Forwarded from Daregot Media
መድኃኔዓለም ወይስ የግል አዳኝ
መዳን እንደ ቀለብ ፤ መዋጀት እንደ እህል፤
በቁና ተሰፍሮ የተሰጠ ይመስል፤
መሲሑን ለብቻ ፤ ኢየሱስን የግል፤
አ’ርገህ ምትቀበል፤
አድራሻህ ከየት ነው ስምህን ማን ልበል?
በእንተዝ ነገር ስምዐ ኮነ መልአክ፤
በጊዜ ልደቱ ወደ እረኞች ሲላክ።
መድኃኒት ክርስቶስ ግርግም መወለዱ ፤ በጨርቅ መጠቅለሉ፤
ለእረኞች በግል የተሰጠ ሳይሆን ለዓለሙ ሁሉ፤
እነሆ ሲታወቅ በምሥራች ቃሉ፤
አልሰማህም አሉ።
ራሱ ባለቤቱ፤
በወንጌል ትምህርቱ፤
“ለድኅነተ ዓለም በመልዕልተ መስቀል
ከምድር ከፍ ብዬ ዕርቃኔን ስሰቀል”
አንድ ሁለት ሰው ሳይሆን “ሁሉን እስባለሁ”
ሲል እየሰማነው፤
ጆሮ ነሳህ ምነው?
ደግሞስ ሳምራዊቷ፤
“ብፍርስንያ” ‘ሚሏት ውሃ ቀጂ ሴቷ፤
ውሃ አጠጭኝ ብሎ ፤ በፍቅር ጎብኝቷት ፤ እሷን ብቻ መርጦ፤
ሕይወት ሆኗት ሲሄድ ታሪኳን ለውጦ፤
አዳኝ ፣ መሲሕ የግል፤
መቼ ሰማን ስትል?
እንስራዋን ጥላ ገሰገሰች እንጂ ሰማርያ መንደር፤
የጠበቅነው አምላክ ተገለጠ ብላ ላ’ለም ልትናገር።
ከዚያማ፤
ድኅነት በሷ ሳይቀር፤
ለሃያ አምስት ምዕት ወገኖቹ መጣ፤
ከዓለት ክርስቶስ ማየ ሕይወት ፈልቆ ሁለት ቀን ተጠጣ።
መጣፍ ባለማወቅ ልቡናህ የሳተ፤
ዝንጕ ‘ምትሆን አንተ፤
“በእውነት ክርስቶስ የዓለም መድኃኒት እንደሆነ አውቀናል።”
ስትል ሰማርያ ፤ በአልሰሜነትህ በጣም ተደንቀናል።
ከእንግዲህስ ስማ የተዋሕዶን አዋጅ፤
“ቤዛ ኵሉ እንጂ ነው ዓለሙን የሚዋጅ፤
የብቻዬም አይደል፤
የብቻህም አይደል፤
ፋሲካን ልታከብር በደመ ክርስቶስ ፤ ነጽታ ምትታጠብ፤
የምድር ሐሴት እንጂ ፤ የምድር ሁሉ ገንዘብ።
እናም፤
“መ ድ ኃ ኔ ዓ ለ ም”
ያለሚለው ቀለም፤
ትድግናውን ገላጭ ምሉዕ ፊደል የለም።”
እያለች ስትጠራው ስማት በየዕለቱ፤
እያት ስታነግሠው በስመ መንግሥቱ፤
በጥንተ ስቅለቱ።
መድኃኔዓለም!
መድኃኔዓለም!
መድኃኔዓለም!
መዳን እንደ ቀለብ ፤ መዋጀት እንደ እህል፤
በቁና ተሰፍሮ የተሰጠ ይመስል፤
መሲሑን ለብቻ ፤ ኢየሱስን የግል፤
አ’ርገህ ምትቀበል፤
አድራሻህ ከየት ነው ስምህን ማን ልበል?
በእንተዝ ነገር ስምዐ ኮነ መልአክ፤
በጊዜ ልደቱ ወደ እረኞች ሲላክ።
መድኃኒት ክርስቶስ ግርግም መወለዱ ፤ በጨርቅ መጠቅለሉ፤
ለእረኞች በግል የተሰጠ ሳይሆን ለዓለሙ ሁሉ፤
እነሆ ሲታወቅ በምሥራች ቃሉ፤
አልሰማህም አሉ።
ራሱ ባለቤቱ፤
በወንጌል ትምህርቱ፤
“ለድኅነተ ዓለም በመልዕልተ መስቀል
ከምድር ከፍ ብዬ ዕርቃኔን ስሰቀል”
አንድ ሁለት ሰው ሳይሆን “ሁሉን እስባለሁ”
ሲል እየሰማነው፤
ጆሮ ነሳህ ምነው?
ደግሞስ ሳምራዊቷ፤
“ብፍርስንያ” ‘ሚሏት ውሃ ቀጂ ሴቷ፤
ውሃ አጠጭኝ ብሎ ፤ በፍቅር ጎብኝቷት ፤ እሷን ብቻ መርጦ፤
ሕይወት ሆኗት ሲሄድ ታሪኳን ለውጦ፤
አዳኝ ፣ መሲሕ የግል፤
መቼ ሰማን ስትል?
እንስራዋን ጥላ ገሰገሰች እንጂ ሰማርያ መንደር፤
የጠበቅነው አምላክ ተገለጠ ብላ ላ’ለም ልትናገር።
ከዚያማ፤
ድኅነት በሷ ሳይቀር፤
ለሃያ አምስት ምዕት ወገኖቹ መጣ፤
ከዓለት ክርስቶስ ማየ ሕይወት ፈልቆ ሁለት ቀን ተጠጣ።
መጣፍ ባለማወቅ ልቡናህ የሳተ፤
ዝንጕ ‘ምትሆን አንተ፤
“በእውነት ክርስቶስ የዓለም መድኃኒት እንደሆነ አውቀናል።”
ስትል ሰማርያ ፤ በአልሰሜነትህ በጣም ተደንቀናል።
ከእንግዲህስ ስማ የተዋሕዶን አዋጅ፤
“ቤዛ ኵሉ እንጂ ነው ዓለሙን የሚዋጅ፤
የብቻዬም አይደል፤
የብቻህም አይደል፤
ፋሲካን ልታከብር በደመ ክርስቶስ ፤ ነጽታ ምትታጠብ፤
የምድር ሐሴት እንጂ ፤ የምድር ሁሉ ገንዘብ።
እናም፤
“መ ድ ኃ ኔ ዓ ለ ም”
ያለሚለው ቀለም፤
ትድግናውን ገላጭ ምሉዕ ፊደል የለም።”
እያለች ስትጠራው ስማት በየዕለቱ፤
እያት ስታነግሠው በስመ መንግሥቱ፤
በጥንተ ስቅለቱ።
መድኃኔዓለም!
