ቅዱሳት መጻሕፍት
#እምነት ክፍል-9 እምነት እና ሥራ በመጽሐፍ ቅዱስ መሠረት ሰው የሚድነው ወይም የሚጸድቀው በእምነት እንጂ በሥራ እንዳልሆነ እርግጥ ነው፤ ይህ በእምነት የመጽደቅ ጉዳይም በሰው ዘንድ ሳይሆን በእግዚአብሔር ዘንድ የሚታየው ነው፡፡ በሮሜ 4፥1‐8 የምናገኘው የእግዚአብሔር ቃል ይህን የሚያረጋግጥ ነው፤ በቊ.1 ላይ «በሥጋ አባታችን የሆነ አብርሃም ምን አገኘ እንላለን?…
#እምነት
ክፍል-10
እምነት እና ሥራ
እግዚአብሔር ይህ እምነት እውነተኛ መሆን አለመሆኑን በራሱ አምላካዊ እውቀት ያውቃል፤ ሰው ግን ይህን የሚያውቀው ሥራውን አይቶ ነው፤ እዚህ ላይ የተጠቀሰው «እምነት አለኝ» ባዩ ሰው ደግሞ ሥራ እንደሌለው ታውቋል፤ ስለዚህ በቊ.17 ላይ «ሥራ የሌለው እምነት ቢኖር በራሱ የሞተ ነው» ተብሏል፡፡ በእግዚአብሔር ዘንድ እውነተኛ እንደሆነ የሚታወቅ እምነት ግን ሥራ የሌለው ሊሆን አይችልም፤ በጊዜው ባይገለጥ እንኳ እግዚአብሔር ጽድቅ አድርጎ የቈጠረው እምነት ከሆነ በሥራ መገለጡ አይቀርም፡፡ ያን ጊዜም በሰው ዘንድ ይታያል፤ ስለዚህ በቊ.18 ላይ እንደተጠቀሰው «አንድ ሰው አንተ እምነት አለህ እኔም ሥራ አለኝ እምነትህን ከሥራህ ለይተህ አሳየኝ እኔም እምነቴን በሥራዬ አሳይሃለሁ ይላል» ተብሎ በሁለት ሰዎች መካከል በዚህ ጉዳይ ሊባል የሚችለው ነገር ተነግሮናል፤ እነዚህ ሁለት ሰዎች አንዱ እምነት አለኝ የሚለው ሰው ሲሆን ሌላው ደግሞ ሥራ ያለውና እምነቱን በሥራው ማሳየት የሚችለው ሰው ነው፤ እየተናገረ ያለውም ይህ እምነቱን በሥራው ማሳየት የሚችለው ሰው ነው፡፡ «እምነቴን በሥራዬ አሳይሃለሁ» በሚለው አገላለጽም ሥራ እውነተኛ እምነት በሰው ዘንድ ወይም ፊት የሚገለጥበት ማሳያ መሆኑን እንረዳለን፤ ይህ እምነቱን በሥራው ማሳየት የሚችለው ሰው ሥራ የሌለው እምነት ያለውን ሰው እንዲህ እያለ ይወቅሰዋል፤
«እግዚአብሔር አንድ እንደሆነ አንተ ታምናለህ መልካም ታደርጋለህ፤ አጋንንት ደግሞ ያምናሉ ይንቀጠቀጡማል፡፡» ይለዋል (ቊ.19)፡፡ በዚህ ቃል ውስጥ ሥራ የሌለው እምነት ያለው ሰው እምነቱ የተነጻጸረው ከአጋንንት እምነት ጋር መሆኑ ሰውየው የዳነ ሰው እንዳልሆነ ያሳያል፤ ምክንያቱም መዳን በእምነት ነው ሲባል በእውነተኛ እምነት እንጂ እንደ አጋንንት እምነት ባለ በዚህ ዓይነት እምነት አይደለም፡፡ በሌላ አገላለጽ "የአጋንንት እምነት" የሚባል አይነት እምነት አለ ማለት ነው። እግዚአብሔር ከዚህ አይነቱ እምነት ይጠብቀን!
