☝☝☝በማህበረሰብ ዉስጥ ነን!
ጅማ ዩኒቨርሲቲ መጋቢት 17/2013ዓ.ም
******************************
በአዌቱ መንደራ፣ በጊንጆ ጉዱሩ እና በበቾ ቦሬ ቀበሌ ለማህበረሰቡ አግልግሎት የሚሰጡ ልዩ ልዩ ፐሮጄክቶች በጅማ ዩኒቨርሲቲ የድህረ-ምረቃ ተማሪዎች ተገንብተው ለህብረተሰቡ ተላለፉ፡፡
ዩኒቨርሲቲያችን በህብረተሰብ አቀፍ ትምህርት የካበተ የብዙ አመታት ልምድና ክህሎት ባለቤት ነዉ፡፡
በመሆኑም፣ ዕድገት ተኮር የቡድን ስልጠና (DTTP) መርሃ ግብር በድህረ-ምረቃ ተማሪዎች የሚተገበር የህብረተሰብ አቀፍ ትምህርትን ከግብ ማድረሻ መንገዶች አንደኛዉ ነዉ፡፡
በተለይም፣ DTTP እና ሌሎች ተግባራት የማህበረሰባችንን ችግር መለየት ብቻ ሳይሆን ችግሩን መመርመር እና የመፍትሄ አካል መሆንን ዋነኛ ግባቸው ነው፡፡፡፡
በዕደገት ተኮር የቡድን ስልጠና እዉን የሆኑ ፕሮጀክቶች የማህበረሰቡን ችግር ከመፍታት እና ማቃለል አንፃር ሚናቸዉ ከፍ ያለ ነዉ፡፡
ባሳለፍነዉ ሳምንት ለማህበረሰቡ ከተላለፉ ፕሮጀክቶች መካከል በአዌቱ መንደራ ቀበሌ ለአካል ጉዳተኞች የሻወር (ገላ መታጠቢያ) እና መፀዳጃ አገልግሎት የሚሰጥ፣ ከመኖሪያ አካባቢያቸዉ ተፈናቅለዉ በአሁኑ ግዜ በጊንጆ ጉዱሩ ቀበሌ ለሚገኙ ዜጎች የምግብ ማብሰያ ቤት እና በበቾ ቦሬ ቀበሌ ተገንብቶ ለህብረተሰቡ የተላለፈ የጤና ኬላ ዋና ዋናዎቹ ናቸዉ፡፡
እንዚህ ፕሮጀክቶች የማህበረሰባችንን የጤና ችግሮች ከመቅረፍና የጤና አገልግሎትን ተደራሽ ከማድረግ፣ እንዲሁም በምግብ ማብሰል ሂደት የሚፈስሰውን ጉልበት ከመቀነስና ለአካል ጉዳተኞችና ዜጎች ምቹ ሁኔታን ከመፍጠር አኳያ ያላቸዉ ሚና ከፍተኛ ነዉ፡፡
ጅማ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ችግሮች ለመቅረፍ የሚያደርገዉን ጥረት በምርምር፣ በፈጠራ እና በቴክኖሎጂ በማገዝ እየተንቀሳቀሰ ይገኛል፡፡
ጅማ ዩኒቨርሲቲ መጋቢት 17/2013ዓ.ም
******************************
በአዌቱ መንደራ፣ በጊንጆ ጉዱሩ እና በበቾ ቦሬ ቀበሌ ለማህበረሰቡ አግልግሎት የሚሰጡ ልዩ ልዩ ፐሮጄክቶች በጅማ ዩኒቨርሲቲ የድህረ-ምረቃ ተማሪዎች ተገንብተው ለህብረተሰቡ ተላለፉ፡፡
ዩኒቨርሲቲያችን በህብረተሰብ አቀፍ ትምህርት የካበተ የብዙ አመታት ልምድና ክህሎት ባለቤት ነዉ፡፡
በመሆኑም፣ ዕድገት ተኮር የቡድን ስልጠና (DTTP) መርሃ ግብር በድህረ-ምረቃ ተማሪዎች የሚተገበር የህብረተሰብ አቀፍ ትምህርትን ከግብ ማድረሻ መንገዶች አንደኛዉ ነዉ፡፡
በተለይም፣ DTTP እና ሌሎች ተግባራት የማህበረሰባችንን ችግር መለየት ብቻ ሳይሆን ችግሩን መመርመር እና የመፍትሄ አካል መሆንን ዋነኛ ግባቸው ነው፡፡፡፡
በዕደገት ተኮር የቡድን ስልጠና እዉን የሆኑ ፕሮጀክቶች የማህበረሰቡን ችግር ከመፍታት እና ማቃለል አንፃር ሚናቸዉ ከፍ ያለ ነዉ፡፡
ባሳለፍነዉ ሳምንት ለማህበረሰቡ ከተላለፉ ፕሮጀክቶች መካከል በአዌቱ መንደራ ቀበሌ ለአካል ጉዳተኞች የሻወር (ገላ መታጠቢያ) እና መፀዳጃ አገልግሎት የሚሰጥ፣ ከመኖሪያ አካባቢያቸዉ ተፈናቅለዉ በአሁኑ ግዜ በጊንጆ ጉዱሩ ቀበሌ ለሚገኙ ዜጎች የምግብ ማብሰያ ቤት እና በበቾ ቦሬ ቀበሌ ተገንብቶ ለህብረተሰቡ የተላለፈ የጤና ኬላ ዋና ዋናዎቹ ናቸዉ፡፡
እንዚህ ፕሮጀክቶች የማህበረሰባችንን የጤና ችግሮች ከመቅረፍና የጤና አገልግሎትን ተደራሽ ከማድረግ፣ እንዲሁም በምግብ ማብሰል ሂደት የሚፈስሰውን ጉልበት ከመቀነስና ለአካል ጉዳተኞችና ዜጎች ምቹ ሁኔታን ከመፍጠር አኳያ ያላቸዉ ሚና ከፍተኛ ነዉ፡፡
ጅማ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ችግሮች ለመቅረፍ የሚያደርገዉን ጥረት በምርምር፣ በፈጠራ እና በቴክኖሎጂ በማገዝ እየተንቀሳቀሰ ይገኛል፡፡
👆👆👆እንኳን ደህና መጣችሁ!