መድኃኔዓለም!
መድኃኔዓለም!
❤3👍1
#ጠላት_ለምን_ከፋው
@Mgetem
እኔው ጎንበስ ብዬ እኔው ቀና ላልኩት
እኔው አመስግኜ እኔው ለሰገድኩት
ጠላት ምን ተነካ የሚያረው በቅናት
እመቤቴ ብዬ እኔው ለወደድኳት
ያንድዬ እናት ብዬ እኔው ላወደስኳት
ብወድቅ ብነሳ እኔው ካልደከመኝ
ሳወድሳት ባድር እኔን ካልሰለቼኝ
ስማፀናት ብውል እኔው ካልታከተኝ
ጠላት ምን አገባው አትስገድ የሚለኝ
ፃድቃንን አይቼ እኔ ብማፀናት
ገብርኤልን አይቼ እኔ ባወድሳት
ሰማዕታትን አይቼ እኔ ብሞትላት
አምላክን አይቼ እኔ እርሷን ብመርጣት
ልጄ ስላለችኝ እናቴ ስላልኳት
ጠላት ለምን ከፋው እኔ እርሷን ብወዳት።
#ከክብሪት_ተፈራ
@@@@@@@@@@@@@@
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem
እኔው ጎንበስ ብዬ እኔው ቀና ላልኩት
እኔው አመስግኜ እኔው ለሰገድኩት
ጠላት ምን ተነካ የሚያረው በቅናት
እመቤቴ ብዬ እኔው ለወደድኳት
ያንድዬ እናት ብዬ እኔው ላወደስኳት
ብወድቅ ብነሳ እኔው ካልደከመኝ
ሳወድሳት ባድር እኔን ካልሰለቼኝ
ስማፀናት ብውል እኔው ካልታከተኝ
ጠላት ምን አገባው አትስገድ የሚለኝ
ፃድቃንን አይቼ እኔ ብማፀናት
ገብርኤልን አይቼ እኔ ባወድሳት
ሰማዕታትን አይቼ እኔ ብሞትላት
አምላክን አይቼ እኔ እርሷን ብመርጣት
ልጄ ስላለችኝ እናቴ ስላልኳት
ጠላት ለምን ከፋው እኔ እርሷን ብወዳት።
#ከክብሪት_ተፈራ
@@@@@@@@@@@@@@
@Mgetem
@Mgetem
🥰3
#ገድፍሃል
@Mgetem
አንደበትህ ክዶህ ሀሰት ከለመደ
መልካሙን ናቅ አርጎ ሴራ ከወደደ
እንደ አምሳል መሰረት ቀረ ሰው መሆንህ
አምላክም አይኖርም ሳይጣን ነው ከጎንህ
በህይዎት እየኖርክ ከሆንክ አሜኬላ
እኔ ሰው ነኝ እያልክ ልብህ ሰው ከጠላ
በእምነቱ ፀንተህ ወስጋ ከደሙ
አልገለጽ ካለህ የህይወት ትረጉሙ
እውነቱን ተቀበል
ጾምህን ገድፍሃል
ለምን! ማለት ጥሩ ለምን ይመስልሃል?
ውሰጥ ተመርዞ
ልብህ ቂም አርግዞ
ላይሰምር ሱባኤ
ልብ ሳይኖር ጉባኤ
ገደብ የለሽ ምኞት
ከአንገት በላይ ፀሎት
በላይኛው አለም ወንዝ አያሻግርም
እዚ እንደለመደከው ማጭበርበር አይኖርም።
➕➕➕➕➕➕➕➕➕➕➕➕
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem
አንደበትህ ክዶህ ሀሰት ከለመደ
መልካሙን ናቅ አርጎ ሴራ ከወደደ
እንደ አምሳል መሰረት ቀረ ሰው መሆንህ
አምላክም አይኖርም ሳይጣን ነው ከጎንህ
በህይዎት እየኖርክ ከሆንክ አሜኬላ
እኔ ሰው ነኝ እያልክ ልብህ ሰው ከጠላ
በእምነቱ ፀንተህ ወስጋ ከደሙ
አልገለጽ ካለህ የህይወት ትረጉሙ
እውነቱን ተቀበል
ጾምህን ገድፍሃል
ለምን! ማለት ጥሩ ለምን ይመስልሃል?
