚቱ
የዶኪማስ ጭንቀት ሀዘኑ እንዲፈታ
ድንግል ልታማልድ ሄደች ወደ ጌታ
ተዓምር የሚያደርግ ስላላት ቃልኪዳን
"ወይንኪ ዓልቦሙ "አለችው ልጇን ።
ልጇም ሰማና የናቱን ልመና
ውሃውን ቀየረዉ ወደ ወይን ቃና ።
ትናገር ኤልሳቤጥ ትመስክር ታምሯን
የሰላምታዋን ቃል ስትሰማዉ ድምጿን
በምንፈስ ተሞልታ ለክብሯ መስገዷን
በማሕፀኗ ያለዉን ፅንስ ማዘለሏን ።
ልቧ ሀሴት አርጎ መጮኋን በደስታ
ፅንሱም እደዘለለ በድንግል ሰላምታ ።
ምድራዉያንን እኛን ወክላ
ለክብሯ ሰገደች "ሰላም ለኪ "ብላ
ሰማያዉያንን ሁሉ ወክሎ
ገብረኤል አበሰራት" ሰላም ለኪ "ብሎ
ታደያ በኛም ዘመን አሁን ባለንበት
የድንግል ተዓምር በሚገለጥበት
ዓለም በምልጃዋ ድህነት ባገኝበት
ታድያ ለምን ካዱ ጠፋባቸው እውነት ።
አይናቸው እያየ ገድል ታምራቷን
ጆሮአቸውም ሰምቶ ሙታን ማስነሳቱዋን
ታድያ ለምን ይሆን ሰው ናት ማልታቸዉ
ስላልተፃፈ እንጂ ፍቅሯ በልባቸው ።
ከዚህ ሓጥያት ለመዉጣት ለመቅመስ ፍቅሯን
እንጠይቅ ስለሷ ይንገሩን ታምሯን ።
እውነትን ተማሩ ግቡ ወደ በረቱ
የእውነት አማላጅ ናት ድንግል አዛኚቱ ።
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem_bot
🔖🔖🔖🔖🔖🔖🔖
፦ዮሐ ፦2 ፥1-11
፦ሉቃ ፦1 ፥ --
እንጠይቅ ስለሷ እውነታው ያልገባችሁ
ከምትናገሩ እንደመጣላችሁ
አበዉን እንጠይቅ ይንገሩን ባካችሁ ።
ብዙ አባቶች አሉ የለበሱ ፍቅሯን እነሱን እንጠይቅ የንገሩን ታምሯን ።
ታምራቱዋን ያየው የተደረገለት
ዶኪማስ ይመስክር ይናገር ስለ እውነት ፦
በዛ በሰረጉ ቤት ቃና ዘገሊላ
ሰርገኛዉ ታድሞ ሲጠጣ ሲበላ ፦
ድንገት በመሀከል ወይኑ በመጥፋቱ
ዶኪማስ ተጨንቆ ሲርድ ሰዉነቱ
የነበረው ደስታ ሁሉም ሲሆን ከንቱ
መቋቋም አቅቶት ሲዝል ጉልበቱ
ተዋረድኩኝ ብሎ ሲታየዉ ሽንፈቱ
እማምላክ አንብባ ጭንቀቱን ከፊቱ ።
እሩህሩህ ናትና እናቴ አዛኚቱ
የዶኪማስ ጭንቀት ሀዘኑ እንዲፈታ
ድንግል ልታማልድ ሄደች ወደ ጌታ
ተዓምር የሚያደርግ ስላላት ቃልኪዳን
"ወይንኪ ዓልቦሙ "አለችው ልጇን ።
ልጇም ሰማና የናቱን ልመና
ውሃውን ቀየረዉ ወደ ወይን ቃና ።
ትናገር ኤልሳቤጥ ትመስክር ታምሯን
የሰላምታዋን ቃል ስትሰማዉ ድምጿን
በምንፈስ ተሞልታ ለክብሯ መስገዷን
በማሕፀኗ ያለዉን ፅንስ ማዘለሏን ።
ልቧ ሀሴት አርጎ መጮኋን በደስታ
ፅንሱም እደዘለለ በድንግል ሰላምታ ።
ምድራዉያንን እኛን ወክላ
ለክብሯ ሰገደች "ሰላም ለኪ "ብላ
ሰማያዉያንን ሁሉ ወክሎ
ገብረኤል አበሰራት" ሰላም ለኪ "ብሎ
ታደያ በኛም ዘመን አሁን ባለንበት
የድንግል ተዓምር በሚገለጥበት
ዓለም በምልጃዋ ድህነት ባገኝበት
ታድያ ለምን ካዱ ጠፋባቸው እውነት ።
አይናቸው እያየ ገድል ታምራቷን
ጆሮአቸውም ሰምቶ ሙታን ማስነሳቱዋን
ታድያ ለምን ይሆን ሰው ናት ማልታቸዉ
ስላልተፃፈ እንጂ ፍቅሯ በልባቸው ።
ከዚህ ሓጥያት ለመዉጣት ለመቅመስ ፍቅሯን
እንጠይቅ ስለሷ ይንገሩን ታምሯን ።
እውነትን ተማሩ ግቡ ወደ በረቱ
የእውነት አማላጅ ናት ድንግል አዛኚቱ ።
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem_bot
👍12❤7
ሀ ብሎ ጀምሮ የፊደል ገበታ
ለመማር አስቦ ከጥዋት እስከማታ
የሰው ሀገር ሂዶ ተጠርቶ ከጌታ
ያለ ምግብ ዋለ የትንሳኤ ለታ
የናቱን ቤት ትቶ
በልጅነት ወጥቶ
ልመና ሲለምን የሚዘከር አጥቶ
በረሃብ ይሰቃያል ውሻውን ፈርቶ
ቢለምንም እንኳን በርትቶ ተፅናንቶ
ትንሽ ነው የሚያገኝ ብዙ ሰአት ለፍቶ
ውሻውን ራቡን ሁለቱን ታግሶ
ይማራል ትምህርቱን ድሪቶውን ለብሶ
የውሻውን ነገር
እረ እንዴት ልናገር
ይመስክረው እንጂ የተማሪው እግር
በውሻ እግሮቹን ተነግሶ ተነግሶ
ለምጡ ምስክር ነው ተጠብሶ ተጠብሶ
ከውሻ ጋር ታግሎ
የሚበለው ቆሎ
ሰውነቱ ከስቶ በውሻ ቆሳስሎ
ሌት ተቀን ቀፅሎ
ተምሬ መምህር እሆናው ብሎ
ከናት ካባቱ ቤት
የላመ የጣመ ሁሉ እያለለት
ይሄን ሁሉ ትቶ ወጣ ትምህርት ቤት
እራቡ ጥማቱ
እንቅልፍ ማጣቱ
የዘመድ ናፍቆቱ
ትምህርቱ ብዛቱ
ብርዱ መሰልቸቱ
ተሎ አይመሽ መአልቱ
አይነጋ ሌሊቱ
የቆሎ ተማሪ ስቃዩ መብዛቱ
ይህን ሁሉ ችሎ
ዳዊቱን ተምሮ ዜማውን ቀፅሎ
ቅኔ ቤት አመራ ጓዙን ጠቀላሎ
ቅኔውን ለመማር ከቅኔ ቤት ገብቶ
ቅፀላ ጀመረ ከሁሉ ተስማምቶ
የሚያውቀው ሰው የለም
አይተዋወቅም
ከዛ ያለው ሁሉም
ሀገር ወዴት ነው ተብሎ አይጠየቅም
መቀፀል ብቻ ነው የቅኔውን ቀለም
የሚለምንበት መንደር ተደልድሎ
መንደሩ እንዲደርስ በቁጥር ተከፍሎ
ለእንግደው ተማሪ መንደሩ ተሰጠው
ለምኖ እንዲማር ትምርት እንዲገባው
ልመና ሲለምን ትንሹ ተማሪ
ውሻው ቢመጣበት እረዳው ፈጣሪ
አኩፋዳ ሞልቶ የያዘው ኮቸሮ
ሲታገል ተደፋ ነጋ ጦሙን አድሮ
ግሱን እያጠና ቅኔውንም ቆጥሮ
ቅኔ እንደተቀኘ አቋቋም ለመማር
አቋቋም ቤት ሄደ ወጣ ሌላ ሀገር
እንዲህ ሁኖ ሳለ ትምህርት የሚማረው
አንዳንዱ ይቀራል ሞት እየነጠቀው
ተረቱም ይባላል
በተለያየ ቃል
ተማሪ በሞተ በሰባት ዓመቱ
ተምሮ ይመጣል ትላለች እናቱ
የተማሪ ነገር ይሄ ነው እውነቱ
አንዱ ውሃ ወስዶት
አንዱ ውሻ በልቶት
አንዱ ወባ ገድሎት
አንዱ ትምህርት ከብዶት
ሀገሩ ሳይመለስ እንደወጣ ቀረ
በትምህርት እንዳለ ስንቱ ተቀበረ
መከራውን አልፎ የሚቀረው ከሞት
እከኩ እርሃቡ መልኩን ቀይሮት
እናቱ ስታየው ሌላ ሰው መሰላት
ሙሉ ሰውነቱን እከኩ አቁስሎት
ይህን ሁሉ ስቃይ የተቀበለው
የእግዚአብሔርን ቃል ለመማር ነው
ልምና የወጣ ስላጣ አይደለም
በስሟ ሲለምን ብሎ በእንተ ማርያም
ቃል ኪዳኗን ይዞ ሊማር ነው ዘላለም
በግብፅ በረሃ ድንግል ስትለምን
ያነን በማሰብ ነው ተማሪ የሚለምን
የማርያም ወዳጂ የቆሎ ተማሪ
ምግቡ ማርያም ናት ሁሌም ስሟን ጠሪ
ሲጠራት ውሎ ሲጠራት አዳሪ
~የተማሪ ስንቁ ድንግል ማርያም ናት
ትምህርት ቤት ሲሄድ የተጓዘ ይዟት
አንድ አኮፈዳ ቁራሽ መለመኚያ
አንድ ዳዊት ጸሎት መፀለያ
ሁለት ዘንጎች ውሻ መከልከያ
አንዲት ቅምጫና የውሃ መቅጂያ
አንድ ደበሎ ብርድ መከልከያ
የተማሪ ሀብቱ እነዚህ ናቸው
ከናት ካባቱ ቤት ይዞ የወጣቸው
የቆሎ ተማሪው እንደዚህ ተምሮ
ቅኔውን ድጓውን መጻፉን ተምሮ
አቋቋም ቅዳሴ ዝማሬን ጨምሮ
አቡሻህር ሳይቀር አራቆ አስመስክሮ
የቤተ ክርስቲያን የሀገር አለኚታ
ተብሎ እየተጠራ የኔታ የኔታ
መምህር መርጌታ ቀኝ ጌታ ግራጌታ
መከራውን አይቶ ተምሮ ሲመጣ
ስራ አላገኘም የሚበላው አጣ
ያልተማረው በዘር ከላይ ተቀምጦ
በጉቦ በጎሳ ስልጣን ተቆናጦ
የተማረው ቀረ ዘበኛ ተቀጥሮ
ይግባኝ ለፈጣሪ እንዲህ ነው ዘንድሮ
የተማረው ከላይ ሲሰቃይ እያየ
ከስር ከስር ያለው ለመማር ዘገየ
የኔታ ተምረው ከወዴት ደረሱ
እያለ ያወራል ትንሹ እርስ በርሱ
አልማርም እኔ ለመሆን እንደሱ
ጉባኤ ቤት ገብቶ የሚማር ሳይጠፋ
ቤተ ክርስቲያን እንድትኖር በተስፋ
የአብነት ትምህርቱ በሁሉ እንዲስፋፋ
ቅድሚያ ለተማረው
ቦታ እንዲኖረው
የተዋህዶ ልጆች ድምፃችን ይሰማ
የጉባኤ ቤቶች ሳይሆኑ ባድማ
የተማረው ታዛዥ
ያልተማረው አዛዥ
ያልተማረው ከላይ
ባማረ ወንበር ላይ
ባበባ ምንጣፍ ላይ
የተማረው ከታች ከሚዳው አፈር ላይ
አይምሮ ይነሳል ይሄ ሁሉ ሲታይ
ወይ ስቃይ ወይ ስቃይ
እረ እሰከመቸ ነው
እንዲህ የሚኖረው
የተማረው ላልተማረው ጉቦ እየከፈለ
ካልከፈለ ጉቦ ስራ እየተከለከለ
እረ መቸ ይሆን ?
