የእሳት ትንታግ ፍንጣሪ
የድል ዜማ ወገን አኩሪ
የክብር ጥግ ማማ
የደስታ ውበት ቄጤማ
የመስቀሉን ሀይል ከግሽን የጠበሉን በረከት ዘግና
ይኸው አየኋት በለንደን የእሳት ልጅ እሳት ሆና
የደም አዙሪት ምሬቱ
የእሳት ትግል ሽረቱ
እየፈላባት አሞቷ እየታገላት ሲቃ
ታቦቷን ከራሷ ሳይሆን ከደረቷ ላይ ደብቃ
ተሻገረችው ያን ጉድ አስለቀሰችን ነፍርቃ
ጀመረች አግዢኝ ብላ
ድንግልን በደረቷ አዝላ
ታሪክ ናት ይህች ማሪያም ለተማፀናት በብርቱ
ልጇን ላመነ በልቡ ፍቅሯን ላሰረ በአንገቱ
ረሳችውና ድካሟን የልፋት ውጤት ወርቋን
ከፍ አደረገች በሥዕሏ የድንግልን ማሪያምን ስሟን
ግሸን ሆነች አሉ ለንደን ተቀይራ
መሰረተ ሕይወት ድንግል ተዘምራ
እምነት ከጉያ ውስጥ ድንገት ፈለቀና
ሃሌ ሃሌ ሆነ ድካም ተረሳና
የእኛ እርግብ አማኝቷ
የኢትዮጵያ ልጅ መሰረቷ
ቢላላባት ያሰረችው ቢበጣጠስ መቀነቷ
ተወራርዳ አሸነፈች በጌታ እናት በአዛኚቷ
➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖
በቀሲስ ማሞ በዕለቱ የተፃፈ
@Mgetem
@Mgetem
@Bahraan
የድል ዜማ ወገን አኩሪ
የክብር ጥግ ማማ
የደስታ ውበት ቄጤማ
የመስቀሉን ሀይል ከግሽን የጠበሉን በረከት ዘግና
ይኸው አየኋት በለንደን የእሳት ልጅ እሳት ሆና
የደም አዙሪት ምሬቱ
የእሳት ትግል ሽረቱ
እየፈላባት አሞቷ እየታገላት ሲቃ
ታቦቷን ከራሷ ሳይሆን ከደረቷ ላይ ደብቃ
ተሻገረችው ያን ጉድ አስለቀሰችን ነፍርቃ
ጀመረች አግዢኝ ብላ
ድንግልን በደረቷ አዝላ
ታሪክ ናት ይህች ማሪያም ለተማፀናት በብርቱ
ልጇን ላመነ በልቡ ፍቅሯን ላሰረ በአንገቱ
ረሳችውና ድካሟን የልፋት ውጤት ወርቋን
ከፍ አደረገች በሥዕሏ የድንግልን ማሪያምን ስሟን
ግሸን ሆነች አሉ ለንደን ተቀይራ
መሰረተ ሕይወት ድንግል ተዘምራ
እምነት ከጉያ ውስጥ ድንገት ፈለቀና
ሃሌ ሃሌ ሆነ ድካም ተረሳና
የእኛ እርግብ አማኝቷ
የኢትዮጵያ ልጅ መሰረቷ
ቢላላባት ያሰረችው ቢበጣጠስ መቀነቷ
ተወራርዳ አሸነፈች በጌታ እናት በአዛኚቷ
➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖
በቀሲስ ማሞ በዕለቱ የተፃፈ
@Mgetem
@Mgetem
@Bahraan
👍2❤1
#የታወረ_ትውልድ
@Mgetem
ከእናቱ አፈንግጦ እምነት ወዲያ ብሎ በአለም የታለለ
በዚህ በእኔ ዘመን ልበ ስውር ወጣት እጂግ ብዙ አለ
ዶግማና ቀኖና መፈፀም ሲያቅተው በስጋው ሲታለል
ይችን ቅድስት እምነት መፍትሄ ነው ብሎ ትታደስ ይላታል
የመለውጥ ትርጉም ጠንቅቆ ያልገባው ልበ ስውር ጓዴ
በኃጢያት ያደፈ እሱነቱን ይዞ ትታደስ ይለኛል ያላረጀ ነገር ይታደሳል እንዴ?
እነዲዎስቆሮስ ፂም የተነጩላት የፀናች ሀይማኖት
ቆዳቸው እንደ ድንች በአህዛብ ጭካኔ ያኔ የተላጡላት
በሚያስፈራ እሳት ነጎድጓድ በላበት
ለኛ ያቆዩልን ህይወትን ሰውተው
ተዋህዶ እምነቴ ምኗ ነው ያረጀው
በሀጥያት አረንቋ የተቆሳቆለ እርሱ ተቀምጦ
ፍርሀት እንኳን አያውቅ ትታደስ ይለኛል ካፉ ቃል አውጥቶ
መላ በሉት'ማ ምከሩት ይህን ስው
የመታደስ ትርጉም ምን አልባት ቢገባው!!!የናቁሽ ሁሉ ወደ እግርሽ ጫማ ይበረከካሉ
ያከበሩሽም የከበሩ ናቸው
ማሪያምን የጠላ የለውም ከለላ
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem
ከእናቱ አፈንግጦ እምነት ወዲያ ብሎ በአለም የታለለ
በዚህ በእኔ ዘመን ልበ ስውር ወጣት እጂግ ብዙ አለ
ዶግማና ቀኖና መፈፀም ሲያቅተው በስጋው ሲታለል
ይችን ቅድስት እምነት መፍትሄ ነው ብሎ ትታደስ ይላታል
የመለውጥ ትርጉም ጠንቅቆ ያልገባው ልበ ስውር ጓዴ
በኃጢያት ያደፈ እሱነቱን ይዞ ትታደስ ይለኛል ያላረጀ ነገር ይታደሳል እንዴ?
እነዲዎስቆሮስ ፂም የተነጩላት የፀናች ሀይማኖት
ቆዳቸው እንደ ድንች በአህዛብ ጭካኔ ያኔ የተላጡላት
በሚያስፈራ እሳት ነጎድጓድ በላበት
ለኛ ያቆዩልን ህይወትን ሰውተው
ተዋህዶ እምነቴ ምኗ ነው ያረጀው
በሀጥያት አረንቋ የተቆሳቆለ እርሱ ተቀምጦ
ፍርሀት እንኳን አያውቅ ትታደስ ይለኛል ካፉ ቃል አውጥቶ
መላ በሉት'ማ ምከሩት ይህን ስው
የመታደስ ትርጉም ምን አልባት ቢገባው!!!የናቁሽ ሁሉ ወደ እግርሽ ጫማ ይበረከካሉ
ያከበሩሽም የከበሩ ናቸው
ማሪያምን የጠላ የለውም ከለላ
@Mgetem
@Mgetem
👍1
መንፈሳዊ ግጥም ብቻ via @like
ውድ የመንፈሳዊ ግጥም ብቻ ቻናላችን ተከታታዮች አብራችሁን ስለሆናችሁ እናመሰግናለን፡፡ 🙏🙏
🖼አዲስ ፕሮፋይል....
#Profile_design Credit to
Sc graphics 📩 @Scgpx
🖼አዲስ ፕሮፋይል....
