ማን ይሆን?
በሃይማኖትዓይን ያየ
ከትንቢቱ ጋር ያስተያየ
አዝመራ ጠፍቶ በቡቃያ
እሕል ሲጠፋ በገበያ
ረኃብ ሲነግስ ጦም ማደሩ
የሞት ዜና ሲተላለፍ በሀገሩ
እስቲ ማን አውቋል ትንቢቱን
የፍጻሜ ምልክቱን
ነቅተን ባንሆን እንድንነቃ
ለእውነተኛ ንስሃ እንድንበቃ
ዝሙት ርኩሰት መዳራቱ
መጠጣት መስከር ጥል ማንሳቱ
ሟርት ቁጣ አድመኝነቱ
ማጨስ መቃም መደነሱ
በየጎዳናው መልከስከሱ
የማይረባ ጣኦት ማምለኩ
ለቃልቻ ለጠንቋ መንበርከኩ
ሁሉ ቀርቶ የስጋ ፈቃድ
በቃለ እግዚአብሄር እንድነሄድ
ፍቅር ደስታ ሰላም ትዕግስት
እምነት ተስፋ ራስን መግዛት
ሆኖ የእኛ ባህሪአችን መለያችን
ፀንተን ነቅተን በተዋህዶ እምነታችን እንነሳ በጉዞአችን።
✦✦✦✦✦✦✦✦✦✦✦
@Mgetem @Mgetem
በሃይማኖትዓይን ያየ
ከትንቢቱ ጋር ያስተያየ
አዝመራ ጠፍቶ በቡቃያ
እሕል ሲጠፋ በገበያ
ረኃብ ሲነግስ ጦም ማደሩ
የሞት ዜና ሲተላለፍ በሀገሩ
እስቲ ማን አውቋል ትንቢቱን
የፍጻሜ ምልክቱን
ነቅተን ባንሆን እንድንነቃ
ለእውነተኛ ንስሃ እንድንበቃ
ዝሙት ርኩሰት መዳራቱ
መጠጣት መስከር ጥል ማንሳቱ
ሟርት ቁጣ አድመኝነቱ
ማጨስ መቃም መደነሱ
በየጎዳናው መልከስከሱ
የማይረባ ጣኦት ማምለኩ
ለቃልቻ ለጠንቋ መንበርከኩ
ሁሉ ቀርቶ የስጋ ፈቃድ
በቃለ እግዚአብሄር እንድነሄድ
ፍቅር ደስታ ሰላም ትዕግስት
እምነት ተስፋ ራስን መግዛት
ሆኖ የእኛ ባህሪአችን መለያችን
ፀንተን ነቅተን በተዋህዶ እምነታችን እንነሳ በጉዞአችን።
✦✦✦✦✦✦✦✦✦✦✦
@Mgetem @Mgetem
❤6
☞ቶማስ ዘመርዓስ✍☜
የደም ዋጋ ያምላክ ጥሪ፣
ከንቱ ሆነሽ እንዳትቀሪ፣
የኖረልሽ ያቆዬሽን፣
መልሽልን መርዓስን፣
ባርኮን ይሂድ እባክሽን።
ስሚኝማ ተዋህዶ ላንቺ ነዉ የማወጋ፣
መዓልቱ አልቆ ልሊቱ እስከሚነጋ፣
ታሪክሽን ለፃፈዉ ለከፈለልሽ የደም ዋጋ።
የእሳተ ክፋይ ያንደበት ፍም፣
መርዓስ ጠበብት ማይጠፋ ስም።
መርዓስ•••••••
የኑፋቄ ህንፃ ደርማሽ፣
በወንጌል ልብን አረስራሽ።
መብረቀ-ሰማይ የአንደበት ቃል፣
የመናፍቃን ሽንፈት ድምፀተ-ደወል።
አዳም አዳም ወዴት ነህ የሚል ጥሪ፣
መርዓስ የትኅትና ዳራ ለምዕመኖቹ ነዋሪ።
የአንፆኪያ፣ቁስጥንጥንያ፣እስክንድርያና ሮሜ፣
የንስጥሮስ የውግዘት ራስ ምታት የተዋህዶ ልምላሜ።
ወየው ለአረማውያን ወየው ለከኀዲወቹ፣
ክቡር ገላህን ላጨሱት ለጨካኝ ግፈኞቹ።
የግፍ ግፍ ለሰሩብህ ገላህን እየሸለቱ፣
አፅቅህን እየቆረጡ በስምህ ለተዛበቱ።
ለ 22 ዓመት የጣር ኑሮ ሰቆቃ፣
በግፍ በበደል ጉርናት በነፍስ ሲቃ፣
መርቅያንና ሲሞን መስርይ ምን አሉ፣
ኢቦኒስት ዶሴቶቹ በጭንቀት ሲያቃጭሉ፣
አረማውያን መርገምቶች ለጣኦት ያቃጠሉህ፣
ያኔ ኒቅያ ስትሔድ መርዓስ ሆይ ምን አሉህ ?