የሚያልፍ ይህ ዘመን
በአፈ ቀላጤ ቦታው ሁሉ ሞልቶ
ያልተማረ መምር ዳር እስከዳር በዝቶ
የተማረው ምሁር መድረሻ ቦታ አጥቶ
የምሁራኑ ግፍ
በድርሳናት ቢፃፍ
ወረቀት አይበቃም
ብእርም የለም
ምድርም አይችለውም
@ይግባኝ ለእልመክኑ
ስለ ምሁራኑ
እባክህ አምላኬ አንድ ነገር ስማኝ
የተማረው ከላይ ሁኖ እንድታሳየኝ
የዚህ ፅሁፍ መታሰቢያነቱ
ይሁንልኝ ለሊቃውንቱ
ለደቀ መዛሙርቱ
በረሃብ በግፍ ለሚንገላቱ
መጋቤ ሐዲስ ሄኖክ ፈንቴ
ነሐሴ 15/2009 (ሸር)
መካነ ጉባኤ ዘቅኔ ተጻፈ
📌ሼር
@Mgetem
@Mgetem
@Solasc
ለመማር አስቦ ከጥዋት እስከማታ
የሰው ሀገር ሂዶ ተጠርቶ ከጌታ
ያለ ምግብ ዋለ የትንሳኤ ለታ
የናቱን ቤት ትቶ
በልጅነት ወጥቶ
ልመና ሲለምን የሚዘከር አጥቶ
በረሃብ ይሰቃያል ውሻውን ፈርቶ
ቢለምንም እንኳን በርትቶ ተፅናንቶ
ትንሽ ነው የሚያገኝ ብዙ ሰአት ለፍቶ
ውሻውን ራቡን ሁለቱን ታግሶ
ይማራል ትምህርቱን ድሪቶውን ለብሶ
የውሻውን ነገር
እረ እንዴት ልናገር
ይመስክረው እንጂ የተማሪው እግር
በውሻ እግሮቹን ተነግሶ ተነግሶ
ለምጡ ምስክር ነው ተጠብሶ ተጠብሶ
ከውሻ ጋር ታግሎ
የሚበለው ቆሎ
ሰውነቱ ከስቶ በውሻ ቆሳስሎ
ሌት ተቀን ቀፅሎ
ተምሬ መምህር እሆናው ብሎ
ከናት ካባቱ ቤት
የላመ የጣመ ሁሉ እያለለት
ይሄን ሁሉ ትቶ ወጣ ትምህርት ቤት
እራቡ ጥማቱ
እንቅልፍ ማጣቱ
የዘመድ ናፍቆቱ
ትምህርቱ ብዛቱ
ብርዱ መሰልቸቱ
ተሎ አይመሽ መአልቱ
አይነጋ ሌሊቱ
የቆሎ ተማሪ ስቃዩ መብዛቱ
ይህን ሁሉ ችሎ
ዳዊቱን ተምሮ ዜማውን ቀፅሎ
ቅኔ ቤት አመራ ጓዙን ጠቀላሎ
ቅኔውን ለመማር ከቅኔ ቤት ገብቶ
ቅፀላ ጀመረ ከሁሉ ተስማምቶ
የሚያውቀው ሰው የለም
አይተዋወቅም
ከዛ ያለው ሁሉም
ሀገር ወዴት ነው ተብሎ አይጠየቅም
መቀፀል ብቻ ነው የቅኔውን ቀለም
የሚለምንበት መንደር ተደልድሎ
መንደሩ እንዲደርስ በቁጥር ተከፍሎ
ለእንግደው ተማሪ መንደሩ ተሰጠው
ለምኖ እንዲማር ትምርት እንዲገባው
ልመና ሲለምን ትንሹ ተማሪ
ውሻው ቢመጣበት እረዳው ፈጣሪ
አኩፋዳ ሞልቶ የያዘው ኮቸሮ
ሲታገል ተደፋ ነጋ ጦሙን አድሮ
ግሱን እያጠና ቅኔውንም ቆጥሮ
ቅኔ እንደተቀኘ አቋቋም ለመማር
አቋቋም ቤት ሄደ ወጣ ሌላ ሀገር
እንዲህ ሁኖ ሳለ ትምህርት የሚማረው
አንዳንዱ ይቀራል ሞት እየነጠቀው
ተረቱም ይባላል
በተለያየ ቃል
ተማሪ በሞተ በሰባት ዓመቱ
ተምሮ ይመጣል ትላለች እናቱ
የተማሪ ነገር ይሄ ነው እውነቱ
አንዱ ውሃ ወስዶት
አንዱ ውሻ በልቶት
አንዱ ወባ ገድሎት
አንዱ ትምህርት ከብዶት
ሀገሩ ሳይመለስ እንደወጣ ቀረ
በትምህርት እንዳለ ስንቱ ተቀበረ
መከራውን አልፎ የሚቀረው ከሞት
እከኩ እርሃቡ መልኩን ቀይሮት
እናቱ ስታየው ሌላ ሰው መሰላት
ሙሉ ሰውነቱን እከኩ አቁስሎት
ይህን ሁሉ ስቃይ የተቀበለው
የእግዚአብሔርን ቃል ለመማር ነው
ልምና የወጣ ስላጣ አይደለም
በስሟ ሲለምን ብሎ በእንተ ማርያም
ቃል ኪዳኗን ይዞ ሊማር ነው ዘላለም
በግብፅ በረሃ ድንግል ስትለምን
ያነን በማሰብ ነው ተማሪ የሚለምን
የማርያም ወዳጂ የቆሎ ተማሪ
ምግቡ ማርያም ናት ሁሌም ስሟን ጠሪ
ሲጠራት ውሎ ሲጠራት አዳሪ
~የተማሪ ስንቁ ድንግል ማርያም ናት
ትምህርት ቤት ሲሄድ የተጓዘ ይዟት
አንድ አኮፈዳ ቁራሽ መለመኚያ
አንድ ዳዊት ጸሎት መፀለያ
ሁለት ዘንጎች ውሻ መከልከያ
አንዲት ቅምጫና የውሃ መቅጂያ
አንድ ደበሎ ብርድ መከልከያ
የተማሪ ሀብቱ እነዚህ ናቸው
ከናት ካባቱ ቤት ይዞ የወጣቸው
የቆሎ ተማሪው እንደዚህ ተምሮ
ቅኔውን ድጓውን መጻፉን ተምሮ
አቋቋም ቅዳሴ ዝማሬን ጨምሮ
አቡሻህር ሳይቀር አራቆ አስመስክሮ
የቤተ ክርስቲያን የሀገር አለኚታ
ተብሎ እየተጠራ የኔታ የኔታ
መምህር መርጌታ ቀኝ ጌታ ግራጌታ
መከራውን አይቶ ተምሮ ሲመጣ
ስራ አላገኘም የሚበላው አጣ
ያልተማረው በዘር ከላይ ተቀምጦ
በጉቦ በጎሳ ስልጣን ተቆናጦ
የተማረው ቀረ ዘበኛ ተቀጥሮ
ይግባኝ ለፈጣሪ እንዲህ ነው ዘንድሮ
የተማረው ከላይ ሲሰቃይ እያየ
ከስር ከስር ያለው ለመማር ዘገየ
የኔታ ተምረው ከወዴት ደረሱ
እያለ ያወራል ትንሹ እርስ በርሱ
አልማርም እኔ ለመሆን እንደሱ
ጉባኤ ቤት ገብቶ የሚማር ሳይጠፋ
ቤተ ክርስቲያን እንድትኖር በተስፋ
የአብነት ትምህርቱ በሁሉ እንዲስፋፋ
ቅድሚያ ለተማረው
ቦታ እንዲኖረው
የተዋህዶ ልጆች ድምፃችን ይሰማ
የጉባኤ ቤቶች ሳይሆኑ ባድማ
የተማረው ታዛዥ
ያልተማረው አዛዥ
ያልተማረው ከላይ
ባማረ ወንበር ላይ
ባበባ ምንጣፍ ላይ
የተማረው ከታች ከሚዳው አፈር ላይ
አይምሮ ይነሳል ይሄ ሁሉ ሲታይ
ወይ ስቃይ ወይ ስቃይ
እረ እሰከመቸ ነው
እንዲህ የሚኖረው
የተማረው ላልተማረው ጉቦ እየከፈለ
ካልከፈለ ጉቦ ስራ እየተከለከለ
እረ መቸ ይሆን ?