ውሰጥ ተመርዞ
ልብህ ቂም አርግዞ
ላይሰምር ሱባኤ
ልብ ሳይኖር ጉባኤ
ገደብ የለሽ ምኞት
ከአንገት በላይ ፀሎት
በላይኛው አለም ወንዝ አያሻግርም
እዚ እንደለመደከው ማጭበርበር አይኖርም።
➕➕➕➕➕➕➕➕➕➕➕➕
@Mgetem
@Mgetem
👍3
#የቆምኩኝ_ሲመስለኝ
@Mgetem
ማዘያው ከጠፋ #የህፃን_አንቀልባ
መልካሙ ተጣሞ #ካጨድን_ገለባ
አፅናኙ ተክዞ መፅናናትን ካጣ
የቆመ የሚመስለው ጎብጦብን ከመጣ
ረሀብ አጠውልጎት ህፃን ካለቀሰ
ጻድቅ መላ ጠፍቶት #ሰይጣን_ከቀየሰ
#ብርታት_አጎንብሶ ድካም ፀንቶ እግሩ
ይሁዳና ዴማስ ጽድቅ ከመከሩ
ሳዖልና ኬፋ ደግ ካልተስማሙ
አቤቱ ለባሪያህ #መንገዱን_አብራለት
ማየትና መስማት ካንተ ይሁንለት።
#ፈትልን_የሚፈትል ተራቁቶ ካደረ
#ውለታ_የበዛለት በሳቅ ካልዘመረ
በብዙ የተሾመ ጥቂት ካልታመነ
ልብን አሳራፊው ልቡ ከጨከነ
#ሰባኪ_እየካደ ዓለሙ ካመነ
አማኙ ሲታበይ #ቀራጭ_አጐንብሶ
የጽድቁን አዝመራ ከወሰደ አፍሶ
#አቤቱ_ለባሪያህ አይነ ልቡን አብራ
የቆምኩኝ ሲመስለኝ እንዳልወድቅ አደራ።
#ሥራዬ_የሞት ነው ጽድቄ የመርገም ጨርቅ
#አቤቱ_አድነኝ በድካሜ ሳትፈርድ
ብርታትህ ያቁመኝ አንተን እንድመስል
#ማስተዋሌን_አድስ ያለማመኔን ቃል፡፡
ΠΠΠΠΠΠΠΠΠΠΠΠΠΠΠΠΠΠΠ
@Mgetem
@Mgetem
@Menfesawi_getem_bot
@Mgetem
ማዘያው ከጠፋ #የህፃን_አንቀልባ
መልካሙ ተጣሞ #ካጨድን_ገለባ
አፅናኙ ተክዞ መፅናናትን ካጣ
የቆመ የሚመስለው ጎብጦብን ከመጣ
ረሀብ አጠውልጎት ህፃን ካለቀሰ
ጻድቅ መላ ጠፍቶት #ሰይጣን_ከቀየሰ
#ብርታት_አጎንብሶ ድካም ፀንቶ እግሩ
ይሁዳና ዴማስ ጽድቅ ከመከሩ
ሳዖልና ኬፋ ደግ ካልተስማሙ
አቤቱ ለባሪያህ #መንገዱን_አብራለት
ማየትና መስማት ካንተ ይሁንለት።
#ፈትልን_የሚፈትል ተራቁቶ ካደረ
#ውለታ_የበዛለት በሳቅ ካልዘመረ
በብዙ የተሾመ ጥቂት ካልታመነ
ልብን አሳራፊው ልቡ ከጨከነ
#ሰባኪ_እየካደ ዓለሙ ካመነ
አማኙ ሲታበይ #ቀራጭ_አጐንብሶ
የጽድቁን አዝመራ ከወሰደ አፍሶ
#አቤቱ_ለባሪያህ አይነ ልቡን አብራ
የቆምኩኝ ሲመስለኝ እንዳልወድቅ አደራ።
#ሥራዬ_የሞት ነው ጽድቄ የመርገም ጨርቅ
#አቤቱ_አድነኝ በድካሜ ሳትፈርድ
ብርታትህ ያቁመኝ አንተን እንድመስል
#ማስተዋሌን_አድስ ያለማመኔን ቃል፡፡
ΠΠΠΠΠΠΠΠΠΠΠΠΠΠΠΠΠΠΠ
@Mgetem
@Mgetem
@Menfesawi_getem_bot
#መዝሙር_አለቀሰ 💧
@Mgetem
የያሬድ ዝማሬ የአዘማመር ስልቱ
የበገናው ቃና መሠንቆ ቅኝቱ
የከበሮው ውበት የዋሽንት ፍሰቱ
ነበረ ተፈጥሮአቸው ስብሐትን ሊዘሩ
ነበር ተፈጥሮአቸው ስርዓትን ሊያከብሩ
መንፈስን አድሰው ውበትና ሊደምሩ
ስንዱዋ እመቤት ቤተክርስቲያን ቅድስት
ሁሉን አስተማረች እንዳለ በስርዓት
ዛሬማ አፍ የፈታ ሁሉ እያንጎራጎረ
ቀኖና ትውፊቱን እየሸረሸረ
የመዝሙር ስርዓቱ ስልቱ ተቀየረ
መዝሙር ዜማ ሳይሆን ጩኸት ሆኖ ቀረ
ለነፍስ ተትቶ ለስጋ እያደረ
ሳኦልም ከደዌው እንዳልተፈወሰ
ወይኒውም በመዝሙር እንዳልፈራረሰ
መዝሙር ቅዱሳንን እንዳላወደሰ
ዜማን ሀዘን ገባው መዝሙር አለቀሰ
ንጉስ ገ/መስቀል ከግሩ ጦር ሰክቶ
በፍፁም ተመስጦ አለምን እረስቶ
እንዳልነበር ሁሉ ፀጋችን ምግባችን
መዝሙር አንገት ደፋ ከመላዕክት በላይ አዋቂዎች ሆነን
ሰይጠፋ መዝሙሩ እስከነ ስረዓቱ
ፈር እየለቀቀ ዘማሪ ነኝ አለ ሁሉም በየቤቱ
በጠፋበት ሁሉ ተጥሶ መክሊቱ
መዝሙር አለቀሰ ተገፎ ውበቱ
