Hope Tutorial Program
3.07K subscribers
111 photos
2 videos
468 files
117 links
ኢንትራንስ ከ500 በላይ ማምጣት ለሚፈልግ ብቻ📚📚📚📚

ለተጨማሪ መረጃ ላይ @eyashua አናግሩን
Download Telegram
#Update

የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት ነገ ይፋ ይደረጋል።

የትምህርት ሚኒስቴር የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት ነገ ይፋ እንደሚደረግ አሳውቋል።

የፈተና ውጤቱን አስመልክቶ ነገ ከቀኑ 10 ሰዓት ጀምሮ መግለጫ ይሰጣል።

#MoE

Via tikvahethiopia
😭41🔥1
በሀገር ደረጃ 8.4 በመቶ ተማሪ 50% በላይ በማምጣት የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተናን አልፏል።

@tikvahethiopia
🕊2
ከፍተኛ ውጤት የት ተመዘገበ ?

በተፈጥሮ ሳይንስ ከ600 ፦

➡️ 591 ወንድ ተማሪ ከዶዶላ ኢፋ ቦሩ ትምህርት ቤት

➡️ 579 ሴት ተማሪ ከብስራተ ገብርኤል ትምህርት ቤት

በማህበራዊ ሳይንስ ፦

➡️ 562 ወንድ ከአምቦ ቦርዲግ ትምህርት ቤት

➡️ 548 ከሴት ከሴንት ጆሴፍ ትምህርት ቤት

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia
👏21
#MoE : 1,249 ትምህርት ቤቶች ምንም ተማሪ ሳያሳልፉ ቀርተዋል።  ከአምናው ጋር ሲነጻጸር 114 ትምህርት ቤቶች ተማሪዎች በማሳለፍ መሻሻል ታይቷል።

መቶ በመቶ ተማሪዎቻቸውን ያሳለፉት 50 ትምህርት ቤቶች ናቸው።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
😭3
ከፍተኛ የተማሪ ቁጥር የት አለፈ ?

" ዘንድሮ 8.4 በመቶ ተማሪ ከ 50 በመቶ በላይ በማስመዝገብ ፈተናውን አልፏል " - ትምህርት ሚኒስቴር

የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ውጤት እየተገለጸ ይገኛል።

በዘንድሮ አመት ፈተናውን ከወሰዱ ተማሪዎች ውስጥ 8.4 በመቶ ተማሪ ከ 50 በመቶ በላይ በማስመዝገብ ፈተናውን አልፏል ተብሏል።

ከፍተኛ ተማሪዎችን ያሳለፉ ክልሎች ፦
- አዲስ አበባ፣
- ሐረሪ
- አማራ ክልል ናቸው።

ዘንድሮ " የተፈታኙ ቁጥር ቀንሷል ያለፈው ተማሪ ቁጥር ግን ጨምሯል " ያሉት ትምህርት ሚኒስትሩ ዘንድሮ በአጠቃላይ 48,929 ተማሪዎች ማለፋቸውን ገልጸዋል።

ባለፈው አመት ያለፈው ተማሪ ቁጥር 36,409 ነበር።

በጾታ ስብጥር
30,451 ወንድ ተማሪዎች አልፈዋል።
18,478 ሴት ተማሪ አልፏል።

በተፈጥሮ ሳይንስ ከፍተኛ ውጤት

ወንድ 591/600 ዶዶላ ኢፋ ቦሩ ትምህርት ቤት
ሴት 579/600 ብስራተ ገብርኤል ትምህርት ቤት

በማህበራዊ ሳይንስ
ወንድ 562/600 አምቦ አምቦ ቦርዲንግ ስኩል።
548 /600 ሴንት ጆሴፍ ትምህርት ቤት።

አማካይ ውጤት
87 በመቶ የአዳሪ ትምህርት ቤቶች
86 በመቶ ዓለማቀፍ ትምህርት ቤቶች
5.4 በመቶ የመንግስት ትምህርት ቤቶች
51 በመቶ የግል ትምህርት ቤት ውጤት

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
#TikvahEthiopiaFamliyAA

@tikvahethiopia
🔥31
በሀገር አቀፍ ደረጃ 2,384 ተማሪዎች ከ500 በላይ ውጤት አስመዝግበዋል።

አዲስ አበባ ከተማ 888 ተማሪዎች ከ500 በላይ በማስመዝገብ ከሁሉም ክልሎች አንደኛ ደረጃ መያዝ ችላለች።

@tikvahethiopia
😱4
ዘንድሮ የሬሜዲያል /አቅም ማሻሻያ/ ፕሮግራም ይኖራል ?

በዘንድሮ ዓመት ሬሜዲያል /የአቅም ማሻሻያ/ ፕሮግራም እንደሚኖር የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ገልጸዋል።

" ከባለፈው ዓመት መግቢያውን ከፍ በማድረግ ሬሚዳል ይሰጣል " ነው ያሉት።

ምን ያህል ተማሪዎች ሬሜዲያል ይገባሉ ? ለሚለው ጥያቄ ሚኒስትሩ " አልወሰንም " ሲሉ መልሰዋል።

" ዘንድሮ ሪሚዲያል እድል የሚሰጣቸውን ተማሪዎች ቁጥር አልተወሰነም። 40-50 በመቶ መካከል ይሁን የሚለው ላይ በውይይት ላይ ነው " ብለዋል።

ካለፈው አመት ግን መግቢያው ከፍ እንደሚደረግ እና የሚገባው ተማሪ ቁጥርም ቅናሽ እንደሚኖረው ተገልጿል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
🤯1
ውጤት መቼ ይለቀቃል ?

" ውጤት እስከ ነገ 6:00 ሰዓት ይለቀቃል " - ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
👍1
Hope Tutorial Program
ውጤት መቼ ይለቀቃል ? " ውጤት እስከ ነገ 6:00 ሰዓት ይለቀቃል " - ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ቲክቫህ ኢትዮጵያ #TikvahEthiopiaFamilyAA @tikvahethiopia
እስከ ነገ ቀን 6:00 ሰዓት ውጤት ይለቀቃል።

" ምንም የተሳሳተ ነገር እንዳይኖርና እርግጠኛ ለመሆን ስለፈለግን የተወሰኑ ልጆች አሉ የተዛባ እሱን አስተካክለን እስከ ነገ ቀን 6:00 ሰዓት የፈተናው ውጤት ይለቀቃል። " - የትምህርት ሚኒስትር ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ

@tikvahethiopia
1
የ2017 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ውጤትን ተፈታኞች የሚያገኙበት አድራሻዎች ይፋ ሆነዋል

ተፈታኞች በሚከተሉት አድራሻዎች ዛሬ ከሰዓት ጀምሮ ውጤታቸውን ማየት ይችላሉ፡፡ ከታች የተጠቀሱትን በመጠቀም ተፈታኞች ጊዜያዊ ሰርቲፊኬታቸውን ወዲያውኑ አውርደው (download አድርገው) መውሰድና መጠቀም ይችላሉ፡፡

1. ዌብ ሳይት፡ https://result.eaes.et
2. ቴሌገራም፡ https://t.me/EAESbot
3.  አጭር የጽሑፍ መልዕክት (SMS)፡  6284

via: የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት
2😭2
Good luck yall🤞
🔥5
ውጤት እንድናይላችሁ ምትፈልጉ connection ያስቸገራችሁ ሰዎች comment ur name and admission number
🙏3😁2
ውጤት የሚታይበት ዌብሳይት እስካሁን እይሰራ አይደለም፡፡ ውጤት ማሳየት እስኪጀምር ትንሽ ሊቆይ ይችላል ታገሱ፡፡