በመቀጠልም ለዚህ አፋዊ እምነት ላለው ሰው የአብርሃም እምነትና ሥራ በማስረጃነት ቀርቦለታል፤ «አንተ ከንቱ ሰው እምነት ከሥራ ተለይቶ የሞተ መሆኑን ልታውቅ ትወዳለህን? አባታችን አብርሃም ልጁን ይስሐቅን በመሠዊያው ባቀረበ ጊዜ በሥራ የጸደቀ አልነበረምን? እምነት ከሥራው ጋር አብሮ ያደርግ እንደነበረ በሥራም እምነት እንደተፈጸመ ትመለከታለህን? መጽሐፍም አብርሃም እግዚአብሔርን አመነ ጽድቅም ሆኖ ተቈጠረለት ያለው ተፈጸመ፤ የእግዚአብሔርም ወዳጅ ተባለ፡፡» ይላል (ቊ.20‐23)፡፡ በዚህ ክፍል አብርሃም ልጁን በመሠዊያው ላይ ማቅረቡ የአብርሃም ሥራ ሆኖ ቀርቧል፤ በዚህም ሥራ የአብርሃም እምነት እንደተፈጸመ ወይም ፍጹም እንደተደረገ(ቊ.22 አ.መ.ት.) ተገልጧል፤ ከዘፍ.15፡4‐6 እንደምንረዳው ደግሞ «አብርሃም በእግዚአብሔር አመነ ጽድቅም ሆኖ ተቈጠረለት» የተባለው እግዚአብሔር ለአብርሃም ከጉልበቱ የሚወጣው እንደሚወርሰው በተናገረውና የሰማይ ከዋክብትን አሳይቶ «ዘርህም እንደዚሁ ይሆናል» ባለው ጊዜ ነው፡፡ ከዚህ በኋላ ይስሐቅን በመሠዊያ ላይ እስከሚያቀርብበት ጊዜ ድረስ ብዙ ዓመታት ተቈጥረዋል፤ በ86 ዓመቱ እስማኤልን ወልዷል(ዘፍ.16፡16)፤ ከ13 ዓመታት በኋላ በ99 ዓመቱ ራሱ አብርሃምና ልጁ እስማኤልም ተገርዘዋል(ዘፍ 17፡24‐25)፤ በ100 ዓመቱ ይስሐቅን ወልዷል(ዘፍ.21፡5)፤ ከዚያም በፍልስጥኤም ምድር ብዙ ቀን እንግዳ ሆኖ ተቀምጧል(ዘፍ.21፡34)፤ እንግዲህ ልጁ ይስሐቅን በመሠዊያ ላይ ያቀረበው ከዚህ ሁሉ በኋላ ይስሐቅ ካደገ በኋላ እንደሆነ እንረዳለን፤ በዚህ ጊዜ አብርሃም በሥራም እንደጸደቀ ተነግሮናል፤ አብርሃም በእግዚአብሔር ዘንድ የጸደቀው ግን «ከጉልበትህ የሚወጣው ይወርስሃል፣ ዘርህ እንደዚሁ ይሆናል» የሚለው የተስፋ ቃል በተሰጠው ጊዜ ማለትም ይስሐቅ ገና ባልነበረበት ጊዜ ነው(ሮሜ 4፥18)፡፡ ያን ጊዜ በእግዚአብሔር ስላመነ ጽድቅ ሆኖ ተቈጠረለት፡፡ ከብዙ ዓመታት በኋላ ደግሞ ልጁን ይስሐቅን በመሠዊያው ባቀረበ ጊዜ በሥራም ጸደቀ፤ ይህም ማለት በሰው ዘንድ ታየ ተረጋገጠ ማለት ነው፡፡ እግዚአብሔር ግን ለአብርሃም ጽድቅን ለመቊጠር ልጁ ይስሐቅን በመሠዊያ ላይ እስኪያቀርብ ድረስ መጠበቅ አላስፈለገውም፤ አብርሃም ባመነ ጊዜ እምነቱን ጽድቅ አድርጎ ቈጥሮለታል፡፡
ይቀጥላል...