የሚያልፍ ይህ ዘመን
በአፈ ቀላጤ ቦታው ሁሉ ሞልቶ
ያልተማረ መምር ዳር እስከዳር በዝቶ
የተማረው ምሁር መድረሻ ቦታ አጥቶ
የምሁራኑ ግፍ
በድርሳናት ቢፃፍ
ወረቀት አይበቃም
ብእርም የለም
ምድርም አይችለውም
@ይግባኝ ለእልመክኑ
ስለ ምሁራኑ
እባክህ አምላኬ አንድ ነገር ስማኝ
የተማረው ከላይ ሁኖ እንድታሳየኝ
የዚህ ፅሁፍ መታሰቢያነቱ
ይሁንልኝ ለሊቃውንቱ
ለደቀ መዛሙርቱ
በረሃብ በግፍ ለሚንገላቱ
መጋቤ ሐዲስ ሄኖክ ፈንቴ
ነሐሴ 15/2009 (ሸር)
መካነ ጉባኤ ዘቅኔ ተጻፈ
📌ሼር
@Mgetem
@Mgetem
@Solasc
👍7❤3
🌺---------------------------------- 🌺
#አቡነ_ተክለ_ሃይማኖት
----------------------------------
📌 ታህሳስ 24 በዚህች ቀን ታላቁ ጻድቅ አቡነ ተክልሃይማኖት የተወለዱበት ቀን ነው። የትውልድ ቦታቸው ሸዋ ጽላልሽ አወራጃ ዞረሬ ነው ፤ የአባታቸው ስም ጸጋ ዘአብ የእናታቸው ስም እግዚ ሐርያ ይባላል መካን ነበሩ ልጅ እንዲሰጣቸው ወደ እግዚያብሔር ዘወትር ይጸልዩ ነበር ፤ መጋቢት 12 ቀን እንዲህ ሆነ ፤ ሞተሎሜ የተባለ ጣኦት አምላኪ ንጉስ አገራቸውን ወረረ መንደሩንም አጠፋ ጸጋ ዘአብ ወንዝ ውስጥ ገብቶ አመለጠ እግዚ ሐርያ ግን ተማርካ ሄደች ፤ በጣም መልከ መልካም ስለነበረች ሞቶሎሜ ሊያገባት አሰበ ታላቅ ድግስም ደገሰ አገር ምድሩ ተሰብስቦ ሲዘፍን ሲጨፍር ሳለ ቅዱስ ሚካኤል ታላቅ መብረቅ ነጎድጓድ አሰማ ብ...ዙዎች ሞቱ እግዚሐርያን በክንፎ ተሸክሞ ዞረሬ ከቤተክርስቲያን ውስጥ አስቀመጣት ከባለቤቷ ጸጋ ዘአብ ጋር ተገናኙ ተቃቅፈው ተላቀሱ ፤ ከሁለት ቀን በኃላ መጋቢት 24 ቀን ተክልዬ ተጸነሱ በዛሬዋ ቀን 1167 ዓ/ም ተወለዱ፡፡
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem_Bot
#አቡነ_ተክለ_ሃይማኖት
----------------------------------
📌 ታህሳስ 24 በዚህች ቀን ታላቁ ጻድቅ አቡነ ተክልሃይማኖት የተወለዱበት ቀን ነው። የትውልድ ቦታቸው ሸዋ ጽላልሽ አወራጃ ዞረሬ ነው ፤ የአባታቸው ስም ጸጋ ዘአብ የእናታቸው ስም እግዚ ሐርያ ይባላል መካን ነበሩ ልጅ እንዲሰጣቸው ወደ እግዚያብሔር ዘወትር ይጸልዩ ነበር ፤ መጋቢት 12 ቀን እንዲህ ሆነ ፤ ሞተሎሜ የተባለ ጣኦት አምላኪ ንጉስ አገራቸውን ወረረ መንደሩንም አጠፋ ጸጋ ዘአብ ወንዝ ውስጥ ገብቶ አመለጠ እግዚ ሐርያ ግን ተማርካ ሄደች ፤ በጣም መልከ መልካም ስለነበረች ሞቶሎሜ ሊያገባት አሰበ ታላቅ ድግስም ደገሰ አገር ምድሩ ተሰብስቦ ሲዘፍን ሲጨፍር ሳለ ቅዱስ ሚካኤል ታላቅ መብረቅ ነጎድጓድ አሰማ ብ...ዙዎች ሞቱ እግዚሐርያን በክንፎ ተሸክሞ ዞረሬ ከቤተክርስቲያን ውስጥ አስቀመጣት ከባለቤቷ ጸጋ ዘአብ ጋር ተገናኙ ተቃቅፈው ተላቀሱ ፤ ከሁለት ቀን በኃላ መጋቢት 24 ቀን ተክልዬ ተጸነሱ በዛሬዋ ቀን 1167 ዓ/ም ተወለዱ፡፡
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem_Bot
❤2👏1
፨እድሜ ለንስሃ፨
ያማረ ያጌጠ አዲስ ቤት ሰርቼ
እስክመለስ ድረስ አደራ ሰጥቼ
ሰፈሩን መንደሩን ቀየውንም ትቼ
ብዙ ዓመታትን ኖሬ ከዛ ሀገር ወጥቼ
አሁን ተመልሼ ስጎበኘው ቤቴን
አይኔን ማመን አቅቶኝ በእጄ ይዤ አፌን
እንዲጠብቅልኝ አደራ ይልኩት ሰው
እሳት ሲያነድበት ሲያጨስበት ኖሮ
ጣሪያውም ጠልሽቶ ግርግዳውም ጦቅሮ
ተረጋግጦ ሳየው ውስጡ ተሰባብሮ
እራሴን ታዘብኩት አዝኜ ከውስጤ
ድሮም!በሰው ተማምኜ ትቼው መቀመጤ
እንግዲ ፍረዱኝ!እስክመለስ ድረስ
ያደፈውን ዘመን በጊዜው እስካድስ
ጣርያ ግርግዳውን ወለሉን አፅደቶ
ያፈራርሰውን ካልጠበቀኝ ሰርቶ
እፋረደዋለው ህግ በፊት አቁሜ
ግን እስከዛው ድረስ
ሰጥቼዋለሁኝ ጥቂት ቀሪ እድሜ።
@Mgetem
ያማረ ያጌጠ አዲስ ቤት ሰርቼ
እስክመለስ ድረስ አደራ ሰጥቼ
ሰፈሩን መንደሩን ቀየውንም ትቼ
ብዙ ዓመታትን ኖሬ ከዛ ሀገር ወጥቼ
አሁን ተመልሼ ስጎበኘው ቤቴን
አይኔን ማመን አቅቶኝ በእጄ ይዤ አፌን
እንዲጠብቅልኝ አደራ ይልኩት ሰው
እሳት ሲያነድበት ሲያጨስበት ኖሮ
ጣሪያውም ጠልሽቶ ግርግዳውም ጦቅሮ
ተረጋግጦ ሳየው ውስጡ ተሰባብሮ
እራሴን ታዘብኩት አዝኜ ከውስጤ
ድሮም!በሰው ተማምኜ ትቼው መቀመጤ
እንግዲ ፍረዱኝ!እስክመለስ ድረስ
ያደፈውን ዘመን በጊዜው እስካድስ
ጣርያ ግርግዳውን ወለሉን አፅደቶ
ያፈራርሰውን ካልጠበቀኝ ሰርቶ
እፋረደዋለው ህግ በፊት አቁሜ
ግን እስከዛው ድረስ
ሰጥቼዋለሁኝ ጥቂት ቀሪ እድሜ።
@Mgetem
👍6❤3
#ማርያም
ማርያም ናት እናቴ
ብደክም ብርታቴ
ብረሳ አስታዋሼ
ብታረዝ አልባሼ
ቢርበኝ አጉራሼ
ብታመም ፈዋሼ
ወይኑን የሰጠችኝ
ስገፋ ያየችኝ
ቢከፋኝ መፅናኛ
ቀን ቢከዳ ዳኛ
ባጣ የሚገኝባት
ቢመሽ የማይባት
ልቤን ያሳረፈች
አምላኬን ያቀፈች
ማርያም ማርያም ስላት
መታለች የኔ እናት
እርፍ ብያለሁ
እመሰክራለሁ
እናንተም እንደኔ
ማርያም ማርያም በሉ
እርፍ በሉ።
@Mgetem
@Mgetem_bot
@Yohannes_mariyam
ማርያም ናት እናቴ
ብደክም ብርታቴ
ብረሳ አስታዋሼ
ብታረዝ አልባሼ
ቢርበኝ አጉራሼ
ብታመም ፈዋሼ
ወይኑን የሰጠችኝ
ስገፋ ያየችኝ
ቢከፋኝ መፅናኛ
ቀን ቢከዳ ዳኛ
ባጣ የሚገኝባት
ቢመሽ የማይባት
ልቤን ያሳረፈች
አምላኬን ያቀፈች
ማርያም ማርያም ስላት
መታለች የኔ እናት
እርፍ ብያለሁ
እመሰክራለሁ
እናንተም እንደኔ
ማርያም ማርያም በሉ
እርፍ በሉ።
@Mgetem
@Mgetem_bot
@Yohannes_mariyam
❤6👍1👏1
👍1👏1
@Mgetem
በክርስቶስ ፍቅር በስመ ስላሴ፤
ከእግሬ በርከክ ብዬ ዝቅ ብዬ ከራሴ።c
በወልድ ሀብተ ወልድ በድንግል ተዋህዶ፤
በክርስቶስ ክርስትያን ያ’ረጋችሁ ፈቅዶ።
በሰማታት አማንያን የተሰኛችሁ፤
ወልደና ወለተ ይህ ድምፅ ሚሰማችሁ፤
እንደምን ከረማችሁ? እንደምን ሰነበታችሁ?
እንደምንስ እስከዚች ሰአት ደረሳችሁ?