ጅማ ዩኒቨርሲቲ መጋቢት 19/2013ዓ.ም
***************************
ከዛሬ ጀምሮ ለሁለት ቀናት የሚቆይ በአካል ጉዳተኝነት ላይ ግንዛቤ ለማስጨበጥ ያለመ ስልጠና እየተሰጠ ነዉ፡፡
ስልጠናዉ ለዩኒቨርሲቲዉ አመራር አካላት እና በተማሪዎች ካዉንስል ስር ያሉ ክለቦችን ለሚመሩ ተማሪዎች ነዉ የሚሰጠዉ፡፡
ለጅማ ዩኒቨርሲቲ ጥበቃና ደህንነት ሰራተኞችም ተመሳሳይ ስልጠና ባለፉት ሁለት ቀናት ሲሰጥ ነበር፡፡
የስልጠናዎቹ ዓላማ፣ የሰልጣኞቹን በአካል ጉዳተኝነት ላይ ያላቸዉን ግንዛቤ በማጎልበት አካል ጉዳተኛ ተማሪዎችን የበለጠ እንዲረዱ በማስቻል ተማሪዎቹ እንደሌሎቹ ጉዳት አልባ ተማሪዎች ዉጤታማ እንዲሆኑ ለማስቻል እና ዩኒቨርሲቲዉን አካታች/inclusive የማድረግ ሂደትን ለመደገፍ ነዉ፡፡
በኮቪድ-19 ምክንያት የተቋረጠዉ ትምህርት ዳግም ሲጀመር በድጋሚ ወደ ዩኒቨርሲቲዉ የመጡ አካል ጉዳተኛ ተማሪዎች የእንኳን ደህና መጣችሁ ዝግጅት ተካሂዷል፡፡
በዝግጅቱ ላይ የልዩ ፍላጎት ትምህርት ክፍል ሃላፊ እና በጅማ ዩኒቨርሲቲ የECDD ፕሮጀክት አስተባባሪ አቶ ጃፋር ሎላ እንዳሉት የፕሮግራሙ ዓላማ አካል ጉዳተኛ ተማሪዎች መረጃዎችን በቀላሉ እንዲያገኙ ለማድረግ፣ በዩኒቨርሲቲዉ ያሉ አገልግሎቶች የት የት እንዳሉ እና ችግር ሲያጋጥማቸዉ ማንን ማነጋገር እንዳለባቸዉ እንዲሁም እርስ በእርስ እንዲተዋወቁ ለማድረግ ነዉ፡፡
ጅማ ዩኒቨርሲቲ ልዩ ፍላጎት ላላቸዉ ተማሪዎች አገልግሎት የሚያገኙበት ማዕከል ከፍቶ ወደ ስራ ከገባ ሰንበትበት ብሏል፡፡
አካል ጉዳተኛ ተማሪዎቹ በትምህርት ቆይታቸዉ ዉጤታማ እንዲሆኑና ምቹ ሁኔታ እንዲፈጠር የሚያግዙ የሳይኮ-ሶሻል እና ኮቪድ-19 ግንዛቤ የሚያስጨብጡ መልዕክቶች ቀርበዋል፡፡
(ኢትዮጵያን ሴንተር ፎር ዲስኤቢሊቲ ኤንድ ዴቨሎፕመንት) በጅማ ዩኒቨርሲቲ፣ ዲላ እና ደብረ ብርሀን ዩኒቨርሲቲዎች አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኝ ተቋም ነዉ፡፡
የECDD ተወካይ አቶ ዮሐንስ ተክላይ ላለፉት ሁለት አመታት አካል ጉዳተኛ ተማሪዎችን በቁሳቁስ እና ስልጠና በመስጠት ድጋፍ ሲያደርግ እንደቀየ ገልፀዉ ይህንኑ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል፡፡
የተቋሙ ድጋፍ በትምህርት ላይ ያሉ አካል ጉዳተኛ ተማሪዎች ከተመረቁም በኋላ የተሻለ ደረጃ እስኪደርሱ ቀጣይነት አለዉ ተብሏል፡፡
ጅማ ዩኒቨርሲቲ ለአካል ጉዳተኞች መገልገያ የሚሆን ልዩ ስፍራን በማዘጋጀቱ እንዲሁም ከበር ጀምሮ ለተማሪዎቹ ቅበላ የተደረገዉ ዝግጅትና አገልግሎት ምስጋና ተችሮታል፡፡
