Forwarded from መንፈሳዊ ግጥም ብቻ (ቦአኔርጌስ ቦት)
፨ ሞትሰ ፨
(በከሳቴብርሃን)
ቅዱስ ያሬድ ሊቁ፤
በሕይወት እናት ሞት ታየ መደነቁ::
እንዲህ በሚል ቃሉ፤
”ሞታ ለማርያም የዓፅብ ለኵሉ“::
ሞትስ ፥ጌታም ቀምሷል፤
የጥሉን ግድግዳ ፥ በመስቀል አፍርሷል::
ታዲያ፤
ሞታ ከመ ወልዳ፤
የነፍሳተ ሲኦል ፥ማምለጫ ቀዳዳ፤
የሆነላት ድንግል ፥ እረፍቷ ምን ይደንቅ?
ድንቅስ ፥ ከድንቅም ድንቅ፤
አብዝቶ ሚያስጨንቅ ፥ አልፎም የሚያሳቅቅ፤
የትንሣኤን እናት ፥ ትንሣኤዋን ሲንቅ፤
ሞታ ቀርታለች ሲል ፥ ልሣነ መናፍቅ!!
@mgetem
@mgetem
(በከሳቴብርሃን)
ቅዱስ ያሬድ ሊቁ፤
በሕይወት እናት ሞት ታየ መደነቁ::
እንዲህ በሚል ቃሉ፤
”ሞታ ለማርያም የዓፅብ ለኵሉ“::
ሞትስ ፥ጌታም ቀምሷል፤
የጥሉን ግድግዳ ፥ በመስቀል አፍርሷል::
ታዲያ፤
ሞታ ከመ ወልዳ፤
የነፍሳተ ሲኦል ፥ማምለጫ ቀዳዳ፤
የሆነላት ድንግል ፥ እረፍቷ ምን ይደንቅ?
ድንቅስ ፥ ከድንቅም ድንቅ፤
አብዝቶ ሚያስጨንቅ ፥ አልፎም የሚያሳቅቅ፤
የትንሣኤን እናት ፥ ትንሣኤዋን ሲንቅ፤
ሞታ ቀርታለች ሲል ፥ ልሣነ መናፍቅ!!
@mgetem
@mgetem
የሰማዩን ምስክር
🌻🌻🌻🌻🌻🌻
ጨለማን ሰባሪ_ብርሃን ወጥቶብሻል
ሞትን የሚገድል_ትንሳኤን ወልደሻል
ንጽሕ መሶበ ወርቅ_ ድንግል ተብለሻል
ለከበረው ክብርሽ_ስግደት ይገባሻል።
የሰማዩ ምስክር_ የታየው በራማ
በምድራዊው ገነት_ እነሆ ተሰማ
የመልአኩን በስራት_ኤልሳቤጥ ስትደግመው
በሆዷ ያለው ጽንስ_ ደስታ አዘለለው
መጥምቀ መለኮት_ክብሩ ከፍ ያለ ነው።
ለኛ ስለሰጠች _ የሕይወት እንጀራን
ሁሌም ለዘለአለም_ እንወዳታለን
የምስራቋ ደጃፍ_የወለደች ፀሐይ
የኤልሳዕ ማሰሮ_ የበረከት ሲሳይ።
የፍቅር የሰላም _ የምሕረት መገኛ
የምንመካብሽ _ ነይ ነይ ወደ እኛ
ኖርዶስ ቀሲመታት_ በጎ መዓዛ ነሽ
የአማኑኤል ማደሪያ_ የለም የሚመስልሽ።
ጌታዬ ከሰጠኝ_ እናቴ እልሻለው
የመንገድ ስንቄ ነሽ_ እመካብሻለው
ለጠየኩሽ ሁሉ _ መልስ የምትሰጪኝ
እንዳልነዋወጥ_ በዐለቱ ትከይኝ።
በመከራ ጊዜ _ መሸሸጊያ ሆኖን
የመከራን ባሕር_ በፍቅሩ አሻግሮን
እንደበደላችን_ ሳያጠፋን ጌታ
አቆመን በደጁ_ ሞልቶን በእልልታ።
ከኛ የበረታችሁ _ አስቡን በጸሎት
በስጋ ፈተና _ እንዳይገለን ምቾች
በሄድንበት ሁሉ_ እንዲገጥመን ሰላም
ፍፃሜአችን እንዲያምር_አማልጅን ማርያም።
የተሰቀለውን _በገና አውርዱ
መሰንቆ ክራሩን_ ከበሮ አሰናዱ
መቆሚያ ጽናጽል_ ይታደል ለሁሉም
በያሬድ ውብ ዜማ_በሚያስረሳ ዓለም
ተነሱ እንዘምር_ ለመድኃኒዓለም።
እንዲህ እናምናለን_ እንታመናለን
በተበተንበት በባዕዱ ምድር_ እንመሰክራለን
የሥላሴን ጥበብ_ ትውልድ እንዲረዳ
ይምጣና ይመገብ_ ከእናቱ ጓዳ
ኋላ ለጥያቄ _እነዳይሆን እንግዳ ትጉኃን
በዝማሬው ጣዕም_ተሞልተን ደስታ
በተዋሕዶነቷም _ ነፍሳችን ተጽናንታ
በቃሉ ምስክር _ ቀርቦልን ማዕድ
በወልድ እናት ምልጃ _በሕይወት መንገድ
ከቅድስት ምድራችን _በመጡት
በደጀ ሰላሙ አለን_ ተሰብስበን።
በመረዋ ድምጹ_ በሚስረቀረቀው
ሲሰማ አርነት_ተሰፋን በሚሰብከው
የአባቶችን ምክር_ትዕዛዝ በሚያከብረው
በረጋው አንደበት_ ከቴድሮስ ሰማነው
ኪዳነምሕረት_ በእቅፏ ታኑረው።
ከዕርስታችን ወተን_ ብንኖርም በእሩቅ
መተላለፋችን_ በስሙ እንዲፋቅ
ክብር ሞገስ ሆነን_ ስራው የሚያስደንቅ።
ሀይማኖት ከምግባር_የነፃነት በፍታ
የሚያስተምር ፍቅር_ ጠዋትና ማታ
የወንጌል አርበኛ_ የሚያስር የሚፈታ
ደጀንን ሸለመን_ የሰራዊት ጌታ።
ለዘመኑ ሕመም_ መድኃኒት ያመርታል
የነፍስ ዶክተር ነው _ትውልድ ይፈውሳል
ብሉይን ከሐዲስ _ እያመሳጠረ
ስንቱን ሐሰተኛ_ ከቤት አባረረ።
በጠላት ተከቦ_ ሲደፈር ተራራው
እንደ ተመረጡት_ በእውነት አብበው
ወንጌልን ተጫምቶ_ በብዕር ይሻገራል
በለበሰው ሞገስ_ ሁሉን ያስደምማል
___________________________
@Mgetem
@Mgetem
@Scgpx
🌻🌻🌻🌻🌻🌻
ጨለማን ሰባሪ_ብርሃን ወጥቶብሻል
ሞትን የሚገድል_ትንሳኤን ወልደሻል
ንጽሕ መሶበ ወርቅ_ ድንግል ተብለሻል
ለከበረው ክብርሽ_ስግደት ይገባሻል።
የሰማዩ ምስክር_ የታየው በራማ
በምድራዊው ገነት_ እነሆ ተሰማ
የመልአኩን በስራት_ኤልሳቤጥ ስትደግመው
በሆዷ ያለው ጽንስ_ ደስታ አዘለለው
መጥምቀ መለኮት_ክብሩ ከፍ ያለ ነው።
ለኛ ስለሰጠች _ የሕይወት እንጀራን
ሁሌም ለዘለአለም_ እንወዳታለን
የምስራቋ ደጃፍ_የወለደች ፀሐይ
የኤልሳዕ ማሰሮ_ የበረከት ሲሳይ።
የፍቅር የሰላም _ የምሕረት መገኛ
የምንመካብሽ _ ነይ ነይ ወደ እኛ
ኖርዶስ ቀሲመታት_ በጎ መዓዛ ነሽ
የአማኑኤል ማደሪያ_ የለም የሚመስልሽ።
ጌታዬ ከሰጠኝ_ እናቴ እልሻለው
የመንገድ ስንቄ ነሽ_ እመካብሻለው
ለጠየኩሽ ሁሉ _ መልስ የምትሰጪኝ
እንዳልነዋወጥ_ በዐለቱ ትከይኝ።
በመከራ ጊዜ _ መሸሸጊያ ሆኖን
የመከራን ባሕር_ በፍቅሩ አሻግሮን
እንደበደላችን_ ሳያጠፋን ጌታ
አቆመን በደጁ_ ሞልቶን በእልልታ።
ከኛ የበረታችሁ _ አስቡን በጸሎት
በስጋ ፈተና _ እንዳይገለን ምቾች
በሄድንበት ሁሉ_ እንዲገጥመን ሰላም
ፍፃሜአችን እንዲያምር_አማልጅን ማርያም።
የተሰቀለውን _በገና አውርዱ
መሰንቆ ክራሩን_ ከበሮ አሰናዱ
መቆሚያ ጽናጽል_ ይታደል ለሁሉም
በያሬድ ውብ ዜማ_በሚያስረሳ ዓለም
ተነሱ እንዘምር_ ለመድኃኒዓለም።
እንዲህ እናምናለን_ እንታመናለን
በተበተንበት በባዕዱ ምድር_ እንመሰክራለን
የሥላሴን ጥበብ_ ትውልድ እንዲረዳ
ይምጣና ይመገብ_ ከእናቱ ጓዳ
ኋላ ለጥያቄ _እነዳይሆን እንግዳ ትጉኃን
በዝማሬው ጣዕም_ተሞልተን ደስታ
በተዋሕዶነቷም _ ነፍሳችን ተጽናንታ
በቃሉ ምስክር _ ቀርቦልን ማዕድ
በወልድ እናት ምልጃ _በሕይወት መንገድ
ከቅድስት ምድራችን _በመጡት
በደጀ ሰላሙ አለን_ ተሰብስበን።
በመረዋ ድምጹ_ በሚስረቀረቀው
ሲሰማ አርነት_ተሰፋን በሚሰብከው
የአባቶችን ምክር_ትዕዛዝ በሚያከብረው
በረጋው አንደበት_ ከቴድሮስ ሰማነው
ኪዳነምሕረት_ በእቅፏ ታኑረው።
ከዕርስታችን ወተን_ ብንኖርም በእሩቅ
መተላለፋችን_ በስሙ እንዲፋቅ
ክብር ሞገስ ሆነን_ ስራው የሚያስደንቅ።
ሀይማኖት ከምግባር_የነፃነት በፍታ
የሚያስተምር ፍቅር_ ጠዋትና ማታ
የወንጌል አርበኛ_ የሚያስር የሚፈታ
ደጀንን ሸለመን_ የሰራዊት ጌታ።
ለዘመኑ ሕመም_ መድኃኒት ያመርታል
የነፍስ ዶክተር ነው _ትውልድ ይፈውሳል
ብሉይን ከሐዲስ _ እያመሳጠረ
ስንቱን ሐሰተኛ_ ከቤት አባረረ።
በጠላት ተከቦ_ ሲደፈር ተራራው
እንደ ተመረጡት_ በእውነት አብበው
ወንጌልን ተጫምቶ_ በብዕር ይሻገራል
በለበሰው ሞገስ_ ሁሉን ያስደምማል
___________________________
@Mgetem
@Mgetem
@Scgpx
👍4❤3
#መጎዳቴን_አይቶ
@Mgetem
መጎዳቴን አይቶ
ሊቀይር ታሪኬን
ካለሁበት መጥቶ
ሊሞላው ጓዳዬን
መዳን ትወዳለህ ?