#Profile_design Credit to
Sc graphics 📩 @Scgpx
#ሁሉም_በምክንያት_ነው
@Mgetem
ለስራ ሲሄዱ አባት ከልጁ ጋር
ሲደክማቸው አረፉ በአንድ የሾላ ዛፍ ስር
ትንሽም ሳይቆዩ ልጅየው ለማረፍ መሬት ላይ ተንጋሎ
አባቱን አላቸው የሾላውን ፍሬ በደንቡ አስተውሎ
አባቴ ተመልከት አምላክ ግን ሞኝ ነው
እንዴት ባክህ ልጄ ምን እያልከኝ ነው
ይህንን በሚያህል ትልቅ ዛፍ
የጥበቡን ስራ ሲያሳርፍ
እፍኝ የማይሞላ ትንሽዬ ፍሬ እንዲያፈራ ፈጥሮ
ግን ለአቅመ ቢሱ ዱባ ትልቅ ፍሬን ፈጥሮ ታዲያ ሞኝ አይደለም ብሎ ሳይጨርሰው
አባት ጣልቃ ገብቶ ልጁን አቋረጠው
አምላክ አላማ አለው ሲፈጥረው6 ሁሉንም በም/ክ ነው እንጂ በአጋጣሚ አይደለም
መቼም እንዳትገባ በፈጣሪ ስራ
ከዛሬ በኋላ እንዲህም አታውራ
ቢሆንም አባቴ አምላክ ልክ አይደለም
ብሎ ተናገረ ሳያስበው ምንም
ትክክል መሆኑን ሊያስረዳ ሲቃጣው
አንዲት ፍሬ ወድቃ ግንባሩን መታችው
አባትም አየና ይናገር ጀመረ
አልሰማም አልክ እንጂ ነግሬህ ነበረ
ልክ አንተ እንዳልከው ይሄ የሾላ ፍሬ ዱባን ቢያክል ኖሮ
ዛሬ ሞተህ ነበር አብቅቶልህ ኑሮ
ስለዚህ አትግባ በሱ ስራ ድንገት
ምክንያቱ ከገባህ ይከተላል ቅጣት
➴
ከሰላማዊት ጌቱ
@Mgetem
@Mgetem
@MENFESAWItsufoche
@Mgetem
ለስራ ሲሄዱ አባት ከልጁ ጋር
ሲደክማቸው አረፉ በአንድ የሾላ ዛፍ ስር
ትንሽም ሳይቆዩ ልጅየው ለማረፍ መሬት ላይ ተንጋሎ
አባቱን አላቸው የሾላውን ፍሬ በደንቡ አስተውሎ
አባቴ ተመልከት አምላክ ግን ሞኝ ነው
እንዴት ባክህ ልጄ ምን እያልከኝ ነው
ይህንን በሚያህል ትልቅ ዛፍ
የጥበቡን ስራ ሲያሳርፍ
እፍኝ የማይሞላ ትንሽዬ ፍሬ እንዲያፈራ ፈጥሮ
ግን ለአቅመ ቢሱ ዱባ ትልቅ ፍሬን ፈጥሮ ታዲያ ሞኝ አይደለም ብሎ ሳይጨርሰው
አባት ጣልቃ ገብቶ ልጁን አቋረጠው
አምላክ አላማ አለው ሲፈጥረው6 ሁሉንም በም/ክ ነው እንጂ በአጋጣሚ አይደለም
መቼም እንዳትገባ በፈጣሪ ስራ
ከዛሬ በኋላ እንዲህም አታውራ
ቢሆንም አባቴ አምላክ ልክ አይደለም
ብሎ ተናገረ ሳያስበው ምንም
ትክክል መሆኑን ሊያስረዳ ሲቃጣው
አንዲት ፍሬ ወድቃ ግንባሩን መታችው
አባትም አየና ይናገር ጀመረ
አልሰማም አልክ እንጂ ነግሬህ ነበረ
ልክ አንተ እንዳልከው ይሄ የሾላ ፍሬ ዱባን ቢያክል ኖሮ
ዛሬ ሞተህ ነበር አብቅቶልህ ኑሮ
ስለዚህ አትግባ በሱ ስራ ድንገት
ምክንያቱ ከገባህ ይከተላል ቅጣት
➴
ከሰላማዊት ጌቱ
@Mgetem
@Mgetem
@MENFESAWItsufoche
👍5❤3
#አልችልም_አስችለኝ
@Mgetem
እየደነገጠ እየፈራ ልቤ
አንድነት አቅቶት ቅጥልጥል ሃሳቤ
ኮሽ ባለ ቁጥር እየፈራች ነፍሴ
አስጨንቀዋለሁ ራሴን በራሴ
አይኖቼ ተስፋዬን ማየት ተስኗቸው
እግሮቼ ጉዞዬን መጓዝ አቅቷቸው
ይቅበዘበዛሉ መሪ ጠፍቶባቸው
ዝም ባለ ጎጆ ጭጭ ባለ ሌሊት
ጩኸት ይሰማኛል ምንም በሌለበት
የሚያሳርፍ ጌታ እንዳለኝ ይወቀው
የሚያስጨንቀኝን አምላኬ አስጨንቀው
አንተ ድረስና የጭንቄን ውል ፍታ
አልችልም አስችለኝ እንዳልጠፋ ጌታ !
🔶🔷🔶🔷🔸🔹🔸🔹🔶🔷🔶
@Mgetem
@Mgetem
@Menfesawi_getem_bot
@Mgetem
እየደነገጠ እየፈራ ልቤ
አንድነት አቅቶት ቅጥልጥል ሃሳቤ
ኮሽ ባለ ቁጥር እየፈራች ነፍሴ
አስጨንቀዋለሁ ራሴን በራሴ
አይኖቼ ተስፋዬን ማየት ተስኗቸው
እግሮቼ ጉዞዬን መጓዝ አቅቷቸው
ይቅበዘበዛሉ መሪ ጠፍቶባቸው
ዝም ባለ ጎጆ ጭጭ ባለ ሌሊት
ጩኸት ይሰማኛል ምንም በሌለበት
የሚያሳርፍ ጌታ እንዳለኝ ይወቀው
የሚያስጨንቀኝን አምላኬ አስጨንቀው
አንተ ድረስና የጭንቄን ውል ፍታ
አልችልም አስችለኝ እንዳልጠፋ ጌታ !
🔶🔷🔶🔷🔸🔹🔸🔹🔶🔷🔶
@Mgetem
@Mgetem
@Menfesawi_getem_bot
#ፍቅር_ማለት
@Mgetem
#ያን_ሁሉ መስዋእት ያን ሁሉ ግርፋት
#ልጅን_ከአባት ጋር አባትን ከልጅ ጋር
አስታርቆ ለማየት ፤
እኔ ያያ ሰው ነኝ የከበረ ዋጋ የተከፈለበት
እኔ ያ. ሰው ነኝ #በደሙ_ታጥቤ
ነፃ የሆንኩበት ፤
ታድያ ለዚህ ከንቱ አለም ላልወደደው
በትንሽነቱ ሰው ሁሉ ለናቀው ፤
እንዴትስ ተገብቶት ጌታ ሊሞትለት
እንዴትስ ተደርጎ ክብሩን ሊተውለት ፤
#ይህ_ፍጡር ማን ቢሆን ነው ከቶ
#የሰማዩን_ንጉስ ግዛቱን አስትቶ
በሀጥያቷ ክርፋት ወደ ገማች ምድር
ጠርቶና ጎትቶ ፤
#ሞትን_ያቀመሰው የትኛው ፍቅር ነው
#የቱ ቅድስና የቱ ማንነቴ የቱ ንፅህና ፤
#ንፁህ_የሆነውን ፅድቅ የለበሰውን
ስጋ ያለበሰው ሀጥያት ያደረገው
የቱ እኔነቴ እሱነቱን ትቶ እንዲያ
ሚያዋርደው ? ፤
#ያንን_ፍቅርማ ቃላት ተቆፍረው
#ያንን_መውደድማ ፊደላት ተጣምረው ፤
#ከቶ አይገልፁትም ፍፁም አይደርሱትም
ብርሀን አያደምቀው ጨለማ አይጋርደው
የቀናት መገስገስ የአመታት መንጎድ
ዘመን የማይሽረው ፤
#ፍ ቅ ር ማለት ያ ያ ነው
#ፍቅር_ውልደቱ ነው ፍቅር መከራው ነው
#ፍቅር_መሞቱ_ነው ፍቅር ትንሳኤው ነው ፤
በዘመን ጅማሬ በዘመን ፍፃሜም
የፍቅር ስንኙ የፍቅር ሀረጉ
እ የ ሱ ስ ብቻ ነው !
