ቅዱሳት መጻሕፍት
7.77K subscribers
1.46K photos
61 videos
348 files
848 links
በዚህ ቻናል

👉ቅዱሳት መጻሕፍት ይጠናሉ::
👉መጽሐፍ ቅዱሳዊ ትምህርቶች ይቀርባሉ::
👉 ለቅዱሳት መጽሐፍት ጥናት የሚያግዙ መጻሕፍት ይለቀቃሉ።

⭐️⭐️⭐️⭐️⭐️

@Holy_scriptures
Download Telegram
ነህምያ ንጉሥ አርጤክስስን በሚያገለግልበት ጊዜ የፋርስ ግዛት ዋና ከተማ ማን ነበረች?
Anonymous Quiz
28%
ባቢሎን
9%
ነነዌ
7%
ደማስቆ
56%
ሱሳ
4👍2
.       ──•◈•─────•◈•─
                 የዕለቱ ጥቅስ 
        ──•◈•─────•◈•─
“ስለዚህ እነርሱ ደግሞ በክርስቶስ ኢየሱስ ያለውን መዳን ከዘላለም ክብር ጋር እንዲያገኙ ስለ ተመረጡት በነገር ሁሉ እጸናለሁ።”
2ኛ ጢሞቴዎስ 2፥10



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
16
በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ የሰሜኑ እስራኤል ዋና ከተማ ማን ነበር?
Anonymous Quiz
28%
ኢየሩሳሌም
9%
ቤቴል
50%
ሰማሪያ
4%
ሴሎ
8%
ኬብሮን
6
ቅዱሳት መጻሕፍት
#አዲስ_ዓመት የእግዚአብሔርን ቃል የማንበብ ጥቅም                  ክፍል-3 የእግዚአብሔር ቃል ያነጻል የእግዚአብሔር ቃል የምንፀዳበትና የምንቀደስበት ብቸኛ የእግዚአብሔር መንገድ ነው፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ ክርስቶስ ለቤተክርስቲያን ያደረገላትን ሲገልጥ ‹‹በውኃ መታጠብና ከቃሉ ጋር አንጽቶ እንዲቀድሳት ስለ እርስዋ ራሱን አሳልፎ ሰጠ›› (ኤፌ.5፡25) ይላል፡፡ በዮሐ.17፡17ም እንዲሁ…
#አዲስ_ዓመት

የእግዚአብሔርን ቃል የማንበብ ጥቅም



                 ክፍል-4
         (የመጨረሻ ክፍል)



በመጀመሪያ የተከሰተው ኃጢአት የእግዚአብሔርን ቃል አለመታዘዝ ነበር፡፡ እግዚአብሔር በእኛ ላይ ያለውን ሥልጣን ግምት ውስጥ ሳናስገባ አንዳች ማድረግ ወይም እናደርገው ሲገባን ሳናደርገው ብንቀር ኃጢአት ይሆናል፡፡ ኃጢአት በ1ዮሐ.3፡4 "ዓመፅ" ተብሎ ተገልጾአል፡፡ የእግዚአብሔርን ፈቃድ ሳንጠይቅ እንደፈቃዱ ሳይሆን በገዛ ፈቃዳችን የምንሠራው ሁሉ ኃጢአት ነው፡፡

ጌታችን ኢየሱስ መታዘዝን እንዴት እንዳሳየ እስኪ እንመልከት፡፡ በዕብራውያን 10፡7 ላይ ‹‹ፈቃድህን ላደርግ መጥቼአለሁ›› ይላል፡፡ ፈቃድን ለማድረግ ደግሞ መታዘዝን መማር ነበረበት (ዕብ.5፡6) እርሱ ዘላለማዊው አምላክ እንደመሆኑ መጠን መታዘዝ ለእርሱ እንግዳ ነበርና፡፡ በወልድነቱም በምድር በነበረበት ጊዜ ሁልጊዜ አብን ደስ የሚያሰኝ ሥራ ይሠራ ነበር፡፡ እንዲህም አለ፤ ‹‹የእኔስ መብል የላከኝን ፈቃድ አድርግ ዘንድ ሥራውንም እፈፅም ዘንድ ነው፡፡›› (ዮሐ.4፡35)

ሰው ሁሉ በየመንገዱ በሚሄድበትና ሁሉም የራሱን ፈቃድ በሚሠራበት በዚህች ምድር ይህ ሰው (ወልድ) ግን ፍጹም ቅዱስ ሆኖ ሳለ የእግዚአብሔርን ፈቃድ ብቻ ሲፈፅም መታየቱ ለእግዚአብሔር ምንኛ ደስ ያሰኘዋል!

በአሁኑ ጊዜም እግዚአብሔርንና ፈቃዱን አውቀው ለማገልገል ደስተኞች የሆኑና ይህንንም ለመረዳት ቃሉን በትጋት የሚመረምሩ ሰዎች ሲገኙ እግዚአብሔር  ምን ያህል ደስ ይሰኝ!

