ቅዱሳት መጻሕፍት
7.45K subscribers
1.36K photos
61 videos
332 files
802 links
በዚህ ቻናል

👉ቅዱሳት መጻሕፍት ይጠናሉ::
👉መጽሐፍ ቅዱሳዊ ትምህርቶች ይቀርባሉ::
👉 ለቅዱሳት መጽሐፍት ጥናት የሚያግዙ መጻሕፍት ይለቀቃሉ።

⭐️⭐️⭐️⭐️⭐️

@Holy_scriptures
Download Telegram
Pilgrim's Progress
Nigusse Denano
#መጻሕፍትን_በድምጽ

📔ርዕስ፦ የመናኝ ጉዞ
👤ጸሐፊ፦ ዮሐንስ ቡንያን
👉ክፍል-10

ይቀጥላል. . .


ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
🔥1
የመንፈሳዊ ራብ በረከት



መንፈሳዊ ራብ ጌታን መናፈቅን፣እሱን ለማግኘት መጓጓትን፣ወደ እሱ ለመጠጋት ማሰብን ወዘተ ያመለክታል፡፡

በግለሰብ ይሁን በወል ደረጃ መንፈሳዊ ራብና ጥማት ለእግዚአብሔር መለኮታዊ ጉብኝት እጅግ ወሳኝ ናቸው፡፡አውነተኛ የሆነ መንፈሳዊ ራብና ጥማት እግዚአብሔርን እንድንሻው፣ እንድንፈልገውና እንድንጠጋው ኃይል ይሆኑናል፡፡ ቃሉ “ጽድቅን የሚራቡና የሚጠሙ ብፁዓን ናቸው” (ማቴዎስ 5፡6) የሚለን ለዚህ ነው፡፡ “ብፁዓን” የሚለውን ቃል አምሊፋይድ መጽሐፍ ቅዱስ (Amplified Bible) ደስተኞች፣ በመንፈስ ባለጸጋ የሆኑ፣ የረኩ፣ የተባረኩ ወዘተ ብሎ ነው የሚገልጸው፡፡

ሐና መንፈሳዊ ራብ ያላቸው ሰዎች በጌታ ፊት ዋጋ ያላቸውና የማይረሱ እንደ ሆነ ስትናገር “ተርበው የነበሩ ከራብ አርፈዋል” (1 ሳሙኤል 2:5) ብላለች፤ አምላኳ የሚያረካ፣የሚያጠግብና የሚያሳርፍ መሆኑን በማወደስ፡፡

መንፈሳዊ ራብ በራሱ ትልቅ በረከት ነው፤ ወደ ፊት እንድንዘረጋ፣ እንድንቃትት፣ ፊቱን አንድንፈልግ ያደርገናል፡፡ የምር የሆነ መንፈሳዊ ራብ የሚመነጨው ደግሞ ያለንበትን ሁኔታ የእግዚአብሔር መንፈስ ሲያሳየንና ያለንበትን አዘቅት ስንጠላው ነው፡፡ መንፈሳዊ ራብ ይጐተጉተናል፣ አያስተኛንም፤ ቃሉ “የሠራተኛ ራብ ለርሱ ይሠራል አፉ ይጐተጉተዋል” (ምሳሌ 16፡26) ይላልና ፡፡ “ለርሱ ይሠራል” የሚለውን አስምሩልኝ፡፡ለማን? ለርሱ! አያስተኛውማ! ሳያገኝ አያሳርፈውማ! ለዚህ ነው መንፈሳዊ ራብ በራሱ የሚጓጓለት በረከት የሆነው፡፡


መንፈሳዊ ራብ ልክ እንደ ኤርምያስ ጌታን በትጋት እንድንፈልገው ያደርገናል፡፡ኤርምያስ ከብዙ ፍለጋ በኋላ ሕይወት የሚሰጠውን፣ መንፈስ የሆነውን፣ የጊዜውን ቃል ሲያገኝ እንዲህ ብሎ ተናገረ፦