ምንጭ፦ 1bible.page
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ክፍል-10
እምነት እና ሥራ
እግዚአብሔር ይህ እምነት እውነተኛ መሆን አለመሆኑን በራሱ አምላካዊ እውቀት ያውቃል፤ ሰው ግን ይህን የሚያውቀው ሥራውን አይቶ ነው፤ እዚህ ላይ የተጠቀሰው «እምነት አለኝ» ባዩ ሰው ደግሞ ሥራ እንደሌለው ታውቋል፤ ስለዚህ በቊ.17 ላይ «ሥራ የሌለው እምነት ቢኖር በራሱ የሞተ ነው» ተብሏል፡፡ በእግዚአብሔር ዘንድ እውነተኛ እንደሆነ የሚታወቅ እምነት ግን ሥራ የሌለው ሊሆን አይችልም፤ በጊዜው ባይገለጥ እንኳ እግዚአብሔር ጽድቅ አድርጎ የቈጠረው እምነት ከሆነ በሥራ መገለጡ አይቀርም፡፡ ያን ጊዜም በሰው ዘንድ ይታያል፤ ስለዚህ በቊ.18 ላይ እንደተጠቀሰው «አንድ ሰው አንተ እምነት አለህ እኔም ሥራ አለኝ እምነትህን ከሥራህ ለይተህ አሳየኝ እኔም እምነቴን በሥራዬ አሳይሃለሁ ይላል» ተብሎ በሁለት ሰዎች መካከል በዚህ ጉዳይ ሊባል የሚችለው ነገር ተነግሮናል፤ እነዚህ ሁለት ሰዎች አንዱ እምነት አለኝ የሚለው ሰው ሲሆን ሌላው ደግሞ ሥራ ያለውና እምነቱን በሥራው ማሳየት የሚችለው ሰው ነው፤ እየተናገረ ያለውም ይህ እምነቱን በሥራው ማሳየት የሚችለው ሰው ነው፡፡ «እምነቴን በሥራዬ አሳይሃለሁ» በሚለው አገላለጽም ሥራ እውነተኛ እምነት በሰው ዘንድ ወይም ፊት የሚገለጥበት ማሳያ መሆኑን እንረዳለን፤ ይህ እምነቱን በሥራው ማሳየት የሚችለው ሰው ሥራ የሌለው እምነት ያለውን ሰው እንዲህ እያለ ይወቅሰዋል፤
«እግዚአብሔር አንድ እንደሆነ አንተ ታምናለህ መልካም ታደርጋለህ፤ አጋንንት ደግሞ ያምናሉ ይንቀጠቀጡማል፡፡» ይለዋል (ቊ.19)፡፡ በዚህ ቃል ውስጥ ሥራ የሌለው እምነት ያለው ሰው እምነቱ የተነጻጸረው ከአጋንንት እምነት ጋር መሆኑ ሰውየው የዳነ ሰው እንዳልሆነ ያሳያል፤ ምክንያቱም መዳን በእምነት ነው ሲባል በእውነተኛ እምነት እንጂ እንደ አጋንንት እምነት ባለ በዚህ ዓይነት እምነት አይደለም፡፡ በሌላ አገላለጽ "የአጋንንት እምነት" የሚባል አይነት እምነት አለ ማለት ነው። እግዚአብሔር ከዚህ አይነቱ እምነት ይጠብቀን!
በመቀጠልም ለዚህ አፋዊ እምነት ላለው ሰው የአብርሃም እምነትና ሥራ በማስረጃነት ቀርቦለታል፤ «አንተ ከንቱ ሰው እምነት ከሥራ ተለይቶ የሞተ መሆኑን ልታውቅ ትወዳለህን? አባታችን አብርሃም ልጁን ይስሐቅን በመሠዊያው ባቀረበ ጊዜ በሥራ የጸደቀ አልነበረምን? እምነት ከሥራው ጋር አብሮ ያደርግ እንደነበረ በሥራም እምነት እንደተፈጸመ ትመለከታለህን? መጽሐፍም አብርሃም እግዚአብሔርን አመነ ጽድቅም ሆኖ ተቈጠረለት ያለው ተፈጸመ፤ የእግዚአብሔርም ወዳጅ ተባለ፡፡» ይላል (ቊ.20‐23)፡፡ በዚህ ክፍል አብርሃም ልጁን በመሠዊያው ላይ ማቅረቡ የአብርሃም ሥራ ሆኖ ቀርቧል፤ በዚህም ሥራ የአብርሃም እምነት እንደተፈጸመ ወይም ፍጹም እንደተደረገ(ቊ.22 አ.መ.ት.) ተገልጧል፤ ከዘፍ.15፡4‐6 እንደምንረዳው ደግሞ «አብርሃም በእግዚአብሔር አመነ ጽድቅም ሆኖ ተቈጠረለት» የተባለው እግዚአብሔር ለአብርሃም ከጉልበቱ የሚወጣው እንደሚወርሰው በተናገረውና የሰማይ ከዋክብትን አሳይቶ «ዘርህም እንደዚሁ ይሆናል» ባለው ጊዜ ነው፡፡ ከዚህ በኋላ ይስሐቅን በመሠዊያ ላይ እስከሚያቀርብበት ጊዜ ድረስ ብዙ ዓመታት ተቈጥረዋል፤ በ86 ዓመቱ እስማኤልን ወልዷል(ዘፍ.16፡16)፤ ከ13 ዓመታት በኋላ በ99 ዓመቱ ራሱ አብርሃምና ልጁ እስማኤልም ተገርዘዋል(ዘፍ 17፡24‐25)፤ በ100 ዓመቱ ይስሐቅን