Information Science and Technology
16.1K subscribers
270 photos
24 videos
100 files
406 links
Information science is a field primarily concerned with the analysis, collection, classification, manipulation, storage, retrieval, movement, dissemination, and transfer of information.
Download Telegram
ውሾች መጥፎ ሰዎች መለየት እደሚችሉ ሳይንስ አረጋገጠ
ውሾች ጥሩ ሰውን ጥሩ ካልሆነ ሰው ሊለዩ እንደሚችሉ ሳይንስ አረጋግጧል። ሳይንስ እንደሚነግረን ውሾች አንድ ሰው ደግነት በጎደለው ጊዜ እንኳን ሳይቀር ሊገነዘቡት ይችላሉ ይላል። ብዙዎች ድመቶች ከውሾች የበለጠ አስተዋይ እንደሆኑ እና ውሾች እንደማንኛውም ሰው ናቸው ብለው ይከራከራሉ ፡ ይህ ጥናት ግን ይህ እውነት አይደለም ይላል፦
በኒውሮሳይንስ እና ባዮቤሃቪዮራል ሪቪውስ የተደረገ ጥናት እንደሚያሳየው ውሾች ጥሩ ሰውን ጥሩ ካልሆነ ሰው ሊለዩ ይችላሉ። በሙከራው ወቅት የውሾች ባለቤቶች ለመክፈት አስቸጋሪ የሆነ መያዣ ይሰጣችዋል ከዚያም የውሻች ባለቤቶች እርዳታ ለማግኘት ወደ ተመራማሪ ይሀዳሉ። ተመራማሪዎቹ አንድም
1. ተመራማሪዎቹ አንድም የውሻውን ባለቤት ረድተውታል
2. ግማሾቹ በስሜት ቆመው ይመለከታሉ
3. ሌሎች ተመራማሪዎች ሙሉ በሙሉ ለመርዳት ፈቃደኛ አልሆኑም ፡
በመቀጠልም ሁሉም ተመራማሪዎች ለውሾች ጥሩ ጣዕም ያልው ምግብ ይዘው ለመስጠት ይጠጋሉ። ከዚህም የተነሳ ውሾቹ ከአንድ አጋዥ ተመራማሪ ወይም እርዳታ ሲሰጥ ከነበረው ተመራማሪ መቀበልን ወይም መውሰድ እድላቸው ከፍተኛ የነበረ ሲሆን ነገር ግን ባለቤታቸውን ለመርዳት ፈቃደኛ ያልሆኑትን ተመራማሪዎች ችላ ብለዋል።
ጥናቱ በግልጽ እንደሚያሳየው ውሾች ሁልጊዜ የራሳቸውን ፍላጎት ጠብቀው የሚሠሩ አይደሉም። ብዚህም የተነሳ ውሾቹ ለባለቤታቸው ደግነት የጎደላቸው ተመራማሪዎች መሆናቸውን የልዩ ሲሆን ውሾቹ ከእነዚህ ተመራማሪዎች ጋር ምንም ኣይነት ግንኝነት ማድረግ እንደማይፈልጉ ተረዱ።
🔍🔍🔍🔍🔍▬▬ Share ▬▬🔎🔎🔎🔎🔎
ለተጨማሪ እውቀት እና ጠቃሚ የቴክኖሎጂ መረጃ ለማግኘት በዚ የቴሌግራም ቻናላችንን ከታች ባለዉን ሊንክ በመጫን ማግኘት ይችላሉ።
here it is

subscribe our You tube channel
https://www.youtube.com/channel/UCpKx7Pd_viT9nnmheRu6o8Q
┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈
ሼር እናድርግ
በአደጋ ምክንያት ለዓመታት ራሱን ስቶ የቆየው ሰው የ40 ዓመት ህይወቱን ረስቶ ተነሳ

የ63 ዓመት እድሜ ያለው ይህ ሰው ራሱን የሚያየው እንደ 24 ዓመት ጎረምሳ ነው

የ30 ዓመት እድሜ ልጅ እና የልጅ ልጅ ያለው ይህ ሰው በቴክኖሎጂዎች ፍጥነት በየዕለቱ እንደተገረመ ነው ተብሏል

በአደጋ ምክንያት ለዓመታት ራሱን ስቶ የቆየው ሰው የ40 ዓመት ህይወቱን ረስቶ ተነሳ፡፡

ሉሲያኖ የተባለው ጣልያናዊ አንድ ከአምስት አመት በፊት ነበር በደረሰበት የትራፊክ አደጋ ራሱን ስቶ ወደ ሆስፒታል የገባው፡፡

የ63 ዓመት እድሜ ያለው ይህ ሰውም ከሰሞኑ ለአምስት ዓመታት ራሱን ስቶ ከቆየ በኋላ ራሱን ሊያውቅ ችሏል፡፡

ይሁንና ይህ ሰው ሚስቱን እና የ30 ዓመት ጎረምሳ ልጁን ጨምሮ ከ1983 ወዲህ ያሉ የሕይወቱን ክስተቶች እንደማያስታውስ ተገልጿል፡፡

ሉሲያኖ ለመጀመሪያ ጊዜ ለዓመታት ከቆየበት የኮማ ህይወት ሲነቃ ሚስቱ ተጠርታ ስሙን ስትጠራው “ስሜን እንዴት አወቅሽ” ሲል መልሶ ጠይቋታል ተብሏል፡፡

አደጋው በደረሰበት ወቅት ባንድ ትምህርት ቤት ውስጥ ተቀጥሮ ሲሰራ ነበር የተባለ ሲሆን እሱ ግን የሚያስታውሰው ከ20 ዓመታት በፊት በጣልያን ኤርፖርት ውስጥ የቴክኒክ ባለሙያ ሆኖ ሲሰራ የነበረውን ስራ ብቻ እንደሚያስታውስ ዴይሊ ሜይል ዘግቧል፡፡