“ቃልህ ተገኝቷል እኔም በልቼዋለሁ፤አቤቱ የሠራዊት ጌታ ሆይ በስምህ ተጠርቻለሁና ቃል ሐሤትና የልብ ደስታ ሆነኝ”
            (ኤርምያስ 15፡16)


ከዚህ ምንባብ በጥቂቱ እንደምንረዳው፣ ኤርምያስ ቃሉን በትጋትና በተራበ መንፈስ ሲፈልግ የቆየ ይመስላል፡፡ ባገኘውም ጊዜ ከነበረው ናፍቆት የተነሣ ለመብላት ፋታ ያገኘም አይመስልም፡፡ እናም እስከሚረካና በሐሤት እስኪጥለቀለቅ ድረስ በላው፡፡

ንጉሥ ዳዊት እውነተኛ መንፈሳዊ ራብ ያላቸውን ሰዎች እግዚአብሔር እንዴት እንደሚባርክ ሲገልጽ፦ “የተራበችን ነፍስ አጥግቦአልና፤ የተራቈተችንም ነፍስ በበረከት ሞልቶአልና” (መዝ 107፡9) ብሎ ተናግሯል፡፡ አዎ መንፈሳዊ ራብ የገባበት ሰው ሲቆፍር፣ ሲፈልግ፣ ሲቃትት ወዘተ ያድራል፤ ዕረፍት አይኖረውም ያንን ራብ ሳያስታግስ፡፡ ራቡ ጐትጓች ነውና፣ አያስተኛውምና፡፡

ይህን መንፈሳዊ ራብ የሚያቀጣጥሉ ሦስት የታወቁ ነገሮች አሉ፡፡እነሱም፡-


1⃣የእግዚአብሔር ቃል አብዝቶ ማጥናትና ማሰላሰል

2⃣ደጋግሞ ለረጅም ጊዜ መጾም

3⃣በጌታ ፊት በውሳኔ መውደቅ


ጌታ እንደ ተስፋ ቃሉ መንፈሳዊን ነገር በሚራቡና በሚጠሙ ሰዎች ሕይወት፣ ከብዙ መሻት በኋላ ሲገለጥ አስደናቂ ነገር የሚሆነው፡፡ለዚህ ነው ሰፋ ካለ መንፈሳዊ መነቃቃት በፊት በቤተ ክርስትያን እርሱን የሚራቡና የሚጠሙ፣ እናም በጓዳ እሱን የሚሹና የሚፈልጉ ሰዎች አስቀድሞ የሚያስነሣው፡፡


አንድ ክርስትያን ይህ ራብ በውስጡ ለረጅም ጊዜ ከጠፋ፣ ለመውደቅ እየተንሸራተተ እንደ ሆነ ሊያስብ ይገባዋል፡፡

መንፈሳዊ ራቡ ልባችንን ባሰፋነው መጠን ያድጋል፡፡ አብዝተን እንድንቃትት ያደርገናል፡፡አብዝተን ስንጸልይ ደግሞ ጸሎቱ ሌላ ከፍ ያለ መንፈሳዊ ራብን ይወልዳል፡፡የሚመጣው መንፈሳዊ ራብ ደግሞ አብዝተን እንድንጸልይ ያደርገናል፡፡ወገኖቼ አንዱ አንዱን እየጨመረ ማብቂያ የሌለው አስደናቂ ነገር ውስጥ ነው የምንገባው፤ እኛ በሥጋዊ አካሄዶች መንፈስን እስካላጠፋን ድረስ፡፡


ጌታ ሆይ ከፍ ያለ አንተን የሚሻና የሚፈልግ ልብ ስጠን !  



