. ──•◈•─────•◈•─
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“የእምነትህም ኅብረት፥ በእኛ ዘንድ ያለውን በጎ ነገር ሁሉ በማወቅ፥ ለክርስቶስ ኢየሱስ ፍሬ እንዲያፈራ እለምናለሁ፤”
ፊልሞና 1፥6
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“የእምነትህም ኅብረት፥ በእኛ ዘንድ ያለውን በጎ ነገር ሁሉ በማወቅ፥ ለክርስቶስ ኢየሱስ ፍሬ እንዲያፈራ እለምናለሁ፤”
ፊልሞና 1፥6
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤11
. ──•◈•─────•◈•─
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“ነገር ግን መናፍስት ስለ ተገዙላችሁ በዚህ ደስ አይበላችሁ፥ ስማችሁ ግን በሰማያት ስለ ተጻፈ ደስ ይበላችሁ።”
ሉቃስ 10፥20
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“ነገር ግን መናፍስት ስለ ተገዙላችሁ በዚህ ደስ አይበላችሁ፥ ስማችሁ ግን በሰማያት ስለ ተጻፈ ደስ ይበላችሁ።”
ሉቃስ 10፥20
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤11👍6
#ከተማ_ወይም_ቦታ_በቅዱሳት_መጻሕፍት
#ኬብሮን
ኅብረት ማለት ነው። ከኢየሩሳሌም በስተደቡብ 30 ኪ.ሜ. ርቆ ያለ የከነዓናውያን ከተማ። አስቀድሞ ቂርያት አርባቅ ይባል ነበር፤ ኢያሱ 14፥15። ኬብሮን ከባሕሩ ጠለል 927 ሜትር ከፍ ይላል። ከኢየሩሳሌምና ከሌሎች የከነዓን ከተማዎች ከፍታ አለው። አብርሃም በኬብሮን ሰፈረ (ዘፍ. 13፥18)፥ የመቃብርም ቦታ በኬብሮን ገዛ፤ አብርሃምና ሣራ ይስሐቅና ርብቃ፥ ያዕቆብና ልያ በኬብሮን ተቀበሩ፤ ዘፍ. 23፤ 49፥31፤ 50፥13። ዛሬ በመቃብሮቹ ላይ መስጊድ ተሠርቷል። የእስልምና ተከታዮች ቦታውን ይጠብቃሉ። ኢያሱ ኬብሮንን ለካሌብ ሰጠ፤ ኢያሱ 14፥6-15። ኬብሮን ለ7 ዓመት የዳዊት መናገሻ ከተማ ነበረ፤ 2ሳሙ. 5፥5። አቤሴሎም በኬብሮን ተወለደ፥ በዚያም በዳዊት ላይ ዐመፀ፤ 2ሳሙ. 15፥10።
ምንጭ፦ የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት፣ ገጽ 193
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
#ኬብሮን
ኅብረት ማለት ነው። ከኢየሩሳሌም በስተደቡብ 30 ኪ.ሜ. ርቆ ያለ የከነዓናውያን ከተማ። አስቀድሞ ቂርያት አርባቅ ይባል ነበር፤ ኢያሱ 14፥15። ኬብሮን ከባሕሩ ጠለል 927 ሜትር ከፍ ይላል። ከኢየሩሳሌምና ከሌሎች የከነዓን ከተማዎች ከፍታ አለው። አብርሃም በኬብሮን ሰፈረ (ዘፍ. 13፥18)፥ የመቃብርም ቦታ በኬብሮን ገዛ፤ አብርሃምና ሣራ ይስሐቅና ርብቃ፥ ያዕቆብና ልያ በኬብሮን ተቀበሩ፤ ዘፍ. 23፤ 49፥31፤ 50፥13። ዛሬ በመቃብሮቹ ላይ መስጊድ ተሠርቷል። የእስልምና ተከታዮች ቦታውን ይጠብቃሉ። ኢያሱ ኬብሮንን ለካሌብ ሰጠ፤ ኢያሱ 14፥6-15። ኬብሮን ለ7 ዓመት የዳዊት መናገሻ ከተማ ነበረ፤ 2ሳሙ. 5፥5። አቤሴሎም በኬብሮን ተወለደ፥ በዚያም በዳዊት ላይ ዐመፀ፤ 2ሳሙ. 15፥10።