ሉሲያኖ በወጣትነት እድሜው የሚያስታውሳት እናቱን ስም እየጠራ የት ሄደች የሚል ጥያቄ ያቀርባል የተባለ ሲሆን እናቱ ግን ከዓመታት በፊት ህይወታቸው እንዳለፈ በስርዓተ ቀብራቸው ላይ መገኘቱን ሲነገረው ለማመን ይቸገራል ተብሏል፡፡

ይህ ሰው አሁን ዘመኑ 1983 እንጂ 2024 ነው ብሎ ለመቀበል ይቸገራል የተባለ ሲሆን እንደ ጎግል ማፕ፣ ሞባይል ስልክ እና ሌሎች ዘመን አመጣሽ ቴክኖሎጂዎችን ሲያይ ይህ እንዴት ሊሆን ቻለ በማለት እንደሚገረም ተገልጿል፡፡
አል ዓይን
የ93 አመት እድሜ ባለጸጋ አዛውንት በድንገት ራሳቸውን ይስቱና መተንፈስ አቅቷቸው ወደ ሆስፒታል ይወስዳሉ። እናም ለ 24 ሰዓታት ኦክስጅን ተሰጥቷቸው ይቆያሉ። ከጥቂት ሰዓት በኋላ ተሽሏቸው ወደቤታቸው እንዲመለሱ ተወሰነ። ዶክተሩም ‘’እስካሁን ለተደረገልዎት የህክምና እርዳታ 5000 ዶላር መክፈል ይጠበቅብዎታል’’ ይልና ሂሳቡን ያሳያቸዋል።

አዛውንቱም ሂሳቡን አይተው ማልቀስ ጀመሩ። ዶክተሩ በሂሳቡ ምክንያት ከሆነ እንዳያለቅሱ ነገራቸው። አዛውንቱ ግን "በገንዘብ ምክንያት አላለቅስም። ገንዘቡን በሙሉ መክፈል እችላለሁ። ያለቀስኩበት ምክንያት ለ 24 ሰአታት ኦክሲጅን በመጠቀሜ 5000 ዶላር መክፈል አለብህ አላችሁኝ። ነገር ግን 93 አመት ሙሉ ፈጣሪዬ የሰጠኝን አየር ስተነፍስ ቆይቻለሁ። ግን ይህን ያህል ዘመን ምንም አልከፍልም ነበር። ከፈጣሪዬ ምን ያህል ዕዳ እንዳለብኝ ታውቃለህ? ይህ ቸርነቱ ነው ያስለቀሰኝ።’’ ብለው መለሱለት።

ዶክተሩም አንገቱን ደፍቶ ስቅስቅ ብሎ ማልቀስ ጀመረ።

ይህን ለምታነቡ ሁሉ፣ ለፈጣሪ ምንም የምንከፍለው ነገር ሳይኖር ለዓመታት ነፃ አየር ስንተነፍስ ኖረናል፣ እንኖራለንም።

በህይወታችን ውስጥ ይህን ሁሉ በገንዘብ የማይተመን አገልግሎት በነፃ ለሰጠን ፈጣሪያችን 2 ሰከንድ ብቻ ወስደን ማመስገን ይከብደናል?