መርዓስ••••
ኧረ የመከራህ መግለጫ ተገድፎ ጠፋኝ፣
ኅሊናዬ ወደ ውስጥ እየደማ ጤናየን እየነሳኝ።
የበረሃው ፍሬ የነጎድጓድ ድምጽ እሩምታ፣
ዲያብሎስ ራሙኤልን በቃል ግዝት ሚረታ።
የቆስጠንጢኖስ ቡራኬ መክፈቻ፣
የጉባዔው ያንድነት ልብ መቀነቻ።
እንቆጳዝዮን የታጋሾች አፍላጋት ጥበበኛ፣
የጽኑነት ተምሳሌት ያንድነት መመዘኛ።
መርዓስ የኃይማኖት እንቁ ፍሬ፣
የሳቶሪኖስ ኒቆላዎስ መቅጫ በርበሬ።
የእምነታችን ጨው ማጣፈጫ፣
የውጉዛን መለያያ ማዳመጫ።
መርዓስ•••••••
የተዋኅዶ ወጋገን የኒቅያ ኤጲስ ቆጶስ፣
ዛሬም ዳግም ፈጥነህ ድረስ፣
ባርከንና እንደድሮው እንቀደስ።
በእሸቴ በቀለ
✦✦✦✦✦✦✦✦✦✦✦✦
@Mgetem @Mgetem
የደም ዋጋ ያምላክ ጥሪ፣
ከንቱ ሆነሽ እንዳትቀሪ፣
የኖረልሽ ያቆዬሽን፣
መልሽልን መርዓስን፣
ባርኮን ይሂድ እባክሽን።
ስሚኝማ ተዋህዶ ላንቺ ነዉ የማወጋ፣
መዓልቱ አልቆ ልሊቱ እስከሚነጋ፣
ታሪክሽን ለፃፈዉ ለከፈለልሽ የደም ዋጋ።
የእሳተ ክፋይ ያንደበት ፍም፣
መርዓስ ጠበብት ማይጠፋ ስም።
መርዓስ•••••••
የኑፋቄ ህንፃ ደርማሽ፣
በወንጌል ልብን አረስራሽ።
መብረቀ-ሰማይ የአንደበት ቃል፣
የመናፍቃን ሽንፈት ድምፀተ-ደወል።
አዳም አዳም ወዴት ነህ የሚል ጥሪ፣
መርዓስ የትኅትና ዳራ ለምዕመኖቹ ነዋሪ።
የአንፆኪያ፣ቁስጥንጥንያ፣እስክንድርያና ሮሜ፣
የንስጥሮስ የውግዘት ራስ ምታት የተዋህዶ ልምላሜ።
ወየው ለአረማውያን ወየው ለከኀዲወቹ፣
ክቡር ገላህን ላጨሱት ለጨካኝ ግፈኞቹ።
የግፍ ግፍ ለሰሩብህ ገላህን እየሸለቱ፣
አፅቅህን እየቆረጡ በስምህ ለተዛበቱ።
ለ 22 ዓመት የጣር ኑሮ ሰቆቃ፣
በግፍ በበደል ጉርናት በነፍስ ሲቃ፣
መርቅያንና ሲሞን መስርይ ምን አሉ፣
ኢቦኒስት ዶሴቶቹ በጭንቀት ሲያቃጭሉ፣
አረማውያን መርገምቶች ለጣኦት ያቃጠሉህ፣
ያኔ ኒቅያ ስትሔድ መርዓስ ሆይ ምን አሉህ ?
መርዓስ••••
ኧረ የመከራህ መግለጫ ተገድፎ ጠፋኝ፣
ኅሊናዬ ወደ ውስጥ እየደማ ጤናየን እየነሳኝ።
የበረሃው ፍሬ የነጎድጓድ ድምጽ እሩምታ፣
ዲያብሎስ ራሙኤልን በቃል ግዝት ሚረታ።
የቆስጠንጢኖስ ቡራኬ መክፈቻ፣
የጉባዔው ያንድነት ልብ መቀነቻ።
እንቆጳዝዮን የታጋሾች አፍላጋት ጥበበኛ፣
የጽኑነት ተምሳሌት ያንድነት መመዘኛ።
መርዓስ የኃይማኖት እንቁ ፍሬ፣
የሳቶሪኖስ ኒቆላዎስ መቅጫ በርበሬ።
የእምነታችን ጨው ማጣፈጫ፣
የውጉዛን መለያያ ማዳመጫ።
መርዓስ•••••••
የተዋኅዶ ወጋገን የኒቅያ ኤጲስ ቆጶስ፣
ዛሬም ዳግም ፈጥነህ ድረስ፣
ባርከንና እንደድሮው እንቀደስ።
በእሸቴ በቀለ
✦✦✦✦✦✦✦✦✦✦✦✦
@Mgetem @Mgetem
❤4
፨ጋብቻ ክቡር ነው፨
ጋብቻ ክቡር ነው ከሁሉ የበለጠ
ከአምላ ለሰው ልጆች ከጥንት የተሰጠ
መረዳጃ እንዲሆን ጋብቻን ገለጠ
ብቸኝነትንም በትዳር ለወጠ፡፡
ገና ሰው ሲፈጠር ጥንት ከመጀመሪያ
አንድ ለአንድ ነው ለፍጥረት መመሪያ
ኋላም በሥጋዊ ተአምር መጀመሪያ
ጋብቻን በማክበር ሆነልን አርአያ
ሰርግ ቤት በመግባት ከእናቱ ጋራ
በድንግል ልመና ታላቅ ስራን ሰራ
ውሃ የነበረ ጋብቻ ተንቆ
ወይን ጠጅ አረገው ሰውን አስደንቆ
አባት ሌለው ልጅ እንዳይሆን ትውልዱ
እናቱን የማያወቅ እንዳይሆን በግዱ
ምንም ላልታደሰ ለዚህ ትውልድ እጣ
ከበሽታ መውደቅ በማውቀው ጣጣ
በዚህ መች አለቀ ጋብቻን ለናቀ
ማንም እየናቀው ሰውነቱ አለቀ
እለተ ሞቱንም በቅርቡ ጠበቀ
ከመጣው በሽታ እንዲሰውረን
ሁለት ከመሆን አንድ በመሆን
ይሻለን ነበረ መኖር ተባብረን
በዚህ መጥፎ ሕይወት ያለን በጠቅላላ
በንስሃ እናምልጥ በእሳት ሳንበላ
እራሳችን ድነን ሌላውን እናድን
እራስን በመግዛት በአንድ መወሰን
ይኸው ስለሆነ ፍቱን መድኃኒቱ
ሌላ ለመፈለግ አንድከም በከንቱ
ለዚህ የበቃችሁ እንኳን ደስ አላችሁ
በሃሳብ መንገድ ላይ በጉዞ ያላችሁ
እናትና ልጇ በአንድነት ይርዱአችሁ፡፡
@Mgetem @Mgetem
ጋብቻ ክቡር ነው ከሁሉ የበለጠ
ከአምላ ለሰው ልጆች ከጥንት የተሰጠ
መረዳጃ እንዲሆን ጋብቻን ገለጠ
ብቸኝነትንም በትዳር ለወጠ፡፡