ብሎ ቢጠይቀኝ
የሰለለ አካሌን
በአይኔ እያማተርኩኝ
እወዳለሁ ! አልኩት
መፈወስን ሽቼ
የመጥምቁ አምላክ
መሆኑን ሰምቼ፡፡
የጫማውን ጠፍር
መፍታት የተሳነው
ዛሬ ሽባ እግሮቼን
መፈወስ ተቻለው፡፡
ዳንኩኝ በጸበሉ
በእጁ ተጠምቄ
ለምስክር በቃው
በምልጃው ደምቄ፡፡
ከረዳኢ ሃዱሽ
_______________________
@Mgetem
@Mgetem
@Scgpx
@Mgetem
መጎዳቴን አይቶ
ሊቀይር ታሪኬን
ካለሁበት መጥቶ
ሊሞላው ጓዳዬን
መዳን ትወዳለህ ?
ብሎ ቢጠይቀኝ
የሰለለ አካሌን
በአይኔ እያማተርኩኝ
እወዳለሁ ! አልኩት
መፈወስን ሽቼ
የመጥምቁ አምላክ
መሆኑን ሰምቼ፡፡
የጫማውን ጠፍር
መፍታት የተሳነው
ዛሬ ሽባ እግሮቼን
መፈወስ ተቻለው፡፡
ዳንኩኝ በጸበሉ
በእጁ ተጠምቄ
ለምስክር በቃው
በምልጃው ደምቄ፡፡
ከረዳኢ ሃዱሽ
_______________________
@Mgetem
@Mgetem
@Scgpx
👍5❤1
በምህረቱ መራኝ
ትላንት ነበርኩኝ እያለው የሌለው
እንዳማረ ተክል ፍሬ እንደሌለው
ደስታዬም ነበረ ለሞቴ መንገዱ
ህይወቴም ሚመስሉ አንዳች ያልተጎዱ
እውነታው ባይገባኝ የመኖሬ ምክንያት
እጆቼን ዘረጋው እምባዬም ፈሰሰ
ጉልበቴም ታዘዙ ለዳንስ እንዳልተነሱ
ልሳኔም በቃሉ ይቅርታን ለመነ
የወደቀልኝን እርሱን አገነነ
መውደቄን ተረድቶ የማይለኝ ችላ
አምላከ ብርሃን ህይወቴን አጎላ
በመሃሪነቱ ምህረቱን ሽሮኝ
ለህይወቴ ፍዳ መፍትሄው ሆነኝ
ጥር 23/2011
*በምንቴ/የአብስራ
___________
@Mgetem
ትላንት ነበርኩኝ እያለው የሌለው
እንዳማረ ተክል ፍሬ እንደሌለው
ደስታዬም ነበረ ለሞቴ መንገዱ
ህይወቴም ሚመስሉ አንዳች ያልተጎዱ
እውነታው ባይገባኝ የመኖሬ ምክንያት
እጆቼን ዘረጋው እምባዬም ፈሰሰ
ጉልበቴም ታዘዙ ለዳንስ እንዳልተነሱ
ልሳኔም በቃሉ ይቅርታን ለመነ
የወደቀልኝን እርሱን አገነነ
መውደቄን ተረድቶ የማይለኝ ችላ
አምላከ ብርሃን ህይወቴን አጎላ
በመሃሪነቱ ምህረቱን ሽሮኝ
ለህይወቴ ፍዳ መፍትሄው ሆነኝ
ጥር 23/2011
*በምንቴ/የአብስራ
___________
@Mgetem
❤1
#ናፈቀኝ ....
ዲ/ን ዳንኤል ክብረት
@Mgetem
የማለዳ ተመስጦ ... ውዳሴ ማርያም መድገሜ
በልጅነት ልመጣልህ .. ጧት ማታ መፍገምገሜ
ዛሬ ግን ናፍቆት ሆነብኝ .. ተዘረረብኝ አቅሜ
እንቅልፌ ሰላም አጣ .... እባብ ሆነብኝ ሕልሜ ።
.
"እግዚኦ" ሲባል ሰምቼ .. ሳልነሳ ከትራሴ
ድንጋጤ ወረረኝ .. ከእግሬ ጥፍር እስከራሴ
ሰዓታቱን እየሰማሁ ... ተቀሰቀሰ መንፈሴ
ትዝዝ አለኝ ማኅሌቱ ... ስትዋብበት ነፍሴ
የእናቴ ስም ናፈቀኝ ...... የሕርያቆስ ቅዳሴ
.
እራሴንም ስላጣሁት ..... ከቤትህ በመራቄ
እንደ ሎጥ ሚስት መሰልኩኝ ፤ አደባባይ ደርቄ
.
የመዝሙረ-ዳዊት ጸሎት .. አነከተኝ በትዝታ
ነፍሴን ስላስጠማኋት ... አነባችብኝ አብዝታ
እሪሪሪ ብላ አለቀሰች ... በስጋ ወንጭፍ ተገዝታ
.
ናፈቀኝ ትምህርቱ ... የቅዱስ ያሬድ ጸጋ
ቁጥር ዜማ መጮሄ .... አንደበቴ እስኪዘጋ
ዛሬ ላለው ማንነቴ .. ምን ይሆን የ'ኔ ዋጋ ??
.
በከበሮ በጽናጽል ... መዘመሩ ማሸብሸቡ
ጃኖ ለብሶ በመሰለፍ ... ማመርገዱ መወረቡ
የትውስታ ስለት ይዘው ፤ ወደ ልቤ ሰርገው ገቡ
.
አምላኬንም ሳመሰግን .. ወደ ሰማይ አንጋጥጬ
እንዲህ ዛሬ ልቀብረው .. በልቤ ውስጥ ረግጬ
አገልግሎቴ ናፈቀኝ ... ከሁሉ በላይ አስበልጬ
ኮርስ ስማር ትዝ አለኝ ... በዛፉ ስር ተቀምጬ
.
አንገቴ ላይ የታሰረው .. ለምን ነበር ማኅተቤ
ዛሬ ለምን አታለልኩት .. በምክንያት ተንተብትቤ ?
.
ምኑ ነው የሆነብኝ .. ለቤተ መቅደስ እንቅፋት ?
ትዳር ለምን መሰለኝ .. ሜዳ ሆኖ ተዳፋት ?
ልቤ ከብዶ እስከመቼ .. እኖራለሁ በጥፋት ?
ነፍሴንስ ምንበወጣት ... በ'ሳት ጅራፍ ላስገርፋት
.
ድጓ ሲሉ ትርጓሜ ... ብዙ ጊዜ ሰምቻለሁ
ድጓ ሲሉ ትርጓሜ ... ብዙ ጊዜ ሰምቻለሁ
ሰው መስዬ ሲመግቡኝ .. ባ'ይኔ ብሌን አይቻለሁ
ታዲያ ግን ምን ዋጋ አለው .. ማንበብ እንደሁ ትቻለሁ
.
እውነት ነው አይካድም .. አውደ ምኅረት መቀመጤ
ወንጌሉንም እየሰማሁ .... ሳላስበው መመሰጤ
ትዝ ይለኛል አጀንዳዬ ... ከንፈሮቼንም መምጠጤ
.
ጽዋ ቢሉ ዝክረ ሰንበት .. እንዳያልፈን ስንጣራ
ዓርብ ጸሎት ስንሰለፍ .. ነጭ ለብሰን በጋራ
ከትንሹም ከትልቁም ... ስለድኅነት ስናወራ
"ጉዞ" ብለን በባዶ እግር .. ሳንደክም በተራራ
ነጭ ለብሰን ጧፍ ይዘን .. እንደ ኮከብ ስናበራ
አዎ! አስታውሳለሁ ... ስልሳ ፍሬ ስናፈራ
.
ጾም ጸሎቱ ትዝ ይለኛል .. በላያችን ስናጌጠው
በስግደት ተሽቀዳድመን ... ሳጥናኤን ስናመልጠው
ብዙ ነበር በንስሐው ... በቁርባኑ የሚገልጠው
.
ጌታ ሆይ!
ተመልሶ ይላክልኝ ... መንፈሳዊ ጀግንነቴ
በመቅደስህ ዋጋ ይክፈል .. የናቡቴ ልጅነቴ
"እሺ" ብሎ እንዳልሰራው .. አይሁንብኝ ማንነቴ
.
ቀራኒዮ አይረሳኝ ... ችንካር ያለው መስቀሉ
በክቡር ደም ተነክሮ .. ቀይ ሆኖ መንቀልቀሉ
.
እመ ብርሐን በልደቷ .. ትመልሰኝ ወደ ጥንቱ
የቅዱሳን ጥበቃቸው .... አይለየኝ በረከቱ
ናፈቀኝ
ሰነፍ ልቤ እየገዛኝ .. በሞት ሰይፍ በጫጨቀኝ
ይቅር በለኝ አምላኬ! ... ከመቅደስህ አታርቀኝ
በግራ መቆም መረረኝ ፤ አሰልፈኝ በልጅህ ቀኝ
አብርሃምን ላክና ... መልስህን ቶሎ አሳውቀኝ
በራሴ አይን ስደናበር.. መታዘብህ አስጨነቀኝ
የምኅረት ቃል አንደበትህ ፤ ፅኑ ፍቅርህ ናፈቀኝ።
#ሙሐዘ ጥበባት ዲ/ን ዳንኤል ክብረት
___________________________
@Mgetem
@Mgetem
@scgpx
ዲ/ን ዳንኤል ክብረት
@Mgetem
የማለዳ ተመስጦ ... ውዳሴ ማርያም መድገሜ
በልጅነት ልመጣልህ .. ጧት ማታ መፍገምገሜ
ዛሬ ግን ናፍቆት ሆነብኝ .. ተዘረረብኝ አቅሜ
እንቅልፌ ሰላም አጣ .... እባብ ሆነብኝ ሕልሜ ።
.