ቃሉን ለማወቅ በመፈለግ ስናጠና የሚሰጠንን ጥቅም ታላቅነት መገመት ይቻላል፡፡ በቃሉ ውስጥ የጌታን ክብርና ጌታ በፍቅሩ ያዘጋጀልንን በረከት ስናይ ልባችን በደስታ ይሞላል፡፡ ቃሉን በማወቅ የእግዚአብሔርን ሐሳብ በበለጠ መረዳት እንችላለን፡፡ ከሰይጣን ጥቃት የምንከላከልበትንና ራሳችንም መልሰን ለሌላው ሰው የነፍሱን ደኅንነት በመንገር ጠላትን የምናጠቃበት የጦር ዕቃችን ቃሉ ነው፡፡

እባክህ ተወኝ ጭንቅላቴ ወንፊት ነው ምንም መያዝ አይችልምና ማጥናቱ ይከበደኛል የሚል ሰው ሊኖር ይችላል፤ ነገር ግን ወንፊቱም ደጋግሞ ውኃ ሲያልፍበት ማቆር ባይችልም ራሱ ግን ይፀዳል፡፡ ውኃውም የወንፊቱን ቆሻሻነት ያስወግዳል፡፡ የእግዚአብሔር ቃልም ሰውን እንዲሁ ያነፃል፡፡ ማንበብ ብቻ ሳይሆን በቃሉ ላይ ጊዜ ወስዶ ማሰላሰል አስፈላጊ ነው፡፡ ጥሩ የሆኑ ማብራሪያዎችንም መጠቀም መልካም ነው፤ ሆኖም ማብራሪያውን ራሱንም በቃሉ ልንፈትነው የተገባ ነው፡፡ ማብራሪያው ቃሉን እንዲተካ ማድረግ የለብንም፤ ምክንያቱም ቃሉን የሚተካ ሌላ የአማራጭ አስተያየት ሊኖር አይገባምና እንደዚህ ማድረግም በራሱ ስሕተት ነው፡፡

‹‹ልጄ ሆይ ቃሌን ብትቀበል ትእዛዜንም በአንተ ዘንድ ሸሽገህ ብትይዛት ጆሮህ ጥበብን እንዲያደምጥ ታደርጋለህ፤ ልብህንም ወደ ማስተዋል ታዘነብላለህ፤ ረቂቅ እውቀትን ብትጠራት ለማስተዋልም ድምፅህን ብታነሳ እርስዋንም እንደ ብር ብታፈላልጋት እርስዋንም እንደ ተቀበረ ገንዘብ ብትሻት የዚያን ጊዜ እግዚአብሔርን መፍራት ታውቃለህ፡፡››
(ምሳ.2፡1-5)፡፡


ምንጭ፦ gbv-online.org



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
7👍2🥰1
.       ──•◈•─────•◈•─
                 የዕለቱ ጥቅስ 
        ──•◈•─────•◈•─
“እግዚአብሔር አምላክ የሚናገረውን እሰማለሁ፤ ሰላምን ለሕዝቡና ለቅዱሳኑ ልባቸውንም ወደ እርሱ ለሚመልሱ ይናገራልና።”
መዝሙር 85፥8



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
19🙏1
በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ ዳዊት በመጀመሪያ በይሁዳ ላይ የነገሰው የት ከተማ ነበር?
Anonymous Quiz
16%
ኢየሩሳሌም
18%
ቤተልሔም
10%
ሴሎ
55%
ኬብሮን
5
.       ──•◈•─────•◈•─
                 የዕለቱ ጥቅስ 
        ──•◈•─────•◈•─
“ምክንያቱም የምንኖረው በእምነት እንጂ በማየት አይደለም።”
2ኛ ቆሮንቶስ 5፥7 (አዲሱ መ.ት)



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
11👍3🔥1🙏1
#እራሳችንን_እንመርምር

በአሁን ወቅት አብዛኞቻችን በቅዱሳን ኅብረት ውስጥ የእኛን አስበልጠን በተለያየ ጎራ ተከፋፍለን የምንገኝ ቢሆንስ? ለክርስቶስ ቀንተን ወይስ በምልክት ወይም በጥበብ የተሻለ ነው ያልነው ጎራ ውስጥ ተሰልፈን? ለክርስቶስ ወግነን ቢሆንስ በመከፋፈል እርሱ ይከብራል?