አሜን አልፋና ኦሜጋ የሰራዊት ጌታ፣
ይመስገን በፍጥረት ከጥኋት እስከ ማታ።
አምላክ ሲመሰገን ሁሌም በባህሪ፣
ለአዳም ዘር በሙሉ የሆነች ተጠሪ፣
ሁል ጊዜም ከቀኙ አትለይም እና፣
ከፍጥረት ይድረሳት የፀጋ ምስጋና።
መላእክት ሰማታት ፃድቃናት በሙሉ፤
ስላዳም ዘር ድነት በመማፀን ያሉ፤
መርጦ ለኛ ድነት ፀጋ ያደላቸው፤
ሁሌም ይመስገኑ እንደዬ ክብራቸው።
#ቃል ነበረ
ጨረቃ ክዋክብት ፀሀይ እና ምድር፤
መላእክት ሰማእታት ስነ-ፍጥረት ሳይኖር፤
አልፋ እና ኦሜጋ የማይመረመር፤
የሁሉ መሰረት ያን ጊዜ ቃል ነበር።
ምድርና ሰማይን በአንድ ቀን ፈጠረ፤
ደግሞም ለአምስት ቀናት ሌሎችን ጨመረ፤
እንደየ አይነቱ ሁሉን አሳመረ፤
በሰባተኛው ቀን መፍጠር በጀመረ፣
እግዚአብሔር እንዲ አለ፦
“ ሰውን በመልካችን እንደምሳሌአችን እንፍጠር፤
አዋፍትንም ይግዛ ይሰልጥን በምድር።”
ከሰባት ባህርያት በጆቹ አበጃጀው፤
የመጀመሪያም ሲል አዳም ብሎ ጠራው፤
ሁሉ ወደአለበት ገነትም ወወሰደው፤
የሞት ሞት እንዳይሞት አንዷን ከለከለው፤
አልፋ እና ኦሜጋ የማይመረመር፤
የሁሉ መሰረት ያን ጊዜም ቃል ነበር።
በሰባተኛው ቀን ከሰባት ባህርያት የተበጀው አዳም፤
የገነት ኑሮውን ከሰባት አመታት ማሳለፍ አልቻለም።
አምላኩን ሰረቀ፤
ሁሉንም አወቀ፤
አውቆም ተደበቀ፤
አልፋና ኦሜጋ ማይመረመረው፤
አዳምን እንዲ አለው፦
ወደምድር ሂድ ጥረህ ግረህ ብላ፤
እሷም ታብቅልብህ እሾህ አሜከላ።
ለአምስት ቀን ከግማሽ ይበዛል መከራህ፤
ስወለድ ነው ምትድን እኔ ከልጅ ልጅህ።
አዳም ተፀፅቶ እጅግ ብዙ ለፋ፤
ነገር ግን አልቻለም ሀፂያቱን ሊያጠፋ።
ከመጠበቅ በቀር ያንን ቃል በተስፋ።
ሁሉንም ከማድረግ አንዳች ማይሳነው፤
መፍረድ እና ማዳን ባህሪው የሆነው፤
የሚገለጥበት የው ደረሰ ጊዜው።
መኖር ሳይጀመር ይኖር የነበረ፤
አልፋና ኦሜጋ ጥንትም ቃል ነበረ።
በሰማይ በምድር ታላቅ ደስታ ሆነ፤
በከብቶቹ በረት ዛሬ ቃል ሰው ሆነ።
በኮከብ ተመርተው ሰባ ሰገል መጡ፤
ለንጉስነቱ ወርቁን አስቀመጡ ፤
ለሞቱ የሚሆን ከርቤውን አወጡ፤
ለአምላክነቱ እጣን ሰግደው ሰጡ።
በደስታ እልል እንበል ልዩ ቀን ነው ለኛ፤
ከድንግል ተወልዷል እውነተኛው ዳኛ፤
አዳምን ለማዳን ከሰይጣን ቁራኛ።
አሲናበል አሲና ገናዬ፤
ተወለደ ጌታችሁ ጌታዬ።
በነብያት የተነገረለት፤
አማኑኤል ነው የተኛው በበረት።
እመብርሃን አብሳሪተ ፀጋ፤
አትለየን ሁሌም ከልጇጋ።
ስናከብር በዐለ እልደቱን፤
ያስቀየምነ ይቅርታ ጠይቀን፤
የተቀየምን ከልብ ይቅር ብለን፤
እንዋደድ እርስበርስ ሁላችን።
እንዲህ ደምቀን እንደተሰባሰብን፤
የበዓሉ ባለቤት በረከት ያድለን።
በማልት በሰርክ ፀሎት ስታደርጉ፤
ለገብረ ሚካኤል ማለትን አዘንጉ።
ያስቀየምኋችሁ በምላስ ወለምታ፤
በእግዚያብሄር ስም ይቅርታ(3)።
ተፃፈ በመስፍን ምትኬ ፪፻፲፪/፬/፪፭ ዓ.ም
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem_bot
በክርስቶስ ፍቅር በስመ ስላሴ፤
ከእግሬ በርከክ ብዬ ዝቅ ብዬ ከራሴ።c
በወልድ ሀብተ ወልድ በድንግል ተዋህዶ፤
በክርስቶስ ክርስትያን ያ’ረጋችሁ ፈቅዶ።
በሰማታት አማንያን የተሰኛችሁ፤
ወልደና ወለተ ይህ ድምፅ ሚሰማችሁ፤
እንደምን ከረማችሁ? እንደምን ሰነበታችሁ?
እንደምንስ እስከዚች ሰአት ደረሳችሁ?
አሜን አልፋና ኦሜጋ የሰራዊት ጌታ፣
ይመስገን በፍጥረት ከጥኋት እስከ ማታ።
አምላክ ሲመሰገን ሁሌም በባህሪ፣
ለአዳም ዘር በሙሉ የሆነች ተጠሪ፣
ሁል ጊዜም ከቀኙ አትለይም እና፣
ከፍጥረት ይድረሳት የፀጋ ምስጋና።
መላእክት ሰማታት ፃድቃናት በሙሉ፤
ስላዳም ዘር ድነት በመማፀን ያሉ፤
መርጦ ለኛ ድነት ፀጋ ያደላቸው፤
ሁሌም ይመስገኑ እንደዬ ክብራቸው።
#ቃል ነበረ
ጨረቃ ክዋክብት ፀሀይ እና ምድር፤
መላእክት ሰማእታት ስነ-ፍጥረት ሳይኖር፤
አልፋ እና ኦሜጋ የማይመረመር፤
የሁሉ መሰረት ያን ጊዜ ቃል ነበር።
ምድርና ሰማይን በአንድ ቀን ፈጠረ፤
ደግሞም ለአምስት ቀናት ሌሎችን ጨመረ፤
እንደየ አይነቱ ሁሉን አሳመረ፤
በሰባተኛው ቀን መፍጠር በጀመረ፣
እግዚአብሔር እንዲ አለ፦
“ ሰውን በመልካችን እንደምሳሌአችን እንፍጠር፤
አዋፍትንም ይግዛ ይሰልጥን በምድር።”
ከሰባት ባህርያት በጆቹ አበጃጀው፤
የመጀመሪያም ሲል አዳም ብሎ ጠራው፤
ሁሉ ወደአለበት ገነትም ወወሰደው፤
የሞት ሞት እንዳይሞት አንዷን ከለከለው፤
አልፋ እና ኦሜጋ የማይመረመር፤
የሁሉ መሰረት ያን ጊዜም ቃል ነበር።
በሰባተኛው ቀን ከሰባት ባህርያት የተበጀው አዳም፤
የገነት ኑሮውን ከሰባት አመታት ማሳለፍ አልቻለም።
አምላኩን ሰረቀ፤
ሁሉንም አወቀ፤
አውቆም ተደበቀ፤
አልፋና ኦሜጋ ማይመረመረው፤
አዳምን እንዲ አለው፦
ወደምድር ሂድ ጥረህ ግረህ ብላ፤
እሷም ታብቅልብህ እሾህ አሜከላ።
ለአምስት ቀን ከግማሽ ይበዛል መከራህ፤
ስወለድ ነው ምትድን እኔ ከልጅ ልጅህ።
አዳም ተፀፅቶ እጅግ ብዙ ለፋ፤
ነገር ግን አልቻለም ሀፂያቱን ሊያጠፋ።
ከመጠበቅ በቀር ያንን ቃል በተስፋ።
ሁሉንም ከማድረግ አንዳች ማይሳነው፤
መፍረድ እና ማዳን ባህሪው የሆነው፤
የሚገለጥበት የው ደረሰ ጊዜው።
መኖር ሳይጀመር ይኖር የነበረ፤
አልፋና ኦሜጋ ጥንትም ቃል ነበረ።
በሰማይ በምድር ታላቅ ደስታ ሆነ፤
በከብቶቹ በረት ዛሬ ቃል ሰው ሆነ።
በኮከብ ተመርተው ሰባ ሰገል መጡ፤
ለንጉስነቱ ወርቁን አስቀመጡ ፤
ለሞቱ የሚሆን ከርቤውን አወጡ፤
ለአምላክነቱ እጣን ሰግደው ሰጡ።
በደስታ እልል እንበል ልዩ ቀን ነው ለኛ፤
ከድንግል ተወልዷል እውነተኛው ዳኛ፤
አዳምን ለማዳን ከሰይጣን ቁራኛ።
አሲናበል አሲና ገናዬ፤
ተወለደ ጌታችሁ ጌታዬ።
በነብያት የተነገረለት፤
አማኑኤል ነው የተኛው በበረት።
እመብርሃን አብሳሪተ ፀጋ፤
አትለየን ሁሌም ከልጇጋ።
ስናከብር በዐለ እልደቱን፤
ያስቀየምነ ይቅርታ ጠይቀን፤
የተቀየምን ከልብ ይቅር ብለን፤
እንዋደድ እርስበርስ ሁላችን።
እንዲህ ደምቀን እንደተሰባሰብን፤
የበዓሉ ባለቤት በረከት ያድለን።
በማልት በሰርክ ፀሎት ስታደርጉ፤
ለገብረ ሚካኤል ማለትን አዘንጉ።
ያስቀየምኋችሁ በምላስ ወለምታ፤
በእግዚያብሄር ስም ይቅርታ(3)።
ተፃፈ በመስፍን ምትኬ ፪፻፲፪/፬/፪፭ ዓ.ም
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem_bot
👍13❤8😢3👏1
፨እልል የምስራች ክርስቶስ ተወልዷል፨
በተባረከችው በዚያች በውብ ምሽት
እረኞችም ሁሉ እደጅ ባደሩበት
ህፃን ተወለደ በከብቶች ግርግም ውስጥ
ቤዛ ሊሆን ኋላ ለዓለም ነፍሱን ሊስጥ
ጌታ ተወለደ የእስራኤል ንጉስ
ከአለም እርኩሰት ትውልድን ሊመልስ
እልል..!የምስራች ክርስቶስ ተወልዷል
ከእናቱ ከማርያም ከማህፀኗ ወጥቷል።
በዚያች ቅድስት ለሊት በከብቶች በረት ውስጥ በጨርቅ ተጠቅልሎ
በረከተ ሥጋን በረከተ ነፍስን ለሰው ልጅ አድሎ
ሊያኖረን ተወልዷል የሠራዊት አምላክ አልፋና ኦሜጋ
ከእናቱ ከማርያም ከነፍሷ ነፍስ ነስቶ ከስጋዋ ሥጋ
እልል... የምስራች ኢየሱስ ተወልዷል
አለምን ከጥፋት ሊያድን ምድር ወርዷል
ከእግዜር የተላኩት ቅዱሳን መላዕክት ብሥራት አብስረዋል
ክብር ለእግዚአብሔር በአርያም ሲሉም መዝሙር ዘምረዋል።
እኛም እስቲ እንዘምር እናሸብሽብላት በምሥጋና ዜማ
የጌታን መወለድ ያልሰማ እንዲሰማ የሰማ እንዲያሰማ።
እልል... የምስራች ክርስቶስ ተወለዷል
ከእናቱ ከማርያም ከማህፀኗ ወጥቷል።
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem
በተባረከችው በዚያች በውብ ምሽት
እረኞችም ሁሉ እደጅ ባደሩበት
ህፃን ተወለደ በከብቶች ግርግም ውስጥ
ቤዛ ሊሆን ኋላ ለዓለም ነፍሱን ሊስጥ
ጌታ ተወለደ የእስራኤል ንጉስ
ከአለም እርኩሰት ትውልድን ሊመልስ
እልል..!የምስራች ክርስቶስ ተወልዷል
ከእናቱ ከማርያም ከማህፀኗ ወጥቷል።
በዚያች ቅድስት ለሊት በከብቶች በረት ውስጥ በጨርቅ ተጠቅልሎ
በረከተ ሥጋን በረከተ ነፍስን ለሰው ልጅ አድሎ
ሊያኖረን ተወልዷል የሠራዊት አምላክ አልፋና ኦሜጋ
ከእናቱ ከማርያም ከነፍሷ ነፍስ ነስቶ ከስጋዋ ሥጋ
እልል... የምስራች ኢየሱስ ተወልዷል
አለምን ከጥፋት ሊያድን ምድር ወርዷል
ከእግዜር የተላኩት ቅዱሳን መላዕክት ብሥራት አብስረዋል
ክብር ለእግዚአብሔር በአርያም ሲሉም መዝሙር ዘምረዋል።
እኛም እስቲ እንዘምር እናሸብሽብላት በምሥጋና ዜማ
የጌታን መወለድ ያልሰማ እንዲሰማ የሰማ እንዲያሰማ።
እልል... የምስራች ክርስቶስ ተወለዷል
ከእናቱ ከማርያም ከማህፀኗ ወጥቷል።
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem
👍5❤1
፨ያኔ ጥንት ነበረ፨
በዱር በገደሉ በዓለም ዙርያ ሁሉ
አምላክ ይወለዳል ብለው ተናገሩ
የነቢያት ተስፋ የነበለአም
አምላክ ተወለደ መድሃኒዓለም
ያኔ ጥንት ነበር...
