. ──•◈•─────•◈•─
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“ጌታ ኢየሱስም ከእነርሱ ጋር ከተናገረ በኋላ ወደ ሰማይ ዐረገ በእግዚአብሔርም ቀኝ ተቀመጠ።”
ማርቆስ 16፥19
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“ጌታ ኢየሱስም ከእነርሱ ጋር ከተናገረ በኋላ ወደ ሰማይ ዐረገ በእግዚአብሔርም ቀኝ ተቀመጠ።”
ማርቆስ 16፥19
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤9👍3
ዛሬ የጌታችን እና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ዕርገት የሚከበርበት ቀን ነው። ከትንሣኤ በኋላ 40 ቀን መሆኑ ነው። ምድራዊ ተልእኮውን ጨርሶ ወደ አብ ያረገበት የክብር ጊዜ ነው። ዕርገቱ የስንብት አይደለም፣ ነገር ግን የተስፋው ቃል ማለትም ስፍራ ሊያዘጋጅልን እንደሚሄድ (ዮሐ. 14፥2-3) እና መንፈስ ቅዱስ ኃይል እንዲሰጠንና እንዲመራን እንደሚልክ የተናገረበትም ነው። ዕርገቱ ክርስቶስ በክብር እንደሚነግሥ፣ ስለ እኛ እንደሚማልድ ያሳስበናል፣ እናም ዜግነታችን በሰማይ መሆኑን ያረጋግጥልናል። ደቀ መዛሙርቱ ቆመው ሰማዩን እየተመለከቱ ሳለ የመላእክት መልእክት አሁንም ያስተጋባል። “... ወደ ሰማይ እየተመለከታችሁ ስለ ምን ቆማችኋል?” (ሐዋርያት 1፥11) አዎ፣ በፍርሃት ቀና ብለን ብቻ ሳይሆን በተልእኮ ወደ ፊት እንሂድ እስከ ምድር ዳርቻ ድረስ ምስክሮቹ እንሁን!
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
🔥10❤4
ቅዱሳት መጻሕፍት
#በዓለ_ኀምሳ #ጰራቅሊጦስ የቀጠለ... ለ. መንፈስ ቅዱስ የእግዚአብሔርን መልእክት ለሕዝቡ ለመንገር ይሠራ ነበር፡፡ ለምሳሌ በምድረ በዳ እስራኤላውያንን ይመራ የነበረው መንፈስ ቅዱስ ነው (ነህ 9፥20)፡፡ የእስራኤል መዘምራን መዝሙራቸውን በዘመሩ ጊዜ፣ የዘመሩት በጌታ መንፈስ ነው (2ሳሙ 23፥2፤ ከሐሥ1፥16፣20)፡፡ እንደዚሁም ነቢያት ቃሉን ለሕዝቡ ለመንገር በእግዚአብሔር መንፈስ ይመሩ…
#በዓለ_ኀምሳ
#ጰራቅሊጦስ
የቀጠለ...
ሠ. መንፈስ ቅዱስ አንድን ሰው ቀጥተኛ በሆነው የጽድቅ አኗኗር ለመምራት ፍላጎት እንዳለው በብሉይ ኪዳን ላይ ተስተውሎአል፤
ከዚህ ሐሳብ ጋር በተያያዘ መልኩም ዳዊት በአንዳንድ መዝሙሮቹ ላይ መስክሮአል (መዝ 51፥10-13፣ 143፥10)። የእግዚአብሔር ሕዝብ እግዚአብሔርን በመስማት ፈንታ የግላቸውን መንገድ የሚከተሉ ከሆነ፣ በትክክል ሲታይ የመንፈስ ቅዱስን መንገድ አንከተልም እያሉ ነው (ዘፍ 16፥2)፡፡ በእግዚአብሔር መንፈስ እየተመሩ ያልኖሩት፣ የእግዚአብሔርን ፍርድ በተለያየ መልኩ ሳይቀበሉ አልቀረም (ዘኊ 14፥29፤ ዘዳ1፥26)፡፡