ገና ሰው ሲፈጠር ጥንት ከመጀመሪያ
አንድ ለአንድ ነው ለፍጥረት መመሪያ
ኋላም በሥጋዊ ተአምር መጀመሪያ
ጋብቻን በማክበር ሆነልን አርአያ
ሰርግ ቤት በመግባት ከእናቱ ጋራ
በድንግል ልመና ታላቅ ስራን ሰራ
ውሃ የነበረ ጋብቻ ተንቆ
ወይን ጠጅ አረገው ሰውን አስደንቆ
አባት ሌለው ልጅ እንዳይሆን ትውልዱ
እናቱን የማያወቅ እንዳይሆን በግዱ
ምንም ላልታደሰ ለዚህ ትውልድ እጣ
ከበሽታ መውደቅ በማውቀው ጣጣ
በዚህ መች አለቀ ጋብቻን ለናቀ
ማንም እየናቀው ሰውነቱ አለቀ
እለተ ሞቱንም በቅርቡ ጠበቀ
ከመጣው በሽታ እንዲሰውረን
ሁለት ከመሆን አንድ በመሆን
ይሻለን ነበረ መኖር ተባብረን
በዚህ መጥፎ ሕይወት ያለን በጠቅላላ
በንስሃ እናምልጥ በእሳት ሳንበላ
እራሳችን ድነን ሌላውን እናድን
እራስን በመግዛት በአንድ መወሰን
ይኸው ስለሆነ ፍቱን መድኃኒቱ
ሌላ ለመፈለግ አንድከም በከንቱ
ለዚህ የበቃችሁ እንኳን ደስ አላችሁ
በሃሳብ መንገድ ላይ በጉዞ ያላችሁ
እናትና ልጇ በአንድነት ይርዱአችሁ፡፡
@Mgetem @Mgetem
👍6❤1🥰1
💗እናቴ ስማፀን በስምሽ💗
ድንግል ማርያም ብዬ ስማፀን በስምሽ
በቅድመ እግዚአብሔር ልመናዬን አድርሽ
እኔ ደካማ ነን ኃጢአቴ የበዛ
እኔ ጎስቋላ ነኝ በደሌ የበዛ
ጊዜዬን ያባከንኩ በዋዛ ፈዛዛ
ጊዜዬን ያባከንኩ በከንቱ በዋዛ
እመብርሃን ስልሽ ፈጥነሽ ድረሽልኝ
ልመናዬን ሰምተሽ ቆመሽ ለምኝልኝ
ኃጢአቴ ቢበዛም ይዣለው አንችን
አስምረሻልና በላዔ ሰብን
አንገቴን ቢያስደፋኝ በዝቶብኝ ኃጢአቴ
ምልጃሽን ፈለኩኝ ድንግል ሆይ እናቴ
ያን ክፉ ጨለማ እንዳላይ አደራ
ድንግል ሆይ ከልይኝ ከዲያብሎስ ጭፍራ
እመብርሃን እያልኩ ቆሜ ከደጅሽ
በብርሃን እጆችሽ እንባዬን አብሽ
አለም አታላይ ነች ወደሷ ተሳብኩኝ
ታማልጅኝ ብዬ አንቺኑ ተራብኩኝ
ከእህተ ማርያም
➣➣➣➣➣➣➣➣➣➣➣➣➣
@Mgetem @Mgetem
ድንግል ማርያም ብዬ ስማፀን በስምሽ
በቅድመ እግዚአብሔር ልመናዬን አድርሽ
እኔ ደካማ ነን ኃጢአቴ የበዛ
እኔ ጎስቋላ ነኝ በደሌ የበዛ
ጊዜዬን ያባከንኩ በዋዛ ፈዛዛ
ጊዜዬን ያባከንኩ በከንቱ በዋዛ
እመብርሃን ስልሽ ፈጥነሽ ድረሽልኝ
ልመናዬን ሰምተሽ ቆመሽ ለምኝልኝ
ኃጢአቴ ቢበዛም ይዣለው አንችን
አስምረሻልና በላዔ ሰብን
አንገቴን ቢያስደፋኝ በዝቶብኝ ኃጢአቴ
ምልጃሽን ፈለኩኝ ድንግል ሆይ እናቴ
ያን ክፉ ጨለማ እንዳላይ አደራ
ድንግል ሆይ ከልይኝ ከዲያብሎስ ጭፍራ
እመብርሃን እያልኩ ቆሜ ከደጅሽ
በብርሃን እጆችሽ እንባዬን አብሽ
አለም አታላይ ነች ወደሷ ተሳብኩኝ
ታማልጅኝ ብዬ አንቺኑ ተራብኩኝ
ከእህተ ማርያም
➣➣➣➣➣➣➣➣➣➣➣➣➣
@Mgetem @Mgetem
❤7👍3🥰2🤬1
""""======ቅድስት እናት ===""""""
""""==="""""
ይቺ ቅድስት እናት _ ቃልን ወሰነችው
በከብቶቹ ግርግም_ ወልዳ ታቀፈችው
በመጠቅለያም_ጠቀለለችው።
ለደቱንም ዘር_ አልቀደመውም
የዳዊት ሥር ነው_መድኃኒአለም
በመወለዱም ድንግልናዋን_አልለወጠውም
የተዘጋች ደጃፍ_እናታችን ማርያም።
ቃል ከአብ _ ያለ ድካም ወጣ
የአዳም ልደቱ_ ደረሰለት ዕጣ
ከድንግልም ያለ _ሕማም ተወለደ
በእውነተኛው ብርሃን_ከሳሽ ተሰደደ።
ምጥ ሳያገኛት_ተሰማ እልልታ
ሰበአ ሰገል መጡ_ሊሰግዱ ለጌታ
እረኞች _ ዘመሩ ተሞልተው ደስታ።
ለአምላክነቱ አመጡለት _ዕጣን
ለንጉሥነቱ _ አቀረቡ ወርቁን
መድኃኒት ነውና _ ገለጡት ትንቢቱን
እነሆ አየነው_ ምስዋዕት ከርቤውን።
ግርማ ያለሽ_ድንግል የአሮን በትር
እናደንቅሻለን _ የሁላችን ክብር
ገናንነትሽን _ልንዘረዝር
በያሬድ ውብ ዜማ_ በዳዊት መዝሙር
ቆመናል ከደጅሽ_ ልንደረድር።
እንደ መልአኩ ገብርኤል_ ከላይ እንደመጣው
ልናመሰግንሽ _ ማርያም ግድ ነው
የባሕሪያችን መዳን_ካንቺ ተገኘልን
በማሕጸንሽ ፍሬ_ሞት ተቀበረልን።
እንደ ሠርግ _ቤት ጉድፍ የሌለብሽ
መንፈስ ቅዱስ _ ያደረብሽ
የልዑል ኃይልም ማርያም ጸለለበሽ ።
ዘለአለም ነዋሪ_የነገስታት ንጉስ
ከኃጢአት ያዳነን_ ይመስገን ኢየሱስ