መዝሙር አለቀሰ ተጥሶ ስርዓቱ።
🕓🕓🕓🕓🕔🕓🕓🕓🕔🕓🕔🕔
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem
የያሬድ ዝማሬ የአዘማመር ስልቱ
የበገናው ቃና መሠንቆ ቅኝቱ
የከበሮው ውበት የዋሽንት ፍሰቱ
ነበረ ተፈጥሮአቸው ስብሐትን ሊዘሩ
ነበር ተፈጥሮአቸው ስርዓትን ሊያከብሩ
መንፈስን አድሰው ውበትና ሊደምሩ
ስንዱዋ እመቤት ቤተክርስቲያን ቅድስት
ሁሉን አስተማረች እንዳለ በስርዓት
ዛሬማ አፍ የፈታ ሁሉ እያንጎራጎረ
ቀኖና ትውፊቱን እየሸረሸረ
የመዝሙር ስርዓቱ ስልቱ ተቀየረ
መዝሙር ዜማ ሳይሆን ጩኸት ሆኖ ቀረ
ለነፍስ ተትቶ ለስጋ እያደረ
ሳኦልም ከደዌው እንዳልተፈወሰ
ወይኒውም በመዝሙር እንዳልፈራረሰ
መዝሙር ቅዱሳንን እንዳላወደሰ
ዜማን ሀዘን ገባው መዝሙር አለቀሰ
ንጉስ ገ/መስቀል ከግሩ ጦር ሰክቶ
በፍፁም ተመስጦ አለምን እረስቶ
እንዳልነበር ሁሉ ፀጋችን ምግባችን
መዝሙር አንገት ደፋ ከመላዕክት በላይ አዋቂዎች ሆነን
ሰይጠፋ መዝሙሩ እስከነ ስረዓቱ
ፈር እየለቀቀ ዘማሪ ነኝ አለ ሁሉም በየቤቱ
በጠፋበት ሁሉ ተጥሶ መክሊቱ
መዝሙር አለቀሰ ተገፎ ውበቱ
መዝሙር አለቀሰ ተጥሶ ስርዓቱ።
🕓🕓🕓🕓🕔🕓🕓🕓🕔🕓🕔🕔
@Mgetem
@Mgetem
👍3❤1
#አቃጥሏት_ግዴለም
@Mgetem
🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥
ቤተ ክርስቲያክርስቲያን ቅድስት እመ ኵሉ፣
የወንጌል ማኅደር የጸናብሽ ቃሉ፣
ስብከትሽ ሰላም ነው ለዓለም በሙሉ፤
አፅራረ ሰላም ግን አንቺን ይጠላሉ፤
ተልእኮሽ ፈውስ ነው ለታመሙ ኹሉ፤
መዳን የማይወዱ ከአንቺ ይሸሻሉ፤
ጭራሽ ሊያሳድዱሽ ይመካከራሉ፤
አጥፍቶ ጠፊዎች ሊያጠፉሽ ይሻሉ።
የጥፋት ልዑካን ለጽድቅ ያልታደሉ፣
ሕንፃሽን በእሳት አቃጠሉት አሉ፤
ጣሪያ ግድግዳዉን አፈረሱት አሉ፤
ባያውቁት ነው እንጂ ቢጠፋቸው ውሉ፣
በአንቺ እሳትነት አብረው ይጨሳሉ፤
በማገዱት እንጨት ኋላ ይነዳሉ፤
ዛሬ እንዳፈረሱሽ ነገ ይፈርሳሉ፤
በሠፈሩት መጠን ዋጋን ያገኛሉ።
አህዛብ ግብዞች ሆይ የሰይጣን ፈረሱ፣
ደስ ካሰኛችሁ እሳት መለኮሱ፣
አቃጥሏት ግዴለም ጣሪያዋን አፍርሱ፤
ግድግዳ ወለሉን ብሎኬቱን አንሡ፤
ለጊዜውም ቢኾን ቅፅሮቿን ደምስሱ፤
ልጆቿን በሙሉ ደም ዕንባ አስለቅሱ።
ነገር ግን ጌታዋ ሲቆጣ ንጉሡ፣
መቃጠላችሁን ፈጽሞ እንዳትረሱ፤
ጽዋ ተርታችሁን ዘወትር አስታውሱ፡፡
ጌታ ችሎ ችሎ መዓቱን ሲያመጣ፣
ቅፅሩን ለማስከበር ሲፈርድ በቁጣ፣
በተራ መንደድ ነው የኹላችሁ ዕጣ፡፡
እስከዚያው ድረስ ግን እስኪመጣ ጌታ፣
የዓለምን መድኀኒት የሕዝብን አለኝታ፣
ቤተ ክርስቲያንን አፍርሷት በአንድ አፍታ፤
አቃጥሏት ግዴለም አንድዷት በተርታ፡፡
እርሷ በትረ ወንጌል የሾለ ብረቱ፣
ብትቆሙ ደፍራችሁ በኃያል ስለቱ፣
ደዌው ለእናንተ ነው ሕመሙ ጉዳቱ።
ጣሪያና ግድግዳው አካሏ ቢደማ፣
ብትነድ ብትቃጠል በክፉዎች ፊርማ፣
መቅደስ ማኅሌቱ ቢመስልም ባድማ፣
አትፈርስም በፍጹም በግብዞች ዐድማ፤
እሳት የሚያነዳት አይደለችም እማ፤
በክርስቶስ ፍቅር ተቃጥላለች ቀድማ፡፡
ቤተ ክርስቲያን ይቺ ምድራዊቷ፣
መለኮት እሳት ነው ጥንትም መሠረቷ፣
የክርስቶስ ደም ነው እስትንፋስ ሕይወቷ፣
አቃጥሏታልና ክርስቶስ እሳቷ፣
አጽንቷታልና አምላክ ባለቤቷ፣
በፍጹም አትፈርስም ጽኑ ነው ዐለቷ፤
በጠላት ዘመቻ አይኾንም ኅልፈቷ፡፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር!