__________________________
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem
#ያን_ሁሉ መስዋእት ያን ሁሉ ግርፋት
#ልጅን_ከአባት ጋር አባትን ከልጅ ጋር
አስታርቆ ለማየት ፤
እኔ ያያ ሰው ነኝ የከበረ ዋጋ የተከፈለበት
እኔ ያ. ሰው ነኝ #በደሙ_ታጥቤ
ነፃ የሆንኩበት ፤
ታድያ ለዚህ ከንቱ አለም ላልወደደው
በትንሽነቱ ሰው ሁሉ ለናቀው ፤
እንዴትስ ተገብቶት ጌታ ሊሞትለት
እንዴትስ ተደርጎ ክብሩን ሊተውለት ፤
#ይህ_ፍጡር ማን ቢሆን ነው ከቶ
#የሰማዩን_ንጉስ ግዛቱን አስትቶ
በሀጥያቷ ክርፋት ወደ ገማች ምድር
ጠርቶና ጎትቶ ፤
#ሞትን_ያቀመሰው የትኛው ፍቅር ነው
#የቱ ቅድስና የቱ ማንነቴ የቱ ንፅህና ፤
#ንፁህ_የሆነውን ፅድቅ የለበሰውን
ስጋ ያለበሰው ሀጥያት ያደረገው
የቱ እኔነቴ እሱነቱን ትቶ እንዲያ
ሚያዋርደው ? ፤
#ያንን_ፍቅርማ ቃላት ተቆፍረው
#ያንን_መውደድማ ፊደላት ተጣምረው ፤
#ከቶ አይገልፁትም ፍፁም አይደርሱትም
ብርሀን አያደምቀው ጨለማ አይጋርደው
የቀናት መገስገስ የአመታት መንጎድ
ዘመን የማይሽረው ፤
#ፍ ቅ ር ማለት ያ ያ ነው
#ፍቅር_ውልደቱ ነው ፍቅር መከራው ነው
#ፍቅር_መሞቱ_ነው ፍቅር ትንሳኤው ነው ፤
በዘመን ጅማሬ በዘመን ፍፃሜም
የፍቅር ስንኙ የፍቅር ሀረጉ
እ የ ሱ ስ ብቻ ነው !
__________________________
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem
👍11❤2
Forwarded from Daregot Media
daregot magazine vol 5 for mobile.pdf
4.5 MB
የዳረጎት መጽሔት አምስተኛ እትም።
አስተያየት በመስጠት፥ ለሌሎች በማጋራት የአገልግሎት ድርሻዎን ይወጡ። መልካም ንባብ
አስተያየት በመስጠት፥ ለሌሎች በማጋራት የአገልግሎት ድርሻዎን ይወጡ። መልካም ንባብ
#ፍልሰታ
@Mgetem
ትፈራው ነበረ ያን መልአከሞት
የልጅሽን ፅዋ ቅመሽው አላት
ይጠፋል ኩነኔ ይጠፋል አበሳ
እንደ ፈጣሪያችን ማርያም ስትነሳ
እየባረከቻት ኢትዮጵያን በእጆቿ
በይባቤ አረገች እሷም እንደ ልጇ
ከሰው የተለየች መሆኗን ሲያበስር
ሞት በጥር ሆነ ነሃሴ መቃብር
አይሁዳዊው ቀንቶ ሲሰርቅ ሥጋዋን
የመለኮቱ ሰይፍ ቆርጠው እጁን
ብዙው ይጾመዋል የፍልሰታን ፆም
ከእህል ተከልክሎ ከሥጋ ከደም
ሐዋርያው ፊሊጶስ ትንሣኤዋን ሲሻ
ከወንድሞቹ ጋር ዕርገቷንም ሲሻ
በስሟ ተነሱ ሊፆሙ በጋራ።
የበረከት ፆም ያድርግልን!
@Mgetem
@Mgetem
@Ask_Boa_Bot
@Mgetem
ትፈራው ነበረ ያን መልአከሞት
የልጅሽን ፅዋ ቅመሽው አላት
ይጠፋል ኩነኔ ይጠፋል አበሳ
እንደ ፈጣሪያችን ማርያም ስትነሳ
እየባረከቻት ኢትዮጵያን በእጆቿ
በይባቤ አረገች እሷም እንደ ልጇ
ከሰው የተለየች መሆኗን ሲያበስር
ሞት በጥር ሆነ ነሃሴ መቃብር
አይሁዳዊው ቀንቶ ሲሰርቅ ሥጋዋን
የመለኮቱ ሰይፍ ቆርጠው እጁን
ብዙው ይጾመዋል የፍልሰታን ፆም
ከእህል ተከልክሎ ከሥጋ ከደም
ሐዋርያው ፊሊጶስ ትንሣኤዋን ሲሻ
ከወንድሞቹ ጋር ዕርገቷንም ሲሻ
በስሟ ተነሱ ሊፆሙ በጋራ።
የበረከት ፆም ያድርግልን!
@Mgetem
@Mgetem
@Ask_Boa_Bot
❤3👍3
#ፆመኛ_ነኝ!
@Mgetem
ከምግብ እርቄ
ሰዓቷን ጠንቅቄ
ሥርዓት አከብራለሁ
ከሥጋ ከወተት ንክች አላደርግም በደንብ እጾማለሁ
በእርግጥ ወዳፍ ሚገባ ነውና የማያረክስው
ጾምን ባልበላበት ሰዶቤበታለሁ
እጄ ሥጋም ባይዝ ሰውን ይጠቁማል
ሰው ይወነጅላል
እግሬ አመድ ሆኖበቅቤ ባዮወዛም
ወደ ጥፋት መንገድ መሮጡ አልቀረም
የውስጡ አካሌ ያ ድብቁ ነገር
ያ የልቤ ወዳጄ ቅቤና ቅባቱ
አልፎ ባይነካካው እዚያ ተደብቆ
ሰዎች ላይ ለማሴር
ክፋት ለማውጠንጠን
እንደምን ይሳነው!
አዎን ይሄ ሳይቆጠር
በርግጥ እጾማለሁ
ነጠላ አድርጌ
ቅዳሴ አስቀድሼ
በአንድ እግሬ ቆሜ
ጸሎት አደርሳለሁ
አዎን ጾመኛ ነኝ
በደንብ አከፍላለሁ
ሩጫዬን ያለግብ እደመድማለሁ።
@Mgetem
@Mgetem
@MENFESAWItsufoche
@Mgetem
ከምግብ እርቄ
ሰዓቷን ጠንቅቄ
ሥርዓት አከብራለሁ
ከሥጋ ከወተት ንክች አላደርግም በደንብ እጾማለሁ
በእርግጥ ወዳፍ ሚገባ ነውና የማያረክስው
ጾምን ባልበላበት ሰዶቤበታለሁ
እጄ ሥጋም ባይዝ ሰውን ይጠቁማል
ሰው ይወነጅላል
እግሬ አመድ ሆኖበቅቤ ባዮወዛም
ወደ ጥፋት መንገድ መሮጡ አልቀረም
የውስጡ አካሌ ያ ድብቁ ነገር
ያ የልቤ ወዳጄ ቅቤና ቅባቱ
አልፎ ባይነካካው እዚያ ተደብቆ
ሰዎች ላይ ለማሴር
ክፋት ለማውጠንጠን
እንደምን ይሳነው!
አዎን ይሄ ሳይቆጠር
በርግጥ እጾማለሁ
ነጠላ አድርጌ
ቅዳሴ አስቀድሼ
በአንድ እግሬ ቆሜ
ጸሎት አደርሳለሁ
አዎን ጾመኛ ነኝ
በደንብ አከፍላለሁ
ሩጫዬን ያለግብ እደመድማለሁ።
@Mgetem
@Mgetem
@MENFESAWItsufoche
👍4❤2
#ተዋህዶ_አትፈርስም
@Mgetem
ድርጅት አይደለም በሰዉ የታነፀ፣
ፖለቲካም አይደል ዘርን ያጣቀሰ፣
ሚስጥሩ ፍቅር ነዉ ቃላት የማይበቃዉ፣
እኛን ስለመዉደድ በፍቅር ተስቦ መስቀል ላይ የወጣዉ።
በደም ታንፀናል በማይጠፋ ቀለም፣
ለእኛ ብሎ እርሱ ጌታ ቢሰቀልም፣
መሠረቱ ኢየሱስ ግድግዳዉ ቅዱሳን፣
ግንቦቹ እኛ ነን የእርሱ ምዕመናን።
ልንወድቅ አንችልም በእርሱ ፍቅር ፀንተን፣
እግዚአብሔርን ይዘን ማን ይሆን የሚከሰን?
