#አፈረሰበት_እቅዱን
@Mgetem
የሰው ዘር ቀዳሚ ጠላት
ለዓለም የሐሰት አባት
የአዳምን ኃጢአት መስራች
በሰዎች ውድቀት ተደሳች
የሐዘን ቤቶችን ለመስራት
ተኝቶ አያውቅም በእውነት
በደምና እንባ እያራሰ
በሰው አጥንት እየማሰ
የሞትን መሰረት በመጣል
የኃጢአት ምሰሶ በመትከል
እጅግ ብዙ ዘመናት ትግሏል
የሞቱን መውጊያ ለመንቀል
ምክንያተ ድኂን ናት ድንግል
የአዳምን እዳ ለማስወገድ
ሥጋን ለበሰ እግዚአብሔር ወልድ
አማኑኤል ሰው በመሆን
ክፉ ተግባሩን የሰይጣንን
አፈረሰበት ዕቅዱን፡፡
____________________________
@Mgetem
@Mgetem
@bubushu
@Mgetem
የሰው ዘር ቀዳሚ ጠላት
ለዓለም የሐሰት አባት
የአዳምን ኃጢአት መስራች
በሰዎች ውድቀት ተደሳች
የሐዘን ቤቶችን ለመስራት
ተኝቶ አያውቅም በእውነት
በደምና እንባ እያራሰ
በሰው አጥንት እየማሰ
የሞትን መሰረት በመጣል
የኃጢአት ምሰሶ በመትከል
እጅግ ብዙ ዘመናት ትግሏል
የሞቱን መውጊያ ለመንቀል
ምክንያተ ድኂን ናት ድንግል
የአዳምን እዳ ለማስወገድ
ሥጋን ለበሰ እግዚአብሔር ወልድ
አማኑኤል ሰው በመሆን
ክፉ ተግባሩን የሰይጣንን
አፈረሰበት ዕቅዱን፡፡
____________________________
@Mgetem
@Mgetem
@bubushu
👍2
#አደበታችን_የድንግልን_ስራ_ያመሰግናል
_____________________
የአለም መዳኒት ከእርሷ ስጋን ነስቶ
የምስራች ዜና በገብርኤል ተሰምቶ
ለልዑል ማደርያ ትሆን ይገባታል
በዳዊት ሀገር ከእርሷ ተወለደ
ለማእፀኗ ፍሬ ትውልዱ ሰገደ
ፅሃይን ታቅፋ ብረሃንን የሰጠች
ከምድር ፍጥረታት እጅግ የተለየች
የተዋህዶ አርማ ላይናችን ድንቅ ነች(፪)
እናትና ድንግል ሁለቱንም ይዛ
በድንግልናው የአለሙን ቤዛ ይዛ
እርኩሰት የሌለባት የተመረጠች ከሰማይ
ኑ እናመስግናት አህዛብ ባንድ ላይ
የህይወት እንጀራን ስላስገኘች ሲሳይ
#ከእህተ_ማርያም
__________________________
@Mgetem
@Mgetem
@kal002
_____________________
የአለም መዳኒት ከእርሷ ስጋን ነስቶ
የምስራች ዜና በገብርኤል ተሰምቶ
ለልዑል ማደርያ ትሆን ይገባታል
በዳዊት ሀገር ከእርሷ ተወለደ
ለማእፀኗ ፍሬ ትውልዱ ሰገደ
ፅሃይን ታቅፋ ብረሃንን የሰጠች
ከምድር ፍጥረታት እጅግ የተለየች
የተዋህዶ አርማ ላይናችን ድንቅ ነች(፪)
እናትና ድንግል ሁለቱንም ይዛ
በድንግልናው የአለሙን ቤዛ ይዛ
እርኩሰት የሌለባት የተመረጠች ከሰማይ
ኑ እናመስግናት አህዛብ ባንድ ላይ
የህይወት እንጀራን ስላስገኘች ሲሳይ
#ከእህተ_ማርያም
__________________________
@Mgetem
@Mgetem
@kal002
❤2👍1
✤ ተሸክሜ አልጋዬን ✤
ጠዋት በማለዳ
ቤትህ እንዳልገሰግስ
ሌሊቴ እንደ ዳዊት
ስምህን እንዳልቀድስ
ካልጋዬ ጋር አስሮ
የያዘኝ ደዌ
የድብርት ብርድልብስ
የእንቅልፍ አባዜ
አርቅልኝና
ተሸክሜ አልጋዬን
ዘወትር በቤትህ
ብሰማ ጩኸቴን።
*ከመቅደስ አያሌው
@Mgetem
ጠዋት በማለዳ
ቤትህ እንዳልገሰግስ
ሌሊቴ እንደ ዳዊት
ስምህን እንዳልቀድስ
ካልጋዬ ጋር አስሮ
የያዘኝ ደዌ
የድብርት ብርድልብስ
የእንቅልፍ አባዜ
አርቅልኝና
ተሸክሜ አልጋዬን
ዘወትር በቤትህ
ብሰማ ጩኸቴን።
*ከመቅደስ አያሌው
@Mgetem
👍4❤2
#ስንት_ቀን_ፈጀብህ?
/መንፈሳዊ መነባንብ /
-----------------✞-------------------
ለአዳም ኪዳን ሰጠህ
እንደምትወለድ ወደ ምድር ወርደህ
እንዴት ነበር ያኔ..?
ወደ እኛ ስትመጣ መላእክትን ትተህ?
………
የሔዋን እርግማን
የባሏም የውርስ ኃጢአት መዘገን
እንዲያ አሳሰበህና
መጣህልን ሁሉን አደረግህ በፅሙና
.........
እንዴት ነበር ያኔ..?
ያችን ንጹሕ ለመፈለግ የወሰደብህ ጊዜ
አድርገህ የሰጠኸንን ፈውስ በበድልን ጊዜ
ግን ምን ያህል ነው ልፋትህ?
ድንግልን ስትፈልግ የፈጀብህ?
.........
ከሰማያት ስትወርድ አጀቡህ መላእክት?
ዓለሙስ ተናወፀ በይባቤ በስብሐት?
ያ ምቀኛ ዲያቢሎስ ግን ምን አለ?
ወደ እኛ ስትመጣ አለ አይደል ኮበለለ?
ነው ሥጋ ለብሶ ጉድ ሠራኝ አለ?
........
እንዴት ነው እርቀቱ
የሰማይ ምጥቀቱ
የምድርስ ሥፋት
ከሷ እስክታርፍባት?
ግን ጌታ...?ሰማያት ምን አሉ
ትትሀቸው መጠህ ባንተ አጉረመረሙ?
ፍጥረታትስ ቢሆን ማሕሌት አቆሙ?
.......
ምሥጢረኛው ጌታ
መንገድህ በየት ነው ወደ እኛ ስትመጣ?
ቤተ ልሔም ስትደርስ
ማን አገለገልህ?ምን አለች ምድሪቱስ
እያቄም ወሐናን እንዴት መረጥሃቸው
አንተ እንድትወለድ ምክንያትህ ናቸው
.......
