#ከተማ_ወይም_ቦታ_በቅዱሳት_መጻሕፍት
ቅፍርናሆም
#ቅፍርናሆም ( ዕብራይስጥ : כְּפַר נַחוּם፣ Kfar Nachum) "የናሆም መንደር" ወይም "የመጽናናት መንደር" ማለት ነው። "ናሆም" ማንን እንደሚያመለክት ግልጽ አይደለም። ምናልባት ከብሉይ ኪዳን የመጣው ነቢዩ ናሆም ላይሆን ይችላል ነገር ግን ስሙ አሁንም ከማጽናናት ወይም ከርህራሄ ጋር የተያያዘ ትርጉሙን ይይዛል።
ቅፍርናሆም በገሊላ ባሕር ዳር በስተሰሜን ያለች ከተማ። ክርስቶስ እየተዘዋወረ ሲሰብክ መኖሪያው በቅፍርናሆም ነበር፤ ማቴ. 4፥13-16። የዘብዴዎስና የጴጥሮስ አገር (ማር. 1፥29-31)፥ ማቴዎስም ከቅፍርናሆም ተጠራ፤ ማቴ. 9፡9። በቅፍርናሆም በአንድ መቶ አለቃ የተሠራ ምኵራብ ነበር፤ ሉቃ. 7፥1-9። ከምኵራብ አለቆች አንዱ ኢያኢሮስ ነበረ፤ ማር. 5፥22። በቅፍርናሆም ክርስቶስ ብዙ አስደናቂ ተአምራትን አደረገ (ማቴ. 8፥5-13፤ ማር. 2፥1-12፤ ዮሐ. 4፥46-54)፥ አስፈላጊ እና ውጤታማ የአሳ ማጥመጃና የንግድ ዋና ቦታ የነበረችው፣ የአህዛብ እና የአይሁድ መኖሪያ ነበር። የመጀመሪያው መቶ አመት የህዝብ ብዛት ከ፩ ሺህ በላይ አልነበሩም። ቅፍርናሆም በለማ ቦታ ተከብቦ፣ የአስፈላጊ የንግድ መንገድ የሚገኝበት ነበር። የሮሜ ወታደሮች ገንዳ መታጠቢያ እና ማከማቻ ቦታዎችን በእዚህ ገነቡ። ከጊዜ በኋላም፣ ቅፍርናሆም ተሰባበረች እናም በእዚያ የሚኖሩትም ወጥተው ሄዱ።
ታላቅ ድርጊቶች፥ ቅፍርናሆም የአዳኝ የእርሱ ከተማ ነበር ተብሎ ይታወቃል (ማቴ. 9፥1–2፤ ማር. 2፥1–5)። በእዚህ ቦታ ብዙ ተዓምራትሰራ። ለምሳሌ፣ ከመቶ አለቃ አገልጋይ (ሉቃ. 7፥1–10)፣ ከጴጥሮስ አማች (ማር. 1፥21፣ 29–31)፣ በጣራ በኩል መኝታው ከወረደው ሽባ (ማር. 2፥1–12)፣ እና እጁ ከሰለለች ሰው (ማቴ. 12፥9–13) በተጨማሪ ብዙ ሰዎችን ፈወሰ (ማር. 1፥32–34 )። በዚህም ብዙ እርኩስ መንፈሶችን አስወጣ (ማር. 1፥21–28፣ 32–34)፣ የኢያኢሮስ ሴት ልጅን ከሞት አስነሳ (ማቴ. 9፥18–19፣ 23–26፤ ማር. 5፥22-24፣ 35-43)፣ እና በቅፍርናሆም ምኩራብ የህይወት-እንጀራ የሚለውን ስብከትን ሰጠ (ዮሐ. 6፥24–59)። አዳኝ ጴጥሮስን ከገሊላ ባህር አሳ እንዲያጠምድ፣ አፉን እንዲከፍት፣ እና ቀረጥ የሚከፍልበት ሳንቲም እንዲያገኝ አዘዘው (ማቴ. 17፥24-27)። ነገር ግን የቅፍርናሆም ሰዎች አላመኑምና ክርስቶስ በቅፍርናሆም ላይ የፍርድ ትንቢት ተናገረባት፤ ማቴ. 11፥23:24። ዛሬ ሰው አይኖርባትም።
ምንጭ፦
የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት ገጽ 98፣
Elwell, W. A., & Beitzel, B. J. (1988). Baker encyclopedia of the Bible (Vol. 1, pp. 381–382). Baker Book House.
