Malae Woreda Sencie and Information Technology
9 subscribers
5 photos
1 video
2 links
Sencie and Information Technology
Download Telegram
የኮምፒዩተር እና ሞባይል ስልክ ላይ የሚጫኑ ጌምዎች እና ቴሌቪዥን የልጆችን የአእምሮ ዕድገት እያቀጨጩ ነው ሲሉ ተመራማሪዎች አስጠነቀቁ።

"በልጆቻችን ላይ እየፈጸምነው ያለው ግፍ ይቅር የማይባል ነው" ይላሉ ሚሸል ደስመርጌት። እኚህ ሰው ፈረንሳዊ ሳይንቲስት ናቸው። ከሰሞኑ ዓለምን እያነጋገሩ ነው።
"በዚህ ዘመን የሚወለዱ ልጆችን ድንዙዝ እያደረግናቸው ነው፤ ይህም የሚሆነው ብዙ ጌሞችን፣ ብዙ የስክሪን ሰዓቶችን ስለፈቀድልናቸው ነው፤ ሳናውቀው ስንፍናን እያወረስናቸው ነው" ይላሉ።

ፕሮፌሰር ሚሸል የኒውሮሳይንስ ሊቅ ናቸው። ዘለግ ላሉ ዓመታት በጉዳዩ ዙርያ ጥናት አድርገው የደረሱበት ሐቅ አንድ ነው። ይህም በዲጂታል ዘመን የተወለዱ ልጆች የአእምሮ ምጥቀት ልኬታቸው (IQ) በሚያስደነግጥ ሁኔታ እያሽቆለቆለ መሆኑን።

ብዙ ወላጆች በተቃራኒው ያስባሉ። ለልጆቻቸው ጌምና ስልክ በገፍ ያቀርቡላቸዋል።

ልጆቻቸው ስልክ ነካክተው በራሳቸው መክፈታቸው የአእምሮ እድገት ልቀት መስሎ ይታያቸዋል።

"ልጄን እኮ…" ብለው ማዳነቅ የሚወዱ ወላጆች ብዙ ናቸው።

ልጆቻቸው ፊልም ተመልከተው መሳቃቸው በራሱ የብልህነታቸው ማሳያ ያደርጉታል።

በመላው ዓለም ልጆች ረዥም ሰዓት በዲጂታል ዓለም ውስጥ ቀልባቸው ይሰወራል። ይህ እንዲሆን የፈቀደው ትውልድ በልጆቹ ላይ ይቅር የማይባል ግፍ ነው እየፈጸመ ያለው ይላሉ ፕሮፌሰር ሚሸል።

የዲጂታል ቁሶች (ስልክ፣ ጌም፣ ቴሌቪዥንና የመሳሰሉት) የልጆችን የአእምሮ ዕድገት እያቀጨጩ ነው ባይ ናቸው ፕሮፌሰሩ።

አሁን የእሳቸው ሐሳብ በሳይንስ ማኅበረሰቡ ዘንድ ከፍተኛ ክርክር ቀስቅሷል።
Forwarded from Tgg
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
በጂንካ የሳኢቴ መምሪያ እና የጂንካ ዩኒቨርሲቲ በቅንጅት ያዘጋጁት የፈጠራ ስራ ኤግዥቢሽን ፕሮግራም
"ዴልታ" የተሰኘው የኮቪድ ዝርያ ኢትዮጵያ ውስጥ ተገኘ።

አደገኛው የኮቪድ ዴልታ ዝርያ ኢትዮጵያ ውስጥ መገኘቱን የጤና ሚኒስቴር ይፋ አደረገ።

የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ በሰጡት መግለጫ “በኢትዮጵያ ባለፉት ሳምንታት በወረርሽኙ የሚያዙ ሰዎች፣ የሚሞቱና ፅኑ ህሙማን ቁጥር በጣም አሻቅቧል” ብለዋል።