ሰማዩ ሰፊ ነው
ምድርንም ታውቃለህ
እንዴት እንድትሰፋ ሆና መረገጫህ
ግን እና ጌታ ሆይ ምኑ ነው የቻለህ?
የድንግል ማሕጸን እሳት መሸከሙ
ምድርም መልኮት በእሷ ላይ መቆሙ
..........
እንዴት ነበር ያኔ
በቤተ ልሔም ውስጥ
አንተን የሚያሞቅ ከእንስሶች ስትሰጥ?
........
ዮሴፍ ምን አለ
አንተን በማየቱ እርጅናው ታጎለ?
አንተን የጠበቀህ አዳምስ በግርማህ ምን አለ?
........
እንዴት ነው ስጦታው
የሰብአ ሰገሉ ወርቅ እጣን አምኃው
የእረኞቹ ደስታ
የመላእክት ብሥራት የልደትህማታ
.........
እንዴት ነበር ያኔ
የልደትህ ማታ
የዝማሬው ለታ
የእናትህ ደስታ
የፍጥረት እልልታ
ሚዳቋ ስትዘል ከኢትዮጵያ አይታ
ግን ጌታ እረቂቁ አምላክ
በየትስ መጠህ ነው ከኛ የተወለድክ
✞ወስብሐት ለእግዚአብሔር ✞
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem
/መንፈሳዊ መነባንብ /
-----------------✞-------------------
ለአዳም ኪዳን ሰጠህ
እንደምትወለድ ወደ ምድር ወርደህ
እንዴት ነበር ያኔ..?
ወደ እኛ ስትመጣ መላእክትን ትተህ?
………
የሔዋን እርግማን
የባሏም የውርስ ኃጢአት መዘገን
እንዲያ አሳሰበህና
መጣህልን ሁሉን አደረግህ በፅሙና
.........
እንዴት ነበር ያኔ..?
ያችን ንጹሕ ለመፈለግ የወሰደብህ ጊዜ
አድርገህ የሰጠኸንን ፈውስ በበድልን ጊዜ
ግን ምን ያህል ነው ልፋትህ?
ድንግልን ስትፈልግ የፈጀብህ?
.........
ከሰማያት ስትወርድ አጀቡህ መላእክት?
ዓለሙስ ተናወፀ በይባቤ በስብሐት?
ያ ምቀኛ ዲያቢሎስ ግን ምን አለ?
ወደ እኛ ስትመጣ አለ አይደል ኮበለለ?
ነው ሥጋ ለብሶ ጉድ ሠራኝ አለ?
........
እንዴት ነው እርቀቱ
የሰማይ ምጥቀቱ
የምድርስ ሥፋት
ከሷ እስክታርፍባት?
ግን ጌታ...?ሰማያት ምን አሉ
ትትሀቸው መጠህ ባንተ አጉረመረሙ?
ፍጥረታትስ ቢሆን ማሕሌት አቆሙ?
.......
ምሥጢረኛው ጌታ
መንገድህ በየት ነው ወደ እኛ ስትመጣ?
ቤተ ልሔም ስትደርስ
ማን አገለገልህ?ምን አለች ምድሪቱስ
እያቄም ወሐናን እንዴት መረጥሃቸው
አንተ እንድትወለድ ምክንያትህ ናቸው
.......
ሰማዩ ሰፊ ነው
ምድርንም ታውቃለህ
እንዴት እንድትሰፋ ሆና መረገጫህ
ግን እና ጌታ ሆይ ምኑ ነው የቻለህ?
የድንግል ማሕጸን እሳት መሸከሙ
ምድርም መልኮት በእሷ ላይ መቆሙ
..........
እንዴት ነበር ያኔ
በቤተ ልሔም ውስጥ
አንተን የሚያሞቅ ከእንስሶች ስትሰጥ?
........
ዮሴፍ ምን አለ
አንተን በማየቱ እርጅናው ታጎለ?
አንተን የጠበቀህ አዳምስ በግርማህ ምን አለ?
........
እንዴት ነው ስጦታው
የሰብአ ሰገሉ ወርቅ እጣን አምኃው
የእረኞቹ ደስታ
የመላእክት ብሥራት የልደትህማታ
.........
እንዴት ነበር ያኔ
የልደትህ ማታ
የዝማሬው ለታ
የእናትህ ደስታ
የፍጥረት እልልታ
ሚዳቋ ስትዘል ከኢትዮጵያ አይታ
ግን ጌታ እረቂቁ አምላክ
በየትስ መጠህ ነው ከኛ የተወለድክ
✞ወስብሐት ለእግዚአብሔር ✞
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem
👍6❤2
#የቆሎ_ተማሪ_ዘድንግል
@Mgetem
በዳዊት በገና በያሬድ ዝማሬ
እኔም ላወድስሽ ቃላትን ደርድሬ
የጌታዬ እናት ስምሽ ይጣፍጣል
ባህዛብ መካከል አፌ አንችን ይጠራል
ማርያም ማርያም ስልሽ ጠላት ይሸበራል
አሁንም ጠራሁሽ አውሬው እርር ይበል
አምላኬ ስጥራሽ ሰምቻለሁ በፍቅር
እናቴ ለክብርሽ አልሻም ምስክር
ምልጃና ፀሎትሽ ምርኩዜ ሆኖኝ
አሰፈሪውን ለሊት ስንቱን አለፈኩኝ
ልቤ አይከፈትም ዝግ ነው ለጠላቴ
ዘውትር አይለየኝም ስእልሽ ከደረቴ።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
፤እንቺ የገነት ምንጭ ፥ የሕይውት ውኃ ጉድጓድ ፥ከሊበኖስም
የሚፈስስ ወንዘ ነሽ። መኃልየመኃለይ ዘሰሎሞን4 ፡ 15
----------------------------------------------
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem
በዳዊት በገና በያሬድ ዝማሬ
እኔም ላወድስሽ ቃላትን ደርድሬ
የጌታዬ እናት ስምሽ ይጣፍጣል
ባህዛብ መካከል አፌ አንችን ይጠራል
ማርያም ማርያም ስልሽ ጠላት ይሸበራል
አሁንም ጠራሁሽ አውሬው እርር ይበል
አምላኬ ስጥራሽ ሰምቻለሁ በፍቅር
እናቴ ለክብርሽ አልሻም ምስክር
ምልጃና ፀሎትሽ ምርኩዜ ሆኖኝ
አሰፈሪውን ለሊት ስንቱን አለፈኩኝ
ልቤ አይከፈትም ዝግ ነው ለጠላቴ
ዘውትር አይለየኝም ስእልሽ ከደረቴ።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
፤እንቺ የገነት ምንጭ ፥ የሕይውት ውኃ ጉድጓድ ፥ከሊበኖስም
የሚፈስስ ወንዘ ነሽ። መኃልየመኃለይ ዘሰሎሞን4 ፡ 15
----------------------------------------------
@Mgetem
@Mgetem
❤2
#ሳልፆም_ሊፈሰክ_ነው
አይ የኔ ነገር!!!