ምንጭ፦ የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት፣ ገጽ 193
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤4👍2
. ──•◈•─────•◈•─
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“ታዳጊህ፥ የእስራኤል ቅዱስ፥ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ እኔ የሚረባህን ነገር የማስተምርህ በምትሄድባትም መንገድ የምመራህ አምላክህ እግዚአብሔር ነኝ።”
ኢሳይያስ 48፥17
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“ታዳጊህ፥ የእስራኤል ቅዱስ፥ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ እኔ የሚረባህን ነገር የማስተምርህ በምትሄድባትም መንገድ የምመራህ አምላክህ እግዚአብሔር ነኝ።”
ኢሳይያስ 48፥17
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤21🙏2
. ──•◈•─────•◈•─
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“ሕይወትና ቸርነት አደረግህልኝ፤ መጐብኘትህም መንፈሴን ጠበቀች።”
ኢዮብ 10፥12
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“ሕይወትና ቸርነት አደረግህልኝ፤ መጐብኘትህም መንፈሴን ጠበቀች።”
ኢዮብ 10፥12
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤10
ራስህን አድን!
ክፍል-1
"ለራስህና ለትምህርትህ ተጠንቀቅ፣ በእነዚህም ጽና፣ ይህን ብታደርግ ራስህንም የሚሰሙህንም ታድናለህና" የሚለውና በ1ኛ ጢሞ.4፥16 ላይ የተመሠረተው የፊኒ ስብከት እንደሚከተለው ነው። “አነሣሴ ሰባኪዎችን ለመስበክ አይደለም። ይልቁንስ በመነሻ ንባቡ ላይ ቃል የተገባውን ደኅንነት በእርግጠኝነት ይጨብጡት ዘንድ አንዳንድ ነጥቦችን ለማመላከት ነው” በማለት የጀመረው ታላቁ ወንጌላዊ ቻርልስ ፊኒ መልእክቱን በተራ ቁጥሮች በመደርደር እንዲህ አስቀምጧቸዋል።
1) ወንጌልን የምትሰብከው ልክ እንደ ክርስቶስ ፍቅር ግድ ብሎህ እንደሆነ እርግጠኛ ሁን።
2) ኃይል እንደወረደብህ በመንፈስ ቅዱስም እንደተጠመቅህ አረጋግጥ።