www.churchofjesuschrist.org
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ቅፍርናሆም
#ቅፍርናሆም ( ዕብራይስጥ : כְּפַר נַחוּם፣ Kfar Nachum) "የናሆም መንደር" ወይም "የመጽናናት መንደር" ማለት ነው። "ናሆም" ማንን እንደሚያመለክት ግልጽ አይደለም። ምናልባት ከብሉይ ኪዳን የመጣው ነቢዩ ናሆም ላይሆን ይችላል ነገር ግን ስሙ አሁንም ከማጽናናት ወይም ከርህራሄ ጋር የተያያዘ ትርጉሙን ይይዛል።
ቅፍርናሆም በገሊላ ባሕር ዳር በስተሰሜን ያለች ከተማ። ክርስቶስ እየተዘዋወረ ሲሰብክ መኖሪያው በቅፍርናሆም ነበር፤ ማቴ. 4፥13-16። የዘብዴዎስና የጴጥሮስ አገር (ማር. 1፥29-31)፥ ማቴዎስም ከቅፍርናሆም ተጠራ፤ ማቴ. 9፡9። በቅፍርናሆም በአንድ መቶ አለቃ የተሠራ ምኵራብ ነበር፤ ሉቃ. 7፥1-9። ከምኵራብ አለቆች አንዱ ኢያኢሮስ ነበረ፤ ማር. 5፥22። በቅፍርናሆም ክርስቶስ ብዙ አስደናቂ ተአምራትን አደረገ (ማቴ. 8፥5-13፤ ማር. 2፥1-12፤ ዮሐ. 4፥46-54)፥ አስፈላጊ እና ውጤታማ የአሳ ማጥመጃና የንግድ ዋና ቦታ የነበረችው፣ የአህዛብ እና የአይሁድ መኖሪያ ነበር። የመጀመሪያው መቶ አመት የህዝብ ብዛት ከ፩ ሺህ በላይ አልነበሩም። ቅፍርናሆም በለማ ቦታ ተከብቦ፣ የአስፈላጊ የንግድ መንገድ የሚገኝበት ነበር። የሮሜ ወታደሮች ገንዳ መታጠቢያ እና ማከማቻ ቦታዎችን በእዚህ ገነቡ። ከጊዜ በኋላም፣ ቅፍርናሆም ተሰባበረች እናም በእዚያ የሚኖሩትም ወጥተው ሄዱ።
ታላቅ ድርጊቶች፥ ቅፍርናሆም የአዳኝ የእርሱ ከተማ ነበር ተብሎ ይታወቃል (ማቴ. 9፥1–2፤ ማር. 2፥1–5)። በእዚህ ቦታ ብዙ ተዓምራትሰራ። ለምሳሌ፣ ከመቶ አለቃ አገልጋይ (ሉቃ. 7፥1–10)፣ ከጴጥሮስ አማች (ማር. 1፥21፣ 29–31)፣ በጣራ በኩል መኝታው ከወረደው ሽባ (ማር. 2፥1–12)፣ እና እጁ ከሰለለች ሰው (ማቴ. 12፥9–13) በተጨማሪ ብዙ ሰዎችን ፈወሰ (ማር. 1፥32–34 )። በዚህም ብዙ እርኩስ መንፈሶችን አስወጣ (ማር. 1፥21–28፣ 32–34)፣ የኢያኢሮስ ሴት ልጅን ከሞት አስነሳ (ማቴ. 9፥18–19፣ 23–26፤ ማር. 5፥22-24፣ 35-43)፣ እና በቅፍርናሆም ምኩራብ የህይወት-እንጀራ የሚለውን ስብከትን ሰጠ (ዮሐ. 6፥24–59)። አዳኝ ጴጥሮስን ከገሊላ ባህር አሳ እንዲያጠምድ፣ አፉን እንዲከፍት፣ እና ቀረጥ የሚከፍልበት ሳንቲም እንዲያገኝ አዘዘው (ማቴ. 17፥24-27)። ነገር ግን የቅፍርናሆም ሰዎች አላመኑምና ክርስቶስ በቅፍርናሆም ላይ የፍርድ ትንቢት ተናገረባት፤ ማቴ. 11፥23:24። ዛሬ ሰው አይኖርባትም።
ምንጭ፦
የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት ገጽ 98፣
Elwell, W. A., & Beitzel, B. J. (1988). Baker encyclopedia of the Bible (Vol. 1, pp. 381–382). Baker Book House.