ይወለዳል ሲሉ በመንፈስ ሲመሩ
አምላክ አዶናይን ለማየት ሲጥሩ
እንደው ኩርምት ብለው በተስፋ ሲኖሩ
ድንግል ትፀንሳለች ብለው ሲናገሩ
ቀናትን ሲቆጥሩ ሳምንታት ሲሠምሩ
ሳምንታት በግንድ ላይ ወራትን ሲሠሩ
ወራት ተቀናጅተው ዓመትን ሲሰጡ
ዓመታት ተቆጥረው ዘመናት ሲመጡ
እናያለን ሲሉ ለማየት ሳይበቁ
በመንፈስ ሲሰክሩ እንዲውል ሲሳለቁ
ያኔ ጥንት ነበር....
ያኔ ጥንት ነበር በመንፈስ መሰከሩ
አምላክ ይወለዳል ብሎ መዘከሩ
በርቀት ተሳልሞ ለዓለም ማብሰሩ
ያኔ ጥንት ነበር የመውደቅ ሚስጥሩ
ሃጢአትን መፀነሱ የመውደቅ ሚስጥሩ
ሃጢያትን መፀነሱ ሞትንም መውለዱ
ከገነት ተባሮ እንዲያው መዋረዱ
ፀጋውን ተገፎ በለስ ማገልደሙ
ያኔ ጥንት ነበር...
አዳምን ሊጎበኝ አምላክ መጣራቱ
አዳም አዳም አዳም ብሎ መፈለጉ
አትብሉ ያልኩህን በላህው ማለቱ
አዳምን በመፍጠር እንዲያው መፀፀቱ
አዳምም አዘነ በሔዋን ፈረደ
ሔዋንም አዘነች እባቡ ነው አለች
እባብ ተረገመች አፈራ ባይሆናት
አዳም ተባረረ ሄዋን አለቀሰች
ምድር ተረገመች እሾህ አበቀለች
አቤት ያኔ ነበር ያኔ ጥንት ነበረ
አዳም መበደሉ ሰዎችን ለውድቀት ለሞት መደረጉ
ያኔ ነበር ፅንሱ ሰዎችን ለሽንፈት ለሞት መፈለጉ
ዛሬ ግን ዛሬ ያ የጥንቱ ቀረና
እራሱን አዋርዶ አዳም ከበረና
ሲወለድ በቤተልሔም በነብዩ ተፅፎአልና
አምላክ ተወለደ በከብቶች መና
ታሪኩ ሲተርክ የሰማህ ወንድሜ
ራስክን መርምረው ና ይልሃል ዛሬ
አቤት ያኔ ጥንት ነበር....
ያኔ ጥንት ነበር የአዳም ውድቀቱ
ዛሬ በክርስቶስ ሕይወትን ማግኘቱ
ዛሬስ እኛ ወገን
የያኔ የጥንቱ ትተን ለንስሐ ቀርበን
ስጋውንም በልተን ደሙንም ጠጥተን
በድያለሁ ብለን ከፊቱ ላይ ወድቀን
መመለስ ይሻላል ክርስቶስን ብለን
መመለስ ያሻል ኪዳነ ምህረትን ብለን።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር!
እንኳን ለብርሃነ ልደቱ በሰላም አደረሳቹ አደረሰን!
መልካም ጥምቅት
መልካም በዓል
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem
በዱር በገደሉ በዓለም ዙርያ ሁሉ
አምላክ ይወለዳል ብለው ተናገሩ
የነቢያት ተስፋ የነበለአም
አምላክ ተወለደ መድሃኒዓለም
ያኔ ጥንት ነበር...
ይወለዳል ሲሉ በመንፈስ ሲመሩ
አምላክ አዶናይን ለማየት ሲጥሩ
እንደው ኩርምት ብለው በተስፋ ሲኖሩ
ድንግል ትፀንሳለች ብለው ሲናገሩ
ቀናትን ሲቆጥሩ ሳምንታት ሲሠምሩ
ሳምንታት በግንድ ላይ ወራትን ሲሠሩ
ወራት ተቀናጅተው ዓመትን ሲሰጡ
ዓመታት ተቆጥረው ዘመናት ሲመጡ
እናያለን ሲሉ ለማየት ሳይበቁ
በመንፈስ ሲሰክሩ እንዲውል ሲሳለቁ
ያኔ ጥንት ነበር....
ያኔ ጥንት ነበር በመንፈስ መሰከሩ
አምላክ ይወለዳል ብሎ መዘከሩ
በርቀት ተሳልሞ ለዓለም ማብሰሩ
ያኔ ጥንት ነበር የመውደቅ ሚስጥሩ
ሃጢአትን መፀነሱ የመውደቅ ሚስጥሩ
ሃጢያትን መፀነሱ ሞትንም መውለዱ
ከገነት ተባሮ እንዲያው መዋረዱ
ፀጋውን ተገፎ በለስ ማገልደሙ
ያኔ ጥንት ነበር...
አዳምን ሊጎበኝ አምላክ መጣራቱ
አዳም አዳም አዳም ብሎ መፈለጉ
አትብሉ ያልኩህን በላህው ማለቱ
አዳምን በመፍጠር እንዲያው መፀፀቱ
አዳምም አዘነ በሔዋን ፈረደ
ሔዋንም አዘነች እባቡ ነው አለች
እባብ ተረገመች አፈራ ባይሆናት
አዳም ተባረረ ሄዋን አለቀሰች
ምድር ተረገመች እሾህ አበቀለች
አቤት ያኔ ነበር ያኔ ጥንት ነበረ
አዳም መበደሉ ሰዎችን ለውድቀት ለሞት መደረጉ
ያኔ ነበር ፅንሱ ሰዎችን ለሽንፈት ለሞት መፈለጉ
ዛሬ ግን ዛሬ ያ የጥንቱ ቀረና
እራሱን አዋርዶ አዳም ከበረና
ሲወለድ በቤተልሔም በነብዩ ተፅፎአልና
አምላክ ተወለደ በከብቶች መና
ታሪኩ ሲተርክ የሰማህ ወንድሜ
ራስክን መርምረው ና ይልሃል ዛሬ
አቤት ያኔ ጥንት ነበር....
ያኔ ጥንት ነበር የአዳም ውድቀቱ
ዛሬ በክርስቶስ ሕይወትን ማግኘቱ
ዛሬስ እኛ ወገን
የያኔ የጥንቱ ትተን ለንስሐ ቀርበን
ስጋውንም በልተን ደሙንም ጠጥተን
በድያለሁ ብለን ከፊቱ ላይ ወድቀን
መመለስ ይሻላል ክርስቶስን ብለን
መመለስ ያሻል ኪዳነ ምህረትን ብለን።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር!
እንኳን ለብርሃነ ልደቱ በሰላም አደረሳቹ አደረሰን!
መልካም ጥምቅት
መልካም በዓል
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem
👍7😢1
#አያምርበት
#ፍቅርህ_የቀመሰ ከማእድህ በልቶ
#ምህረት_የጠገበ ይቅርታን ጠጥቶ
#ምንስ ያምርበታል ደምህን ረግጦ ?
በምክርህ ተቃኝቶ ተሰርቶ ያደገ
በመንፈስህ ህይወትን ስቦ እየማገ
መከራ ቢያይል ተስፋ አለው ለነገ
#በእጅህ_ተዳሶ በረከት ያገኘ
#በፍቅርህ_ጥልቅ ባህር በደስታ የዋኘ
#ምኑ_ማርኮት ይሆን ምድርን የተመኘ ?
በትእግስትህ በር ወጥቶ እየገባ
ዳዴን ከአንተ ተምሮ ከአንተው የጠባ
ግና ዛሬ አድጎ ከወጥመድ ሊገባ
#በሰላምህ ምርኩዝ በደስታህ ዘይት
#ነፍሱ_የመገብሃት ቃልህ ያጠገብሀት
#ከአንተ_ሌላማ ጌጥም አያምርባት
ድቅድቁን ጨለማ ረግጦ የመጣ
ይቅርታን ተምሮ ለቂም ቦታ ያጣ
እንዴት ያምርበታል ከቤትህ ቢወጣ ?
#ጠረንህን_ለምዶ ግሩሙን መዓዛ
#ምንጩ_ቀራኒዮ የህይወቱ ለዛ
#የነበረው_ፍሬ ስለምን ይጠንዛ ?
መኖሪያ አጥሩ መሸሸግያ ቅጥሩ
ለሆንህለት ጥላ እንዲፀና ስሩ
#አያምርበት_ቢርቅ ቢስት ከመስመሩ 🙏
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem
#ፍቅርህ_የቀመሰ ከማእድህ በልቶ
#ምህረት_የጠገበ ይቅርታን ጠጥቶ
#ምንስ ያምርበታል ደምህን ረግጦ ?
በምክርህ ተቃኝቶ ተሰርቶ ያደገ
በመንፈስህ ህይወትን ስቦ እየማገ
መከራ ቢያይል ተስፋ አለው ለነገ
#በእጅህ_ተዳሶ በረከት ያገኘ
#በፍቅርህ_ጥልቅ ባህር በደስታ የዋኘ
#ምኑ_ማርኮት ይሆን ምድርን የተመኘ ?
በትእግስትህ በር ወጥቶ እየገባ
ዳዴን ከአንተ ተምሮ ከአንተው የጠባ
ግና ዛሬ አድጎ ከወጥመድ ሊገባ
#በሰላምህ ምርኩዝ በደስታህ ዘይት
#ነፍሱ_የመገብሃት ቃልህ ያጠገብሀት
#ከአንተ_ሌላማ ጌጥም አያምርባት
ድቅድቁን ጨለማ ረግጦ የመጣ
ይቅርታን ተምሮ ለቂም ቦታ ያጣ
እንዴት ያምርበታል ከቤትህ ቢወጣ ?
#ጠረንህን_ለምዶ ግሩሙን መዓዛ
#ምንጩ_ቀራኒዮ የህይወቱ ለዛ
#የነበረው_ፍሬ ስለምን ይጠንዛ ?
መኖሪያ አጥሩ መሸሸግያ ቅጥሩ
ለሆንህለት ጥላ እንዲፀና ስሩ
#አያምርበት_ቢርቅ ቢስት ከመስመሩ 🙏
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem
👍4🥰4
#ወይ_ማወቅ_ደጉ !