ምንጭ:-Divine Wisdom4




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
🔥117👍1
.       ──•◈•─────•◈•─
                          የዕለቱ ጥቅስ
        ──•◈•─────•◈•─
“ከእርሱ ዘንድ ካልሆነ ማን መብላትና መደሰት ይችላል?”
መክብብ 2፥25 (አዲሱ መ.ት)



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
🥰91
Pilgrm's progress
Nigusse Denano
#መጻሕፍትን_በድምጽ

📔ርዕስ፦ የመናኝ ጉዞ
👤ጸሐፊ፦ ዮሐንስ ቡንያን
👉ክፍል-11

ይቀጥላል. . .


ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ቅዱሳት መጻሕፍት
#በዓለ_ኀምሳ #ጰራቅሊጦስ የቀጠለ... የጉባኤ ኒቂያ ዘመን የኒቂያ ጉባኤ መነሻ ምክንያት የሆነው አርዮስ የተባለ የኑፋቄ መምህር ወልድ እና መንፈስ ቅዱስ ከእግዚአብሔር አብ ጋር በባሕርይ አንድ ያልሆኑ እና ፍጡራን ናቸው ብሎ በማስተማሩ ምክንያት ነው። በመጨረሻም ለአሪዮስ መንፈስ ቅዱስ በእግዚአብሔር ወልድ የተፈጠረ፣ በተፈጠረ አካል የተፈጠረ ፍጡር (የፍጡር ፍጡር) ነው። የአሪዮስ ኑፋቄያዊ አስተምህሮ…
#በዓለ_ኀምሳ
#ጰራቅሊጦስ

የቀጠለ...



የፕሮቴስታን ተሓድሶ ዘመን

የሮም ካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን በቅድመ ተሓድሶ ዘመን ከቅዱስ አውግስጢኖስ ሐሳብ ዞር በማለት የቶማስ አኳይናስን የሥነ መለኮት አስተምህሮ የቤተ ክርስቲያንቷ የእምነት አቋም ምሰሶ አድርጋ ይዛ ነበር። ይሁን እንጂ በፕሮቴስታንት ተሓድሶ ዘመን ቤተ ክርስቲያን በቅድመ ተሓድሶ ዘመን ተዘንግቶ ወደ ነበረው ወደ የቅዱስ አውግስጢኖስ ሐሳብ የተመለሰችበት ዘመን ነው። ሆኖም በፕሮቴስታንት የተሓድሶ ዘመን ቅዱሳት መጻሕፍትን አንብቦ መረዳት ላይ ከፍተኛ ትኩረት የተሰጠበት ዘመን ከመሆኑ የተነሣ፣ እንደ ማርቲን ሉተር ያሉት የፕሮቴስታንት የተሓድሶ አራማጆች፣ “አንድ ሰው በክርስቶስ የሚያምነው ቅዱሳት መጻሕፍትን አንብቦ መረዳት ሲችል ብቻ ነው” ብለው ያስተምሩና ለዚህ አስተምህሮ ከፍተኛ አጽንዖት ይሰጡ ስለ ነበር ሰዎችን በማዳን ሂደት ውስጥ መንፈስ ቅዱስ ያለው ሚና ምን እንደ ሆነ የተዘነጋ ይመስላል። ይሁን እንጂ ከተሓድሶ አራማጆች መካከል የሆነው ጆን ካልቪን በሮም ቤተ ክርስቲያን ውስጥ በቅድመ ተሓድሶ ዘመን ተዘንግቶ የነበረውን የቅዱስ አውግስጢኖስ አስተምህሮ፣ ማለትም መንፈስ ቅዱስ በሰዎች ድነት ውስጥ ያለውን ሚና እንደገና አነቃቅቷል።