መሃመዳዊያን ወይም ጅሆቫ ዊትነስ፣
ፕሮቴስታንትም ሁን ወይ ደግሞ ካቶሊክ
አለቱን ላታፈርስ የሰዉ ደም አታፍስስ፣
ምንጩንም ላታደርቅ ከመቅደሱ እራቅ።
ካህኑ ቢታረድ መቅደሱ ቢቃጠል፣
እንበዛለን እንጂ የለም የሚጎድል።
ስንሞት እንበዛለን መከራዉ ሲበዛ በፍቅር እንፀናለን፣
በእሳት ስንቃጠል እንለመልማለን።
ከማይደክም አባት ተፈጥረናልና፣
አርዮስ አትልፋ እንላለን ቀና።
ሰልፉ የእኛ ነዉ ድልም የእኛ ብቻ፣
እንደ አሸዋ የበዛን እስከዓለም ዳርቻ።
ካህኑን ግደሉ መቅደሱን አቃጥሉ፣
ቅጥሩንም አፍርሱ ልጆቹን በትኑ፣
እናንተ ስትጠፉ በገሀነም እሳት፣
ሰማዕታት በአባታቸዉ እቤት
ይሰበሰባሉ መንግስተ ሰማያት።
ይህ ነዉ ክርስትና የማይጠፋ ቀለም፣
በፍፁም ማይጨልም ሁሌ ሚሰጥ ብርሃን።
እናማ አርዮስ ቁርጥህን እወቀ፣
ድል ላታደርግ እንደዉ ራስህን አታስጨንቀዉ፣
ሃሰት እዉነትን መቼ ነዉ አሸንፎ የሚያቀዉ?
ባንድነት ተነሱ የእምነትን ሰይፍ ያዙ፣
በፍቅር ማርኩና የዲያቢሎስን ሴራ በእምነታችሁ ናዱ።
በእምነት እንሞላ በፅናት እንቁም በተስፋ እንዉጣ፣
ጠላት አፍሮ እንዲቀር መድረሻም እንዲያጣ።
የጦር ዕቃችሁን ልበሱ እንደ ካባ፣
ዘመቻዉን አፅኑት ቅድስቲቷ ምድር አርዮስ እንዳይገባ።
የጦር ሠልፍ አንሻም ቀስት አንወረዉርም፣
ደም እያፈሰስን እርሱ የፈጠረዉን እኛ አንገድልም።
ቀስትና ጦር ይዘን አንወጣም ዘመቻ፣
ጠጠርም አንለቅምም አሳዳጁን መምቻ።
መምቻው ክርስቶስ ነው የእሳት መዶሻ፣
ምሽጋችን ቅድስት የኃጥአን መሸሻ።
🔸🔸🔸🔸🔸🔸🔸🔸🔸🔸🔸🔸
@Mgetem
@Mgetem
@AskBoaBot
@Mgetem
ድርጅት አይደለም በሰዉ የታነፀ፣
ፖለቲካም አይደል ዘርን ያጣቀሰ፣
ሚስጥሩ ፍቅር ነዉ ቃላት የማይበቃዉ፣
እኛን ስለመዉደድ በፍቅር ተስቦ መስቀል ላይ የወጣዉ።
በደም ታንፀናል በማይጠፋ ቀለም፣
ለእኛ ብሎ እርሱ ጌታ ቢሰቀልም፣
መሠረቱ ኢየሱስ ግድግዳዉ ቅዱሳን፣
ግንቦቹ እኛ ነን የእርሱ ምዕመናን።
ልንወድቅ አንችልም በእርሱ ፍቅር ፀንተን፣
እግዚአብሔርን ይዘን ማን ይሆን የሚከሰን?
መሃመዳዊያን ወይም ጅሆቫ ዊትነስ፣
ፕሮቴስታንትም ሁን ወይ ደግሞ ካቶሊክ
አለቱን ላታፈርስ የሰዉ ደም አታፍስስ፣
ምንጩንም ላታደርቅ ከመቅደሱ እራቅ።
ካህኑ ቢታረድ መቅደሱ ቢቃጠል፣
እንበዛለን እንጂ የለም የሚጎድል።
ስንሞት እንበዛለን መከራዉ ሲበዛ በፍቅር እንፀናለን፣
በእሳት ስንቃጠል እንለመልማለን።
ከማይደክም አባት ተፈጥረናልና፣
አርዮስ አትልፋ እንላለን ቀና።
ሰልፉ የእኛ ነዉ ድልም የእኛ ብቻ፣
እንደ አሸዋ የበዛን እስከዓለም ዳርቻ።
ካህኑን ግደሉ መቅደሱን አቃጥሉ፣
ቅጥሩንም አፍርሱ ልጆቹን በትኑ፣
እናንተ ስትጠፉ በገሀነም እሳት፣
ሰማዕታት በአባታቸዉ እቤት
ይሰበሰባሉ መንግስተ ሰማያት።
ይህ ነዉ ክርስትና የማይጠፋ ቀለም፣
በፍፁም ማይጨልም ሁሌ ሚሰጥ ብርሃን።
እናማ አርዮስ ቁርጥህን እወቀ፣
ድል ላታደርግ እንደዉ ራስህን አታስጨንቀዉ፣
ሃሰት እዉነትን መቼ ነዉ አሸንፎ የሚያቀዉ?
ባንድነት ተነሱ የእምነትን ሰይፍ ያዙ፣
በፍቅር ማርኩና የዲያቢሎስን ሴራ በእምነታችሁ ናዱ።
በእምነት እንሞላ በፅናት እንቁም በተስፋ እንዉጣ፣
ጠላት አፍሮ እንዲቀር መድረሻም እንዲያጣ።
የጦር ዕቃችሁን ልበሱ እንደ ካባ፣
ዘመቻዉን አፅኑት ቅድስቲቷ ምድር አርዮስ እንዳይገባ።
የጦር ሠልፍ አንሻም ቀስት አንወረዉርም፣
ደም እያፈሰስን እርሱ የፈጠረዉን እኛ አንገድልም።
ቀስትና ጦር ይዘን አንወጣም ዘመቻ፣
ጠጠርም አንለቅምም አሳዳጁን መምቻ።
መምቻው ክርስቶስ ነው የእሳት መዶሻ፣
ምሽጋችን ቅድስት የኃጥአን መሸሻ።
🔸🔸🔸🔸🔸🔸🔸🔸🔸🔸🔸🔸
@Mgetem
@Mgetem
@AskBoaBot
❤4👍4
++ ልብሱ ዘመብረቅ ++
@Mgetem
ዲ/ን ከሣቴብርሃን ገ/ኢየሱስ
(ውርስ ትርጉም)
ሊቀ ነቢይ ሙሴ፤
ከሲና ሲመለስ ፥ሕጉን ተቀብሎ፤
ካ’ምላክ ተነጋግሮ፤
ብርሃነ ገጹ አንፀባርቆ ኖሮ፤
የሰናፍጭ ታህል ቅንጣተ ፀዳሉ፤
በፊቱ መሳሉ፤
አሮን ፣ እስራኤልን ፍጹም አስፈራቸው፤
ሊያዩትም አልቻሉ።
ስለዚህ ለመኑት፤
“ፊትህን በበፍታ ሸፍንልን” አሉት።
ዛሬ ግን ብርሃኑ እንደሙሴ ያይደለ፤
ቅንጣት ሳይሆን ምሉዕ፤
“የዓለም ብርሃን” ፣ “ፀሐይ” የተባለ፤
የሙሴ ፈጣሪ፤
በታቦር ተራራ ከሙሴ ጋር ሳለ፤
ብርሃነ መለኮት ክብሩን መመልከቱ፤
ከብዷቸው ሲወድቁ ፤
ከእርሱ ጋራ ያሉት ደቀ መዛሙርቱ፤
በምን ይሸፍነው?