“ክርስቶስ ተከፍሎአልን? ጳውሎስስ ስለ እናንተ ተሰቀለን? ወይስ በጳውሎስ ስም ተጠመቃችሁን?”
1ኛ ቆሮንቶስ 1፥13



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
5
.       ──•◈•─────•◈•─
                 የዕለቱ ጥቅስ 
        ──•◈•─────•◈•─
“አቤቱ፥ ሥራችንን ሁሉ ሠርተህልናልና ሰላምን ትሰጠናለህ።”
ኢሳይያስ 26፥12



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
17
ኤርሚያስና መልእክቱ.pdf
3.5 MB
📔ርዕስ፦ ኤርምያስና መልእክቱ
👤ጸሐፊ፦
💾መጠን፦23.5MB የገጽ ብዛት፦95



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
1
.       ──•◈•─────•◈•─
                 የዕለቱ ጥቅስ 
        ──•◈•─────•◈•─
“እኔም እንዳልሞት በሕይወቴ ዘመን የእግዚአብሔርን ቸርነት አድርግልኝ፤”
1ኛ ሳሙኤል 20፥14



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍96👏1🙏1
#አዲስ_ዓመት
#New_Year

መጽሐፍ ቅዱስን እንዴት እናንብብ? ጠቃሚ መርሆች




             ክፍል-1



መጽሐፍ ቅዱስ ማዕከላዊ መልዕክቱ ለማንኛውም ሰው ግልፅ ሊሆን በሚችልበት ሁኔታ የተቀመጠ ስለሆነ በሁሉም የዕድሜ ክልሎችና በየትኛውም የትምህርት ደረጃ ላይ ላሉ ሰዎች መናገር የሚችል መጽሐፍ ነው፡፡ 2ኛ ጢሞቴዎስ 3፡14-15 ላይ ህጻናት እንኳ የመጽሐፍ ቅዱስን ዋና መልዕክት መረዳት እንደሚችሉ ይናገራል፡፡ ይህ ማለት ግን ሁሉም የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች እኩል በሆነ ሁኔታ ግልፅ ናቸው ወይንም ደግሞ በቀላሉ ለመረዳት የሚያዳግቱ ክፍሎች የሉም ማለት አይደለም፡፡ ነገር ግን ማንኛውም ሰው የዘላለምን ሕይወት ማግኘት እንዲችል ማዕከላዊ መልእክቱ ብዙ ጊዜ በመደጋገምና እጅግ ግልጽ በሆነ ሁኔታ ተቀምጧል፡፡

መጽሐፍ ቅዱስ የተጻፈው እንድናነበው እንጂ እንደ ምትሃታዊ መጽሐፍ በመቁጠር ተንተርሰነው እንድንተኛ ወይንም ደግሞ ሊነካካ በማይችልበት ስፍራ በጥንቃቄ እንድናስቀምጠው አይደለም፡፡ የእግዚአብሔር ቃል በሕይወታችን ውስጥ ሊሠራ የሚችለው ሲነበብ ነው፡፡ የእግዚአብሔር ቃል እንደ አድካሚ ኃይማኖታዊ ሕግጋት ስብስብ ሊታሰብ አይገባም፡፡ የእግዚአብሔር ቃል የሕይወት ቃል ነው፤ ሕያውና የሚሠራም ነው፡፡ ስናነበው እምነትን በውስጣችን ይፈጥራል፣ ነፍሳችንን ያድሳል፤ ይለውጠናልም፡፡ በውስጡ የተቀመጡትን ሕግጋት በራሳችን ኃይልና ጥረት ልንፈፅማቸው እንደምንችል መቁጠር አይኖርብንም፡፡ በእግዚአብሔር ቃል ሐሳብ ለመኖር መጀመርያ ቃሉ በውስጣችን በሚፈጥረው እምነት በክርስቶስ ኢየሱስ አዳኝነት በማመን አዲስ ፍጥረት መሆን ያስፈልገናል፤ ከዚያም ኃይል የሚሰጠውን የክርስቶስን መንፈስ መቀበል ያስፈልገናል፡፡

የእግዚአብሔርን ቃል አንብበን የምንረዳው ሰዎች ባወጡት ቀመር መሠረት ባይሆንም ነገር ግን ሊታወቁ የሚገባቸው መርሆች አሉ፡፡ በማስከተል እነዚህን መርሆች እንዳስሳለን፡፡

የልብ ዝግጅት

አንዳድ ሰዎች በተደጋጋሚ የሚናገሩት የተለመደ ነገር ቢኖር መጽሐፍ ቅዱስን በማንበባቸው ሳብያ ትክክል አለመሆኑን እንደተገነዘቡና በቀደመው ሃይማኖታቸው እንዲፀኑ እንደረዳቸው ነው፡፡ እነዚህ ወገኖቻችን ያልተገነዘቡት አንድ እውነት ቢኖር የእግዚአብሔር ቃል ተልዕኮ ሁለት ገጽታ ያለው መሆኑን ነው፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ እውነትን ለሚጠሙ ሰዎች የሕይወት ቃል ሲሆን በእውነት ላይ ለሚያምጹ ሰዎች ደግሞ የፍርድ ቃል ነው፡፡ የእግዚአብሔር ቃል ሰዎችን ወደ እምነት ያመጣል አለዚያም ደግሞ ልባቸውን በማደንደን ይገፈትራቸዋል፡፡ ሁለቱም ውጤቶች ግን ከሰዎቹ የልብ ዝግጅት አንጻር የሚከወኑ ናቸው፡፡ የእግዚአብሔር ቃል ሕይወት አልባ ንግግር ሳይሆን የሚሠራ ነው፡-

