ከዛ ይቀጥልና መጽሀፈ ሄኖክ እንዲህ ይላል ከመላእክት ሩፋኤል ከእግዚአብሔር ተልኮ ውጊያ ያስተማራቸውን የኔፍሊሞች አለቃ አዛዝኤልን እጅና እግሩን አስሮ 👉ዱዳኤል👈በምትባል ቦታ የነበረች ምድረበዳን ከፍቶ ጨለማ ውስጥ እንዳሰረው ፣በላዩም ጠማማና ሻፎ ሚባሉ ወይም ስልስል ድንጋዮችን እንደገጠመበት፣እክከ ፍርድ ቀን ድረስ ብርሀንን እንዳያይ እንደሸፈነው ሄኖክ ጨምሮ ፅፏል።በተለይ ይህን ምታነቡ እህት ወንድሞቼ ምእራፍ 2ት እና 3ትን በደንብ እንድታነቡ እነግራችኋለሁ
ሌላው ደግሞ 70 ትውልዶች የሚጠጉትን እንደገና በምድር ኮረብታ በታች ደግሞ እንደታሰሩ ጭምር ይናገራል።ከዛ በኋላ ከእሳቱ በታች ወዳለ ጭንቅ ቦታ እንደሚወሰዱና በግዞት ቤት ይዘጋባቸዋል የሚል በጣም በጣም ምስጢራዊ የሆነ ነገርን ፅፏል፣ 🙄😯🤔🤔70ው ትውልዶች ማን ናቸው?
አዛዝኤል ዱድኤል የምትባለው ቦታስ የት ናት?ሻፎ ድንጋይ የተገጠመበት ቦታ ምንድናት??????
ይህ ሁሉ ሚስጥር ነው።
እና መፅሀፈ ሄኖክን የሚያጠኑ ሁሉ እነዚህን ሁሉ ምስጢሮች ሁሌ ያብሰለስላሉ እና የኔፍሊም ጉዳይ ይህ ብቻም አይደለም 👉👉ነቢየ እግዚአብሔር ሙሴም እንደገና ጨምሮ ይፅፋል።
እንዲህ ሆነ ይላል በተለይ ኦሪቱ ላይ "ሰዎች በምድር ላይ መብዛት በጀመሩ ጊዜ ሴቶች ልጆች ተወለዱላቸው፣የእግዚአብሔር ልጆችም የሰውን ሴቶች ልጆች መልካሞች እንደሆኑ አዩ፣ከመረጧቸውም ሚስት ለራሳቸው ወሰዱ "በማለት ይፅፋል ,,,,,,,,ዘመኖቻቸውም ደ 120 ዘመን እግዚአብሔር እንደወሰነባቸው ፣ልጆችም በወለዱ ጊዜ ስማቸው ሀያላን ተብሎ እንደተጠራ ሰፋ ያለ ፅሁፍ በተለይ ዘፍጥረት 6 አከባቢ ላይ ፅፏል፣ይሄ ሁለተኛው Source ነው የመጀመርያው ሄኖክ ሁለተኛው ዘፍጥረት ማለት ነው!
ሌላ ሦስተኛው ሶርስ ኩፋሌ ነው፣ኩፋሌም ተመሳሳይ ነገር ነው ሚፅፈው፣"የአዳም ልጆች በምድር ላይ ይበዙ ዘንድ በጀመሩ ጊዜ እንዲ ሆነ፣ሴቶች ልጆች ተወለዱላቸው 👉፣የእግዚአብሔር መላእክትም👈በዚህ ኢዮቤልዮ በአንዲቱ አመት እነዚህን አዩአቸው ።እነዚህም ላዩአቸው መልከ መልካሞች ነበሩ፣ከመረጧቸውም ሁሉ ሚስቶች እንዲሆኗቸው ወሰዷቸው ፣ወንዶች ልጆችንም ወለዱላቸው፣እነዚህም ረዐይት ናቸው "በማለት ኩፋሌ ቁጭ አድርጎ ፅፎታል ።
ስለዚህ የእግዚአብሔር መላእክት ፣የእግዚአብሔር ልጆች ወዘተርፈ ተብለው ተጠርተዋል በእነዚህ 3ት ታላላቅ መፃህፍት ፣ማለትም በ ሄኖክ ፣ዘፍጥረት ፣እና ኩፋሌ
.......ይቀጥላል
👇👇👇👇
👉👉 @Leoulu 👈👈
👉👉 @Leoulu 👈👈
👉👉 @Leoulu 👈👈
👉👉 @Leoulu 👈👈
☝️☝️☝️☝️
https://telegram.me/Leoulu
ሌላው ደግሞ 70 ትውልዶች የሚጠጉትን እንደገና በምድር ኮረብታ በታች ደግሞ እንደታሰሩ ጭምር ይናገራል።ከዛ በኋላ ከእሳቱ በታች ወዳለ ጭንቅ ቦታ እንደሚወሰዱና በግዞት ቤት ይዘጋባቸዋል የሚል በጣም በጣም ምስጢራዊ የሆነ ነገርን ፅፏል፣ 🙄😯🤔🤔70ው ትውልዶች ማን ናቸው?
አዛዝኤል ዱድኤል የምትባለው ቦታስ የት ናት?ሻፎ ድንጋይ የተገጠመበት ቦታ ምንድናት??????
ይህ ሁሉ ሚስጥር ነው።
እና መፅሀፈ ሄኖክን የሚያጠኑ ሁሉ እነዚህን ሁሉ ምስጢሮች ሁሌ ያብሰለስላሉ እና የኔፍሊም ጉዳይ ይህ ብቻም አይደለም 👉👉ነቢየ እግዚአብሔር ሙሴም እንደገና ጨምሮ ይፅፋል።
እንዲህ ሆነ ይላል በተለይ ኦሪቱ ላይ "ሰዎች በምድር ላይ መብዛት በጀመሩ ጊዜ ሴቶች ልጆች ተወለዱላቸው፣የእግዚአብሔር ልጆችም የሰውን ሴቶች ልጆች መልካሞች እንደሆኑ አዩ፣ከመረጧቸውም ሚስት ለራሳቸው ወሰዱ "በማለት ይፅፋል ,,,,,,,,ዘመኖቻቸውም ደ 120 ዘመን እግዚአብሔር እንደወሰነባቸው ፣ልጆችም በወለዱ ጊዜ ስማቸው ሀያላን ተብሎ እንደተጠራ ሰፋ ያለ ፅሁፍ በተለይ ዘፍጥረት 6 አከባቢ ላይ ፅፏል፣ይሄ ሁለተኛው Source ነው የመጀመርያው ሄኖክ ሁለተኛው ዘፍጥረት ማለት ነው!
ሌላ ሦስተኛው ሶርስ ኩፋሌ ነው፣ኩፋሌም ተመሳሳይ ነገር ነው ሚፅፈው፣"የአዳም ልጆች በምድር ላይ ይበዙ ዘንድ በጀመሩ ጊዜ እንዲ ሆነ፣ሴቶች ልጆች ተወለዱላቸው 👉፣የእግዚአብሔር መላእክትም👈በዚህ ኢዮቤልዮ በአንዲቱ አመት እነዚህን አዩአቸው ።እነዚህም ላዩአቸው መልከ መልካሞች ነበሩ፣ከመረጧቸውም ሁሉ ሚስቶች እንዲሆኗቸው ወሰዷቸው ፣ወንዶች ልጆችንም ወለዱላቸው፣እነዚህም ረዐይት ናቸው "በማለት ኩፋሌ ቁጭ አድርጎ ፅፎታል ።
ስለዚህ የእግዚአብሔር መላእክት ፣የእግዚአብሔር ልጆች ወዘተርፈ ተብለው ተጠርተዋል በእነዚህ 3ት ታላላቅ መፃህፍት ፣ማለትም በ ሄኖክ ፣ዘፍጥረት ፣እና ኩፋሌ
.......ይቀጥላል
👇👇👇👇
👉👉 @Leoulu 👈👈
👉👉 @Leoulu 👈👈
👉👉 @Leoulu 👈👈
👉👉 @Leoulu 👈👈
☝️☝️☝️☝️
https://telegram.me/Leoulu
Telegram
የሥላሴ ባርያ የልዑል ት/ት ቤት
ሥላሴ ትትረመም ወትትነከር
እንግዲህ ጠቅለል አድርገን ስናየው እይታው ለ 3 ተከፍሏል
👉1 የመጀመርያው ወይም አንደኛው እይታ ፣የወደቁ መላእክት ናቸው እንጂ በፍፁም ሰዎች አይደሉም የሚል 1 ምልከታ አለ፣the fallen angels ናቸው፣መላእክት ናቸው እንጂ ከሰው ልጆች ጋራ የተዋለዱት ሰዎች አይደሉም የሚል 1 ምልከታ አለ
👉2 ሁለተኛው ምልከታ ፣የሴት ልጆችና የ ቃየል ልጆች ናቸው እንጂ መላእክት እዚህ ውስጥ አልገቡም የሚሉ ደግሞ ሁለተኛ አመለካከት አለ
👉 3 ሦስተኛው አመለካከት ምንድነው፣ስጋ እንዲለብሱ የተደረጉ መላእክት ናቸው ነው ሚለው፣
አሁን ለ 3 ከፍለን ሰፋ አድርገን ነው የምናየው፣እንደ አጥኚ ሁሉን ነገር ማየት፣ማወቅ፣መመርመር፣መፈተሽ በተፈጥሮ የተሰጠን ስጦታ መሆኑን ማወቅ ይገባል እንጂ እንደማንም ጭፍን ጭፍንፍን ያለ ሰው ልንሆን አይገባም፣
እንዳልኳችሁ 3ት እይታ አለ፣እናነጥራለን፣እንፈትሻለን፣መልካም የሆነውን እንይዛለን ማለት ነው።
እነዚህን እይታዎች ነገ በሰፊው እንደምናይ ሙሉ እምነቱ አለኝ ፣መልካም ቆይታ ።
ሰላመ እግዚአብሔር አይለያችሁ በያላችሁበት በርቱ።
👉1 የመጀመርያው ወይም አንደኛው እይታ ፣የወደቁ መላእክት ናቸው እንጂ በፍፁም ሰዎች አይደሉም የሚል 1 ምልከታ አለ፣the fallen angels ናቸው፣መላእክት ናቸው እንጂ ከሰው ልጆች ጋራ የተዋለዱት ሰዎች አይደሉም የሚል 1 ምልከታ አለ
👉2 ሁለተኛው ምልከታ ፣የሴት ልጆችና የ ቃየል ልጆች ናቸው እንጂ መላእክት እዚህ ውስጥ አልገቡም የሚሉ ደግሞ ሁለተኛ አመለካከት አለ
👉 3 ሦስተኛው አመለካከት ምንድነው፣ስጋ እንዲለብሱ የተደረጉ መላእክት ናቸው ነው ሚለው፣
አሁን ለ 3 ከፍለን ሰፋ አድርገን ነው የምናየው፣እንደ አጥኚ ሁሉን ነገር ማየት፣ማወቅ፣መመርመር፣መፈተሽ በተፈጥሮ የተሰጠን ስጦታ መሆኑን ማወቅ ይገባል እንጂ እንደማንም ጭፍን ጭፍንፍን ያለ ሰው ልንሆን አይገባም፣
እንዳልኳችሁ 3ት እይታ አለ፣እናነጥራለን፣እንፈትሻለን፣መልካም የሆነውን እንይዛለን ማለት ነው።
እነዚህን እይታዎች ነገ በሰፊው እንደምናይ ሙሉ እምነቱ አለኝ ፣መልካም ቆይታ ።
ሰላመ እግዚአብሔር አይለያችሁ በያላችሁበት በርቱ።
ክፍል 3 # ኔፍሊም ...የቀጠለ
👉👉1 የመጀመርያው ምልከታ እንግዲህ የወደቁ መላእክት ናቸው ፣ሰዎች አይደሉም እነዚህ፣ሁለት መቶ ከሰማይ የመጡት እነዚህ መላእክት ናቸው ካሉት ከጥንቶቹ ሊቃውን መካከል Tertulian (ጠርጠሉስ) የሚባል አንድተጠቃሽ ነው ። በተለይ ከ 240ዎቹ ጀምሮ የነበረ ከ 𝖆𝖓𝖈𝖎𝖊𝖓𝖙 𝖈𝖍𝖚𝖗𝖈𝖍 𝖋𝖆𝖙𝖍𝖊𝖗𝖘 መካከል የነበረ አንዱ እሱ ይጠቀሳል።
ሌላው ግን ከ 250-325 የነበረው 𝖑𝖆𝖈𝖙𝖆𝖓𝖙𝖆𝖓𝖎𝖚𝖘(ላክታንታኒዩስ) የተባለው ተጠቃሽ ነው። እንግዲህ እነዚህ ተመራማሪዎች በፅሁፎቻቸው 𝖋𝖆𝖑𝖑𝖊𝖓 𝖆𝖓𝖌𝖊𝖑𝖘 ወይም የወደቁ መላእክት ናቸው፣ከሰው ልጆች ጋር ተዋልደው እነዚህን ያስገኙት ሚሉት፣
እንግዲህ የእነዚህ የሁለቱ ተመራማሪዎች 𝖆𝖗𝖌𝖚𝖒𝖊𝖓𝖙 ወይም ክርክራቸው ምንድነው (𝖆𝖗𝖌𝖚𝖒𝖊𝖒𝖙1)👉1👈 3000 ክንድ ቁመትን በምንም አይነት ተአምር ከሰው ሊገኝ አይችልም ነው የእነዚህ እይታ፣ሰው 3ክንድ ከስንዝር ነው፣ 3ክንድ ከ ስንዝር ምንም ያህል ሀጥያት ቢሰራ ፣ቢዋለድም እስከ 3000 ሊረዝሙ የሚችሉ ደመና ሊነኩ የሚችሉ ፍጡራንን ሊያስገኙ አይችሉም ብለው ይሟገቱና ይከራከሩ ነበር፣እንግዲህ ይህ አንዱ እይታ ነው።።።በፍፁም ሰውች ከ3ክንድ ከስንዝር ያለፈ 3000 ክንድ ማድረስ አይችሉም ስለዚህ እነዚህ 𝖋𝖆𝖑𝖑𝖊𝖓 𝖆𝖓𝖌𝖊𝖑𝖘 የወደቁ መላእክት ናቸው እንጂ ሰዎች አይደሉም ነው ሚሉት.........
🙏💜ሁሉም እንግዲህ ለእነዚህ ቅዱሳት መጻህፍትን ይጠቅሳሉ ለዚህ ምርምራቸው ።እኛ የሁሉንም ሀሳቦች ቀንጨብ አድርገን ለማየት እንሞክራለን ፣እናያለን፣እንፈትሻለንም፣
👉👉
👉እዚችጋ በማስተዋል አንብቡ 👈👈 👉👉እንግዲህ እነሱ ሚሉት ምንድነው በ 2ኛ ጴጥ 2÷4-5 ላይ ስለ ኖህ ፅፎ ,አከታትሎ ስለ እነዚህ መላእክት ፅፏል ነውሚሉት ጴጥሮስን፣
ምነድነው ሚለው "እግዚአብሔር ሀጥያትን ላደረጉ መላእክት ሳይራራላቸው ወደ ገሀነም ጥሎ በጨለማ ጉድጓድ ለፍርድ እንዲጠበቁ አሳልፎ ሰጣቸው፣ለቀደመው አለም ሳይራራ 👉?እዚጋ ከኖህ በፊት አንድ አለም ነበረ አለ ማለት ነው 👈
"ለቀደመው አለም ሳይራራ ከሌሎች ሰባት ጋር ፅድቅን የሚሰብከውን ኖህን አድኖ በሀጥያተኞች አለም ላይ የጥፋትን ውሀ ካወረደ "ብሎ ጠቅሷል ነው ሚሉት ስለዚህ በኖህ ዘመን የመጡት ፣👉ኖህን አከታትሎ ጠቅሶ ፣መላእክት አስቀድሞ መናገሩ 👈 እነዚህ ከወረዱ በኋላ ነው የጥፋት ውሀ የመጣው የሚል እሳቤ ኢሄን ይዘው አስተምረዋል ፣ሌላው እንደገና ይሁዳ 1÷6 ላይ
"መኖርያቸውን የተውትን እንጂ የራሳቸውን አለቅነት ያልጠበቁት መላእክትን በዘለአለም እስራት ከጨለማ በታች እስከ ታላቋ ፍርድ ቀን ድረስ ጠብቋቸዋል " የሚለውን ይይዙና ፣በሄኖክ ዘመን ሻፎ ድንጋዮች ተገጠመባቸው ፣ግዞት ቤት ታሰሩ የሚለውን መኖርያቸውን ትተው የመጡ መላእክት ናቸው ፣በይሁዳ የተፃፉት ብለው ይጠቅሳሉ እነ 𝖙𝖊𝖗𝖙𝖚𝖑𝖆𝖓 እነ ,,𝖑𝖆𝖈𝖙𝖆𝖓𝖙𝖆𝖓𝖎𝖚𝖘
ሌላው የሚጠቅሱት አንድ ዶክመንት አለ በተለይ የቁምራን 11 ዋሻዎች በሚከፈቱበት ጊዜና እነዛ ዶክመንቶች ሲወጡ ""D𝖆𝖒𝖆𝖘𝖈𝖚𝖘 𝖉𝖔𝖈𝖚𝖒𝖊𝖓𝖙" (የደማስቆ ሰነድ) የሚባሉት እነዚህ ሁሉ የሚያስረዱት እነዚህ ሰዎች ሳይሆኑ ቦታቸውን ለቅቀው የወረዱ 200 መላእክት ነበሩ ብለው ነው ሀሳባቸውን ያስቀመጡት,,,,,,,,,,
👉💜👉💜ይህ 1ኛው ምልከታ መሆኑን ብቻ እወቁ እንዳትረሱ 3ት ምልከታ ነው ያለው,👈💜👈💜
........ይቀጥላል....