የድኅረ ተሓድሶ ዘመን

በድኅረ ተሓድሶ ዘመን የመንፈስ ቅዱስ ኀይል ሰዎችን በማዳን ረገድ የሚያከናውናቸው ሁለት ነገሮች ጎልተው ወጥተዋል፤ እነዚህም የውሸት ብህትውና (False Mystcism) እና የውሸት አመክኑያዊነት (False Rationalism) ናቸው። ጆን ዊስሊ ከተሓድሶ ዘመን በኋላ በመንፈስ ቅዱስን አስተምህሮ ላይ ትልቅ ብርሃን የፈነጠቀው በዚህ ወቅት ነበር። ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ቤተ ክርስቲያን ስለ መንፈስ ቅዱስ ይበልጥ መረዳት ጀመረች። ምንም እንኳ የጆን ዊስሊ ሥነ መለኮት ፍጹም ባይሆንም ቤተ ክርስቲያን ስለ መንፈስ ቅዱስ በደንብ መረዳት የጀመረችው ግን በእርሱ ዘመን መሆኑን መካድ አይቻልም።

መንፈስ ቅዱስ በዘመናችን

ከዚህ በላይ በተመለከትነው የቤተ ክርስቲያን ታሪክ ውስጥ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ተያያዥነት ያላቸው ኑፋቄዎች አብዛኞቹ በመንፈስ ቅዱስ ማንነት የሚያጠነጥኑ የአስተምህሮዊ ኑፋቄዎች ናቸው። ይሁን እንጂ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በኢትዮጵያ ውስጥ ከፍተኛ ትኩረት የሚሰጠው ለአስተምህሮ ሳይሆን ለክንዋኔ ሆኗል። በአተገባበርም ወቅት የሚፈጠሩ ስሕተቶች በብዛት በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ይስተዋላሉ። እነዚህን ስሕተቶች እንደ ኑፋቄ መመልከት አለብን ወይስ የለብንም? እነዚህ በአስተምህሮ ሊገሩ የሚችሉ ቀላል ስሕተቶች በመሆናቸው በኑፋቄ ጎራ ሊፈረጁ አይገባም የሚል
ሙግት ሊነሣ ይችላል። ይሁን እንጂ አንዳንድ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ከፍተኛ ቁርኝት ያላቸው የኢትዮጵያን ቤተ ክርስቲያን ልምምዶች ታሳቢ የሚያደርጉት ምንጫቸውን (አስተምህሯቸውን) በመሆኑ ልምምዶቹም የነፈቁ ናቸው ለማለት ያስደፍራል።



ምንጭ:- hintset.org



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
9🔥1
.       ──•◈•─────•◈•─
                          የዕለቱ ጥቅስ
        ──•◈•─────•◈•─
“እነሆ፥ እግዚአብሔር የሚገሥጸው ሰው ምስጉን ነው፤ ስለዚህ ሁሉን የሚችለውን የአምላክን ተግሣጽ አትናቅ።”
ኢዮብ 5፥17



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
10
Pilgrm's progress
Nigusse Denano
#መጻሕፍትን_በድምጽ

📔ርዕስ፦ የመናኝ ጉዞ
👤ጸሐፊ፦ ዮሐንስ ቡንያን
👉ክፍል-12

ይቀጥላል. . .


ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የእግዚአብሔርን ፀጋ የምንጥልባቸው አራቱ መንገዶች


የእግዚአብሄርን ፀጋ የምናጣበት ሃይል አልባ የሚያደርጉን አራቱ መንገዶች

1. ትህትናን መጣል  

ሰው ትህትናን ከጣለ የጊዜ ጉዳይ ነው እንጂ እንደሚወድቅ ምንም ጥርጥር የለውም፡፡ ሰው እግዚአብሄር ከሰጠው ደረጃ በላይ ራሱን ከፍ አድርጎ ሲያይ ከእግዚአብሄር ጋር ይተላለፋል፡፡ እግዚአብሄር ፀጋን መስጠትና ማንሳት ከፍ ማድረግ እየፈለገ በራሱ ነገሮችን ማደርግ እንደሚችል የሚያስበውን ትእቢተኛን ሰው ግን ከመቃወም ውጭ ምንም ሊያደርገው አይችልም፡፡  