www.churchofjesuschrist.org
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤11👍1
ከሚከተሉት በቅዱሳት መጻሕፍት ከሚገኙ በሐዋርያው ጳውሎስ ከተጻፉ መጻሕፍት ውስጥ በእስር ቤት ያልተጻፈው መጽሐፍ የቱ ነው?
Anonymous Quiz
23%
ሀ. ኤፌሶን
48%
ለ. ቲቶ
13%
ሐ. ፊልጵስዩስ
16%
መ. ቆላስይስ
❤3
. ──•◈•─────•◈•─
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“ክርስቶስ በእጅ ወደ ተሰራች፥ የእውነተኛይቱ ምሳሌ ወደ ምትሆን ቅድስት አልገባምና፥ ነገር ግን በእግዚአብሔር ፊት ስለ እኛ አሁን ይታይ ዘንድ ወደ እርስዋ ወደ ሰማይ ገባ።”
ዕብራውያን 9፥24
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“ክርስቶስ በእጅ ወደ ተሰራች፥ የእውነተኛይቱ ምሳሌ ወደ ምትሆን ቅድስት አልገባምና፥ ነገር ግን በእግዚአብሔር ፊት ስለ እኛ አሁን ይታይ ዘንድ ወደ እርስዋ ወደ ሰማይ ገባ።”
ዕብራውያን 9፥24
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤11❤🔥1
#የእግዚአብሔር_ቃል_ምን_ይላል?
መዝሙር 27
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ እግዚአብሔር ብርሃኔና መድኃኒቴ ነው፤ የሚያስፈራኝ ማን ነው? እግዚአብሔር የሕይወቴ መታመኛዋ ነው፤ የሚያስደነግጠኝ ማን ነው?
² ክፉዎች፥ አስጨናቂዎቼ ጠላቶቼም፥ ሥጋዬን ይበሉ ዘንድ በቀረቡ ጊዜ፥ እነርሱ ተሰናከሉና ወደቁ።
³ ሠራዊትም ቢሰፍርብኝ ልቤ አይፈራም፤ ሰልፍም ቢነሣብኝ በዚህ እተማመናለሁ።
⁴ እግዚአብሔርን አንዲት ነገር ለመንሁት እርስዋንም እሻለሁ፤ በሕይወቴ ዘመን ሁሉ በእግዚአብሔር ቤት እኖር ዘንድ፥ እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኘውንም አይ ዘንድ፥ መቅደሱንም እመለከት ዘንድ።
⁵ በመከራዬ ቀን በድንኳኑ ሰውሮኛልና፥ በድንኳኑም መሸሸጊያ ሸሽጎኛልና፥ በዓለት ላይ ከፍ ከፍ አድርጎኛልና።
⁶ እነሆ፥ አሁን በዙሪያ ባሉ በጠላቶቼ ላይ ራሴን ከፍ ከፍ አደረገ፤ በድንኳኑም የእልልታ መሥዋዕትን ሠዋሁ፥ ለእግዚአብሔር እቀኛለሁ እዘምርለትማለሁ።
⁷ አቤቱ፥ ወደ አንተ የጮኽሁትን ቃሌን ስማኝ፤ ማረኝና አድምጠኝ።
⁸ አንተ ፊቴን እሹት ባልህ ጊዜ፦ አቤቱ፥ ፊትህን እሻለሁ ልቤ አንተን አለ።
⁹ ፊትህን ከእኔ አትሰውር፥ ተቈጥተህ ከባሪያህ ፈቀቅ አትበል፤ ረዳት ሁነኝ፥ አትጣለኝም፥ የመድኃኒቴም አምላክ ሆይ፥ አትተውኝ።
¹⁰ አባቴና እናቴ ትተውኛልና፥ እግዚአብሔር ግን ተቀበለኝ።
¹¹ አቤቱ፥ መንገድህን አስተምረኝ፥ ስለ ጠላቶቼም በቀና መንገድ ምራኝ።
¹² የሐሰት ምስክሮችና ዓመፀኞች ተነሥተውብኛልና ለጠላቶቼ ፈቃድ አትስጠኝ።
¹³ የእግዚአብሔርን ቸርነት በሕያዋን ምድር አይ ዘንድ አምናለሁ።
¹⁴ እግዚአብሔርን ተስፋ አድርግ፤ በርታ፥ ልብህም ይጽና፤ እግዚአብሔርን ተስፋ አድርግ።
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
መዝሙር 27
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ እግዚአብሔር ብርሃኔና መድኃኒቴ ነው፤ የሚያስፈራኝ ማን ነው? እግዚአብሔር የሕይወቴ መታመኛዋ ነው፤ የሚያስደነግጠኝ ማን ነው?