ስብሀት ለእግዚአብሔር ኪያነ ዘፈጠረ ከመ ናምልኮ💜
ስብሀት ለማርያም እመ አምላክ እግዚእትነ ወመድሀኒትነ💜
ስብሀት ለመስቀለ ክርስቶስ እፀ መድሀኒት ሀይልነ ወፀወንነ💜
ሰላመ እግዚአብሔር አይለያችሁ
አንብቡ ተመራመሩ ጥቅስ እየጠቀሳችሁ ብቻ እንደ አዋቂ ነን ባዮች አትሁኑ ። የመፅሀፍ ቅዱስን ጥቅስ ማወቅ መጥፎ ነው ማለቴ ግን አይደለም፣፣ፍሬ ነገሩን ነው እንጂ ፣መፅሀፍ ቅዱስ ቀለል ተደርጎ ሚነበብ ስድ ንባብ ወይም ድርሰት አይደለም ፣በማስተዋል በማራቀቅ እና በመሠጠት በውስን ሰዎች ብቻ ሚፈታ በወርቆች የተሳሰረ ቅኔ ነው። ፣ህብረቃሉን ብቻ እያነበባችሁ ሆ አትበሉ ፣መጀመርያ ጠይቁ፣ለምሰሌ ስጋ ምትለዋን ቃል መፅሀፍ ቅዱስ ላይ ስታገኙ ወይም ስናገኝ ሆዳም ስለሆንን እና(ወይም) ምግብ ስለመሰለን(ስለወደድን)ሚበላ ስጋ ብለን እንተረጉማለን! እንደዛ አይደለም መፅሀፍ ቅዱስ ሚነበበው ፣በርግጥ ስጋ ማለት ሚበላ የምግብ አይነት ነው፣ሚስጥራዊ ፍቹ ግን ለነፍስህ ስጋ ፣ፍራ ማለትም ነው ፣ማስጠንቀቅያ ነው እና ወዘተርፈ፣ ፣ሊቃውንቱ በአንድምታ በምኑ ያስቀምጣሉ ፣ስለዚህ ጠይቁ ፣"መጠየቅ ያደርጋል ሊቅ"
https://telegram.me/Leoulu
👉👉1 የመጀመርያው ምልከታ እንግዲህ የወደቁ መላእክት ናቸው ፣ሰዎች አይደሉም እነዚህ፣ሁለት መቶ ከሰማይ የመጡት እነዚህ መላእክት ናቸው ካሉት ከጥንቶቹ ሊቃውን መካከል Tertulian (ጠርጠሉስ) የሚባል አንድተጠቃሽ ነው ። በተለይ ከ 240ዎቹ ጀምሮ የነበረ ከ 𝖆𝖓𝖈𝖎𝖊𝖓𝖙 𝖈𝖍𝖚𝖗𝖈𝖍 𝖋𝖆𝖙𝖍𝖊𝖗𝖘 መካከል የነበረ አንዱ እሱ ይጠቀሳል።
ሌላው ግን ከ 250-325 የነበረው 𝖑𝖆𝖈𝖙𝖆𝖓𝖙𝖆𝖓𝖎𝖚𝖘(ላክታንታኒዩስ) የተባለው ተጠቃሽ ነው። እንግዲህ እነዚህ ተመራማሪዎች በፅሁፎቻቸው 𝖋𝖆𝖑𝖑𝖊𝖓 𝖆𝖓𝖌𝖊𝖑𝖘 ወይም የወደቁ መላእክት ናቸው፣ከሰው ልጆች ጋር ተዋልደው እነዚህን ያስገኙት ሚሉት፣
እንግዲህ የእነዚህ የሁለቱ ተመራማሪዎች 𝖆𝖗𝖌𝖚𝖒𝖊𝖓𝖙 ወይም ክርክራቸው ምንድነው (𝖆𝖗𝖌𝖚𝖒𝖊𝖒𝖙1)👉1👈 3000 ክንድ ቁመትን በምንም አይነት ተአምር ከሰው ሊገኝ አይችልም ነው የእነዚህ እይታ፣ሰው 3ክንድ ከስንዝር ነው፣ 3ክንድ ከ ስንዝር ምንም ያህል ሀጥያት ቢሰራ ፣ቢዋለድም እስከ 3000 ሊረዝሙ የሚችሉ ደመና ሊነኩ የሚችሉ ፍጡራንን ሊያስገኙ አይችሉም ብለው ይሟገቱና ይከራከሩ ነበር፣እንግዲህ ይህ አንዱ እይታ ነው።።።በፍፁም ሰውች ከ3ክንድ ከስንዝር ያለፈ 3000 ክንድ ማድረስ አይችሉም ስለዚህ እነዚህ 𝖋𝖆𝖑𝖑𝖊𝖓 𝖆𝖓𝖌𝖊𝖑𝖘 የወደቁ መላእክት ናቸው እንጂ ሰዎች አይደሉም ነው ሚሉት.........
🙏💜ሁሉም እንግዲህ ለእነዚህ ቅዱሳት መጻህፍትን ይጠቅሳሉ ለዚህ ምርምራቸው ።እኛ የሁሉንም ሀሳቦች ቀንጨብ አድርገን ለማየት እንሞክራለን ፣እናያለን፣እንፈትሻለንም፣
👉👉
👉እዚችጋ በማስተዋል አንብቡ 👈👈 👉👉እንግዲህ እነሱ ሚሉት ምንድነው በ 2ኛ ጴጥ 2÷4-5 ላይ ስለ ኖህ ፅፎ ,አከታትሎ ስለ እነዚህ መላእክት ፅፏል ነውሚሉት ጴጥሮስን፣
ምነድነው ሚለው "እግዚአብሔር ሀጥያትን ላደረጉ መላእክት ሳይራራላቸው ወደ ገሀነም ጥሎ በጨለማ ጉድጓድ ለፍርድ እንዲጠበቁ አሳልፎ ሰጣቸው፣ለቀደመው አለም ሳይራራ 👉?እዚጋ ከኖህ በፊት አንድ አለም ነበረ አለ ማለት ነው 👈
"ለቀደመው አለም ሳይራራ ከሌሎች ሰባት ጋር ፅድቅን የሚሰብከውን ኖህን አድኖ በሀጥያተኞች አለም ላይ የጥፋትን ውሀ ካወረደ "ብሎ ጠቅሷል ነው ሚሉት ስለዚህ በኖህ ዘመን የመጡት ፣👉ኖህን አከታትሎ ጠቅሶ ፣መላእክት አስቀድሞ መናገሩ 👈 እነዚህ ከወረዱ በኋላ ነው የጥፋት ውሀ የመጣው የሚል እሳቤ ኢሄን ይዘው አስተምረዋል ፣ሌላው እንደገና ይሁዳ 1÷6 ላይ
"መኖርያቸውን የተውትን እንጂ የራሳቸውን አለቅነት ያልጠበቁት መላእክትን በዘለአለም እስራት ከጨለማ በታች እስከ ታላቋ ፍርድ ቀን ድረስ ጠብቋቸዋል " የሚለውን ይይዙና ፣በሄኖክ ዘመን ሻፎ ድንጋዮች ተገጠመባቸው ፣ግዞት ቤት ታሰሩ የሚለውን መኖርያቸውን ትተው የመጡ መላእክት ናቸው ፣በይሁዳ የተፃፉት ብለው ይጠቅሳሉ እነ 𝖙𝖊𝖗𝖙𝖚𝖑𝖆𝖓 እነ ,,𝖑𝖆𝖈𝖙𝖆𝖓𝖙𝖆𝖓𝖎𝖚𝖘
ሌላው የሚጠቅሱት አንድ ዶክመንት አለ በተለይ የቁምራን 11 ዋሻዎች በሚከፈቱበት ጊዜና እነዛ ዶክመንቶች ሲወጡ ""D𝖆𝖒𝖆𝖘𝖈𝖚𝖘 𝖉𝖔𝖈𝖚𝖒𝖊𝖓𝖙" (የደማስቆ ሰነድ) የሚባሉት እነዚህ ሁሉ የሚያስረዱት እነዚህ ሰዎች ሳይሆኑ ቦታቸውን ለቅቀው የወረዱ 200 መላእክት ነበሩ ብለው ነው ሀሳባቸውን ያስቀመጡት,,,,,,,,,,
👉💜👉💜ይህ 1ኛው ምልከታ መሆኑን ብቻ እወቁ እንዳትረሱ 3ት ምልከታ ነው ያለው,👈💜👈💜
........ይቀጥላል....
ስብሀት ለእግዚአብሔር ኪያነ ዘፈጠረ ከመ ናምልኮ💜
ስብሀት ለማርያም እመ አምላክ እግዚእትነ ወመድሀኒትነ💜
ስብሀት ለመስቀለ ክርስቶስ እፀ መድሀኒት ሀይልነ ወፀወንነ💜
ሰላመ እግዚአብሔር አይለያችሁ
አንብቡ ተመራመሩ ጥቅስ እየጠቀሳችሁ ብቻ እንደ አዋቂ ነን ባዮች አትሁኑ ። የመፅሀፍ ቅዱስን ጥቅስ ማወቅ መጥፎ ነው ማለቴ ግን አይደለም፣፣ፍሬ ነገሩን ነው እንጂ ፣መፅሀፍ ቅዱስ ቀለል ተደርጎ ሚነበብ ስድ ንባብ ወይም ድርሰት አይደለም ፣በማስተዋል በማራቀቅ እና በመሠጠት በውስን ሰዎች ብቻ ሚፈታ በወርቆች የተሳሰረ ቅኔ ነው። ፣ህብረቃሉን ብቻ እያነበባችሁ ሆ አትበሉ ፣መጀመርያ ጠይቁ፣ለምሰሌ ስጋ ምትለዋን ቃል መፅሀፍ ቅዱስ ላይ ስታገኙ ወይም ስናገኝ ሆዳም ስለሆንን እና(ወይም) ምግብ ስለመሰለን(ስለወደድን)ሚበላ ስጋ ብለን እንተረጉማለን! እንደዛ አይደለም መፅሀፍ ቅዱስ ሚነበበው ፣በርግጥ ስጋ ማለት ሚበላ የምግብ አይነት ነው፣ሚስጥራዊ ፍቹ ግን ለነፍስህ ስጋ ፣ፍራ ማለትም ነው ፣ማስጠንቀቅያ ነው እና ወዘተርፈ፣ ፣ሊቃውንቱ በአንድምታ በምኑ ያስቀምጣሉ ፣ስለዚህ ጠይቁ ፣"መጠየቅ ያደርጋል ሊቅ"
https://telegram.me/Leoulu
Telegram
የሥላሴ ባርያ የልዑል ት/ት ቤት
ሥላሴ ትትረመም ወትትነከር
መስጠት ወይም ልግስና ትእዛዙን ሟሟላት ብቻ አይደለም መጽሐፍ ቅዱስ "እግዚአብሔር በደስታ የሚሰጠውን ይወዳልና።" /2ቆሮ 9፥7/ እንዲል። እግዚአብሔር የምትሰጠውን ገንዘብ ሳይሆን የመጀመሪያውን ፍሬ እና ቃል ኪዳን የሆነውን ከማዕረጎች ሁሉ የሚልቀውንና ያለ ነቀፋ በነፃነት የሚሰጠውን ፍቅር ከአንተ ይጠብቃል።
ፍቅር የመንፈስ ቅዱስ የመጀመርያ ፍሬ ነው። ስለዚህ ጌታ የኤፌሶንን ቤተ ክርስቲያን በነቀፋ ንሥሓም እንዲገባ በጠራው ጊዜ ነቀፋውን የተወሰነ ኃጢአትን በመግለጽ ሳይሆን በአንድ ሐረግ አጠቃልሎ "ዳሩ ግን የምነቅፍብህ ነገር አለኝ የቀደመውን ፍቅርህን ትተሃልና።" /ራዕ 2፥4/ በማለት ነው።
እግዚአብሔር ይህንን ፍቅር ይፈልጋል ስለዚህ "ልጄ ሆይ ልብህን ስጠኝ ዓይኖችህም መንገዴን ይውደዱ።" /ምሳ 23፥26/ አለ። ትእዛዙን መፈጸም የፍቅር ተፈጥሮአዊ ፍሬ ነው።
ውጪያዊ የንሥሓ ሕይወት ብቻ የሚኖሩ ነገር ግን ውስጣዊ ፍቅር የሌላቸው ይወድቃሉ። ምክንያቱም ሥራዎቻቸውና ከእግዚአብሔር ጋር ያላቸው ግንኙነት ፍቅር የጎደለው ነውና።
መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሕግ ማንኛይቱ ትእዛዝ ታላቅ ናት? ተብሎ ለተጠየቀው ጥያቄ የሰጠው መልስ "ጌታ አምላክህን በፍጹም ልብህ በፍጹም ነፍስህም በፍጹም አሳብህም ውደድ፣ ታላቂቱና ፊተኛይቱ ትእዛዝ ይህች ናት። ሁለተኛይቱም ይህችን ትመስላለች እርሷም ባልጀራህን እንደ ነፍስህ ውደድ የምትል ናት። ኦሪትና ነቢያት በነዚህ በሁለቱም ትእዛዛት ጸኑ።" /ማቴ 22፥36-40/ የሚል ነበር።
በዚያን ቀን ብዙዎቹ "ጌታ ሆይ በስምህ ትንቢት አልተናገርንም በስምህ አጋንንት አላወጣንም?" /ማቴ 7፥22/ ይሉታል። ነገር ግን እርሱ ይህን ሁሉ ትቶ በውስጣቸው ስላለው ፍቅር ይጠይቃቸዋል።
ይህ የተአምራት እና የስጦታዎች ችግር አይደለም፣ ባሏቸው በተሰጡአቸው ስጦታዎች የተነሳ የሚጠፉ ብዙዎች ናቸውና። ለዚያ ነው ሐዋርያት ስለመንፈሳዊ ስጦታዎች ባወሩ ጊዜ ሁሉ ይህንን ከሁሉ ይልቅ በተሻለ መንገድ አብራርተውታል።
#አብነ_ሺኖዳ_ሣልሳዊ
ፍቅር የመንፈስ ቅዱስ የመጀመርያ ፍሬ ነው። ስለዚህ ጌታ የኤፌሶንን ቤተ ክርስቲያን በነቀፋ ንሥሓም እንዲገባ በጠራው ጊዜ ነቀፋውን የተወሰነ ኃጢአትን በመግለጽ ሳይሆን በአንድ ሐረግ አጠቃልሎ "ዳሩ ግን የምነቅፍብህ ነገር አለኝ የቀደመውን ፍቅርህን ትተሃልና።" /ራዕ 2፥4/ በማለት ነው።
እግዚአብሔር ይህንን ፍቅር ይፈልጋል ስለዚህ "ልጄ ሆይ ልብህን ስጠኝ ዓይኖችህም መንገዴን ይውደዱ።" /ምሳ 23፥26/ አለ። ትእዛዙን መፈጸም የፍቅር ተፈጥሮአዊ ፍሬ ነው።
ውጪያዊ የንሥሓ ሕይወት ብቻ የሚኖሩ ነገር ግን ውስጣዊ ፍቅር የሌላቸው ይወድቃሉ። ምክንያቱም ሥራዎቻቸውና ከእግዚአብሔር ጋር ያላቸው ግንኙነት ፍቅር የጎደለው ነውና።
መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሕግ ማንኛይቱ ትእዛዝ ታላቅ ናት? ተብሎ ለተጠየቀው ጥያቄ የሰጠው መልስ "ጌታ አምላክህን በፍጹም ልብህ በፍጹም ነፍስህም በፍጹም አሳብህም ውደድ፣ ታላቂቱና ፊተኛይቱ ትእዛዝ ይህች ናት። ሁለተኛይቱም ይህችን ትመስላለች እርሷም ባልጀራህን እንደ ነፍስህ ውደድ የምትል ናት። ኦሪትና ነቢያት በነዚህ በሁለቱም ትእዛዛት ጸኑ።" /ማቴ 22፥36-40/ የሚል ነበር።
በዚያን ቀን ብዙዎቹ "ጌታ ሆይ በስምህ ትንቢት አልተናገርንም በስምህ አጋንንት አላወጣንም?" /ማቴ 7፥22/ ይሉታል። ነገር ግን እርሱ ይህን ሁሉ ትቶ በውስጣቸው ስላለው ፍቅር ይጠይቃቸዋል።
ይህ የተአምራት እና የስጦታዎች ችግር አይደለም፣ ባሏቸው በተሰጡአቸው ስጦታዎች የተነሳ የሚጠፉ ብዙዎች ናቸውና። ለዚያ ነው ሐዋርያት ስለመንፈሳዊ ስጦታዎች ባወሩ ጊዜ ሁሉ ይህንን ከሁሉ ይልቅ በተሻለ መንገድ አብራርተውታል።
#አብነ_ሺኖዳ_ሣልሳዊ
ከምን ዓይነት ነገር መላቀቅ እንዳለብህ ታዉቃለህ ??
ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ሺኖዳ ሳልሳዊ ምድራዊ ምኞት ምን ያህል አስከፊ እንደሆነና እንዴት ከዚህ ነገር ነፃ መውጣት እንዳለብን እንዲህ በማለት ይመክሩናል፦
"ወዳጄ ከምድራዊ ምኞትህ ተላቀቅ ከምን አይነት ነገር መራቅ እንዳለብህ ታውቃለህ? ከምድራዊ ፍላጎት ከመሳሰሉት ራቅ ፍፁም የመንፈስ ነፃነት እንዲኖርህ ከፈለክ ከምድራዊ ምኞቶችህ ተላቀቅ።
በእርጋታና በግልጽነት ላውጋህ እጅግ አብዝተህ የምትጨነቅባቸው ልብህን የተቆጣጠሩት ታላላቅ ምድራዊ ተስፋዎች አሉህ።
እነኚህም ሃሳብህን ሁሉ ይቆጣጠሩታል ብቻህን በምቶንበት ጊዜ በምናብ ይመጡብሃል በምትተኛ ጊዜ ህልምህ ሁሉ ይህ ይሆናል ልትክዳቸው የማትችለው ነገር ግን የምታውቃቸው ምድራዊ አላማዎች አሉህ። ተፈላጊነት እንዲኖርህ ትመኛለህ፣ ስልጣን እንዲኖርህና፣ ኃያል እንድትሆን፣ ዕውቅና እንዲኖርህና ስምህ ከጽንፍ እስከ አጽናፍ እንዲናኝ ትፈልጋለህ።
በሀብት፣ በምድራዊ ስልጣን፣ በዕውቀት በማዕረግና በመልክ ዝነኛ የመሆን ተስፋ አለህ ፣ በመኖሪያ ቤት፣ በምግብ፣ በልብስና በሰውነት ደስታን በሚሰጡ ነገሮችም ተስፋ አለህ።
ዓለም በአንተ እንጂ አንተ በዓለም እየኖርክ አይደለም። ስለዚህ አንተነትህ በዚህ ምድራዊ ተስፋ የታጠረ ነው። መንፈስህም ከስጋ ፍላጎቶች መራቅን ትመኛለች ሥጋ በመንፈስ ላይ መንፈስ በሥጋ ላይ ይመኛልና። (ገላ.5፥17) እነዚህ ሥጋዊ ተስፋዎችና ፍላጎቶች ስኬታማ ስለማይሆኑ ግራ ትጋባለህ።
ይህን በእርግጥ ቅሬታን ያመጣብሃል።
እነዚህን ነገሮች ሁሉ ትናፍቃለህ ነገር ግን ናፍቆትህ አያስደስትህም። ስለዚህ ለምኞትህ ሁሉ ማስተካከያ ታበጅለት ይሆናል ምናልባትም ይጠቅሙኛል የምትላቸውን ሰዎች ማግኘት፣ በምኞትህ ዙሪያ የተጻፈ መዛግብት ማገላበጥ ትፈልግ ይሆናል በዚህም ላይ ታች ስትል ምኞትህን ለማሳካት ትታገላለህ እንዲሆን ሌላ ዘዴ ልትፈጥር ትችላለህ ይሁን እንጂ ሳይሳካልህ ቀርቶ በሃሳብና በጥረት ትታክታለህ ከዚያም ትበሳጫለህ። ከዚህ የከፋው ነገር በእነዚህ ምኞቶችና ተስፋዎች ስኬታማ አለመሆን ምክንያት ለከፋ ሕይወት መዳረግህ ነው።
እንደምትሰለች አውቃለሁ አዘንኩልህ እስከመቼ ድርስ በምኞት ማዕበል ውስጥ ትኖራለህ? የምትመኘውን ባገኘህ ጊዜ ደስተኛ ትሆናለህ ይህ ደስታ ስለማያረካህ ሌላ አዲስ ደስታን እንድትመኝ ያደርግሃል። ልክ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ "ከዚህ ውሃ የሚጠጣ ሁሉ እንደገና ይጠማል" (ዮሐ.4፥13 ) እንዳለው እርካታ አይኖርህም።
ስለዚህ ውድ ወንድሜ ነገሩን በእርጋታ ከአንተ ጋር ለመነጋገር እፈልጋለሁ። "አለሙም ምኞቱም ያልፋል" (1ኛ ዮሐ.2፥17) ታዲያ ይህን ቃል ካወክ ለምን አለማዊ ፍላጎቶችን ለማግኘት ትታክታለህ? አንተ ልክ እንደ እኔ ለመሬት እንግዳ ነህ። ዓለም የሚያልፍበት አንተም የምትጠፋበት ጊዜ ይመጣል ልክ ከእናትህ ማህጸን ራቁትህን እንደመጣህ እንደዚሁ ራቁትህን ትመለሳለህ።(ኢዮ. 1፥21)
ዓለምን ከነክብሯ ከነሀብቷና ከነስሟ ለቀሃት እንድትሄድ በመገደድ እንደ ማንኛውም ሰው ወደ መሬት ትወርዳለህ። ከዚያም ከዓለም ያገኘኽውን ደስታ ታወቂነት ወይም ምንም ይሁን ምን ሥጋህን ከሞት ሊከላከልልህ አልያም ሥጋን ከሚበሉት ትል ሊከላከልልህ አይችልም። በፍርድ ቀን ከዓለም ሀብትና ንብረት ውጭ በእግዚአብሔር ፊት ትቆማለህ። መልካም ይሁን ክፉ የሰራኸው ሥራ እንጂ የዓለም ቁሳዊ ነገር አይከተልህም።
ስለዚህ ውድ ወንድሜ ምኞትህንና ተስፋህን በዓለም ላይ በማድረግ መታወክህ ለአንተ ጥሩ አይደለም ይህችን ምድር እሾህንና አሜኬላን እንዳበቀለችልህ ትዘነጋለህን!!! ከእኛ በፊት የነበሩና ምድርን ሊረግጧት የማይገባት የቅዳሳን አባቶችና እናቶች አሠራርና ፈለግ ተከተል ቅድስናቸውን ያገኙት ይህችን ዓለም በመውደድ ሳይሆን በመናቅ ነበር ሁኔታዎች ሁሉ ተመቻችተውላቸው ሳለ በዓለም ስላሉ ነገሮች ለማንኛውም ጉጉት አልነበራቸውም ።
ውድ ወንድሜ አሁንም ምኞት አሉህ መዝገብህ ባለበት ልብህ ደግሞ በዚያ ይሆናልና (ማቴ.6፥21) የሥጋን ምኞቶችን ስለተቆራኘ መንፈሳዊ ነገሮች በአንተ አመለካከት ዋጋቸውን ያጣሉ ይህ የክብር ጌታ እንደተፈተነው ዓይነት ፈተና ነው። (ማቴ.4፥8-9)
አሁን አስተውል እነዚህን ነገሮችን ብትይዝ በጥሩ ምኞት ያላሰርካት ነፍስህን ብታጣ ጥቅሙ ምንድን ነው? ነፍስህ ነጻነትን ትሻለች።
ከስጋ ምኞት ተላቀን የመንፈስ ፍሬ የሆኑትን " የመንፈስ ፍሬ ግን ፍቅር፣ ደስታ፣ ሰላም፣ ትዕግሥት፣ ቸርነት፣ በጎነት፣ እምነት፣ የውሃት፣ ራስን መግዛት ነው።"(ገላ.5፥22) እንዳለው ብርሃነ ዓለም ቅዱስ ጳውሎስ እነዚህን ገንዘብ አድርገን እንድንኖር እግዚአብሔር አምላክ ይርዳን!!
(የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ሺኖዳ ሳልሳዊ "የመንፈስ ነጻነት "ከሚለውና በዲ/ን ደስታ ፍፁም ከተተረጎመው መጽሐፍ ላይ የተወሰደ)
ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ሺኖዳ ሳልሳዊ ምድራዊ ምኞት ምን ያህል አስከፊ እንደሆነና እንዴት ከዚህ ነገር ነፃ መውጣት እንዳለብን እንዲህ በማለት ይመክሩናል፦
"ወዳጄ ከምድራዊ ምኞትህ ተላቀቅ ከምን አይነት ነገር መራቅ እንዳለብህ ታውቃለህ? ከምድራዊ ፍላጎት ከመሳሰሉት ራቅ ፍፁም የመንፈስ ነፃነት እንዲኖርህ ከፈለክ ከምድራዊ ምኞቶችህ ተላቀቅ።
በእርጋታና በግልጽነት ላውጋህ እጅግ አብዝተህ የምትጨነቅባቸው ልብህን የተቆጣጠሩት ታላላቅ ምድራዊ ተስፋዎች አሉህ።
እነኚህም ሃሳብህን ሁሉ ይቆጣጠሩታል ብቻህን በምቶንበት ጊዜ በምናብ ይመጡብሃል በምትተኛ ጊዜ ህልምህ ሁሉ ይህ ይሆናል ልትክዳቸው የማትችለው ነገር ግን የምታውቃቸው ምድራዊ አላማዎች አሉህ። ተፈላጊነት እንዲኖርህ ትመኛለህ፣ ስልጣን እንዲኖርህና፣ ኃያል እንድትሆን፣ ዕውቅና እንዲኖርህና ስምህ ከጽንፍ እስከ አጽናፍ እንዲናኝ ትፈልጋለህ።
በሀብት፣ በምድራዊ ስልጣን፣ በዕውቀት በማዕረግና በመልክ ዝነኛ የመሆን ተስፋ አለህ ፣ በመኖሪያ ቤት፣ በምግብ፣ በልብስና በሰውነት ደስታን በሚሰጡ ነገሮችም ተስፋ አለህ።
ዓለም በአንተ እንጂ አንተ በዓለም እየኖርክ አይደለም። ስለዚህ አንተነትህ በዚህ ምድራዊ ተስፋ የታጠረ ነው። መንፈስህም ከስጋ ፍላጎቶች መራቅን ትመኛለች ሥጋ በመንፈስ ላይ መንፈስ በሥጋ ላይ ይመኛልና። (ገላ.5፥17) እነዚህ ሥጋዊ ተስፋዎችና ፍላጎቶች ስኬታማ ስለማይሆኑ ግራ ትጋባለህ።
ይህን በእርግጥ ቅሬታን ያመጣብሃል።
እነዚህን ነገሮች ሁሉ ትናፍቃለህ ነገር ግን ናፍቆትህ አያስደስትህም። ስለዚህ ለምኞትህ ሁሉ ማስተካከያ ታበጅለት ይሆናል ምናልባትም ይጠቅሙኛል የምትላቸውን ሰዎች ማግኘት፣ በምኞትህ ዙሪያ የተጻፈ መዛግብት ማገላበጥ ትፈልግ ይሆናል በዚህም ላይ ታች ስትል ምኞትህን ለማሳካት ትታገላለህ እንዲሆን ሌላ ዘዴ ልትፈጥር ትችላለህ ይሁን እንጂ ሳይሳካልህ ቀርቶ በሃሳብና በጥረት ትታክታለህ ከዚያም ትበሳጫለህ። ከዚህ የከፋው ነገር በእነዚህ ምኞቶችና ተስፋዎች ስኬታማ አለመሆን ምክንያት ለከፋ ሕይወት መዳረግህ ነው።
እንደምትሰለች አውቃለሁ አዘንኩልህ እስከመቼ ድርስ በምኞት ማዕበል ውስጥ ትኖራለህ? የምትመኘውን ባገኘህ ጊዜ ደስተኛ ትሆናለህ ይህ ደስታ ስለማያረካህ ሌላ አዲስ ደስታን እንድትመኝ ያደርግሃል። ልክ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ "ከዚህ ውሃ የሚጠጣ ሁሉ እንደገና ይጠማል" (ዮሐ.4፥13 ) እንዳለው እርካታ አይኖርህም።
ስለዚህ ውድ ወንድሜ ነገሩን በእርጋታ ከአንተ ጋር ለመነጋገር እፈልጋለሁ። "አለሙም ምኞቱም ያልፋል" (1ኛ ዮሐ.2፥17) ታዲያ ይህን ቃል ካወክ ለምን አለማዊ ፍላጎቶችን ለማግኘት ትታክታለህ? አንተ ልክ እንደ እኔ ለመሬት እንግዳ ነህ። ዓለም የሚያልፍበት አንተም የምትጠፋበት ጊዜ ይመጣል ልክ ከእናትህ ማህጸን ራቁትህን እንደመጣህ እንደዚሁ ራቁትህን ትመለሳለህ።(ኢዮ. 1፥21)
ዓለምን ከነክብሯ ከነሀብቷና ከነስሟ ለቀሃት እንድትሄድ በመገደድ እንደ ማንኛውም ሰው ወደ መሬት ትወርዳለህ። ከዚያም ከዓለም ያገኘኽውን ደስታ ታወቂነት ወይም ምንም ይሁን ምን ሥጋህን ከሞት ሊከላከልልህ አልያም ሥጋን ከሚበሉት ትል ሊከላከልልህ አይችልም። በፍርድ ቀን ከዓለም ሀብትና ንብረት ውጭ በእግዚአብሔር ፊት ትቆማለህ። መልካም ይሁን ክፉ የሰራኸው ሥራ እንጂ የዓለም ቁሳዊ ነገር አይከተልህም።
ስለዚህ ውድ ወንድሜ ምኞትህንና ተስፋህን በዓለም ላይ በማድረግ መታወክህ ለአንተ ጥሩ አይደለም ይህችን ምድር እሾህንና አሜኬላን እንዳበቀለችልህ ትዘነጋለህን!!! ከእኛ በፊት የነበሩና ምድርን ሊረግጧት የማይገባት የቅዳሳን አባቶችና እናቶች አሠራርና ፈለግ ተከተል ቅድስናቸውን ያገኙት ይህችን ዓለም በመውደድ ሳይሆን በመናቅ ነበር ሁኔታዎች ሁሉ ተመቻችተውላቸው ሳለ በዓለም ስላሉ ነገሮች ለማንኛውም ጉጉት አልነበራቸውም ።
ውድ ወንድሜ አሁንም ምኞት አሉህ መዝገብህ ባለበት ልብህ ደግሞ በዚያ ይሆናልና (ማቴ.6፥21) የሥጋን ምኞቶችን ስለተቆራኘ መንፈሳዊ ነገሮች በአንተ አመለካከት ዋጋቸውን ያጣሉ ይህ የክብር ጌታ እንደተፈተነው ዓይነት ፈተና ነው። (ማቴ.4፥8-9)
አሁን አስተውል እነዚህን ነገሮችን ብትይዝ በጥሩ ምኞት ያላሰርካት ነፍስህን ብታጣ ጥቅሙ ምንድን ነው? ነፍስህ ነጻነትን ትሻለች።
ከስጋ ምኞት ተላቀን የመንፈስ ፍሬ የሆኑትን " የመንፈስ ፍሬ ግን ፍቅር፣ ደስታ፣ ሰላም፣ ትዕግሥት፣ ቸርነት፣ በጎነት፣ እምነት፣ የውሃት፣ ራስን መግዛት ነው።"(ገላ.5፥22) እንዳለው ብርሃነ ዓለም ቅዱስ ጳውሎስ እነዚህን ገንዘብ አድርገን እንድንኖር እግዚአብሔር አምላክ ይርዳን!!
(የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ሺኖዳ ሳልሳዊ "የመንፈስ ነጻነት "ከሚለውና በዲ/ን ደስታ ፍፁም ከተተረጎመው መጽሐፍ ላይ የተወሰደ)
ወርኃ ጽጌ - 🌼🌼
(ከመስከረም 26 እስከ ኅዳር 6)
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ስርአት መሰረት ከመስከረም 26 ቀን እስከ ሕዳር 6 ቀን ያለው 40 ቀን የእመቤታችን ና የልጇን ስደት በማሰብ ወርኃ ጽጌን (ዘመነ ጽጌን) ታከብራለች፡፡ ይህ 40 ቀን የእመቤታችንና የጌታ ስደት የሚታሰብበት ዘመን ነው፡፡ ወቅቱ የአበባና የፍሬ ወቅት በመሆኑ እመቤታችን በአበባ ጌታን በፍሬ እየተመሰሉ ጌታችን በአምልኮት እመቤታችን በፈጣሪ እናትነቷ በተለየ ምስጋና ይመሰገናሉ ፡፡
በዚህ በወርኃ ጽጌ (በዘመነ ጽጌ) የሚጾሙ ክርስቲያኖች ሲኖሩ ጾሙን መንፈሳውያን ሰዎች ሳይታዘዙ በራሳቸው ፈቃድ የሚጾሙት ጾም በመሆኑ (የፈቃድ) የትሩፋት ጾም ይባላል፡፡ በቀኖና ቤተክርስቲያን ከታዘዙት ከ7ቱ አጽዋማት ውጪ የሆነ ትርፍ ጾም ማለት ነው፡፡ ከታዘዘው አትርፎ የጾመ ሰው የመጾሙን ዋጋ ያገኛል፡፡ ብዙ መንፈሳዊ ሥራ የሰራ ሰው ብዙ ክብር እንደሚያገኝ መጽሐፍ ይናገራልና፡፡ ‘’እጅግ ወዳለችና ብዙ ያለው ሐጢአትዋ ተሰርዮላታል፡፡ ጥቂት ግን የሚሰረይለት ጥቂት ይወዳል’’ (ሉቃ. 7፡47) እንዲል፡፡
የጽጌን ጾም የሚጾሙ ሰዎች በክብርም ከእመቤታችን ጋር ይተባበራሉ፡፡ ነገር ግን የጽጌን ጾም የሚጾሙ ሰዎች ለመመጻደቅ መጾም የለባቸውም፡፡ የማይጾሙ ሰዎችንም መንቀፍና መክሰስ የለባቸውም፡፡ የጽጌ ጾም እንዲጾም በቀኖና ቤተክርስቲያን ከሰባቱ አጽዋማት አንዱ ተደርጎ ስላልተወሰነ የማይጾሙ ሰዎች ሕገ ጾምን እንዳፈረሱ አድርጎ መውሰድ ስሕተት ነው፡፡ ይልቁንም የሚጾሙ ሰዎች ቢችሉ መጾማቸው እንዳይታወቅባቸው ቢያደርጉ የተሻለ ነው፡፡ "ስትጾሙ እንደግብዞች አትጠውልጉ" (ማቴ. 6፥16) የተባለው ለዚህ ዓይነቱ ጾም ነው፡፡
@Leoulu @Leoulu @Leoulu
@Leoulu @Leoulu @Leoulu
(ከመስከረም 26 እስከ ኅዳር 6)
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ስርአት መሰረት ከመስከረም 26 ቀን እስከ ሕዳር 6 ቀን ያለው 40 ቀን የእመቤታችን ና የልጇን ስደት በማሰብ ወርኃ ጽጌን (ዘመነ ጽጌን) ታከብራለች፡፡ ይህ 40 ቀን የእመቤታችንና የጌታ ስደት የሚታሰብበት ዘመን ነው፡፡ ወቅቱ የአበባና የፍሬ ወቅት በመሆኑ እመቤታችን በአበባ ጌታን በፍሬ እየተመሰሉ ጌታችን በአምልኮት እመቤታችን በፈጣሪ እናትነቷ በተለየ ምስጋና ይመሰገናሉ ፡፡
በዚህ በወርኃ ጽጌ (በዘመነ ጽጌ) የሚጾሙ ክርስቲያኖች ሲኖሩ ጾሙን መንፈሳውያን ሰዎች ሳይታዘዙ በራሳቸው ፈቃድ የሚጾሙት ጾም በመሆኑ (የፈቃድ) የትሩፋት ጾም ይባላል፡፡ በቀኖና ቤተክርስቲያን ከታዘዙት ከ7ቱ አጽዋማት ውጪ የሆነ ትርፍ ጾም ማለት ነው፡፡ ከታዘዘው አትርፎ የጾመ ሰው የመጾሙን ዋጋ ያገኛል፡፡ ብዙ መንፈሳዊ ሥራ የሰራ ሰው ብዙ ክብር እንደሚያገኝ መጽሐፍ ይናገራልና፡፡ ‘’እጅግ ወዳለችና ብዙ ያለው ሐጢአትዋ ተሰርዮላታል፡፡ ጥቂት ግን የሚሰረይለት ጥቂት ይወዳል’’ (ሉቃ. 7፡47) እንዲል፡፡
የጽጌን ጾም የሚጾሙ ሰዎች በክብርም ከእመቤታችን ጋር ይተባበራሉ፡፡ ነገር ግን የጽጌን ጾም የሚጾሙ ሰዎች ለመመጻደቅ መጾም የለባቸውም፡፡ የማይጾሙ ሰዎችንም መንቀፍና መክሰስ የለባቸውም፡፡ የጽጌ ጾም እንዲጾም በቀኖና ቤተክርስቲያን ከሰባቱ አጽዋማት አንዱ ተደርጎ ስላልተወሰነ የማይጾሙ ሰዎች ሕገ ጾምን እንዳፈረሱ አድርጎ መውሰድ ስሕተት ነው፡፡ ይልቁንም የሚጾሙ ሰዎች ቢችሉ መጾማቸው እንዳይታወቅባቸው ቢያደርጉ የተሻለ ነው፡፡ "ስትጾሙ እንደግብዞች አትጠውልጉ" (ማቴ. 6፥16) የተባለው ለዚህ ዓይነቱ ጾም ነው፡፡
@Leoulu @Leoulu @Leoulu
@Leoulu @Leoulu @Leoulu
💜❤"ይቅርታ"💜❤💚
💚 በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ❤
ከሠራተኞችህ አንዱ ከአንተ መቶ ቅንጣት ወርቆችን ተበደረ እንበል፡፡ ሌላ ሰው ደግሞ ከዚህ ሠራተኛህ የተበደረው ጥቂት ብር ነበረው፡፡ ከዚህ ሠራተኛህ የተበደረው ያ ሰውም ወደ አንተ መጥቶ ቸርነትን እንድታደርግለት ለመነህ፡፡ አንተም ሠራተኛህን ጠርተህ፡- “የዚህን ሰው ዕዳ ተውለት፤ ከእኔ ከተበደርከው ዕዳህም እቀንስልሃለሁ” ብትለውና ይህ ሠራተኛህ ከዚያ በኋላ በዚያ ሰው ላይ ቢጨክንና ቢከፋ ይህን ሠራተኛ ከእጅህ ሊያድነው የሚችል ሰው አለን? እጅግ እንደ ነቀፈህ አድርገህ ቆጥረህ ብዙ ግርፋትን አትገርፈውምን? [እንዲህ ብታደርግ] እጅግ ፍትሐዊ ነው፡፡ እግዚአብሔርም የሚያደርገው እንደዚህ ነው፤ በዚያች ዕለተ ምጽአት ላይ እንዲህ ይልሃልና፡- “አንተ ክፉና ተንኰለኛ ባሪያ ያንን ሰው ይቅር ብትለው ይቅርታው የአንተ ነበርን? ለእርሱ እንድታደርግለት የታዘዝከው ከእኔ የተበደርከውን ነበር፡፡ ያልኩህ ‘ዕዳዉን ብትተውለት እኔም እተውልሃለሁ’ ነው፡፡ በእውነት እንዲህ ይህን ኹኔታ ጨምሬ ባልነግርህም እንኳን ስለ እግዚአብሔር ብለህ ዕዳዉን ትተውለት ዘንድ በተገባህ ነበር፡፡ ነገር ግን እንደ ወዳጅ ኾኜ ውለታን ጠየቅሁህ እንጂ እንደ ጌታ አላዘዝኩህም፡፡ የጠየቅሁህ የእኔ ከኾነው ነው፤ ይህን ካደረግህም እጅግ በረከተ ሥጋን በረከተ ነፍስን እንደምሰጥህ ቃል ገብቼልህ ነበር፡፡ ነገር ግን ምንም ልትሻሻል አልቻልክም፡፡”
ከዚህም በላይ ሰዎች እንደዚህ ሲያደርጉ የሚቀንሱት የዕዳ መጠን ሠራተኞቻቸው ላበደሩአቸው ሌሎች ሰዎች የቀነሱትን ያህል ነው፡፡ ለምሳሌ እንበልና አንድ ሠራተኛ ከአሠሪው መቶ ቅንጣት ወርቅን ይበደራል፡፡ ሌላው ሰው ደግሞ ከዚህ ሠራተኛ ዐሥር ቅንጣት ይበደራል፡፡ ሠራተኛው ዐሥር ቅንጣት ላበደረው ብድሩን ቢተዉለት አሠሪው ግን መቶ ቅንጣቱን አይተውለትም፤ የሚተውለት ዐሥር ቅንጣቱን ብቻ ነው፤ ሌላዉን እንዲመልስለት ይፈልጋል፡፡ በእግዚአብሔር ዘንድ ግን እንደዚህ አይደለም፡፡ አንተ ለባልንጀራህ ጥቂቱን ስትተውለት እግዚአብሔር ደግሞ ዕዳህን ኹሉ ይተውልሃል፡፡ ይህስ [መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ] የት ይገኛል? [ጌታችን] ስለ ጸሎት ባስተማረው ትምህርት ውስጥ አለ፡፡ “ለሰዎች ኃጢአታቸውን ይቅር ብትሉ የሰማዩ አባታችሁ እናንተን ደግሞ ይቅር ይላችኋልና” እንዲል (ማቴ.6፡14)፡፡ በ“መቶ ዲናር” እና በ“እልፍ መክሊት” መካከል ያለው ልዩነት ያህል ለሰው ይቅር የምንለው ዕዳና ከእግዚአብሔር ይቅር የሚባልልን ዕዳም አይነጻጸርም (ማቴ.18፡24፣28)!