#በባህር_በጥልቁ በሰማይ ተማክሮ
#ሊወጋው_ምስኪኑን ሃይል አስተባብሮ
#ሄደ ከምስኪኑ ሰፈር
ሊያጠፋው መታሰቢያው ሳይቀር
ዉጣ ይለይልህ ኪዳን አለኝ ማለት
ፀሎቱ መዝሙሩ አይደለም ከማጀት
ይህን ሁሉ ፉከራ የሰማው ምስኪን ሰው
ወዬው ጠፋሁ ብሎ ፍርሃት ብርክ ያዘው
የሞት ሞቱን ጨክኖ ብቅ ቢልባቸው
#የያዙት_መሳሪያ ወደቀ ከጃቸው
#እግሬ_አውጭኝ እግሬ አውጭኝ
እያሉ በሽቅድምድም
ሄዱ ከመጡበት አለም
#ይህ ሁሉ የሆነው..ምክንያቱ ምንድነው?
#ጋሻ ጦር አልያዝኩኝ....ይሄው ባዶየን ነኝ
#ምን አይተው ሮጡ......ሊገሉኝ የመጡ
እያለ ምስኪኑ ግራ እየተጋባ
ግድግዳው ላይ ካለው መስታወት ተጠጋ
ድንገት ቀና ብሎ ፊቱን ቢመለከት
#ለካስ_የኢየሱስ ደም በግንባሩ አለበት
#አሃ ! ደሙን አይተው ነው የተመለሱት
ወይ ማወቅ ደጉ!
#ለካስ_መፍትሄው ግንባርን ማሳየት
#ያኔ_ይመለሳል ሰይጣን ከመጣበት ። 🙏
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem
#በባህር_በጥልቁ በሰማይ ተማክሮ
#ሊወጋው_ምስኪኑን ሃይል አስተባብሮ
#ሄደ ከምስኪኑ ሰፈር
ሊያጠፋው መታሰቢያው ሳይቀር
ዉጣ ይለይልህ ኪዳን አለኝ ማለት
ፀሎቱ መዝሙሩ አይደለም ከማጀት
ይህን ሁሉ ፉከራ የሰማው ምስኪን ሰው
ወዬው ጠፋሁ ብሎ ፍርሃት ብርክ ያዘው
የሞት ሞቱን ጨክኖ ብቅ ቢልባቸው
#የያዙት_መሳሪያ ወደቀ ከጃቸው
#እግሬ_አውጭኝ እግሬ አውጭኝ
እያሉ በሽቅድምድም
ሄዱ ከመጡበት አለም
#ይህ ሁሉ የሆነው..ምክንያቱ ምንድነው?
#ጋሻ ጦር አልያዝኩኝ....ይሄው ባዶየን ነኝ
#ምን አይተው ሮጡ......ሊገሉኝ የመጡ
እያለ ምስኪኑ ግራ እየተጋባ
ግድግዳው ላይ ካለው መስታወት ተጠጋ
ድንገት ቀና ብሎ ፊቱን ቢመለከት
#ለካስ_የኢየሱስ ደም በግንባሩ አለበት
#አሃ ! ደሙን አይተው ነው የተመለሱት
ወይ ማወቅ ደጉ!
#ለካስ_መፍትሄው ግንባርን ማሳየት
#ያኔ_ይመለሳል ሰይጣን ከመጣበት ። 🙏
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem
👍4❤1🤬1
፨እናምናለን በምስጢረ ጥምቀቱ፨
በመጋቤ ምስጢርነቱ
በመንግሥተ ሰማይ በርነቱ
ሰው ካልተወለደ ከውኃና ከመንፈስ
ሕይወት እንደሌለው ርስት እንደማይወርስ
ያመነ የተጠመቀ ይድናል
በጥምቀቱ ልጅነት ያገኛል
ባያምን ባይጠመቅ ከልጅነቱ ይወጣል
ኢጥዮጵያዊው ባኮስ በሐዋርያው በፊሊጶስ
ከነቤተሰቦቹ እስጢፋኖስ
ቅዱስ ጳውሎስ ከደማስቆ መልስ
በጥምቀት ተወልደዋል ከመንፈስ ቅዱስ
ሔዋን በሰማንያ አዳም በአርባ ቀኑ
ገነት እንደገቡ ልጅነት እንዳገኙ
ሴቶች በሰማንያ ወንዶች ደግሞ በአርባ
ልጅነት እንዲያገኝ ተጠምቆ እንዲገባ
እናምናለን በእውነት
ያለጥርጥር በእምነት፡፡
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem
በመጋቤ ምስጢርነቱ
በመንግሥተ ሰማይ በርነቱ
ሰው ካልተወለደ ከውኃና ከመንፈስ
ሕይወት እንደሌለው ርስት እንደማይወርስ
ያመነ የተጠመቀ ይድናል
በጥምቀቱ ልጅነት ያገኛል
ባያምን ባይጠመቅ ከልጅነቱ ይወጣል
ኢጥዮጵያዊው ባኮስ በሐዋርያው በፊሊጶስ
ከነቤተሰቦቹ እስጢፋኖስ
ቅዱስ ጳውሎስ ከደማስቆ መልስ
በጥምቀት ተወልደዋል ከመንፈስ ቅዱስ
ሔዋን በሰማንያ አዳም በአርባ ቀኑ
ገነት እንደገቡ ልጅነት እንዳገኙ
ሴቶች በሰማንያ ወንዶች ደግሞ በአርባ
ልጅነት እንዲያገኝ ተጠምቆ እንዲገባ
እናምናለን በእውነት
ያለጥርጥር በእምነት፡፡
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem
❤2👍2🤬1
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
ውድ የቻናላችን ቤተሰቦች እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ በሰላም በጤና አደረሰን አደረሳችሁ...!!!
በዓሉ የሰላም የጤና የንስሐ እንዲሆንላችሁ ምኞታችን ነው....!
ውድ የቻናላችን ቤተሰቦች እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ በሰላም በጤና አደረሰን አደረሳችሁ...!!!
በዓሉ የሰላም የጤና የንስሐ እንዲሆንላችሁ ምኞታችን ነው....!
❤1
*:ጊዜ ምን በደለ;*
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
እውነትን ደብቀን ሀሰትን አንግሰን
አባቶች እያሉ ልጆች እያስተማርን
አርብ እሮቡን ሳናውቅ ሁልጊዜ አየበላን
ቤቱ መመላለስ ጭራሹን አቁመን
*
*
የእግዛብሔርን መቅደስ በሀጢያት ስንሞላ
እንደሰዶም ሆነን ህግን ስንጠላ
አህዛቦች ሲቀድሙን እኛ ቁመን ሇላ
ፀጋችን እያለ እሱን ሳናውቅበት ስንፈልግ ሌላ
*
*
የምንጓዝበት መንገዱ ረዝሞብን ቤቱ መሄድ ሲቀር
ሀይማኖት በገንዘብ እንደስም ሲቀየር
መፅሀፍትን ሳናነብ አባቶች እግር ስር ቁጭ ብለን ሳንማር
ቅዱስ ሁኑ ተብለን ምርጫችን ሲቀየር
*
*
ውበት ከአምላክ በላይ እኛ ስንሰራ
ቀለም እያማረጥን አለምን ስንመርጥ አምላክን ሳንፈራ
ማህሌት አዳር ትተን ስንመርጥ ጭፈራ
ሀብታችን ሀጢያት ገዝቶ ሲያስመስል ተራራ
*
*
ልብሳችንን ጥለን እርቃንን ስንመርጥ
በማናውቀው አለም ከላይ ሁነን ሳለ ወደ ታች ሰንዘቅጥ
አማርጠን ስንበላ ከደረቅ እስከ ቁርጥ
በደካማው ስጋ ለነፍሳችን ስንቅ ጭራሽ ሳናስቀምጥ
*
*
አወቀን ብለን ሳናውቅ በትቢት እየተጓዝን
ምርጫችን ከኛ በልጦ እኛኑ ሲመክረን
አልመለስ ስንል አምላክ እላይ ሁኖ በትዝብት ሲያዩን
ፍርጃ እላይ ቆመን ጌታ ሊመዝነን
እኛ ከሱ በልጠን ጭራሽ ፈራጅ ሁነን
*
*
ክፋትን አንግሰን ጠፋቶብን በጎነት
የውጩን አድንቀን ስንጓዝ በስህተት
ምርጫችን ተምታትቶ ስናማርጥ ውሸት
ሚስጥሩን ሳናውቀው ለመፋረድ ስንዋትት
*
*
በል በትርርህን አፅና የሚባል ሲጠፋ
መገንዘብ ሲያቅተን ምንድነን እንደሆነ የወደፊት ተስፋ
በማይጠቅም ህይወት ስንማስን ስንለፋ
ማወቁ ሲጠፋን ሁሉም ሟች መሆኑን ጠብቆ ወረፋ
*
መቶ ለማይሞላው ለዚህ አጭር እድሜችን
ምን ለማይጠቅመው እንጨነቃለን ለአፈሩ ስጋችን
አድሜአችን ሲቀንስ ከግባራችን ሲለቅ ፀጉራችን
መመለስ ሲያቅተን ዛሬ ነገ እያልን ሲመርሽ ቀናችን
*
አባቶችን ሰምተን ታሪክ ካልጠበቅን
ዘመናዊነት ሚስጥሩ ካልገባን
በአምና ተምረን ዘንድሮ ካልነቃን
ጊዜ ምን በደለ በሱ የፈረድን
*
ጊዜማ ሂደት ነው ድሮም የነበረ
እራሱን ሳይለውጥ ይሆን ሁሉ ዘመን በክብር የኖረ
ታዲያ ምን አጠፋ በሰው ተደፈረ
ንገረኝ ወንድሜ(ቴ) ጊዜ ምን በደለ":;"""''!?