“ነገር ግን ጸጋን አብልጦ ይሰጣል፤ ስለዚህ፦ እግዚአብሔር ትዕቢተኞችን ይቃወማል፥ ለትሑታን ግን ጸጋን ይሰጣል ይላል።”
ያዕቆብ 4፥6

2. እውቀትን መጣል

ሰው ከመሬት ተነስቶ አውቆ የጨረሰ ከመሰለው በህይወቱ ማደግና መለወጥ አቁሟል ማለት ነው፡፡ ይህ ሰው ለአዲስ ተግዳሮት በእውቀት ራሱን ካላስታጠቀ መውደቁ አይቀሬ ነው፡፡ ይህ ሰው ያወቀና የጨረሰ ከመሰለው እጅግ አሰቃቂ ነው፡፡

"ለጣዖት ስለ ተሠዋ ሥጋም፥ ሁላችን እውቀት እንዳለን እናውቃለን። እውቀት ያስታብያል ፍቅር ግን ያንጻል። ማንም አንዳች የሚያውቅ ቢመስለው ሊያውቅ እንደሚገባው ገና አላወቀም፤" (1ኛ ቆሮ. 8፡1-2)

“ሕዝቤ እውቀት ከማጣቱ የተነሣ ጠፍቶአል፤ አንተም እውቀትን ጠልተሃልና እኔ ካህን እንዳትሆነኝ እጠላሃለሁ፤ የአምላክህንም ሕግ ረስተሃልና እኔ ደግሞ ልጆችህን እረሳለሁ።”
ሆሴዕ 4፥6

"በእግዚአብሔርና በጌታችን በኢየሱስ እውቀት ጸጋና ሰላም ይብዛላችሁ።"( 2ኛ ጴጥ. 1፥2)

3. እምነትን መጣል

ሰው በእግዚአብሄር ላይ መደገፍን ትቶ በራሱ ስራ ላይ ሲደገፍ ከእግዚአብሄር ፀጋ ይጎድላል፡፡ ሰው ለመዳንም ሆነ ከዳነ በኋላ ለመቀደስ ፣ ለእግዚአብሄር መንግስት ለመስራትና እግዚአብሄርን ለማስደሰት በራሱ ጉልበትና ቅልጥፍና ላይ ሲደገፍ ከእግዚአብሄር ፀጋ ይጎድላል፡፡

"በሕግ ልትጸድቁ የምትፈልጉ ከክርስቶስ ተለይታችሁ ከጸጋው ወድቃችኋል።" (ገላ. 5፥4)

4. ምስጋናን መጣል

ሰው ምንም ከማይወጣለት መልካም አምላክ ጋር እየኖረ ካጉረመረመና ማመስገን ካቃተው ከእግዚአብሄር ፀጋ ይጎድላል፡፡ ሰው በእግዚአብሄር አሰራር ላይ አቃቂር ማውጣት ከቻለ የሆነ የሳተው ነገር አለ ማለት ነው፡፡ ሰው ከእግዚአብሄር በላይ የሚያውቅ ከመሰለው የሆነ የተዛባ ነገር አለ ማለት ነው፡፡ ሰው በእግዚአብሄር አሰራር ካልታመነ ከእግዚአብሄር ጋር በየዋህነት መኖር ፣ ራሱን መስጠት ፣ ለእግዚአብሄር በየዋህነት መስራትና ፍሬያማ መሆን ያቅተዋል፡፡   

"አንድ መክሊትም የተቀበለው ደግሞ ቀርቦ፦ ጌታ ሆይ፥ካልዘራህባት የምታጭድ ካልበተንህባትም የምትሰበስብ ጨካኝ ሰው መሆንህን አውቃለሁ፤ ፈራሁም ሄጄም መክሊትህን በምድር ቀበርሁት፤ እነሆ፥ መክሊትህ አለህ አለ።"(ማቴ. 25፥24-25)

"ከእነርሱም አንዳንዶቹ እንዳንጎራጎሩ በሚያጠፋውም እንደጠፉ አታንጐርጕሩ።" (1ኛ ቆሮ. 10፥10)