“የእግዚአብሔር ቃል ሕያው ነውና፥ የሚሠራም፥ ሁለትም አፍ ካለው ሰይፍ ሁሉ ይልቅ የተሳለ ነው፥ ነፍስንና መንፈስንም ጅማትንና ቅልጥምንም እስኪለይ ድረስ ይወጋል፥ የልብንም ስሜትና አሳብ ይመረምራል”
    (ዕብ. 4፡12)

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንደተናገረው በመጨረሻው ቀን በኛ ላይ የሚፈርደው ቃሉ ነው፡-

“ዓለምን ላድን እንጂ በዓለም ልፈርድ አልመጣሁምና ቃሌን ሰምቶ የማይጠብቀው ቢኖር የምፈርድበት እኔ አይደለሁም። የሚጥለኝ ቃሌንም የማይቀበለው እርሱ የሚፈርድበት አለው፤ እኔ የተናገርሁት ቃል እርሱ በመጨረሻው ቀን ይፈርድበታል።”
  (ዮሐ. 12፡47-48)

ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በ2ኛ ቆሮንቶስ መልዕክቱ ላይ የሚከተለውን ይናገራል፡-

“በሚድኑቱና በሚጠፉቱ ዘንድ ለእግዚአብሔር የክርስቶስ መዓዛ ነንና፤ ለእነዚህ ለሞት የሚሆን የሞት ሽታ ለእነዚያም ለሕይወት የሚሆን የሕይወት ሽታ ነን። ለዚህም ነገር የሚበቃ ማን ነው?” 2ኛ ቆሮንቶስ 2፡15-16

ሐዋርያው እያለ ያለው ነገር ቢኖር ወንጌል ዝም ብለን የምንቀበለው ወይንም ደግሞ የምንጥለው ነገር ሳይሆን ብንቀበለው ወይንም ደግሞ ባንቀበለው በሕይወታችን ላይ ተፅዕኖ ማምጣቱ ግድ መሆኑን ነው፡፡ ስለዚህ ሰዎች የእግዚአብሔርን ቃል ሲንቁ፣ መዘባበቻ ሲያደርጉና ሲያምጹበት የተሸነፉት እነርሱ እንጂ ቃሉ አይደለም፡፡ በዚህም ሆነ በዚያ የእግዚአብሔር ቃል አሸናፊ ነው፡፡ ለተቀበሉት የዘላለምን ሕይወት ሲሰጥ ባልተቀበሉት ላይ ግን ይፈርዳል፡፡ የወንጌል መልዕክት እውነትን ለማወቅ ለሚፈልጉ ሰዎች የሕይወት ዜና ነው፤ ለዘባቾች ግን የሞት ዜና ነው፡፡ ውድ አንባቢያን እናንተ የእግዚአብሔርን ቃል እውነትን በሚፈልግ ልብ ከሚያነቡት ወገን ናችሁ ወይንስ ከቃሉ ውስጥ “ስህተቶችን” ነቅሰው ለማውጣት ከሚያነቡት ሰዎች ወገን ናችሁ? ቀና በሆነ ልብ ቃሉን በማንበብ የዘላለምን ሕይወት ታገኙ ዘንድ ምኞታችንና ጸሎታችን ነው፡፡

ሥነ ፍታቴ (Hermeneutics)

የሥነ ፍታቴ ጥቅም መጽሐፍ ቅዱስ በተጻፈበት ዘመን ለመጀመርያዎቹ ተቀባዮች የነበረውን ትርጉምና ዛሬም ደግሞ ለኛ ምን ማለት እንደሆነ እንድንረዳ ማገዝ ነው፡፡ በዘመናት መካከል ሰዎች ይህንን ቃል ብዙ ክፉ ሥራዎቻቸውን ለማጽደቅ ጠቅሰውታል፡፡ በዚህ ዘመንም ብዙ ሰዎች በመልካምም ሆነ በእኩይ ፍላጎት በመነሳሳት መጽሐፍ ቅዱስ ያላለውን ነገር ሲያስብሉት እናያለን፡፡  በቤተ ክርስቲያን ውስጥ የሚገኙ ብዙ ሰባኪያን ትግላቸው በአንድ ጥቅስ ውስጥ ያለን ልዩ ትርጉም ማግኘት ይመስላል፡፡ የስህተት አስተማሪዎችና ከክርስትና ውጪ ያሉ የአንዳንድ ሃይማኖቶች ተከታዮችም ደግሞ የራሳቸውን አስተምህሮ ለመደገፍ ወይንም ደግሞ መጽሐፍ ቅዱስ ስህተት እንዳለበት ለማሳየት በማለም ጥቅሶችን ይጠመዝዛሉ፡፡

መጽሐፍ ቅዱስን በምናጠናበት ሰዓት ከመሠረታዊ የሥነ ፍታቴ መርሆች ጋራ የሚጣረስ አተረጓጎም የምንጠቀም ከሆነ ወደ ስህተት እንገባለን፡፡ ስለዚህ ማንኛውም መጽሐፍ ቅዱስን ለግል ሕይወቱም ሆነ ሌሎችን ለማስተማር ማጥናት የሚፈልግ ሰው እነዚህን ጠቃሚ መርሆች ማወቅ ይኖርበታል፡፡