3) ወንጌልን መስበክ ወደአእምሮህ ሽው ያለ አሳብ ሳይሆን ውስጥህን የሞላ ነገር መሆኑን እርግጠኛ ሁን። ይህንን ስል የሌሎች መዳን ልብህን የሞላ በጽኑ ምኞትም የተደገፈ ይሁን ማለቴ ነው። ልብህ ያላረፈበትን አታድርግ።
4) ከእግዚአብሔር ጋር ተጣብቀህ መራመድን አታቋርጥ።
5) መጽሐፍ ቅዱስ ቁጥር አንድ መጽሐፍህ ይሁን። መለኮታዊውን ብርሃን እየተጠባበቅህ ተንበርክከህና አብዝተህ አጥናው።
6)ማብራሪያዎችን ስታጠና ተጠንቀቅ። እንደ አመቺነቱ አንብባቸው። ግን የራስህን ሚዛህ በመንፈስ ቅዱስ ብርሃን ጠብቅ።
7)ስትናገርም ይሁን ስትሠራ ፍቃድህን፤ አሳብና ድርጊትህን በንጽሕና ጠብቅ።
8) ይድኑ ዘንድ ያለህ ፍላጎት እንዲበረታ ኃጢአተኞች የሚጋፈጡት አደጋና ፀፀት ከአሳብህ አይጥፋ።
9) ደግሞም ክርስቶስ ለኃጢአተኞች ያለውን ገደብ የለሽ ርኅራኄና ፍቅር አሰላስል።
10) ስለዚህ አንተም ልትሞትላቸው እስከመፍቀድ ድረስ ውደዳቸው።
11) መላ አስተሳሰብህን ሰዎችን እንዴት ማዳን እንደምትችል ለማሰላሰል አውለው። ትልቁና የምታተኩርበት የጥናትህ ክፍልም ይሄ ይሁን።
12)ከጽኑ መሻትህ ሊጎትትህ ከሚሞክር ማንኛውም ፈተና ራስህን ጠብቅ። ከዚህ ተልዕኮ አሳብህ እንዲነሣ ከቶም አትፍቀድ።
13) ለዚህ ሥራ በሚያስፈልግህ ሁሉ ይረዳህ ዘንድ ክርስቶስ ሁልጊዜና በሁሉም ሥፍራ አብሮህ እንዳለ ጽኑ እምነት ይኑርህ።
14)"ነፍሶችንም የሚሰበስብ እርሱ ጠቢብ ነው" (ምሳ11፥30)። "ከእናንተ ግን ማንም ጥበብ ቢጎድለው፥ ሳይነቅፍ በልግስና ለሁሉ የሚሰጠውን እግዚአብሔርን ይለምን፥ ለእርሱም ይሰጠዋል"(ያዕ1፥5) ተብሎ ተጽፎአል። ስለሆነም ይህን አስታውስ። ነፍሳትን ለክርስቶስ ማሸነፍ የሚያስችል ጥበብ ይኑርህ።
15) በእግዚአብሔር ለሥራው ከተጠራህ ከእርሱ ጋር የምትሟገተው ለስኬታማነት የሚያስፈልግህን ሁሉ ታገኝ ዘንድ ይሁን።
16) በጊዜውም ያለጊዜውም (2 ጢሞ.4፥2) ጠንቃቃና ትጉ ሁን።
ይቀጥላል.....
ምንጭ:- alemayehuwrites.blogspot.com
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ክፍል-1
"ለራስህና ለትምህርትህ ተጠንቀቅ፣ በእነዚህም ጽና፣ ይህን ብታደርግ ራስህንም የሚሰሙህንም ታድናለህና" የሚለውና በ1ኛ ጢሞ.4፥16 ላይ የተመሠረተው የፊኒ ስብከት እንደሚከተለው ነው። “አነሣሴ ሰባኪዎችን ለመስበክ አይደለም። ይልቁንስ በመነሻ ንባቡ ላይ ቃል የተገባውን ደኅንነት በእርግጠኝነት ይጨብጡት ዘንድ አንዳንድ ነጥቦችን ለማመላከት ነው” በማለት የጀመረው ታላቁ ወንጌላዊ ቻርልስ ፊኒ መልእክቱን በተራ ቁጥሮች በመደርደር እንዲህ አስቀምጧቸዋል።
1) ወንጌልን የምትሰብከው ልክ እንደ ክርስቶስ ፍቅር ግድ ብሎህ እንደሆነ እርግጠኛ ሁን።
2) ኃይል እንደወረደብህ በመንፈስ ቅዱስም እንደተጠመቅህ አረጋግጥ።