እንግዲህ መቶ ዲናርን ዕዳ ይቅር ብሎ እልፍ መክሊትን የሚቀበል ኾኖ ሳለ ይህቺን ጥቂት ዕዳስ እንኳን ይቅር ሳይል ጸሎቱን በራሱ ላይ የሚያደርስ ይህ ሰው የማይገባው ቅጣት እንደ ምን ያለ ቅጣት ነው? ምክንያቱም “እኛ የበደሉንን ይቅር እንደምንል በደላችንን ይቅር በለን” ብለህ እየጸለይክ ሳለ አንተ ግን ከዚያ በኋላ ይቅር የማትል ከኾነ እግዚአብሔር ምሕረቱን ወይም ቸርነቱን ኹሉ እንዲያርቅብህ ካልኾነ በቀር ሌላ ምንም እየለመንከው አይደለም፡፡ “እኔ ይቅር በለኝ ብቻ ነው እንጂ የበደሉኝን ይቅር እንደምል በደሌን ይቅር በለኝ ብዬ አልጸልይም” የሚል ሰው ደግሞ አለ፡፡ ታዲያ ይኼ ምንድን ነው? አንተ እንዲህ ብለህ ባትጸልይም እግዚአብሔር ግን እንዲህ አያደርግም፤ ይቅር የሚልህ አንተ ይቅር ስትል ነው፡፡ ይህም ከዚያ በኋላ እንዲህ ብሎ ግልጽ አድርጎታል፡- “ለሰዎች ኃጢአታቸውን ይቅር ባትሉ የሰማዩ አባታችሁም ኃጢአታችሁን ይቅር አይላችሁም” (ማቴ.6፡15)፡፡ ስለዚህ ጸሎቱን ሙሉ ባትደግመው ወይም ዕለት ዕለት እንደዚያ ብለህ ስትጸልይ ፈርተህ ከባልንጀራህ ጋር እንድትታረቅ ብሎ እንድትጸልው ባዘዘህ መንገድ ሳይኾን ቈርጠህ ብትደግመው እንኳን ደገኛ መንገድ ነው ብለህ አታስብ፡፡
“ብዙ ጊዜ ለምኜዋለሁ፤ ተማጽኜዋለሁ፤ ማልጄዋለሁ፤ ሊታረቀኝ ግን አልቻለም” ብለህ አትንገረኝ፡፡ እስክትታረቀው ድረስ በፍጹም አታቁም፡፡ ጌታችን ሲናገር፡- “መባህን ትተህ ኺድ፤ ወንድምህንም ለምነው” አይደለምና፡፡ ያለው፡- “ኺድ፤ ታረቅ” ነው (ማቴ.5፡24)፡፡ ስለዚህ ምንም እንኳን ብዙ ጊዜ ለምነኸው ቢኾንም እስክታሳምነው ድረስ ግን ይህን ማድረግህን አታቋርጥ፡፡ እግዚአብሔር ዕለት ዕለት ይለምነናል፤ እኛ ግን አንሰማውም፡፡ ኾኖም [አልሰሙኝም ብሎ] መለመኑን አላቋረጠም፡፡ ታዲያ አንተ ባልንጀራህን ለመለመን ትታጀራለህን? እንዲህ የምታደርግ ከኾነስ ልትድን የምትችለው እንዴት ነው?
የይቅርታ ልብ ይስጠን
https://telegram.me/Leoulu
https://telegram.me/Leoulu
https://telegram.me/Leoulu
💚 በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ❤
ከሠራተኞችህ አንዱ ከአንተ መቶ ቅንጣት ወርቆችን ተበደረ እንበል፡፡ ሌላ ሰው ደግሞ ከዚህ ሠራተኛህ የተበደረው ጥቂት ብር ነበረው፡፡ ከዚህ ሠራተኛህ የተበደረው ያ ሰውም ወደ አንተ መጥቶ ቸርነትን እንድታደርግለት ለመነህ፡፡ አንተም ሠራተኛህን ጠርተህ፡- “የዚህን ሰው ዕዳ ተውለት፤ ከእኔ ከተበደርከው ዕዳህም እቀንስልሃለሁ” ብትለውና ይህ ሠራተኛህ ከዚያ በኋላ በዚያ ሰው ላይ ቢጨክንና ቢከፋ ይህን ሠራተኛ ከእጅህ ሊያድነው የሚችል ሰው አለን? እጅግ እንደ ነቀፈህ አድርገህ ቆጥረህ ብዙ ግርፋትን አትገርፈውምን? [እንዲህ ብታደርግ] እጅግ ፍትሐዊ ነው፡፡ እግዚአብሔርም የሚያደርገው እንደዚህ ነው፤ በዚያች ዕለተ ምጽአት ላይ እንዲህ ይልሃልና፡- “አንተ ክፉና ተንኰለኛ ባሪያ ያንን ሰው ይቅር ብትለው ይቅርታው የአንተ ነበርን? ለእርሱ እንድታደርግለት የታዘዝከው ከእኔ የተበደርከውን ነበር፡፡ ያልኩህ ‘ዕዳዉን ብትተውለት እኔም እተውልሃለሁ’ ነው፡፡ በእውነት እንዲህ ይህን ኹኔታ ጨምሬ ባልነግርህም እንኳን ስለ እግዚአብሔር ብለህ ዕዳዉን ትተውለት ዘንድ በተገባህ ነበር፡፡ ነገር ግን እንደ ወዳጅ ኾኜ ውለታን ጠየቅሁህ እንጂ እንደ ጌታ አላዘዝኩህም፡፡ የጠየቅሁህ የእኔ ከኾነው ነው፤ ይህን ካደረግህም እጅግ በረከተ ሥጋን በረከተ ነፍስን እንደምሰጥህ ቃል ገብቼልህ ነበር፡፡ ነገር ግን ምንም ልትሻሻል አልቻልክም፡፡”
ከዚህም በላይ ሰዎች እንደዚህ ሲያደርጉ የሚቀንሱት የዕዳ መጠን ሠራተኞቻቸው ላበደሩአቸው ሌሎች ሰዎች የቀነሱትን ያህል ነው፡፡ ለምሳሌ እንበልና አንድ ሠራተኛ ከአሠሪው መቶ ቅንጣት ወርቅን ይበደራል፡፡ ሌላው ሰው ደግሞ ከዚህ ሠራተኛ ዐሥር ቅንጣት ይበደራል፡፡ ሠራተኛው ዐሥር ቅንጣት ላበደረው ብድሩን ቢተዉለት አሠሪው ግን መቶ ቅንጣቱን አይተውለትም፤ የሚተውለት ዐሥር ቅንጣቱን ብቻ ነው፤ ሌላዉን እንዲመልስለት ይፈልጋል፡፡ በእግዚአብሔር ዘንድ ግን እንደዚህ አይደለም፡፡ አንተ ለባልንጀራህ ጥቂቱን ስትተውለት እግዚአብሔር ደግሞ ዕዳህን ኹሉ ይተውልሃል፡፡ ይህስ [መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ] የት ይገኛል? [ጌታችን] ስለ ጸሎት ባስተማረው ትምህርት ውስጥ አለ፡፡ “ለሰዎች ኃጢአታቸውን ይቅር ብትሉ የሰማዩ አባታችሁ እናንተን ደግሞ ይቅር ይላችኋልና” እንዲል (ማቴ.6፡14)፡፡ በ“መቶ ዲናር” እና በ“እልፍ መክሊት” መካከል ያለው ልዩነት ያህል ለሰው ይቅር የምንለው ዕዳና ከእግዚአብሔር ይቅር የሚባልልን ዕዳም አይነጻጸርም (ማቴ.18፡24፣28)!
እንግዲህ መቶ ዲናርን ዕዳ ይቅር ብሎ እልፍ መክሊትን የሚቀበል ኾኖ ሳለ ይህቺን ጥቂት ዕዳስ እንኳን ይቅር ሳይል ጸሎቱን በራሱ ላይ የሚያደርስ ይህ ሰው የማይገባው ቅጣት እንደ ምን ያለ ቅጣት ነው? ምክንያቱም “እኛ የበደሉንን ይቅር እንደምንል በደላችንን ይቅር በለን” ብለህ እየጸለይክ ሳለ አንተ ግን ከዚያ በኋላ ይቅር የማትል ከኾነ እግዚአብሔር ምሕረቱን ወይም ቸርነቱን ኹሉ እንዲያርቅብህ ካልኾነ በቀር ሌላ ምንም እየለመንከው አይደለም፡፡ “እኔ ይቅር በለኝ ብቻ ነው እንጂ የበደሉኝን ይቅር እንደምል በደሌን ይቅር በለኝ ብዬ አልጸልይም” የሚል ሰው ደግሞ አለ፡፡ ታዲያ ይኼ ምንድን ነው? አንተ እንዲህ ብለህ ባትጸልይም እግዚአብሔር ግን እንዲህ አያደርግም፤ ይቅር የሚልህ አንተ ይቅር ስትል ነው፡፡ ይህም ከዚያ በኋላ እንዲህ ብሎ ግልጽ አድርጎታል፡- “ለሰዎች ኃጢአታቸውን ይቅር ባትሉ የሰማዩ አባታችሁም ኃጢአታችሁን ይቅር አይላችሁም” (ማቴ.6፡15)፡፡ ስለዚህ ጸሎቱን ሙሉ ባትደግመው ወይም ዕለት ዕለት እንደዚያ ብለህ ስትጸልይ ፈርተህ ከባልንጀራህ ጋር እንድትታረቅ ብሎ እንድትጸልው ባዘዘህ መንገድ ሳይኾን ቈርጠህ ብትደግመው እንኳን ደገኛ መንገድ ነው ብለህ አታስብ፡፡
“ብዙ ጊዜ ለምኜዋለሁ፤ ተማጽኜዋለሁ፤ ማልጄዋለሁ፤ ሊታረቀኝ ግን አልቻለም” ብለህ አትንገረኝ፡፡ እስክትታረቀው ድረስ በፍጹም አታቁም፡፡ ጌታችን ሲናገር፡- “መባህን ትተህ ኺድ፤ ወንድምህንም ለምነው” አይደለምና፡፡ ያለው፡- “ኺድ፤ ታረቅ” ነው (ማቴ.5፡24)፡፡ ስለዚህ ምንም እንኳን ብዙ ጊዜ ለምነኸው ቢኾንም እስክታሳምነው ድረስ ግን ይህን ማድረግህን አታቋርጥ፡፡ እግዚአብሔር ዕለት ዕለት ይለምነናል፤ እኛ ግን አንሰማውም፡፡ ኾኖም [አልሰሙኝም ብሎ] መለመኑን አላቋረጠም፡፡ ታዲያ አንተ ባልንጀራህን ለመለመን ትታጀራለህን? እንዲህ የምታደርግ ከኾነስ ልትድን የምትችለው እንዴት ነው?
የይቅርታ ልብ ይስጠን
https://telegram.me/Leoulu
https://telegram.me/Leoulu
https://telegram.me/Leoulu
Telegram
የሥላሴ ባርያ የልዑል ት/ት ቤት
ሥላሴ ትትረመም ወትትነከር
"ሰማዕትነት ስር ነው፡፡ ክርስቲያኖች ደግሞ ከዚኽ ስር የሚያቆጠቁጡ ምርጥ ዘሮች ናቸው፡፡ ብዙ ዛፍ የሚያቆጠቁጥበት ስር በለም አፈር ስለሚሸፈን አይታይም፡፡ ከዚያ በሚያቆጠቁጡ ዛፎች ግን ስሩ እንዴት እንደተመቸው ይታወቃል፡፡ ሰማዕታትም በግዙፉ ዓይናችን እንደምን ያለ አክሊል ሽልማት እንደተቀበሉ አይታየንም፡፡ ፍሬያቸው ግን እነርሱን መስለው እነርሱን አኽለው በሚጋደሉ ምርጥ ዘሮች ይታወቃል፡፡
ሰማዕታት አክብሩን ብለው አይናገሩም፡፡ ነገር ግን በክርስቲያኖች ልብ የሚዘሩት ፍሬ ምእመናንን በፍቅር ያስገድዳል፡፡ እነርሱን እንዲመስሉ ያሳስባል፡፡
ሰማዕታት እንደ ፍቅረኛ ናቸው፡፡ አንድ ሰው የፍቅረኛውን ስም በየአጋጣሚው ያነሣል፡፡ በዓይነ ሕሊናው ያስባል፡፡ በተለያየ መልኩ ያያል፡፡ ሰማዕታትም ለክርስቲያኖች እንደዚያ ናቸው፡፡ እጅግ የተወደዱና በፍጹም ከሕሊና የማይጠፉ ተወዳጆች ናቸው፡፡ የልጆቻችንን ስም በነርሱ ስም የምንሰይመው፣ ሥዕላቸውን ሥለን የምንተሻሸው የምንስመው ለሰማዕታቱ ያለንን ጥልቅ ፍቅር የምንገልጽበት መንገድ ስለኾነ ነው፡፡"
(ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ)
የሰማዕቷ ቅድስት አርሴማ በረከት አይለየን!
ሰማዕታት አክብሩን ብለው አይናገሩም፡፡ ነገር ግን በክርስቲያኖች ልብ የሚዘሩት ፍሬ ምእመናንን በፍቅር ያስገድዳል፡፡ እነርሱን እንዲመስሉ ያሳስባል፡፡
ሰማዕታት እንደ ፍቅረኛ ናቸው፡፡ አንድ ሰው የፍቅረኛውን ስም በየአጋጣሚው ያነሣል፡፡ በዓይነ ሕሊናው ያስባል፡፡ በተለያየ መልኩ ያያል፡፡ ሰማዕታትም ለክርስቲያኖች እንደዚያ ናቸው፡፡ እጅግ የተወደዱና በፍጹም ከሕሊና የማይጠፉ ተወዳጆች ናቸው፡፡ የልጆቻችንን ስም በነርሱ ስም የምንሰይመው፣ ሥዕላቸውን ሥለን የምንተሻሸው የምንስመው ለሰማዕታቱ ያለንን ጥልቅ ፍቅር የምንገልጽበት መንገድ ስለኾነ ነው፡፡"
(ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ)
የሰማዕቷ ቅድስት አርሴማ በረከት አይለየን!