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
እውነትን ደብቀን ሀሰትን አንግሰን
አባቶች እያሉ ልጆች እያስተማርን
አርብ እሮቡን ሳናውቅ ሁልጊዜ አየበላን
ቤቱ መመላለስ ጭራሹን አቁመን
*
*
የእግዛብሔርን መቅደስ በሀጢያት ስንሞላ
እንደሰዶም ሆነን ህግን ስንጠላ
አህዛቦች ሲቀድሙን እኛ ቁመን ሇላ
ፀጋችን እያለ እሱን ሳናውቅበት ስንፈልግ ሌላ
*
*
የምንጓዝበት መንገዱ ረዝሞብን ቤቱ መሄድ ሲቀር
ሀይማኖት በገንዘብ እንደስም ሲቀየር
መፅሀፍትን ሳናነብ አባቶች እግር ስር ቁጭ ብለን ሳንማር
ቅዱስ ሁኑ ተብለን ምርጫችን ሲቀየር
*
*
ውበት ከአምላክ በላይ እኛ ስንሰራ
ቀለም እያማረጥን አለምን ስንመርጥ አምላክን ሳንፈራ
ማህሌት አዳር ትተን ስንመርጥ ጭፈራ
ሀብታችን ሀጢያት ገዝቶ ሲያስመስል ተራራ
*
*
ልብሳችንን ጥለን እርቃንን ስንመርጥ
በማናውቀው አለም ከላይ ሁነን ሳለ ወደ ታች ሰንዘቅጥ
አማርጠን ስንበላ ከደረቅ እስከ ቁርጥ
በደካማው ስጋ ለነፍሳችን ስንቅ ጭራሽ ሳናስቀምጥ
*
*
አወቀን ብለን ሳናውቅ በትቢት እየተጓዝን
ምርጫችን ከኛ በልጦ እኛኑ ሲመክረን
አልመለስ ስንል አምላክ እላይ ሁኖ በትዝብት ሲያዩን
ፍርጃ እላይ ቆመን ጌታ ሊመዝነን
እኛ ከሱ በልጠን ጭራሽ ፈራጅ ሁነን
*
*
ክፋትን አንግሰን ጠፋቶብን በጎነት
የውጩን አድንቀን ስንጓዝ በስህተት
ምርጫችን ተምታትቶ ስናማርጥ ውሸት
ሚስጥሩን ሳናውቀው ለመፋረድ ስንዋትት
*
*
በል በትርርህን አፅና የሚባል ሲጠፋ
መገንዘብ ሲያቅተን ምንድነን እንደሆነ የወደፊት ተስፋ
በማይጠቅም ህይወት ስንማስን ስንለፋ
ማወቁ ሲጠፋን ሁሉም ሟች መሆኑን ጠብቆ ወረፋ
*
መቶ ለማይሞላው ለዚህ አጭር እድሜችን
ምን ለማይጠቅመው እንጨነቃለን ለአፈሩ ስጋችን
አድሜአችን ሲቀንስ ከግባራችን ሲለቅ ፀጉራችን
መመለስ ሲያቅተን ዛሬ ነገ እያልን ሲመርሽ ቀናችን
*
አባቶችን ሰምተን ታሪክ ካልጠበቅን
ዘመናዊነት ሚስጥሩ ካልገባን
በአምና ተምረን ዘንድሮ ካልነቃን
ጊዜ ምን በደለ በሱ የፈረድን
*
ጊዜማ ሂደት ነው ድሮም የነበረ
እራሱን ሳይለውጥ ይሆን ሁሉ ዘመን በክብር የኖረ
ታዲያ ምን አጠፋ በሰው ተደፈረ
ንገረኝ ወንድሜ(ቴ) ጊዜ ምን በደለ":;"""''!?
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem
👍7🥰3❤2👏1
የሚያጠፋት የለም።
✨✨✨⛪✨✨✨
ማዕበሉ ቢነሳ ቢነፍስ ነፋሱ
እሳት ቢንቀለቀል ቢጥጎለጎል ጢሱ
ሰይፎች ቢመዘዙ አበው ቢታረዱ
ወጣት አዛውንቱ እስር ቤት ቢወርዱ
ሰባኪው ዘማሪው ከመድረክ ቢባረር
መነኩሴው ካህኑ ወሕኒ ቢወረወር
ያንሰራራል እንጅ የስም አጠራሯ
ገኖ ያድራል እንጅ ተጽፎ ተአምሯ
የሴረኞች ሴራ እየተነገረ
መዝሙር በስማቼው እየተዘመረ
የሚያፈርሷት ፈርሰው
የሚያጠፏት ጠፈተው
የሚያነዷት ነደው
ጎስቁለው ተዋርደው
እናያለን እንጅ ኑራ ለዘለዓለም
ቤተክርስቲያንን የሚያጠፋት የለም።
አብ እሳት ወልድ እሳት ተብሎ ተቀድሶ
መንፈስ ቅዱስ እሳት ተብሎ ተወድሶ
ጠላት ቢያቃጥላት በእሳት ለኩሶ
እሳት ነው አምላኳ ያቃጥላል መልሶ
አወ እሳት ነው መንፈስ ቅዱስ
እሳት ነው ጰራቅሊጦስ
አሳት በላዒ ለአማፂያን
ወአቃጣይ ለከሀዲያን
ስሙን ለሚክዱ
መቅደሱን ለሚያዋርዱ
እንደቆሬ ካሕናት
የሚያቃጥል ሕያው እሳት
እንደ አዛርያስ ለቀነጣ
ግምባርን በለምጽ የሚቀጣ
በምድሩ እሳት በደካማው
ጥፋት ጥፋት በሚሰማው
የማይጠፋ እሳት ላያጠፉ
አሕዛብ በከንቱ ቢለፉ
ከንቱ ልፋት ከንቱ ድካም
ፍላጎትን አያሳካም
ዱለት ቢደወለት ቢፈጭ ቢቦካ
በግፈኞች ሚዛን ግፋችን ቢለካ
ጠላት ሰይፍ አንግቦ ቢሸልል ቢያሽካካ
ቤተክርስቲያን ክብሯ ሳይነካ
ትኖራለች እንጅ ጸንታ ለዘለዓለም
የክርስቶስን ቤት የሚያፈርሳት የለም።
አሕዛብ መናፍቃን በርሷ ላይ ቢነሱ
ሰይፍ ተሸክመው እሳት ቢለኩሱ
በሔሮድስ ቁጣ በክብሯ ቢዝቱ
አዋጅ አስነግረው በጋራ ቢዘምቱ
ከክርስቶስ ጋር ነው ፍልሚያው ጦርነቱ።
ያኔ ሰይፍ ያነሱ በሰይፍ ይጠፋሉ
ጉድጓድ የቆፈሩም በጉድጓድ ያልቃሉ
አሕዛብ መናፍቃን ይህነን አውቃችሁ
የሰይፍ የመሣሪያ ወጩን ቀንሳችሁ
ልብ እንድትገዙበት ልቦና ይስጣችሁ
ትኖራለች እንጅ ፀንታ ለዘለዓለም
ቤተክርስቲያን የሚያጠፋት የለም።
አንተ ግን አደራ
አንተ ግን አደራ በአፄ ካሌብ ገድል
በአብርሃና አጽብሃ በሰላማ መስቀል
በአቡነ አረጋዊ በክርስቶስ ሰምራ
በተክለሃይማኖት በነላሊበላ
በብርብር ማርያም በአክሱም በዝቋላ
በኤሊ ገብርኤል በደብረ ሊባኖስ
በደብር ማርያም በመስቀለ ኢየሱስ
በመስቀሉ ግማድ በግሸን ማርያም
በአቡነ ዐሮን በአሰቦት ገዳም
ምሥራቁ ምእራቡ ሰሜኑ ደቡቡ
ሁሉም በእምነቱ ሁሉም በማተቡ
ባንጃበበው ስቃይ መከራ ሰቁቃ
በቼልታ እንዳታልፍ ክርስቲያን ሲጠቃ
የተኛህ ተነሳ ያንቀላፋህ ንቃ
አንተ ለዘር ለጎጥ ስትገነጣጠል
ለወንዝ ለተራራ ልብህ ሲንጠለጠል
የወለጋን መቅደስ ለፓስተር እንትና
አርባምንጭ ጎፋን ለመንፈስ ትወና
የዝቋላን ገዳም ለኢሉማንቱ
ቅዱስ ላሊበላን ለ666ቱ
ጎንደርን ለጅዳ አክሱምን ለመካ
አማጭ እንደላኩ አልሰማህም ለካ
አንተ ግን አደራ ክርስቲያን ወገኔ
የደም እዳ አለብህ ከፈሰሰው ያኔ
በዮዲት ጭፍጨፋ በግራኝ ወረራ
ያጥንትና የደም አለብህ አደራ
ማነምን ሳታፍር ማነምን ሳትፈራ
መቅደስህን ጠብቅ ካባቶችህ ጋራ
አንተ ግን አደራ
አገልጋይ ካሕኑ
አማኙ ምእመኑ
የአቋቋም ምሁሩ
በላዜማ ባለመዝሙሩ
የቅኔው ዘራፊ
የድጓው ፀሐፊ
የዝማሬው የቅዳሴው
የትርጓሜው የውዳሴው
፬ ዓይናው ልበ ሰፊው
አስተዳደሩ ሀላፊው
መነኮሱ ቆሞሱ
ኤጲስ ቆጶሱ ጳጳሱ
የቴውሎጅው ተመራቂ
የምሥጢራቱ አርቃቂ
ሰንበት ተማሪው ማሕበራቱ
ማሕበረ ቅዱሳን ባለሕጉ
ደጆችሽ አይዘጉ
ኦረቶዶክሳዊ በሙሉ
ተማማለህ በመስቀሉ
ጠብቅ ያንተን አደራ
እንዳትሽሽ አንዳትፈራ
እንደበግ ጨው እያላሱ
እያሳሳቁ እያወደሱ
እያጠጋጉን ወደነሱ
ደሮን በጥሬ እንዲጥሉ
ሊበሉን እያታለሉ
ማዕዳቼውን ሊያቀርቡ
በደማችን ከታጠቡ
ይበቃል ከዚህ በላይ
ማን አታላይ ማን ተታላይ
ማንስ አግላይ ማን ተገላይ
ማን ሆነና ባለርስቱ
የሀገር መሠረቱ
የሀገር ፍቅርን እየመገብነ
እኛው አቅፈን ባሳደግነ
ከአውሮፖውያን ተልኮ
ከዓረብ ልጅ ልጁን ልኮ
እኛን እኛን ከገፋ
ድብቅ ሴራውን ካስፋፋ
አንተ ግን አደራ
እንዳትወሰልት እንዳትፈራ
ክርስቶስ የወለደህ
እስከሞት የወደደህ
በፍቅሩ ያሳደገህ
አንተንማ ምን አስፈራህ
ያምላክህ ስራ የተጻፈ
ሞትን በሞት ያሸነፈ
ሰይፍ አትሻ የገዘፈ
ሰይፍ አለህ የረቀቀ
ጎልያድን ያወደቀ
ሰይፍ አለን ባንገታችን
ማተባችን መስቀላችን
ሰይፍ አለን በእጃችን
ዳዊታችን ድርሳናችን
እንጠብቅ አደራችችን።
ጸልዩ በእንቲያነ ስለኛ ጸልዩ ።
አቡነ ናትናኤል አቡነ ፊሊጶስ
አቡነ አረጋዊ አባ መርሓ ክርስቶስ
አባ መልከ ጼዴቅ ወአባ ሰላማ
አቡነ አረጋዊ አቡነ ገሪማ
በአንድነት ሁናችሁ በገነት ከተማ
ስለኛ ጸልዩ ድምፃችሁ ይሰማ፡
ኦርቶዶክሳውያን እንደበግ ታርደዋል