3) ወንጌልን መስበክ ወደአእምሮህ ሽው ያለ አሳብ ሳይሆን ውስጥህን የሞላ ነገር መሆኑን እርግጠኛ ሁን። ይህንን ስል የሌሎች መዳን ልብህን የሞላ በጽኑ ምኞትም የተደገፈ ይሁን ማለቴ ነው። ልብህ ያላረፈበትን አታድርግ።
4) ከእግዚአብሔር ጋር ተጣብቀህ መራመድን አታቋርጥ።
5) መጽሐፍ ቅዱስ ቁጥር አንድ መጽሐፍህ ይሁን። መለኮታዊውን ብርሃን እየተጠባበቅህ ተንበርክከህና አብዝተህ አጥናው።
6)ማብራሪያዎችን ስታጠና ተጠንቀቅ። እንደ አመቺነቱ አንብባቸው። ግን የራስህን ሚዛህ በመንፈስ ቅዱስ ብርሃን ጠብቅ።
7)ስትናገርም ይሁን ስትሠራ ፍቃድህን፤ አሳብና ድርጊትህን በንጽሕና ጠብቅ።
8) ይድኑ ዘንድ ያለህ ፍላጎት እንዲበረታ ኃጢአተኞች የሚጋፈጡት አደጋና ፀፀት ከአሳብህ አይጥፋ።
9) ደግሞም ክርስቶስ ለኃጢአተኞች ያለውን ገደብ የለሽ ርኅራኄና ፍቅር አሰላስል።
10) ስለዚህ አንተም ልትሞትላቸው እስከመፍቀድ ድረስ ውደዳቸው።
11) መላ አስተሳሰብህን ሰዎችን እንዴት ማዳን እንደምትችል ለማሰላሰል አውለው። ትልቁና የምታተኩርበት የጥናትህ ክፍልም ይሄ ይሁን።
12)ከጽኑ መሻትህ ሊጎትትህ ከሚሞክር ማንኛውም ፈተና ራስህን ጠብቅ። ከዚህ ተልዕኮ አሳብህ እንዲነሣ ከቶም አትፍቀድ።
13) ለዚህ ሥራ በሚያስፈልግህ ሁሉ ይረዳህ ዘንድ ክርስቶስ ሁልጊዜና በሁሉም ሥፍራ አብሮህ እንዳለ ጽኑ እምነት ይኑርህ።
14)"ነፍሶችንም የሚሰበስብ እርሱ ጠቢብ ነው" (ምሳ11፥30)። "ከእናንተ ግን ማንም ጥበብ ቢጎድለው፥ ሳይነቅፍ በልግስና ለሁሉ የሚሰጠውን እግዚአብሔርን ይለምን፥ ለእርሱም ይሰጠዋል"(ያዕ1፥5) ተብሎ ተጽፎአል። ስለሆነም ይህን አስታውስ። ነፍሳትን ለክርስቶስ ማሸነፍ የሚያስችል ጥበብ ይኑርህ።
15) በእግዚአብሔር ለሥራው ከተጠራህ ከእርሱ ጋር የምትሟገተው ለስኬታማነት የሚያስፈልግህን ሁሉ ታገኝ ዘንድ ይሁን።
16) በጊዜውም ያለጊዜውም (2 ጢሞ.4፥2) ጠንቃቃና ትጉ ሁን።
ይቀጥላል.....
ምንጭ:- alemayehuwrites.blogspot.com
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤13
. ──•◈•─────•◈•─
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“እኔም የዘላለም ሕይወትን እሰጣቸዋለሁ፥ ለዘላለምም አይጠፉም፥ ከእጄም ማንም አይነጥቃቸውም።”
ዮሐንስ 10፥28
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“እኔም የዘላለም ሕይወትን እሰጣቸዋለሁ፥ ለዘላለምም አይጠፉም፥ ከእጄም ማንም አይነጥቃቸውም።”
ዮሐንስ 10፥28
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤8
ራስህን አድን!
ክፍል ሁለት