አዲሱ ዝርያ ሁሉንም የዕድሜ ክልል የሚያጠቃ፣ ለከባድ ህመምና ሞት የሚዳርግ በተለይም ባልተከተቡ ሰዎች ላይ የሚበረታ ዝርያ መሆኑን ገልፀዋል።

ክትባት በየጤና ተቋማቱ በመገኘት እንዲወስዱ፣ የኮቪድ ፕሮቶኮልን ከሁሉም ተቋማትና ግለሰቦች እንደሚጠበቅም አሳስበዋል።

በኢትዮጵያ ባለፈው ሳምንት ብቻ 8 ሺህ 300 ሰዎች በወረርሽኙ ተይዘዋል።

እስካሁን በአገሪቱ 313 ሺህ ሰዎች በበሽታው ተይዘዋል። ከ4 ሺህ 700 በላይ ሰዎች ደግሞ በወረርሽኙ ሳቢያ ሕይወታቸው አልፏል።

በኮቪድ ወረርሽኝ የመያዝ ምጣኔውም ከ1 በመቶ ወደ 20 በመቶ አሻቅቧል ፤ ባለፈው ሳምንት 118 ሰዎች ሞተዋል። #ENA

@tikvahethiopia
Forwarded from Tgg
በፈጣን ኢንተርኔት ዘገምተኛ አገልግሎት
*************************************
በኢንተርኔት ተጠቃሚዎች ዘንድ በአሰልቺነታቸው ከሚታወቁ ችግሮች መካከል አንደኛው ከፍተኛ የሆነ ፍጥነት ያለው የበይነ መረብ አገልግሎት እየተጠቀምን እንኳን በተግባር ያለው ፍጥነቱ በጣም ዘገምተኛ መሆን ነው፡፡ ለምሳሌ በአውስትራሊያ ካሉ 8.2 ሚሊዮን የመኖሪያና የንግድ ቤቶች ባሳለፍነው ነሀሴ 2021 የተሰበሰበ መረጃ እንደሚያመለክተው 77 በመቶ የሚሆኑ ተጠቃሚዎች በገመድ የሚተላለፍን የበይነ መረብ አገልግሎት የሚጠቀሙ ሲሆን ይህም በሴኮንድ 50 ሜጋ ባይት ማስጠቀም የሚያስችል ነው፡፡

ይህም በቤት ውስጥም ሆነ በስራ ቦታ የተለያዩ ከፍተኛ የኢንተርኔት ፍጥነት የሚፈልጉ አገልግሎቶችን ለማግኘት በቂ እንደሆነ ይታወቃል፡፡ ለምሳሌ አንድ ሰው ኔትፍሊክስን ለመከታተል 12 ሜጋ ባይት የሚደርስ ፍጥነት ያስፈልገዋል፡፡ ለቪዲዮ ኮንፍረንስ ደግሞ ከ2-3 ሜጋ ባይት በሴኮንድ ሲያስፈልገው ለተለያዩ ጌሞች ከ1 ሜጋ ባይት ያነሰ ፍጥነት ያስፈልገዋል፡፡

ይሁን እንጂ 50 ሜጋ ባይት ፍጥነት ያለውን የበይነ መረብ አገልግሎት የሚጠቀም ሰው የቪዲዮዎች መቆራረጥ፣ የምስሎች በፍጥነት አለመክፈት እና መረጃዎችን በፍጥነት የማስተላለፍ ችግር ይገጥመዋል፡፡ ይህ ችግር ማለትም ፈጣን ኢንተርኔት እያለ እንኳን የሚከሰት መቆራረጥ መሰረታዊ ችግሩ የሚመነጨው ከኢንተርኔት ፍጥነት ሳይሆን ከፍጥነት ጋር ከማይያያዙ latency እና loss ከተባሉ ችግሮች ነው፡፡