"እግዚኦ" ሲባል ሰምቼ .. ሳልነሳ ከትራሴ
ድንጋጤ ወረረኝ .. ከእግሬ ጥፍር እስከራሴ
ሰዓታቱን እየሰማሁ ... ተቀሰቀሰ መንፈሴ
ትዝዝ አለኝ ማኅሌቱ ... ስትዋብበት ነፍሴ
የእናቴ ስም ናፈቀኝ ...... የሕርያቆስ ቅዳሴ
.
እራሴንም ስላጣሁት ..... ከቤትህ በመራቄ
እንደ ሎጥ ሚስት መሰልኩኝ ፤ አደባባይ ደርቄ
.
የመዝሙረ-ዳዊት ጸሎት .. አነከተኝ በትዝታ
ነፍሴን ስላስጠማኋት ... አነባችብኝ አብዝታ
እሪሪሪ ብላ አለቀሰች ... በስጋ ወንጭፍ ተገዝታ
.
ናፈቀኝ ትምህርቱ ... የቅዱስ ያሬድ ጸጋ
ቁጥር ዜማ መጮሄ .... አንደበቴ እስኪዘጋ
ዛሬ ላለው ማንነቴ .. ምን ይሆን የ'ኔ ዋጋ ??
.
በከበሮ በጽናጽል ... መዘመሩ ማሸብሸቡ
ጃኖ ለብሶ በመሰለፍ ... ማመርገዱ መወረቡ
የትውስታ ስለት ይዘው ፤ ወደ ልቤ ሰርገው ገቡ
.
አምላኬንም ሳመሰግን .. ወደ ሰማይ አንጋጥጬ
እንዲህ ዛሬ ልቀብረው .. በልቤ ውስጥ ረግጬ
አገልግሎቴ ናፈቀኝ ... ከሁሉ በላይ አስበልጬ
ኮርስ ስማር ትዝ አለኝ ... በዛፉ ስር ተቀምጬ
.
አንገቴ ላይ የታሰረው .. ለምን ነበር ማኅተቤ
ዛሬ ለምን አታለልኩት .. በምክንያት ተንተብትቤ ?
.
ምኑ ነው የሆነብኝ .. ለቤተ መቅደስ እንቅፋት ?
ትዳር ለምን መሰለኝ .. ሜዳ ሆኖ ተዳፋት ?
ልቤ ከብዶ እስከመቼ .. እኖራለሁ በጥፋት ?
ነፍሴንስ ምንበወጣት ... በ'ሳት ጅራፍ ላስገርፋት
.
ድጓ ሲሉ ትርጓሜ ... ብዙ ጊዜ ሰምቻለሁ
ድጓ ሲሉ ትርጓሜ ... ብዙ ጊዜ ሰምቻለሁ
ሰው መስዬ ሲመግቡኝ .. ባ'ይኔ ብሌን አይቻለሁ
ታዲያ ግን ምን ዋጋ አለው .. ማንበብ እንደሁ ትቻለሁ
.
እውነት ነው አይካድም .. አውደ ምኅረት መቀመጤ
ወንጌሉንም እየሰማሁ .... ሳላስበው መመሰጤ
ትዝ ይለኛል አጀንዳዬ ... ከንፈሮቼንም መምጠጤ
.
ጽዋ ቢሉ ዝክረ ሰንበት .. እንዳያልፈን ስንጣራ
ዓርብ ጸሎት ስንሰለፍ .. ነጭ ለብሰን በጋራ
ከትንሹም ከትልቁም ... ስለድኅነት ስናወራ
"ጉዞ" ብለን በባዶ እግር .. ሳንደክም በተራራ
ነጭ ለብሰን ጧፍ ይዘን .. እንደ ኮከብ ስናበራ
አዎ! አስታውሳለሁ ... ስልሳ ፍሬ ስናፈራ
.
ጾም ጸሎቱ ትዝ ይለኛል .. በላያችን ስናጌጠው
በስግደት ተሽቀዳድመን ... ሳጥናኤን ስናመልጠው
ብዙ ነበር በንስሐው ... በቁርባኑ የሚገልጠው
.
ጌታ ሆይ!
ተመልሶ ይላክልኝ ... መንፈሳዊ ጀግንነቴ
በመቅደስህ ዋጋ ይክፈል .. የናቡቴ ልጅነቴ
"እሺ" ብሎ እንዳልሰራው .. አይሁንብኝ ማንነቴ
.
ቀራኒዮ አይረሳኝ ... ችንካር ያለው መስቀሉ
በክቡር ደም ተነክሮ .. ቀይ ሆኖ መንቀልቀሉ
.
እመ ብርሐን በልደቷ .. ትመልሰኝ ወደ ጥንቱ
የቅዱሳን ጥበቃቸው .... አይለየኝ በረከቱ
ናፈቀኝ
ሰነፍ ልቤ እየገዛኝ .. በሞት ሰይፍ በጫጨቀኝ
ይቅር በለኝ አምላኬ! ... ከመቅደስህ አታርቀኝ
በግራ መቆም መረረኝ ፤ አሰልፈኝ በልጅህ ቀኝ
አብርሃምን ላክና ... መልስህን ቶሎ አሳውቀኝ
በራሴ አይን ስደናበር.. መታዘብህ አስጨነቀኝ
የምኅረት ቃል አንደበትህ ፤ ፅኑ ፍቅርህ ናፈቀኝ።
#ሙሐዘ ጥበባት ዲ/ን ዳንኤል ክብረት
___________________________
@Mgetem
@Mgetem
@scgpx
👍10❤3🥰1🤬1
ሩጫ ✞............🏃🏃🏃🏃
ማልያህን ታጠቅ
ቀበቶህን አጥብቅ
ጫማህን አጠባብቅ
መስመርህን ጠብቅ
አትይ ወደ ኋላ
ተብሎ ተነግሮን
ጀምረን ሩጫ
ለመቀበል ዋንጫ
እኛ ዞርን ስናይ
እነሱ ፈጠኑ
ከሽልማት ጌታ ጽዋም ተቀበሉ።
@Mgeteme
ማልያህን ታጠቅ
ቀበቶህን አጥብቅ
ጫማህን አጠባብቅ
መስመርህን ጠብቅ
አትይ ወደ ኋላ
ተብሎ ተነግሮን
ጀምረን ሩጫ
ለመቀበል ዋንጫ
እኛ ዞርን ስናይ
እነሱ ፈጠኑ
ከሽልማት ጌታ ጽዋም ተቀበሉ።
@Mgeteme
👍3
#ዳግም_ምን_አሏቸው?
/መነባንብ/
@Mgetem
እናታለም ተዋህዶ
ባንችነትሽ የሚኮራ
በስምሽ ስም የሚጠራ
ዛሬ ጠፋ የሚያበራ
ስለፍቅርሽ ቀልጠው ነደው
ስለ አምላካቸው ተማግደው
በሃይማኖት ፍቅር እጅጉን ተነክተው
ካንቺ ጉያ በኖሩ
እግሮችሽ ስር በተማሩ
ለምን/2/ ተዋህዶ ጠላቸው መንደሩ
ምን አሏቸው ደግሞ ቅዱሳን አበውን
አንቺን እናት እምነት ከዚህ ያበቁትን
ምን አሏቸው ደግሞ አበው ሊቃውንትን
አንድምታውን ፈተው ባመሰጠሩልን
ሚስጢርን መሰጥርው ለኛ ባኖሩልን
ብራና ወጥረው አምድ በፃፉልን
ውለታቸው ታዲያ ይህ ነው?
ስላደረጉልን የምንከፍለው
ጭራሽማ አምላክ ባከበራቸው
አክሊሉን በደፋላቸው
በሀሴት በተቀበላቸው
ልባችን ለምን አመፀ ለምንድን ማይቀበል
ተፈትኖ ያለውን የተፃፈላቸውን የህይወት ገድል
ለምንድን! የማናምን በምልጃቸው
እሱ እግዚአብሔር በሰጣቸው
ደግሞስ ምን አሏቸው?
እሄ......./በለቅሶ/
ሁሌም እውነት ነው
መልከ መልካም ሙሽራዋ
የፀናች በድንግልናዋ
ማን አለ እንደዝች እንደ ቅድስት እናት
ያልተረታ በነገስታት
አንገቷን ለሰይፍ የሠጠች
ክርስቶስን ብላ የኖረች
እኮስ ምን አሏት ይህችን እናት
የስጋ ፋላጎት ያልሠበራት።
ተዋህዶ እናት አለም
እንደድሮ ፀንቶ የሚኖር ልጆችሽ ፈርተዋል የሉም
የምልጃ ታላቅ ስራ
ለህዝቦቿ እያበራ
እየለመኑ ምህረት
ሲያስተዳድሩ አናብርቱ አናብስቱን
ከባህር ውስጥ የፀለዩ
በስራቸው የተለዩ
ገብረ መንፈስ ቅዱስ ታላቅ አባት
ምን አሏቸው ይሆን አንቺ ምስኪን እምነት
አይደል እንዴ ተዋሕዶ
ስጋቸውን የገበሩ
በእርኩሳን መናፍስት የተፈሩ
በእግዜር ጥበብ የከበሩ
ምን አሏቸው ቅዱሳንን ሰማዕታት ፃድቃናትን
የክርስቶስ ደቀመዝሙር ሃዋርያት
ትንቢት ፀሀፊ ነቢያት
ተዋህዶ ውዷ እናቴ ምን አሏቸው?
በዕቶን ውስጥ ማግደዋቸው
እንደ እንስሳ አረደዋቸው
በቁም ቆመው ቆዳቸውንገፈዋቸው
ላንቺ ቋሚ ልጆችሽን ምን አሏቸው
አይ ተዋህዶ....
በአንድ እግራቸው ሰባት ዓመት የፀለዩ
ባንቺ የፍቅር መግቦትሽ ከዓለም ላይ የተለዩ
የተክለሃይማኖት እናት አንቺ ቅድስት እምነት
አያማልዱም ሲላቸው ልጆችሽን
ዛሬ ምን ተሰማሽ ንገሪኝ በእውነት
የልጆችሽን ምልጃ ሊያስታርቅ ሊቃትት
መቻል ደጉ....
ስንቱን ቻልሽው እናታለም....
እሄ......