ተለውጦ ፀሐይ የሆነውን ፊቱ’።
ምክንያቱማ ልብሱ ፤ ይሸፍናል ሲባል፤
ፀአዳም ከመሆን፤
ሊያዩ እስኪሳናቸው ፤
እንደ መብረቅ ባርቋል።
መነሻ ቅኔ፦ ሥላሴ
ዘመልአከ ብርሃን አድማሱ ጀንበሬ
ሰአልዎ ፡እስራኤል፤
ለሙሴ፡ ይትገልበብ ፡በሰንዱናት፤
ኅጠተ-ብርሃን ንስቲተ ፡በገጹ ፥
አመ ነጽሮተ ፈርሁ፤
ይእዜሰ እምኀበ -ኢኮነ፥ ብርሃኑ ከማሁ፤
እግዚአ- ሙሴ ክርስቶስ፥
ለዘሀለዉ ምስሌሁ፤
በምንት ይትገልበብ ፥ገጸ ዚአሁ?
እስመ -ከመ -መብረቅ በረቀ አልባሲሁ፤
እስከ ስዕኑ ነጽሮ ኪያሁ።
________________________
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem
ዲ/ን ከሣቴብርሃን ገ/ኢየሱስ
(ውርስ ትርጉም)
ሊቀ ነቢይ ሙሴ፤
ከሲና ሲመለስ ፥ሕጉን ተቀብሎ፤
ካ’ምላክ ተነጋግሮ፤
ብርሃነ ገጹ አንፀባርቆ ኖሮ፤
የሰናፍጭ ታህል ቅንጣተ ፀዳሉ፤
በፊቱ መሳሉ፤
አሮን ፣ እስራኤልን ፍጹም አስፈራቸው፤
ሊያዩትም አልቻሉ።
ስለዚህ ለመኑት፤
“ፊትህን በበፍታ ሸፍንልን” አሉት።
ዛሬ ግን ብርሃኑ እንደሙሴ ያይደለ፤
ቅንጣት ሳይሆን ምሉዕ፤
“የዓለም ብርሃን” ፣ “ፀሐይ” የተባለ፤
የሙሴ ፈጣሪ፤
በታቦር ተራራ ከሙሴ ጋር ሳለ፤
ብርሃነ መለኮት ክብሩን መመልከቱ፤
ከብዷቸው ሲወድቁ ፤
ከእርሱ ጋራ ያሉት ደቀ መዛሙርቱ፤
በምን ይሸፍነው?
ተለውጦ ፀሐይ የሆነውን ፊቱ’።
ምክንያቱማ ልብሱ ፤ ይሸፍናል ሲባል፤
ፀአዳም ከመሆን፤
ሊያዩ እስኪሳናቸው ፤
እንደ መብረቅ ባርቋል።
መነሻ ቅኔ፦ ሥላሴ
ዘመልአከ ብርሃን አድማሱ ጀንበሬ
ሰአልዎ ፡እስራኤል፤
ለሙሴ፡ ይትገልበብ ፡በሰንዱናት፤
ኅጠተ-ብርሃን ንስቲተ ፡በገጹ ፥
አመ ነጽሮተ ፈርሁ፤
ይእዜሰ እምኀበ -ኢኮነ፥ ብርሃኑ ከማሁ፤
እግዚአ- ሙሴ ክርስቶስ፥
ለዘሀለዉ ምስሌሁ፤
በምንት ይትገልበብ ፥ገጸ ዚአሁ?
እስመ -ከመ -መብረቅ በረቀ አልባሲሁ፤
እስከ ስዕኑ ነጽሮ ኪያሁ።
________________________
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem
👍4❤2
#ስውር_ቅኔ
@Mgetem
#የቤተ_ክርስትያን ደጅ ዕለት ተለት ስሜ
#በፆም_በፀሎት በስግደት ደክሜ
አምላኬን ለመንኩት
የሚያስፈልገኝን ዘርዝሬ ነገርኩት
የሚያስፈልገኝ ነገር ቢዘገይ ጊዜ
ነፈከኝ ብዬ በምሬት አንካሴ
#ፈጣሪን_ወጋሁት
#ልቡን_አደማሁት
#በስርዓት_አጥ_ምሬቴ
በአጉል እምነቴ
ልቡ ስለቆሰለ
#በደመና_መሀል ጌታዬ እንዲህ አለ
‹‹ ሁሉን የማቀው እኔ ሆኘ ሳለ
ነፈከኝ ለማለት ምነው ልቦናህ ቸኮለ
ዘርዝረህ የላከውን የልመና ፀሎት
ይመለከት ዘንድ ዐይኔ ተተከለ
የምትፈልገው እንጅ የሚያስፈልግህ አንድም እንደሌሌ
የታዘበው እጄ የጠየከኝን ከማድረግ ተከለከለ
ግና ልጄ አዕምሮህ በደንብ ካሰተዋለ
ባለማድረግ ውስጥም ታላቅ ማድረግ አለ>>
_________________________
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem
#የቤተ_ክርስትያን ደጅ ዕለት ተለት ስሜ
#በፆም_በፀሎት በስግደት ደክሜ
አምላኬን ለመንኩት
የሚያስፈልገኝን ዘርዝሬ ነገርኩት
የሚያስፈልገኝ ነገር ቢዘገይ ጊዜ
ነፈከኝ ብዬ በምሬት አንካሴ
#ፈጣሪን_ወጋሁት
#ልቡን_አደማሁት
#በስርዓት_አጥ_ምሬቴ
በአጉል እምነቴ
ልቡ ስለቆሰለ
#በደመና_መሀል ጌታዬ እንዲህ አለ
‹‹ ሁሉን የማቀው እኔ ሆኘ ሳለ
ነፈከኝ ለማለት ምነው ልቦናህ ቸኮለ
ዘርዝረህ የላከውን የልመና ፀሎት
ይመለከት ዘንድ ዐይኔ ተተከለ
የምትፈልገው እንጅ የሚያስፈልግህ አንድም እንደሌሌ
የታዘበው እጄ የጠየከኝን ከማድረግ ተከለከለ
ግና ልጄ አዕምሮህ በደንብ ካሰተዋለ
ባለማድረግ ውስጥም ታላቅ ማድረግ አለ>>
_________________________
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem
👍3
#ይህችን_ዓመት_ተወኝ 🌼
ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
@MGETEM
ከዓመት እስከ ዓመት - ፍሬን ሳላፈራ - ደረቅ እንደሆንኩኝ
በራድ ወይም ትኩስ - ሁለቱንም ሳልሆን - እንዲያው ለብ እንዳልኩኝ
አለሁኝ በቤትህ - ለሙን መሬትህን - እያጎሳቆልኩኝ
አውቃለሁ አምላኬ - ፍሬዬን ለመልቀም - እንዳመላለስኩህ
ዛሬም ሳላፈራ - እሾህን አብቅዬ - ደርቄ ጠበቅሁህ
ያልተደረገልኝ - ያላፈሰሰክብኝ - ያልሰጠኸኝ የለም
ነገር ግን ይህ ሁሉ - አላርምህ አለኝ - አልለየኝም ከዓለም
የማትሰለቸኝ ሆይ - ተነሥቼ እስክቆም - እባክህ ታገሠኝ
የእኔን ክፋት ተወው - መልአክህን ሰምተህ - ይህችን ዓመት ተወኝ!
አውቃለሁ ታውቃለህ - ቀጠሮን ሰጥቼ - እንደማላከብር
ብዙ ጊዜ አቅጄ - ብዙ ጊዜ ዝቼ - በወሬ እንደምቀር
‹ዘንድሮስ…!› እንዳልኩኝ - አምና ይሄን ጊዜ - ሰምተኸኝ ነበረ
ምንም ሳልለወጥ - ‹ዘንድሮዬ› አልፎ - በአዲስ ተቀየረ
ፍሬ የማይወጣኝ - እኔን በመኮትኮት - እጆችህ ደከሙ
እኔ ግን አለሁኝ - ዛሬም አልበቃኝም - በኃጢአት መታመሙ
የቃልህን ውኃ - በድንጋይ ልጅህ ላይ - ሳትታክት ስታፈስስ -
ዘመን ተቆጠረ
ወደ ልቤ ሳይሰርግ - ሕይወቴን ሳይለውጥ - እንዲያው ፈስሶ ቀረ
ቃልህን ጠግቤ - እያገሳሁት ነው - ሌሎች እስኪሰሙ
በቃልህ መኖር ግን - አልያዝህ አለኝ - ከበደኝ ቀለሙ
ብዙ ጥቅስ አገኘሁ - ከቅዱስ መጽሐፍህ - ገልጬ አይቼ
ከራሴ ላይ ብቻ - አንድ ጥቅስ አጣሁኝ - በበደል ተኝቼ
ውጤቴ ደካማ - ትምህርት የማይሠርጸኝ - ተማሪ ብሆንም
ይህችን ዓመት ተወኝ - ደግሞ ትንሽ ልማር - ታገሠኝ አሁንም!