የልባችን ሰላም_ፍቅርህ በኛ ይንገስ።
ከአብ የተወለደ _ከአለም በፊት የነበረ
አንዱ ቃል እራሱን ( ባሕሪዩን) ሰወረ
እንደምን ይረቃል_የሰማዩ ምስጢር
የሱ ያደረገን_ ይመስገን እግዚአብሔር።
የኪዳን ጽላት_ያለብሽ
የተሰወረ መና_የተሸከምሽ
የወርቅ መሶብ_ የምንልሽ
ደብተራ ድንኳን _አንቺ ነሽ
የጥበብን ወንጌል_ በክንድሽ የታቀፍሽ
አሳስቢ ድንግል ሆይ_ ለመሃሪው ልጅሽ
እናምናለንና _ ሁሉ እንደሚቻልሽ
="""""ቅድስት እናት="""""""""
✍እህተ ማርያም
@Mgetem @Mgetem
📌📌📌📌📌📌📌📌📌
@MENFESAWItsufoche
""""==="""""
ይቺ ቅድስት እናት _ ቃልን ወሰነችው
በከብቶቹ ግርግም_ ወልዳ ታቀፈችው
በመጠቅለያም_ጠቀለለችው።
ለደቱንም ዘር_ አልቀደመውም
የዳዊት ሥር ነው_መድኃኒአለም
በመወለዱም ድንግልናዋን_አልለወጠውም
የተዘጋች ደጃፍ_እናታችን ማርያም።
ቃል ከአብ _ ያለ ድካም ወጣ
የአዳም ልደቱ_ ደረሰለት ዕጣ
ከድንግልም ያለ _ሕማም ተወለደ
በእውነተኛው ብርሃን_ከሳሽ ተሰደደ።
ምጥ ሳያገኛት_ተሰማ እልልታ
ሰበአ ሰገል መጡ_ሊሰግዱ ለጌታ
እረኞች _ ዘመሩ ተሞልተው ደስታ።
ለአምላክነቱ አመጡለት _ዕጣን
ለንጉሥነቱ _ አቀረቡ ወርቁን
መድኃኒት ነውና _ ገለጡት ትንቢቱን
እነሆ አየነው_ ምስዋዕት ከርቤውን።
ግርማ ያለሽ_ድንግል የአሮን በትር
እናደንቅሻለን _ የሁላችን ክብር
ገናንነትሽን _ልንዘረዝር
በያሬድ ውብ ዜማ_ በዳዊት መዝሙር
ቆመናል ከደጅሽ_ ልንደረድር።
እንደ መልአኩ ገብርኤል_ ከላይ እንደመጣው
ልናመሰግንሽ _ ማርያም ግድ ነው
የባሕሪያችን መዳን_ካንቺ ተገኘልን
በማሕጸንሽ ፍሬ_ሞት ተቀበረልን።
እንደ ሠርግ _ቤት ጉድፍ የሌለብሽ
መንፈስ ቅዱስ _ ያደረብሽ
የልዑል ኃይልም ማርያም ጸለለበሽ ።
ዘለአለም ነዋሪ_የነገስታት ንጉስ
ከኃጢአት ያዳነን_ ይመስገን ኢየሱስ
የልባችን ሰላም_ፍቅርህ በኛ ይንገስ።
ከአብ የተወለደ _ከአለም በፊት የነበረ
አንዱ ቃል እራሱን ( ባሕሪዩን) ሰወረ
እንደምን ይረቃል_የሰማዩ ምስጢር
የሱ ያደረገን_ ይመስገን እግዚአብሔር።
የኪዳን ጽላት_ያለብሽ
የተሰወረ መና_የተሸከምሽ
የወርቅ መሶብ_ የምንልሽ
ደብተራ ድንኳን _አንቺ ነሽ
የጥበብን ወንጌል_ በክንድሽ የታቀፍሽ
አሳስቢ ድንግል ሆይ_ ለመሃሪው ልጅሽ
እናምናለንና _ ሁሉ እንደሚቻልሽ
="""""ቅድስት እናት="""""""""
✍እህተ ማርያም
@Mgetem @Mgetem
📌📌📌📌📌📌📌📌📌
@MENFESAWItsufoche
👍7❤2🥰1
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#የአፎምያ_አጽናኝ
@Mgetem
ከቀደመው መንገድ ከላይ በተሰጠን
ዕድሳት በማያውቅ በማይሻርው ዘመን
በድንቅ ምስክሮች ብርሃን በሆኑን
እንድንጓዝ ሁሌም የአፎምያ አጽናኝ
ጠላት ቀስቱን ሰብቆ ሊያጠፋን ሲመጣ
እንደ ቋጥኝ ከቦን የዚህ አለም ጣጣ
በከንቱ ስንሮጥ ኋላ እንዳንቀጣ
አማልደን መላኩ የነፍሳችን ዕጣ
የሁሉንም ጸሎት ከአምላክ የምታደርስ
ፍቅር እና ርህራሄ በሰው የምታለብስ
ልክ እንደ ትላንቱ ዛሬም ፈጥነህ ድረስ
በአንደበትህ ፍሬ ውስጣችን ይታደስ
የዳንኤል አጽናኝ የአፎምያ ረዳት
በህይወት የቀየርክ የባህራንን ጽሕፈት
በለአምን የታደክ ከእርግማን መቅጸፍት
እኛንም ጠብቀን ከምናየው መአት
የምጽአት ዋዜማ ለመሆኑ ምስክር
በመጽሐፍ ያለው ቃሉ ሲተገበር
መተማመን ጠፍቶ ሲቀወቅዝ ፍቅር
በወንጌሉ አንድምታ ልባችን ይታጠር
ይቅርታ ምህርቱ ይምጣልን የእግዚአብሔር
እረኛ እንደሌለው ሲጨነቅ ትውልዱ
ተመሳስሎ ቆሞ ሲያስት በመንገዱ
ግራ በመጋት ስንቶቹ ተጎዱ
በየዋህነታቸው አብረው ተሰደዱ
ዘንዶ አፉን ከፍቶ ነፍሳት እንዳይወጥ
የተዋህዶን መዝገብ እውነቱን ለመግለጥ
የቆመውን ሁሉ በአውደ ምህረቱ
ያበረታን አምላክ እሰከ ምጽአቱ።
_____________________________
እንኳን ለሊቀመላአኩ ለቅዱስ ሚካኤል ወርሃዊ ክብር በዓል በሰላም አደርሳቹ አደረሰን የመላአኩ ረድኤት እና ምልጃው አይለየን አሜን!