የእመብርሃን አስራት ኢትዮጵያ
የቅዱሳን የፃድቃን መፍለቂያ
አንቺስ ጋር ምን አሏቸው
መሠረቶችሽን ሲገፏቸው
ምን አልሻቸው ይሆን እንደው ዝም አልሻቸው
የመኖሬ ምስጢር
የመኖሬ ዘመን እምነቴ እሷናት ብለሽ ሳትነግሪያቸው
የቅዱሳንን ምልጃ የፃድቃንን ምልጃ ሳታሰተምሪያቸው
ለዚህ ይሆን አማላጅ አይደሉም ብለው የናቋቸው
ለነገሩ አይደለም
ስንቴ አስተማርሻቸው
በግልጽ አሳይተሽ አስቀምጠሽላቸው
ሰብከሻቸው ነበር ጊዜ ነጎደና በመናፍቅ እስር
የማማላዳቸው ያን ሁሉ ምስክር
ቀበሩት ከአፈር
እና ተዋህዶ ያንቺን ጓዳ የሚያውቁ
በፍቅርሽ ማነቆ የታነቁ
ቀስ በቀስ ወጡ እያለቁ
አሁንማ እናቴ
ባንቺ ጉያ እየኖሩ
አንቺንም እያሳፈሩ
ፈሉብሽ እንደ አሸን ቅዱሳንሽን እየካዱ
አያማልዱም ብለው ረግጠው እየሄዱ
ታዲያ ምን አሏቸው
ያንቺን ልጆች በቤታቸው
ዛሬስ ምን አሏቸው???
ወስብሐት ለእግዚአብሔር!
#ከሙሉብርሃን_የማነ
____________________________
@Mgetem
@Mgetem
@Scgpx
/መነባንብ/
@Mgetem
እናታለም ተዋህዶ
ባንችነትሽ የሚኮራ
በስምሽ ስም የሚጠራ
ዛሬ ጠፋ የሚያበራ
ስለፍቅርሽ ቀልጠው ነደው
ስለ አምላካቸው ተማግደው
በሃይማኖት ፍቅር እጅጉን ተነክተው
ካንቺ ጉያ በኖሩ
እግሮችሽ ስር በተማሩ
ለምን/2/ ተዋህዶ ጠላቸው መንደሩ
ምን አሏቸው ደግሞ ቅዱሳን አበውን
አንቺን እናት እምነት ከዚህ ያበቁትን
ምን አሏቸው ደግሞ አበው ሊቃውንትን
አንድምታውን ፈተው ባመሰጠሩልን
ሚስጢርን መሰጥርው ለኛ ባኖሩልን
ብራና ወጥረው አምድ በፃፉልን
ውለታቸው ታዲያ ይህ ነው?
ስላደረጉልን የምንከፍለው
ጭራሽማ አምላክ ባከበራቸው
አክሊሉን በደፋላቸው
በሀሴት በተቀበላቸው
ልባችን ለምን አመፀ ለምንድን ማይቀበል
ተፈትኖ ያለውን የተፃፈላቸውን የህይወት ገድል
ለምንድን! የማናምን በምልጃቸው
እሱ እግዚአብሔር በሰጣቸው
ደግሞስ ምን አሏቸው?
እሄ......./በለቅሶ/
ሁሌም እውነት ነው
መልከ መልካም ሙሽራዋ
የፀናች በድንግልናዋ
ማን አለ እንደዝች እንደ ቅድስት እናት
ያልተረታ በነገስታት
አንገቷን ለሰይፍ የሠጠች
ክርስቶስን ብላ የኖረች
እኮስ ምን አሏት ይህችን እናት
የስጋ ፋላጎት ያልሠበራት።
ተዋህዶ እናት አለም
እንደድሮ ፀንቶ የሚኖር ልጆችሽ ፈርተዋል የሉም
የምልጃ ታላቅ ስራ
ለህዝቦቿ እያበራ
እየለመኑ ምህረት
ሲያስተዳድሩ አናብርቱ አናብስቱን
ከባህር ውስጥ የፀለዩ
በስራቸው የተለዩ
ገብረ መንፈስ ቅዱስ ታላቅ አባት
ምን አሏቸው ይሆን አንቺ ምስኪን እምነት
አይደል እንዴ ተዋሕዶ
ስጋቸውን የገበሩ
በእርኩሳን መናፍስት የተፈሩ
በእግዜር ጥበብ የከበሩ
ምን አሏቸው ቅዱሳንን ሰማዕታት ፃድቃናትን
የክርስቶስ ደቀመዝሙር ሃዋርያት
ትንቢት ፀሀፊ ነቢያት
ተዋህዶ ውዷ እናቴ ምን አሏቸው?
በዕቶን ውስጥ ማግደዋቸው
እንደ እንስሳ አረደዋቸው
በቁም ቆመው ቆዳቸውንገፈዋቸው
ላንቺ ቋሚ ልጆችሽን ምን አሏቸው
አይ ተዋህዶ....
በአንድ እግራቸው ሰባት ዓመት የፀለዩ
ባንቺ የፍቅር መግቦትሽ ከዓለም ላይ የተለዩ
የተክለሃይማኖት እናት አንቺ ቅድስት እምነት
አያማልዱም ሲላቸው ልጆችሽን
ዛሬ ምን ተሰማሽ ንገሪኝ በእውነት
የልጆችሽን ምልጃ ሊያስታርቅ ሊቃትት
መቻል ደጉ....
ስንቱን ቻልሽው እናታለም....
እሄ......
የእመብርሃን አስራት ኢትዮጵያ
የቅዱሳን የፃድቃን መፍለቂያ
አንቺስ ጋር ምን አሏቸው
መሠረቶችሽን ሲገፏቸው
ምን አልሻቸው ይሆን እንደው ዝም አልሻቸው
የመኖሬ ምስጢር
የመኖሬ ዘመን እምነቴ እሷናት ብለሽ ሳትነግሪያቸው
የቅዱሳንን ምልጃ የፃድቃንን ምልጃ ሳታሰተምሪያቸው
ለዚህ ይሆን አማላጅ አይደሉም ብለው የናቋቸው
ለነገሩ አይደለም
ስንቴ አስተማርሻቸው
በግልጽ አሳይተሽ አስቀምጠሽላቸው
ሰብከሻቸው ነበር ጊዜ ነጎደና በመናፍቅ እስር
የማማላዳቸው ያን ሁሉ ምስክር
ቀበሩት ከአፈር
እና ተዋህዶ ያንቺን ጓዳ የሚያውቁ
በፍቅርሽ ማነቆ የታነቁ
ቀስ በቀስ ወጡ እያለቁ
አሁንማ እናቴ
ባንቺ ጉያ እየኖሩ
አንቺንም እያሳፈሩ
ፈሉብሽ እንደ አሸን ቅዱሳንሽን እየካዱ
አያማልዱም ብለው ረግጠው እየሄዱ
ታዲያ ምን አሏቸው
ያንቺን ልጆች በቤታቸው
ዛሬስ ምን አሏቸው???
ወስብሐት ለእግዚአብሔር!
#ከሙሉብርሃን_የማነ
____________________________
@Mgetem
@Mgetem
@Scgpx
👍3❤2😢1
\\ልቤ_ሰላም_አርገልኝ//
ቸር ጠባቂ የሰራዊት ጌታ
ቀና ስል የማይህ በጥዋት በማታ
በረከትህ ብዙ ስጦታህን የማያልቅ
የማይደርቅ ምንጭህ ፍፅም
ክፉ ስራችን አይተህ ሳትፈርድብን
ሳትቆጣን በምህረትህ በቸርነትህን
ከዘመን ዘመን አሻገርከን ተመስገን
የሚደነቅ፦
ብላቴና ሳትል ታላቁን አዛውንት
ቀሳውስቱን ሳትል ታላቁን ሊቃውንት
ሁለን በየፍርዱ ታሰድስተዋለህ
በፀጋህ በፍቅርህ ትባርከዋለህ
እኔም ልመና አለኝ ሳለሁ በመቅደስህ
በወርቁ ማጠኛ በመሰቀሉ እንዳይህ
ልበ ሰላም አርገልኝ ባርከኝ በእጅህ"።
አቤቱ_አምላኬ_ሆይ_የመጠሪያዩን_ዘመን_አላዉቀውምና_ለንሰሐ_ሞት_አበቃኝ_ዘንድ_ቅዱስ_ፍቃድህ_ይሁን_ኣሜን፫
ወስብሓት_ለእግዚአብሔር
ወለወላዲቱ_ድንግል ወለመስቀሉ_ክብር_ይቆየን_አሜን፫
*ከእህተ ማርያም
=====================
@Mgetem
ቸር ጠባቂ የሰራዊት ጌታ
ቀና ስል የማይህ በጥዋት በማታ
በረከትህ ብዙ ስጦታህን የማያልቅ
የማይደርቅ ምንጭህ ፍፅም
ክፉ ስራችን አይተህ ሳትፈርድብን
ሳትቆጣን በምህረትህ በቸርነትህን
ከዘመን ዘመን አሻገርከን ተመስገን
የሚደነቅ፦
ብላቴና ሳትል ታላቁን አዛውንት
ቀሳውስቱን ሳትል ታላቁን ሊቃውንት
ሁለን በየፍርዱ ታሰድስተዋለህ
በፀጋህ በፍቅርህ ትባርከዋለህ
እኔም ልመና አለኝ ሳለሁ በመቅደስህ
በወርቁ ማጠኛ በመሰቀሉ እንዳይህ
ልበ ሰላም አርገልኝ ባርከኝ በእጅህ"።
አቤቱ_አምላኬ_ሆይ_የመጠሪያዩን_ዘመን_አላዉቀውምና_ለንሰሐ_ሞት_አበቃኝ_ዘንድ_ቅዱስ_ፍቃድህ_ይሁን_ኣሜን፫
ወስብሓት_ለእግዚአብሔር
ወለወላዲቱ_ድንግል ወለመስቀሉ_ክብር_ይቆየን_አሜን፫
*ከእህተ ማርያም
=====================
@Mgetem
👍2❤1
#የቱ_ላይ_ነው_ፍቅርህ?
@Mgetem
በጥጋቡ ዘመን አብሬክ ታድሜ
ስጠማ ጠጥቼ ስራብ ተመግቤ
ላልክድህ ምያለው ከቤትህ ላልርቅ
በሰው ፊት መስክሬ ኪዳንህን ልጠብቅ
አሁን ትቼክ ከሄድኩ ቀራንዮ ሳለህ
ብለህ ስጠይቀኝ የቱ ላይ ነው ፍቅርህ
ጌታዬ ጨነቀኝ ምን ልመልስልህ
.
.
.
ዘወትር ስጠራኝ ዘውትር ሳንቀላፋ
ሁሌ ስትፈልገኝ ሁልጊዜ ስጠፋ
አንተ ከእኔ ስርቅ ኃጢአትን ስለምዳት
ሶስት የዶሮ ጬኸት ሲያልፈኝ እንደዘበት
ብለህ ስጠይቀኝ ምኑ ላይ ነው ፍቅርህ
ጌታዬ ጨነቀኝ ምን ልመልስልህ
.
.