ፈጣሪያችንን እናመስግነው!
አቶ ታዲዮስ ታንቱ በ6 ዓመት ከ6 ወራት ጽኑ እስራትና በገንዘብ ተቀጡ
አቶ ታዲዮስ ታንቱ በ6 ዓመት ከ6 ወራት ጽኑ እስራትና በገንዘብ ተቀጡ
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 15፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የጥላቻ ንግግር ማሰራጨት እና ግጭት መቀስቀስ ወንጀል የተከሰሱትን አቶ ታዲዮስ ታንቱ በ6 ዓመት ከ6 ወራት ጽኑ እስራትና በገንዘብ ተቀጡ።
የፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ የህገ-መንግስትና ህገ መንግስታዊ ጉዳዮች ወንጀል ችሎት አቶ ታዲዮስ ታንቱን በተከሰሱበትና ጥፋተኝነት በተባሉባቸው 3 ክሶች ነው የጽኑ እስራትና የገንዘብ ቅጣት የጣለባቸው።
አቶ ታዲዮስ ታንቱ ሰኔ 20 ቀን 2014 ዓ.ም የጥላቻ ንግግር በማሰራጨት እና የእርስ በርስ ግጭት መቀስቀስ ወንጀል ፈጽመዋል ተብለው በፍትህ ሚኒስቴር በተደራጁና ድንበር ተሻጋሪ ጉዳዮች ዐቃቤ ሕግ በኩል ተደራራቢ አራት ክሶች ቀርቦባቸው እንደነበር ይታወሳል።
ዐቃቤ ሕግ ባቀረበው አንደኛው ክስ ላይ እንዳመላክተው በ1996 ዓ.ም የወጣውን የወንጀል ህግ አንቀጽ 32/(1)ሀ እና አንቀጽ 257/ሀ ስር የተደነገገውን በመተላለፍ ግንቦት 11 ቀን እና በመጋቢት 22 ቀን 2014 ዓ.ም እና በተለያዩ የዩቲዩብ ቻናሎች ህዝባዊ አመጽ መቀስቀስ ወንጀል የሚል ነው።
በ2ኛ ክስ በተመለከተ ደግሞ የጥላቻ ንግግርንና ሀሰተኛ መረጃን ስርጭትን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የወጣውን አዋጅ ቁ 1185/2012 አንቀጽ 4 እና 7/4 በመተላለፍ ታህሳስ 3 ቀን 2014 ዓ.ም በአንድ የዩቲዩብ ቻናል ሀሰተኛ መረጃ አሰራጭተዋል የሚል ክስ በዐቃቤ ሕግ ክስ ቀርቦባቸው ነበር።
በ3ኛ ክስ ደግሞ የወንጀል ህግ ከንቀጽ 32 /1ሀ ና አንቀጽ 337 በመተላለፍ የመከላከያ ሰራዊትን እቅስቃሴን ለማሰናከልና የመከላከል አደጋ እንዲደርስ ለማድረግ በማሰብ ሀሰተኛ ወሬ በመንዛት ቅስቀሳ ማድረግ ወንጀል የተከሰሱ ሲሆን በ4ኛ ክስ የኮምፒዩተር ወንጀል አዋጅ ቁ 958/2008 አንቀጽ 14 በመተላለፍ ህዝባዊ አመጽ እንዲፈጠር ቀስቃሽ መልዕክት በድምጽና በተቀሳቃሽ ምስል ተሰራጭቷል የሚል ክስ ቀርቦባቸው እንደነበር ይታወሳል።
በአጠቃላይ ዐቃቤ ሕግ ባቀረበባቸው አራት ክሶች ላይ የተጠቀሱትን የወንጀል ድርጊት አለመፈጸማቸውን ገልጸው፤ የሰጡትን የዕምነት ክህደት ቃል ተከትሎ ዐቃቤ ሕግ ለወንጀሉ መፈጸም ያስረዳሉ ያላቸውን ምስክሮችን አቅርቦ አሰምቷል።
ፍርድ ቤቱም የዐቃቤ ሕግ ምስክርን መርምሮ እንዲከላከሉ በሙሉ ድምጽ ብይን መስጠቱ ይታወሳል።
አቶ ታዲዮስ እንዲከላከሉ በተሰጠ ብይን መነሻ የተለያዩ የመከላከያ ምስክሮችን አቅርበው አሰምተው የነበሩ ቢሆንም ባቀረቡት የመከላከያ ማስረጃ ግን የዐቃቤ ሕግ ማስረጃን በተገቢው መከላከል (ማስተባበል) አለመቻላቸው ተገልጾ በ3 ክሶች የጥፋተኝነት ፍርድ ተላልፎባቸዋል።
ፍርድ ቤቱ የግራ ቀኝ የቅጣት አስተያየትን ለመጠባበቅ ጥቅምት 12 ቀን 2017 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቶ የነበረ ቢሆንም አቶ ታዲዮስ በዚህ እለት የቅጣት ማቅለያ ማቅረብ እንደማይፈልጉና የጥፋተኝነት ፍርዱን እንደማይቀበሉ ለችሎቱ አስታውቀው ነበር።
ይሁንና ፍርድ ቤቱ ግን የ6 ልጆች አባት መሆናቸውንና የ70 ዓመት አዛውንት መሆናቸውን ከግምት ውስጥ አስገብቶ ሁለት የቅጣት ማቅለያ በመያዝ በዕርከን 24 መሰረት በ6 ዓመት ከ6 ወራት ጽኑ እስራትና በ20 ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጡ ወስኗል።
የአዲስ አበባ ማረሚያ ቤት ተከሳሹ ላይ የተጣለውን ቅጣት እጃቸው ከተያዘበት ጊዜ ጀምሮ ታሳቢ በማድረግ እንዲያስፈጽም ታዟል።
ከኬጂ እስከ ዩኒቨርስቲ በጣም ቡዙ መፃህፍት የያዘ የቴሌግራም ቻነል https://t.me/Tigray_Digital_Library
በኢትዮጵያ 76 ከመቶ የሚሆነው ሕዝብ የሞባይል ኢንተርኔት እንደማይጠቀም አንድ ጥናት አመለከተ

ብቅ ባይ መስኮት የድምፅ መስምያ
በኢትዮጵያ የቴሌኮም አገልግሎት ላይ ጥናት ያደረገ፣ ግሎባል ሲስተምስ ፎር ሞባይል ኮሚኒኬሽንስ አሶስየሽን ወይም በምህፃሩ ጂኤስኤምኤ የተባለ ተቋም፣ 76 በመቶ የሚሆነው ህዝብ የሞባይል ኢንተርኔት ተጠቃሚ እንዳልሆነ አስታወቀ፡፡

ተቋሙ በዛሬው ዕለት ይፋ ባደረገው ሪፖርቱ፣ በኢትዮጵያ፣ ኢንተርኔትን መሰረት ያደረገ የዲጂታል አገልግሎት ለማግኘት፣ የስማርት ስልክ ቀፎዎች እጥረት አንዱ ችግር መሆኑን አመልክቷል፡፡

በጉዳዩ ላይ ለአሜሪካ ድምፅ አስተያየት የሰጡ የዘርፉ ባለሞያ ደግሞ፣ የቴሌኮም አገልግሎት አቅራቢዎቹ፣ ትኩረታቸውን በከተሞች ላይ ስለሚያደርጉ፣ በገጠር አካባቢ ይህ ችግር ሊፈጠር እንደሚችል ገልፀዋል፡፡

የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈፃሚ ፍሬህይወት ታምሩ በበኩላቸው በገጠር አካባቢዎች ያለውን የዲጂታል አገልግሎት ለማሻሻል፣ በዚህ ዓመት 250 ሺህ ስማርት የሞባይል ቀፎዎችን የማሰራጨት ዕቅድ መያዙን ገልፀዋል፡፡
Pi Mobile(π)
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
በዓለም ዙሪያ ያሉ ፓይ አቅኚዎች እ.ኤ.አ. በ2024 መጨረሻ ይደሰታሉ ይላል ቴስላ ስልክ ኣምራች። በዚህ ክፍለ ዘመን እጅግ የላቀው የቴስላ ስልክ ምርት የኤሎን ማስክ ንብረት የሆነው ብራንድ ፒ በ2024 መጨረሻ ላይ በገበያ ላይ ሊውል ነው። ቴስላ ፒ ስልክና ሌሎች ስማርትፎኖች የሌላቸው ባህሪያት፡-

1. ባትሪውን መሙላት አያስፈልግም, ምክንያቱም የፀሐይ ኃይልን ስለሚጠቀም, በራስ-ሰር ለመሙላት ብርሃን ብቻ ይፈልጋል (ለዛውም ለፀሐይ ብርሃን መጋለጥ ወይም ፀሃይ ብርሃን ባለበት ማስቀመጥ አያስፈልግም).