ወልዷል(ዘፍ.21፡5)፤ ከዚያም በፍልስጥኤም ምድር ብዙ ቀን እንግዳ ሆኖ ተቀምጧል(ዘፍ.21፡34)፤ እንግዲህ ልጁ ይስሐቅን በመሠዊያ ላይ ያቀረበው ከዚህ ሁሉ በኋላ ይስሐቅ ካደገ በኋላ እንደሆነ እንረዳለን፤ በዚህ ጊዜ አብርሃም በሥራም እንደጸደቀ ተነግሮናል፤ አብርሃም በእግዚአብሔር ዘንድ የጸደቀው ግን «ከጉልበትህ የሚወጣው ይወርስሃል፣ ዘርህ እንደዚሁ ይሆናል» የሚለው የተስፋ ቃል በተሰጠው ጊዜ ማለትም ይስሐቅ ገና ባልነበረበት ጊዜ ነው(ሮሜ 4፥18)፡፡ ያን ጊዜ በእግዚአብሔር ስላመነ ጽድቅ ሆኖ ተቈጠረለት፡፡ ከብዙ ዓመታት በኋላ ደግሞ ልጁን ይስሐቅን በመሠዊያው ባቀረበ ጊዜ በሥራም ጸደቀ፤ ይህም ማለት በሰው ዘንድ ታየ ተረጋገጠ ማለት ነው፡፡ እግዚአብሔር ግን ለአብርሃም ጽድቅን ለመቊጠር ልጁ ይስሐቅን በመሠዊያ ላይ እስኪያቀርብ ድረስ መጠበቅ አላስፈለገውም፤ አብርሃም ባመነ ጊዜ እምነቱን ጽድቅ አድርጎ ቈጥሮለታል፡፡
ይቀጥላል...
ምንጭ፦ 1bible.page
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤6👍2
መልእክተ ይሁዳ.pdf
985 KB
👍3❤1
. ──•◈•─────•◈•─
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“በጠበበው በር ለመግባት ተጋደሉ፤ እላችኋለሁና፥ ብዙዎች ሊገቡ ይፈልጋሉ አይችሉምም።”
ሉቃስ 13፥24
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“በጠበበው በር ለመግባት ተጋደሉ፤ እላችኋለሁና፥ ብዙዎች ሊገቡ ይፈልጋሉ አይችሉምም።”
ሉቃስ 13፥24
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤8🥰1
ትንቢተ_ዳንኤል_የጥናት_መምሪያና_ማብራሪያ.pdf
8 MB
👉ርዕስ፦ ትንቢተ ዳንኤል የጥናት መምሪያና ማብራሪያ፣
በትምህርተ መለኮት ማስፋፊያ (ት.መ.ማ) መልክ የተዘጋጀ
✍ጸሐፊ፦ ቲም ፌሎስ
🖨አሳታሚ፦ ኤስ.አይ.ኤም
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
በትምህርተ መለኮት ማስፋፊያ (ት.መ.ማ) መልክ የተዘጋጀ
✍ጸሐፊ፦ ቲም ፌሎስ
🖨አሳታሚ፦ ኤስ.አይ.ኤም
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤14
. ──•◈•─────•◈•─
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“እንግዲህ እንደ ተወደዱ ልጆች እግዚአብሔርን የምትከተሉ ሁኑ፥”
ኤፌሶን 5፥1
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“እንግዲህ እንደ ተወደዱ ልጆች እግዚአብሔርን የምትከተሉ ሁኑ፥”
ኤፌሶን 5፥1
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤9🔥1
በእግዚአብሔር ፊት ማን ሊቆም ይችላል?
አቤቱ፥ በድንኳንህ ውስጥ ማን ያድራል? በተቀደሰውም ተራራህ ማን ይኖራል?
በቅንነት የሚሄድ፥
Those who lead blameless lives
ጽድቅንም የሚያደርግ፥
do what is right
በልቡም እውነትን የሚናገር።
speaking the truth from sincere hearts.
በአንደበቱ የማይሸነግል፥
Those who refuse to slander others
በባልንጀራው ላይ ክፋትን የማያደርግ፥
Those who refuse to harm their neighbors
ዘመዶቹንም የማይሰድብ።
Those who refuse to speak evil of their friends.