ምትህ ሞቴን ሲሽር ስቃይህ ስቃዬን ስደት ስደቴን
የርህራሄ ጥልቀት የፍቅርህ ስፋቱ
ሳይረዳኝ ሲቀር እንዲው እንደከንቱ
ይህን ተገንዝበህ ብለህ ስጠይቀኝ የቱ ላይ ነው ፍቅርህ
ጌታዬ ጨነቀኝ ምን ልመልስልህ
.
.
እንባዬ ሲታበስ ጭንቀቴ ሲፈታ
ፈጥነህ ስደርስልኝ የጠራሁ ለታ
ቀይ ባህር ሲከፈል ፈርኦንም ሰጥሞ ሲቀር
ከበሮ እየመታሁ በደስታ ስዘምር
ቆይቼ -ቆይቼ-ሁሉን እረስቼ
ሃጢአት ውስጥ ገብቼ ጣኦት አረስቼ
ስክድህ ስታየኝ ውሌን በጥሼብህ
ብለህ ስትጠይቀኝ የቱ ላይ ነው ፍቅርህ
ጌታዬ ጨነቀኝ ምን ልመልስልህ።
__________________________
@Mgetem
@Mgetem
@Menfesawi_getem_bot
@Mgetem
በጥጋቡ ዘመን አብሬክ ታድሜ
ስጠማ ጠጥቼ ስራብ ተመግቤ
ላልክድህ ምያለው ከቤትህ ላልርቅ
በሰው ፊት መስክሬ ኪዳንህን ልጠብቅ
አሁን ትቼክ ከሄድኩ ቀራንዮ ሳለህ
ብለህ ስጠይቀኝ የቱ ላይ ነው ፍቅርህ
ጌታዬ ጨነቀኝ ምን ልመልስልህ
.
.
.
ዘወትር ስጠራኝ ዘውትር ሳንቀላፋ
ሁሌ ስትፈልገኝ ሁልጊዜ ስጠፋ
አንተ ከእኔ ስርቅ ኃጢአትን ስለምዳት
ሶስት የዶሮ ጬኸት ሲያልፈኝ እንደዘበት
ብለህ ስጠይቀኝ ምኑ ላይ ነው ፍቅርህ
ጌታዬ ጨነቀኝ ምን ልመልስልህ
.
.
ምትህ ሞቴን ሲሽር ስቃይህ ስቃዬን ስደት ስደቴን
የርህራሄ ጥልቀት የፍቅርህ ስፋቱ
ሳይረዳኝ ሲቀር እንዲው እንደከንቱ
ይህን ተገንዝበህ ብለህ ስጠይቀኝ የቱ ላይ ነው ፍቅርህ
ጌታዬ ጨነቀኝ ምን ልመልስልህ
.
.
እንባዬ ሲታበስ ጭንቀቴ ሲፈታ
ፈጥነህ ስደርስልኝ የጠራሁ ለታ
ቀይ ባህር ሲከፈል ፈርኦንም ሰጥሞ ሲቀር
ከበሮ እየመታሁ በደስታ ስዘምር
ቆይቼ -ቆይቼ-ሁሉን እረስቼ
ሃጢአት ውስጥ ገብቼ ጣኦት አረስቼ
ስክድህ ስታየኝ ውሌን በጥሼብህ
ብለህ ስትጠይቀኝ የቱ ላይ ነው ፍቅርህ
ጌታዬ ጨነቀኝ ምን ልመልስልህ።
__________________________
@Mgetem
@Mgetem
@Menfesawi_getem_bot
👍3
#ነበርኩ_መች_ያድናል
@Mgetem
ሀጢያትን ስትሰራ አምላክን እረስተህ
ቅዱሱን ሰውነት በሀጢያት አርክሰህ
ትእዛዝን ሳትፈጽም መልካምን ሳትሰራ
ዘይት ሳታዘጋጅ መብራትህ ሳይበራ
በተጠራህ ጊዜ መላከሞት ሲመጣ
ለማያልፈው አለም ሲወጣልህ እጣ
ለሚዛን ስትቀርብ አገልጋይ ነበርኩኝ እያልክ መናገሩ
መዝሙር ዘምሬያለው ሄጃለው ከበሩ
ብሎ መከራከር ያኔ መች ይጠቅማል
ይዞ መገኘት ነው ነበርኩ መች ያድናል!!!!
____________________________
@Mgetem
@Mgetem
@Menfesawi_getem_bot
@Mgetem
ሀጢያትን ስትሰራ አምላክን እረስተህ
ቅዱሱን ሰውነት በሀጢያት አርክሰህ
ትእዛዝን ሳትፈጽም መልካምን ሳትሰራ
ዘይት ሳታዘጋጅ መብራትህ ሳይበራ
በተጠራህ ጊዜ መላከሞት ሲመጣ
ለማያልፈው አለም ሲወጣልህ እጣ
ለሚዛን ስትቀርብ አገልጋይ ነበርኩኝ እያልክ መናገሩ
መዝሙር ዘምሬያለው ሄጃለው ከበሩ
ብሎ መከራከር ያኔ መች ይጠቅማል
ይዞ መገኘት ነው ነበርኩ መች ያድናል!!!!
____________________________
@Mgetem
@Mgetem
@Menfesawi_getem_bot
#ስጋ_ነው_ምርኩዜ
@Mgetem
ስጋዬ ወፍሮ አፌ ክፉ ደፍሮ
ሓሰትን መስክሮ እውነት ቅሉን ሽሮ
እውነት ተሸሸጋ ማን እውነት ሊያወጋ
ስለ ክፉ ስጋ።
ስለ ክፉ ስጋ ነፍሴ ስትወጋ
የአንደበቴ ችቦ የአንደበቴ ሰንጋ
ነፍሴ ስትቃትት የስጋ ጦር ወግቷት
ቀንም ሌሊትም ቁስሉ ሲያሰቃያት
ጭንቅ ጥብብ አለች ቀኑ ጨልሞባት
የምታውቀው ቤቷ ተዘግቶባት
ስጋ ሲበድላት በሐዘን በትካዜ
በሐሰት ባለሟል በስጋ ምርኩዜ
እኔንም ተረድታ በእምነት መደብዘዜ
በህይወት ልታልፍ ልትጓዝ በግዜ
ነፍሴ የተዘጋጀች ልታቀርብ ኑዛዜ።
____________________________
@Mgetem
@Mgetem
@Menfesawi_getem_bot
@Mgetem
ስጋዬ ወፍሮ አፌ ክፉ ደፍሮ
ሓሰትን መስክሮ እውነት ቅሉን ሽሮ
እውነት ተሸሸጋ ማን እውነት ሊያወጋ
ስለ ክፉ ስጋ።
ስለ ክፉ ስጋ ነፍሴ ስትወጋ
የአንደበቴ ችቦ የአንደበቴ ሰንጋ
ነፍሴ ስትቃትት የስጋ ጦር ወግቷት
ቀንም ሌሊትም ቁስሉ ሲያሰቃያት
ጭንቅ ጥብብ አለች ቀኑ ጨልሞባት
የምታውቀው ቤቷ ተዘግቶባት
ስጋ ሲበድላት በሐዘን በትካዜ
በሐሰት ባለሟል በስጋ ምርኩዜ
እኔንም ተረድታ በእምነት መደብዘዜ
በህይወት ልታልፍ ልትጓዝ በግዜ
ነፍሴ የተዘጋጀች ልታቀርብ ኑዛዜ።
____________________________
@Mgetem
@Mgetem
@Menfesawi_getem_bot
❤3👍1
እንዴት ተሸነፍን ?
✍ከሣቴብርሃን ገ/ኢየሱስ
እንዴት ተሸነፍን?
ለምን እጅ ሰጠን?
የፈቃድ ምርኮኞች አርጎ ማን ለወጠን?
በሥጋ አበው በመንፈስ ጠላት፤
የኾ’ንባትን ግብር ማን ይሆን ልብ ያላት?
እነሆ ምሥክር. . . . . . ከሕያዋን መዝገብ፤
የደም የአጥንት ጽሕፈት ደምቆ ሚታይ ሳይነትብ፤
ዓድዋ ብራና ተገልጦ ይነበብ!
በእምዬ ምኒልክ እምዬ ምትባል፤
በልቡ የምትሣል፤
የከንፈሩ ውብ ቃል፤
የኪዳን ማሠርያ ኾና የምትማል፤
በምልጃ ጸሎቷ በልመናዋ ኃይል፤
ድል ብታቀዳጀው ይኼ ምን ይገርማል?
ለ’ኛም ደበዘዘች የማንነት ፊደል፤
ድል ማንበብ ተስኖን… በዕውር ለዕውር ምሪት ተያይዘን ገደል፤
ወትሮስ የአሣ ግማት ከጭንቅላቱ አይደል?
እንዴት ተሸነፍን?
ለምን እጅ ሰጠን?
ምክንያቱማ ይኸው፤
ልብ ለሚል ልቡ ለሚሰማ ጆሮው::
ቅድመ ምእተ ዓመት..
ለሃገር ለሃይማኖት ሲሆን የሞት ሽረት፤
ለዚያ የቁርጥ ዕለት..
ምን እንደተሠራ ከታሪክ መመልከት!
የጥይት እሩምታ የሞት ጥላ መሃል ያስቀደሰ ቆሞ፤
በእምነት የተዋጋ ታቦት ተሸክሞ፤
የጠገበን ፋሽስት ድራሹን ያጠፋ በባዶ ሆድ ገጥሞ…
እስከ ሠርክ ጦሞ፤
ያ ነበልባል ትውልድ፤
ልጁ ሆነና አመድ፤
“ጊዮርጊስ ታቦት ከንቱ፤
ቤል ጣዖት ውእቱ፤
ይልቅ ጊዮርጊስ ቢራን ብሉ ጠጡ ተደሰቱ!!”
ብሎ የሚሣለቅ ሲነሣ ዛሬ ላይ፤
ጾም ጸሎት ወዲያልኝ ስግደት ለምኔ ባይ ፤
በሑዳዴ ረቡዕ ጮማ ቆራጭ ጠጅ ጣይ፤
ሲነሣ በዛ ባይ ቅዳሴ ረዘመ፤
ለባሕር ማዶ ኳስ ማኅሌት እየቆመ፤
የድል ምዕራፋችን ያኔ አከተመ::
በጓዳችን ሞልቶ የተረፈን ውሰት፤
ከባሕር ማዶ ጫፍ ያማተርን ዕለት፤
አበው በደማቸው የተጋደሉለት፤
የባህል የታሪክ የሃይማኖት ዓለት፤
በቸልታችን ጎርፍ በክሕደት ዓውሎ፤
እንደሚፈራርስ ከሥር ተመንግሎ፤
እንቅጩን በማወቅ ብንነቃ ቶሎ፤
መች መማረክ ነበር እጅ ወደላይ ብሎ?