17) አሳባቸውን፣ ስሕተታቸውንና ፍላጎታቸውን ለመረዳት ትችል ዘንድ ስለመዳን ባላቸው ጥያቄ ላይ ከሁሉም ዓይነት አድማጮችህ ጋር አብዝተህ ተነጋገር። ትምህርትህን ከነርሱ ፍላጎት ጋር ለማዛመድ ትችል ዘንድ አመለካከታቸውንና ስሜታቸውን አጢን። ልማዶቻቸውን ልብ በል። ምን እንደተጋረደባቸውም አስተውል። ማወቅ የሚገባህን ሁሉ እወቅ።
18) ሥራዬ ብለህ የምታደርጋቸው ሁሉ ትክክል መሆናቸውን አያያዝህም ርጋታ ያለተለየው መሆኑን:አጢን። ከትንባሆ፤ የአልኮል መጠጥና አደንዛዥ ዕፆች ሌሎችም አንተን ሊያሳፍሩ ሌሎችንም ሊያሰናክሉ ከሚችሉ ነገሮች እድፍና ጠረን ነፃ መሆንህን ርግጠኛ ሁን።
19) ቁርጠኝነት አይጉደልህ፤ ነገር ግን ሁልጊዜ እግዚአብሔርን አስቀድም (መዝ. 16:8)።
20) ለአንደበትህ ልጓም አብጅለት፤ ለከንቱና ዋጋ ቢስ ንግግር ራስህን አሳልፈህ አትስጥ።
21) መድረክ ላይ ስትወጣም ይሁን ከዚያ ስትወርድ ቁርጠኛና እርግጠኛ መሆንህንሰዎች ይረዱት። ከእነርሱ ጋር ያለህ የዕለት ተዕለት ግንኙነት በሰንበት ቀን የምታቀርበውን ወሳኝ ትምህርት ዋጋ ቢስ አያድርገው።
22) ከተሰቀለው ኢየሱስ ክርስቶስ በቀር ሌላ እንደማታውቅ ለሚቀርቡህ ሁሉ ይታወቅ። በክርስቶስ አምባሣደርነትህ ከእነርሱ ጋር ያለህ ሕብረት ስለነፍሳቸው መዳን ብቻ መሆኑን ይረዱት።
23) መሆን አለበት:ብለህ የምታስተምረውን በምሳሌነት አሳይ። የምትሰብከውን ኑር።
24) ያልሆነ አሳብ ወይም ጥርጣሬ እንዳያስከትልና ንጽሕናህን እንዳይነካ በተለይ ከሴቶች ጋር ስለሚኖርህ ግንኙነት ተጠንቀቅ።
25) ደካማ ጎኖችህን ተከላከል። አላስፈላጊ ወደሆነ ነገርም ይሁን ርካሽ ፈንጠዝያ ፍለጋ ወደዚያ አቅጣጫ ከሚያዘሙህ አጋጣሚዎች ተጠንቀቅ።
26) በተፈጥሮህ ኮስታራ ወይም ገለልተኛ ከሆንክ መራራና ሰዎችን የማትቀርብ ሆነህ እንዳትቆጠር ተጠንቀቅ።
27) የሰውን ጆሮ ለማግኘት ብቻ የሚደረግን ጥረትና ካባ የለበሰ ውሸትን አስወግድ። ያኔ የማስመሰል ድርጊት ለመፈጸም አትፈተንም።
28) ጽናት፣ እውነተኝነትና ክርስቲያናዊ ባለቤትነት የሁለንተናዊ ኑሮህ መለያ ይሁኑ።
29) በቀንም ይሁን በማታ ሁልጊዜ ለጸሎትና ከእግዚአብሔር ጋር ሕብረት ለማድረግ ብዙ ጊዜ ውሰድ። ይህም ለማዳን ብዙ ኃይል ይሆንልሃል። የዚህን ሕብረት መታጣት ግን የትኛውም ዓይነት ትምህርት ይሁን ጥናት ሊያካካሰው አይችልም። ከእግዚአብሔር ጋር ሕብረት ከሌለህ እንደማንኛውም ሰው ደካማ ነህ።
30) ዳግም ልደት የለም የሚለውንና ያንንም ተከትሎ የነፍሳትን መዳን የሚጠራጠረውን ስሕተት አስወግድ።
31) ዳግም ልደት የሞራልና ይልቁንም የፍቃደኝነት ለውጥ መሆኑን ልብ በል።
32) ወንጌል የሰዎችን ልብ መለወጥ እንደሚችል ሆኖ ተዘጋጅቷል። ያንን በጥበብ ስትሰብከው ደግሞ ከመንፈስ ቅዱስ ውጤታማ እገዛ እንደምታገኝ ጠብቅ።
ይቀጥላል.....