ረ. በብሉይ ኪዳን ዘመን፣ መንፈስ ቅዱስ ለአገልግሎት ለማብቃት ወይም ትንቢት እንዲናገሩ ለማድረግ የመጣው በጣት በሚቈጠሩ ሰዎች ላይ መሆኑን ማስተዋል ተገቢ ነው
ለእስራኤል ሕዝብ ሁሉ የሆነ የመንፈስ ቅዱስ መውረድ አልነበረም (ከኢዮኤል 2፥28-29፤ ከሐሥ 2፥4፡16-18)፤ እስከ ታላቁ የጰንጠቆስጤ ዕለት ድረስ፣ ሰፋ ባለ መልኩ የመንፈስ ቅዱስ መውረድ አልተከሠተም ነበር (ሐሥ 2)።
2. በአዲስ ኪዳን መንፈስ ቅዱስ ራሱን የገለጠበት ሥራ፡፡
ሀ. መንፈስ ቅዱስ ስለ በደል የሚወቅስ (ዮሐ 16፥7-8)፣
ስለ ኢየሱስ ያለውን እውነት የሚገልጥ (ዮሐ 14፥16፡26)፣ አዲስ ልደትን የሚሰጥ (ዮሐ 3፥3-6)፣ ወደ ክርስቶስ አካል ውስጥ እንድንገባ የሚያደርግ የድነት ኀይል ነው። በክርስቶስ አምነን ስንለወጥ መንፈስ ቅዱስን እንቀበላለን (ዮሐ 3፥3-6፤ 20፥22)፤ የመለኮታዊ ባሕርይ ተካፋይም እንሆናለን (2ጴጥ 1፥4)።
ለ. መንፈስ ቅዱስ መቀደስን የሚያመጣ ኀይል ነው፡፡
በክርስቶስ አምነው በሚለወጡበት ጊዜ አማኞች የመንፈስ ቅዱስ ማደሪያ ይሆናሉ፤ ከዚያም በእርሱ የመቀደስ ተግባር ሥር ይሆናሉ (ሮሜ 8፥9፤ 1ቆሮ 6፡19)፡፡ መንፈስ ቅዱስ በውስጣችን ሲኖር፣ የሚሠራውን ሥራ ልብ በሉ፡፡ እርሱ ይቀድሰናል፣ ይኸውም ያነጻናል፤ ከኀጢአት ባርነት ነጻ በማውጣትም (ሮሜ 8፥24፣ ገላ 5፥16-17፤ 2ተሰ 2፥13) በቅዱስ ኑሮ እንድንመራ ያደፋፍረናል ማለት ነው፡፡ የእግዚአብሔር ልጆች እንደ ሆንን ይነግረናል (ሮሜ 8፥6)፣ እግዚአብሔርን በምናመልክበት ጊዜ (ሐሥ 10፥46) እና በጸሎት ሕይወታችን ያግዘናል፤ ወደ እግዚአብሔርም በምንጮኸበት ጊዜ ይማልድልናል (ሮሜ 8፥26-27)። ክርስቶስን እናከብር ዘንድ የክርስቶስ የሆኑትን የጸጋ ባሕርያት በውስጣችን ይፈጥርልናል (ገላ 5፥22-23፤ 1ጴጥ 1፥2)። እርሱ ኢየሱስን ለእኛ በመግለጥ፣ ከኢየሱስ ጋር የቀረበ ኅብረትና አንድነት እንዲኖረን በማድረግ (ዮሐ 14፥16-18፤ 16፥14)፡፡ ወደ እውነት ሁሉ የሚመራን መለኮታዊ አስተማሪያችን ነው (ዮሐ 16፥13፤ 14፥26፤ 1ቆሮ 2፥9-16)፡፡ ባለማቋረጥ የእግዚአብሔርን ፍቅር ወደ እኛ ያስተላልፋል (ሮሜ 5፥5)፡ ደስታን መጽናናትንና ርዳታን ይሰጠናል (ዮሐ 14፥16፤ 1ተሰ 1፥6)፡፡
ይቀጥላል...
ምንጭ፦ ምሉእ ሕይወት፤ ገጽ 1314-1315፣ 1679-80
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
#ጰራቅሊጦስ
የቀጠለ...