2.የኢንተርኔት ዳታ መግዛት አይኖርም ማለት የበይነመረብ አቅም አያስፈልግም, ምክንያቱም ፒ አለም አቀፍ የሽፋን አውታር ካለው የኤሎን ሙክ ስታርሊንክ ጋር በቀጥታ ይገናኛል.

3. ከምድር - ጨረቃ - ከምድር ማርስ ጋር መገናኘት ይችላል ይህ ማለት ማርስ ላይ ቁጭ ብለህ ምድር ጋር ካለው ሰው በስልክህ ሲያሻህ በኢንትርኔት ሲይስፍልግህ ቀጥታ ደውለህ ማውራት ትችላለህ ታወራለህ ማለት ነው. አሁንም እያሰብክ ይሆናል... ግድ የለህም Pi Network ማለት ምናባዊ ዓለም ነው...።

እንኳን ደስ ያለህ ለ DR. ኒኮላስ ኮካሊስ፣ የፒ የፓተንት ባለቤት፣ እና በዓለም ላይ ካሉት ባለጸጎች አንዱ በሆነው የአንድ ኩባንያ ዋና ስራ አስፈፃሚዎች አንዱ።👍

👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
don’t miss out
🔍🔍🔍🔍🔍▬▬ Share ▬▬🔎🔎🔎🔎🔎
ለተጨማሪ እውቀት እና ጠቃሚ የቴክኖሎጂ መረጃ ለማግኘት በዚ የቴሌግራም ቻናላችንን ከታች ባለዉን ሊንክ በመጫን ማግኘት ይችላሉ።
here it is
https://t.me/Information_Science_Technology
የዩቲዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ ይቀላቀሉ፦ሰፋ ያለ ይዘት ያላቸው የቴክኖሎጂ ቪዲዮዎቻችን ሰቅለናል በማየት ከእኛ ጋር ይማሩ ከኛ ጋር ይዘምኑ ራስዎን ያሳድጉ።
"Subscribe to our YouTube channel and become part of our family! Explore our technology-based lecture videos and learn with us. We've got a wide range of content to help you grow—don’t miss out!"
https://www.youtube.com/channel/UCpKx7Pd_viT9nnmheRu6o8Q
┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈
ሼር እናድርግ
በአፍሪካ ረጅሙ የመንገድ ፕሮጀክት የሆነው ትራንስ አፍሪካን ሀይዌይ ኔትወርክ 56,683 ኪ.ሜ የሚሸፍኑ ሲሆን ዘጠኝ አውራ ጎዳናዎችን ለማዋሃድ ያለመ የመላው አፍሪካ ተነሳሽነት ፕሮጀክት ነው።
መንገዱ በደቡብ አፍሪካ 🇿🇦፣ ኬንያ 🇰🇪፣ ኡጋንዳ 🇺🇬፣ ናይጄሪያ 🇳🇬፣ ካሜሩን ኢትዮጵያ 🇪🇹፣ ሱዳን 🇸🇩፣ ቦትስዋና 🇧🇼፣ አንጎላ 🇦🇴፣ ዛምቢያ 🇿🇲፣ ናሚቢያ 🇩።
ይህ አውታረ መረብ አፍሪካ ለዕድገት ያላትን ቁርጠኝነት እና የተሻሻለ የእርስ በርስ ግንኙነትን ለመፍጠር ያለመ ፕሮጀክት ነው።
የነጭ ሽንኩርት መድኃኒትነት
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
1. 👉👉ነጭ ሽንኩርት ስራን በትክክል ለማከናወን፣ የሰውነት ሕዋሳትን ጤናማ ለማድረግ ፣ድካምን ለማስወገድ፣ዕድሜን ለመጨመር፣በአይጥና በልዩ ልዩ ተባዮች የሚመጡትን ተስቦ በሸታዎችን ለመከላከል ነጭ ሽንኩርት መብላት በጣም ጠቃሚ ነው፡፡
2. 👉👉ማንኛውም ሰው መጥፎ ሽታ ባለበት አካባቢ ለፅዳት ከመሰማራቱ በፊት ነጭ ሽንኩርት ከትፎ ቢበላ ከማንኛውም በሽታ ከሚያመጡ ተዋህሲያን ለመዳን ይቻላል፡፡
3. 👉👉በቂ ሕክምና በሌለበት አካባቢ በቁስል ለሚሰቃይ ሕሙማን በነጭ ሽንኩርት ጭማቂ አጥቦ በቁስሉ ዙሪያ በመደምደም በፋሻ ወይም በንፁህ ጨርቅ በማሰር ሕመምተኛውን ለመፈወስ ይችላል፡፡
4.👉👉 ነጭ ሽንኩርት ቀቅሎ እንፋሎቱን የካንሰርንና የቲቢ በሽታዎችን ለመከላከልና በሳንባ አካባቢ ብርድና ጉንፋን ለማዳን ፍቱን መድኃኒቱ ነው፡፡
5. 👉👉ብርድ ብርድ በሚያሰኝ ሕመምና በተለይም በጥርስ ሕመም ለሚሰቃዩት ሕሙማን ሁለት ራስ ነጭ ሽንኩርት የውስጠኛውን ሽፋናቸውን በመላጥ በሁለቱም ጉንጫቸው በተለይም በተነቃነቀው ጥርስ በኩል ነክሰው ረዘም ላሉት ሰዓት ቢጠቀሙበት መልሶ መልሶ ይጠነክራል፡፡
6. 👉👉ለአስም፣ ለጉሮሮ ክርካሪ ወይም ኮርታ ለተባለው በሽታ እንዲሁም ጉሮሮ ለማፅዳት የነጭ ሽንኩርት ጭማቂ በስኳር ወይም በማር መጠጣት የተፈተነ መድኃኒት ነው፡፡
7.👉👉 ነጭ ሽንኩርት የራስ ምታትና የደም ብዛት ያለባቸው ሰዎች ከ3 እስከ 5 ቀናት በማከታተል ሦስት ሦስት ፍንካች በቀን ሦስት ጊዜ ቢበሉ ከድካምና ከደም ብዛት ሊፈወሱ ይችላሉ፡፡
8. 👉👉በደም መርጋት ምክንያት ለሚሰቃዩ ፣የልብ በሽታን፣ የፊንጢጣ ኪንታሮትና የእግር ደም ሥር እብጠት varicose የተባሉትን በሽታዎች ለመከላከልና ለመዳን ነጭ ሽንኩርት በመብላት መፈወስ ይችላል፡፡
9.👉👉 ነጭ ሽንኩርት የቆላ ቁስል፣ችፌን፣የጨጓራ በሽታን ወረርሽኝን ኮሌራን ሳይቲካን የቁርጥማትን ሕመምን እንደሚያድን የተረጋገጠ ነው፡፡
ጤና ይስጥልን
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
don’t miss out
🔍🔍🔍🔍🔍▬▬ Share ▬▬🔎🔎🔎🔎🔎
ለተጨማሪ እውቀት እና ጠቃሚ የቴክኖሎጂ መረጃ ለማግኘት በዚ የቴሌግራም ቻናላችንን ከታች ባለዉን ሊንክ በመጫን ማግኘት ይችላሉ።
here it is
https://t.me/Information_Science_Technology
የዩቲዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ ይቀላቀሉ፦ሰፋ ያለ ይዘት ያላቸው የቴክኖሎጂ ቪዲዮዎቻችን ሰቅለናል በማየት ከእኛ ጋር ይማሩ ከኛ ጋር ይዘምኑ ራስዎን ያሳድጉ።
"Subscribe to our YouTube channel and become part of our family! Explore our technology-based lecture videos and learn with us. We've got a wide range of content to help you grow—don’t miss out!"
https://www.youtube.com/channel/UCpKx7Pd_viT9nnmheRu6o8Q
┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈
ሼር እናድርግ
ግምቱ 1 መቶ 55 ሚሊዮን ብር በላይ የሆነ ህገወጥ የመድሃኒት ምርት በቁጥጥር ስር መዋሉ ተነገረ፡፡