እባክህ አልቆረጥ - በቅዱስ መሬትህ - ልቆይ ፍቀድልኝ
ያፈሩት ቅዱሳን - የፍሬያቸው ሽታ - መዓዛ እንዲደርሰኝ
የተሸከምከኝ ሆይ - ዛሬም ተሸከመኝ - አትሰልቸኝ አደራ
ማን ይታገሠኛል - ጠላት እየሆንኩት - አይሠሩ ስሠራ!
አታውጣኝ ከቤትህ - ብዙ ቦታ አልይዝም - ፍሬ ስለሌለኝ
ስፍራ የማያሻኝ - ቤት የማላጣብብ - ፍሬ አልባ በለስ ነኝ!
ቦታስ የሚይዙት - ባለ ምግባሮቹ - ቅዱሳንህ ናቸው
ልክ እንደ ዘንባባ - የተንዠረገገ - ተጋድሎ ጽድቃቸው!
ከሊባኖስ ዝግባ - እጅጉን የበዛ - ገድል ትሩፋታቸው!
እኔ አይደለሁም - ቦታስ የምትይዘው - የአንተው እናት ናት
ሥሮቿ በምድር - ጫፎቿ በሰማይ - ሲደርሱ ያየናት
ይሀችን ዓመት ተወኝ - ከሥርዋ እሆናለሁ - ባፈራ ምናልባት!..
ይህችን ዓመት ተወኝ - እባክህ አምላኬ - አንድ ዓመት ምንህ ናት
ሺህ ዓመት አንድ ቀን - አይደለም ወይ ለአንተ - ዓመት ኢምንት ናት!
ይሄ ዓመት አልፎ - ዳግም ‹ዓመት ሥጠኝ› - እስከምልህ ድረስ
እባክህን ጌታ - ይህችን ዓመት ተወኝ - የወጉን እንዳደርስ!
🌼🌸🌼🌸🌼🌸🌼🌸🌼🌸🌼🌸
@Mgetem
@Mgetem
@AlewROBOT
ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
@MGETEM
ከዓመት እስከ ዓመት - ፍሬን ሳላፈራ - ደረቅ እንደሆንኩኝ
በራድ ወይም ትኩስ - ሁለቱንም ሳልሆን - እንዲያው ለብ እንዳልኩኝ
አለሁኝ በቤትህ - ለሙን መሬትህን - እያጎሳቆልኩኝ
አውቃለሁ አምላኬ - ፍሬዬን ለመልቀም - እንዳመላለስኩህ
ዛሬም ሳላፈራ - እሾህን አብቅዬ - ደርቄ ጠበቅሁህ
ያልተደረገልኝ - ያላፈሰሰክብኝ - ያልሰጠኸኝ የለም
ነገር ግን ይህ ሁሉ - አላርምህ አለኝ - አልለየኝም ከዓለም
የማትሰለቸኝ ሆይ - ተነሥቼ እስክቆም - እባክህ ታገሠኝ
የእኔን ክፋት ተወው - መልአክህን ሰምተህ - ይህችን ዓመት ተወኝ!
አውቃለሁ ታውቃለህ - ቀጠሮን ሰጥቼ - እንደማላከብር
ብዙ ጊዜ አቅጄ - ብዙ ጊዜ ዝቼ - በወሬ እንደምቀር
‹ዘንድሮስ…!› እንዳልኩኝ - አምና ይሄን ጊዜ - ሰምተኸኝ ነበረ
ምንም ሳልለወጥ - ‹ዘንድሮዬ› አልፎ - በአዲስ ተቀየረ
ፍሬ የማይወጣኝ - እኔን በመኮትኮት - እጆችህ ደከሙ
እኔ ግን አለሁኝ - ዛሬም አልበቃኝም - በኃጢአት መታመሙ
የቃልህን ውኃ - በድንጋይ ልጅህ ላይ - ሳትታክት ስታፈስስ -
ዘመን ተቆጠረ
ወደ ልቤ ሳይሰርግ - ሕይወቴን ሳይለውጥ - እንዲያው ፈስሶ ቀረ
ቃልህን ጠግቤ - እያገሳሁት ነው - ሌሎች እስኪሰሙ
በቃልህ መኖር ግን - አልያዝህ አለኝ - ከበደኝ ቀለሙ
ብዙ ጥቅስ አገኘሁ - ከቅዱስ መጽሐፍህ - ገልጬ አይቼ
ከራሴ ላይ ብቻ - አንድ ጥቅስ አጣሁኝ - በበደል ተኝቼ
ውጤቴ ደካማ - ትምህርት የማይሠርጸኝ - ተማሪ ብሆንም
ይህችን ዓመት ተወኝ - ደግሞ ትንሽ ልማር - ታገሠኝ አሁንም!
እባክህ አልቆረጥ - በቅዱስ መሬትህ - ልቆይ ፍቀድልኝ
ያፈሩት ቅዱሳን - የፍሬያቸው ሽታ - መዓዛ እንዲደርሰኝ
የተሸከምከኝ ሆይ - ዛሬም ተሸከመኝ - አትሰልቸኝ አደራ
ማን ይታገሠኛል - ጠላት እየሆንኩት - አይሠሩ ስሠራ!
አታውጣኝ ከቤትህ - ብዙ ቦታ አልይዝም - ፍሬ ስለሌለኝ
ስፍራ የማያሻኝ - ቤት የማላጣብብ - ፍሬ አልባ በለስ ነኝ!
ቦታስ የሚይዙት - ባለ ምግባሮቹ - ቅዱሳንህ ናቸው
ልክ እንደ ዘንባባ - የተንዠረገገ - ተጋድሎ ጽድቃቸው!
ከሊባኖስ ዝግባ - እጅጉን የበዛ - ገድል ትሩፋታቸው!
እኔ አይደለሁም - ቦታስ የምትይዘው - የአንተው እናት ናት
ሥሮቿ በምድር - ጫፎቿ በሰማይ - ሲደርሱ ያየናት
ይሀችን ዓመት ተወኝ - ከሥርዋ እሆናለሁ - ባፈራ ምናልባት!..
ይህችን ዓመት ተወኝ - እባክህ አምላኬ - አንድ ዓመት ምንህ ናት
ሺህ ዓመት አንድ ቀን - አይደለም ወይ ለአንተ - ዓመት ኢምንት ናት!
ይሄ ዓመት አልፎ - ዳግም ‹ዓመት ሥጠኝ› - እስከምልህ ድረስ
እባክህን ጌታ - ይህችን ዓመት ተወኝ - የወጉን እንዳደርስ!