ምንጭ:- alemayehuwrites.blogspot.com
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ክፍል ሁለት
17) አሳባቸውን፣ ስሕተታቸውንና ፍላጎታቸውን ለመረዳት ትችል ዘንድ ስለመዳን ባላቸው ጥያቄ ላይ ከሁሉም ዓይነት አድማጮችህ ጋር አብዝተህ ተነጋገር። ትምህርትህን ከነርሱ ፍላጎት ጋር ለማዛመድ ትችል ዘንድ አመለካከታቸውንና ስሜታቸውን አጢን። ልማዶቻቸውን ልብ በል። ምን እንደተጋረደባቸውም አስተውል። ማወቅ የሚገባህን ሁሉ እወቅ።
18) ሥራዬ ብለህ የምታደርጋቸው ሁሉ ትክክል መሆናቸውን አያያዝህም ርጋታ ያለተለየው መሆኑን:አጢን። ከትንባሆ፤ የአልኮል መጠጥና አደንዛዥ ዕፆች ሌሎችም አንተን ሊያሳፍሩ ሌሎችንም ሊያሰናክሉ ከሚችሉ ነገሮች እድፍና ጠረን ነፃ መሆንህን ርግጠኛ ሁን።
19) ቁርጠኝነት አይጉደልህ፤ ነገር ግን ሁልጊዜ እግዚአብሔርን አስቀድም (መዝ. 16:8)።
20) ለአንደበትህ ልጓም አብጅለት፤ ለከንቱና ዋጋ ቢስ ንግግር ራስህን አሳልፈህ አትስጥ።
21) መድረክ ላይ ስትወጣም ይሁን ከዚያ ስትወርድ ቁርጠኛና እርግጠኛ መሆንህንሰዎች ይረዱት። ከእነርሱ ጋር ያለህ የዕለት ተዕለት ግንኙነት በሰንበት ቀን የምታቀርበውን ወሳኝ ትምህርት ዋጋ ቢስ አያድርገው።
22) ከተሰቀለው ኢየሱስ ክርስቶስ በቀር ሌላ እንደማታውቅ ለሚቀርቡህ ሁሉ ይታወቅ። በክርስቶስ አምባሣደርነትህ ከእነርሱ ጋር ያለህ ሕብረት ስለነፍሳቸው መዳን ብቻ መሆኑን ይረዱት።
23) መሆን አለበት:ብለህ የምታስተምረውን በምሳሌነት አሳይ። የምትሰብከውን ኑር።
24) ያልሆነ አሳብ ወይም ጥርጣሬ እንዳያስከትልና ንጽሕናህን እንዳይነካ በተለይ ከሴቶች ጋር ስለሚኖርህ ግንኙነት ተጠንቀቅ።
25) ደካማ ጎኖችህን ተከላከል። አላስፈላጊ ወደሆነ ነገርም ይሁን ርካሽ ፈንጠዝያ ፍለጋ ወደዚያ አቅጣጫ ከሚያዘሙህ አጋጣሚዎች ተጠንቀቅ።
26) በተፈጥሮህ ኮስታራ ወይም ገለልተኛ ከሆንክ መራራና ሰዎችን የማትቀርብ ሆነህ እንዳትቆጠር ተጠንቀቅ።
27) የሰውን ጆሮ ለማግኘት ብቻ የሚደረግን ጥረትና ካባ የለበሰ ውሸትን አስወግድ። ያኔ የማስመሰል ድርጊት ለመፈጸም አትፈተንም።
28) ጽናት፣ እውነተኝነትና ክርስቲያናዊ ባለቤትነት የሁለንተናዊ ኑሮህ መለያ ይሁኑ።
29) በቀንም ይሁን በማታ ሁልጊዜ ለጸሎትና ከእግዚአብሔር ጋር ሕብረት ለማድረግ ብዙ ጊዜ ውሰድ። ይህም ለማዳን ብዙ ኃይል ይሆንልሃል። የዚህን ሕብረት መታጣት ግን የትኛውም ዓይነት ትምህርት ይሁን ጥናት ሊያካካሰው አይችልም። ከእግዚአብሔር ጋር ሕብረት ከሌለህ እንደማንኛውም ሰው ደካማ ነህ።
30) ዳግም ልደት የለም የሚለውንና ያንንም ተከትሎ የነፍሳትን መዳን የሚጠራጠረውን ስሕተት አስወግድ።
31) ዳግም ልደት የሞራልና ይልቁንም የፍቃደኝነት ለውጥ መሆኑን ልብ በል።
32) ወንጌል የሰዎችን ልብ መለወጥ እንደሚችል ሆኖ ተዘጋጅቷል። ያንን በጥበብ ስትሰብከው ደግሞ ከመንፈስ ቅዱስ ውጤታማ እገዛ እንደምታገኝ ጠብቅ።
ይቀጥላል.....