_____________________________
@Mgetem
@Mgetem
@Menfesawi_getem_bot
@Mgetem
ከቀደመው መንገድ ከላይ በተሰጠን
ዕድሳት በማያውቅ በማይሻርው ዘመን
በድንቅ ምስክሮች ብርሃን በሆኑን
እንድንጓዝ ሁሌም የአፎምያ አጽናኝ
ጠላት ቀስቱን ሰብቆ ሊያጠፋን ሲመጣ
እንደ ቋጥኝ ከቦን የዚህ አለም ጣጣ
በከንቱ ስንሮጥ ኋላ እንዳንቀጣ
አማልደን መላኩ የነፍሳችን ዕጣ
የሁሉንም ጸሎት ከአምላክ የምታደርስ
ፍቅር እና ርህራሄ በሰው የምታለብስ
ልክ እንደ ትላንቱ ዛሬም ፈጥነህ ድረስ
በአንደበትህ ፍሬ ውስጣችን ይታደስ
የዳንኤል አጽናኝ የአፎምያ ረዳት
በህይወት የቀየርክ የባህራንን ጽሕፈት
በለአምን የታደክ ከእርግማን መቅጸፍት
እኛንም ጠብቀን ከምናየው መአት
የምጽአት ዋዜማ ለመሆኑ ምስክር
በመጽሐፍ ያለው ቃሉ ሲተገበር
መተማመን ጠፍቶ ሲቀወቅዝ ፍቅር
በወንጌሉ አንድምታ ልባችን ይታጠር
ይቅርታ ምህርቱ ይምጣልን የእግዚአብሔር
እረኛ እንደሌለው ሲጨነቅ ትውልዱ
ተመሳስሎ ቆሞ ሲያስት በመንገዱ
ግራ በመጋት ስንቶቹ ተጎዱ
በየዋህነታቸው አብረው ተሰደዱ
ዘንዶ አፉን ከፍቶ ነፍሳት እንዳይወጥ
የተዋህዶን መዝገብ እውነቱን ለመግለጥ
የቆመውን ሁሉ በአውደ ምህረቱ
ያበረታን አምላክ እሰከ ምጽአቱ።
_____________________________
እንኳን ለሊቀመላአኩ ለቅዱስ ሚካኤል ወርሃዊ ክብር በዓል በሰላም አደርሳቹ አደረሰን የመላአኩ ረድኤት እና ምልጃው አይለየን አሜን!
_____________________________
@Mgetem
@Mgetem
@Menfesawi_getem_bot
👍4❤2👏1
#ስውር_ቅኔ
@Mgetem
የቤተ ክርስትያን ደጅ ዕለት ተለት ስሜ
በፆም በፀሎት በስግደት ደክሜ
አምላኬን ለመንኩት
የሚያስፈልገኝን ዘርዝሬ ነገርኩት
የሚያስፈልገኝ ነገር ቢዘገይ ጊዜ
ነፈከኝ ብዬ በምሬት አንካሴ
ፈጣሪን ወጋሁት
ልቡን አደማሁት
በስርዓት አጥ ምሬቴ
በአጉል እምነቴ
ልቡ ስለቆሰለ
በደመና መሀል ጌታዬ እንዲህ አለ
‹‹ ሁሉን የማቀው እኔ ሆኘ ሳለ
ነፈከኝ ለማለት ምነው ልቦናህ ቸኮለ
ዘርዝረህ የላከውን የልመና ፀሎት
ይመለከት ዘንድ ዐይኔ ተተከለ
የምትፈልገው እንጅ የሚያስፈልግህ አንድም እንደሌሌ
የታዘበው እጄ የጠየከኝን ከማድረግ ተከለከለ
ግና ልጄ አዕምሮህ በደንብ ካሰተዋለ
ባለማድረግ ውስጥም ታላቅ ማድረግ አለ>>
✍ ዳንኤል ከበደ
@Mgetem
@Mgetem
@Menfesawi_getem_bot
ግጥሞቻችሁን ላኩልን
@Mgetem
የቤተ ክርስትያን ደጅ ዕለት ተለት ስሜ
በፆም በፀሎት በስግደት ደክሜ
አምላኬን ለመንኩት
የሚያስፈልገኝን ዘርዝሬ ነገርኩት
የሚያስፈልገኝ ነገር ቢዘገይ ጊዜ
ነፈከኝ ብዬ በምሬት አንካሴ
ፈጣሪን ወጋሁት
ልቡን አደማሁት
በስርዓት አጥ ምሬቴ
በአጉል እምነቴ
ልቡ ስለቆሰለ
በደመና መሀል ጌታዬ እንዲህ አለ
‹‹ ሁሉን የማቀው እኔ ሆኘ ሳለ
ነፈከኝ ለማለት ምነው ልቦናህ ቸኮለ
ዘርዝረህ የላከውን የልመና ፀሎት
ይመለከት ዘንድ ዐይኔ ተተከለ
የምትፈልገው እንጅ የሚያስፈልግህ አንድም እንደሌሌ
የታዘበው እጄ የጠየከኝን ከማድረግ ተከለከለ
ግና ልጄ አዕምሮህ በደንብ ካሰተዋለ
ባለማድረግ ውስጥም ታላቅ ማድረግ አለ>>
✍ ዳንኤል ከበደ
@Mgetem
@Mgetem
@Menfesawi_getem_bot
ግጥሞቻችሁን ላኩልን
❤3👍1🥰1
#አፈረሰበት_እቅዱን
@Mgetem
የሰው ዘር ቀዳሚ ጠላት
ለዓለም የሐሰት አባት
የአዳምን ኃጢአት መስራች
በሰዎች ውድቀት ተደሳች
የሐዘን ቤቶችን ለመስራት
ተኝቶ አያውቅም በእውነት
በደምና እንባ እያራሰ
በሰው አጥንት እየማሰ