🌼🌸🌼🌸🌼🌸🌼🌸🌼🌸🌼🌸
@Mgetem
@Mgetem
@AlewROBOT
👍7❤5
Forwarded from የorthodox መዝሙር ብቻ
🌼የእንቁጣጣሽ መዝሙር🌼
🌼🌼
እሰይ /ደስ ደስ ይበላችሁ/(፪)
ቅዱስ ሉቃስ መጣላችሁ
ደስ ደስ ይበላችሁ
ደስ ብሎን መጣን ደስ ብሎን(፪)ጌቶች አሉ ብለን
ደስ ብሎን መጣን ደስ ብሎን(፪)እሜቴ አሉ ብለን
አበባዮሽ 🌼 ለምለም አበባዮሽ 🌼 ለምለም
እንቆቅልሽ - - ንግሥት ልትፈትል ሄዳ - - ንግሥት
ንግስተ አዜብ - - ንግሥት እናት ማክዳ - - ንግሥት
በልቧ ያለውን - ንግሥት አጫወታቸው - - ንግሥት
አሰቀምጣ አበባ🌼 ንግሥት እያሳየችው - - ንግሥት
መአዛው የሚሸት - - ከሁለቱ የቱ ነው አለቸው - - ለንጉሥ
ንግስት ሆይ ለጥያቄሽ ጥበብ አለሽ(፪)
🌼የአገር አምባር የሚሆነው ከልብ ሽተሽ
እንቆቅልሹ - - የሳባ ከበድም ቢለው - -🌼 የሳባ
ጥበብ ሰላለው - - ንጉሡ ሚሥጥሩን ሊያውቀው - - ንጉሡ
ክፈት መስኮቱን - - ሰለሞን ቢለው ለሎሌው - -ሰለሞን
ገቡ ንቦቹ - - ሊቀስሙ🌼 ከአባባው አርፈው - - ሊቀስሙ
ብልህ ጠቢቡ - - መለሠ ለተጠየቀው - - በእውነት
ንጉስ ሰለሞን - - አለ አልተሠወረው 🌼 በእውነት
🌼አደይ ቅድስት ሀገሬ እልል በይ (፪)
🌼 ኢትዩዮጲያ የዝና ስሟ በዓለም ተሠማ (፪)
🌼
ለፈጣሪዋ - - ንግሥት ምስጋና አቅርባ - - ንግሥት
ኢትዮጲያዊቷ - - ንግሥት ንግስተ ሣባ 🌼 ንግሥት
ጥበቡን አይታ - - ንግሥት አደነቀችው - - ንግሥት
ወርቅ ሸቶውን - - ንግሥት ዕንቁ ሰጠችው - - ንግሥት
ንግስት ሆይ ምስክር ሆንሽ ለሀገርሽ (፪)🌼🌼
የአምላክን የፈጣሪያችን ስሙን ጠርተሽ (፪)🌼🌼
የኢትዮጵያ ሠዎች - -ለንግሥት ቆሙ በተራ - -ለንግሥት
እደጅ ሆነው 🌼 ለንግሥት ለዙፋን ክብሯ - - ለንግሥት
በመስከረም ወር - - ለንግሥት ሀገር ስትገባ - - ለንግሥት
ይዘው ሥጦታ - - ለንግሥት የፈካ አበባ 🌼ለንግሥት
🌼አደይ የብርሃን ጮራ በኢትዮጵያ በራ (፪)🌼🌼
🌼ኢትዮጲያ በታሪክሽ ጥንታዊት ነሽ (፪)🌼🌼
ኢየሩሳሌም - - ንግሥት ደርሠሽ መጣሽ - - ንግሥት
እንኳን በክብር - - ንግሥት ለዚህ አበቃሽ - - ንግሥት
ከአምላክ በረከት - - ንግሥት ፍሬ አግኝተሽ - - ንግሥት
የዘሽ ስጦታ - - ንግሥት ዕንቁ ለጣጣሽ - - ንግሥት
🌼ንግስት ሆይ ለታሪክሽ ክብር አለሽ (፪)🌼🌼
🌼ልጆችሽ አበባዮሽ እያልን እናስታውስሽ (፪)🌼🌼
🌼የአባቶች ተስፋ - - ለፃድቃን የነቢያት ትንቢት - - ለፅናት
የሙሴ ፅላት - - ለፀሎት የአሮን በትር - - ለፅናት
የዳዊት መንግስት - - ለፅናት ይዘሸ የመጣሽ - - ከጥንት
አምስቱን አውታር - - ለሠጠሽ ለሀገር መሠረት - በእውነት🌼🌼
🌼 አደይ ቅድስት ኢትዮጵያ እልል በይ (፪)🌼🌼
🌼ኢትዮጵያ በልጆችሽ ደስ ይበልሽ (፪)🌼🌼
በህገ ልቦና - - ህጉን ፈጣሪን አውቀሽ - - ህጉን
ህገ ነቢያትን - - ከዓለም ፈጥነሽ ተቀበልሽ - - ከዓለም
በብሉይ ኪዳን 🌼ለጌታ መስዋዕት አቅርበሽ - - ለጌታ
ተስፋ ካረጉት - - ከአይሁድ ከአስራኤል - - ከአይሁድ
ህገ ወንጌልን- -በፊት ይዘሽ ተገኘሽ 🌼 በፊት
🌼ኢትዮጵያ ደስ ይበልሽ ትልቅ ፀጋ አለሽ(፪)🌼🌼
🌼ስለፈፀምሽ ሦስቱን ህግጋት ለፈጣሪሽ (፪)🌼🌼
ካለፈው ሰህተት - - ሁላችን እንድንመለስ - - ሁላችን
አዲሱ ዓመት - - ለሁሉም መጣ ማቴዎስ- -ለሁሉም
ይህም ያልፍና - - በጊዜው ይመጣል ማርቆስ - - በጊዜው
ሌላው ይተካል - - በጊዜው ዘመነ ሉቃስ - - በጊዜው
ወልደነጓድጓድ - - በጊዜው 🌼 ሲደርስ ዮሐንስ - - በጊዜው
በየአራት ዓመት - - በጊዜው ለሁሉም ሲደርስ - - በጊዜው
በየዓመቱ - - መጥምቁ ቅዱስ ዩሐንስ - - በጊዜው🌼🌼
🌼አደይ የብርሃን ጮራ በዮሐንስ በራ(፪)🌼🌼
🌼 ኢትዮጵያ ባሕል ቋንቋሽ የሚያኮራሽ (፪)🌼🌼
ልጅ አበባ ልጅ አበባዬ አዬ ውዲቷ እናቴ
ልጅ አበባ እያለች እማማ አዬ ውዲቷ እናቴ
ምክሯን ሁሌ እኔ እንድሰማ አዬ ውዲቷ እናቴ
እያሻሸች እንድሆን ጤናማ አዬ ውዲቷ እማማ
አዬ ውዲቷ እናቴ (፪)
አበባ ለምለም ቀጤማ ለምለም
ኢትዮጵያ እንዳንቺ የለም (፪)
አብዬ ኧኸ ደግሞም እማምዬ
መጣሁ ለሰላምታ ከቤት አሉ ብዬ
እንኳን ለቅዱስ ዮሐንስ አደረሰዎት ብዬ (፪)
ይሸታል ዶሮ ዶሮ (፪) ከማምዬ ጓሮ (፪)
ይሸታል የወይን ጠጅ (፪) ከጋሽዬ ደጅ (፪)
ከበረው ይቆዩ ከብረው
አመት አወደ አመት ደርሰው
ቅን ታዛዥ ልጅን ወልደው
ትሁት ሰው አክባሪ ሆነው
የፍቅር ሸማን ለብሰው
ንስሐ ገብተው ቆርበው
ከብረው ይቆዩ ከብረው
❤@yeorthodoxmezmur💝
💝@yeorthodoxmezmur❤
💖@yeorthodoxmezmur💖
🌼🌼
እሰይ /ደስ ደስ ይበላችሁ/(፪)
ቅዱስ ሉቃስ መጣላችሁ
ደስ ደስ ይበላችሁ
ደስ ብሎን መጣን ደስ ብሎን(፪)ጌቶች አሉ ብለን
ደስ ብሎን መጣን ደስ ብሎን(፪)እሜቴ አሉ ብለን
አበባዮሽ 🌼 ለምለም አበባዮሽ 🌼 ለምለም
እንቆቅልሽ - - ንግሥት ልትፈትል ሄዳ - - ንግሥት
ንግስተ አዜብ - - ንግሥት እናት ማክዳ - - ንግሥት
በልቧ ያለውን - ንግሥት አጫወታቸው - - ንግሥት