ኃጢአተኛ በፊቱ የተናቀ፥
Those who despise persistent sinners
እግዚአብሔርንም የሚፈሩትን የሚያከብር፥
honor the faithful followers of the Lord
ለባልንጀራው የሚምል የማይከዳም።
keep their promises even when it hurts.
ገንዘቡን በአራጣ የማያበድር፥
Those who do not charge interest on the money they lend
በንጹሑ ላይ መማለጃን የማይቀበል።
who refuse to accept bribes to testify against the innocent.
እንዲህ የሚያደርግ ለዘላለም አይታወክም።
Such people will stand firm forever.
ምንጭ:- መዝሙር 15
Psalms 15 (NLT)
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
አቤቱ፥ በድንኳንህ ውስጥ ማን ያድራል? በተቀደሰውም ተራራህ ማን ይኖራል?
በቅንነት የሚሄድ፥
Those who lead blameless lives
ጽድቅንም የሚያደርግ፥
do what is right
በልቡም እውነትን የሚናገር።
speaking the truth from sincere hearts.
በአንደበቱ የማይሸነግል፥
Those who refuse to slander others
በባልንጀራው ላይ ክፋትን የማያደርግ፥
Those who refuse to harm their neighbors
ዘመዶቹንም የማይሰድብ።
Those who refuse to speak evil of their friends.
ኃጢአተኛ በፊቱ የተናቀ፥
Those who despise persistent sinners
እግዚአብሔርንም የሚፈሩትን የሚያከብር፥
honor the faithful followers of the Lord
ለባልንጀራው የሚምል የማይከዳም።
keep their promises even when it hurts.
ገንዘቡን በአራጣ የማያበድር፥
Those who do not charge interest on the money they lend
በንጹሑ ላይ መማለጃን የማይቀበል።
who refuse to accept bribes to testify against the innocent.
እንዲህ የሚያደርግ ለዘላለም አይታወክም።
Such people will stand firm forever.
ምንጭ:- መዝሙር 15
Psalms 15 (NLT)
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤17🔥1
Types_of_Fallacies_From_Hurley_Patrick_Introduction_to_Logic_book.pdf
1017.4 KB
ይህ "Types of Fallacy" ወይንም የተፋልሶ ዓይነቶች ከ "PATRICK J. HURLEY" "A Concise Introduction to Logic" ከሚለው መጽሐፍ የተወሰደ ነው። ዓላማውም ለእቅበተ እምነት ሥራ ፍላጎት ላላቸው እንዲሆን የተለጠፈ ነው። ሙሉው መጽሐፍ የሚፈልግ ካለ ይለቀቃል።
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤9
. ──•◈•─────•◈•─
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“ክፉ ከሆነ ከአሁኑ ዓለም ያድነን ዘንድ እንደ አምላካችንና እንደ አባታችን ፈቃድ ስለ ኃጢአታችን ራሱን ሰጠ።”
ገላትያ 1፥4
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“ክፉ ከሆነ ከአሁኑ ዓለም ያድነን ዘንድ እንደ አምላካችንና እንደ አባታችን ፈቃድ ስለ ኃጢአታችን ራሱን ሰጠ።”
ገላትያ 1፥4
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤12
A Concise Introduction to Logic, 12th Edition.pdf
45.3 MB
Author: - PATRICK J. HURLEY
Title: - A Concise Introduction to Logic, 12th Edition Edition
Page no. :- 738
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
Title: - A Concise Introduction to Logic, 12th Edition Edition
Page no. :- 738
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤2👏1
#እንወያይ
ስለምንገኝበት አጥቢያ ቤተክርስቲያን ወይም ማኅበረ ምዕመናን መሠረታዊ አስተምህሮ (doctrine) ማወቅን እንዴት ትመለከቱታላችሁ? በጣም አስፈላጊ ነው ወይስ እምብዛም ጥቅም የለውም? በዚህ ዙሪያ ብዙ የእውቀት ክፍተት ያለብን አይመስላችሁም?
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ስለምንገኝበት አጥቢያ ቤተክርስቲያን ወይም ማኅበረ ምዕመናን መሠረታዊ አስተምህሮ (doctrine) ማወቅን እንዴት ትመለከቱታላችሁ? በጣም አስፈላጊ ነው ወይስ እምብዛም ጥቅም የለውም? በዚህ ዙሪያ ብዙ የእውቀት ክፍተት ያለብን አይመስላችሁም?