ምንጭ:- አብይ ዋቁማ



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
8🙏4👍2🔥2
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
5
ተግተህ አገልግል.pdf
6.5 MB
👉ርዕስ፦ ተግተህ አገልግል
የማርቆስ ወንጌል
ከአገልጋዩ ጌታ ጋር ስትጓዝ ሌሎችንም አገልግል
✍️ጸሐፊ፦ ዋረን ደብልዩ ዌርዝቢ
🗣ትርጉም፦ ግርማዊ
✏️እርማት፦ ኃይሌ ጀናይ


ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
9
.       ──•◈•─────•◈•─
                          የዕለቱ ጥቅስ
        ──•◈•─────•◈•─
“በሰይፋቸው ምድርን አልወረሱም ክንዳቸውም አላዳናቸው፤ ቀኝህና ክንድህ የፊትህም ብርሃን ነው እንጂ፤ ወድደሃቸዋልና።”
መዝሙር 44፥3



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍51
PPlgims Progress
Nigusse Denano
#መጻሕፍትን_በድምጽ

📔ርዕስ፦ የመናኝ ጉዞ
👤ጸሐፊ፦ ዮሐንስ ቡንያን
👉ክፍል-13

ይቀጥላል. . .


ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ለጌታ-የተገዛህ ሁን.pdf
9.5 MB
👉ርዕስ፦ ለጌታ-የተገዛህ ሁን
የማቴዎስ ወንጌል
የክብር ንጉሥን በማወቅና በማገልገል ሐሤት አድርግ
✍️ጸሐፊ፦ ዋረን ደብልዩ ዌርዝቢ
🗣ትርጉም፦ ግርማዊ
✏️እርማት፦ ዐብይ ደምሴ እና ኃይሌ ጀናይ


ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
8🥰3
#እራሳችንን_እንመርምር



በየትኛውም በሕይወት መስክ፣ ምንም ይሁን የትም የምንሰራው እንዴት ነው? በቸልተኝነት? በዋዛ ፈዛዛ? በሙሉ ልብ?

“ለሰው ሳይሆን ለጌታ እንደምታደርጉ፥ የምታደርጉትን ሁሉ በትጋት አድርጉት፥”
ቆላስይስ 3፥23



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍61🤔1
.       ──•◈•─────•◈•─
                          የዕለቱ ጥቅስ
        ──•◈•─────•◈•─
“ጌታቸው በመጣ ጊዜ ሲተጉ የሚያገኛቸው እነዚያ ባሪያዎች ብፁዓን ናቸው፤ እውነት እላችኋለሁ፥ ታጥቆ በማዕድ ያስቀምጣቸዋል ቀርቦም ያገለግላቸዋል።”
ሉቃስ 12፥37



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍3
Plgrim's progress
Nigusse Denano
#መጻሕፍትን_በድምጽ

📔ርዕስ፦ የመናኝ ጉዞ
👤ጸሐፊ፦ ዮሐንስ ቡንያን
👉ክፍል-14

ይቀጥላል. . .


ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ቅዱሳት መጻሕፍት
ክርስቲያናዊ ዓቅብተ እምነት – CHRISTIAN APOLOGETICS           ክፍል-2 1.2. የክርስቲያን ዓቅብተ እምነት ታሪክ የክርስቲያን ዓቅብተ እምነት ታሪክ ከመጀመርያው ክፍለ ዘመን የሚጀምር ቢሆንም እንደ አንድ የጥናት ዘርፍ የጎለበተውና ወጥ የሆነ መልክ የያዘው ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ነው፡፡ ክርስቲያናዊው ዓቅብተ እምነት በተለያዩ የዕድገት ደረጃዎች ውስጥ አልፏል፡፡ ክርስትና በተጀመረበት…
ክርስቲያናዊ ዓቅብተ እምነት – CHRISTIAN APOLOGETICS