በግድ ያልተያዘ በፈቃድ ኮብልሎ፡፡
እንዴት ተሸነፍን?
ለምን እጅ ሰጠን?
በሥጋ የአበው በመንፈስ የጠላት፤
የኾን’ባትን ግብር ማን ይሆን ልብ ያላት?
የጉዞ ሥንቃችን ድንግልን የት ተውናት?
ፈረሰኛው ጊዮርጊስ ታቦቱ እንደትናንት፤
ፊት እየቀደመ ድል ማድረግ ወዴት ናት?
ማን ያዘው ጋሻውን ቅዳሴ ሰዓታት፤
ጾም ጸሎት ስግደቱን ገቢረ ትሩፋት::
እንዴት ተሸነፍን?
ለምን እጅ ሰጠን?
23/06/2009 ዓ.ም
@Mgetem
@Mgetem
@Scgpx
✍ከሣቴብርሃን ገ/ኢየሱስ
እንዴት ተሸነፍን?
ለምን እጅ ሰጠን?
የፈቃድ ምርኮኞች አርጎ ማን ለወጠን?
በሥጋ አበው በመንፈስ ጠላት፤
የኾ’ንባትን ግብር ማን ይሆን ልብ ያላት?
እነሆ ምሥክር. . . . . . ከሕያዋን መዝገብ፤
የደም የአጥንት ጽሕፈት ደምቆ ሚታይ ሳይነትብ፤
ዓድዋ ብራና ተገልጦ ይነበብ!
በእምዬ ምኒልክ እምዬ ምትባል፤
በልቡ የምትሣል፤
የከንፈሩ ውብ ቃል፤
የኪዳን ማሠርያ ኾና የምትማል፤
በምልጃ ጸሎቷ በልመናዋ ኃይል፤
ድል ብታቀዳጀው ይኼ ምን ይገርማል?
ለ’ኛም ደበዘዘች የማንነት ፊደል፤
ድል ማንበብ ተስኖን… በዕውር ለዕውር ምሪት ተያይዘን ገደል፤
ወትሮስ የአሣ ግማት ከጭንቅላቱ አይደል?
እንዴት ተሸነፍን?
ለምን እጅ ሰጠን?
ምክንያቱማ ይኸው፤
ልብ ለሚል ልቡ ለሚሰማ ጆሮው::
ቅድመ ምእተ ዓመት..
ለሃገር ለሃይማኖት ሲሆን የሞት ሽረት፤
ለዚያ የቁርጥ ዕለት..
ምን እንደተሠራ ከታሪክ መመልከት!
የጥይት እሩምታ የሞት ጥላ መሃል ያስቀደሰ ቆሞ፤
በእምነት የተዋጋ ታቦት ተሸክሞ፤
የጠገበን ፋሽስት ድራሹን ያጠፋ በባዶ ሆድ ገጥሞ…
እስከ ሠርክ ጦሞ፤
ያ ነበልባል ትውልድ፤
ልጁ ሆነና አመድ፤
“ጊዮርጊስ ታቦት ከንቱ፤
ቤል ጣዖት ውእቱ፤
ይልቅ ጊዮርጊስ ቢራን ብሉ ጠጡ ተደሰቱ!!”
ብሎ የሚሣለቅ ሲነሣ ዛሬ ላይ፤
ጾም ጸሎት ወዲያልኝ ስግደት ለምኔ ባይ ፤
በሑዳዴ ረቡዕ ጮማ ቆራጭ ጠጅ ጣይ፤
ሲነሣ በዛ ባይ ቅዳሴ ረዘመ፤
ለባሕር ማዶ ኳስ ማኅሌት እየቆመ፤
የድል ምዕራፋችን ያኔ አከተመ::
በጓዳችን ሞልቶ የተረፈን ውሰት፤
ከባሕር ማዶ ጫፍ ያማተርን ዕለት፤
አበው በደማቸው የተጋደሉለት፤
የባህል የታሪክ የሃይማኖት ዓለት፤
በቸልታችን ጎርፍ በክሕደት ዓውሎ፤
እንደሚፈራርስ ከሥር ተመንግሎ፤
እንቅጩን በማወቅ ብንነቃ ቶሎ፤
መች መማረክ ነበር እጅ ወደላይ ብሎ?
በግድ ያልተያዘ በፈቃድ ኮብልሎ፡፡
እንዴት ተሸነፍን?
ለምን እጅ ሰጠን?
በሥጋ የአበው በመንፈስ የጠላት፤
የኾን’ባትን ግብር ማን ይሆን ልብ ያላት?
የጉዞ ሥንቃችን ድንግልን የት ተውናት?
ፈረሰኛው ጊዮርጊስ ታቦቱ እንደትናንት፤
ፊት እየቀደመ ድል ማድረግ ወዴት ናት?
ማን ያዘው ጋሻውን ቅዳሴ ሰዓታት፤
ጾም ጸሎት ስግደቱን ገቢረ ትሩፋት::
እንዴት ተሸነፍን?
ለምን እጅ ሰጠን?
23/06/2009 ዓ.ም
@Mgetem
@Mgetem
@Scgpx
👍6❤3
#ለአባ_የትናንቱ
ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
ያለ ማወቅ ጽልመት ሀገሩን ሲወርሰው
ማን ነበር ትውልዱን በወንጌል ያረሰው?
አባ ተክለ ሃይማኖት አባ የትናንቱ
ትዝ አለኝ ተጋድሎው ውል አለኝ ሕይወቱ
በቆላ በደጋ የተንከራተትኸው
የሃይማኖትን ተክል ዞረህ የተከልኸው
የኢትዮጵያ ፀሐይ አባ ተክለ አብ
እስቲ መለስ ብዬ ሥራህን ላስብ
የክህደት ጨለማ በአንተ ሲርቅ
የሃይማኖት ብርሃን ሲያንጸባርቅ
በቀንና ሌሊት ከላይ ታች ዞረህ
ሕዝቡን አደረስከው አስተምረህ መክረህ
ስንት ነበር አባ ‹የጉዞ አበልህ›?
ያረፍህበት ስፍራ የተዘጋጀልህ
የት ነበር መኝታው ጎን ማሳረፊያህ?
ንገረኝ እባክህ ማን ነበር የሸኘህ?
እሳት አባቴ ሆይ እኔ አመድ ልጅህ
በዘመኔ ቋንቋ እስኪ ልጠይቅህ?
@Mgetem
@Mgetem
@Menfesawi_getem_bot
ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
ያለ ማወቅ ጽልመት ሀገሩን ሲወርሰው
ማን ነበር ትውልዱን በወንጌል ያረሰው?
አባ ተክለ ሃይማኖት አባ የትናንቱ
ትዝ አለኝ ተጋድሎው ውል አለኝ ሕይወቱ
በቆላ በደጋ የተንከራተትኸው
የሃይማኖትን ተክል ዞረህ የተከልኸው
የኢትዮጵያ ፀሐይ አባ ተክለ አብ
እስቲ መለስ ብዬ ሥራህን ላስብ
የክህደት ጨለማ በአንተ ሲርቅ
የሃይማኖት ብርሃን ሲያንጸባርቅ
በቀንና ሌሊት ከላይ ታች ዞረህ
ሕዝቡን አደረስከው አስተምረህ መክረህ
ስንት ነበር አባ ‹የጉዞ አበልህ›?
ያረፍህበት ስፍራ የተዘጋጀልህ
የት ነበር መኝታው ጎን ማሳረፊያህ?
ንገረኝ እባክህ ማን ነበር የሸኘህ?
እሳት አባቴ ሆይ እኔ አመድ ልጅህ
በዘመኔ ቋንቋ እስኪ ልጠይቅህ?
@Mgetem
@Mgetem
@Menfesawi_getem_bot
❤2👍1😢1
#እሱ_ነው_እሱ
@Mgetem
ጥንት ያለ የነበረ
ዓለሙን በጥበቡ የመሠረተ
ምድርን በኃይሉ የፈጠረ
ዘመናትን የለካ የቀመረ
ነቢያትን ያናገረ
ኃያል ሱባኤ ያስቀጠረ
ከይስሐቅ ጋር የተሰዋ
እስራኤልን ያከበረ
ከዮናስ ጋር በዓሣ ሆድ
ከዮሴፍ ጋር የታሰረ
እሱ ነው እሱ ለሙሴ
ሕጉን ትእዛዙን ያስተማረ
በተረዳ ሦስትነቱ
በስም በግብሩ በአካላቱ
የሚመለክ በአንድነቱ
በሕልውናው በመለኮቱ
በአገዛዙ በጌትነቱ
እሱ ነው እሱ የጥንት የጠዋቱ
እንዘ አሐዱ ሠለስቱ
በእጹብ ብቻ ይወሰናል
ቀዳማዊ ልደቱ
አይመረመርም ረቂቅ ነው
ዳግማዊ ሰውነቱ
ከወላዲተ-ቃል እናቱ
ግሩም ድንቅ ነው ጥበቡ
ወሰን የለውም ቸርነቱ
ወልደ አብ ወልደ ማርያም
የሰማዩ የመሬቱ
እሱ ነው እሱ አልፋና ዖሜጋ
የሚታዘዙለት መላዕክቱ
የሚታሰብ በቀዳሚ በሳምንቱ
በዘወረደ በቅዳሴው በሰዓታቱ
እሱ ነው እሱ ፍጹም አምላክ ፍጹም ሰው የሆነ
ይጠብቀን በምህረቱ
ስለ እናቱም ከመዓቱ።።።።
___________________________
@Mgetem
@Mgetem
@helansane
@Mgetem
ጥንት ያለ የነበረ
ዓለሙን በጥበቡ የመሠረተ
ምድርን በኃይሉ የፈጠረ
ዘመናትን የለካ የቀመረ
ነቢያትን ያናገረ
ኃያል ሱባኤ ያስቀጠረ
ከይስሐቅ ጋር የተሰዋ
እስራኤልን ያከበረ
ከዮናስ ጋር በዓሣ ሆድ
ከዮሴፍ ጋር የታሰረ
እሱ ነው እሱ ለሙሴ
ሕጉን ትእዛዙን ያስተማረ
በተረዳ ሦስትነቱ
በስም በግብሩ በአካላቱ
የሚመለክ በአንድነቱ
በሕልውናው በመለኮቱ
በአገዛዙ በጌትነቱ
እሱ ነው እሱ የጥንት የጠዋቱ
እንዘ አሐዱ ሠለስቱ
በእጹብ ብቻ ይወሰናል
ቀዳማዊ ልደቱ
አይመረመርም ረቂቅ ነው
ዳግማዊ ሰውነቱ
ከወላዲተ-ቃል እናቱ
ግሩም ድንቅ ነው ጥበቡ
ወሰን የለውም ቸርነቱ
ወልደ አብ ወልደ ማርያም
የሰማዩ የመሬቱ
እሱ ነው እሱ አልፋና ዖሜጋ
የሚታዘዙለት መላዕክቱ
የሚታሰብ በቀዳሚ በሳምንቱ
በዘወረደ በቅዳሴው በሰዓታቱ
እሱ ነው እሱ ፍጹም አምላክ ፍጹም ሰው የሆነ
ይጠብቀን በምህረቱ
ስለ እናቱም ከመዓቱ።።።።
___________________________
@Mgetem
@Mgetem
@helansane
👍3
አዳም ሆይ ንገረኝ
አንተስ አንድ ጊዜ
ትዕዛዝን ተላልፈክ
መለከቱን ሰምተክ
በቃሉ ተመለስክ
እኔስ ስንት ጊዜ
ስንት ጊዜ ወደኩ
ልጅነቴን በእጨት
ሰቅዬ አንጠለጠልኩ
@Mgetem
አንተስ አንድ ጊዜ
ትዕዛዝን ተላልፈክ
መለከቱን ሰምተክ
በቃሉ ተመለስክ
እኔስ ስንት ጊዜ
ስንት ጊዜ ወደኩ
ልጅነቴን በእጨት
ሰቅዬ አንጠለጠልኩ
@Mgetem
❤1
በዜሮ ይባዛል!