ሌተንሲ ወይም አንድ መረጃ ከመረጃ ቋት ወደ መገልገያ ቦታችን ለመድረስ የሚጨርስበት ጊዜ የሚመለከት ሲሆን አነስተኛ እና በአመዛኙ ተመጣጠኝ ወይም ወጥ የሆነ እንዲሆን በማድረግ ችግሩን መቅረፍ ይቻላል፡፡ ሁለተኛው ደግሞ ከመረጃ ቋት ወደ ቤታችን ወይም ወደ መገልገያ ኮምፒውተራችን ወይም ስልካችን መረጃ ሲተላለፍ በጉዞ ሂደት የመጥፋት (loss) ወይም መንገድ ላይ የመቅረት ችግር ነው፡፡

ከላይ በተጠቀሰው ቦታ የተሰራው ጥናት እንደሚያመለክተው ሰዎች ለአገልግሎት ከከፈሉት የኢንተርኔት ፍጥነት ውስጥ በብዛት የሚጠቀሙት ከ6 በመቶ የማይበልጠውን ነው፡፡ ከዚህ በተቃራኒው ደግሞ በኦንላን ያለን ቆይታ ካለፈው አመት በ59 በመቶ መጨመሩ ተነግሯል፡፡

ምንጭ techxplore
ተጨማሪ ንባብ https://techxplore.com/news/2021-09-internet-jumpy-high.html
ቴሌግራም ለሳይበር ወንጀለኞች ምቹ እየሆነ መምጣቱን ጥናት አመለከተ፡፡

የመልዕክት መላላኪያ መተግበሪያው ቴሌግራም ለሳይበር ወንጀለኞች እንቅስቃሴ ምቹ እየሆነ መምጣቱ ተገለፀ፡፡

የሳይበር ደህንነት ተቋም የሆነው ሳይበርኢንት እና ፋይናንሺያል ታይምስ በጋራ ባደረጉት ጥናት መተግበሪያው የተመዘበሩ መረጃዎች እና ለጠለፋ (hack) የሚውሉ መጠቀሚያዎችን ለመሸጥና ለመግዛት በሳይበር ወንጀለኞች ዘንድ በከፍተኛ ደረጃ ተመራጭ እየሆነ መምጣቱ ተመላክቷል፡፡

ከዚህ ቀደም ወንጀለኞቹ ለመሰል ተግባራት ዳርክ ዌብ የተባለውን ምስጢራዊ የበይነ መረብ ሥርዓት ይጠቀሙ እንደነበር ፋይናንሺያል ታይምስ ያወጣው ሀተታ ያመላክታል፡፡

ቴሌግራም ለአጠቃቀም ቀላል እና የሚደረግበት ቁጥጥር መላላት ወንጀለኞቹ ወደ መተግበሪያው ፊታቸውን ለማዞራቸው በምክንያትነት ተቀምጧል፡፡

በመቶ ሺዎች የሚጠጉ የተለያዩ ግለሰቦች መጠቀሚያ ኢሜይሎች እና የምስጢር ቁልፎች ወንጀለኞቹ በሚጠቀሙባቸው የመተግበሪያው ቻናሎች እና የቡድን መጠቀሚያዎች (group) ውስጥ ለሽያጭ ሲተዋወቁ መታዘቡን ዘገባው አመላክቷል፡፡

ለክፍያ አገልግሎት የሚውል ካርድ እና የግለሰቦች የባንክ መረጃ እንዲሁም የፓስፖርት ቅጂዎች በመተግበሪያው መጠቀሚዎች ለሽያጭ ከሚቀርቡት መካከል መሆናቸው ተጠቁሟል፡፡ ከነዚህ በተጨማሪም የሰዎችን መረጃ ለመበርበር የሚያገለግሉ ሶፍትዌሮች እና መመሪያዎች በወንጀለኞቹ እንደሚቀርቡ ጥናቱ ታዝቧል፡፡
Live stream finished (52 seconds)