አብያተ ክርስቲያን በእሳት ተቃጥለዋል
ቅዱሳት ንዋያት እንደጧፍ ነደዋል
ክርስቲያኖች ሁሉ ለመኖር ሰግተዋል
በግፈኞች ሰይፍ ተከበው ቁመዋል
ሱማሌ ጅግጅጋ ጅማና ሲዳማ
መለውና ጎፋ ያገሬ ከተማ
ኦርቶዶክሳውያን እየተሰደዱ
ካህናት ሊቃውንት እየተዋረዱ
ቅዱሳን ቦታዎች እየተነጠቁ
ምእመናን ካህናት እየተጨነቁ
እጅግ ስለበዛ ግፉና ስቃዩ
አሳስቡን ከጌታ ስለኛ ጸልዩ
➴ ከመምህር ኤፍሬም ተስፋ
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem
✨✨✨⛪✨✨✨
ማዕበሉ ቢነሳ ቢነፍስ ነፋሱ
እሳት ቢንቀለቀል ቢጥጎለጎል ጢሱ
ሰይፎች ቢመዘዙ አበው ቢታረዱ
ወጣት አዛውንቱ እስር ቤት ቢወርዱ
ሰባኪው ዘማሪው ከመድረክ ቢባረር
መነኩሴው ካህኑ ወሕኒ ቢወረወር
ያንሰራራል እንጅ የስም አጠራሯ
ገኖ ያድራል እንጅ ተጽፎ ተአምሯ
የሴረኞች ሴራ እየተነገረ
መዝሙር በስማቼው እየተዘመረ
የሚያፈርሷት ፈርሰው
የሚያጠፏት ጠፈተው
የሚያነዷት ነደው
ጎስቁለው ተዋርደው
እናያለን እንጅ ኑራ ለዘለዓለም
ቤተክርስቲያንን የሚያጠፋት የለም።
አብ እሳት ወልድ እሳት ተብሎ ተቀድሶ
መንፈስ ቅዱስ እሳት ተብሎ ተወድሶ
ጠላት ቢያቃጥላት በእሳት ለኩሶ
እሳት ነው አምላኳ ያቃጥላል መልሶ
አወ እሳት ነው መንፈስ ቅዱስ
እሳት ነው ጰራቅሊጦስ
አሳት በላዒ ለአማፂያን
ወአቃጣይ ለከሀዲያን
ስሙን ለሚክዱ
መቅደሱን ለሚያዋርዱ
እንደቆሬ ካሕናት
የሚያቃጥል ሕያው እሳት
እንደ አዛርያስ ለቀነጣ
ግምባርን በለምጽ የሚቀጣ
በምድሩ እሳት በደካማው
ጥፋት ጥፋት በሚሰማው
የማይጠፋ እሳት ላያጠፉ
አሕዛብ በከንቱ ቢለፉ
ከንቱ ልፋት ከንቱ ድካም
ፍላጎትን አያሳካም
ዱለት ቢደወለት ቢፈጭ ቢቦካ
በግፈኞች ሚዛን ግፋችን ቢለካ
ጠላት ሰይፍ አንግቦ ቢሸልል ቢያሽካካ
ቤተክርስቲያን ክብሯ ሳይነካ
ትኖራለች እንጅ ጸንታ ለዘለዓለም
የክርስቶስን ቤት የሚያፈርሳት የለም።
አሕዛብ መናፍቃን በርሷ ላይ ቢነሱ
ሰይፍ ተሸክመው እሳት ቢለኩሱ
በሔሮድስ ቁጣ በክብሯ ቢዝቱ
አዋጅ አስነግረው በጋራ ቢዘምቱ
ከክርስቶስ ጋር ነው ፍልሚያው ጦርነቱ።
ያኔ ሰይፍ ያነሱ በሰይፍ ይጠፋሉ
ጉድጓድ የቆፈሩም በጉድጓድ ያልቃሉ
አሕዛብ መናፍቃን ይህነን አውቃችሁ
የሰይፍ የመሣሪያ ወጩን ቀንሳችሁ
ልብ እንድትገዙበት ልቦና ይስጣችሁ
ትኖራለች እንጅ ፀንታ ለዘለዓለም
ቤተክርስቲያን የሚያጠፋት የለም።
አንተ ግን አደራ
አንተ ግን አደራ በአፄ ካሌብ ገድል
በአብርሃና አጽብሃ በሰላማ መስቀል
በአቡነ አረጋዊ በክርስቶስ ሰምራ
በተክለሃይማኖት በነላሊበላ
በብርብር ማርያም በአክሱም በዝቋላ
በኤሊ ገብርኤል በደብረ ሊባኖስ
በደብር ማርያም በመስቀለ ኢየሱስ
በመስቀሉ ግማድ በግሸን ማርያም
በአቡነ ዐሮን በአሰቦት ገዳም
ምሥራቁ ምእራቡ ሰሜኑ ደቡቡ
ሁሉም በእምነቱ ሁሉም በማተቡ
ባንጃበበው ስቃይ መከራ ሰቁቃ
በቼልታ እንዳታልፍ ክርስቲያን ሲጠቃ
የተኛህ ተነሳ ያንቀላፋህ ንቃ
አንተ ለዘር ለጎጥ ስትገነጣጠል
ለወንዝ ለተራራ ልብህ ሲንጠለጠል
የወለጋን መቅደስ ለፓስተር እንትና
አርባምንጭ ጎፋን ለመንፈስ ትወና
የዝቋላን ገዳም ለኢሉማንቱ
ቅዱስ ላሊበላን ለ666ቱ
ጎንደርን ለጅዳ አክሱምን ለመካ
አማጭ እንደላኩ አልሰማህም ለካ
አንተ ግን አደራ ክርስቲያን ወገኔ
የደም እዳ አለብህ ከፈሰሰው ያኔ
በዮዲት ጭፍጨፋ በግራኝ ወረራ
ያጥንትና የደም አለብህ አደራ
ማነምን ሳታፍር ማነምን ሳትፈራ
መቅደስህን ጠብቅ ካባቶችህ ጋራ
አንተ ግን አደራ
አገልጋይ ካሕኑ
አማኙ ምእመኑ
የአቋቋም ምሁሩ
በላዜማ ባለመዝሙሩ
የቅኔው ዘራፊ
የድጓው ፀሐፊ
የዝማሬው የቅዳሴው
የትርጓሜው የውዳሴው
፬ ዓይናው ልበ ሰፊው
አስተዳደሩ ሀላፊው
መነኮሱ ቆሞሱ
ኤጲስ ቆጶሱ ጳጳሱ
የቴውሎጅው ተመራቂ
የምሥጢራቱ አርቃቂ
ሰንበት ተማሪው ማሕበራቱ
ማሕበረ ቅዱሳን ባለሕጉ
ደጆችሽ አይዘጉ
ኦረቶዶክሳዊ በሙሉ
ተማማለህ በመስቀሉ
ጠብቅ ያንተን አደራ
እንዳትሽሽ አንዳትፈራ
እንደበግ ጨው እያላሱ
እያሳሳቁ እያወደሱ
እያጠጋጉን ወደነሱ
ደሮን በጥሬ እንዲጥሉ
ሊበሉን እያታለሉ
ማዕዳቼውን ሊያቀርቡ
በደማችን ከታጠቡ
ይበቃል ከዚህ በላይ
ማን አታላይ ማን ተታላይ
ማንስ አግላይ ማን ተገላይ
ማን ሆነና ባለርስቱ
የሀገር መሠረቱ
የሀገር ፍቅርን እየመገብነ
እኛው አቅፈን ባሳደግነ
ከአውሮፖውያን ተልኮ
ከዓረብ ልጅ ልጁን ልኮ
እኛን እኛን ከገፋ
ድብቅ ሴራውን ካስፋፋ
አንተ ግን አደራ
እንዳትወሰልት እንዳትፈራ
ክርስቶስ የወለደህ
እስከሞት የወደደህ
በፍቅሩ ያሳደገህ
አንተንማ ምን አስፈራህ
ያምላክህ ስራ የተጻፈ
ሞትን በሞት ያሸነፈ
ሰይፍ አትሻ የገዘፈ
ሰይፍ አለህ የረቀቀ
ጎልያድን ያወደቀ
ሰይፍ አለን ባንገታችን
ማተባችን መስቀላችን
ሰይፍ አለን በእጃችን
ዳዊታችን ድርሳናችን
እንጠብቅ አደራችችን።
ጸልዩ በእንቲያነ ስለኛ ጸልዩ ።
አቡነ ናትናኤል አቡነ ፊሊጶስ
አቡነ አረጋዊ አባ መርሓ ክርስቶስ
አባ መልከ ጼዴቅ ወአባ ሰላማ
አቡነ አረጋዊ አቡነ ገሪማ
በአንድነት ሁናችሁ በገነት ከተማ
ስለኛ ጸልዩ ድምፃችሁ ይሰማ፡
ኦርቶዶክሳውያን እንደበግ ታርደዋል
አብያተ ክርስቲያን በእሳት ተቃጥለዋል
ቅዱሳት ንዋያት እንደጧፍ ነደዋል
ክርስቲያኖች ሁሉ ለመኖር ሰግተዋል
በግፈኞች ሰይፍ ተከበው ቁመዋል
ሱማሌ ጅግጅጋ ጅማና ሲዳማ
መለውና ጎፋ ያገሬ ከተማ
ኦርቶዶክሳውያን እየተሰደዱ
ካህናት ሊቃውንት እየተዋረዱ
ቅዱሳን ቦታዎች እየተነጠቁ
ምእመናን ካህናት እየተጨነቁ
እጅግ ስለበዛ ግፉና ስቃዩ
አሳስቡን ከጌታ ስለኛ ጸልዩ
➴ ከመምህር ኤፍሬም ተስፋ
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem
👍22❤7🥰3
፨ጊዜዬን ባርክልኝ፨
በዝናብ አብቅለህ በፀሐይ አብስለህ
የምትመግብ ጌታ ሁሉን አዘጋጅተህ
ነጻነቱን ሰጥተህ ጥበቡን አድለህ
እዚህ ላደረስከኝ ምስጋና ይድረስህ
ሁሌም ጠብቀኸኝ በምሕረት ጥላ
ጊዜን ባርክልኝ ሰርቼ እንድበላ
ከፍጥረታት ሁሉ አልቀህ ፈጥረኸኝ
የጸጋን ገዢነት በፍቅርህ አድለኸኝ
ከቤትህ እንድኖር ርስትአውረሰኸኝ
ለዚህ ያበቃህኝ ከቶ እኔ ማነኝ
ያለኝ ምስጋና ነው አምላክ ክበርልኝ
እኔ ስበድልህ አንተ ስትምረኝ
በምሕረት ታግለህ ፈጥነህ ሳታጠፋኝ
ንስሐ እንድገባ ጊዜን ባርክልኝ።
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem
በዝናብ አብቅለህ በፀሐይ አብስለህ
የምትመግብ ጌታ ሁሉን አዘጋጅተህ
ነጻነቱን ሰጥተህ ጥበቡን አድለህ
እዚህ ላደረስከኝ ምስጋና ይድረስህ
ሁሌም ጠብቀኸኝ በምሕረት ጥላ
ጊዜን ባርክልኝ ሰርቼ እንድበላ
ከፍጥረታት ሁሉ አልቀህ ፈጥረኸኝ
የጸጋን ገዢነት በፍቅርህ አድለኸኝ
ከቤትህ እንድኖር ርስትአውረሰኸኝ
ለዚህ ያበቃህኝ ከቶ እኔ ማነኝ
ያለኝ ምስጋና ነው አምላክ ክበርልኝ
እኔ ስበድልህ አንተ ስትምረኝ
በምሕረት ታግለህ ፈጥነህ ሳታጠፋኝ
ንስሐ እንድገባ ጊዜን ባርክልኝ።
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem
👍5❤2