የሞትን መሰረት በመጣል
የኃጢአት ምሰሶ በመትከል
እጅግ ብዙ ዘመናት ትግሏል
የሞቱን መውጊያ ለመንቀል
ምክንያተ ድኂን ናት ድንግል
የአዳምን እዳ ለማስወገድ
ሥጋን ለበሰ እግዚአብሔር ወልድ
አማኑኤል ሰው በመሆን
ክፉ ተግባሩን የሰይጣንን
አፈረሰበት ዕቅዱን፡፡
____________________________
@Mgetem
@Mgetem
@bubushu
@Mgetem
የሰው ዘር ቀዳሚ ጠላት
ለዓለም የሐሰት አባት
የአዳምን ኃጢአት መስራች
በሰዎች ውድቀት ተደሳች
የሐዘን ቤቶችን ለመስራት
ተኝቶ አያውቅም በእውነት
በደምና እንባ እያራሰ
በሰው አጥንት እየማሰ
የሞትን መሰረት በመጣል
የኃጢአት ምሰሶ በመትከል
እጅግ ብዙ ዘመናት ትግሏል
የሞቱን መውጊያ ለመንቀል
ምክንያተ ድኂን ናት ድንግል
የአዳምን እዳ ለማስወገድ
ሥጋን ለበሰ እግዚአብሔር ወልድ
አማኑኤል ሰው በመሆን
ክፉ ተግባሩን የሰይጣንን
አፈረሰበት ዕቅዱን፡፡
____________________________
@Mgetem
@Mgetem
@bubushu
👍2
#አደበታችን_የድንግልን_ስራ_ያመሰግናል
_____________________
የአለም መዳኒት ከእርሷ ስጋን ነስቶ
የምስራች ዜና በገብርኤል ተሰምቶ
ለልዑል ማደርያ ትሆን ይገባታል
በዳዊት ሀገር ከእርሷ ተወለደ
ለማእፀኗ ፍሬ ትውልዱ ሰገደ
ፅሃይን ታቅፋ ብረሃንን የሰጠች
ከምድር ፍጥረታት እጅግ የተለየች
የተዋህዶ አርማ ላይናችን ድንቅ ነች(፪)
እናትና ድንግል ሁለቱንም ይዛ
በድንግልናው የአለሙን ቤዛ ይዛ
እርኩሰት የሌለባት የተመረጠች ከሰማይ
ኑ እናመስግናት አህዛብ ባንድ ላይ
የህይወት እንጀራን ስላስገኘች ሲሳይ
#ከእህተ_ማርያም
__________________________
@Mgetem
@Mgetem
@kal002
_____________________
የአለም መዳኒት ከእርሷ ስጋን ነስቶ
የምስራች ዜና በገብርኤል ተሰምቶ
ለልዑል ማደርያ ትሆን ይገባታል
በዳዊት ሀገር ከእርሷ ተወለደ
ለማእፀኗ ፍሬ ትውልዱ ሰገደ
ፅሃይን ታቅፋ ብረሃንን የሰጠች
ከምድር ፍጥረታት እጅግ የተለየች
የተዋህዶ አርማ ላይናችን ድንቅ ነች(፪)
እናትና ድንግል ሁለቱንም ይዛ
በድንግልናው የአለሙን ቤዛ ይዛ
እርኩሰት የሌለባት የተመረጠች ከሰማይ
ኑ እናመስግናት አህዛብ ባንድ ላይ
የህይወት እንጀራን ስላስገኘች ሲሳይ
#ከእህተ_ማርያም
__________________________
@Mgetem
@Mgetem
@kal002
❤2👍1
✤ ተሸክሜ አልጋዬን ✤
ጠዋት በማለዳ
ቤትህ እንዳልገሰግስ
ሌሊቴ እንደ ዳዊት
ስምህን እንዳልቀድስ
ካልጋዬ ጋር አስሮ
የያዘኝ ደዌ
የድብርት ብርድልብስ
የእንቅልፍ አባዜ
አርቅልኝና
ተሸክሜ አልጋዬን
ዘወትር በቤትህ
ብሰማ ጩኸቴን።
*ከመቅደስ አያሌው
@Mgetem
ጠዋት በማለዳ
ቤትህ እንዳልገሰግስ
ሌሊቴ እንደ ዳዊት
ስምህን እንዳልቀድስ
ካልጋዬ ጋር አስሮ
የያዘኝ ደዌ
የድብርት ብርድልብስ
የእንቅልፍ አባዜ
አርቅልኝና
ተሸክሜ አልጋዬን
ዘወትር በቤትህ
ብሰማ ጩኸቴን።
*ከመቅደስ አያሌው
@Mgetem
👍4❤2
#ስንት_ቀን_ፈጀብህ?
/መንፈሳዊ መነባንብ /
-----------------✞-------------------
ለአዳም ኪዳን ሰጠህ
እንደምትወለድ ወደ ምድር ወርደህ
እንዴት ነበር ያኔ..?
ወደ እኛ ስትመጣ መላእክትን ትተህ?
………
የሔዋን እርግማን
የባሏም የውርስ ኃጢአት መዘገን
እንዲያ አሳሰበህና
መጣህልን ሁሉን አደረግህ በፅሙና
.........
እንዴት ነበር ያኔ..?
ያችን ንጹሕ ለመፈለግ የወሰደብህ ጊዜ
አድርገህ የሰጠኸንን ፈውስ በበድልን ጊዜ
ግን ምን ያህል ነው ልፋትህ?