@Mgetem
እርግጥ አልበላሁም ስጋም ሆነ ቅቤ
አልፆም አለኝ እንጂ አመፀኛ ልቤ
ካምናና ካቻምና የዘንድሮ ብሶ
መላ ማንነቴ በሀጢያት ተለውሶ
ስዋሽ ስቀጥፍ
ህግን ስተላለፍ
ስሰድብ ሳደማ
የሰው ስጋ ሳማ
ባይኔ ሳመነዝር
የሰው ሰው ሳማትር
ገላዬን ሳራቁት
አዳምን/ሔዋንን ሳሳስት
ስረሳ ስቃይህን
መስቀል ህማምህን
ያን ሁሉ ግርፋት
ነብሴ ሳያስጨንቃት
አይ እኔ
በሀሰት ስመሰክር
በሀጢያት ስዳክር
ለማይሞላ ኑሮ
ሳልሻል ዘንድሮ
ፆሙ ተጋመሰ
ጊዜው ተጋመሰ
ጌታ ሆይ
አቤቱ አስበኝ
ለንሰሀ አብቃኝ
እስቲ የቀረውን ለበረከት በለው
አመፀኛ ልቤ ፆምህን ይፁመው
"ከደጀ ሰላሙ ከካህኑ እግር ስር
ንስሀዬን ልውሰድ ስለመስቀል ፍቅር"
የንሰሀ ህይወት ይስጠን!
___________________________
@Mgetem
@Mgetem
@Menfesawi_getem_bot
አይ የኔ ነገር!!!
@Mgetem
እርግጥ አልበላሁም ስጋም ሆነ ቅቤ
አልፆም አለኝ እንጂ አመፀኛ ልቤ
ካምናና ካቻምና የዘንድሮ ብሶ
መላ ማንነቴ በሀጢያት ተለውሶ
ስዋሽ ስቀጥፍ
ህግን ስተላለፍ
ስሰድብ ሳደማ
የሰው ስጋ ሳማ
ባይኔ ሳመነዝር
የሰው ሰው ሳማትር
ገላዬን ሳራቁት
አዳምን/ሔዋንን ሳሳስት
ስረሳ ስቃይህን
መስቀል ህማምህን
ያን ሁሉ ግርፋት
ነብሴ ሳያስጨንቃት
አይ እኔ
በሀሰት ስመሰክር
በሀጢያት ስዳክር
ለማይሞላ ኑሮ
ሳልሻል ዘንድሮ
ፆሙ ተጋመሰ
ጊዜው ተጋመሰ
ጌታ ሆይ
አቤቱ አስበኝ
ለንሰሀ አብቃኝ
እስቲ የቀረውን ለበረከት በለው
አመፀኛ ልቤ ፆምህን ይፁመው
"ከደጀ ሰላሙ ከካህኑ እግር ስር
ንስሀዬን ልውሰድ ስለመስቀል ፍቅር"
የንሰሀ ህይወት ይስጠን!
___________________________
@Mgetem
@Mgetem
@Menfesawi_getem_bot
👍4❤2🥰1
❖የሰማዩ ጌታ የአርያም ባለቤት❖
❖የአምላኮች አምላክ የፍጥረታት አባት❖
❖ሀያል ፍቅር ስቦት ከመንበሩ ወርዶ❖️
❖በዛ በበረት በከብቶች ግርግም ️
..ከንፅህት ቅድስት ድንግል ማርያም ተወልዶ❖
❖እኛን ላዳነበት ለብርሃነ ልደቱ❖
❖እንኳን አደረሰን አደረሳችሁ።❖
-----ከ ሰመረ ፍስሃ---
#መልካም_በአል
❖የአምላኮች አምላክ የፍጥረታት አባት❖
❖ሀያል ፍቅር ስቦት ከመንበሩ ወርዶ❖️
❖በዛ በበረት በከብቶች ግርግም ️
..ከንፅህት ቅድስት ድንግል ማርያም ተወልዶ❖
❖እኛን ላዳነበት ለብርሃነ ልደቱ❖
❖እንኳን አደረሰን አደረሳችሁ።❖
-----ከ ሰመረ ፍስሃ---
#መልካም_በአል
🥰1
ውድ የቻናላችን ቤተሰቦች እንኳን ለጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያልን
የግጥም ችሎታ ያላችሁ ወይም ደግሞ እዚህ ቻናል ላይ ቢለቀቅ ይጠቅማሉ የምትሏቸው ግጥሞች ካላችሁ በመላክ መሳተፍ ትችላላችሁ
#ግጥሞችን_ለመላክ
በ @Menfesawi_getem_bot ላይ
/start ብላችሁ ብትልኩልን ይደርሱናል
አልያም ደግሞ በአድሚኖቻችን አድራሻ
@bubushu
@kal002 ላይ መላክ ትችላላችሁ
ስለ ተሳትፎአችሁ እናመሠግናለን
የግጥም ችሎታ ያላችሁ ወይም ደግሞ እዚህ ቻናል ላይ ቢለቀቅ ይጠቅማሉ የምትሏቸው ግጥሞች ካላችሁ በመላክ መሳተፍ ትችላላችሁ
#ግጥሞችን_ለመላክ
በ @Menfesawi_getem_bot ላይ
/start ብላችሁ ብትልኩልን ይደርሱናል
አልያም ደግሞ በአድሚኖቻችን አድራሻ
@bubushu
@kal002 ላይ መላክ ትችላላችሁ
ስለ ተሳትፎአችሁ እናመሠግናለን
👍2👏1
#እነዃት_እናትህ ዮሐ 19:27
(በሰመረ ፍስሃ)
የበዛው በደሌ ሀጢያቴ ለመደምሰስ
ያጣሁት ልጅነት ዳግም ለመመለስ
ፈጣሪ ሆነህ ሳለ እንደ ፍጡር ተቆጠርክ
እውነተኛው አምላክ በሀሰት ከሰሱህ
ጥፋተኛ ብለው መስቀል ላይ ሰቀሉህ::
እኔም ደግነትህ ፍቅርህን ተመልክቼ
እንደ በግ ሲጎትቱህ ስትከተላቸው አይቼ
ችንካሮችህ አይተው አለቀሱ አይኖቼ
እንባዬ እንደ ጅረት ጉንጬ ላዬ ፈሰሰ
ውስጤ ሀዘን ገባው ሆዴም ተላወሰ
አንተ ግን...