ምንጭ:- alemayehuwrites.blogspot.com
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤7👏1
. ──•◈•─────•◈•─
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“የዚያን ጊዜ እግዚአብሔርን የሚፈሩ እርስ በእርሳቸው ተነጋገሩ፤ እግዚአብሔርም አደመጠ፥ ሰማም፥ እግዚአብሔርንም ለሚፈሩ ስሙንም ለሚያስቡ የመታሰቢያ መጽሐፍ በፊቱ ተጻፈ።”
ሚልክያስ 3፥16
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“የዚያን ጊዜ እግዚአብሔርን የሚፈሩ እርስ በእርሳቸው ተነጋገሩ፤ እግዚአብሔርም አደመጠ፥ ሰማም፥ እግዚአብሔርንም ለሚፈሩ ስሙንም ለሚያስቡ የመታሰቢያ መጽሐፍ በፊቱ ተጻፈ።”
ሚልክያስ 3፥16
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤🔥11❤1
#እራሳችንን_እንመርምር
“አቤቱ፥ ፍጻሜዬን አስታውቀኝ፥ የዘመኔ ቍጥሮች ምን ያህል እንደ ሆኑ፥ እኔ ምን ያህል ወደ ኋላ እንደምቀር አውቅ ዘንድ።”
መዝሙር 39፥4
“እግዚአብሔር ሆይ፤ የሕይወቴን ፍጻሜ፣ የዘመኔንም ቍጥር አስታውቀኝ፤ አላፊ ጠፊ መሆኑንም ልረዳ።”
መዝሙር 39፥4 (አዲሱ መ.ት)
እግዚአብሔር ሆይ ፥ የሕይወቴ ፍጻሜ መቼ እንደ ሆነና የዕድሜዬ ልክ ስንት እንደ ሆነ ግለጽልኝ፤ በዚህ ዓለም የምኖረው ዘመን ፈጥኖ የሚያልፍ መሆኑን ለማወቅ አስችለኝ።"
መዝሙር 39፥4 (ሕያው ቃል)
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
“አቤቱ፥ ፍጻሜዬን አስታውቀኝ፥ የዘመኔ ቍጥሮች ምን ያህል እንደ ሆኑ፥ እኔ ምን ያህል ወደ ኋላ እንደምቀር አውቅ ዘንድ።”
መዝሙር 39፥4
“እግዚአብሔር ሆይ፤ የሕይወቴን ፍጻሜ፣ የዘመኔንም ቍጥር አስታውቀኝ፤ አላፊ ጠፊ መሆኑንም ልረዳ።”
መዝሙር 39፥4 (አዲሱ መ.ት)
እግዚአብሔር ሆይ ፥ የሕይወቴ ፍጻሜ መቼ እንደ ሆነና የዕድሜዬ ልክ ስንት እንደ ሆነ ግለጽልኝ፤ በዚህ ዓለም የምኖረው ዘመን ፈጥኖ የሚያልፍ መሆኑን ለማወቅ አስችለኝ።"
መዝሙር 39፥4 (ሕያው ቃል)
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤8👏4
. ──•◈•─────•◈•─
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“አካሄድን እንደ ቃልህ አቅና፤ ኃጢአትም ሁሉ አይግዛኝ።”
መዝሙር 119፥133
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“አካሄድን እንደ ቃልህ አቅና፤ ኃጢአትም ሁሉ አይግዛኝ።”
መዝሙር 119፥133
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤7👏1
Forwarded from Tabor Bible Study (ሐዋሳ ታቦር መካነ ኢየሱስ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት)
እንደሚታወቀው ከፈረንጆቹ October 1-31 የተሐድሶ ወር በመባል በሉተራዊያን ዘንድ ወር በሙሉ ስለተሐድሶ ይወሳል፣ ውይይት ይደረጋል ይዘከራልም። ይህን በማስመልከት እኛም ይህን ወር በልዩ ሁኔታ ለማስታወስ በተለያዩ ትምህርቶች፣ ውይይቶች፣ እጅግ ለየት ያሉ ፕሮግራሞችን አዘጋጅተን ጨርሰናል። በቅርብ ቀን በዚህ ቻናል ብቻ ይጠብቁን
#ተሐድሶ
#reformation
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል👉 @TME_bible_study
#ተሐድሶ
#reformation
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል👉 @TME_bible_study
👍9❤3👏3