ድንግልን ስትፈልግ የፈጀብህ?
.........
ከሰማያት ስትወርድ አጀቡህ መላእክት?
ዓለሙስ ተናወፀ በይባቤ በስብሐት?
ያ ምቀኛ ዲያቢሎስ ግን ምን አለ?
ወደ እኛ ስትመጣ አለ አይደል ኮበለለ?
ነው ሥጋ ለብሶ ጉድ ሠራኝ አለ?
........
እንዴት ነው እርቀቱ
የሰማይ ምጥቀቱ
የምድርስ ሥፋት
ከሷ እስክታርፍባት?
ግን ጌታ...?ሰማያት ምን አሉ
ትትሀቸው መጠህ ባንተ አጉረመረሙ?
ፍጥረታትስ ቢሆን ማሕሌት አቆሙ?
.......
ምሥጢረኛው ጌታ
መንገድህ በየት ነው ወደ እኛ ስትመጣ?
ቤተ ልሔም ስትደርስ
ማን አገለገልህ?ምን አለች ምድሪቱስ
እያቄም ወሐናን እንዴት መረጥሃቸው
አንተ እንድትወለድ ምክንያትህ ናቸው
.......
ሰማዩ ሰፊ ነው
ምድርንም ታውቃለህ
እንዴት እንድትሰፋ ሆና መረገጫህ
ግን እና ጌታ ሆይ ምኑ ነው የቻለህ?
የድንግል ማሕጸን እሳት መሸከሙ
ምድርም መልኮት በእሷ ላይ መቆሙ
..........
እንዴት ነበር ያኔ
በቤተ ልሔም ውስጥ
አንተን የሚያሞቅ ከእንስሶች ስትሰጥ?
........
ዮሴፍ ምን አለ
አንተን በማየቱ እርጅናው ታጎለ?
አንተን የጠበቀህ አዳምስ በግርማህ ምን አለ?
........
እንዴት ነው ስጦታው
የሰብአ ሰገሉ ወርቅ እጣን አምኃው
የእረኞቹ ደስታ
የመላእክት ብሥራት የልደትህማታ
.........
እንዴት ነበር ያኔ
የልደትህ ማታ
የዝማሬው ለታ
የእናትህ ደስታ
የፍጥረት እልልታ
ሚዳቋ ስትዘል ከኢትዮጵያ አይታ
ግን ጌታ እረቂቁ አምላክ
በየትስ መጠህ ነው ከኛ የተወለድክ
✞ወስብሐት ለእግዚአብሔር ✞
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem
/መንፈሳዊ መነባንብ /
-----------------✞-------------------
ለአዳም ኪዳን ሰጠህ
እንደምትወለድ ወደ ምድር ወርደህ
እንዴት ነበር ያኔ..?
ወደ እኛ ስትመጣ መላእክትን ትተህ?
………
የሔዋን እርግማን
የባሏም የውርስ ኃጢአት መዘገን
እንዲያ አሳሰበህና
መጣህልን ሁሉን አደረግህ በፅሙና
.........
እንዴት ነበር ያኔ..?
ያችን ንጹሕ ለመፈለግ የወሰደብህ ጊዜ
አድርገህ የሰጠኸንን ፈውስ በበድልን ጊዜ
ግን ምን ያህል ነው ልፋትህ?
ድንግልን ስትፈልግ የፈጀብህ?
.........
ከሰማያት ስትወርድ አጀቡህ መላእክት?
ዓለሙስ ተናወፀ በይባቤ በስብሐት?
ያ ምቀኛ ዲያቢሎስ ግን ምን አለ?
ወደ እኛ ስትመጣ አለ አይደል ኮበለለ?
ነው ሥጋ ለብሶ ጉድ ሠራኝ አለ?
........
እንዴት ነው እርቀቱ
የሰማይ ምጥቀቱ
የምድርስ ሥፋት
ከሷ እስክታርፍባት?
ግን ጌታ...?ሰማያት ምን አሉ
ትትሀቸው መጠህ ባንተ አጉረመረሙ?
ፍጥረታትስ ቢሆን ማሕሌት አቆሙ?
.......
ምሥጢረኛው ጌታ
መንገድህ በየት ነው ወደ እኛ ስትመጣ?
ቤተ ልሔም ስትደርስ
ማን አገለገልህ?ምን አለች ምድሪቱስ
እያቄም ወሐናን እንዴት መረጥሃቸው
አንተ እንድትወለድ ምክንያትህ ናቸው
.......
ሰማዩ ሰፊ ነው
ምድርንም ታውቃለህ
እንዴት እንድትሰፋ ሆና መረገጫህ
ግን እና ጌታ ሆይ ምኑ ነው የቻለህ?
የድንግል ማሕጸን እሳት መሸከሙ
ምድርም መልኮት በእሷ ላይ መቆሙ
..........
እንዴት ነበር ያኔ
በቤተ ልሔም ውስጥ
አንተን የሚያሞቅ ከእንስሶች ስትሰጥ?
........
ዮሴፍ ምን አለ
አንተን በማየቱ እርጅናው ታጎለ?
አንተን የጠበቀህ አዳምስ በግርማህ ምን አለ?
........
እንዴት ነው ስጦታው
የሰብአ ሰገሉ ወርቅ እጣን አምኃው
የእረኞቹ ደስታ
የመላእክት ብሥራት የልደትህማታ
.........