የእንግልትህ ብዛት ስቃይ ሳይገድብህ
ርሀቡ ጥማቱ ድካም ሳይዳግትህ
ደጋፊዬ እንድትሆነኝ ለችግሬ መከታ
እንባዬን ተመልክታ ቀኜን እንድታበረታ
መስቀልህ ስር ያለችውን አዛኝቷ አናትህ
ብለህ አስረከብከኝ እነዃት እናትህ::
እኔም ደስ ብሎኝ እናቴ ናት ብዬ
ወደ ቤቴ አስገባኀት ወደ ህይወት ጎጆዬ::
ለኔም መፅናኛዬ አማላጅ እንድትሆነኝ
እነሆ ልጅሽ ብለህ እናትህ ሰጠሀኝ::
__________________________
@Mgetem
@Menfesawi_getem_bot
@kal002
(በሰመረ ፍስሃ)
የበዛው በደሌ ሀጢያቴ ለመደምሰስ
ያጣሁት ልጅነት ዳግም ለመመለስ
ፈጣሪ ሆነህ ሳለ እንደ ፍጡር ተቆጠርክ
እውነተኛው አምላክ በሀሰት ከሰሱህ
ጥፋተኛ ብለው መስቀል ላይ ሰቀሉህ::
እኔም ደግነትህ ፍቅርህን ተመልክቼ
እንደ በግ ሲጎትቱህ ስትከተላቸው አይቼ
ችንካሮችህ አይተው አለቀሱ አይኖቼ
እንባዬ እንደ ጅረት ጉንጬ ላዬ ፈሰሰ
ውስጤ ሀዘን ገባው ሆዴም ተላወሰ
አንተ ግን...
የእንግልትህ ብዛት ስቃይ ሳይገድብህ
ርሀቡ ጥማቱ ድካም ሳይዳግትህ
ደጋፊዬ እንድትሆነኝ ለችግሬ መከታ
እንባዬን ተመልክታ ቀኜን እንድታበረታ
መስቀልህ ስር ያለችውን አዛኝቷ አናትህ
ብለህ አስረከብከኝ እነዃት እናትህ::
እኔም ደስ ብሎኝ እናቴ ናት ብዬ
ወደ ቤቴ አስገባኀት ወደ ህይወት ጎጆዬ::
ለኔም መፅናኛዬ አማላጅ እንድትሆነኝ
እነሆ ልጅሽ ብለህ እናትህ ሰጠሀኝ::
__________________________
@Mgetem
@Menfesawi_getem_bot
@kal002
❤4
✤ ይበዛል✤
ጠይቄ ካደረክልኝ
ሳልጠይቅ የሰጠኸኝ
ይበዛል...
ከተወረወረብኝ ከማየው ጦር
የሰወርኝ ከማላየው ጾር
ይበዛል...
ስምህን ሳልጠራ ከዋልኩበት
ከኔ ያልተለየህበት በምሕረት
በይቅርታ የጠራኽኝ ባባትነት
ይበዛል...
ከኔ ብርታት ቸርነት
ከብዙ በደሌ ይቅርታህ
ከአሸናፊነቴ ድልህ
ይበዛል...
ይበዛል ይበዛል ይበልጣል
እንዲበዛልን መጥተሃል
እንዲበዛልን ሞተሃል።
ከመታሰቢያ መስፍን
@Mgetem
ጠይቄ ካደረክልኝ
ሳልጠይቅ የሰጠኸኝ
ይበዛል...
ከተወረወረብኝ ከማየው ጦር
የሰወርኝ ከማላየው ጾር
ይበዛል...
ስምህን ሳልጠራ ከዋልኩበት
ከኔ ያልተለየህበት በምሕረት
በይቅርታ የጠራኽኝ ባባትነት
ይበዛል...
ከኔ ብርታት ቸርነት
ከብዙ በደሌ ይቅርታህ
ከአሸናፊነቴ ድልህ
ይበዛል...
ይበዛል ይበዛል ይበልጣል
እንዲበዛልን መጥተሃል
እንዲበዛልን ሞተሃል።
ከመታሰቢያ መስፍን
@Mgetem
❤3👍1
፨መኖርን ሳትኖረ፨
ትእዛዙን ሰምተህ
ቃሉን እያወቅኸው
መቼ ታገልክና
ሥጋክን አሸነፍከው
ወድቆ መነሳት
ተሰብሮ መጠገን
ማዕቀሉ ሲያይል
በጌታህ መታመን
በተስፋ ስትወጣ
የመከራን ዳገት
አክሊሉ ይታይህ
የዘላለም ሕይወት
ዓላማ ሳይኖርህ
በልማድ ተጉዘህ
መኖርን ሳትኖር
ለምን ትሞታለህ
ከሱናማዊት
@Mgetem
ትእዛዙን ሰምተህ
ቃሉን እያወቅኸው
መቼ ታገልክና
ሥጋክን አሸነፍከው
ወድቆ መነሳት
ተሰብሮ መጠገን
ማዕቀሉ ሲያይል
በጌታህ መታመን
በተስፋ ስትወጣ
የመከራን ዳገት
አክሊሉ ይታይህ
የዘላለም ሕይወት
ዓላማ ሳይኖርህ
በልማድ ተጉዘህ
መኖርን ሳትኖር
ለምን ትሞታለህ
ከሱናማዊት
@Mgetem
❤1
#ሃይማኖት_አንዲት_ናት
@Mgetem
ሀይማኖት አንዲት ናት
አንዲት ናት ሃይማኖት፣ ፃድቃን የሄዱባት ከአበው ያገኘናት።
እማ ተዋህዶ ፈተና ቢበዛ በአውሎ በወጀቡ ክፉውን አንፈራም የመጣ ቢመጣ
መስቀሉ ሃይል ነው አለ በልባችን።
የአንገቴ ማህተም ያሰርኩት ጥቁር ክር፣ ስለ ተዋህዶ ይናገር ይመስክር። እናም አልበጥስም ማህተቤን ካንገቴ፣ ብኩርናዬ እኮ ናት ኦርተዶክስነቴ። የደሙን መሰረት ተዋህዶን ንቄ እንዴት ፍልስፋናን ልመን እውነት ብዬ። የመሰረተውን ማንም ሰው ተነስቶ፣ እንዴት ይታመናል ፍልስፍና ከቶ። እምነቴን ከምክድ ለገንዘብ ለእንጀራ፣ ይቅርብኝ መክበሩ ስሜም አይጠራ። ጓዳዬም ሳይሞላ ኑሮዬም ሳያምር፣ ከአበው መቃብር ላይ ከዋሻው ልቀበር፣ ነፍስ ያስምራልና የቃልኪዳኑ አፈር። በውርደት ከምለብስ የሲኦልን ካባ፣ ሌጦው ይሻለኛል የአባቶቼ ዳባ። ያመንኩት እውነት ነው አልጠራጠርም ፣ እሞታለሁ እንጂ እምነቴን አልክድም። ከሰማዕታቱ ከፃድቃኑ ህይወት ፣ ይሄን ነው የማውቀው ስለ ስሙ መሞት።
✤ ስብሐት ለእግዚአብሔር ✤
____________________________
ኢየሩሳሌም (ተዋህዶ ) ሆይ ብረሳሽ ቀኜ ትርሳኝ!