→→→→→→→→→→→→→→
መርከቧን የሚያውክ ንፋስ መቷል
አድነን ክርስቶስ ተጨንቀናል
አድነን ክርስቶስ ተማጽነናል 🙏
ቅድስት ቤተክርስቲያናችንን እግዚአብሔር አምላክ ይጠብቅልን
ሀገራችን ኢትዮጵያን ሰላም ያድርግልን አሜን!!!፫
→→→→→→→→→→→→→→
@Mgetem
@Mgetem
@Menfesawi_getem_bot
@Mgetem
🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥
ቤተ ክርስቲያክርስቲያን ቅድስት እመ ኵሉ፣
የወንጌል ማኅደር የጸናብሽ ቃሉ፣
ስብከትሽ ሰላም ነው ለዓለም በሙሉ፤
አፅራረ ሰላም ግን አንቺን ይጠላሉ፤
ተልእኮሽ ፈውስ ነው ለታመሙ ኹሉ፤
መዳን የማይወዱ ከአንቺ ይሸሻሉ፤
ጭራሽ ሊያሳድዱሽ ይመካከራሉ፤
አጥፍቶ ጠፊዎች ሊያጠፉሽ ይሻሉ።
የጥፋት ልዑካን ለጽድቅ ያልታደሉ፣
ሕንፃሽን በእሳት አቃጠሉት አሉ፤
ጣሪያ ግድግዳዉን አፈረሱት አሉ፤
ባያውቁት ነው እንጂ ቢጠፋቸው ውሉ፣
በአንቺ እሳትነት አብረው ይጨሳሉ፤
በማገዱት እንጨት ኋላ ይነዳሉ፤
ዛሬ እንዳፈረሱሽ ነገ ይፈርሳሉ፤
በሠፈሩት መጠን ዋጋን ያገኛሉ።
አህዛብ ግብዞች ሆይ የሰይጣን ፈረሱ፣
ደስ ካሰኛችሁ እሳት መለኮሱ፣
አቃጥሏት ግዴለም ጣሪያዋን አፍርሱ፤
ግድግዳ ወለሉን ብሎኬቱን አንሡ፤
ለጊዜውም ቢኾን ቅፅሮቿን ደምስሱ፤
ልጆቿን በሙሉ ደም ዕንባ አስለቅሱ።
ነገር ግን ጌታዋ ሲቆጣ ንጉሡ፣
መቃጠላችሁን ፈጽሞ እንዳትረሱ፤
ጽዋ ተርታችሁን ዘወትር አስታውሱ፡፡
ጌታ ችሎ ችሎ መዓቱን ሲያመጣ፣
ቅፅሩን ለማስከበር ሲፈርድ በቁጣ፣
በተራ መንደድ ነው የኹላችሁ ዕጣ፡፡
እስከዚያው ድረስ ግን እስኪመጣ ጌታ፣
የዓለምን መድኀኒት የሕዝብን አለኝታ፣
ቤተ ክርስቲያንን አፍርሷት በአንድ አፍታ፤
አቃጥሏት ግዴለም አንድዷት በተርታ፡፡
እርሷ በትረ ወንጌል የሾለ ብረቱ፣
ብትቆሙ ደፍራችሁ በኃያል ስለቱ፣
ደዌው ለእናንተ ነው ሕመሙ ጉዳቱ።
ጣሪያና ግድግዳው አካሏ ቢደማ፣
ብትነድ ብትቃጠል በክፉዎች ፊርማ፣
መቅደስ ማኅሌቱ ቢመስልም ባድማ፣
አትፈርስም በፍጹም በግብዞች ዐድማ፤
እሳት የሚያነዳት አይደለችም እማ፤
በክርስቶስ ፍቅር ተቃጥላለች ቀድማ፡፡
ቤተ ክርስቲያን ይቺ ምድራዊቷ፣
መለኮት እሳት ነው ጥንትም መሠረቷ፣
የክርስቶስ ደም ነው እስትንፋስ ሕይወቷ፣
አቃጥሏታልና ክርስቶስ እሳቷ፣
አጽንቷታልና አምላክ ባለቤቷ፣
በፍጹም አትፈርስም ጽኑ ነው ዐለቷ፤
በጠላት ዘመቻ አይኾንም ኅልፈቷ፡፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር!
→→→→→→→→→→→→→→
መርከቧን የሚያውክ ንፋስ መቷል
አድነን ክርስቶስ ተጨንቀናል
አድነን ክርስቶስ ተማጽነናል 🙏
ቅድስት ቤተክርስቲያናችንን እግዚአብሔር አምላክ ይጠብቅልን
ሀገራችን ኢትዮጵያን ሰላም ያድርግልን አሜን!!!፫
→→→→→→→→→→→→→→
@Mgetem
@Mgetem
@Menfesawi_getem_bot
👍6🥰1
#ሳይፀልዩ_ማደር
@Mgetem
የተራበ ነብር ከሩቅ ተመልክታ
ሚዳቋ ፀለየች....
"አውጣኝ አውጣኝ" አለች ለፈጠራት ጌታ
ነብሩም ተርቦ
ወደ አምላኩ ቀርቦ
ሚዳቆዋን አይቶ - አንጀቱ ከሆዱ እንደጠጣበቀ
ፈቅዶ እንዲሰጠው - አምላኩን ጠየቀ
የሁለቱን ማብላት - የሁላችን ሰሪ
ፀሎታቸውንም - ሰማቸው ፈጣሪ
አምላክም በድምፁ - ሚዳቆዋን አላት
"እሩጠሽ አምልጪ - ከበረታ ጠላት"
ነብሩንም አለው - "እሩጥ ተከተላት
ምግብህ አርገህ ብላት
ሚዳቆዋ ስትሮጥ
ከነብር ለማምለጥ
ነብሩም ሲከተላት
ሆዱን ሊሞላባት
ቋጥኙን ስትዘል እግሯ ተስፈንጥሮ
ሆዱን ብትረግጠው የተኛው ከርከሮ
ከእንቅልፉ ሲነቃ ልክ ሲደነብር
ጉሮሮውን ያዘው የፀለየው ነብር
አውጣኝ ያለው_ወቶ - አብላኝ ያለው በላ
ሳይፀልይ ያደረው - ከርከሮ ተበላ 🙏
💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem
የተራበ ነብር ከሩቅ ተመልክታ
ሚዳቋ ፀለየች....