ፆም×0=0 ስግደት×0=0
ጸሎት ×0=0
ተግቼ ብጸልይ እጆቼን ዘርግቼ
ቤቴ ባዶ ቢቀር ያለኝን መጽውቼ
ቀኑን ሙሉ ብጾም እስኪቆረጥ አንጀቴ
ዘወትር ብሰግድ እስኪዝል ጉልበቴ
በቀድስ ባስቀድስ በመቅደሱ ግርማ
ብዘምር ባወድስ የሚጣፍጥ ዜማ
ወንጌልን ብሰብክ ምስጢር አመስጥሬ
ብናገር ባስተምር ትርጉሙን ዘርዝሬ
ጥልና ክርክር ካሉ በህይወቴ
ሐሜት ክርክር ካልጠፉ ከቤቴ
በዜሮ ይባዛል ፍቅር በማጣቴ።
ስብሐት ለእግዚአብሔር!
ፆም×ፍቅር= 30 ያማር ፍሬ
ጸሎት×ፍቅር= 60ያማር ፍሬ
ስግደት× ትህትና= 100ያማረ ፍሬ
@Mgetem
ፆም×0=0 ስግደት×0=0
ጸሎት ×0=0
ተግቼ ብጸልይ እጆቼን ዘርግቼ
ቤቴ ባዶ ቢቀር ያለኝን መጽውቼ
ቀኑን ሙሉ ብጾም እስኪቆረጥ አንጀቴ
ዘወትር ብሰግድ እስኪዝል ጉልበቴ
በቀድስ ባስቀድስ በመቅደሱ ግርማ
ብዘምር ባወድስ የሚጣፍጥ ዜማ
ወንጌልን ብሰብክ ምስጢር አመስጥሬ
ብናገር ባስተምር ትርጉሙን ዘርዝሬ
ጥልና ክርክር ካሉ በህይወቴ
ሐሜት ክርክር ካልጠፉ ከቤቴ
በዜሮ ይባዛል ፍቅር በማጣቴ።
ስብሐት ለእግዚአብሔር!
ፆም×ፍቅር= 30 ያማር ፍሬ
ጸሎት×ፍቅር= 60ያማር ፍሬ
ስግደት× ትህትና= 100ያማረ ፍሬ
@Mgetem
👍3❤1
፨ምነው እመብርሃን፨
🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹
አዬ ምነው እመብርሀን
ኢትዮጵያን ጨከንሽባት
ምነው ቀኝሽን እረሳሻት
እስከመቼ ድረስ እንዲህ መቀነትሽን ታጠብቂባት
ልቦናሽን ታዞሪባት
ፈተናዋን ሰቀቀኗን ጣሯን ይበቃል ሳትያት
አላንቺ እኮ ማንም የላት
አውሮፓ እደሁ ትናጋዋን በፋሺስታዊ ነቀርሳ
ታርሳ ተምሳ በስብሳ
ምድራዊ እባጭ ጫንቃዋን እንደ ኮረብታ ተጭኗት
ቀና ብላ እውነት እንዳታይ አንገቷን ቁልቁል ጠምዝዟት
ነፍሷን ድጦ ያስበረከካት ስልጡን ብኩን መፃጉዕ ናት
እና ፈርቼ እንዳልባክን ሲርቀኝ የሀይልሽ ውጋጋን
አንቺ ካጠገቤ አትራቂ በርታ በይኝ እመብርሀን
ቃልኪዳኔን እንዳልረሳት እንዳልዘነጋት ኢትዮጵያን
አዎን ብቻዬን ነኝ ፈራሁ
እሸሸግበት ጥግ አጣሁ
እምፀናበት ልብ አጣሁ
እማማ ኢትዮጵያን መንፈሴ ተፈትቶ እንዳይክዳት ሰጋሁ
አዋጅ የምስራች ብዬ የትብት ምግቤን ገድፌ
ከእናቴ ማህፀን አልፌ በኢትዮጵያ ማህፀን አርፌ
ካፈሯ አጥንቴን ቀፍፌ ደሜን ከደሟ አጠንፍፌ
ከወዟወዟን ቀፍፌ
በህፃን እግሬ ድኬባት በህልም አክናፌ ከንፌ
እረኝነቴን በሰብሏ በምድሯ ላብ አሳልፌ
ከጫጩት እና ከጥጃ ከግልገል ጋር ተቃቅፌ
በጋው የረኛ አደባባይ ክረምት እንደ ወዙ ፍሳሽ
በገጠር የደመና ዳስ በገደል የሸለቆ አዳራሽ
ከቆቅና ከሚዳቋ ከጅግራ ጠረን ስተሻሽ
በወንዝ አፋፍ ሐረግ ዝላይ መወርወር መንጠልጠል ጢሎሽ
ከፍልፈል ጋር እሩጫ ስገጥም ከቀበሮ ድብብቆሽ
ከራዳ ጫፍ ሳር ለግት ላሜ ትንሽ ግጦሽ
ለጥጃዬ የሌት ግርዶሽ
ለጥማድ በሬዎቼ እራት ለማታቸው ጥቂት ድርቆሽ
ለግልገሌ ከአውሬ ከለል እማሳው ስር ጎጆ መትከል
ለፀሐይ የሾላ ጠለል ለዝናብ የገሳ ጠለል
ውሎ የንብ ቀፎ ማሰስ ያበባ እምቡጥ ሲፈነዳ
የግጦሽ ሳር ሲለመልም ሲሰማሩ ሰደድ ሜዳ
አዝመራው ጣል ከምበል ሲል ከብቱ ለሆራ ሲነዳ
ፈረስ ግልቢያ ስሸመጥጥ ከወፎች ዜማ ስቀዳ
ልቤ በንፋስ ተንሳፎ በዋሽንት ዋይታ ሲከዳ
ያቺን ነው ኢትዮጵያ የምላት
እመብርሀን ምነው እረሳሻት
ያቺን የልጅነት ምስራች የህፃንነት ብስራት
የሳቅ የፍንደቃ ዘመን የምኞት የተስፋ ብፅዓት
ያቺን የልጅነት እናት
አዛኝቱ እንዴት ብለሽ ጥርሶችሽን ትነክሺባት
ስሜን በስምሽ ሰይሜ ባገልግሎትሽ ስዋትት
ከዜማ ቤት ቅኔ ቤት ከድጓ ቤት መጻህፍት
ካንቺ ተቆራኝታ እድሌ ካንቺ ተቆራኝታ ነፍሴ
ከቀፈፋ ደጀ ሰላም ከቤተልሄም ቅዳሴ
አኮ... ቀዶ.. ቀፍፎ .... ዳባ ለብሶ
ቅኔ ዘርፎ .....ግስ ገሶ
መቅደስ አጥኖ ማሕሌት ቆሞ
በልብሰ ተክሕኖ አጊጦ በብር አክሊል ተሸልሞ
እመብርሀን ያንቺ ፅላት ነፍሴ ላይ በሳት ታትሞ
የመናኒው የአባ ተድላ ርድ ሆኜ አብሮኝ ታድሞ
ሕይወቴ እምነትሽን ፀንሶ
ስጋ ፈቃዴ ተድሶ
ለሕንፃሽ መዲና ቆሞ ለክብርሽ ድባብ ምሰሶ
ስሜን በስምሽ ሰይሜ ሆነሽኝ የእምነቴ ፋኖስ
ለዋዜማሽ ግሸን ማርያም ለክብርሽ ደብረ ሊባኖስ
ስሮጥ በወንበሩ አኖርሽኝ በአንበሳው በቅዱስ ማርቆስ
ታዲያን ዛሬ ኢትየጵያ ስትወድቅ ከምትሰጪኝ ለፍርሃት ጦስ
ምነው በእረኝነት እድሜ አይኔን በጓጎጣት የሎስ
የጋኔል ጥምብ አንሳ ከንፎ ወርዶ በጨለማ በርኖስ
እባክሽ እመብርሀን ይብቃሽ እባክሽ ስለ ፍቅሩ ወልዳ
ፅናት ስጪኝ እንድካፈል የእናቴን የኢትዮጵያን ፍዳ
ከነከሳት መርዝ እንድቀምስ ከነደደችበት እቶን
የእሷን ሞት እኔ እንድሞታት ገላዋ ገላዬ እንዲሆን
አዎን ብቻዬን ነኝ ፈራሁ
እምፀናበት ልብ አጣሁ
እሸሸግበት ጥግ አጣሁ
ህፃን ሆኜ የርግብ ጫጩት
አንዳንዴ ራብ ሲያዳክማት
ችጋር ከጎጆዋ ገፍቶ እዛፉ ግርጌ ሲጥላት
እናቷ በርራ ደርሳላት
በአክናፏ ሙቀት ታቅፋት
እፍ እያለች ግንባሯ ላይ ሕይወት ስተነፍስባት
ወዲያው ነፍስ ትዘራለች
ችር.... ብር.... ትር.... እያለች
እባክሽ
* ከ (ሰቆቃው ጴጥሮስ- ሎሬት ፀጋዬ ገ/መድህን )
@Mgetem
🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹
አዬ ምነው እመብርሀን
ኢትዮጵያን ጨከንሽባት
ምነው ቀኝሽን እረሳሻት
እስከመቼ ድረስ እንዲህ መቀነትሽን ታጠብቂባት
ልቦናሽን ታዞሪባት
ፈተናዋን ሰቀቀኗን ጣሯን ይበቃል ሳትያት
አላንቺ እኮ ማንም የላት
አውሮፓ እደሁ ትናጋዋን በፋሺስታዊ ነቀርሳ
ታርሳ ተምሳ በስብሳ
ምድራዊ እባጭ ጫንቃዋን እንደ ኮረብታ ተጭኗት
ቀና ብላ እውነት እንዳታይ አንገቷን ቁልቁል ጠምዝዟት
ነፍሷን ድጦ ያስበረከካት ስልጡን ብኩን መፃጉዕ ናት
እና ፈርቼ እንዳልባክን ሲርቀኝ የሀይልሽ ውጋጋን
አንቺ ካጠገቤ አትራቂ በርታ በይኝ እመብርሀን
ቃልኪዳኔን እንዳልረሳት እንዳልዘነጋት ኢትዮጵያን
አዎን ብቻዬን ነኝ ፈራሁ