ከስንታየው
____________________________
@Mgetem
@Mgetem
@Menfesawi_getem_bot
@Mgetem
ሀይማኖት አንዲት ናት
አንዲት ናት ሃይማኖት፣ ፃድቃን የሄዱባት ከአበው ያገኘናት።
እማ ተዋህዶ ፈተና ቢበዛ በአውሎ በወጀቡ ክፉውን አንፈራም የመጣ ቢመጣ
መስቀሉ ሃይል ነው አለ በልባችን።
የአንገቴ ማህተም ያሰርኩት ጥቁር ክር፣ ስለ ተዋህዶ ይናገር ይመስክር። እናም አልበጥስም ማህተቤን ካንገቴ፣ ብኩርናዬ እኮ ናት ኦርተዶክስነቴ። የደሙን መሰረት ተዋህዶን ንቄ እንዴት ፍልስፋናን ልመን እውነት ብዬ። የመሰረተውን ማንም ሰው ተነስቶ፣ እንዴት ይታመናል ፍልስፍና ከቶ። እምነቴን ከምክድ ለገንዘብ ለእንጀራ፣ ይቅርብኝ መክበሩ ስሜም አይጠራ። ጓዳዬም ሳይሞላ ኑሮዬም ሳያምር፣ ከአበው መቃብር ላይ ከዋሻው ልቀበር፣ ነፍስ ያስምራልና የቃልኪዳኑ አፈር። በውርደት ከምለብስ የሲኦልን ካባ፣ ሌጦው ይሻለኛል የአባቶቼ ዳባ። ያመንኩት እውነት ነው አልጠራጠርም ፣ እሞታለሁ እንጂ እምነቴን አልክድም። ከሰማዕታቱ ከፃድቃኑ ህይወት ፣ ይሄን ነው የማውቀው ስለ ስሙ መሞት።
✤ ስብሐት ለእግዚአብሔር ✤
____________________________
ኢየሩሳሌም (ተዋህዶ ) ሆይ ብረሳሽ ቀኜ ትርሳኝ!
ከስንታየው
____________________________
@Mgetem
@Mgetem
@Menfesawi_getem_bot
❤3👍2
♥ጥምቀተ ኢየሱስ♥
(ጥምቀተ ክርስቶስ ) (ጥምቀተ ወልድ)
በድጋሜ የተለጠፈ
የጥምቀቱ ባለቤት የሆናችው በዓለም ያላችው ክርስቲያኖች በሙሉ እንኳን አደረሳችው ሸር በማረግ ለሁሉም አዳርሱ
++በመጋቤ ሐዲስ ሄኖክ ፈንቴ+
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሰላሳ ዓመት ሲመላው
ዮሐንስ ሰላሳ ዓመት ከስድስት ወር ሲሆነው በዮሐንስ እጅ ሊጠመቅ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ ሄደ
ለምን ወደዮሐንስ ሄደ ዮሐንስ ወደ ኢየሱስ ለምን አልመጣም ቢሉ ባሪያ በጌታው እጅ ይጠመቃል እንጂ ጌታ በባሪያው እጅ ይጠመቃልን ቢሉ ?
1 ለትህትና
ጌታችን ከሰማየ ሰማያት ወርዶ ሰው የሆነው ለትህትና ነው እንጂ ለልእልና አይደለምና
2 አብነት ለመሆን
ጌታችን ዮሐንስን መጥተህ አጥምቀኝ ቢለው ዛሬ ነገሥታት መኳንንት ሀብታሞች መታችው አጥምቁን ይሉ ነበርና ሂዳችው ተጠመቁ ለማለት
ከሌሎች ወንዞች ለይቶ ጥምቀቱን ለምን በዮርዳኖስ አደረገው ቢሉ?
1 ትንቢቱን ለመፈፀም
ዮርዳኖስ ወደሃላው ተመለሰ ብሎ መዝሙረኛው ዳዊት ስለ ዮርዳኖስ ትንቢት ተናግሮ ነበርና ለመፈፀም ነው
2 የአዳምና የሄዋን የእዳ ደብዳቤአቸውን ለመደምሰስ
ከእለታት አንድ ቀን ዲያብሎስ በአዳምና በሔዋን ላይ የጨለማ መጋረጃ ጋርዶ ድቃይ አጽንቶ ስመ ግብርናታችውን ጽፋችው ብተሰጡኝ ስቃይ አቀልላችዋለው ብሏቸው ስቃዩን ያቀለለልን መስሏቸው
አዳም የዲያብሎስ ባሪያ ነው ሔዋን የዲያብሎስ ባሪያ ናት ብለው ጽፈው ሰጡት።
ያን ተቀብሎ በሁለት እብነ ሩካም ጽፎ አንዱን ሲኦል አንዱን ዮርዳኖስ ጥሎት ነበርና በዮርዳኖስ የተጣለውን በጥምቀቱ ለመደምሰስ ዮርዳኖስን መርጧል።
ሲጠመቅም እንደአምላክነቱ አቅልጦ እንደ ሰውነቱ ረግጦ የእዳ ደብዳቤአቸውን አጥፍቶላቸዋል ።
በሲኦል የጣለውን በዕለተ አ ዓርብ በአካለ ነፍስ ወርዶ ደምስሶታል።
ጌታችን ዮሐንስን አጥምቀቀኝ ሲለው
ሌላውን
በአንተ ስም
በአብ ስም
በመንፈስ ቅዱስ ስም
አጠምቃለው አንተን በማን ስም ላጥምቅህ? አለው።
የቡሩክ አብ ልጁ ብርሃንን የምትገልጥ ይቅር በለን የዓለምን ኀጢአት የሚያስወግደው የእግዚአብሔር በግ እነሆ
ክህነትህ እንደ መልከጼዴቅ ክህነት ለዘለአለም ነው እያልክ አጥምቀኝ አለው።
+የአብ ልጅ መሆኑን
+ብርሃን የሚገልጥ መሆኑን
+ይቅር ባይ መሆኑን
+የዓለምን ኀጢአት የሚያስወግድ የእግዚአብሔር በግ መሆኑን
+ክህነቱ ዘለዓለማዊ መሆኑን እየመሰከረ አጥምቆታል
ጥምቀቱን በውሃ ያደረገው ስለምን ነው ቢሉ?
+ውሃ በዙፋን ካለ ንጉሥ በአደባባይ እስካለ ጽኑስ ለሁሉ የሚገኝ ነው።
+ውሃ ጽንፍ እስከ ጽንፍ ይፈሳል ጥምቀትም ጽንፍ እስከ ጽንፍ ይደርሳልና
+ወሃ ከእድፍ ያነጻል ጥምቀትም ከኀጢአት ያነጻልና
+ወሃ የወሰደው ፍለጋ የለውም በጥምቀትም የተሰረየ ኀጢአት በፍዳ አያስዝምና
,
+ውሃ መልክ ያሳያል መልክ ያለመልማል
ጥምቀትም መልክአ ነፍስ ያሳያል መልክአ ነፍስ ያለመልማልና
+በውሃ የታጠበ ልብስ እየቀደም እየነፃ ኃይል ግዘፍ እየነሳ ይሄዳል
ምእመናንም ተጠምቀው ገድል ትሩፋት ከጊዚ ወደ ጊዜ እየሰሩ እየጨመሩ ይሄዳሉና
+ርብቃ ለይስሐቅ የታጨችው ውሃ ስትቀዳ ነው
ምእመናንም ለክርስቶስ ሙሰሽራነት የሚታጬት በውሃ ተጠምቀው ነውና
+በውሃ ቀድሞ ሰብአ ትካት ሰብኣ ግብጽ ጠፍተው ነበርና ውሃ ለመአት እንጂ ለምህረት አልተፈጠረም ብለውት ነበርና ለመአትም ለምህረትም እንደተፈጠረ ለመግለጽ ከሁሉም ውሃን መርጦ በውሃ ተጠመቀ።
በመአር በወተት በወይን በዘይት ተጠምቆ ቢሆን ኑሮ
ሀብታሞች እንጂ ድሃዎች አያገኙትምና ሁሉ በሚያገኘው በውሃ ተጠመቀ።
ሲጠመቅም መንፈስ ቅዱስ በረግብ አምሰሰልወርዷል።
መንፈስቅዱስን ስለምን ርግብ አለው ቢሉ?