            ክፍል-3


በክርስቲያን ዓቅብተ እምነት ታሪክ ውስጥ የእስክንድሪያ ክርስቲያኖች ያበረከቱት አስተዋጽዖ ከሁሉም የላቀ ነበር፡፡ የእስክንድሪያው ቀለሜንጦስ “ፕሮትሬፕቲከስ” (ልባዊ ምክር) በሚል ርዕስ የጻፈው ዓቃቤ እምነታዊ ጽሑፍ በሁለተኛው ክፍለ ዘመን ከተጻፉ ተመሳሳይ ጽሑፎች ሁሉ የላቀ ነበር፡፡

በሦስተኛው ክፍለ ዘመን ከተነሱት ክርስቲያን አቃቤ እምነታውያን መካከል ኦሪጎን (185-254 ዓ.ም.) ቀዳሚውን ስፍራ ይይዛል፡፡ ሴልሰስ የተባለ ሰው በክርስትና ላይ ላቀረበው ፍልስፍናዊ፣ ግብረ ገባዊና ታሪካዊ ትችት ምላሽ ለመስጠት “ኮንትራ ሴልሰስ” በሚል ርዕስ የጻፈው ረዘም ያለ ጽሑፉ እስከ አሁኑ ዘመን ድረስ ጠቃሚ የመረጃ ምንጭ በመሆን እያገለገለ ይገኛል፡፡ በዚህ ጽሑፉ ኦሪጎን ኢየሱስ ተዓምራቱን በአስማት እንዳላደረገና የአረማውያን የተዓምራት ታሪኮች ከኢየሱስ ታሪኮች እጅግ ያነሰ ተዓማኒነት እንዳላቸው ተሟግቷል፡፡ የኢየሱስን ትንሣኤ ታሪካዊነት “ከቁም ቅዠት” (Hallucination) መላ ምት በመከላከል ረገድም የሚደነቅ የመከላከያ ሐሳብ አቅርቧል፡፡

የሂፖ ሬጊዩስ ሊቀ ጳጳስ የነበረው ቅዱስ አውጉስጢኖስ (354-430 ዓ.ም.) ክርስቲያኖች በንጉሥ ቆስጠንጢኖስ አዋጅ ነጻነትን ከተጎናጸፉ በኋላ ከተነሱት ክርስቲያን ዓቃቤ እምነታውያን መካከል ቀዳሚውን ስፍራ ይይዛል፡፡ ክርስትና ከአረማዊነት የላቀ መሆኑን የሚያሳዩ፣ የስህተት ትምህርቶችን የሚያጋልጡና የክርስትናን አስተምህሮዎች ቀና በሆነ መንገድ የሚያስተምሩ ብዙ ጽሑፎችን የጻፈ ታላቅ ሊቅ ነበር፡፡ የአውጉስጢኖስ ክርስቲያናዊ ፍልስፍና የበለጠ ሰፋ ባለ መልኩ ሰፍሮ የምናገኘው በምዕራቡ ዓለም ውስጥ ከተጻፉ አስር በጣም ጠቃሚ መጻሕፍት መካከል አንዱ ተደርጎ በሚቆጠረው “የእግዚአብሔር ከተማ” በሚል ርዕስ በጻፈው የመጨረሻ መጽሐፉ ውስጥ ነው፡፡ አውጉስጢኖስ ስለ ዓቅብተ እምነት ያስተማረው ትምህርት ከርሱ ዘመን ጀምሮ እስከዚህ ዘመን ድረስ ለብዙ ክርስቲያን ዓቃቤ እምነታውያንና የነገረ መለኮት ምሑራን መነሳት ምክንያት ሆኗል፡፡