እንዴት ነበር ያኔ
የልደትህ ማታ
የዝማሬው ለታ
የእናትህ ደስታ
የፍጥረት እልልታ
ሚዳቋ ስትዘል ከኢትዮጵያ አይታ
ግን ጌታ እረቂቁ አምላክ
በየትስ መጠህ ነው ከኛ የተወለድክ
✞ወስብሐት ለእግዚአብሔር ✞
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem
👍6❤2
#የቆሎ_ተማሪ_ዘድንግል
@Mgetem
በዳዊት በገና በያሬድ ዝማሬ
እኔም ላወድስሽ ቃላትን ደርድሬ
የጌታዬ እናት ስምሽ ይጣፍጣል
ባህዛብ መካከል አፌ አንችን ይጠራል
ማርያም ማርያም ስልሽ ጠላት ይሸበራል
አሁንም ጠራሁሽ አውሬው እርር ይበል
አምላኬ ስጥራሽ ሰምቻለሁ በፍቅር
እናቴ ለክብርሽ አልሻም ምስክር
ምልጃና ፀሎትሽ ምርኩዜ ሆኖኝ
አሰፈሪውን ለሊት ስንቱን አለፈኩኝ
ልቤ አይከፈትም ዝግ ነው ለጠላቴ
ዘውትር አይለየኝም ስእልሽ ከደረቴ።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
፤እንቺ የገነት ምንጭ ፥ የሕይውት ውኃ ጉድጓድ ፥ከሊበኖስም
የሚፈስስ ወንዘ ነሽ። መኃልየመኃለይ ዘሰሎሞን4 ፡ 15
----------------------------------------------
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem
በዳዊት በገና በያሬድ ዝማሬ
እኔም ላወድስሽ ቃላትን ደርድሬ
የጌታዬ እናት ስምሽ ይጣፍጣል
ባህዛብ መካከል አፌ አንችን ይጠራል
ማርያም ማርያም ስልሽ ጠላት ይሸበራል
አሁንም ጠራሁሽ አውሬው እርር ይበል
አምላኬ ስጥራሽ ሰምቻለሁ በፍቅር
እናቴ ለክብርሽ አልሻም ምስክር
ምልጃና ፀሎትሽ ምርኩዜ ሆኖኝ
አሰፈሪውን ለሊት ስንቱን አለፈኩኝ
ልቤ አይከፈትም ዝግ ነው ለጠላቴ
ዘውትር አይለየኝም ስእልሽ ከደረቴ።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
፤እንቺ የገነት ምንጭ ፥ የሕይውት ውኃ ጉድጓድ ፥ከሊበኖስም
የሚፈስስ ወንዘ ነሽ። መኃልየመኃለይ ዘሰሎሞን4 ፡ 15
----------------------------------------------
@Mgetem
@Mgetem
❤2
#ሳልፆም_ሊፈሰክ_ነው
አይ የኔ ነገር!!!
@Mgetem
እርግጥ አልበላሁም ስጋም ሆነ ቅቤ
አልፆም አለኝ እንጂ አመፀኛ ልቤ
ካምናና ካቻምና የዘንድሮ ብሶ
መላ ማንነቴ በሀጢያት ተለውሶ
ስዋሽ ስቀጥፍ
ህግን ስተላለፍ
ስሰድብ ሳደማ
የሰው ስጋ ሳማ
ባይኔ ሳመነዝር
የሰው ሰው ሳማትር
ገላዬን ሳራቁት
አዳምን/ሔዋንን ሳሳስት
ስረሳ ስቃይህን
መስቀል ህማምህን
ያን ሁሉ ግርፋት
ነብሴ ሳያስጨንቃት
አይ እኔ
በሀሰት ስመሰክር
በሀጢያት ስዳክር
ለማይሞላ ኑሮ
ሳልሻል ዘንድሮ
ፆሙ ተጋመሰ
ጊዜው ተጋመሰ
ጌታ ሆይ
አቤቱ አስበኝ
ለንሰሀ አብቃኝ
እስቲ የቀረውን ለበረከት በለው
አመፀኛ ልቤ ፆምህን ይፁመው
"ከደጀ ሰላሙ ከካህኑ እግር ስር
ንስሀዬን ልውሰድ ስለመስቀል ፍቅር"
የንሰሀ ህይወት ይስጠን!
___________________________
@Mgetem
@Mgetem
@Menfesawi_getem_bot
አይ የኔ ነገር!!!
@Mgetem
እርግጥ አልበላሁም ስጋም ሆነ ቅቤ
አልፆም አለኝ እንጂ አመፀኛ ልቤ
ካምናና ካቻምና የዘንድሮ ብሶ
መላ ማንነቴ በሀጢያት ተለውሶ
ስዋሽ ስቀጥፍ
ህግን ስተላለፍ
ስሰድብ ሳደማ
የሰው ስጋ ሳማ
ባይኔ ሳመነዝር
የሰው ሰው ሳማትር
ገላዬን ሳራቁት
አዳምን/ሔዋንን ሳሳስት
ስረሳ ስቃይህን
መስቀል ህማምህን
ያን ሁሉ ግርፋት
ነብሴ ሳያስጨንቃት
አይ እኔ
በሀሰት ስመሰክር
በሀጢያት ስዳክር
ለማይሞላ ኑሮ
ሳልሻል ዘንድሮ
ፆሙ ተጋመሰ
ጊዜው ተጋመሰ
ጌታ ሆይ
አቤቱ አስበኝ
ለንሰሀ አብቃኝ
እስቲ የቀረውን ለበረከት በለው
አመፀኛ ልቤ ፆምህን ይፁመው
"ከደጀ ሰላሙ ከካህኑ እግር ስር
ንስሀዬን ልውሰድ ስለመስቀል ፍቅር"
የንሰሀ ህይወት ይስጠን!
___________________________
@Mgetem
@Mgetem
@Menfesawi_getem_bot
👍4❤2🥰1
❖የሰማዩ ጌታ የአርያም ባለቤት❖
❖የአምላኮች አምላክ የፍጥረታት አባት❖
❖ሀያል ፍቅር ስቦት ከመንበሩ ወርዶ❖️
❖በዛ በበረት በከብቶች ግርግም ️
..ከንፅህት ቅድስት ድንግል ማርያም ተወልዶ❖
❖እኛን ላዳነበት ለብርሃነ ልደቱ❖
❖እንኳን አደረሰን አደረሳችሁ።❖
-----ከ ሰመረ ፍስሃ---
#መልካም_በአል
❖የአምላኮች አምላክ የፍጥረታት አባት❖
❖ሀያል ፍቅር ስቦት ከመንበሩ ወርዶ❖️
❖በዛ በበረት በከብቶች ግርግም ️
..ከንፅህት ቅድስት ድንግል ማርያም ተወልዶ❖
❖እኛን ላዳነበት ለብርሃነ ልደቱ❖
❖እንኳን አደረሰን አደረሳችሁ።❖
-----ከ ሰመረ ፍስሃ---
#መልካም_በአል
🥰1