+ርግብ ሀዳጊተ በቀል ናትመንፈስ ቅዱስም ሀዳጌ በቀል ነውና
+ርግብ በኖህ ጊዜ ኀፀ ማየ አይኅ ነትገ ማየ አይኅ ስትል ቆጽለ እፀ ዘይት ይዛ ተገኝታለች መንፈስ ቅዱስም ተስፋ መስቀልን ያበስራልና
+ርግብ ክንፋን ቢመቷት እነረቁላሏን።ቢሰብሩባት ቤታን ካላፈረሱባት ቦተዋን አትለቅም መንፈስ ቅዱስም ኀጢአት ቢሰሩም ለንስሃ ይጠራል እንጂ ፈፅሞ ካልካዱት አይርቅምና ።
ጥምቀቱን በመአልት ያላደረገው በሌሊት ያደረገው ስለምነው ቢሉ?
በመአልት አድርጎት ቢሆን መንፈስ ቅዱስ በቁሙ ርግብ ነው ብለው በተጠራጠሩ ነበና
አሁንስ ርግብ አለመሆኑ በምን ይታወቃል ቢሉ ?ጌታችን የተጠመቀ ከሌሊቱ አስር ሰአት ነው
በአስር ሰአት ወፎች ርግቦች አይበሩም ተሀዋስያን ከቦታቸው አይንቀሳቀሱምና በዚህ ርግብ አለመሆኑ ይታወቃል።
መንፈስ ቅዱስ የወረደው ከውሀው ከወጣ ከዮሀንስ ከተለየ በሇላ ነው
ከውሃው ሳለ ወርዶ ቢሆን ለቀድሶተ ማያት የወረደ ነው ባሉ ነበርና።
ከዮሀንስ ጋራም ሳለ ቢሆን ስለ ክብረ ዮሐንስ የወረደ ነው ባሉ ነበርና ።
ሲወርድም ረቦ ወርዷልቢሉ
አብ ምሉእ ነው
አንተም ምሉእ ነህ
እኔም ምሉእ ነኝ ሲል ነው
አንድም አሰይፎ ወርዷል ቢሉ
የብሉየ መዋእል የአብሕይወት ነኝ
የብሉየ መዋእል የአንተም ህይወት ነኝ
እኔም ብሉየ መዋእል ሕይወት ነኝ ሲል ነው።
ወርዶም ራሱን ቆንጠጥ አድርጎ ይዞታል
አብ አኃዜ ዓለም ነው
አንተም አኀዜ ዓለም ነህ
እኔም አኀዜ ዓለም ነኝ ሲል ነው።
መውረዱ ለአብነት ነው
እናንተም ስትጠመቁ እንደዚህ እወርድላችዋለው ሲል ነው።
ከዚህ በሃላ አብ በደመና ሁኖ የምወደው ልጄ ይህ ነው እርሱን ስሙት ብሎ ልጁ መሆኑን መስክሯል።
ጌታችን ሲጠመቅ አንድነት ሶስትነት ተገልፇል
ወልድ በመጠመቅ
መንፈስ ቅዱስ በርግብ አምሳል በመውረድ
አብ በደመና ሁኖ በመመስከር
አንድ ሲሆኑ ሶስት ሶስት ሲሆኑ አንድ መሆናቸው ተገልጧል ማቴ 3÷13-17።
እውነተኛው ሃይማኖት የትኛው ነው ?
ከተሰኘው ክፍል አንድ መጻፌ ላይና
የማቴዎስ ወንጌል ትርጓሜ ላይ የተወሰደ
መጋቤ ሐዲስ ሄኖክ ፈንቴ
ጥር 8+2010
ዱባይ አላይን ተጻፈ
(ጥምቀተ ክርስቶስ ) (ጥምቀተ ወልድ)
በድጋሜ የተለጠፈ
የጥምቀቱ ባለቤት የሆናችው በዓለም ያላችው ክርስቲያኖች በሙሉ እንኳን አደረሳችው ሸር በማረግ ለሁሉም አዳርሱ
++በመጋቤ ሐዲስ ሄኖክ ፈንቴ+
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሰላሳ ዓመት ሲመላው
ዮሐንስ ሰላሳ ዓመት ከስድስት ወር ሲሆነው በዮሐንስ እጅ ሊጠመቅ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ ሄደ
ለምን ወደዮሐንስ ሄደ ዮሐንስ ወደ ኢየሱስ ለምን አልመጣም ቢሉ ባሪያ በጌታው እጅ ይጠመቃል እንጂ ጌታ በባሪያው እጅ ይጠመቃልን ቢሉ ?
1 ለትህትና
ጌታችን ከሰማየ ሰማያት ወርዶ ሰው የሆነው ለትህትና ነው እንጂ ለልእልና አይደለምና
2 አብነት ለመሆን
ጌታችን ዮሐንስን መጥተህ አጥምቀኝ ቢለው ዛሬ ነገሥታት መኳንንት ሀብታሞች መታችው አጥምቁን ይሉ ነበርና ሂዳችው ተጠመቁ ለማለት
ከሌሎች ወንዞች ለይቶ ጥምቀቱን ለምን በዮርዳኖስ አደረገው ቢሉ?