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤19
. ──•◈•─────•◈•─
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“ከእንግዲህስ ወዲያ ለኃጢአት እንዳንገዛ የኃጢአት ሥጋ ይሻር ዘንድ አሮጌው ሰዋችን ከእርሱ ጋር እንደ ተሰቀለ እናውቃለን፤ የሞተስ ከኃጢአቱ ጸድቋልና።”
ሮሜ 6፥6
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“ከእንግዲህስ ወዲያ ለኃጢአት እንዳንገዛ የኃጢአት ሥጋ ይሻር ዘንድ አሮጌው ሰዋችን ከእርሱ ጋር እንደ ተሰቀለ እናውቃለን፤ የሞተስ ከኃጢአቱ ጸድቋልና።”
ሮሜ 6፥6
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤4👍4
#ከተማ_ወይም_ቦታ_በቅዱሳት_መጻሕፍት
#ኢይዝራኤል፤
የቃሉ ትርጒም እግዚአብሔር ይበትናል ወይም «እግዚአብሔር ይዘራል» ማለት ነው። የሆሴዕ ታላቅ ልጅ ስያሜም ነው። ከቦታው ስንጀምር የይሁዳ ከተማ፤ ኢያሱ 15፥56፤ 1ሳሙ. 25፥43። በይሳኮር ርስት ድርሻ ውስጥ ነበረ። በከተማውም አቅራቢያ ያለው ሰፊ ሸለቆ በዚህ ስም ተጠራ፤ ኢያሱ 19፥18፤ ሆሴዕ 1፥5። የናቡቴ ወይን ቦታ በዚያ ነበረ፤ 1ነገ. 20። በዚያም ኢዩ የአክዓብን ቤተ ሰዎችና አለቆች አስፈጀ፤ 2ነገ. 9፥ 17-10፥11። በዚህ ስፍራ በገዦች ላይ ይፈጸም ዘንድ የተነገረውን ፍርድ የሚያጸና ነው፡፡ ዳግማዊ ኢዮርብዓም፣ የአክአብን ልጅ የኢዮራምን መንግሥት በመገልበጥ (2ነገ 9፥14-37፤ ከ1ነገ19፥16-17) በኢይዝራኤል ከተመሠረተው ከኢዩ ሥርወ መንግሥት የመጣ ነው (በ841-814 ዓመተ ቅድመ ክርስቶስ)፤ የኢዩ ሥርወ መንግሥት ያከተመው ዘካርያስ በተገደለበት በ753 ዓመተ ቅድመ ክርስቶስ ነው (2ነገ 15፥8-10)፡፡
ለሆሴዕና ለጎሜር ሦስት ልጆች ተወለዱ፤ ለእያንዳንዳቸውም ትእምርታዊ ስም ተሰጥቶአቸዋል፡፡ “ኢይዝራኤል” የሚለው ስም የሚያመለክተው፣ ኢዩ ያፈሰሰውን “ደም” ለመበቀል እግዚአብሔር በቅጣት የሚነሣበትን የወደፊቱን ቀን ነው፡፡ ኢዩ የእግዚአብሔርን ትእዛዝ በመፈጸሙ መልካም ቢያደርግም (2ነገ 9፥1-10)፣ እግዚአብሔር ካዘዘው በላይ ብዙ ሰዎችን ገድሎ ነበር፡፡ የኢዩ ኀጢአት የተቀጣው እስራኤል መንግሥት መሆኗ እንዲቆም በመደረጉ ነበር (ይህ በ722 ዓመተ ቅድመ ክርስቶስ ሆኖአል)፡፡
ምንጭ፦ የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት፤ ገጽ 170፣ አዲሱ መደበኛ ትርጉም ከማጥኛ ጹሑፍ ጋር፤ ገጽ 1318፣ የብሉይ ኪዳን ማብራሪያ፤ ገጽ 1005
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
#ኢይዝራኤል፤
የቃሉ ትርጒም እግዚአብሔር ይበትናል ወይም «እግዚአብሔር ይዘራል» ማለት ነው። የሆሴዕ ታላቅ ልጅ ስያሜም ነው። ከቦታው ስንጀምር የይሁዳ ከተማ፤ ኢያሱ 15፥56፤ 1ሳሙ. 25፥43። በይሳኮር ርስት ድርሻ ውስጥ ነበረ። በከተማውም አቅራቢያ ያለው ሰፊ ሸለቆ በዚህ ስም ተጠራ፤ ኢያሱ 19፥18፤ ሆሴዕ 1፥5። የናቡቴ ወይን ቦታ በዚያ ነበረ፤ 1ነገ. 20። በዚያም ኢዩ የአክዓብን ቤተ ሰዎችና አለቆች አስፈጀ፤ 2ነገ. 9፥ 17-10፥11። በዚህ ስፍራ በገዦች ላይ ይፈጸም ዘንድ የተነገረውን ፍርድ የሚያጸና ነው፡፡ ዳግማዊ ኢዮርብዓም፣ የአክአብን ልጅ የኢዮራምን መንግሥት በመገልበጥ (2ነገ 9፥14-37፤ ከ1ነገ19፥16-17) በኢይዝራኤል ከተመሠረተው ከኢዩ ሥርወ መንግሥት የመጣ ነው (በ841-814 ዓመተ ቅድመ ክርስቶስ)፤ የኢዩ ሥርወ መንግሥት ያከተመው ዘካርያስ በተገደለበት በ753 ዓመተ ቅድመ ክርስቶስ ነው (2ነገ 15፥8-10)፡፡