"አውጣኝ አውጣኝ" አለች ለፈጠራት ጌታ
ነብሩም ተርቦ
ወደ አምላኩ ቀርቦ
ሚዳቆዋን አይቶ - አንጀቱ ከሆዱ እንደጠጣበቀ
ፈቅዶ እንዲሰጠው - አምላኩን ጠየቀ
የሁለቱን ማብላት - የሁላችን ሰሪ
ፀሎታቸውንም - ሰማቸው ፈጣሪ
አምላክም በድምፁ - ሚዳቆዋን አላት
"እሩጠሽ አምልጪ - ከበረታ ጠላት"
ነብሩንም አለው - "እሩጥ ተከተላት
ምግብህ አርገህ ብላት
ሚዳቆዋ ስትሮጥ
ከነብር ለማምለጥ
ነብሩም ሲከተላት
ሆዱን ሊሞላባት
ቋጥኙን ስትዘል እግሯ ተስፈንጥሮ
ሆዱን ብትረግጠው የተኛው ከርከሮ
ከእንቅልፉ ሲነቃ ልክ ሲደነብር
ጉሮሮውን ያዘው የፀለየው ነብር
አውጣኝ ያለው_ወቶ - አብላኝ ያለው በላ
ሳይፀልይ ያደረው - ከርከሮ ተበላ 🙏
💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠
@Mgetem
@Mgetem
👍6❤2
#ይቅርታ_አድርጉልኝ
@Mgetem
#ትናንት_ለበደለን ፡ አምና ላስቀየመን
#ቅሬታን_አጥፍተን ፡ በደል መቁጠር ትተን
የንስሀን ጊዜ ፡ ጨምሮ ሊሰጠን
ይቅርታ እንድናደርግ፡ #ጷጉሜ_ተለገሰን ።
ፈንድቆ ለመኖር ፡ እንደ ጨቅላ ህፃን
በሰላም ይፈታ ፡ የቂም ቋጠራችን
ይቅር እንባባል ፡ #አንዳችን_ለአንዳችን
ለዚህ ነው የተሰጠን ፡ #ጷጉሜ_ድልድያችን።
እስካሁን ላረኩት ፡ በደል በናንተ ላይ
ይቅርታ አድርጉልኝ ፦
ይቅርታ የሚያደርግ ፡ #ነውና_አስተዋይ።
#ለጥሩም_ለመጥፎም ፡ ፍርድ አለ ከሰማይ
ግን እስካለን ድረስ ፡ በጥፉት ምድር ላይ
ለገዛ ጥቅሜ ስል ፡ ለሰራሁት ጉዳይ
እያወኩኝ ሳላውቅ ፡ እያየሁኝ ሳላይ
ለበደሌ ሁሉ ፡ በሞት ሳንለያይ
#ይቅርታ_አድርጉኝ ፦
ሰው ከአባቱ ገዳይ ፡ ይታረቅ የለም ወይ። 🙏
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem
#ትናንት_ለበደለን ፡ አምና ላስቀየመን
#ቅሬታን_አጥፍተን ፡ በደል መቁጠር ትተን
የንስሀን ጊዜ ፡ ጨምሮ ሊሰጠን
ይቅርታ እንድናደርግ፡ #ጷጉሜ_ተለገሰን ።
ፈንድቆ ለመኖር ፡ እንደ ጨቅላ ህፃን
በሰላም ይፈታ ፡ የቂም ቋጠራችን
ይቅር እንባባል ፡ #አንዳችን_ለአንዳችን
ለዚህ ነው የተሰጠን ፡ #ጷጉሜ_ድልድያችን።
እስካሁን ላረኩት ፡ በደል በናንተ ላይ
ይቅርታ አድርጉልኝ ፦
ይቅርታ የሚያደርግ ፡ #ነውና_አስተዋይ።
#ለጥሩም_ለመጥፎም ፡ ፍርድ አለ ከሰማይ
ግን እስካለን ድረስ ፡ በጥፉት ምድር ላይ
ለገዛ ጥቅሜ ስል ፡ ለሰራሁት ጉዳይ
እያወኩኝ ሳላውቅ ፡ እያየሁኝ ሳላይ
ለበደሌ ሁሉ ፡ በሞት ሳንለያይ
#ይቅርታ_አድርጉኝ ፦
ሰው ከአባቱ ገዳይ ፡ ይታረቅ የለም ወይ። 🙏
@Mgetem
@Mgetem
👍3
#ኒቆዲሞስ ዩሐ 3÷2
@Mgetem
ፈሪሳዊው እውቅ መምህር
ሊቅ አልነበርክ ያገር ክብር?
የምርጥ ምርጥ ከእውቅም እውቅ
ነበርክ እኮ የአይሁድ ሊቅ
ግና ሕግ አዋቂ ነህ መባሉ
መምህር ነው ቢልህ ሁሉ
የውስጥህን ስቃይ ገልጠህ
ሚዛን ባይደፋ እውቀትህ
የሰው ሙገሳ ድለላ
ውስጥ ባዶህን ባይሞላ
አስገራሚው ድብቅ ጉዞህ
ከቀን ለሊት አስመርጦህ
ወደ ጌታ መገስገስህ
ሊቅ ስትባል መጠየቅህ
ሕይወት አሲዞ መለሰህ።
______________________
@Mgetem
@Mgetem
@Menfesawi_getem_bot
@Mgetem
ፈሪሳዊው እውቅ መምህር
ሊቅ አልነበርክ ያገር ክብር?
የምርጥ ምርጥ ከእውቅም እውቅ
ነበርክ እኮ የአይሁድ ሊቅ
ግና ሕግ አዋቂ ነህ መባሉ
መምህር ነው ቢልህ ሁሉ
የውስጥህን ስቃይ ገልጠህ
ሚዛን ባይደፋ እውቀትህ
የሰው ሙገሳ ድለላ
ውስጥ ባዶህን ባይሞላ
አስገራሚው ድብቅ ጉዞህ
ከቀን ለሊት አስመርጦህ
ወደ ጌታ መገስገስህ
ሊቅ ስትባል መጠየቅህ
ሕይወት አሲዞ መለሰህ።
______________________
@Mgetem
@Mgetem
@Menfesawi_getem_bot
👍1
#አህያዋ
@Mgetem
ከእንስሳት ተለይታ
ልትቆም በሰው ተርታ
ሊቀመጥባት ጌታዋ
ሊታወቅላት ዋጋዋ
ላይጠፋባት አደራዋ
ሰው የማገልገል ስራዋ
ሲመጣላት ፈጣሪዋ
ደስ አላት አህያዋ
ሲቀመጥባት በጀርባዋ።
ውርንጭላነቷ ቀርቶ
የታሰረችበት ገመድ ተፈቶ
መናቅ መሰደቧ ጠፍቶ
የዋሁ የጺዮን ልጅ ትህትናን ተመልቶ
አስገባት ከተማ በህዝቡ ፊት መርቶ።