² ክፉዎች፥ አስጨናቂዎቼ ጠላቶቼም፥ ሥጋዬን ይበሉ ዘንድ በቀረቡ ጊዜ፥ እነርሱ ተሰናከሉና ወደቁ።
³ ሠራዊትም ቢሰፍርብኝ ልቤ አይፈራም፤ ሰልፍም ቢነሣብኝ በዚህ እተማመናለሁ።
⁴ እግዚአብሔርን አንዲት ነገር ለመንሁት እርስዋንም እሻለሁ፤ በሕይወቴ ዘመን ሁሉ በእግዚአብሔር ቤት እኖር ዘንድ፥ እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኘውንም አይ ዘንድ፥ መቅደሱንም እመለከት ዘንድ።
⁵ በመከራዬ ቀን በድንኳኑ ሰውሮኛልና፥ በድንኳኑም መሸሸጊያ ሸሽጎኛልና፥ በዓለት ላይ ከፍ ከፍ አድርጎኛልና።
⁶ እነሆ፥ አሁን በዙሪያ ባሉ በጠላቶቼ ላይ ራሴን ከፍ ከፍ አደረገ፤ በድንኳኑም የእልልታ መሥዋዕትን ሠዋሁ፥ ለእግዚአብሔር እቀኛለሁ እዘምርለትማለሁ።
⁷ አቤቱ፥ ወደ አንተ የጮኽሁትን ቃሌን ስማኝ፤ ማረኝና አድምጠኝ።
⁸ አንተ ፊቴን እሹት ባልህ ጊዜ፦ አቤቱ፥ ፊትህን እሻለሁ ልቤ አንተን አለ።
⁹ ፊትህን ከእኔ አትሰውር፥ ተቈጥተህ ከባሪያህ ፈቀቅ አትበል፤ ረዳት ሁነኝ፥ አትጣለኝም፥ የመድኃኒቴም አምላክ ሆይ፥ አትተውኝ።
¹⁰ አባቴና እናቴ ትተውኛልና፥ እግዚአብሔር ግን ተቀበለኝ።
¹¹ አቤቱ፥ መንገድህን አስተምረኝ፥ ስለ ጠላቶቼም በቀና መንገድ ምራኝ።
¹² የሐሰት ምስክሮችና ዓመፀኞች ተነሥተውብኛልና ለጠላቶቼ ፈቃድ አትስጠኝ።
¹³ የእግዚአብሔርን ቸርነት በሕያዋን ምድር አይ ዘንድ አምናለሁ።
¹⁴ እግዚአብሔርን ተስፋ አድርግ፤ በርታ፥ ልብህም ይጽና፤ እግዚአብሔርን ተስፋ አድርግ።
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤11👍1
Audio
❤2
. ──•◈•─────•◈•─
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“በመከራዬ ቀን በድንኳኑ ሰውሮኛልና፥ በድንኳኑም መሸሸጊያ ሸሽጎኛልና፥ በዓለት ላይ ከፍ ከፍ አድርጎኛልና።”
መዝሙር 27፥5
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“በመከራዬ ቀን በድንኳኑ ሰውሮኛልና፥ በድንኳኑም መሸሸጊያ ሸሽጎኛልና፥ በዓለት ላይ ከፍ ከፍ አድርጎኛልና።”
መዝሙር 27፥5
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
🔥6❤4
አምላካችን ማን ነዉ?