ለሆሴዕና ለጎሜር ሦስት ልጆች ተወለዱ፤ ለእያንዳንዳቸውም ትእምርታዊ ስም ተሰጥቶአቸዋል፡፡ “ኢይዝራኤል” የሚለው ስም የሚያመለክተው፣ ኢዩ ያፈሰሰውን “ደም” ለመበቀል እግዚአብሔር በቅጣት የሚነሣበትን የወደፊቱን ቀን ነው፡፡ ኢዩ የእግዚአብሔርን ትእዛዝ በመፈጸሙ መልካም ቢያደርግም (2ነገ 9፥1-10)፣ እግዚአብሔር ካዘዘው በላይ ብዙ ሰዎችን ገድሎ ነበር፡፡ የኢዩ ኀጢአት የተቀጣው እስራኤል መንግሥት መሆኗ እንዲቆም በመደረጉ ነበር (ይህ በ722 ዓመተ ቅድመ ክርስቶስ ሆኖአል)፡፡
ምንጭ፦ የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት፤ ገጽ 170፣ አዲሱ መደበኛ ትርጉም ከማጥኛ ጹሑፍ ጋር፤ ገጽ 1318፣ የብሉይ ኪዳን ማብራሪያ፤ ገጽ 1005
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤4👏1
. ──•◈•─────•◈•─
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“ነገር ግን በጌታችንና በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና እውቀት እደጉ።”
2ኛ ጴጥሮስ 3፥18
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“ነገር ግን በጌታችንና በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና እውቀት እደጉ።”
2ኛ ጴጥሮስ 3፥18
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤9👍1
ክርስትና በ ፓልስቲን ሲጀምር ሕይወት ነበረ ፣ ወደ ግሪክ ሲደርስ ፍልስፍና ሆነ ፣ሮም ሲገባ ተቋም ሆነ ፣ አውሮፓና አሜሪካ ሲደርስ ንግድ ሆነ!!
#በእኛ_ህይወትስ?🤔
ዶክተር ማሙሻ ፈንታ
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
#በእኛ_ህይወትስ?🤔
ዶክተር ማሙሻ ፈንታ
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤8🤔8😢2👏1🤯1
#የእግዚአብሔር_ቃል_ምን_ይላል
ሚልክያስ 1
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁰ በመሠዊያዬ ላይ እሳትን በከንቱ እንዳታቃጥሉ ከእናንተ ዘንድ ደጅ የሚዘጋ ሰው ምነው በተገኘ! በእናንተ ደስ አይለኝም፥ ቍርባንንም ከእጃችሁ አልቀበልም፥ ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር።
¹¹ ከፀሐይ መውጫ ጀምሮ እስከ መግቢያዋ ድረስ ስሜ በአሕዛብ ዘንድ ታላቅ ይሆናልና፤ በየስፍራውም ለስሜ ዕጣን ያጥናሉ፥ ንጹሕም ቍርባን ያቀርባሉ፤ ስሜ በአሕዛብ ዘንድ ታላቅ ይሆናልና፥ ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር።
¹² እናንተ ግን፦ የእግዚአብሔር ገበታ ርኩስ ነው፤ ፍሬውና መብሉም የተናቀ ነው በማለታችሁ አስነቀፋችሁት።
¹³ እናን፦ እነሆ፥ ይህ ድካም ነው ብላችሁ ጢቅ አላችሁበት፥ ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር፤ በቅሚያ የያዛችሁትንም አንካሳውንም የታመመውንም አቅርባችኋል፤ እንዲሁ ቍርባንን ታመጣላችሁ በውኑ ከእጃችሁ ይህን ልቀበለውን? ይላል እግዚአብሔር።
¹⁴ እኔ ታላቅ ንጉሥ ነኝና፥ ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር፥ ስሜም በአሕዛብ ዘንድ የተፈራ ነውና በመንጋው ውስጥ ተባት እያለው ለጌታ ተስሎ ነውረኛውን የሚሠዋ ሸንጋይ ሰው ርጉም ይሁን።
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ሚልክያስ 1