ሠ. መንፈስ ቅዱስ አንድን ሰው ቀጥተኛ በሆነው የጽድቅ አኗኗር ለመምራት ፍላጎት እንዳለው በብሉይ ኪዳን ላይ ተስተውሎአል፤
ከዚህ ሐሳብ ጋር በተያያዘ መልኩም ዳዊት በአንዳንድ መዝሙሮቹ ላይ መስክሮአል (መዝ 51፥10-13፣ 143፥10)። የእግዚአብሔር ሕዝብ እግዚአብሔርን በመስማት ፈንታ የግላቸውን መንገድ የሚከተሉ ከሆነ፣ በትክክል ሲታይ የመንፈስ ቅዱስን መንገድ አንከተልም እያሉ ነው (ዘፍ 16፥2)፡፡ በእግዚአብሔር መንፈስ እየተመሩ ያልኖሩት፣ የእግዚአብሔርን ፍርድ በተለያየ መልኩ ሳይቀበሉ አልቀረም (ዘኊ 14፥29፤ ዘዳ1፥26)፡፡
ረ. በብሉይ ኪዳን ዘመን፣ መንፈስ ቅዱስ ለአገልግሎት ለማብቃት ወይም ትንቢት እንዲናገሩ ለማድረግ የመጣው በጣት በሚቈጠሩ ሰዎች ላይ መሆኑን ማስተዋል ተገቢ ነው
ለእስራኤል ሕዝብ ሁሉ የሆነ የመንፈስ ቅዱስ መውረድ አልነበረም (ከኢዮኤል 2፥28-29፤ ከሐሥ 2፥4፡16-18)፤ እስከ ታላቁ የጰንጠቆስጤ ዕለት ድረስ፣ ሰፋ ባለ መልኩ የመንፈስ ቅዱስ መውረድ አልተከሠተም ነበር (ሐሥ 2)።
2. በአዲስ ኪዳን መንፈስ ቅዱስ ራሱን የገለጠበት ሥራ፡፡
ሀ. መንፈስ ቅዱስ ስለ በደል የሚወቅስ (ዮሐ 16፥7-8)፣
ስለ ኢየሱስ ያለውን እውነት የሚገልጥ (ዮሐ 14፥16፡26)፣ አዲስ ልደትን የሚሰጥ (ዮሐ 3፥3-6)፣ ወደ ክርስቶስ አካል ውስጥ እንድንገባ የሚያደርግ የድነት ኀይል ነው። በክርስቶስ አምነን ስንለወጥ መንፈስ ቅዱስን እንቀበላለን (ዮሐ 3፥3-6፤ 20፥22)፤ የመለኮታዊ ባሕርይ ተካፋይም እንሆናለን (2ጴጥ 1፥4)።
ለ. መንፈስ ቅዱስ መቀደስን የሚያመጣ ኀይል ነው፡፡
በክርስቶስ አምነው በሚለወጡበት ጊዜ አማኞች የመንፈስ ቅዱስ ማደሪያ ይሆናሉ፤ ከዚያም በእርሱ የመቀደስ ተግባር ሥር ይሆናሉ (ሮሜ 8፥9፤ 1ቆሮ 6፡19)፡፡ መንፈስ ቅዱስ በውስጣችን ሲኖር፣ የሚሠራውን ሥራ ልብ በሉ፡፡ እርሱ ይቀድሰናል፣ ይኸውም ያነጻናል፤ ከኀጢአት ባርነት ነጻ በማውጣትም (ሮሜ 8፥24፣ ገላ 5፥16-17፤ 2ተሰ 2፥13) በቅዱስ ኑሮ እንድንመራ ያደፋፍረናል ማለት ነው፡፡ የእግዚአብሔር ልጆች እንደ ሆንን ይነግረናል (ሮሜ 8፥6)፣ እግዚአብሔርን በምናመልክበት ጊዜ (ሐሥ 10፥46) እና በጸሎት ሕይወታችን ያግዘናል፤ ወደ እግዚአብሔርም በምንጮኸበት ጊዜ ይማልድልናል (ሮሜ 8፥26-27)። ክርስቶስን እናከብር ዘንድ የክርስቶስ የሆኑትን የጸጋ ባሕርያት በውስጣችን ይፈጥርልናል (ገላ 5፥22-23፤ 1ጴጥ 1፥2)። እርሱ ኢየሱስን ለእኛ በመግለጥ፣ ከኢየሱስ ጋር የቀረበ ኅብረትና አንድነት እንዲኖረን በማድረግ (ዮሐ 14፥16-18፤ 16፥14)፡፡ ወደ እውነት ሁሉ የሚመራን መለኮታዊ አስተማሪያችን ነው (ዮሐ 16፥13፤ 14፥26፤ 1ቆሮ 2፥9-16)፡፡ ባለማቋረጥ የእግዚአብሔርን ፍቅር ወደ እኛ ያስተላልፋል (ሮሜ 5፥5)፡ ደስታን መጽናናትንና ርዳታን ይሰጠናል (ዮሐ 14፥16፤ 1ተሰ 1፥6)፡፡
ይቀጥላል...