“እረሱ (ክርስቶስ) የማይታየዉ አምላክ አምሳል ነዉ፤ ከፍጥረትም ሁሉ በፊት በኩር ነዉ፤ ሁሉ ነገር በእርሱ ተፈጥሮአል፤ በሰማይና በምድር ያሉ፣ የሚታዩና የማይታዩ፣ ዙፋናት ቢሆኑ ወይም ኀይላት፣ ገዦች ቢሆኑ ወይም ባለሥልጣናት፣ ሁሉም ነገር በእርሱና ለእርሱ ተፈጥሮአል። እርሱ ከሁሉ በፊት ነዉ፤ ሁሉ ነገር በአንድ ላይ ተያይዞ የጸናዉ በእርሱ ነዉ። እርሱ አካሉ የሆነችዉ የቤተክርስቲያን ራስ ነዉ፤ በሁሉ ነገር የበላይነት ይኖረዉ ዘንድ እርሱ የመጀመሪያ፣ ከሙታን መካከልም በኩር ነዉ።” (ቆላስያስ 1፡15-18)
እግዚአብሔር “ሕዝቤን ልቀቅ” ባለ ጊዜ ፈርኦን የተናገረዉ ሁልጊዜ ተገዳዳሪዎቻችን በህሊናችን የሚያቃጭሉት ጥያቄ ነዉ። ፈርኦን “ቃሉን እሰማ ዘንድ እስራኤልንስ እለቅቅ ዘንድ እግዚአብሔር ማን ነዉ?” ነበር ያለዉ (ዘጸ 5፡2)። ዛሬም “አምላክህ/ሽ ማን ነዉ?” ለሚለን ቆላ 1 አስደናቂ እዉነታ ነዉ። አምላካችን ክርስቶስ ፍጥረተ ዓለሙን ካለመኖር ወደ መኖር ያመጣ ብቻ ሳይሆን አሁንም ፍጥረት ሥርዐት ይዞ እንዲቀጥል ሁሉን በአንድ ላይ አያይዞ ያስቀጥለዋል፣ ያጸናዋል። ፍጥረት ምን እንደሚያክል፣ በቢሊዮኖች የሚቆጠሩ ግዙፍ ከዋክብትና ክምችቶቻቸውም ምን እንደሚመስሉ ለማሰብ ያስቸግራል። እነኝህን ሁሉ በእጆቹ ይዞ የሚያጸናቸዉ… አምላካችን ነው (ኢሳ 40፡27-31)። ክርስቶስ የሁሉ ፈጣሪና የበላይ ነዉ።
የኛ ችግርና ተግዳሮትማ ለእርሱ እንዴት ቀላል ነዉ? ስለሆነም አማኝ ነፍሱን
“እረፊ፣ አትጨነቂ፣ አትታወኪ፣ ዝም ብለሽ በኃያሉ አምላክሽ ታመኚ” ይበል፡፡
ምንጭ :- mamushafenta.com
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
“እረሱ (ክርስቶስ) የማይታየዉ አምላክ አምሳል ነዉ፤ ከፍጥረትም ሁሉ በፊት በኩር ነዉ፤ ሁሉ ነገር በእርሱ ተፈጥሮአል፤ በሰማይና በምድር ያሉ፣ የሚታዩና የማይታዩ፣ ዙፋናት ቢሆኑ ወይም ኀይላት፣ ገዦች ቢሆኑ ወይም ባለሥልጣናት፣ ሁሉም ነገር በእርሱና ለእርሱ ተፈጥሮአል። እርሱ ከሁሉ በፊት ነዉ፤ ሁሉ ነገር በአንድ ላይ ተያይዞ የጸናዉ በእርሱ ነዉ። እርሱ አካሉ የሆነችዉ የቤተክርስቲያን ራስ ነዉ፤ በሁሉ ነገር የበላይነት ይኖረዉ ዘንድ እርሱ የመጀመሪያ፣ ከሙታን መካከልም በኩር ነዉ።” (ቆላስያስ 1፡15-18)
እግዚአብሔር “ሕዝቤን ልቀቅ” ባለ ጊዜ ፈርኦን የተናገረዉ ሁልጊዜ ተገዳዳሪዎቻችን በህሊናችን የሚያቃጭሉት ጥያቄ ነዉ። ፈርኦን “ቃሉን እሰማ ዘንድ እስራኤልንስ እለቅቅ ዘንድ እግዚአብሔር ማን ነዉ?” ነበር ያለዉ (ዘጸ 5፡2)። ዛሬም “አምላክህ/ሽ ማን ነዉ?” ለሚለን ቆላ 1 አስደናቂ እዉነታ ነዉ። አምላካችን ክርስቶስ ፍጥረተ ዓለሙን ካለመኖር ወደ መኖር ያመጣ ብቻ ሳይሆን አሁንም ፍጥረት ሥርዐት ይዞ እንዲቀጥል ሁሉን በአንድ ላይ አያይዞ ያስቀጥለዋል፣ ያጸናዋል። ፍጥረት ምን እንደሚያክል፣ በቢሊዮኖች የሚቆጠሩ ግዙፍ ከዋክብትና ክምችቶቻቸውም ምን እንደሚመስሉ ለማሰብ ያስቸግራል። እነኝህን ሁሉ በእጆቹ ይዞ የሚያጸናቸዉ… አምላካችን ነው (ኢሳ 40፡27-31)። ክርስቶስ የሁሉ ፈጣሪና የበላይ ነዉ።