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁰ በመሠዊያዬ ላይ እሳትን በከንቱ እንዳታቃጥሉ ከእናንተ ዘንድ ደጅ የሚዘጋ ሰው ምነው በተገኘ! በእናንተ ደስ አይለኝም፥ ቍርባንንም ከእጃችሁ አልቀበልም፥ ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር።
¹¹ ከፀሐይ መውጫ ጀምሮ እስከ መግቢያዋ ድረስ ስሜ በአሕዛብ ዘንድ ታላቅ ይሆናልና፤ በየስፍራውም ለስሜ ዕጣን ያጥናሉ፥ ንጹሕም ቍርባን ያቀርባሉ፤ ስሜ በአሕዛብ ዘንድ ታላቅ ይሆናልና፥ ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር።
¹² እናንተ ግን፦ የእግዚአብሔር ገበታ ርኩስ ነው፤ ፍሬውና መብሉም የተናቀ ነው በማለታችሁ አስነቀፋችሁት።
¹³ እናን፦ እነሆ፥ ይህ ድካም ነው ብላችሁ ጢቅ አላችሁበት፥ ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር፤ በቅሚያ የያዛችሁትንም አንካሳውንም የታመመውንም አቅርባችኋል፤ እንዲሁ ቍርባንን ታመጣላችሁ በውኑ ከእጃችሁ ይህን ልቀበለውን? ይላል እግዚአብሔር።
¹⁴ እኔ ታላቅ ንጉሥ ነኝና፥ ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር፥ ስሜም በአሕዛብ ዘንድ የተፈራ ነውና በመንጋው ውስጥ ተባት እያለው ለጌታ ተስሎ ነውረኛውን የሚሠዋ ሸንጋይ ሰው ርጉም ይሁን።
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍5❤2🙏1
. ──•◈•─────•◈•─
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“አካሄዳችሁ ገንዘብን ያለ መውደድ ይሁን፥ ያላችሁም ይብቃችሁ፤ እርሱ ራሱ፦ አልለቅህም ከቶም አልተውህም ብሎአልና፤”
ዕብራውያን 13፥5
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“አካሄዳችሁ ገንዘብን ያለ መውደድ ይሁን፥ ያላችሁም ይብቃችሁ፤ እርሱ ራሱ፦ አልለቅህም ከቶም አልተውህም ብሎአልና፤”
ዕብራውያን 13፥5
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤12
ቅዱሳት መጻሕፍት
. ──•◈•─────•◈•─ የዕለቱ ጥቅስ ──•◈•─────•◈•─ “አካሄዳችሁ ገንዘብን ያለ መውደድ ይሁን፥ ያላችሁም ይብቃችሁ፤ እርሱ ራሱ፦ አልለቅህም ከቶም አልተውህም ብሎአልና፤” ዕብራውያን 13፥5 ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
"የገንዘብ ፍቅር አይግዛችሁ ፤ ባላችሁ ነገር ረክታችሁ ለመኖር ጣሩ። ምክንያቱም እግዚአብሔር፥ 'ምን ጊዜም ቢሆን በችግራችሁ እደርስላችኋለሁ ፤ ምን ጊዜም ቢሆን አልተዋችሁም' ብሎ ተናግሮአልና።"
ዕብራውያን 13፥5 (ሕያው ቃል)
ዕብራውያን 13፥5 (ሕያው ቃል)
❤11🥰7🔥1
#እራሳችንን_እንመርምር
ኃጢአትን እንዴት አድርገን ነው የምንመለከተው? ይዘናት፣ አቅፈናት እና አሽሞንሙነናት ወይስ ተጸይፈን፣ ትተን እና ነግሰንባት ነው ያለነው?
“ኃጢአቱን የሚሰውር አይለማም፤ የሚናዘዝባትና የሚተዋት ግን ምሕረትን ያገኛል።”
ምሳሌ 28፥13
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ኃጢአትን እንዴት አድርገን ነው የምንመለከተው? ይዘናት፣ አቅፈናት እና አሽሞንሙነናት ወይስ ተጸይፈን፣ ትተን እና ነግሰንባት ነው ያለነው?
“ኃጢአቱን የሚሰውር አይለማም፤ የሚናዘዝባትና የሚተዋት ግን ምሕረትን ያገኛል።”
ምሳሌ 28፥13
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤7🙏4