የኢትዮጲያ ምግብ እና መድሃኒት ቁጥጥር  የመጀመሪያው ሩብ ዓመት አጠቃላይ ግምቱ ከ1 መቶ 55 ሚሊዮን ብር በላይ የሆነ ህገ-ወጥ የመድኃኒት ምርት በቁጥጥር ስር ማዋሉን አስታውቋል፡፡

በዚህም መሰረት በኦሮሚያ ክልል ወደ 15 ሚሊዮን፣ በደቡብ ምዕራብ 6 ሚሊዮን፣በቤኒሻንጉል ጉሙዝ 500 ሺ ፣በጋምቤላ 26 ሚሊዮን 6 መቶ ሺ እና በማእከላዊ ኢትዮጲያ ደግሞ 1 መቶ 7.5 ሚሊዮን ብር የሚገመቱ ህገወጥ መድሀኒቶች መያዛቸውን ነው የጠቀሱት፡፡

ይህን ህገወጥ ተግባር ሲፈፅሙ የተገኙ አካላት ላይ ከተወሰደባቸው እርምጃዎች መካከል የማሸግ ፣የእገዳ፣ የመጨረሻ የፅሑፍ ማስጠንቀቂያ እና ፍቃድ የመሰረዝ እርምጃዎች እንደሚገኙበት ነግረውናል፡፡

በቁጥጥር ስራው የተገኙት ህገ-ወጥ መድሃኒቶችም የህብረተሰቡ ጤና ላይ ጉዳት እንዳያስከትሉ የማስወገድ እርምጃዎች እንደተወሰደባቸው አንስተዋል፡፡
በኢትዮጵያ በቂ የኮንዶም አቅርቦት እና ስርጭት እንደሌለ ተገለጸ

በኢትዮጵያ በየዓመቱ ከ21 ሺህ በላይ አዳዲስ ሰዎች በኤች አይ ቪ ኤድስ እንደሚያዙና 26 ሺህ ሰዎች ኤች አይ ቪን ጨምሮ ተያያዥ በሆኑ የጤና እክሎች እንደሚሞቱ ጥናቶች ያመላክታሉ፡፡

ከሁለት አመት በፊት በተከሰተው የኮንዶም እጥረት ምክንያት በአንዳንድ የክልል ከተሞች ምርቱ በውድ ዋጋ ሲሸጥ እንደነበርም ተገልጿል፡፡

በኢትዮጵያ በሃገር አቀፍ ደረጃ ከ250 ሚሊዮን በላይ የኮንዶም አቅርቦት እና ስርጭት እንደሚያስፈልግ በኤም ኤስ አይ ሪፕሮዳክቲቭ ቾይዝ ካንትሪ ዳይሬክተር ዶ/ር አበበ ሽብሩ ገልጸዋል፡፡ አሁን ያለው ስርጭት ከ50 በመቶ በታች እንደሆነም አስታውቀዋል፡፡