ጎርደን ዲ. ፊ. እና ዳግላስ ስቱዋርት የተባሉ ክርስቲያን ጸሐፍት የሥነ ፍታቴን አስፈላጊነት በተመለከተ የሚከተለውን ብለዋል፡-

ሥነ ፍታቴ አስፈላጊ መሆኑን የሚያሳይ መርህ በመጽሐፍ ቅዱስ ባሕርይ ውስጥ ይገኛል፡፡ ቤተክርስቲያን የመጽሐፍ ቅዱስን ባሕርይ የክርስቶስን ባሕርይ በምትረዳበት ሁኔታ ስትረዳ እንደኖረች ታሪክ ያሳያል፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ በአንድ ጊዜ ሰብዓዊም መለኮታዊም ነው፡፡ ፕሮፌሰር ጆርጅ ላድ አንድ ጊዜ እንደተናገሩት፦ “መጽሐፍ ቅዱስ በሰዎች ቃላት በታሪክ ውስጥ የተሰጠ የእግዚአብሔር ቃል ነው፡፡” እንግዲህ ይህ ሁለትዮሽያዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ባሕርይ ነው እንድንተረጉመው የሚያስገድደን፡፡


ይቀጥላል...


ምንጭ:- www.ewnetlehulu.org




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
11👍1
በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ የሰሜኑ እስራኤል ዋና ከተማ ማን ነበርች?
Anonymous Quiz
23%
ኢየሩሳሌም
10%
ደማስቆ
9%
ኬብሮን
58%
ሰማሪያ
.       ──•◈•─────•◈•─
                 የዕለቱ ጥቅስ 
        ──•◈•─────•◈•─
“እግዚአብሔር ልመናዬን ሰማኝ፤ እግዚአብሔር ጸሎቴን ተቀበለ።”
መዝሙር 6፥9


ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
12👎1
በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ እስራኤላውያን ወደ ከነዓን ከገቡ በኋላ ዋና የአምልኮ ማዕከል የነበረው ከተማ የቱ ነው?
Anonymous Quiz
23%
ኢየሩሳሌም
14%
ኬብሮን
23%
ቤቴል
31%
ሴሎ
9%
ሰማሪያ
6
ቅዱሳት መጻሕፍት
#አዲስ_ዓመት #New_Year መጽሐፍ ቅዱስን እንዴት እናንብብ? ጠቃሚ መርሆች              ክፍል-1 መጽሐፍ ቅዱስ ማዕከላዊ መልዕክቱ ለማንኛውም ሰው ግልፅ ሊሆን በሚችልበት ሁኔታ የተቀመጠ ስለሆነ በሁሉም የዕድሜ ክልሎችና በየትኛውም የትምህርት ደረጃ ላይ ላሉ ሰዎች መናገር የሚችል መጽሐፍ ነው፡፡ 2ኛ ጢሞቴዎስ 3፡14-15 ላይ ህጻናት እንኳ የመጽሐፍ ቅዱስን ዋና መልዕክት…
#አዲስ_ዓመት
#New_Year


መጽሐፍ ቅዱስን እንዴት እናንብብ? ጠቃሚ መርሆች



                    ክፍል-2


መጽሐፍ ቅዱስ የእግዚአብሔር ቃል በመሆኑ ዘላለማዊ አስፈላጊነት አለው፤ የእግዚአብሔር ቃል በመሆኑ ልንሰማውና ልንታዘዘው ይገባናል፡፡ ነገር ግን እግዚአብሔር ቃሉን በታሪክ ውስጥ በሰው ቋንቋ ለመናገር ስለመረጠ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ያለ መጽሐፍ ሁሉ ታሪካዊ ውስንነት አለው፡፡ እያንዳንዱ ክፍል መጀመርያ በተጻፈበት ቋንቋ፣ ዘመንና ባሕል የተወሰነ ነው (በአንዳንድ ሁኔታዎች ውስጥ በተጨማሪም በጽሑፍ ከመስፈሩ በፊት በነበረው የአፈታሪክ ትውፊት [የተወሰነ ነው])፡፡ በዘላለማዊ አስፈላጊነቱና  በታሪካዊ ውስንነቱ መካከል ያለው “ውጥረት” መተርጎምን አስፈላጊ ያደርገዋል፡፡ (Gordon D. Fee & Douglas Stuart: How to Read the Bible For All Its Worth, Second Edition, Zondervan, Grand Rapids, 1993, Introduction)

ይህ ርዕስ በጣም ሰፊና ጥልቅ ቢሆንም ነገር ግን መጽሐፍ ቅዱስን በግላቸው ለማጥናትና በትክክል ለመረዳት ለሚሹ ወገኖች ጠቃሚ የሆኑ ምክረ ሐሳቦችን ብቻ አጠር አድርገን እናስቀምጣለን፡፡