ቤተ ክርስቲያን ካፈራቻቸው ታላላቅ ሊቃውንት መካከል የካንቴርበሪ ሊቀ ጳጳስ የነበረው አንሴልም (1033-1109 ዓ.ም.) ይጠቀሳል፡፡ ከርሱ በፊት ያልተነገሩ የራሱ የሆኑ አዳዲስ ሐሳቦችን በማመንጨት የሚታወቅ ሲሆን አውጉስጢኖስ ስለ እምነትና ምክንያት ያስተማራቸውን ነገሮች በማጉላትም ይታወቃል፡፡ ስለ እምነትና ስለ ምክንያት ከተናገራቸው ነገሮች መካከል የሚከተለው ይገኝበታል፦ “ለማመን መረዳት እንዲኖረኝ ጥረት አላደርግም ነገር ግን ለመረዳት እምነት እንዲኖረኝ ጥረት አደርጋለሁ፡፡” አንሴልም ፈላስፎች “Ontological Argument” በማለት ለሚጠሩት የእግዚአብሔርን መኖር ለሚያስረዳ እጅግ ጠቃሚ ሐሳብ መሠረት የጣለ ሰው ነበር፡፡ “ኩር ዴኡስ ሆሞ” (አምላክ ሰው የሆነበት ምክንያት) በሚለው መጽሐፉ ውስጥ የኢየሱስ በሰው ሥጋ መምጣት ለምን እንዳስፈለገ አመክንዮአዊ በሆነ መንገድ በማስረዳት ለክርስቲያን ዓቅብተ እምነት ከፍተኛ አስተዋጽዖ አበርክቷል፡፡

በአስራ ሦስተኛው ክፍለ ዘመን አቬሮስ በተባለ የእስፔን አረብ አማካይነት የአርስጣጣሊስ (አርስቶትል) ፍልስፍና በመላው አውሮፓ በሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ ከመሰራጨቱ የተነሳ ክርስቲያናዊው ንፅረተ ዓለም ከፍተኛ ቀውስ ገጥሞት ነበር፡፡ ሊቃውንት ያለ ምንም ምርመራ የአርስጣጣሊስን አስተሳሰብ የተቀበሉ ሲሆኑ የቤተ ክርስቲያን መሪዎችም ያለ ምንም ምርመራ ከአርስጣጣሊስ ፍልስፍና ጋር የተያያዙትን ነገሮች ሁሉ ይቃወሙ ነበር፡፡ ታላቁ አልበርት የተባለ ክርስቲያን ሊቅ ለአቬሮስ ምላሽ የሚሆን ጽሑፍ የጻፈ ቢሆንም ነገር ግን ለዚህ ተግዳሮት ምላሽን በመስጠት የክርስቲያናዊውን ፍልስፍናና ዓቅብተ እምነት አቅጣጫ ማስለወጥ የቻለው የአልበርት ደቀ መዝሙር የነበረው ቶማስ አኳይነስ (1225-1274) ነበር፡፡ ለአቬሮስ ምላሽ ሊሆን የሚችል ጽሑፍ የአርስጣጣሊስን ቋንቋ በመጠቀም ከመጻፉ ሌላ ለክርስቲያን ተማሪዎች ሊሆን የሚችል የሥነ መለኮት መጽሐፍም አበርክቷል፡፡ አኳይነስ በቤተ ክርስቲያን ታሪክ ከተነሱ ታላላቅ ፈላስፎች መካከል አንዱ ነበር፡፡


ይቀጥላል...


ምንጭ:- ewnetlehulu.org



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
9
.       ──•◈•─────•◈•─
                          የዕለቱ ጥቅስ
        ──•◈•─────•◈•─
“እግዚአብሔር ስለ ጽድቁ ሕጉን ታላቅ ያደርግና ያከብር ዘንድ ወደደ።”
ኢሳይያስ 42፥21



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
8
Plgrim's Progress
Nigusse Denano
#መጻሕፍትን_በድምጽ

📔ርዕስ፦ የመናኝ ጉዞ
👤ጸሐፊ፦ ዮሐንስ ቡንያን
👉ክፍል-15

ይቀጥላል. . .


ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
2
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
1