አፋቸው ተለጉሞ
ሃሳባቸው ከፍቶ ጠሞ
አዋቂ ነን ባዮቹ
የአይሁድ ካህናት ግብዞቹ
ዝም ቢሉ ለምስጋና
ለመራቸው በደመና
ለመገባቸው ከሰማይ መና
መመስገኑ መቼ ቀረና
እየተባለ ሆሳእና።
በሴቶች በወንዶቹ
በአዛውንት በልጆቹ
በህጻናት ጡት ጠቢዎቹ።
የዘኪዮስ ምኞት
መቼ ተረሳ በእጥረቱ
ዛፍ ላይ ብቻ በመታየቱ
አለቀረም ፍላጎቱ
ለመዘመር መጓጓቱ
ገብቶለታል ወደ ቤቱ
የጺዮን ልጅ ያትሁቱ
ሊበላ አብሮት ከፍትፍቱ።
መቅደስ ገብቶ ዞሮ ሲቃኝ
ሲመለከት ጊዜ አባካኝ
ጽሎት ትቶ ሲቸረችር
ከሌባ ጋር ሲደራደር
አልቻለም ስለ ቤቱ
ሲያቃጥለው ቅንአቱ
ጅራፍ ሰራ ለትምህርቱ
ቤቱን ሊያጠራ ከጠላቱ።
________________
@Mgetem
@Mgetem
@Menfesawi_getem_bot
@Mgetem
ከእንስሳት ተለይታ
ልትቆም በሰው ተርታ
ሊቀመጥባት ጌታዋ
ሊታወቅላት ዋጋዋ
ላይጠፋባት አደራዋ
ሰው የማገልገል ስራዋ
ሲመጣላት ፈጣሪዋ
ደስ አላት አህያዋ
ሲቀመጥባት በጀርባዋ።
ውርንጭላነቷ ቀርቶ
የታሰረችበት ገመድ ተፈቶ
መናቅ መሰደቧ ጠፍቶ
የዋሁ የጺዮን ልጅ ትህትናን ተመልቶ
አስገባት ከተማ በህዝቡ ፊት መርቶ።
አፋቸው ተለጉሞ
ሃሳባቸው ከፍቶ ጠሞ
አዋቂ ነን ባዮቹ
የአይሁድ ካህናት ግብዞቹ
ዝም ቢሉ ለምስጋና
ለመራቸው በደመና
ለመገባቸው ከሰማይ መና
መመስገኑ መቼ ቀረና
እየተባለ ሆሳእና።
በሴቶች በወንዶቹ
በአዛውንት በልጆቹ
በህጻናት ጡት ጠቢዎቹ።
የዘኪዮስ ምኞት
መቼ ተረሳ በእጥረቱ
ዛፍ ላይ ብቻ በመታየቱ
አለቀረም ፍላጎቱ
ለመዘመር መጓጓቱ
ገብቶለታል ወደ ቤቱ
የጺዮን ልጅ ያትሁቱ
ሊበላ አብሮት ከፍትፍቱ።
መቅደስ ገብቶ ዞሮ ሲቃኝ
ሲመለከት ጊዜ አባካኝ
ጽሎት ትቶ ሲቸረችር
ከሌባ ጋር ሲደራደር
አልቻለም ስለ ቤቱ
ሲያቃጥለው ቅንአቱ
ጅራፍ ሰራ ለትምህርቱ
ቤቱን ሊያጠራ ከጠላቱ።
________________
@Mgetem
@Mgetem
@Menfesawi_getem_bot
👍3❤2
#አቤቱ_ይቅር_በለኝ 😢
@Mgetem
የዕንባ ጅረት ባይታይ በጉኝጭ በደረት ባይኖር ማቅ መልበስ ማንባት ቢሳን በአንደበት
ከል መነስነስ ቢቀር ቅይጥ ቢሆን ህሊና
መድረስ ባንችል ከዚያ ጥግ ሕይወት አዙሪት ሆና
ቅርብ ማደራችን እንደሁ አይቀር ከዚህ
ዕጣ ፈንታችን ነውና
እንደ ኖኅ ዘመን እንደጠፉ በማይ ንፍር
ተለካክፈን በሥጋዊ ጥምር ፍቅር
ቀልጠን እንዳንቀር እንደ ሰዶም ድኝ ገሞራ
ፋታ በሚያሳጣን ስጋዊ ምንዘራ
እስከ መቼ ይሆን እኔስ በውስጤ ማልቀሴ
ጥርኝ አልባ ሕይወት ማጣቴ ለነፍሴ
ስንት ዘመን ሙሉ ከኔው እየዋሉ ጥልና ክርክር
የናኙ በውሰጤ ፍቅር አልባ ምስጢር
ተጣብቀው ’ሚኖሩ ከጉያዬ ሥር
ከኔው ጋር ሲከርሙ ነፍሴን እያደሙ
ቁስለቱ ቢሰማኝ ውስጤን ቢያሳምሙ
ካቅሜ በላይ ስበላ
ያገኘሁ መስሎኝ መጋቢ አባ መላ
ሆዴን ሳጠረቃ ሥጋዬን ሳደልብ
ሆድ አምላኩ ሆኜ ሳብል ስስገበገብ
ነፍሴን ጥግ ጥዬ ከታዛው ባሻገር
ሕይወት ይጥም መስሎኝ እንዲያው ስውተረተር
ያ’ለም ሕይወት ሳንካው መዘዙ
መጨነቅ መተከዙ
ከውስጤ ገብቶ እኔነቴን ቢያምስ
ከነፍሴ ጥጋት መንጭቶ የውስጤ ረቂቁ መንፈስ
አነቃኝ አናጥቦ ከጠሊቁ እንቅልፍ
ሊመልሰኝ በንስሐ ከውድቀት አፋፍ
አነባ ውስጤ የንስሐ እንባ
ቢያቀል ሸክሜን ንዶ ለላይኛው አምባ
ምን ገዶኝ ማንባቱ ቢመነጭ ከልቤ
የጌታዬን ማዕድ እንዳልቀር ተርቤ
በንስሐ ጠበል ኃጢአቴን አጥቤ
መኖርን እሻለሁ ትሩፋት ደርቤ
♻️♻️♻️♻️♻️♻️♻️♻️♻️♻️♻️♻️
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem
የዕንባ ጅረት ባይታይ በጉኝጭ በደረት ባይኖር ማቅ መልበስ ማንባት ቢሳን በአንደበት
ከል መነስነስ ቢቀር ቅይጥ ቢሆን ህሊና
መድረስ ባንችል ከዚያ ጥግ ሕይወት አዙሪት ሆና
ቅርብ ማደራችን እንደሁ አይቀር ከዚህ
ዕጣ ፈንታችን ነውና
እንደ ኖኅ ዘመን እንደጠፉ በማይ ንፍር
ተለካክፈን በሥጋዊ ጥምር ፍቅር
ቀልጠን እንዳንቀር እንደ ሰዶም ድኝ ገሞራ
ፋታ በሚያሳጣን ስጋዊ ምንዘራ
እስከ መቼ ይሆን እኔስ በውስጤ ማልቀሴ
ጥርኝ አልባ ሕይወት ማጣቴ ለነፍሴ
ስንት ዘመን ሙሉ ከኔው እየዋሉ ጥልና ክርክር
የናኙ በውሰጤ ፍቅር አልባ ምስጢር