በሥነ ፍታቴ ውስጥ ሦስቱ መሠረታውያን ነጥቦች፡- ሐቲት፣ መተርጎምና ማዛመድ ናቸው፡፡

ሐቲት (Exegesis)

“ኤክሰጂሰስ” የሚለው የእንግሊዘኛ ቃል ከግሪክ የተገኘ ነው፤ ትርጉሙም “ማውጣት” እንደማለት ሲሆን አንድ ቃል ለመጀመርዎቹ ተቀባዮች በራሳቸው ቋንቋና ባሕል ምን ማለት እንደነበር ለማግኘት የሚደረግ ሥርዓትን የጠበቀ ጥናት ነው፡፡ በሐቲት ውስጥ ሁለት መሠረታውያን ነጥቦች አሉ፡፡ የመጀመርያው አውድ ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ ይዘት ነው፡፡

1. አውድ

ሁለት ዓይነት አውዶች አሉ፡-

ሀ. ታሪካዊ አውድ

ይህ መጽሐፉ የተጻፈበትን ጊዜና ባሕል የሚመለከት ሲሆን የጸሐፊውንና የተደራሲያኑን መንፈሳዊ፣ ማህበራዊ፣ ፖለቲካዊ፣ ምጣኔ ሃብታዊ፣ መልክአ ምድራዊ አቀማመጥና ሌሎች ከጽሑፉ ይዘትና ትርጉም ጋር ሊገናኙ የሚችሉ ነጥቦችን ሁሉ ከግምት ውስጥ የማስገባት ሥራ ነው፡፡ የሚከተሉትን ጥያቄዎች በመጠየቅ የአንድን የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ታሪካዊ አውድ ማወቅ እንችላለን፡-

👉ጸሐፊው ማነው? (የጸሐፊውን ስም እርግጠኛ በመሆን ማወቅ ቢሳነን እንኳ ከአጻጻፉ በመነሳት ስለ እርሱ መገመት እንችላለን)

👉ተደራሲያኑ እነ ማን ናቸው?

👉መቼ ተጻፈ?

👉የት ተጻፈ?

👉የተጻፈበት ምክንያት ምን ነበር?

ከላይ የተጠቀሱትንና ሌሎች ጥያቄዎችን ብንጠይቅ የመጽሐፉን ታሪካዊ አውድ በቀላሉ ማወቅ እንችላለን፡፡ እነዚህን ለመሳሰሉ ጥያቄዎች ምላሽ ማግኘት ያን ያህል የሚቸግር ባይሆንም ነገር ግን ስለ ጉዳዩ የበለጠ እውቀት ባላቸው ሰዎች የተጻፉ ጥሩ ሐተታዎችንና መዝገበ ቃላትን ብንጠቀም ግንዛቤያችን ይበልጥ ሊሰፋ ይችላል፡፡

ለ.የምንባብ አውድ

ይህ ቀላል የሆነ፣ ነገር ግን ብዙ ሰዎች ትኩረት ስለማይሰጡት በመጽሐፍ ቅዱስ አተረጓጎም ላይ ትልልቅ ስህተቶችን እንዲሰሩ ምክንያት የሚሆናቸው ነጥብ ነው፡፡ የሥነ ፍታቴ ምሑራን የዚህን መርህ አስፈላጊነት አፅንዖት ሰጥተው ሲናገሩ “#ምንባቡ_ንጉሥ_ነው” ይላሉ፡፡ አንድን ቃል፣ ሐረግ ወይንም ደግሞ ዓረፍተ ነገር በምንባብ አውድ ውስጥ መረዳት ማለት ዙሪያ ገባውን በማንበብ በተጻፈበት በዚያ ክፍል መሠረት የሚሰጠውን ትርጉም መረዳት ማለት ነው፡፡ ዛሬ ብዙ ሰዎች፣ በተለይም ደግሞ ሙስሊም ጸሐፍት ይህንን ቀላል መርህ ባይዘነጉ ኖሮ ስለ መጽሐፍ ቅዱስ “ስህተቶችና” “ግጭቶች” ብዙ በመጻፍ ባልደከሙ ነበር፡፡ በተደጋጋሚ የሚነሳውን አንድ ምሳሌ ለመጥቀስ ያህል፤ የምንባብ አውዱን ባንጠብቅ መጽሐፍ ቅዱስን “አምላክ የለም” ልናስብለው እንኳ እንችላለን፡፡ መዝሙር 14፥1 “አምላክ የለም” ይላል፡፡ ነገር ግን ሙሉ ጥቅሱ፡- “ሰነፍ በልቡ አምላክ የለም ይላል። በሥራቸው ረከሱ፥ ጐሰቈሉ በጎ ነገርን የሚሠራ የለም” የሚል ነው፡፡ ብዙ ጊዜ በተለያዩ መጻሕፍት ታትመው የሚወጡ  ስለ መጽሐፍ ቅዱስ “ግጭቶችና” “ስህተቶች” የሚነገሩ አብዘኞቹ ውንጀላዎች ከዚህ የዘለለ ጥልቀት የሌላቸው ናቸው፡፡


ይቀጥላል...