ጅማ ዩኒቨርሲቲ መጋቢት 19/2013ዓ.ም
***************************
ከዛሬ ጀምሮ ለሁለት ቀናት የሚቆይ በአካል ጉዳተኝነት ላይ ግንዛቤ ለማስጨበጥ ያለመ ስልጠና እየተሰጠ ነዉ፡፡
ስልጠናዉ ለዩኒቨርሲቲዉ አመራር አካላት እና በተማሪዎች ካዉንስል ስር ያሉ ክለቦችን ለሚመሩ ተማሪዎች ነዉ የሚሰጠዉ፡፡
ለጅማ ዩኒቨርሲቲ ጥበቃና ደህንነት ሰራተኞችም ተመሳሳይ ስልጠና ባለፉት ሁለት ቀናት ሲሰጥ ነበር፡፡
የስልጠናዎቹ ዓላማ፣ የሰልጣኞቹን በአካል ጉዳተኝነት ላይ ያላቸዉን ግንዛቤ በማጎልበት አካል ጉዳተኛ ተማሪዎችን የበለጠ እንዲረዱ በማስቻል ተማሪዎቹ እንደሌሎቹ ጉዳት አልባ ተማሪዎች ዉጤታማ እንዲሆኑ ለማስቻል እና ዩኒቨርሲቲዉን አካታች/inclusive የማድረግ ሂደትን ለመደገፍ ነዉ፡፡
በኮቪድ-19 ምክንያት የተቋረጠዉ ትምህርት ዳግም ሲጀመር በድጋሚ ወደ ዩኒቨርሲቲዉ የመጡ አካል ጉዳተኛ ተማሪዎች የእንኳን ደህና መጣችሁ ዝግጅት ተካሂዷል፡፡
በዝግጅቱ ላይ የልዩ ፍላጎት ትምህርት ክፍል ሃላፊ እና በጅማ ዩኒቨርሲቲ የECDD ፕሮጀክት አስተባባሪ አቶ ጃፋር ሎላ እንዳሉት የፕሮግራሙ ዓላማ አካል ጉዳተኛ ተማሪዎች መረጃዎችን በቀላሉ እንዲያገኙ ለማድረግ፣ በዩኒቨርሲቲዉ ያሉ አገልግሎቶች የት የት እንዳሉ እና ችግር ሲያጋጥማቸዉ ማንን ማነጋገር እንዳለባቸዉ እንዲሁም እርስ በእርስ እንዲተዋወቁ ለማድረግ ነዉ፡፡
ጅማ ዩኒቨርሲቲ ልዩ ፍላጎት ላላቸዉ ተማሪዎች አገልግሎት የሚያገኙበት ማዕከል ከፍቶ ወደ ስራ ከገባ ሰንበትበት ብሏል፡፡
አካል ጉዳተኛ ተማሪዎቹ በትምህርት ቆይታቸዉ ዉጤታማ እንዲሆኑና ምቹ ሁኔታ እንዲፈጠር የሚያግዙ የሳይኮ-ሶሻል እና ኮቪድ-19 ግንዛቤ የሚያስጨብጡ መልዕክቶች ቀርበዋል፡፡
(ኢትዮጵያን ሴንተር ፎር ዲስኤቢሊቲ ኤንድ ዴቨሎፕመንት) በጅማ ዩኒቨርሲቲ፣ ዲላ እና ደብረ ብርሀን ዩኒቨርሲቲዎች አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኝ ተቋም ነዉ፡፡
የECDD ተወካይ አቶ ዮሐንስ ተክላይ ላለፉት ሁለት አመታት አካል ጉዳተኛ ተማሪዎችን በቁሳቁስ እና ስልጠና በመስጠት ድጋፍ ሲያደርግ እንደቀየ ገልፀዉ ይህንኑ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል፡፡
የተቋሙ ድጋፍ በትምህርት ላይ ያሉ አካል ጉዳተኛ ተማሪዎች ከተመረቁም በኋላ የተሻለ ደረጃ እስኪደርሱ ቀጣይነት አለዉ ተብሏል፡፡
ጅማ ዩኒቨርሲቲ ለአካል ጉዳተኞች መገልገያ የሚሆን ልዩ ስፍራን በማዘጋጀቱ እንዲሁም ከበር ጀምሮ ለተማሪዎቹ ቅበላ የተደረገዉ ዝግጅትና አገልግሎት ምስጋና ተችሮታል፡፡