ተጣብቀው ’ሚኖሩ ከጉያዬ ሥር
ከኔው ጋር ሲከርሙ ነፍሴን እያደሙ
ቁስለቱ ቢሰማኝ ውስጤን ቢያሳምሙ
ካቅሜ በላይ ስበላ
ያገኘሁ መስሎኝ መጋቢ አባ መላ
ሆዴን ሳጠረቃ ሥጋዬን ሳደልብ
ሆድ አምላኩ ሆኜ ሳብል ስስገበገብ
ነፍሴን ጥግ ጥዬ ከታዛው ባሻገር
ሕይወት ይጥም መስሎኝ እንዲያው ስውተረተር
ያ’ለም ሕይወት ሳንካው መዘዙ
መጨነቅ መተከዙ
ከውስጤ ገብቶ እኔነቴን ቢያምስ
ከነፍሴ ጥጋት መንጭቶ የውስጤ ረቂቁ መንፈስ
አነቃኝ አናጥቦ ከጠሊቁ እንቅልፍ
ሊመልሰኝ በንስሐ ከውድቀት አፋፍ
አነባ ውስጤ የንስሐ እንባ
ቢያቀል ሸክሜን ንዶ ለላይኛው አምባ
ምን ገዶኝ ማንባቱ ቢመነጭ ከልቤ
የጌታዬን ማዕድ እንዳልቀር ተርቤ
በንስሐ ጠበል ኃጢአቴን አጥቤ
መኖርን እሻለሁ ትሩፋት ደርቤ
♻️♻️♻️♻️♻️♻️♻️♻️♻️♻️♻️♻️
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem
👍3❤2
#ክርስቶስ ተነሳ
@Mgetem
ድውይ በፈወሰ ሙታንን ባነሳ
ይሰቀል ተባለ ውለታው ተረሳ።
ክርስቶስ ይሰቀል በርባንን ልቀቀው
ብሎ ተናገረ ሀጢያት የናፈቀው።
የይሁዳ ክህደት ዓይኑን ያፈጠጠ
ለሰላሳ ብር ሲል አምላኩን የሸጠ።
ቸሩ መድሐኒዓለም ብዙ ተገረፈ
መከራው ቢጠናም በትዕግስት አለፈ።
እየተጋገዙ ጨርሶ እስኪቀር አጥንቱ
የአዳም ዘርን ሁሉ ከሲኦል ለማውጣት
ፈጣሪ በፍጡር ተቀበለ ቅጣት።
ተሰቀለ ብላ ስታዝን እናቱ
ገድለነዋል ብለው አህዛብ ሲዘብቱ
አዳኙን ቢገድሉት ያለ አንዳች አበሳ
ሞትን ድል አድርጎ ክርስቶስ ተነሳ።
__________________________
እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤው በሰላም አደረሳችሁ
__________________________
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem
ድውይ በፈወሰ ሙታንን ባነሳ
ይሰቀል ተባለ ውለታው ተረሳ።
ክርስቶስ ይሰቀል በርባንን ልቀቀው
ብሎ ተናገረ ሀጢያት የናፈቀው።
የይሁዳ ክህደት ዓይኑን ያፈጠጠ
ለሰላሳ ብር ሲል አምላኩን የሸጠ።
ቸሩ መድሐኒዓለም ብዙ ተገረፈ
መከራው ቢጠናም በትዕግስት አለፈ።
እየተጋገዙ ጨርሶ እስኪቀር አጥንቱ
የአዳም ዘርን ሁሉ ከሲኦል ለማውጣት
ፈጣሪ በፍጡር ተቀበለ ቅጣት።
ተሰቀለ ብላ ስታዝን እናቱ
ገድለነዋል ብለው አህዛብ ሲዘብቱ
አዳኙን ቢገድሉት ያለ አንዳች አበሳ
ሞትን ድል አድርጎ ክርስቶስ ተነሳ።
__________________________
እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤው በሰላም አደረሳችሁ
__________________________
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem
👍4
#ማህሌት
@Mgetem
ፈልቀሽ የተገኘሽ ከአፈ መላእክት፣
ያሬድ የተማረሽ ከላይ ከሰማያት፣
እንከን የሌለብሽ አዲሷ ምስጋና።
ምስጢርሽ ሲገለጥ በአስደናቂ ዜማ፣
ከሰማይ መንጭተሽ በምድር ሲሰማ፣
በቃናሽ መሰጠሽ ልቡናን በመክፈት፣
ማርከሽ ትወስጃለሽ ነፍስን ወደ ገነት።
የፍቅር መግለጫ የሕይወታችን አርማ፣
ጣእምሽ ልዩ ነው ሲገለጥ በዜማ።
የአድባራቱ ሁሉ ቋንቋና ድምጻቸው፣
የካህናት ቅኔ ሰምና ወርቃቸው፣
ለህዝብ ኢትዮጵያ የነፍስ ምግባቸው፣
ማኅሌት እኮነሽ ጸጋና ሃብታቸው።
____________________________
@Mgetem
@Mgetem
@Menfesawi_getem_bot
@Mgetem
ፈልቀሽ የተገኘሽ ከአፈ መላእክት፣
ያሬድ የተማረሽ ከላይ ከሰማያት፣
እንከን የሌለብሽ አዲሷ ምስጋና።
ምስጢርሽ ሲገለጥ በአስደናቂ ዜማ፣
ከሰማይ መንጭተሽ በምድር ሲሰማ፣
በቃናሽ መሰጠሽ ልቡናን በመክፈት፣
ማርከሽ ትወስጃለሽ ነፍስን ወደ ገነት።
የፍቅር መግለጫ የሕይወታችን አርማ፣
ጣእምሽ ልዩ ነው ሲገለጥ በዜማ።
የአድባራቱ ሁሉ ቋንቋና ድምጻቸው፣
የካህናት ቅኔ ሰምና ወርቃቸው፣
ለህዝብ ኢትዮጵያ የነፍስ ምግባቸው፣
ማኅሌት እኮነሽ ጸጋና ሃብታቸው።
____________________________
@Mgetem
@Mgetem
@Menfesawi_getem_bot