የአቅርቦት እጥረቱ በተለያዩ ክልሎች የኤች አይቪ ኤድስ ስርጭት በከፍተኛ ሁኔታ እንዲጨምር እና እንዲስፋፋ አድርጎታልም ነው ያሉት፡፡

ዶ/ር አበበ አክለውም፤ አቅርቦት እና ፍላጎት ባለመመጣጠኑ ምክንያት በክልሎች እና በሃገሪቱ የገጠር ክፍል በተጋነነ ዋጋ እንዲሸጥ እንዳደረገው ተናግረዋል፡፡ በተለይም የኤች.አይ.ቪ ኤድስ ስርጭት ከፍተኛ በሆኑባቸው አካባቢዎች እጥረቱ እና የዋጋ ውድነቱ እንደሚስተዋል አመላክተዋል፡፡

በዚህም ኤም ኤስ አይ ኢትዮጵያ ከአጋር ድርጅቶች ጋር በመሆን በማህበራዊ ግብይት አማካኝነት በሁሉም የሃገሪቱ ክፍሎች ለማዳረስ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

በኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2022 እና በ2023 በተሠራው አገራዊ የኤች.አይ.ቪ ሥርጭት ግምታዊ የዳሰሳ ጥናት 8ሺ 257 ሰዎች በኤች.አይ.ቪ መያዛቸው መገለጹ ይታወቃል፡፡
ጎግል ኖትቡክ LM AI መሳርያ አስተዋወቀ

ለተማሪዎች፣ተመራማሪዎች እና በተለያዩ ዘርፎች ላሉ ባለሙያዎች የተዘጋጀ የAI መሳሪያ ነው። ዶኩሜንት በመስጠት መረጃን ለማስተዳደር፣ ለመዘርዘር፣ ለማሳጠር እና ከሰጠሀው ዶኩሜንት ጋር መስተጋብር ለመፍጠር የተነደፈ ነው።

ጎግል ኖትቡክ
ባህሪያቱንና በውስጡ ያካተታቸው በዝርዝር እንመልከት፡-

ቁልፍ ባህሪያት

1. በሰነድ ላይ የተመሰረተ ማጠቃለያ መስጠት፡-

ማስታወሻ ደብተር LM በሚሰቅሏቸው ሰነዶች ይዘት ላይ በመመስረት ማጠቃለያዎችን መፍጠር ይችላል ፣ ይህም ሙሉውን ጽሑፍ ሳያነቡ ዋና ዋና ሀሳቦችን በፍጥነት እንዲረዱ ይረዳዎታል ።


2. የጥናት ጥያቄ መጠይቆች መፍጠር መልስ መስጠት፡-

ከሰነዱ ወይም ካዘጋጁት ዶኩሜንት ጋር የተያያዙ የ AI ጥያቄዎችን መጠየቅ ይችላሉ, እና ከጽሑፉ በቀጥታ የተገኙ መልሶችን ይሰጣል. በተጨማሪም ማስታወሻ ደብተር LM ስለ ሰነዱ ጥያቄዎችን ያመነጫል፣ ይህም ለጥናት መመሪያዎች ወይም የውይይት ነጥቦችን ለማዘጋጀት ጠቃሚ ዘዴ ነው።


3. ማብራሪያዎች ማዘጋጀት፡-

ሁለት AI ሞዴሎችን በመጠቀም ኖትቡክ ኤልኤም ግልጽ ማብራሪያዎችን ይሰጣል፣ አንዳንዴም በሁለት ድምጽ ወይም አመለካከቶች የውይይት ቅርጸት በማዘጋጀት፣ ግንዛቤን ያሳድጋል።

4. የቪዲዮ ውህደት፡-

ከሰነዶች በተጨማሪ ማስታወሻ ደብተር LM ከዩቲዩብ ቪዲዮዎች ጋር እንዲዋሃድ ይፈቅዳል። ቪዲዮዎችን ማከል፣ ስለ ይዘቱ ጥያቄዎችን መጠየቅ እና ለመልቲሚዲያ ግብዓቶች ማጠቃለያዎችን መቀበል ይችላሉ፣ ይህም ለተለያዩ የመማሪያ ዘይቤዎች ሁለገብ መሳሪያ ያደርገዋል።