ምንጭ:- www.ewnetlehulu.org




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍43🙏1
.       ──•◈•─────•◈•─
                 የዕለቱ ጥቅስ 
        ──•◈•─────•◈•─
“ሁለት አሳብ ላለው በመንገዱም ሁሉ ለሚወላውል ለዚያ ሰው ከጌታ ዘንድ አንዳች እንዲያገኝ አይምሰለው።”
ያዕቆብ 1፥7-8



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
8👍2🙏1
በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ ኢያሱ ከአሞራውያን ጋር ሲዋጋ ጠላቶቹን እስኪበቀል ድረስ በየትኛው ከተማ ነው ፀሐይ እንድትቆም የጸለየው?
Anonymous Quiz
10%
ኢያሪኮ
7%
ጌልገላ
81%
ገባዖን
2%
ኬብሮን
👍2
ቅዱሳት መጻሕፍት
#አዲስ_ዓመት #New_Year መጽሐፍ ቅዱስን እንዴት እናንብብ? ጠቃሚ መርሆች                     ክፍል-2 መጽሐፍ ቅዱስ የእግዚአብሔር ቃል በመሆኑ ዘላለማዊ አስፈላጊነት አለው፤ የእግዚአብሔር ቃል በመሆኑ ልንሰማውና ልንታዘዘው ይገባናል፡፡ ነገር ግን እግዚአብሔር ቃሉን በታሪክ ውስጥ በሰው ቋንቋ ለመናገር ስለመረጠ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ያለ መጽሐፍ ሁሉ ታሪካዊ ውስንነት አለው፡፡…
#አዲስ_ዓመት
#New_Year


መጽሐፍ ቅዱስን እንዴት እናንብብ? ጠቃሚ መርሆች


            ክፍል-3


የአንድን የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል የምንባብ አውድ ለመረዳት የሚከተሉትን ጥያቄዎች ልናነሳ እንችላለን፡-

👉ተናጋሪው ማነው?

👉ለማነው የተናገረው?

👉ጸሐፊው ለምን ይህንን በዚህ ስፍራ አስገባው?

👉ከፊት ምን ተባለ?

👉ከኋላ ምን ተባለ?

👉ይህ ቃል፣ ሐረግ ወይም አረፍተ ነገር በዚህ ስፍራ ላይ የሚሰጠው ትርጉም ምንድነው?

👉ዋናው ጭብጥ ምንድነው?

ማንኛውንም የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል በተጻፈበት አውድ ውስጥ ለመረዳት እነዚህንና መሰል ቀላል ጥያቄዎች ማንሳት ጠቃሚ ነው፡፡

2. ይዘቱን ማተት

ይዘት ከቃላትና ሐረጎች ትርጉም፣ የሰዋሰው አወቃቀርና በጥንታውያን የእጅ ጽሑፎች ውስጥ የተለያዩ አነባበቦች የሚገኙ ከሆነ ትክክለኛውን ከመምረጥ ጋር ይያያዛል፡፡ እነዚህን ነጥቦች ለማወቅ በዘርፉ ላይ ዕውቀት ባላቸው ሰዎች የተጻፉ የተለያዩ ሐተታዎችንና መዝገበ ቃላትን መጠቀም በጣም አስፈላጊ ነው፡፡

በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ እኛ ከለመድናቸው ትርጉሞች የተለየ ትርጉም ያላቸው ቃላትና ሐረጎች ሊኖሩ ይችላሉ፡፡ እንደምሳሌ ለማንሳት ያህል የጥንት አይሁዳውያን ማንኛውንም የቀን ክፍል እንደ ሙሉ ቀንና ሌሊት ነው የሚቆጥሩት፡፡ ለምሳሌ ሦስት ቀንና ሦስት ሌሊት ማለት የግድ 72 ሰዓታት ማለት ላይሆን ይችላል፡፡ አንዳንድ ጊዜ ደግሞ የአማርኛ ቃላት እንኳ ሆነው በትክክል የማንረዳቸው ቃላትና ሐረጎች ያጋጥማሉ፡፡ 

መጽሐፍ ቅዱስ በተጻፈበት ዘመን የነበሩ የተለያዩ መለኪያዎች፣ የቀን አቆጣጠሮችና የመሳሰሉት እኛ ከምናውቃቸው የተለዩ ስለሆኑ ምን ማለት እንደሆኑ ለማወቅ መዝገበ ቃላትን ወይንም ደግሞ ሐተታዎችን መጠቀም ያስፈልገናል፡፡ ሌላው ስለ ይዘት ሲታሰብ ሊታወቅ የሚገባው ነገር ቢኖር አንዳንድ ጊዜ የዓረፍተ ነገሮች ሰዋሰዋዊ አወቃቀር ዓረፍተ ነገሩ የተለያዩ ሁለት ትርጉሞች እንዲኖሩት ሊያደርግ መቻሉ ነው፡፡ በዚህ ጊዜ ሌሎች ትርጉሞችን ማየት ወይንም ደግሞ ሐተታዎችን በመጠቀም በመጀመርያዎቹ ቋንቋዎች ውስጥ ያለውን ትርጉም መፈለግ ጠቃሚ ነው፡፡