የጋስጫው ሊቅ አባ ጊዮርጊስ እንዲህ አለ
የዓለም ሁሉ መድኃኒት የምትሆን ብላቴና እግሯ የተመላለሰበቱን ምድር እስም ዘንድ ማን በከፈለኝ፡፡ ይቅርታን የምታሰጥ ብላቴና ጥላዋ ይነካኝ ዘንድ ማን በከፈለኝ፡፡ የብርሃን ልጅ ወደ ሄደችበት እከተላት ዘንድ ማን በከፈለኝ የእግሯንም ጫማ እሸከም ዘንድ ማን በከፈለኝ፡፡
አሁንም ያን ጊዜ በዕብራይስጥ ማሪሃም ከተባለች ከተመረጠች ድንግል ማርያም ጋራ ያን ጊዜ ካሉት አላንስም ሀሳቤን ከዚያ እንዳለሁ አድርጌ አለሁና፡፡ በስጋ አልነበርሁም በመንፈስ ግን አለሁ፡፡ ባነዋወር አልነበርሁም በሃይማኖት ግን አለሁ በገጽ አልነበርሁም በማመን ግን አለሁ፡፡ ሳልኖር እራሴን እንዳለሁ ያረደረግሁ እኔ የተመሰገንሁ ነኝ ጌታችን በወንጌል እንደተናገረ እንዲህ ሲል ሳያዩኝ የሚያምኑብኝ ግን የተመሰገኑ ናቸው፡፡
እኔ ባሪያህ ስለሃይማኖቴ የተመሰገንሁ ነኝ፡፡ ስለ ዕውነቴ አይደለም ስለ መረዳቴም የተመሰገንሁ ነኝ፡፡ ስለ ንጽህናዬም አይደለም በእግዚአብሔር ስም ስለ አመንኩ የተመሰገንሁ ነኝ፡፡ በናቱም ጸሎት ስለ አመንሁ ንዑድ ክቡር ነኝ፡፡
የዓለም ሁሉ መድኃኒት የምትሆን ብላቴና እግሯ የተመላለሰበቱን ምድር እስም ዘንድ ማን በከፈለኝ፡፡ ይቅርታን የምታሰጥ ብላቴና ጥላዋ ይነካኝ ዘንድ ማን በከፈለኝ፡፡ የብርሃን ልጅ ወደ ሄደችበት እከተላት ዘንድ ማን በከፈለኝ የእግሯንም ጫማ እሸከም ዘንድ ማን በከፈለኝ፡፡
አሁንም ያን ጊዜ በዕብራይስጥ ማሪሃም ከተባለች ከተመረጠች ድንግል ማርያም ጋራ ያን ጊዜ ካሉት አላንስም ሀሳቤን ከዚያ እንዳለሁ አድርጌ አለሁና፡፡ በስጋ አልነበርሁም በመንፈስ ግን አለሁ፡፡ ባነዋወር አልነበርሁም በሃይማኖት ግን አለሁ በገጽ አልነበርሁም በማመን ግን አለሁ፡፡ ሳልኖር እራሴን እንዳለሁ ያረደረግሁ እኔ የተመሰገንሁ ነኝ ጌታችን በወንጌል እንደተናገረ እንዲህ ሲል ሳያዩኝ የሚያምኑብኝ ግን የተመሰገኑ ናቸው፡፡
እኔ ባሪያህ ስለሃይማኖቴ የተመሰገንሁ ነኝ፡፡ ስለ ዕውነቴ አይደለም ስለ መረዳቴም የተመሰገንሁ ነኝ፡፡ ስለ ንጽህናዬም አይደለም በእግዚአብሔር ስም ስለ አመንኩ የተመሰገንሁ ነኝ፡፡ በናቱም ጸሎት ስለ አመንሁ ንዑድ ክቡር ነኝ፡፡
ኢይፃእ ዐብይ ነገር እምአፉክሙ
#አንደበትም እሳት ነው።ይላል የጌታ ወንድም ያዕቆብ በመልዕክቱ በሰዎች መካከል ጠብን ክርክርን ያነሳል ከዛም አልፎ ሥጋን ያሳድፋል የፍጥረትንም ሩጫ ያቃጥላል በሕይወት ዘመን ውስጥ ጥቁር የሆነ አስተሳሰብን እንዲኖርህ ያደርጋ። ቅዱስ ጳውሎስ በመልክታቶቹ አብዛኛው ጊዜ ጸያፍ ንግሮች ያወግዛል በኤፌሶን መልዕክቱ ላይ “ክፉ ቃል ከአፋችሁ ከቶ አይውጣ።” በቆላስይስ መልዕክቱ ላይም እንዲህ ይላል “ከአፋችሁም ስድብን የሚያሳፍርንም ንግግር እነዚህን ሁሉ አስወግዱ” አንደበት የመልካም ንግግሮች መፍሰሻ ነው ከዚህ በቀር ውጭ የኃጢአት መፈንጫ ነው ጠቢብ ሰሎሞን በምሳሌ መጽሐፉ ላይ ሲናገር “በቃል ብዛት ውስጥ ኃጢአት ሳይኖር አይቀርም ከንፈሩን የሚገታ ግን አስተዋይ ነው።”
#የአንደበት ጸያፍ ንግግሮች በዓለም እስከኖርንበት ድረስ ዋጋ ታስከፍላለች። ጌታችን በማቴዎስ ወንጌል ላይ መስማት ና ማየት የተሳነው ሰው ጌታችን ጋኔኑን ፈውሷል ይህን በማድረጉ ፈሪሳውያን ጸያፍ ቃላት አውጥተው ከሰሁት ነበር ጌታችን በጸያፍ አነጋገራቸው በማውገዝ ለዐብይ አነጋገራቸው በሚገርም ሐረጎች መልስ ሰቶቿዋል "ኄር ብእሲ እምሠናይ መዝገበ ልቡ ያወፅእ ሠናየ "መልካም ሰው ከልቡ መልካም መዝገብ መልካም ነገርን ያወጣል እናትተ ግን ስራችሁ ከዳቢሎስ መዝገባች ልባችሁ ከሲኦል ስለሆነ ለምን መልካም ነገር ትናገራለች "ወመዐምፅ ብእሲ እመዝገበ ዐመፃ ያወፅእ ዐመፃ" ክፉ ሰውም ከክፉ መዝገብ ክፉ ነገርን ያወጣል። ከፈሪሳዊያን እስከ ሌዋዋውያን ነን እስከሚሉ ሊቃነ ካህናት ድረስ የአንደበታቸው ውሸት የሐሰት ፍርድ ያወግዝ ይገጽጻቸዋል።
#የሰው ልጆች በቀን ውስጥ ከ፴፭፻/3,500 በላይ ቃላትን ይናገር ከእነዚህ ውስጥ መልካምም የአንደበት የስህተት ንግግርም ዋጋ የሚከፈለንም የምንጠየቅበት ነው። አብዛኞቻችን በንግግር ኃጢያት ፍርድ ያለ አይመስለንም ጌታችን ለፈሪሳዊያን በመለሰላቸው ገጽ ላይ እንዲህ ይላል
"ሰዎች ስለሚናገሩት ስለ ከንቱ ነገር ሁሉ በፍርድ ቀን መልስ ይሰጡበታል" የአንደበታችን ተርታ ንግግሮች በፍርድ ፍዳ የምናገኝበት መከራ ሲኦል የምንቀላቀልበት ነው። እዛው በማቴዎስ ወንጌል ላይ '' ከቃልህ የተነሣ ትጸድቃለህና ከቃልህም የተነሣ ትኰነናለህ።'' ቃላችን ዋጋ አላት በቃላች መጽደቅ በቃላችን በኃጢያት መኖ ይገኛል።
#አንደበት ከሽንገላ ካልገራን የብዙን ሰው መቃብር ትሆናች መዝሙረኛው እንዲህ “በአፋቸው እውነት የለምና ልባቸውም ከንቱ ነው ጕሮሮአቸው የተከፈተ መቃብር ነው በምላሳቸው ይሸነግላሉ።” ከእንደዚህ ያለ ንግር እርቀን መልካም በሆነው ወይም ቅዱስ ጳውሎስ በቆላስይስ መልዕክቱ ላይ “ለእያንዳንዱ እንዴት እንድትመልሱ እንደሚገባችሁ ታውቁ ዘንድ ንግግራችሁ ሁልጊዜ፥ በጨው እንደ ተቀመመ፥ በጸጋ ይሁን።”አባ መቃርስ ስለ ልብ ንጽሕና ሲናገር አንተ ባህታዊ ሆይ ለወራት በርህን መዝጋትህ ምን ጥቅም የለውጥ ግን ከዚህ ቀድመህ የአንደበትህ እና የልብህን በር ካልዘጋ የአንተ በር ዘግቶ በተባትኦ መቀመጥ ምን አይጠቅም ይላል።
ቅዱስ ኤፍሬም እንዲህ ይላል "ለአፍህ ተጠንቀቅ ግን በዋነኝነት በአእምሮህ ክፉ ሐሳቦች ከአንተ ጋር ማውራት አትፍቀድ። አፍህ ምናልባት ወንድምህን ሊጎዳ የሚችል ቃላትን ይናገራልና። ድፍረት እና ተስፋ ውስጣዊውን ሰው የሚገልጠው የአንድ ሰው አፍ ነውና።"
#ይቆየን
@Leoulu
@Leoulu
@Leoulu
''ወእግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ የሀሉ ምስለ መንፈሰክሙ ወጸጋሁ ምስሌክሙ አሜን!''
“ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ከመንፈሶቻችን ጋር ይሁን። ጸጋ ከእናንተ ጋር ይሁን፤ አሜን።”
#አንደበትም እሳት ነው።ይላል የጌታ ወንድም ያዕቆብ በመልዕክቱ በሰዎች መካከል ጠብን ክርክርን ያነሳል ከዛም አልፎ ሥጋን ያሳድፋል የፍጥረትንም ሩጫ ያቃጥላል በሕይወት ዘመን ውስጥ ጥቁር የሆነ አስተሳሰብን እንዲኖርህ ያደርጋ። ቅዱስ ጳውሎስ በመልክታቶቹ አብዛኛው ጊዜ ጸያፍ ንግሮች ያወግዛል በኤፌሶን መልዕክቱ ላይ “ክፉ ቃል ከአፋችሁ ከቶ አይውጣ።” በቆላስይስ መልዕክቱ ላይም እንዲህ ይላል “ከአፋችሁም ስድብን የሚያሳፍርንም ንግግር እነዚህን ሁሉ አስወግዱ” አንደበት የመልካም ንግግሮች መፍሰሻ ነው ከዚህ በቀር ውጭ የኃጢአት መፈንጫ ነው ጠቢብ ሰሎሞን በምሳሌ መጽሐፉ ላይ ሲናገር “በቃል ብዛት ውስጥ ኃጢአት ሳይኖር አይቀርም ከንፈሩን የሚገታ ግን አስተዋይ ነው።”
#የአንደበት ጸያፍ ንግግሮች በዓለም እስከኖርንበት ድረስ ዋጋ ታስከፍላለች። ጌታችን በማቴዎስ ወንጌል ላይ መስማት ና ማየት የተሳነው ሰው ጌታችን ጋኔኑን ፈውሷል ይህን በማድረጉ ፈሪሳውያን ጸያፍ ቃላት አውጥተው ከሰሁት ነበር ጌታችን በጸያፍ አነጋገራቸው በማውገዝ ለዐብይ አነጋገራቸው በሚገርም ሐረጎች መልስ ሰቶቿዋል "ኄር ብእሲ እምሠናይ መዝገበ ልቡ ያወፅእ ሠናየ "መልካም ሰው ከልቡ መልካም መዝገብ መልካም ነገርን ያወጣል እናትተ ግን ስራችሁ ከዳቢሎስ መዝገባች ልባችሁ ከሲኦል ስለሆነ ለምን መልካም ነገር ትናገራለች "ወመዐምፅ ብእሲ እመዝገበ ዐመፃ ያወፅእ ዐመፃ" ክፉ ሰውም ከክፉ መዝገብ ክፉ ነገርን ያወጣል። ከፈሪሳዊያን እስከ ሌዋዋውያን ነን እስከሚሉ ሊቃነ ካህናት ድረስ የአንደበታቸው ውሸት የሐሰት ፍርድ ያወግዝ ይገጽጻቸዋል።
#የሰው ልጆች በቀን ውስጥ ከ፴፭፻/3,500 በላይ ቃላትን ይናገር ከእነዚህ ውስጥ መልካምም የአንደበት የስህተት ንግግርም ዋጋ የሚከፈለንም የምንጠየቅበት ነው። አብዛኞቻችን በንግግር ኃጢያት ፍርድ ያለ አይመስለንም ጌታችን ለፈሪሳዊያን በመለሰላቸው ገጽ ላይ እንዲህ ይላል
"ሰዎች ስለሚናገሩት ስለ ከንቱ ነገር ሁሉ በፍርድ ቀን መልስ ይሰጡበታል" የአንደበታችን ተርታ ንግግሮች በፍርድ ፍዳ የምናገኝበት መከራ ሲኦል የምንቀላቀልበት ነው። እዛው በማቴዎስ ወንጌል ላይ '' ከቃልህ የተነሣ ትጸድቃለህና ከቃልህም የተነሣ ትኰነናለህ።'' ቃላችን ዋጋ አላት በቃላች መጽደቅ በቃላችን በኃጢያት መኖ ይገኛል።
#አንደበት ከሽንገላ ካልገራን የብዙን ሰው መቃብር ትሆናች መዝሙረኛው እንዲህ “በአፋቸው እውነት የለምና ልባቸውም ከንቱ ነው ጕሮሮአቸው የተከፈተ መቃብር ነው በምላሳቸው ይሸነግላሉ።” ከእንደዚህ ያለ ንግር እርቀን መልካም በሆነው ወይም ቅዱስ ጳውሎስ በቆላስይስ መልዕክቱ ላይ “ለእያንዳንዱ እንዴት እንድትመልሱ እንደሚገባችሁ ታውቁ ዘንድ ንግግራችሁ ሁልጊዜ፥ በጨው እንደ ተቀመመ፥ በጸጋ ይሁን።”አባ መቃርስ ስለ ልብ ንጽሕና ሲናገር አንተ ባህታዊ ሆይ ለወራት በርህን መዝጋትህ ምን ጥቅም የለውጥ ግን ከዚህ ቀድመህ የአንደበትህ እና የልብህን በር ካልዘጋ የአንተ በር ዘግቶ በተባትኦ መቀመጥ ምን አይጠቅም ይላል።
ቅዱስ ኤፍሬም እንዲህ ይላል "ለአፍህ ተጠንቀቅ ግን በዋነኝነት በአእምሮህ ክፉ ሐሳቦች ከአንተ ጋር ማውራት አትፍቀድ። አፍህ ምናልባት ወንድምህን ሊጎዳ የሚችል ቃላትን ይናገራልና። ድፍረት እና ተስፋ ውስጣዊውን ሰው የሚገልጠው የአንድ ሰው አፍ ነውና።"
#ይቆየን
@Leoulu
@Leoulu
@Leoulu
''ወእግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ የሀሉ ምስለ መንፈሰክሙ ወጸጋሁ ምስሌክሙ አሜን!''
“ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ከመንፈሶቻችን ጋር ይሁን። ጸጋ ከእናንተ ጋር ይሁን፤ አሜን።”
በአንድ ወቅት አንድ መንፈሳዊ አባት ከነበሩበት ቦታ ወደ በረሃ መሰደድ ግድ ሆነባቸው። ከቅዱስ መጽሐፋቸው ሌላ ሦስት ነገሮች ነበሯቸው።
እነሱም፦
1ኛ ቅዱስ መጽሐፉን በጨለማ ወቅት ለማንበብ የሚጠቅማቸው ኩራዝ ።
2ኛ ጎህ ከመቅደዱ በፊት ከእንቅልፍ የሚቀሰቅሳቸው አንድ አውራ ዶሮ።
3ኛ ለመጓጓዣነት የሚገለገሉበት አንድ አህያ ነበሩ።
አንድ ቀን ምሽት ከጉዞ የተነሣ በጣም ስለ ደከሙ እኚህ መንፈሳዊ አባት ወደ አንድ መንደር ቀርበው ማደሪያ ቢጠይቁም መንደርተኛው በሙሉ ልክ እንደተመካከረ ሰው ፈቃደኛ ባለመሆኑ ማንም አላሳደራቸውም።
ስለዚህም አማራጭ ስላልነበራቸው ከመንደሩ አቅራቢያ አንድ ጉድጓድ ያገኙና በዚያ ውስጥ ገብቶ ለማደር በመወሰን ወደ ጉድጓዱ ገብተው አደሩ። እንደ ወትሮው ቅዱስ መጽሐፋቸውን ለማንበብ ኩራዛቸውን ቢለኩሱትም የነበረው ብርቱ ነፋስ አጠፋባቸው። ደጋግመው ቢሞክሩም ሊሳካላቸው አልቻለም
ስለዚህም ለመተኛት ጋደም እንዳሉ ተኩላ መጥቶ አውራ ዶሮዋቸውን፣ አንበሳም አህያቸውን በሉባቸው።
የተደራረበ ጉዳት ስለደረሰባቸው ሽማግሌው እርዳታን በመሻት ወደዚያ መንደር ቢመለሱ ዘራፊ ሽፍታዎች የመንደሩን ነዋሪዎች በሙሉ ገድለው ንብረት ዘርፈው ዖና መንደር ሆኖ አገኙት።
ሽማግሌው ይህን ሁሉ ባጤኑ ጊዜ እግዚአብሔር ምን ያህል መልካም ነገርን እንዳደረገላቸው አስተዋሉ። በዚያች ምሽት በመንደርተኞቹ በአንዱ ቤት ቢያድሩ ኖሮ የዘራፊዎች ሰለባ ሆነው ሊገደሉ በቻሉ ነበር።
ቀንዲላቸውንም (ኩራዝ) ነፋስ ባያጠፋው የብርሃኑ ወጋገን እዚህ ጋር ሰው አለ በማለት ለሽፍታዎቹ ያሳብቅ ነበር። አውራ ዶሮአቸውና አህያቸውም ባይበሉ ኖሮ ከሽፍታዎቹ ተደብቀው ማደር ባልቻሉ ነበር።” እግዚአብሔር ከክፉ ነገሮች ውስጥ መልካም ነገር ማውጣት የሚችል አምላክ ነው
@Leoulu
እነሱም፦
1ኛ ቅዱስ መጽሐፉን በጨለማ ወቅት ለማንበብ የሚጠቅማቸው ኩራዝ ።
2ኛ ጎህ ከመቅደዱ በፊት ከእንቅልፍ የሚቀሰቅሳቸው አንድ አውራ ዶሮ።
3ኛ ለመጓጓዣነት የሚገለገሉበት አንድ አህያ ነበሩ።
አንድ ቀን ምሽት ከጉዞ የተነሣ በጣም ስለ ደከሙ እኚህ መንፈሳዊ አባት ወደ አንድ መንደር ቀርበው ማደሪያ ቢጠይቁም መንደርተኛው በሙሉ ልክ እንደተመካከረ ሰው ፈቃደኛ ባለመሆኑ ማንም አላሳደራቸውም።
ስለዚህም አማራጭ ስላልነበራቸው ከመንደሩ አቅራቢያ አንድ ጉድጓድ ያገኙና በዚያ ውስጥ ገብቶ ለማደር በመወሰን ወደ ጉድጓዱ ገብተው አደሩ። እንደ ወትሮው ቅዱስ መጽሐፋቸውን ለማንበብ ኩራዛቸውን ቢለኩሱትም የነበረው ብርቱ ነፋስ አጠፋባቸው። ደጋግመው ቢሞክሩም ሊሳካላቸው አልቻለም
ስለዚህም ለመተኛት ጋደም እንዳሉ ተኩላ መጥቶ አውራ ዶሮዋቸውን፣ አንበሳም አህያቸውን በሉባቸው።
የተደራረበ ጉዳት ስለደረሰባቸው ሽማግሌው እርዳታን በመሻት ወደዚያ መንደር ቢመለሱ ዘራፊ ሽፍታዎች የመንደሩን ነዋሪዎች በሙሉ ገድለው ንብረት ዘርፈው ዖና መንደር ሆኖ አገኙት።
ሽማግሌው ይህን ሁሉ ባጤኑ ጊዜ እግዚአብሔር ምን ያህል መልካም ነገርን እንዳደረገላቸው አስተዋሉ። በዚያች ምሽት በመንደርተኞቹ በአንዱ ቤት ቢያድሩ ኖሮ የዘራፊዎች ሰለባ ሆነው ሊገደሉ በቻሉ ነበር።
ቀንዲላቸውንም (ኩራዝ) ነፋስ ባያጠፋው የብርሃኑ ወጋገን እዚህ ጋር ሰው አለ በማለት ለሽፍታዎቹ ያሳብቅ ነበር። አውራ ዶሮአቸውና አህያቸውም ባይበሉ ኖሮ ከሽፍታዎቹ ተደብቀው ማደር ባልቻሉ ነበር።” እግዚአብሔር ከክፉ ነገሮች ውስጥ መልካም ነገር ማውጣት የሚችል አምላክ ነው
@Leoulu
"የወንድምህን ኃጢአት መሸፈንና የእርሱን ኃጢአት እንደራስህ አድርግህ በእርሱ ፋንታ መሞት ካልቻልክ ቢያንስ ስለ ኃጢአቱ አትፍረድበት።››
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
††† እንኩዋን ለቅዱሳን ነገሥታት "አብርሃ ወአጽብሃ" እና ለቅዱስ "ሐናንያ ሐዋርያ" ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ †††
+"+ ቅዱሳን አብርሃ ወአጽብሃ +"+
=>እነዚህ ነገሥታት ሞገሶቻችን: ብርሃኖቻችን ናቸውና ደስ እያለን እንወዳቸዋለን: እናከብራቸዋለን:: ሥላሴ ቢመርጧቸው ዛሬ ላለንበት ሕይወት መሠረቱን ጥለው አልፈዋልና::
+2ቱ ቅዱሳን ነግሥታት መንትያዎች ሲሆኑ ወላጆቻቸው ንጉሥ ታዜር / አይዛና / ሠይፈ አርዕድ እና ንግሥት አሕየዋ / ሶፍያ ይባላል:: ንጉሡና ባለቤቱ ልጅ ቢያጡ ወደ እግዚአብሔር ለመኑ:: ፈጣሪም በቅዱስ ሚካኤል አብሳሪነት 2 ዕንቁዎችን አስረከባቸው::
+ንግስት አሕየዋ (ሶፍያም) መጋቢት 29 ቀን በ311 ዓ/ም ጸንሳ: ታሕሳስ 29 ቀን በ312 ዓ/ም 2ቱን ቅዱሳን ወልዳቸዋለች:: "አምላክ ሽሙጥን አራቀልኝ" ስትልም "አዝጉዋጉ" ብላቸዋለች:: እነዚህ 2 ፍሬዎች በልጅነታቸው ከወቅቱ ሊቀ ካህናት እንበረም ኦሪቱን ጠንቅቀው ተምረዋል::
+ከእግዚአብሔር የተሰጡ ናቸውና በ12 ዓመታቸው ወደ ቤተ መቅደስ ገብተዋል:: ትንሽ ቆይቶ ግን አባታቸው ታዜር በማረፉ ሕዝቡ 2ቱን ቅዱሳን "ንገሡልን" አሏቸው:: እነርሱም "እኛ የፈጣሪ አገልጋዮች ነንና አንችልም" በማለታቸው ለተወሰነ ጊዜ እናታቸው አስተዳደረች::
+ቆይቶ ግን ቅዱስ ሚካኤል ለሊቀ ካህናቱ እንበረም "የፈጣሪ ፈቃዱ ስለ ሆነ አትዘኑ:: 2ታችሁም በአንድ ዙፋን ላይ ንገሡ: ታላቅ ጸጋ ለሃገሪቱ ይሆናል በላቸው" አለው::
+ሊቀ ካህናቱም የታዘዘውን ተናግሮ: በ19 ዓመታቸው: 2ቱንም በአንድ ዙፋን ላይ "ነገሥተ ኢትዮዽያ" ሲል አስቀምጦ ቀባቸው:: ስማቸውን "ኢዛና" እና "ሳይዛና" አላቸው:: ቅዱሳኑ እንደ ነገሡ ቀዳሚ ሥራቸው የቀናችውን ሃይማኖት መፈለግ ሆነ::
+በወቅቱ ፍሬምናጦስ (የሁዋላው አቡነ ሰላማ) በቤተ መንግስቱ ውስጥ የቅርብ አማካሪ ነበርና ጠርተው ተጨዋወቱት:: "አንተ ወንድማችን! ክርስቶስ ይወርዳል: ይወለዳል ተብሎ የተቆጠረው ሱባኤ እኮ አልፏል:: ምነው ቀረሳ?
ምሥጢሩን ንገረን" አሉት::
+እርሱም አትቶ: አመሥጥሮ: ከ300 ዓመታት በፊት አምላክ ሰው መሆኑንና ዓለምን ማዳኑን አስተማራቸው:: "አጥምቀን?" ቢሉት "አልችልም" አላቸው:: እነርሱም ከብዙ ስጦታ ጋር ወደ ግብጽ ላኩት::
+ቅዱስ አትናቴዎስም ፍሬምናጦስን "አቡነ ሰላማ" ብሎ ከብዙ መጻሕፍት ጋር ላከው:: በመጀመሪያ ኢዛናና ሳይዛና ተጠመቁ:: ስማቸውም "አብርሃ ወአጽብሃ" ተባለ:: ቀጥሎም ሠራዊቱና ሕዝቡ ተጠመቀ::
+ሃገራችንም በእነዚህ ቅዱሳን አማካኝነት ከጨለማ ወደ ብርሃን መጣች:: የክርስትና ደሴት ሆነች:: ሃገረ እግዚአብሔርነቷንም አጸናች:: ቅዱሳኑ ከዚህ በሁዋላ በሞገስ ክርስትናን ያስፋፉ ዘንድ ደከሙ:: ከ154 በላይ አብያተ ክርስቲያናትን ሲያንጹ አብዛኞቹ ፍልፍል ነበሩ::
+በተለይ ግን በአክሱም ከተማ ላይ ያነጿትና 12 ቤተ መቅደሶች የነበሯት የጽዮን ቤተ ክርስቲያን ልናያት ትናፍቀናለች:: ጌጧ: ብርሃኗ ውል ውል ይልብናል:: ይህቺው ቤተ ክርስቲያን በ10 ኛው ክ/ዘመን ዮዲት ጉዲት በእሳት አውድማታለችና:: መሠረቱ ግን ዛሬም አለ::
+ቅዱሳን አብርሃ ወአጽብሃ ግን ክርስትናን ለማስፋፋትና መንግስትን ለማጽናት ሲሉ ከአክሱም በተጨማሪ በሽዋም ዙፋንን ዘረጉ:: ለብዙ ዓመታትም አምላክ በፈቀደው መንገድ እስከ የመን ድረስ ገዙ:: ክርስትናንም አስፋፉ::
+ቅዱስ አብርሃ በተወለደ በ52 ዓመቱ: በ364 ዓ/ም ጥቅምት 4 ቀን ሲያርፍ ወንድሙ ለ15 ዓመታት ብቻውን አስተዳድሯል:: በ379 ዓ/ም ደግሞ በዚሁ በጥቅምት 4 ቀን ቅዱስ አጽብሃም በተወለደ በ67 ዓመቱ በክብር ዐርፏል::
+ከሁለቱም መቃብር ላይ ለ30 ቀናት የብርሃን ምሰሶ ተተክሎ ታይቷል:: ጌታችንም በማይታበል ቃሉ "ስማችሁን የጠራውን: መታሰቢያችሁን ያደረገውንም እምርላቹሃለሁ" ሲል ቃል ኪዳን ገብቶላቸዋል::
+"+ ቅዱስ ሐናንያ ሐዋርያ +"+
=>ሐናንያ ቁጥሩ ከ72ቱ አርድእት ሲሆን መጽሐፍ ቅዱስ ላይ ስማቸው ተመዝግቦ ከተቀመጠልን ከጥቂቶቹ ዋነኛው ነው:: ከነገደ እሥራኤል ተወልዶ: በሕገ ኦሪት አድጐ: ከወጣትነት ዕድሜው ትንሽ እልፍ ሲል ጌታችን ወንጌልን ማስተማር ጀምሯልና ጠራው:: እርሱም በበጐ ፈቃድ ተከትሎታልና ከ72ቱ አርድእት ደመረው::
+ለ3 ዓመታት ከጌታ እግር ተምሮ: ከዕለተ ስቅለት በፊት ሀብተ ፈውስም ተሰጥቶት ነበር:: ምክንያቱም ቅዱስ ሉቃስ እንደ ጻፈልን ሰብዐው አርድእት "ጌታ ሆይ! አጋንንት በስምህ ተገዙልን" ማለታቸውን አስቀምጦልናል:: (ሉቃ. 10:17) ቅዱስ ሐናንያ በበዓለ ዕርገት ተባርኮ በ50ኛው ቀንም መንፈስ ቅዱስን ተቀብሎ ለስብከተ ወንጌል ወጥቷል::
+በሚያስተምር ጊዜ የሶርያዋን ደማስቆን ማዕከል አድርጐ ነበር:: በሁዋላም አበው ሐዋርያት የዚህች ከተማ የመጀመሪያው ዻዻስ አድርገው ሹመውታል:: ጌታ ባረገ በ8ኛው ዓመት ክርስቲያኖችን ያሰቃይ የነበረው ሳውል (የሁዋላው ቅዱስ ዻውሎስ) ወደ ደማስቆ የተጉዋዘው ክርስቲያኖችን በተለይም ቅዱስ ሐናንያን ለማሠር ነበር::
+ለእግዚአብሔር ምርጥ ዕቃ ይሆን ዘንድ መብረቅ ዐይኑን አጠፋው:: ወዲያውም ጌታችን ሳውልን ወደ ሐናንያ እንዲሔድ ነው የነገረው:: ከ3 ቀናት በሁዋላ ጌታችን ለሐናንያ ተገልጦ አነጋግሮታል:: ሳውል (ዻውሎስ) ወደ ሐናንያ የደረሰው በመሪ ነበር::
+2ቱ እንደተገናኙ ቅዱስ ሐናንያ ሳውልን አስተማረው: ፈወሰው: አጠመቀው: በጐ መንገድንም መራው:: በዚህ ምክንያት ቅዱሱ ሐዋርያ የቅዱስ ዻውሎስ የንስሃ አባቱ ይሰኛል:: (ሐዋ. 9:1-19)
+ከዚህ በሁዋላ ቅዱስ ሐናንያ ለብዙ ዓመታት በተለያዩ የዓለም ክፍሎች ወንጌልን አስተማረ መከራንም ተቀበለ:: በመጨረሻም በዚህ ቀን ክፉዎች ከብዙ ስቃይ በሁዋላ በድንጋይ ወግረው ገድለውታል::
=>አምላከ አብርሃ ወአጽብሃ "ድሃ ተበደለ: ፍርድ ተጉዋደለ" የሚል ዳኛ: ሃይማኖቱ የቀና መሪንም ያምጣልን:: የቅዱሳኑን ክብር በእኛ ላይ ያድርግልን::
=>ጥቅምት 4 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.ቅዱሳን ነገሥት አብርሃ ወአጽብሃ
2.ቅዱስ ሐናንያ ሐዋርያ (ከ72ቱ አርድእት)
3.ቅዱስ በርተሎሜዎስ ሐዋርያ
4.ቅዱስ ባኮስ ሰማዕት
5.ቅዱሳን ባባ እና ማማ
6.ቅዱስ ዮሐንስ ሕጽው
=>ወርኀዊ በዓላት
1.ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ
2.ቅዱስ እንድርያስ ሐዋርያ
3.ቅድስት ሶፍያ ሰማዕት
4.ቅዱስ ዮሐንስ ዘሐራቅሊ (ሰማዕት)
=>+"+ እንግዲህ እግዚአብሔርን በመምሰልና በጭምትነት ሁሉ: ጸጥና ዝግ ብለን እንድንኖር: ልመናና ጸሎት: ምልጃም: ምስጋናም ስለ ሰዎች ሁሉ: ስለ ነገሥታትና መኩዋንንትም ሁሉ እንዲደረጉ ከሁሉ በፊት እመክራለሁ:: ሰዎች ሁሉ ሊድኑና እውነቱን ወደ ማወቅ ሊደርሱ በሚወድ በእግዚአብሔር በመድኃኒታችን ፊት መልካምና ደስ የሚያሰኝ ይህ ነው:: +"+ (1ጢሞ. 2:1-4)
††† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †††
+"+ ቅዱሳን አብርሃ ወአጽብሃ +"+
=>እነዚህ ነገሥታት ሞገሶቻችን: ብርሃኖቻችን ናቸውና ደስ እያለን እንወዳቸዋለን: እናከብራቸዋለን:: ሥላሴ ቢመርጧቸው ዛሬ ላለንበት ሕይወት መሠረቱን ጥለው አልፈዋልና::
+2ቱ ቅዱሳን ነግሥታት መንትያዎች ሲሆኑ ወላጆቻቸው ንጉሥ ታዜር / አይዛና / ሠይፈ አርዕድ እና ንግሥት አሕየዋ / ሶፍያ ይባላል:: ንጉሡና ባለቤቱ ልጅ ቢያጡ ወደ እግዚአብሔር ለመኑ:: ፈጣሪም በቅዱስ ሚካኤል አብሳሪነት 2 ዕንቁዎችን አስረከባቸው::
+ንግስት አሕየዋ (ሶፍያም) መጋቢት 29 ቀን በ311 ዓ/ም ጸንሳ: ታሕሳስ 29 ቀን በ312 ዓ/ም 2ቱን ቅዱሳን ወልዳቸዋለች:: "አምላክ ሽሙጥን አራቀልኝ" ስትልም "አዝጉዋጉ" ብላቸዋለች:: እነዚህ 2 ፍሬዎች በልጅነታቸው ከወቅቱ ሊቀ ካህናት እንበረም ኦሪቱን ጠንቅቀው ተምረዋል::
+ከእግዚአብሔር የተሰጡ ናቸውና በ12 ዓመታቸው ወደ ቤተ መቅደስ ገብተዋል:: ትንሽ ቆይቶ ግን አባታቸው ታዜር በማረፉ ሕዝቡ 2ቱን ቅዱሳን "ንገሡልን" አሏቸው:: እነርሱም "እኛ የፈጣሪ አገልጋዮች ነንና አንችልም" በማለታቸው ለተወሰነ ጊዜ እናታቸው አስተዳደረች::
+ቆይቶ ግን ቅዱስ ሚካኤል ለሊቀ ካህናቱ እንበረም "የፈጣሪ ፈቃዱ ስለ ሆነ አትዘኑ:: 2ታችሁም በአንድ ዙፋን ላይ ንገሡ: ታላቅ ጸጋ ለሃገሪቱ ይሆናል በላቸው" አለው::
+ሊቀ ካህናቱም የታዘዘውን ተናግሮ: በ19 ዓመታቸው: 2ቱንም በአንድ ዙፋን ላይ "ነገሥተ ኢትዮዽያ" ሲል አስቀምጦ ቀባቸው:: ስማቸውን "ኢዛና" እና "ሳይዛና" አላቸው:: ቅዱሳኑ እንደ ነገሡ ቀዳሚ ሥራቸው የቀናችውን ሃይማኖት መፈለግ ሆነ::
+በወቅቱ ፍሬምናጦስ (የሁዋላው አቡነ ሰላማ) በቤተ መንግስቱ ውስጥ የቅርብ አማካሪ ነበርና ጠርተው ተጨዋወቱት:: "አንተ ወንድማችን! ክርስቶስ ይወርዳል: ይወለዳል ተብሎ የተቆጠረው ሱባኤ እኮ አልፏል:: ምነው ቀረሳ?