እሸሸግበት ጥግ አጣሁ
እምፀናበት ልብ አጣሁ
እማማ ኢትዮጵያን መንፈሴ ተፈትቶ እንዳይክዳት ሰጋሁ
አዋጅ የምስራች ብዬ የትብት ምግቤን ገድፌ
ከእናቴ ማህፀን አልፌ በኢትዮጵያ ማህፀን አርፌ
ካፈሯ አጥንቴን ቀፍፌ ደሜን ከደሟ አጠንፍፌ
ከወዟወዟን ቀፍፌ
በህፃን እግሬ ድኬባት በህልም አክናፌ ከንፌ
እረኝነቴን በሰብሏ በምድሯ ላብ አሳልፌ
ከጫጩት እና ከጥጃ ከግልገል ጋር ተቃቅፌ
በጋው የረኛ አደባባይ ክረምት እንደ ወዙ ፍሳሽ
በገጠር የደመና ዳስ በገደል የሸለቆ አዳራሽ
ከቆቅና ከሚዳቋ ከጅግራ ጠረን ስተሻሽ
በወንዝ አፋፍ ሐረግ ዝላይ መወርወር መንጠልጠል ጢሎሽ
ከፍልፈል ጋር እሩጫ ስገጥም ከቀበሮ ድብብቆሽ
ከራዳ ጫፍ ሳር ለግት ላሜ ትንሽ ግጦሽ
ለጥጃዬ የሌት ግርዶሽ
ለጥማድ በሬዎቼ እራት ለማታቸው ጥቂት ድርቆሽ
ለግልገሌ ከአውሬ ከለል እማሳው ስር ጎጆ መትከል
ለፀሐይ የሾላ ጠለል ለዝናብ የገሳ ጠለል
ውሎ የንብ ቀፎ ማሰስ ያበባ እምቡጥ ሲፈነዳ
የግጦሽ ሳር ሲለመልም ሲሰማሩ ሰደድ ሜዳ
አዝመራው ጣል ከምበል ሲል ከብቱ ለሆራ ሲነዳ
ፈረስ ግልቢያ ስሸመጥጥ ከወፎች ዜማ ስቀዳ
ልቤ በንፋስ ተንሳፎ በዋሽንት ዋይታ ሲከዳ
ያቺን ነው ኢትዮጵያ የምላት
እመብርሀን ምነው እረሳሻት
ያቺን የልጅነት ምስራች የህፃንነት ብስራት
የሳቅ የፍንደቃ ዘመን የምኞት የተስፋ ብፅዓት
ያቺን የልጅነት እናት
አዛኝቱ እንዴት ብለሽ ጥርሶችሽን ትነክሺባት
ስሜን በስምሽ ሰይሜ ባገልግሎትሽ ስዋትት
ከዜማ ቤት ቅኔ ቤት ከድጓ ቤት መጻህፍት
ካንቺ ተቆራኝታ እድሌ ካንቺ ተቆራኝታ ነፍሴ
ከቀፈፋ ደጀ ሰላም ከቤተልሄም ቅዳሴ
አኮ... ቀዶ.. ቀፍፎ .... ዳባ ለብሶ
ቅኔ ዘርፎ .....ግስ ገሶ
መቅደስ አጥኖ ማሕሌት ቆሞ
በልብሰ ተክሕኖ አጊጦ በብር አክሊል ተሸልሞ
እመብርሀን ያንቺ ፅላት ነፍሴ ላይ በሳት ታትሞ
የመናኒው የአባ ተድላ ርድ ሆኜ አብሮኝ ታድሞ
ሕይወቴ እምነትሽን ፀንሶ
ስጋ ፈቃዴ ተድሶ
ለሕንፃሽ መዲና ቆሞ ለክብርሽ ድባብ ምሰሶ
ስሜን በስምሽ ሰይሜ ሆነሽኝ የእምነቴ ፋኖስ
ለዋዜማሽ ግሸን ማርያም ለክብርሽ ደብረ ሊባኖስ
ስሮጥ በወንበሩ አኖርሽኝ በአንበሳው በቅዱስ ማርቆስ
ታዲያን ዛሬ ኢትየጵያ ስትወድቅ ከምትሰጪኝ ለፍርሃት ጦስ
ምነው በእረኝነት እድሜ አይኔን በጓጎጣት የሎስ
የጋኔል ጥምብ አንሳ ከንፎ ወርዶ በጨለማ በርኖስ
እባክሽ እመብርሀን ይብቃሽ እባክሽ ስለ ፍቅሩ ወልዳ
ፅናት ስጪኝ እንድካፈል የእናቴን የኢትዮጵያን ፍዳ
ከነከሳት መርዝ እንድቀምስ ከነደደችበት እቶን
የእሷን ሞት እኔ እንድሞታት ገላዋ ገላዬ እንዲሆን
አዎን ብቻዬን ነኝ ፈራሁ
እምፀናበት ልብ አጣሁ
እሸሸግበት ጥግ አጣሁ
ህፃን ሆኜ የርግብ ጫጩት
አንዳንዴ ራብ ሲያዳክማት
ችጋር ከጎጆዋ ገፍቶ እዛፉ ግርጌ ሲጥላት
እናቷ በርራ ደርሳላት
በአክናፏ ሙቀት ታቅፋት
እፍ እያለች ግንባሯ ላይ ሕይወት ስተነፍስባት
ወዲያው ነፍስ ትዘራለች
ችር.... ብር.... ትር.... እያለች
እባክሽ
* ከ (ሰቆቃው ጴጥሮስ- ሎሬት ፀጋዬ ገ/መድህን )
@Mgetem
❤2👍1🥰1
፨ ተዘጋችተን እኑር፨
ርቀን ከቆምን ከተዋሕዶ አምባ
ምግባር ጎዶሎ እንዳንሆን ገለባ
ለማይበጀን ዓለም ጭራሽ ለማይረባ
በማይሆንን ሁሉ ስንል ወጣ ገባ
ያቺ ቀን ሳትመጣ ሳናውቅ እንደሌባ
ተዘጋጅተን እንኑር ንስሐም እንግባ።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
*ከገብረየስ ገቢቶ
@Mgetem
ርቀን ከቆምን ከተዋሕዶ አምባ
ምግባር ጎዶሎ እንዳንሆን ገለባ
ለማይበጀን ዓለም ጭራሽ ለማይረባ
በማይሆንን ሁሉ ስንል ወጣ ገባ
ያቺ ቀን ሳትመጣ ሳናውቅ እንደሌባ
ተዘጋጅተን እንኑር ንስሐም እንግባ።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
*ከገብረየስ ገቢቶ
@Mgetem
፨ማን ነው አትበሉኝ፨
ማን ነው አትበሉኝ የደማ ላንተ
ማን ነው አትበሉኝ አደኖህ የሞተ
በአብ በወልድ ስም በመንፈስ ቅዱስ
በምድር የመጣ የሰማይ ንጉስ
ከከብቶቹ ጋጥ ውስጥ የተወለደለኝ ከድንግል እናቴ
እኔ ሞቼበት ነው ሊያድን ከሃጥያቴ
ማን ነው አትበሉኝ ደም የደማ ላንተ
ማን ነው አትበሉኝ አድኖህ የሞተ
በወርቅ አክሊል ምትክ እሾህ የለበሰ
እንባዬን ሊያብሰው ደሙን ያፈሰሰ
እኔኑ ሊያድነኝ ሲገርፍ የዋለ እኔ ግን የካድኩት
ለማተብ መኖርን ያስተማረኝ እምነት
ብርክክ የምልለት የንጉሶች ንጉስ
እልል ይባልለት ለኔ ጌታ እየሱስ
ማን ነው አትበሉኝ ደም የደማ ላንተ
ማን ነው አትበሉኝ አድኖህ የሞተ
እንደ ጴጥሮስ ሆኜ ብክደውም ቅሉ
ዶሮ ሳይጮህ ሶስቴ ሳይል አኩሉሉ
እሱ ግን እሱ ነው የይቅርታ ንጉስ
ምህረትን ለመስጠት ማይጠይቅ
እየሱስ ነው ጌታ ፊቱ የሚያበራ
ግርማው የሚያስፈራ
እናም..
ማን ነው አትበሉኝ ደም የደማ ላንተ
ማን ነው አትበሉኝ ሊያድንህ የሞተ።
@Mgetem @Mgetem
ማን ነው አትበሉኝ የደማ ላንተ
ማን ነው አትበሉኝ አደኖህ የሞተ
በአብ በወልድ ስም በመንፈስ ቅዱስ
በምድር የመጣ የሰማይ ንጉስ
ከከብቶቹ ጋጥ ውስጥ የተወለደለኝ ከድንግል እናቴ
እኔ ሞቼበት ነው ሊያድን ከሃጥያቴ
ማን ነው አትበሉኝ ደም የደማ ላንተ
ማን ነው አትበሉኝ አድኖህ የሞተ
በወርቅ አክሊል ምትክ እሾህ የለበሰ
እንባዬን ሊያብሰው ደሙን ያፈሰሰ
እኔኑ ሊያድነኝ ሲገርፍ የዋለ እኔ ግን የካድኩት
ለማተብ መኖርን ያስተማረኝ እምነት
ብርክክ የምልለት የንጉሶች ንጉስ
እልል ይባልለት ለኔ ጌታ እየሱስ
ማን ነው አትበሉኝ ደም የደማ ላንተ
ማን ነው አትበሉኝ አድኖህ የሞተ
እንደ ጴጥሮስ ሆኜ ብክደውም ቅሉ
ዶሮ ሳይጮህ ሶስቴ ሳይል አኩሉሉ
እሱ ግን እሱ ነው የይቅርታ ንጉስ
ምህረትን ለመስጠት ማይጠይቅ
እየሱስ ነው ጌታ ፊቱ የሚያበራ
ግርማው የሚያስፈራ
እናም..
ማን ነው አትበሉኝ ደም የደማ ላንተ
ማን ነው አትበሉኝ ሊያድንህ የሞተ።
@Mgetem @Mgetem
❤4👍1