የማስታወሻ ደብተር ኤልኤም LMን ለመጠቀም ወይም ለመጀመር የሚከተለው ሊንክ ይጠቀሙ። https://notebooklm.google.com
ቀልጣፋ የትምህርት እና የምርምር ተሞክሮ ለማግኘት ባህሪያቱን ለማወቅ ሊንኩን በመጠቀም አሁኑኑ ይጀምሩ።
እርግዝና እንዴትና መቼ?
እርግዝና እንዴትና መቼ እንደሚከሰት ማወቅ ማርገዝ ለሚፈልጉም ሆነ ለማይፈልጉ ጠቀሜታው የላቀ ነው፡፡ ማርገዝ ለሚፈልጉ ጊዜና ሁኔታዎችን አመቻችቶ ለመሞከር ሲረዳ ለማይፈልጉ ደግሞ ዝግጁ እስኪሆኑ ድረስ ለመጠንቀቅ ያግዛቸዋል፡፡ ይሁንና ካልተፈለገ እርግዝና ለመጠበቅ ወይም አራርቆ መዉለድ ለሚሹ የእርግዝና መከላከያ መውሰድ ዋነኛው መፍትሄ መሆኑ መዘንጋት የለበትም፡፡
በአንድ የወር አበባ ኡደት ውስጥ ለፈርቲላይዜሽን(ለእርግዝና) የደረሰ የሴት እንቁላል ከመቀመጫው ከኦቫሪ ወጥቶ በማህጸን ቱቦ አድርጎ ወደ ማህጸን ይጓዛል፡፡ ይህ ሂደት ኦቩሌሽን ይባላል፡፡ በመደበኛነት አንድ ሴት ኦቩሌት (አማርኛዉ ስለከበደን ነዉ። የተሻለ ያላችሁ ብትጠቁሙን እናስተካክለዋለን) የምታደርገው በአንድ የወር አበባ ኡደት ውስጥ አንድ ጊዜ ብቻ ነው፡፡ ከኦቫሪ የወጣው እንቁላል ለፈርቲላይዜሽን(ለእርግዝና) ብቁ ሆኖ በማህጸን ቱቦ ውስጥ የሚቆየው ከ12 እስከ 24 ሰአት ብቻ ነው፡፡ በዚህ ጊዜ ውስጥ ከወንድ ዘር ጋር ተገናኝቶ እርግዝና ካልተፈጠረ እንቁላሉ ከማህጸን ግድግዳ ጋር አብሮ በወር አበባ መልክ ይወገዳል፡፡
ኦቩሌት የሚደረግበትን ጊዜ ማወቅ ቶሎ ለማርገዝ ይረዳል፡፡ አንዲት ሴት ኦቩሌት የምታደርግበትን ጊዜ በእርግጠኛነት መናገር ባይቻልም ለመገመት የሚያስችሉ የተለያዩ ምልክቶችን ማወቅና ለማርገዝ የሚደረገውን ሙከራ በነዚህ ጊዜያት ውስጥ ማድረግ የማርገዝን እድል ይጨምራል።፡ይህንን ጊዜ መገመት ከሚያስችሉት ዘዴዎች አንዱና ቀለል ያለው ቀን መቁጠር ነው፡፡ እንደ የወር አበባ ኡደት ሁሉ የኦቩሌሽን ጊዜም ከሴት ሴት እንዲሁም አንድ ሴት ላይ ከወር ወር የተለያየ ስለሆነ ይህ ነው ብሎ አንድን ቀን መጠቆም አይቻልም። በአማካይ የወር አበባቸዉ ኡደት ከ28-32 ቀን ለሆነ ሴቶች ኦቩሌት ያደርጋሉ ተብሎ የሚገመተው ያለፈው የወር አበባቸው ከጀመረበት ቀን በኋላ ከ11ኛው እስከ 21ኛው ቀን ባለው ጊዜ ውስጥ ነው፡፡ ይህ ጊዜ ለእርግዝና ምቹ ጊዜ ተብሎ ይታወቃል።
ከላይ እንደተገለጸው ከኦቩሌሽን በኋላ እንቁላሉ ለፈርቲላይዜሽ (ለእርግዝና) ብቁ ሆኖ የሚቆየው ከ12-24 ሰአት ያህል ቢሆንም የወንድ ዘር ግን ከግብረስጋ ግንኙነት በኋላ በሴቷ ሰውነት ውስጥ ከሶስት እስከ አምስት ቀን መቆየት ስለሚችል እርግዝና ሊፈጠር የሚችልባቸውን ቀናት ሰፋ ያደርገዋል፡፡ ለእርግዝና ምቹ ነዉ ተብሎ ከላይ በተጠቀሱት ቀናት ዉስጥ በየቀኑ አሊያም አንድ ቀን እየዘለሉ የግብረስጋ ግንኙነት ማድረግ የማርገዝን እድል ያሰፋል፡፡ ከግንኙነት በኋላ በጀርባ ተኝቶ ከ10-15 ደቂቃ መቆየት የወንዱ ዘር ወደ ማህጸን በር ለመግባት በቂ ጊዜ ይሰጠዋል።
በተቃራኒዉ ማርገዝ ለማይፈልጉ ደግሞ ኦቩሌሽን ከሚጠበቅበት 3-5 ቀናት በፊት ጀምሮ በኦቩሌሽን ወቅትም ግንኙነት አለማድረግ ይመረጣል። ኮንዶም ወይም ሌሎች የእርግዝና መከላከያ መንገዶችም ጥሩ አማራጭ ናቸው፡፡
ጤናማ የወንድ ዘር የእርግዝናን እድል ለመጨመር ስለሚረዳ ለማርገዝ ሙከራ በሚደረግበት ጊዜ ወንዱም አልኮል መጠጥን በመቀነስ፤ ሲጃራ በማቆምና የሰውነት ክብደትን በመቆጣጠር የበኩሉን ዝግጅት ማድረግ ይጠበቅበታል፡፡ ሌላስ ጊዜ ቢሆን ባይጠጣና ባይጨስ አይሻልም?
ሌሎች ኦቩሌሽንን ሊጠቁሙ የሚችሉ ምልክቶች ደግሞ ከላይ በተጠቀሱት ቀናት መካከል የማህጸን ፈሳሽ መጠን መጨመር፤ ባንዳንድ ሴቶች ላይ በኦቩሌሽን ወቅት በአንደኛው ጎናቸው ህመም ቢጤ መሰማት፣ በሌሎች ደግሞ ከሚቀጥለው የወር አበባ በፊት መሀከለኛው ቀን አካባቢ ትንሽ ደም መፍሰስ የመሳሰሉት ናቸው፡፡