ምሥጢሩን ንገረን" አሉት::
+እርሱም አትቶ: አመሥጥሮ: ከ300 ዓመታት በፊት አምላክ ሰው መሆኑንና ዓለምን ማዳኑን አስተማራቸው:: "አጥምቀን?" ቢሉት "አልችልም" አላቸው:: እነርሱም ከብዙ ስጦታ ጋር ወደ ግብጽ ላኩት::
+ቅዱስ አትናቴዎስም ፍሬምናጦስን "አቡነ ሰላማ" ብሎ ከብዙ መጻሕፍት ጋር ላከው:: በመጀመሪያ ኢዛናና ሳይዛና ተጠመቁ:: ስማቸውም "አብርሃ ወአጽብሃ" ተባለ:: ቀጥሎም ሠራዊቱና ሕዝቡ ተጠመቀ::
+ሃገራችንም በእነዚህ ቅዱሳን አማካኝነት ከጨለማ ወደ ብርሃን መጣች:: የክርስትና ደሴት ሆነች:: ሃገረ እግዚአብሔርነቷንም አጸናች:: ቅዱሳኑ ከዚህ በሁዋላ በሞገስ ክርስትናን ያስፋፉ ዘንድ ደከሙ:: ከ154 በላይ አብያተ ክርስቲያናትን ሲያንጹ አብዛኞቹ ፍልፍል ነበሩ::
+በተለይ ግን በአክሱም ከተማ ላይ ያነጿትና 12 ቤተ መቅደሶች የነበሯት የጽዮን ቤተ ክርስቲያን ልናያት ትናፍቀናለች:: ጌጧ: ብርሃኗ ውል ውል ይልብናል:: ይህቺው ቤተ ክርስቲያን በ10 ኛው ክ/ዘመን ዮዲት ጉዲት በእሳት አውድማታለችና:: መሠረቱ ግን ዛሬም አለ::
+ቅዱሳን አብርሃ ወአጽብሃ ግን ክርስትናን ለማስፋፋትና መንግስትን ለማጽናት ሲሉ ከአክሱም በተጨማሪ በሽዋም ዙፋንን ዘረጉ:: ለብዙ ዓመታትም አምላክ በፈቀደው መንገድ እስከ የመን ድረስ ገዙ:: ክርስትናንም አስፋፉ::
+ቅዱስ አብርሃ በተወለደ በ52 ዓመቱ: በ364 ዓ/ም ጥቅምት 4 ቀን ሲያርፍ ወንድሙ ለ15 ዓመታት ብቻውን አስተዳድሯል:: በ379 ዓ/ም ደግሞ በዚሁ በጥቅምት 4 ቀን ቅዱስ አጽብሃም በተወለደ በ67 ዓመቱ በክብር ዐርፏል::
+ከሁለቱም መቃብር ላይ ለ30 ቀናት የብርሃን ምሰሶ ተተክሎ ታይቷል:: ጌታችንም በማይታበል ቃሉ "ስማችሁን የጠራውን: መታሰቢያችሁን ያደረገውንም እምርላቹሃለሁ" ሲል ቃል ኪዳን ገብቶላቸዋል::
+"+ ቅዱስ ሐናንያ ሐዋርያ +"+
=>ሐናንያ ቁጥሩ ከ72ቱ አርድእት ሲሆን መጽሐፍ ቅዱስ ላይ ስማቸው ተመዝግቦ ከተቀመጠልን ከጥቂቶቹ ዋነኛው ነው:: ከነገደ እሥራኤል ተወልዶ: በሕገ ኦሪት አድጐ: ከወጣትነት ዕድሜው ትንሽ እልፍ ሲል ጌታችን ወንጌልን ማስተማር ጀምሯልና ጠራው:: እርሱም በበጐ ፈቃድ ተከትሎታልና ከ72ቱ አርድእት ደመረው::
+ለ3 ዓመታት ከጌታ እግር ተምሮ: ከዕለተ ስቅለት በፊት ሀብተ ፈውስም ተሰጥቶት ነበር:: ምክንያቱም ቅዱስ ሉቃስ እንደ ጻፈልን ሰብዐው አርድእት "ጌታ ሆይ! አጋንንት በስምህ ተገዙልን" ማለታቸውን አስቀምጦልናል:: (ሉቃ. 10:17) ቅዱስ ሐናንያ በበዓለ ዕርገት ተባርኮ በ50ኛው ቀንም መንፈስ ቅዱስን ተቀብሎ ለስብከተ ወንጌል ወጥቷል::
+በሚያስተምር ጊዜ የሶርያዋን ደማስቆን ማዕከል አድርጐ ነበር:: በሁዋላም አበው ሐዋርያት የዚህች ከተማ የመጀመሪያው ዻዻስ አድርገው ሹመውታል:: ጌታ ባረገ በ8ኛው ዓመት ክርስቲያኖችን ያሰቃይ የነበረው ሳውል (የሁዋላው ቅዱስ ዻውሎስ) ወደ ደማስቆ የተጉዋዘው ክርስቲያኖችን በተለይም ቅዱስ ሐናንያን ለማሠር ነበር::
+ለእግዚአብሔር ምርጥ ዕቃ ይሆን ዘንድ መብረቅ ዐይኑን አጠፋው:: ወዲያውም ጌታችን ሳውልን ወደ ሐናንያ እንዲሔድ ነው የነገረው:: ከ3 ቀናት በሁዋላ ጌታችን ለሐናንያ ተገልጦ አነጋግሮታል:: ሳውል (ዻውሎስ) ወደ ሐናንያ የደረሰው በመሪ ነበር::
+2ቱ እንደተገናኙ ቅዱስ ሐናንያ ሳውልን አስተማረው: ፈወሰው: አጠመቀው: በጐ መንገድንም መራው:: በዚህ ምክንያት ቅዱሱ ሐዋርያ የቅዱስ ዻውሎስ የንስሃ አባቱ ይሰኛል:: (ሐዋ. 9:1-19)
+ከዚህ በሁዋላ ቅዱስ ሐናንያ ለብዙ ዓመታት በተለያዩ የዓለም ክፍሎች ወንጌልን አስተማረ መከራንም ተቀበለ:: በመጨረሻም በዚህ ቀን ክፉዎች ከብዙ ስቃይ በሁዋላ በድንጋይ ወግረው ገድለውታል::
=>አምላከ አብርሃ ወአጽብሃ "ድሃ ተበደለ: ፍርድ ተጉዋደለ" የሚል ዳኛ: ሃይማኖቱ የቀና መሪንም ያምጣልን:: የቅዱሳኑን ክብር በእኛ ላይ ያድርግልን::
=>ጥቅምት 4 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.ቅዱሳን ነገሥት አብርሃ ወአጽብሃ
2.ቅዱስ ሐናንያ ሐዋርያ (ከ72ቱ አርድእት)
3.ቅዱስ በርተሎሜዎስ ሐዋርያ
4.ቅዱስ ባኮስ ሰማዕት
5.ቅዱሳን ባባ እና ማማ
6.ቅዱስ ዮሐንስ ሕጽው
=>ወርኀዊ በዓላት
1.ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ
2.ቅዱስ እንድርያስ ሐዋርያ
3.ቅድስት ሶፍያ ሰማዕት
4.ቅዱስ ዮሐንስ ዘሐራቅሊ (ሰማዕት)
=>+"+ እንግዲህ እግዚአብሔርን በመምሰልና በጭምትነት ሁሉ: ጸጥና ዝግ ብለን እንድንኖር: ልመናና ጸሎት: ምልጃም: ምስጋናም ስለ ሰዎች ሁሉ: ስለ ነገሥታትና መኩዋንንትም ሁሉ እንዲደረጉ ከሁሉ በፊት እመክራለሁ:: ሰዎች ሁሉ ሊድኑና እውነቱን ወደ ማወቅ ሊደርሱ በሚወድ በእግዚአብሔር በመድኃኒታችን ፊት መልካምና ደስ የሚያሰኝ ይህ ነው:: +"+ (1ጢሞ. 2:1-4)
††† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †††
Forwarded from ዝክረ ቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት - ዘብሔረ ጎንደር (ዲ/ዮርዳኖስ አበበ)
✞✞✞ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ ✞✞✞
❖ ጥቅምት ፭ (5) ❖
✞✞✞ እንኩዋን ለጻድቁ "አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ" እና "ቅዱስ ኪራኮስ አረጋዊ" ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ✞✞✞
+"+ አቡነ ገብረ ሕይወት +"+
=>ጻድቁ የተወለዱት ግብፅ (ንሒሳ አካባቢ) ሲሆን
አባታቸው ስምዖን እናታቸው አቅሌስያ ይባላሉ:: አባታችን
ገብረ ሕይወት የጻድቃን አለቃ: የቅዱሳን የበላይ:
ተጋድሎአቸውና ድንቅ ተአምራቸው እንደ ሰማይ
ከዋክብት የበዛ ቅዱስ ሰው ናቸው::
+የጻድቁን ክብር መናገር የሚችል ምን አነደበት
ይኖራል?
እንደ ምንስ ባለ ብራና ይጻፋል?
ዜናቸውንስ ለመስማት የታደለ እንደ ምን ዓይነት ሰው
ይሆን?
+አባታችን ገብረ መንፈስ ቅዱስ ለ562 ዓመታት በዚህች
ዓለም ሲኖሩ እህል ያልቀመሱ (ምግባቸው ምስጋና
ነውና): ልብስ ያልለበሱ (ጠጉር አካላቸውን ይሸፍን
ነበርና): ሐዋርያዊ ሆነው ከግብፅ እስከ ኢትዮዽያ ብዙ
ነፍሳትን ያዳኑ አባት: ሃገራችንን አስምረው: አስራት
እንድትሆናቸውም ተቀብለው ምድረ ከብድ አካባቢ
አርፈዋል::
+ጻድቁ ገብረ መንፈስ ቅዱስም: ገብረ ሕይወትም
ይባላሉ:: በ562 ዓመታት ሕይወታቸው እንደ ሐዋርያት
ከምድረ ግብጸ እስከ ኢትዮዽያ ወንጌልን ሰብከዋል::
በዚህም በሚሊየን (አእላፍ) ለሚቆጠሩ ነፍሳት የድኅነት
ምክንያት ሆነዋል::
+ጻድቁ እንደ ሰማዕታትም ከከሃዲ ሰዎች ብዙ መከራን
ተቀብለዋል:: እንደ ባሕታውያን ለብዙ መቶ ዓመታት ሰው
ሳያዩ ቆይተዋል:: ለየት የሚለው ግን የጽድቅ
ሕይወታቸው ነው:: ከእልፍ አዕላፍ አጋንንት ጋር
ተዋግተው ድል ማድረግ ችለዋልና::
+የንሒሳው ኮከብ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ለኢትዮዽያ ልዩ
ፍቀር አላቸው:: ስለ ሃገሪቱና ሕዝቧ ፍቅር ሲሉ ለ100
ዓመታት በደብረ ዝቁዋላ መከራን ተቀብለዋል:: ምሕረትን ሲለምኑ ሥጋቸው አልቆ በአጥንታቸው ቁመው
ነበርና ሃገራችን አሥራት ሆና ተሰጠቻቸው::
+ስለዚህም ነው በሃገሪቱ ውስጥ ከ2,000 በላይ የጻድቁ
አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳማትና አድባራት ዛሬም
ድረስ ያሉት:: በ8ኛው ክ/ዘመን አካባቢ የተወለዱት
አባታችን ያረፉት በ14ኛው መቶ ክ/ዘመን አካባቢ ነው::
ፍጥረታትን ሁሉ አዘው መጋቢት 5 ቀን ሲያርፉ ግሩማን
መላእክት ገንዘው አካላቸውን ሠውረዋል::
+ሥላሴን የተሸከመ አካላቸው በጐልጐታ ተቀብሯል
የሚሉም አሉ::
"ሰላም ለመቃብሪከ ዘኢተከሥተ ለባዕድ:
ከመ መቃብሩ ለሙሴ ወልደ ዮካብድ:
ዜና መቃብሪከሰ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ጸማድ:
ቦ ዘይቤ በኢየሩሳሌም አጸድ:
ወቦ ዘይቤ ኀለወ በከብድ::" እንዲል::
+የጻድቁ በዓል ጥቅምት 5 ቀን የሚከበረው ብዙ ጊዜ
መጋቢት 5 ዐቢይ ጾም ውስጥ ስለሚውል ተውላጥ
(ቅያሪ) ሆኖ ነው::
+"+ ቅዱስ ኪራኮስ አረጋዊ +"+
=>ይህ ቅዱስ አባት ስም አጠራሩ የከበረ:
ሽምግልናውም ያማረ ነው:: ብዙዎቻችን የምናውቀው
በበዓለ መስቀል ስሙ ተደጋግሞ ሲጠራ ነው:: ግን ይህ
ታላቅ ሰው ለቅድስት እሌኒ መካነ መስቀሉን አሳያት
ከሚል አረፍተ ነገር የዘለለ ታሪኩ ሲነገርለት ብዙ ጊዜ
አንሰማምና እስኪ በዕለተ ዕረፍቱ ስለ ቅዱሱ ጥቂት
እንበል::
+ቅዱስ ኪራኮስ የተወለደው በ3ኛው መቶ ክ/ዘመን
ሲሆን እናቱ ቅድስት ሐና ትባላለች:: በእጅጉ የተባረከች
ሴት ናት:: ምንም በነገዳቸው አይሁድ ቢሆኑም የዘመኑ
የአይሁድ ክፋት አልገዛቸውም:: የተባረከች እናቱ ታሪክ
እያስጠናች ከማሳደጉዋ ባለፈ አስቀድማ ኦሪቱን:
ነቢያቱን እንዲያውቅ አደረገች::
+አስከትላም ሕገ ክርስትናን እንዲረዳ አደረገችው::
የታሪክና የመጻሕፍት ምሑሩ ቅዱስ ኪራኮስ ከእናቱ ጋር
ሆኖ እግዚአብሔርን እያገለገለ: ክርስቶስን እያመለከ
ቆየ:: በዚህ ጊዜ ግን እድሜው እየገፋ ነበር::
+ሠለስቱ ምዕት (318ቱ ሊቃውንት) ጉባኤያቸውን
ከፈጸሙ በሁዋላ ቅድስት እሌኒም መስቀሉን ፍለጋ
ስትወጣ ትልቁ ፈተናዋ የተቀበረበትን ቦታ ማወቅ
አለመቻሏ ነበር:: እንዲያውም አማራጭ ስታጣ
በአካባቢው የነበሩ አይሁድን ምሥጢር እንዲያወጡ
ቀጥታቸው ነበር:: በሁዋላ ግን ኪራኮስ ስለሚባል ደግ
ታሪክ አዋቂ ሰው ሰምታ ተገናኙ::
+ቅዱስ ኪራኮስም አባቶቹ አይሁድ ናቸውና አካባቢውን
ያውቀው ነበር:: ችግሩ ቆሻሻው ተራራ በመሆኑ ከ3ቱ
የትኛው እንደ ሆነ አለመታወቁ ነበር:: ቅዱሱ ግን
ለዚህም መፍትሔ ነበረውና "ደመራ ደምረሽ: በእሳት
አቃጥለሽ: እጣን ጨምሪበትና ይገለጥልሻል" አላት::
+ቅድስት እሌኒም የተባለችውን በትክክል ፈጽማ
የመድኅን ክርስቶስን ቅዱስ ዕጸ መስቀል አገኘች::
ቅድስት እሌኒ ወደ ሃገሯ ከተመለሰች በሁዋላም ቅዱስ
ኪራኮስ በኢየሩሳሌም አካባቢ ዻዻስ ሆኖ ተሾመ::
+አረጋዊው ቅዱስ የሚገርም እረኛ ነውና የባዘኑትን
ሲፈልግ: በቤቱ ያሉትንም ሲያጸና ብዙ ደከመ:: በቅርቡ
ያሉትን በአፉ: የራቁትን ደግሞ በጦማር (በመልእክት)
አስተማረ:: በወቅቱ በአካባቢው ኤልያኖስ የሚሉት ከሃዲ
ንጉሥ ነበርና በቅዱስ ኪራኮስ ላይ ተቆጣ::
+ወደ እርሱ አስጠርቶ በአደባባይ: ቅዱስ ቃሉን ይጽፍበት
የነበረው ቀኝ እጁን አስቆረጠው:: ቅዱስ ኪራኮስ ግን
እጁ መሬት ላይ ወድቃ: ደሙ እየተንጠፈጠፈ ተናገረ:-
"አንተ ልብ የሌለህ ንጉሥ! እጄን ቆርጠህ ከክርስቶስ
ፍቅር ልትለየኝ አትችልም" አለው::
+በዚህ የተበሳጨ ንጉሡ እሳት አስነድዶ: አልጋውን
አግሎ ቅዱሱን ጠበሰው:: ኪራኮስ ግን በእሳቱ ላይ ሳለ
ወደ እሥራኤል ፈጣሪ በእብራይስጥኛ ጸለየ:: በማግስቱ
እናቱን ቅድስት ሐናን አምጥተው የነደደ እሳት ውስጥ
ጣሏት::
+ለ3 ሰዓት ያህል በእሳት ውስጥ ስትጸልይ ቆይታ በጦር
ወግተው ገደሏት:: ቅዱስ ኪራኮስንም ለአራዊት ሰጡት::
አራዊቱ ሰገዱለት:: በሌሎች ዓይነት ስቃዮችም ፈተኑት:
ግን እንቢ አላቸው:: በመጨረሻው በዚህ ቀን ገድለውት
የክብርን አክሊል ተቀዳጅቷል::
=>አምላከ ቅዱሳን በእነርሱ ላይ የበዛች ፍቅሩን ለእኛም
ያድለን:: ፍሬ ትሩፋት: ፍሬ ክብር እንድናፈራም ይርዳን::
ክብራቸውንም አያጉድልብን::
=>ጥቅምት 5 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ጻድቅ
2.ቅዱስ ኪራኮስ አረጋዊ (ዻዻስ ወሰማዕት)
3.ቅድስት ሐና ሰማዕት (እናቱ)
4.ቅዱስ ያዕቆብ ወልደ እልፍዮስ (ከ12ቱ ሐዋርያት)
5.አባ ዻውሎስ ሰማዕት (አርዮሳውያን አንቀው የገደሉት አባት)
=>ወርሐዊ በዓላት
1.ቅዱስ ዼጥሮስ ሊቀ ሐዋርያት
2.ቅዱስ ዻውሎስ ብርሃነ ዓለም
3.ቅዱስ ዮሐኒ ኢትዮዽያዊ
4.ቅዱስ አሞኒ ዘናሒሶ
5.ቅድስት አውጋንያ (ሰማዕትና ጻድቅ)
=>+"+ ነገር ግን ዓለም ለእኔ የተሰቀለበት: እኔም
ለዓለም የተሰቀልሁበት ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ
መስቀል በቀር ሌላ ትምክህት ከእኔ ይራቅ:: በክርስቶስ
ኢየሱስ አዲስ ፍጥረት መሆን ይጠቅማል እንጂ መገረዝ
ቢሆን ወይም አለመገረዝ አይጠቅምምና:: +"+ (ገላ. 6:14)
<<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >>>
❖ ጥቅምት ፭ (5) ❖
✞✞✞ እንኩዋን ለጻድቁ "አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ" እና "ቅዱስ ኪራኮስ አረጋዊ" ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ✞✞✞
+"+ አቡነ ገብረ ሕይወት +"+
=>ጻድቁ የተወለዱት ግብፅ (ንሒሳ አካባቢ) ሲሆን
አባታቸው ስምዖን እናታቸው አቅሌስያ ይባላሉ:: አባታችን
ገብረ ሕይወት የጻድቃን አለቃ: የቅዱሳን የበላይ:
ተጋድሎአቸውና ድንቅ ተአምራቸው እንደ ሰማይ
ከዋክብት የበዛ ቅዱስ ሰው ናቸው::
+የጻድቁን ክብር መናገር የሚችል ምን አነደበት
ይኖራል?
እንደ ምንስ ባለ ብራና ይጻፋል?
ዜናቸውንስ ለመስማት የታደለ እንደ ምን ዓይነት ሰው
ይሆን?