መተርጎም

ይህ ርዕስ እጅግ ሰፊ ከመሆኑ የተነሳ ወደ ውስጥ ጠልቀን በመግባት እያንዳንዱን ነጥብ መተንተን ስለማንችል ጠቅለል ባለ ሁኔታ መሠረታዊውን ሐሳብ ብቻ እናስቀምጣለን፡፡ በመጀመርያው ምዕራፍ ላይ መጽሐፍ ቅዱስ አንድ ዓይነት የሥነ ጽሑፍ ዘይቤን ያልተከተለ መሆኑን ገልፀናል፡፡ ለተለያዩ የሥነ ጽሑፍ ዓይነቶች የተለያዩ አተረጓገሞችን እንጠቀማለን፡፡

#የሕግ_መጻሕፍት- የብሉይ ኪዳን ሕግጋት በ 3 ይከፈላሉ፡፡ እነርሱም:-

ሀ. የግብረገብ ሕግጋት

ለ. የሥርዓት ሕግጋትና

ሐ. የማሕበረሰብ ሕግጋት ናቸው፡፡

የግብረገብ ሕግጋት የማይለወጠውን የእግዚአብሔርን ባሕርይ የሚገልጹ ስለሆኑ ሊለወጡ ወይንም ደግሞ ሊሻሻሉ የሚችሉ አይደሉም፡፡ ስለዚህ እነዚህ ሕግጋት በየትኛውም ዘመን ሊጠበቁ ይገባል፡፡ ለምሳሌ አትግደል፣ አትስረቅ፣ አታመንዝር ወዘተ. የሚሉት እነዚህ ሕግጋት የግብረገብ ሕግጋት ስለሆኑ ዓለም አቀፋዊ ናቸው፡፡ የሥርዓት ሕግጋትና የማሕበረሰብ ሕግጋት ግን ለእስራኤላውያን ብቻ የተሰጡ ናቸው፡፡ የሥርዓት ሕግጋት ስለ መቅደሱ የአምልኮ ሥርዓቶች፣ ስለሚበሉና የማይበሉ እንስሳት፣ ስለ መንጻት ሥርአቶች፣ ወዘተ... የሚናገሩ ናቸው፡፡ አይሁዳውያን ያልሆኑ ሕዝቦች እነዚህን ሕግጋት የመጠበቅ ግዴታ የለባቸውም፡፡ የማሕበረሰብ ሕግጋት ደግሞ የጋብቻ ሥርዓቶች፣ የወንጀለኛ መቅጫ ሕግጋት፣ የካሳ አከፋፈል፣ የንብረት ክፍፍል፣ ወዘተ... ናቸው፡፡ እነዚህ ሕግጋት ሊሠሩ የሚችሉት መለኮታዊ አስተዳደር (Theocracy) ባለበት ቦታ ብቻ ነው፡፡ ስለዚህ የሕግ መጻሕፍትን ስናጠና እነዚህን ሦስቱን በመለየትና የትኞቹ ለእስራኤላውያን ብቻ እንደተሰጡና የትኞቹ ደግሞ ዓለም አቀፋዊ ይዘት እንዳላቸው በመረዳት መሆን አለበት፡፡

ሌላው እዚህ ጋር ሊታወስ የሚገባው ነጥብ ቢኖር አብዛኞቹ የመቅደሱ የአምልኮ ሥርዓቶች ክርስቶስ ኢየሱስን የሚያሳዩ መሆናቸው ነው፡፡ ስለዚህ የትኞቹ በክርስቶስ ሕይወት እንደተፈጸሙ መመልከት ያስፈልገናል፡፡ ይህንን በሚገባ ለመረዳት የዕብራውያንን መጽሐፍ ማንበብ በጣም ጠቃሚ ነው፡፡


ይቀጥላል...


ምንጭ:- www.ewnetlehulu.org




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
4
1ኛና 2ኛ ሳሙኤል.pdf
1.7 MB
1ኛና 2ኛ ሳሙኤል የብሉይ ኪዳን ማብራሪያ


ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
🔥1
.       ──•◈•─────•◈•─
                 የዕለቱ ጥቅስ 
        ──•◈•─────•◈•─
“ታላቅ ተራራ ሆይ፥ አንተ ምንድር ነህ? በዘሩባቤል ፊት ደልዳላ ሜዳ ትሆናለህ፤ ሰዎችም፦ ሞገስ፥ ሞገስ ይሁንለት ብለው እየጮኹ እርሱ መደምደሚያውን ድንጋይ ያወጣል ብሎ ተናገረኝ።”
ዘካርያስ 4፥7



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
12