1 ትንቢቱን ለመፈፀም
ዮርዳኖስ ወደሃላው ተመለሰ ብሎ መዝሙረኛው ዳዊት ስለ ዮርዳኖስ ትንቢት ተናግሮ ነበርና ለመፈፀም ነው
2 የአዳምና የሄዋን የእዳ ደብዳቤአቸውን ለመደምሰስ
ከእለታት አንድ ቀን ዲያብሎስ በአዳምና በሔዋን ላይ የጨለማ መጋረጃ ጋርዶ ድቃይ አጽንቶ ስመ ግብርናታችውን ጽፋችው ብተሰጡኝ ስቃይ አቀልላችዋለው ብሏቸው ስቃዩን ያቀለለልን መስሏቸው
አዳም የዲያብሎስ ባሪያ ነው ሔዋን የዲያብሎስ ባሪያ ናት ብለው ጽፈው ሰጡት።
ያን ተቀብሎ በሁለት እብነ ሩካም ጽፎ አንዱን ሲኦል አንዱን ዮርዳኖስ ጥሎት ነበርና በዮርዳኖስ የተጣለውን በጥምቀቱ ለመደምሰስ ዮርዳኖስን መርጧል።
ሲጠመቅም እንደአምላክነቱ አቅልጦ እንደ ሰውነቱ ረግጦ የእዳ ደብዳቤአቸውን አጥፍቶላቸዋል ።
በሲኦል የጣለውን በዕለተ አ ዓርብ በአካለ ነፍስ ወርዶ ደምስሶታል።
ጌታችን ዮሐንስን አጥምቀቀኝ ሲለው
ሌላውን
በአንተ ስም
በአብ ስም
በመንፈስ ቅዱስ ስም
አጠምቃለው አንተን በማን ስም ላጥምቅህ? አለው።
የቡሩክ አብ ልጁ ብርሃንን የምትገልጥ ይቅር በለን የዓለምን ኀጢአት የሚያስወግደው የእግዚአብሔር በግ እነሆ
ክህነትህ እንደ መልከጼዴቅ ክህነት ለዘለአለም ነው እያልክ አጥምቀኝ አለው።
+የአብ ልጅ መሆኑን
+ብርሃን የሚገልጥ መሆኑን
+ይቅር ባይ መሆኑን
+የዓለምን ኀጢአት የሚያስወግድ የእግዚአብሔር በግ መሆኑን
+ክህነቱ ዘለዓለማዊ መሆኑን እየመሰከረ አጥምቆታል
ጥምቀቱን በውሃ ያደረገው ስለምን ነው ቢሉ?
+ውሃ በዙፋን ካለ ንጉሥ በአደባባይ እስካለ ጽኑስ ለሁሉ የሚገኝ ነው።
+ውሃ ጽንፍ እስከ ጽንፍ ይፈሳል ጥምቀትም ጽንፍ እስከ ጽንፍ ይደርሳልና
+ወሃ ከእድፍ ያነጻል ጥምቀትም ከኀጢአት ያነጻልና
+ወሃ የወሰደው ፍለጋ የለውም በጥምቀትም የተሰረየ ኀጢአት በፍዳ አያስዝምና
,
+ውሃ መልክ ያሳያል መልክ ያለመልማል
ጥምቀትም መልክአ ነፍስ ያሳያል መልክአ ነፍስ ያለመልማልና
+በውሃ የታጠበ ልብስ እየቀደም እየነፃ ኃይል ግዘፍ እየነሳ ይሄዳል
ምእመናንም ተጠምቀው ገድል ትሩፋት ከጊዚ ወደ ጊዜ እየሰሩ እየጨመሩ ይሄዳሉና
+ርብቃ ለይስሐቅ የታጨችው ውሃ ስትቀዳ ነው
ምእመናንም ለክርስቶስ ሙሰሽራነት የሚታጬት በውሃ ተጠምቀው ነውና
+በውሃ ቀድሞ ሰብአ ትካት ሰብኣ ግብጽ ጠፍተው ነበርና ውሃ ለመአት እንጂ ለምህረት አልተፈጠረም ብለውት ነበርና ለመአትም ለምህረትም እንደተፈጠረ ለመግለጽ ከሁሉም ውሃን መርጦ በውሃ ተጠመቀ።
በመአር በወተት በወይን በዘይት ተጠምቆ ቢሆን ኑሮ
ሀብታሞች እንጂ ድሃዎች አያገኙትምና ሁሉ በሚያገኘው በውሃ ተጠመቀ።
ሲጠመቅም መንፈስ ቅዱስ በረግብ አምሰሰልወርዷል።
መንፈስቅዱስን ስለምን ርግብ አለው ቢሉ?
+ርግብ ሀዳጊተ በቀል ናትመንፈስ ቅዱስም ሀዳጌ በቀል ነውና
+ርግብ በኖህ ጊዜ ኀፀ ማየ አይኅ ነትገ ማየ አይኅ ስትል ቆጽለ እፀ ዘይት ይዛ ተገኝታለች መንፈስ ቅዱስም ተስፋ መስቀልን ያበስራልና
+ርግብ ክንፋን ቢመቷት እነረቁላሏን።ቢሰብሩባት ቤታን ካላፈረሱባት ቦተዋን አትለቅም መንፈስ ቅዱስም ኀጢአት ቢሰሩም ለንስሃ ይጠራል እንጂ ፈፅሞ ካልካዱት አይርቅምና ።
ጥምቀቱን በመአልት ያላደረገው በሌሊት ያደረገው ስለምነው ቢሉ?
በመአልት አድርጎት ቢሆን መንፈስ ቅዱስ በቁሙ ርግብ ነው ብለው በተጠራጠሩ ነበና
አሁንስ ርግብ አለመሆኑ በምን ይታወቃል ቢሉ ?ጌታችን የተጠመቀ ከሌሊቱ አስር ሰአት ነው
በአስር ሰአት ወፎች ርግቦች አይበሩም ተሀዋስያን ከቦታቸው አይንቀሳቀሱምና በዚህ ርግብ አለመሆኑ ይታወቃል።
መንፈስ ቅዱስ የወረደው ከውሀው ከወጣ ከዮሀንስ ከተለየ በሇላ ነው
ከውሃው ሳለ ወርዶ ቢሆን ለቀድሶተ ማያት የወረደ ነው ባሉ ነበርና።
ከዮሀንስ ጋራም ሳለ ቢሆን ስለ ክብረ ዮሐንስ የወረደ ነው ባሉ ነበርና ።
ሲወርድም ረቦ ወርዷልቢሉ
አብ ምሉእ ነው
አንተም ምሉእ ነህ
እኔም ምሉእ ነኝ ሲል ነው
አንድም አሰይፎ ወርዷል ቢሉ
የብሉየ መዋእል የአብሕይወት ነኝ
የብሉየ መዋእል የአንተም ህይወት ነኝ
እኔም ብሉየ መዋእል ሕይወት ነኝ ሲል ነው።
ወርዶም ራሱን ቆንጠጥ አድርጎ ይዞታል
አብ አኃዜ ዓለም ነው
አንተም አኀዜ ዓለም ነህ
እኔም አኀዜ ዓለም ነኝ ሲል ነው።
መውረዱ ለአብነት ነው
እናንተም ስትጠመቁ እንደዚህ እወርድላችዋለው ሲል ነው።
ከዚህ በሃላ አብ በደመና ሁኖ የምወደው ልጄ ይህ ነው እርሱን ስሙት ብሎ ልጁ መሆኑን መስክሯል።
ጌታችን ሲጠመቅ አንድነት ሶስትነት ተገልፇል
ወልድ በመጠመቅ
መንፈስ ቅዱስ በርግብ አምሳል በመውረድ
አብ በደመና ሁኖ በመመስከር
አንድ ሲሆኑ ሶስት ሶስት ሲሆኑ አንድ መሆናቸው ተገልጧል ማቴ 3÷13-17።
እውነተኛው ሃይማኖት የትኛው ነው ?