+አባታችን ገብረ መንፈስ ቅዱስ ለ562 ዓመታት በዚህች
ዓለም ሲኖሩ እህል ያልቀመሱ (ምግባቸው ምስጋና
ነውና): ልብስ ያልለበሱ (ጠጉር አካላቸውን ይሸፍን
ነበርና): ሐዋርያዊ ሆነው ከግብፅ እስከ ኢትዮዽያ ብዙ
ነፍሳትን ያዳኑ አባት: ሃገራችንን አስምረው: አስራት
እንድትሆናቸውም ተቀብለው ምድረ ከብድ አካባቢ
አርፈዋል::
+ጻድቁ ገብረ መንፈስ ቅዱስም: ገብረ ሕይወትም
ይባላሉ:: በ562 ዓመታት ሕይወታቸው እንደ ሐዋርያት
ከምድረ ግብጸ እስከ ኢትዮዽያ ወንጌልን ሰብከዋል::
በዚህም በሚሊየን (አእላፍ) ለሚቆጠሩ ነፍሳት የድኅነት
ምክንያት ሆነዋል::
+ጻድቁ እንደ ሰማዕታትም ከከሃዲ ሰዎች ብዙ መከራን
ተቀብለዋል:: እንደ ባሕታውያን ለብዙ መቶ ዓመታት ሰው
ሳያዩ ቆይተዋል:: ለየት የሚለው ግን የጽድቅ
ሕይወታቸው ነው:: ከእልፍ አዕላፍ አጋንንት ጋር
ተዋግተው ድል ማድረግ ችለዋልና::
+የንሒሳው ኮከብ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ለኢትዮዽያ ልዩ
ፍቀር አላቸው:: ስለ ሃገሪቱና ሕዝቧ ፍቅር ሲሉ ለ100
ዓመታት በደብረ ዝቁዋላ መከራን ተቀብለዋል:: ምሕረትን ሲለምኑ ሥጋቸው አልቆ በአጥንታቸው ቁመው
ነበርና ሃገራችን አሥራት ሆና ተሰጠቻቸው::
+ስለዚህም ነው በሃገሪቱ ውስጥ ከ2,000 በላይ የጻድቁ
አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳማትና አድባራት ዛሬም
ድረስ ያሉት:: በ8ኛው ክ/ዘመን አካባቢ የተወለዱት
አባታችን ያረፉት በ14ኛው መቶ ክ/ዘመን አካባቢ ነው::
ፍጥረታትን ሁሉ አዘው መጋቢት 5 ቀን ሲያርፉ ግሩማን
መላእክት ገንዘው አካላቸውን ሠውረዋል::
+ሥላሴን የተሸከመ አካላቸው በጐልጐታ ተቀብሯል
የሚሉም አሉ::
"ሰላም ለመቃብሪከ ዘኢተከሥተ ለባዕድ:
ከመ መቃብሩ ለሙሴ ወልደ ዮካብድ:
ዜና መቃብሪከሰ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ጸማድ:
ቦ ዘይቤ በኢየሩሳሌም አጸድ:
ወቦ ዘይቤ ኀለወ በከብድ::" እንዲል::
+የጻድቁ በዓል ጥቅምት 5 ቀን የሚከበረው ብዙ ጊዜ
መጋቢት 5 ዐቢይ ጾም ውስጥ ስለሚውል ተውላጥ
(ቅያሪ) ሆኖ ነው::
+"+ ቅዱስ ኪራኮስ አረጋዊ +"+
=>ይህ ቅዱስ አባት ስም አጠራሩ የከበረ:
ሽምግልናውም ያማረ ነው:: ብዙዎቻችን የምናውቀው
በበዓለ መስቀል ስሙ ተደጋግሞ ሲጠራ ነው:: ግን ይህ
ታላቅ ሰው ለቅድስት እሌኒ መካነ መስቀሉን አሳያት
ከሚል አረፍተ ነገር የዘለለ ታሪኩ ሲነገርለት ብዙ ጊዜ
አንሰማምና እስኪ በዕለተ ዕረፍቱ ስለ ቅዱሱ ጥቂት
እንበል::
+ቅዱስ ኪራኮስ የተወለደው በ3ኛው መቶ ክ/ዘመን
ሲሆን እናቱ ቅድስት ሐና ትባላለች:: በእጅጉ የተባረከች
ሴት ናት:: ምንም በነገዳቸው አይሁድ ቢሆኑም የዘመኑ
የአይሁድ ክፋት አልገዛቸውም:: የተባረከች እናቱ ታሪክ
እያስጠናች ከማሳደጉዋ ባለፈ አስቀድማ ኦሪቱን:
ነቢያቱን እንዲያውቅ አደረገች::
+አስከትላም ሕገ ክርስትናን እንዲረዳ አደረገችው::
የታሪክና የመጻሕፍት ምሑሩ ቅዱስ ኪራኮስ ከእናቱ ጋር
ሆኖ እግዚአብሔርን እያገለገለ: ክርስቶስን እያመለከ
ቆየ:: በዚህ ጊዜ ግን እድሜው እየገፋ ነበር::
+ሠለስቱ ምዕት (318ቱ ሊቃውንት) ጉባኤያቸውን
ከፈጸሙ በሁዋላ ቅድስት እሌኒም መስቀሉን ፍለጋ
ስትወጣ ትልቁ ፈተናዋ የተቀበረበትን ቦታ ማወቅ
አለመቻሏ ነበር:: እንዲያውም አማራጭ ስታጣ
በአካባቢው የነበሩ አይሁድን ምሥጢር እንዲያወጡ
ቀጥታቸው ነበር:: በሁዋላ ግን ኪራኮስ ስለሚባል ደግ
ታሪክ አዋቂ ሰው ሰምታ ተገናኙ::
+ቅዱስ ኪራኮስም አባቶቹ አይሁድ ናቸውና አካባቢውን
ያውቀው ነበር:: ችግሩ ቆሻሻው ተራራ በመሆኑ ከ3ቱ
የትኛው እንደ ሆነ አለመታወቁ ነበር:: ቅዱሱ ግን
ለዚህም መፍትሔ ነበረውና "ደመራ ደምረሽ: በእሳት
አቃጥለሽ: እጣን ጨምሪበትና ይገለጥልሻል" አላት::
+ቅድስት እሌኒም የተባለችውን በትክክል ፈጽማ
የመድኅን ክርስቶስን ቅዱስ ዕጸ መስቀል አገኘች::
ቅድስት እሌኒ ወደ ሃገሯ ከተመለሰች በሁዋላም ቅዱስ
ኪራኮስ በኢየሩሳሌም አካባቢ ዻዻስ ሆኖ ተሾመ::
+አረጋዊው ቅዱስ የሚገርም እረኛ ነውና የባዘኑትን
ሲፈልግ: በቤቱ ያሉትንም ሲያጸና ብዙ ደከመ:: በቅርቡ
ያሉትን በአፉ: የራቁትን ደግሞ በጦማር (በመልእክት)
አስተማረ:: በወቅቱ በአካባቢው ኤልያኖስ የሚሉት ከሃዲ
ንጉሥ ነበርና በቅዱስ ኪራኮስ ላይ ተቆጣ::
+ወደ እርሱ አስጠርቶ በአደባባይ: ቅዱስ ቃሉን ይጽፍበት
የነበረው ቀኝ እጁን አስቆረጠው:: ቅዱስ ኪራኮስ ግን
እጁ መሬት ላይ ወድቃ: ደሙ እየተንጠፈጠፈ ተናገረ:-
"አንተ ልብ የሌለህ ንጉሥ! እጄን ቆርጠህ ከክርስቶስ
ፍቅር ልትለየኝ አትችልም" አለው::
+በዚህ የተበሳጨ ንጉሡ እሳት አስነድዶ: አልጋውን
አግሎ ቅዱሱን ጠበሰው:: ኪራኮስ ግን በእሳቱ ላይ ሳለ
ወደ እሥራኤል ፈጣሪ በእብራይስጥኛ ጸለየ:: በማግስቱ
እናቱን ቅድስት ሐናን አምጥተው የነደደ እሳት ውስጥ
ጣሏት::
+ለ3 ሰዓት ያህል በእሳት ውስጥ ስትጸልይ ቆይታ በጦር
ወግተው ገደሏት:: ቅዱስ ኪራኮስንም ለአራዊት ሰጡት::
አራዊቱ ሰገዱለት:: በሌሎች ዓይነት ስቃዮችም ፈተኑት:
ግን እንቢ አላቸው:: በመጨረሻው በዚህ ቀን ገድለውት
የክብርን አክሊል ተቀዳጅቷል::
=>አምላከ ቅዱሳን በእነርሱ ላይ የበዛች ፍቅሩን ለእኛም
ያድለን:: ፍሬ ትሩፋት: ፍሬ ክብር እንድናፈራም ይርዳን::
ክብራቸውንም አያጉድልብን::
=>ጥቅምት 5 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ጻድቅ
2.ቅዱስ ኪራኮስ አረጋዊ (ዻዻስ ወሰማዕት)
3.ቅድስት ሐና ሰማዕት (እናቱ)
4.ቅዱስ ያዕቆብ ወልደ እልፍዮስ (ከ12ቱ ሐዋርያት)
5.አባ ዻውሎስ ሰማዕት (አርዮሳውያን አንቀው የገደሉት አባት)
=>ወርሐዊ በዓላት
1.ቅዱስ ዼጥሮስ ሊቀ ሐዋርያት
2.ቅዱስ ዻውሎስ ብርሃነ ዓለም
3.ቅዱስ ዮሐኒ ኢትዮዽያዊ
4.ቅዱስ አሞኒ ዘናሒሶ
5.ቅድስት አውጋንያ (ሰማዕትና ጻድቅ)
=>+"+ ነገር ግን ዓለም ለእኔ የተሰቀለበት: እኔም
ለዓለም የተሰቀልሁበት ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ
መስቀል በቀር ሌላ ትምክህት ከእኔ ይራቅ:: በክርስቶስ
ኢየሱስ አዲስ ፍጥረት መሆን ይጠቅማል እንጂ መገረዝ
ቢሆን ወይም አለመገረዝ አይጠቅምምና:: +"+ (ገላ. 6:14)
<<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >>>
እንኳን ለአጋእዝተ ዓለም ሥላሴ እና ለቅዱሳን አበው አብርሃም ወርሀዊ መታሰቢያ በአል አደረሳችሁ
ሥሉስ ቅዱስ
በአንድነቱ ምንታዌ (ሁለትነት): በሦስትነቱ ርባዔ (አራትነት) የሌለበት የዘለዓለም አምላክ: የፍጥረታት ሁሉ ፈጣሪ እግዚአብሔር ነው:: አብ :ወልድ : መንፈስ ቅዱስ በስም: በአካል: በግብር ሦስትነት: በባሕርይ: በሕልውናና በፈቃድ አንድነት የጸኑ ናቸው:: በዚህ ጊዜ ተገኙ: በዚህ ጊዜ ያልፋሉ አይባሉም:: መጀመሪያም መጨረሻም እነርሱ ናቸውና::
ርሕሩሐን ናቸውና በእናት ሥርዓት "ቅድስት ሥላሴ" እንላቸዋለን:: የሚጠላቸው (የማያምንባቸውን) አይጠሉም:: የሚወዳቸውን ግን እጽፍ ድርብ ይወዱታል:: በቤቱም መጥተው
ያድራሉ::
ከፍጥረታት ወገን ከእመቤታችን ቀጥሎ የአብርሃምን ያህል በሥላሴ ዘንድ የተወደደ ፍጡር የለም:: አባታችን ቅዱስ አብርሃም የደግነት ሁሉ አባት ነውና በኬብሮን በመምሬ ዛፍ ሥር ሥላሴን ተቀብሎ አስተናግዷል:: ሥላሴ አኀዜ ዓለም (ዓለምን በእጁ የያዘ) ነው:: ነገር ግን በፍቅር ለሚሻው በፍቅር ይመጣል::
አባታችን አብርሃም በ99 ዓመቱ: እናታችን ሣራ በ89 ዓመቷ ሥላሴን በድንኩዋናቸው አስተናገዱ:: አብርሃም እግራቸውን አጠበ:: (ወይ መታደል!) በጀርባውም አዘላቸው:: (ድንቅ አባት!) ምሳቸውንም አቀረበላቸው:: እንደሚበሉ ሆኑለት:: በዚያው ዕለትም የይስሐቅን መወለድ አበሠሩት:: ቅድስት ሣራ ሳቀች::
እንደ ዘንድሮ ወገኖቻችን የማሾፍ አይደለም:: ደስታና ጉጉት የፈጠረው እንጂ:: ሥላሴ "ምንት አስሐቃ ለሣራ በባሕቲታ" ብለው ነበርና በዚህም ምክንያት ነው "ይስሐቅ" የተባለው::
@Leoulu
ሥላሴን ያስተናገደች ድንኩዋን (ሐይመት) የድንግል እመቤታችን ማርያም ምሳሌ ናት:: በድንግል ላይ አብ ለአጽንኦ: መንፈስ ቅዱስ ለአንጽሖ: ወልድ በተለየ አካሉ ለሥጋዌ በእርሷ ላይ አርፈዋል / አድረዋልና::
ሐምሌ 7 ሥሉስ ቅዱስ ለአብርሃም የተገለጠለት በቤቱም የተስተናገዱበት ዕለት ነው ፣ይህም ስለሆነ እኛ ኦርቶዶክሳውያን ይህን የተባረከ እለት በአለ ሥላሴ ብለን በየወሩ ወር በገባ 7 ቀን አክብረን :በስማቸው ዘክረን በረከት ተቀብለን ፣እናሳልፋለን !
@Leoulu
@Leoulu
ሥሉስ ቅዱስ
በአንድነቱ ምንታዌ (ሁለትነት): በሦስትነቱ ርባዔ (አራትነት) የሌለበት የዘለዓለም አምላክ: የፍጥረታት ሁሉ ፈጣሪ እግዚአብሔር ነው:: አብ :ወልድ : መንፈስ ቅዱስ በስም: በአካል: በግብር ሦስትነት: በባሕርይ: በሕልውናና በፈቃድ አንድነት የጸኑ ናቸው:: በዚህ ጊዜ ተገኙ: በዚህ ጊዜ ያልፋሉ አይባሉም:: መጀመሪያም መጨረሻም እነርሱ ናቸውና::
ርሕሩሐን ናቸውና በእናት ሥርዓት "ቅድስት ሥላሴ" እንላቸዋለን:: የሚጠላቸው (የማያምንባቸውን) አይጠሉም:: የሚወዳቸውን ግን እጽፍ ድርብ ይወዱታል:: በቤቱም መጥተው
ያድራሉ::
ከፍጥረታት ወገን ከእመቤታችን ቀጥሎ የአብርሃምን ያህል በሥላሴ ዘንድ የተወደደ ፍጡር የለም:: አባታችን ቅዱስ አብርሃም የደግነት ሁሉ አባት ነውና በኬብሮን በመምሬ ዛፍ ሥር ሥላሴን ተቀብሎ አስተናግዷል:: ሥላሴ አኀዜ ዓለም (ዓለምን በእጁ የያዘ) ነው:: ነገር ግን በፍቅር ለሚሻው በፍቅር ይመጣል::
አባታችን አብርሃም በ99 ዓመቱ: እናታችን ሣራ በ89 ዓመቷ ሥላሴን በድንኩዋናቸው አስተናገዱ:: አብርሃም እግራቸውን አጠበ:: (ወይ መታደል!) በጀርባውም አዘላቸው:: (ድንቅ አባት!) ምሳቸውንም አቀረበላቸው:: እንደሚበሉ ሆኑለት:: በዚያው ዕለትም የይስሐቅን መወለድ አበሠሩት:: ቅድስት ሣራ ሳቀች::
እንደ ዘንድሮ ወገኖቻችን የማሾፍ አይደለም:: ደስታና ጉጉት የፈጠረው እንጂ:: ሥላሴ "ምንት አስሐቃ ለሣራ በባሕቲታ" ብለው ነበርና በዚህም ምክንያት ነው "ይስሐቅ" የተባለው::
@Leoulu
ሥላሴን ያስተናገደች ድንኩዋን (ሐይመት) የድንግል እመቤታችን ማርያም ምሳሌ ናት:: በድንግል ላይ አብ ለአጽንኦ: መንፈስ ቅዱስ ለአንጽሖ: ወልድ በተለየ አካሉ ለሥጋዌ በእርሷ ላይ አርፈዋል / አድረዋልና::
ሐምሌ 7 ሥሉስ ቅዱስ ለአብርሃም የተገለጠለት በቤቱም የተስተናገዱበት ዕለት ነው ፣ይህም ስለሆነ እኛ ኦርቶዶክሳውያን ይህን የተባረከ እለት በአለ ሥላሴ ብለን በየወሩ ወር በገባ 7 ቀን አክብረን :በስማቸው ዘክረን በረከት ተቀብለን ፣እናሳልፋለን !
@Leoulu
@Leoulu
መልካም አድርግና እርሳው...
ስላደርግኸው ስለዚህ ነገር ማንኛውንም ዓይነት ውዳሴም ሆነ ሙገሳ አትሻ። መልካም ያደረግህለት ሰው አንተ እንዳደረግህለት ለአንተ መልካም የሆነውን አጸፋ እንዲመልስልህ ወይም አንተ አንደተንከባከብከው እርሱም እንዲንከባከብህ አትጠብቅ።
መልካም ስታደርግ በምላሹ መልካም ዋጋ አገኛለሁ ብለህ በመጠበቅ ላለመሆኑ እርግጠኛ ሁን! መልካም የምታደርገው መልካም ማድርግን ስለምትወድ ወይም መልካም ከማድረግ መከልከል ስለማትችል ለመሆኑ እርግጠኛ ሁን። መልካም መሆን በውስጥህ ያለ ጠባይ ይሁን። መልካም ጠባይ እንደ መተንፈስ ምንም ዓይነት ጥረት የማይጠይቅ ግብታዊ ነገር ይሁን።
እንዲህ ያለውን ነገር የምትረሳው ከሆነ እግዚአብሔር በዚህ ምድርም ሆነ በሚመጣው ዓለም ያስታውስሃል። መልካም ማድረግህን የምታስታውሰውና በውስጥህ ይዘኸው የምትቆይ ከሆነ ግን ታጣዋለህ
ስላደርግኸው ስለዚህ ነገር ማንኛውንም ዓይነት ውዳሴም ሆነ ሙገሳ አትሻ። መልካም ያደረግህለት ሰው አንተ እንዳደረግህለት ለአንተ መልካም የሆነውን አጸፋ እንዲመልስልህ ወይም አንተ አንደተንከባከብከው እርሱም እንዲንከባከብህ አትጠብቅ።
መልካም ስታደርግ በምላሹ መልካም ዋጋ አገኛለሁ ብለህ በመጠበቅ ላለመሆኑ እርግጠኛ ሁን! መልካም የምታደርገው መልካም ማድርግን ስለምትወድ ወይም መልካም ከማድረግ መከልከል ስለማትችል ለመሆኑ እርግጠኛ ሁን። መልካም መሆን በውስጥህ ያለ ጠባይ ይሁን። መልካም ጠባይ እንደ መተንፈስ ምንም ዓይነት ጥረት የማይጠይቅ ግብታዊ ነገር ይሁን።
እንዲህ ያለውን ነገር የምትረሳው ከሆነ እግዚአብሔር በዚህ ምድርም ሆነ በሚመጣው ዓለም ያስታውስሃል። መልካም ማድረግህን የምታስታውሰውና በውስጥህ ይዘኸው የምትቆይ ከሆነ ግን ታጣዋለህ