በሃገራችን መኖሩን እንጃ እንጂ ለቤት ውስጥ መጠቀሚያ የሚሆን ኦቩሌት መደረግ አለመደረጉን የሚጠቁም መመርመሪያ መሳሪያም አለ፡፡ ቀን መቁጠር ከደከማችሁ ፋርማሲ ሄዳችሁ መኖር አለመኖሩን መጠየቅ ወይም ዳያስፖራ ዘመዳችሁን አደራ አምጣልኝ ማለትም ይቻላል!
መረገዝ አለመረገዙን ለማወቅ የሚቀጥለው የወር አበባ መምጫ ጊዜ እስኪደርስ መጠበቅ ያስፈልጋል፡፡ በተጠበቀበት ጊዜ ካልመጣ የእርግዝና ምርመራ ማድረግ፤ ከመጣ ደግሞ በሚቀጥለው ዙር ተመሳሳይ ሙከራ መቀጠል ነዉ፡፡
የኦቩሌሽን ጊዜ በትክክል ባለመታወቁ የተነሳ ሙከራ በተደረገ በመጀመሪያው ወር ላይረገዝ ይችላል፡፡ ስለዚህም ደጋግሞ መሞከር ይመከራል፡፡ እድሜያቸው ከ35 አመት በታች ለሆኑ ከአንድ አመት ሙከራ በኋላ፤ ከዛ በላይ ለሆኑ ከስድስት ወር ሙከራ በኋላ በዘርፉ የተሰማሩ የጤና ባለሙያዎችን ማማከር ይበረታታል፡፡
እርግዝና ሲታቀድ ቢያንስ ከወር በፊት ፎሊክ አሲድ የተባለውን ንጥረ ነገር ከመድሃኒት ቤት ገዝቶ መጠቀም መጀመር ጤናማ ልጅ ለመውለድ የላቀ አስተዋጽኦ ያደርጋል፡፡
፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥
እርግዝናን ምክንያት በማድረግ የተለያዩ ጥያቄዎች ልነሱ ይችለሉ
======================
1. በእርግዝና ጊዜ የግብረስጋ ግንኙነት ማድረግ ይቻላል?
በተለያየ የጤና መታወክ የተነሳ ሀኪም ካልከለከለ በስተቀር በእርግዝና ጊዜ የግብረስጋ ግንኙነት ማድረግ ይቻላል፡፡ በማህጸን ውስጥ ያለው ልጅ በተከበበበት ውሃ፤ በማህጸን ጡንቻዎችና በእናትየዋ የሆድ ጡንቻ ተከቦ ስለሚገኝ በግብረስጋ ግንኙነት ጊዜ የሚደረግ እንቅስቃሴ ጉዳት አይደርስበትም ወይም አይረብሸውም፡፡ የወንዱ የዘር ፈሳሽ ምጥ ለማስጀመር የሚችል ፕሮስታግላንዲን የተባለ ሆርሞን በውስጡ ስለሚገኝ አንዳንድ ሃኪሞች የመውለጃ ጊዜ እየተቃረበ ሲመጣ የግብረስጋ ግንኙነት አለማድረግን ይመክራሉ፡፡ ነገር ግን ምጥ ሲዘገይ ደግሞ በተለያየ ምክንያት ሀኪም ካልከለከለ እና የእንሽርት ውሃ እስካልፈሰሰ ድረስ የግብረስጋ ግንኙነትን እንደ ምጥ ማምጫ አማራጭ መሞከርም ይቻላል፡፡
የግብረስጋ ግንኙነት በሃኪም ሊከለከልባቸው የሚችሉ ከእርግዝና ጋር የተያያዙ ምክንያቶች ውስጥ የሚከተሉት ይገኙበታል፡ (እነዚህ ክስተቶች ሲያጋጥሙ ሁሌም ፈጥኖ ወደ ህክምና መሄድ ያስፈልጋል)
o በእርግዝና ጊዜ የሚታይ ምክንያቱ ያልታወቀ ደም መፍሰስ፤ የማህጸን ፈሳሽ ወይም ቁርጠት ሲኖር
o የእንሽርት ውሃ መፍሰስ
o እናትየዋ ከዚህ በፊት ምክንያቱ ያልታወቀ ማስወረድ አጋጥሟት ከነበር
እያንዳንዷ ሴት በእርግዝና ጊዜ ለተለያዩ ነገሮች የሚኖራት ስሜት የተለያየ ነው፡፡ አንዳንድ ሴቶች በእርግዝና ጊዜ የግብረስጋ ግንኙነት ፍላጎታቸው ሊቀንስ አንዳንዶች ላይ ደግሞ ሊጨምር ይችላል፡፡ ስለዚህ ባሎች የልጆቻችሁን እናት ስሜት ተረድታችሁ በዉይይት እንደሚሆን አርጉ!
• ከ4-5 ወር ጀምሮ የሆድ መጠን ስለሚጨምርና ትልልቅ የደምስሮችን ሊጫን ስለሚችል በግንኙነት ጊዜ በጀርባ መተኛት አይመከርም፡፡
2. ወንድ ወይንም ሴት ልጅ ለመውለድ ምን ማድረግ እችላለሁ?
ሳይንስ እስከሚያዉቀዉ ድረስ ይሄ ቢደረግ ወንድ ልጅ፣ ያ ቢደረግ ደግሞ ሴት ልጅ ማርገዝ የሚቻልበት መንገድ የለም።
3. የመንታ እርግዝና እንይህ ይፈጠራል?
ሁለት አይነት የመንታ እርግዝና አለ፡፡ የመጀመሪው - ልጆቹ መልካቸውም ሆነ ጾታቸው አንድ አይነት የሚሆንበት ነው፡፡ ይህ የሚሆነዉ የወንዱ ዘር እና የሴቷ እንቁላል ከተዋሃዱ በኋላ አንድ ሆኖ በማደግ ፋንታ ለሁለት ሲከፈል ነው፡፡ ከአንድ የወንድ ዘር እና አንድ የሴቷ እንቁላል ከመምጣታቸዉም የተነሳ አንድ አይነት መልክ፣ አንድ አይነት ጾታ ይኖራቸዋል። ይህ ከአንድ ወደ ሁለት መከፈል መንሰኤዉ አይታወቅም፡፡ በቤተሰብም የሚተላለፍ አይደለም፡፡