ከተሰኘው ክፍል አንድ መጻፌ ላይና
የማቴዎስ ወንጌል ትርጓሜ ላይ የተወሰደ
መጋቤ ሐዲስ ሄኖክ ፈንቴ
ጥር 8+2010
ዱባይ አላይን ተጻፈ
❤2👍2
፨እናምናለን በምስጢረ ጥምቀቱ፨
በመጋቤ ምስጢርነቱ
በመንግሥተ ሰማይ በርነቱ
ሰው ካልተወለደ ከውኃና ከመንፈስ
ሕይወት እንደሌለው ርስት እንደማይወርስ
ያመነ የተጠመቀ ይድናል
በጥምቀቱ ልጅነት ያገኛል
ባያምን ባይጠመቅ ከልጅነቱ ይወጣል
ኢጥዮጵያዊው ባኮስ በሐዋርያው በፊሊጶስ
ከነቤተሰቦቹ እስጢፋኖስ
ቅዱስ ጳውሎስ ከደማስቆ መልስ
በጥምቀት ተወልደዋል ከመንፈስ ቅዱስ
ሔዋን በሰማንያ አዳም በአርባ ቀኑ
ገነት እንደገቡ ልጅነት እንዳገኙ
ሴቶች በሰማንያ ወንዶች ደግሞ በአርባ
ልጅነት እንዲያገኝ ተጠምቆ እንዲገባ
እናምናለን በእውነት
ያለጥርጥር በእምነት፡፡
@Mgetem
✤✤✤✤✤✤✞✤✤✤✤✤✤
✞@MENFESAWItsufoche✞
✤✤✤✤✤✤✞✤✤✤✤✤✤
በመጋቤ ምስጢርነቱ
በመንግሥተ ሰማይ በርነቱ
ሰው ካልተወለደ ከውኃና ከመንፈስ
ሕይወት እንደሌለው ርስት እንደማይወርስ
ያመነ የተጠመቀ ይድናል
በጥምቀቱ ልጅነት ያገኛል
ባያምን ባይጠመቅ ከልጅነቱ ይወጣል
ኢጥዮጵያዊው ባኮስ በሐዋርያው በፊሊጶስ
ከነቤተሰቦቹ እስጢፋኖስ
ቅዱስ ጳውሎስ ከደማስቆ መልስ
በጥምቀት ተወልደዋል ከመንፈስ ቅዱስ
ሔዋን በሰማንያ አዳም በአርባ ቀኑ
ገነት እንደገቡ ልጅነት እንዳገኙ
ሴቶች በሰማንያ ወንዶች ደግሞ በአርባ
ልጅነት እንዲያገኝ ተጠምቆ እንዲገባ
እናምናለን በእውነት
ያለጥርጥር በእምነት፡፡
@Mgetem
✤✤✤✤✤✤✞✤✤✤✤✤✤
✞@MENFESAWItsufoche✞
✤✤✤✤✤✤✞✤✤✤✤✤✤
👍3
#ጨረቃን_ማን_መራው?
@Mgetem
የጨረቃን ያህል አዕምሮ ስታጣ፤
መታደል ሲሳንህ የፀሐይን ዕጣ፤
ውሸት ታውጃለህ
አዲስ ነገር ላታመጣ፤
እውነት ግን ታይታለች
በምሽት ተገልጣ።
ያቺ ውብ ጨረቃ ዮርዳኖስን ሆና፤
በከዋክብት ወረብ
ታጅባ በደመና፤
በዮሐንስ እጅ በዮርዳኖስ ሰማይ፤
ሲጠመቅ አሳየች
መድኃኔዓለም በማይ።
በላይ በሰማያት ተደገመች ቃና፤
ዕፁብ ዕፁብ አልን እኛም አየንና።
አዕምሮ ያለው ሰው
ያልገባውን እውነት፤
በስሜታዊነት የካደውን እምነት፤
የጌታዋን ጥምቀት
ጨረቃ ተረድታ፤
በስቅለቱ ደም የሆነች
ዛሬ ታየች በርታ።
"ይሄን ደማቅ ስዕል
ማን ሳለው ይባላል?
ምድሩን ይልቀቅ ስንል....
#ጨረቃን_ማን_መራው
ሊወርድ ይገባል።"
ብለህ በመናደድ ትናገር ይሆናል።
ግና የዚ ባለቤት........
በሰማይ ጨረቃ በምድር ይቅርና፤
አላየኸው እንጂ በደማቅ ተስሏል ባንተም ልቦና።
ከአምላክ ሰው መሆን በላይ ድንቅ እወነትም ተዓምርም የለም ግን አብዛኞቻችን ይህ ምስጢር ሊገባን አልቻለም አምላክ ምስጢሩን ይግለጥልን
✍በሄኖክ ክበበው 13/5/2011
በትላንትናው ዕለት ለታየው ድንቅ ተአምር የተገጠመ መንፈሳዊ ስነ-ግጥም
@Mgetem
@Mgetem
@kal002
@Mgetem
የጨረቃን ያህል አዕምሮ ስታጣ፤
መታደል ሲሳንህ የፀሐይን ዕጣ፤
ውሸት ታውጃለህ
አዲስ ነገር ላታመጣ፤
እውነት ግን ታይታለች
በምሽት ተገልጣ።
ያቺ ውብ ጨረቃ ዮርዳኖስን ሆና፤
በከዋክብት ወረብ
ታጅባ በደመና፤
በዮሐንስ እጅ በዮርዳኖስ ሰማይ፤
ሲጠመቅ አሳየች
መድኃኔዓለም በማይ።
በላይ በሰማያት ተደገመች ቃና፤
ዕፁብ ዕፁብ አልን እኛም አየንና።
አዕምሮ ያለው ሰው
ያልገባውን እውነት፤
በስሜታዊነት የካደውን እምነት፤
የጌታዋን ጥምቀት
ጨረቃ ተረድታ፤
በስቅለቱ ደም የሆነች
ዛሬ ታየች በርታ።
"ይሄን ደማቅ ስዕል
ማን ሳለው ይባላል?
ምድሩን ይልቀቅ ስንል....
#ጨረቃን_ማን_መራው
ሊወርድ ይገባል።"
ብለህ በመናደድ ትናገር ይሆናል።
ግና የዚ ባለቤት........
በሰማይ ጨረቃ በምድር ይቅርና፤
አላየኸው እንጂ በደማቅ ተስሏል ባንተም ልቦና።
ከአምላክ ሰው መሆን በላይ ድንቅ እወነትም ተዓምርም የለም ግን አብዛኞቻችን ይህ ምስጢር ሊገባን አልቻለም አምላክ ምስጢሩን ይግለጥልን
✍በሄኖክ ክበበው 13/5/2011
በትላንትናው ዕለት ለታየው ድንቅ ተአምር የተገጠመ መንፈሳዊ ስነ-ግጥም
@Mgetem
@Mgetem
@kal002
👍3❤1