አሰቀምጣ አበባ🌼 ንግሥት እያሳየችው - - ንግሥት
መአዛው የሚሸት - - ከሁለቱ የቱ ነው አለቸው - - ለንጉሥ
ንግስት ሆይ ለጥያቄሽ ጥበብ አለሽ(፪)
🌼የአገር አምባር የሚሆነው ከልብ ሽተሽ
እንቆቅልሹ - - የሳባ ከበድም ቢለው - -🌼 የሳባ
ጥበብ ሰላለው - - ንጉሡ ሚሥጥሩን ሊያውቀው - - ንጉሡ
ክፈት መስኮቱን - - ሰለሞን ቢለው ለሎሌው - -ሰለሞን
ገቡ ንቦቹ - - ሊቀስሙ🌼 ከአባባው አርፈው - - ሊቀስሙ
ብልህ ጠቢቡ - - መለሠ ለተጠየቀው - - በእውነት
ንጉስ ሰለሞን - - አለ አልተሠወረው 🌼 በእውነት
🌼አደይ ቅድስት ሀገሬ እልል በይ (፪)
🌼 ኢትዩዮጲያ የዝና ስሟ በዓለም ተሠማ (፪)
🌼
ለፈጣሪዋ - - ንግሥት ምስጋና አቅርባ - - ንግሥት
ኢትዮጲያዊቷ - - ንግሥት ንግስተ ሣባ 🌼 ንግሥት
ጥበቡን አይታ - - ንግሥት አደነቀችው - - ንግሥት
ወርቅ ሸቶውን - - ንግሥት ዕንቁ ሰጠችው - - ንግሥት
ንግስት ሆይ ምስክር ሆንሽ ለሀገርሽ (፪)🌼🌼
የአምላክን የፈጣሪያችን ስሙን ጠርተሽ (፪)🌼🌼
የኢትዮጵያ ሠዎች - -ለንግሥት ቆሙ በተራ - -ለንግሥት
እደጅ ሆነው 🌼 ለንግሥት ለዙፋን ክብሯ - - ለንግሥት
በመስከረም ወር - - ለንግሥት ሀገር ስትገባ - - ለንግሥት
ይዘው ሥጦታ - - ለንግሥት የፈካ አበባ 🌼ለንግሥት
🌼አደይ የብርሃን ጮራ በኢትዮጵያ በራ (፪)🌼🌼
🌼ኢትዮጲያ በታሪክሽ ጥንታዊት ነሽ (፪)🌼🌼
ኢየሩሳሌም - - ንግሥት ደርሠሽ መጣሽ - - ንግሥት
እንኳን በክብር - - ንግሥት ለዚህ አበቃሽ - - ንግሥት
ከአምላክ በረከት - - ንግሥት ፍሬ አግኝተሽ - - ንግሥት
የዘሽ ስጦታ - - ንግሥት ዕንቁ ለጣጣሽ - - ንግሥት
🌼ንግስት ሆይ ለታሪክሽ ክብር አለሽ (፪)🌼🌼
🌼ልጆችሽ አበባዮሽ እያልን እናስታውስሽ (፪)🌼🌼
🌼የአባቶች ተስፋ - - ለፃድቃን የነቢያት ትንቢት - - ለፅናት
የሙሴ ፅላት - - ለፀሎት የአሮን በትር - - ለፅናት
የዳዊት መንግስት - - ለፅናት ይዘሸ የመጣሽ - - ከጥንት
አምስቱን አውታር - - ለሠጠሽ ለሀገር መሠረት - በእውነት🌼🌼
🌼 አደይ ቅድስት ኢትዮጵያ እልል በይ (፪)🌼🌼
🌼ኢትዮጵያ በልጆችሽ ደስ ይበልሽ (፪)🌼🌼
በህገ ልቦና - - ህጉን ፈጣሪን አውቀሽ - - ህጉን
ህገ ነቢያትን - - ከዓለም ፈጥነሽ ተቀበልሽ - - ከዓለም
በብሉይ ኪዳን 🌼ለጌታ መስዋዕት አቅርበሽ - - ለጌታ
ተስፋ ካረጉት - - ከአይሁድ ከአስራኤል - - ከአይሁድ
ህገ ወንጌልን- -በፊት ይዘሽ ተገኘሽ 🌼 በፊት
🌼ኢትዮጵያ ደስ ይበልሽ ትልቅ ፀጋ አለሽ(፪)🌼🌼
🌼ስለፈፀምሽ ሦስቱን ህግጋት ለፈጣሪሽ (፪)🌼🌼
ካለፈው ሰህተት - - ሁላችን እንድንመለስ - - ሁላችን
አዲሱ ዓመት - - ለሁሉም መጣ ማቴዎስ- -ለሁሉም
ይህም ያልፍና - - በጊዜው ይመጣል ማርቆስ - - በጊዜው
ሌላው ይተካል - - በጊዜው ዘመነ ሉቃስ - - በጊዜው
ወልደነጓድጓድ - - በጊዜው 🌼 ሲደርስ ዮሐንስ - - በጊዜው
በየአራት ዓመት - - በጊዜው ለሁሉም ሲደርስ - - በጊዜው
በየዓመቱ - - መጥምቁ ቅዱስ ዩሐንስ - - በጊዜው🌼🌼
🌼አደይ የብርሃን ጮራ በዮሐንስ በራ(፪)🌼🌼
🌼 ኢትዮጵያ ባሕል ቋንቋሽ የሚያኮራሽ (፪)🌼🌼
ልጅ አበባ ልጅ አበባዬ አዬ ውዲቷ እናቴ
ልጅ አበባ እያለች እማማ አዬ ውዲቷ እናቴ
ምክሯን ሁሌ እኔ እንድሰማ አዬ ውዲቷ እናቴ
እያሻሸች እንድሆን ጤናማ አዬ ውዲቷ እማማ
አዬ ውዲቷ እናቴ (፪)
አበባ ለምለም ቀጤማ ለምለም
ኢትዮጵያ እንዳንቺ የለም (፪)
አብዬ ኧኸ ደግሞም እማምዬ
መጣሁ ለሰላምታ ከቤት አሉ ብዬ
እንኳን ለቅዱስ ዮሐንስ አደረሰዎት ብዬ (፪)
ይሸታል ዶሮ ዶሮ (፪) ከማምዬ ጓሮ (፪)
ይሸታል የወይን ጠጅ (፪) ከጋሽዬ ደጅ (፪)
ከበረው ይቆዩ ከብረው
አመት አወደ አመት ደርሰው
ቅን ታዛዥ ልጅን ወልደው
ትሁት ሰው አክባሪ ሆነው
የፍቅር ሸማን ለብሰው
ንስሐ ገብተው ቆርበው
ከብረው ይቆዩ ከብረው
❤@yeorthodoxmezmur💝
💝@yeorthodoxmezmur❤
💖@yeorthodoxmezmur💖
👍6❤1
#እሰይ_የምስራች
@Mgetem
እሰይ የምስራች ዘመን ተሻገርን
አምናን አሳልፎ ለዘንድሮ አበቃን
ይመስገን ፈጣሪ ለንስሀ ህይወት እድሜ ጨመረልን
አሁን ካካፈለን ከዚህ አዲስ አመት
ሳይሆን መዋተቱ ለስጋ ፍላጎት
ልክ እንደ አበቦቹ አፍርተን አሽተን
ደግሞ እንደ አዕዋፉቱ ለእርሱ ዘምረን
ዘመን ለንስሀ ዕድሜ ለፍስሀ አምላክ ካቀናጀን
ተመስገን እንበለው ምን አለ የሌለን
Nani girma
@Mgetem
@Mgetem
@Sulamatiz
እንኳን አደረሳችሁ
@Mgetem
እሰይ የምስራች ዘመን ተሻገርን
አምናን አሳልፎ ለዘንድሮ አበቃን
ይመስገን ፈጣሪ ለንስሀ ህይወት እድሜ ጨመረልን
አሁን ካካፈለን ከዚህ አዲስ አመት
ሳይሆን መዋተቱ ለስጋ ፍላጎት
ልክ እንደ አበቦቹ አፍርተን አሽተን
ደግሞ እንደ አዕዋፉቱ ለእርሱ ዘምረን
ዘመን ለንስሀ ዕድሜ ለፍስሀ አምላክ ካቀናጀን
ተመስገን እንበለው ምን አለ የሌለን
Nani girma
@Mgetem
@Mgetem
@Sulamatiz
እንኳን አደረሳችሁ
❤1