የኛ ችግርና ተግዳሮትማ ለእርሱ እንዴት ቀላል ነዉ? ስለሆነም አማኝ ነፍሱን
“እረፊ፣ አትጨነቂ፣ አትታወኪ፣ ዝም ብለሽ በኃያሉ አምላክሽ ታመኚ” ይበል፡፡
ምንጭ :- mamushafenta.com
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤14🙏1
. ──•◈•─────•◈•─
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“አንተ ግን፥ የሰው ልጅ ሆይ፥ የምነግርህን ስማ፤ እንደዚያ እንደ ዓመፀኛው ቤት ዓመፀኛ አትሁን፤ አፍህን ክፈት የምሰጥህንም ብላ።”
ሕዝቅኤል 2፥8
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“አንተ ግን፥ የሰው ልጅ ሆይ፥ የምነግርህን ስማ፤ እንደዚያ እንደ ዓመፀኛው ቤት ዓመፀኛ አትሁን፤ አፍህን ክፈት የምሰጥህንም ብላ።”
ሕዝቅኤል 2፥8
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤10
#እራሳችንን_እንመርምር
"ታዲያ እግዚአብሔር ጸጋውን ያበዛልናል በማለት ኃጢአት መሥራታችንን መቀጠል አለብን ማለት ነውን? እግዚአብሔርም አይበለው! ከእርሱ ጋር ሕብረት እንዲኖረን በጌታችን በኢየሱስ ስም በተጠመቅንበት ጊዜ ፥ ኃጢአት መሥራት የሚቀናው አሮጌው ባሕርያችን ከእርሱ ጋር የሞተ መሆኑን እንዴት ዘነጋችሁት?"
ሮሜ 6፥1-3 (ሕያው ቃል)
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
"ታዲያ እግዚአብሔር ጸጋውን ያበዛልናል በማለት ኃጢአት መሥራታችንን መቀጠል አለብን ማለት ነውን? እግዚአብሔርም አይበለው! ከእርሱ ጋር ሕብረት እንዲኖረን በጌታችን በኢየሱስ ስም በተጠመቅንበት ጊዜ ፥ ኃጢአት መሥራት የሚቀናው አሮጌው ባሕርያችን ከእርሱ ጋር የሞተ መሆኑን እንዴት ዘነጋችሁት?"
ሮሜ 6፥1-3 (ሕያው ቃል)
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤14
. ──•◈•─────•◈•─
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“ከእግዚአብሔር ጋር አብረን የምንሠራ እንደ መሆናችን መጠን፣ የተቀበላችሁትን የእግዚአብሔርን ጸጋ ከንቱ እንዳታደርጉት ዐደራ እንላችኋለን።”
2ኛ ቆሮንቶስ 6፥1 (አዲሱ መ.ት)
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“ከእግዚአብሔር ጋር አብረን የምንሠራ እንደ መሆናችን መጠን፣ የተቀበላችሁትን የእግዚአብሔርን ጸጋ ከንቱ እንዳታደርጉት ዐደራ እንላችኋለን።”
2ኛ ቆሮንቶስ 6፥1 (አዲሱ መ.ት)
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤7
ባለራእይነት.pdf
2.8 MB
👏6❤1