ምንጭ፦ ምሉእ ሕይወት፤ ገጽ 1314-1315፣ 1679-80
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤6👍4
. ──•◈•─────•◈•─
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“የእግዚአብሔር ፈቃድ እርሱም በጎና ደስ የሚያሰኝ ፍጹምም የሆነው ነገር ምን እንደ ሆነ ፈትናችሁ ታውቁ ዘንድ በልባችሁ መታደስ ተለወጡ እንጂ ይህን ዓለም አትምሰሉ።”
ሮሜ 12፥2
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“የእግዚአብሔር ፈቃድ እርሱም በጎና ደስ የሚያሰኝ ፍጹምም የሆነው ነገር ምን እንደ ሆነ ፈትናችሁ ታውቁ ዘንድ በልባችሁ መታደስ ተለወጡ እንጂ ይህን ዓለም አትምሰሉ።”
ሮሜ 12፥2
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤12
ቅዱሳት መጻሕፍት
#በዓለ_ኀምሳ #ጰራቅሊጦስ የቀጠለ... ሠ. መንፈስ ቅዱስ አንድን ሰው ቀጥተኛ በሆነው የጽድቅ አኗኗር ለመምራት ፍላጎት እንዳለው በብሉይ ኪዳን ላይ ተስተውሎአል፤ ከዚህ ሐሳብ ጋር በተያያዘ መልኩም ዳዊት በአንዳንድ መዝሙሮቹ ላይ መስክሮአል (መዝ 51፥10-13፣ 143፥10)። የእግዚአብሔር ሕዝብ እግዚአብሔርን በመስማት ፈንታ የግላቸውን መንገድ የሚከተሉ ከሆነ፣ በትክክል ሲታይ የመንፈስ ቅዱስን…
#በዓለ_ኀምሳ
#ጰራቅሊጦስ
የቀጠለ...
ሐ. መንፈስ ቅዱስ አማኞችን ለአገልግሎትና ለምስክርነት የሚያስታጥቅ የአገልግሎት ብርትት ነው፡፡
ይህ የመንፈስ ቅዱስ ሥራ በመንፈስ ቅዱስ ከመጠመቅ ወይም በመንፈስ ቅዱስ ከመሞላት ጋር የተያያዘ ነው፡፡ በመንፈስ ቅዱስ ስንጠመቅ፣ ለክርስቶስ ለመመስከር እንዲሁም በቤተ ክርስቲያንና በዓለም ፊት ውጤታማ ሥራ ለመሥራት የሚያስችለንን ኀይል እንቀበላለን (ሐሥ 1፥8)። የእግዚአብሔርን ቃል እንድንናገርና (ሐሥ 1፥8፡4፥31) ታምራትን እንድናደርግ (ሐሥ 2፥43፣ 3፥2-8፤ 5፥15፤ 6፥8፡ 10፥38) የሚያስችለንን በደቀ መዛሙርትና (ሐ 2፥4፤ 1፥5 ይመ) በክርስቶስ (ዮሐ 1፥32-33) ላይ የወረደውን ዐይነት መለኮታዊ ቅባት እንቀበላለን፡፡ በዚህ ዘመን ያሉ ክርስቲያኖች በሙሉ በመንፈስ ቅዱስ እንዲጠመቁ ማድረግ እግዚአብሔር አስቀድሞ ያሰበው ዐላማ ነው (ሐሥ 2፥39):: በአገልግሎት ረገድ መንፈስ ቅዱስ በቤተ ክርስቲያን ያሉ ግለሰብ አባላት ቤተ ክርስቲያንን ለማነጽ ወይም ለማጠንከር የሚያስችሉአቸውን የመንፈስ ቅዱስ ስጦታዎችን ይሰጣቸዋል (1ቆሮ 12-14)፡፡ እነዚህ ስጦታዎች መንፈስ ቅዱስ በግለሰብ አማኞች ሕይወት ውስጥ የሚገለጥባቸው ምልክቶች ሲሆኑ፣ የክርስቶስ ሀልዎት፣ ፍቅር፣ እውነትና ጻድቅ መለኪያዎች ለጋራ ጥቅም (1ቆሮ 12፥7-10) በአማኞች ኅብረት ውስጥ እውን እንዲሆኑ የሚያደርጉ ናቸው::
መ. መንፈስ ቅዱስ አማኞች በአንዱ በክርስቶስ አካል ውስጥ እንዲተባበሩ የሚያደርግ ኀይል ነው (1ቆሮ 12፥13)፤
እርሱ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ይኖራል (1ቆሮ 3፥16)፤ ቤተ ክርስቲያንን ይገነባል (ኤፌ 2፥22)፣ የቤተ ክርስቲያንን አምልኮ ያንቀሳቅሳል (ፊል 3፥3 ) ፤ ተልእኮዋን ይመራል (ሐሥ 13፥2፡4)፡ ሠራተኞቿን ይሾማል (ሐሥ 20፥28)፣ ለቤተ ክርስቲያን ስጦታን ይሰጣል (ቆሮ 12፥1-11)፤ ሰባኪዎቿን ይቀባል (ሐሥ 2፥4፤ 1ቆሮ 2፥4)፡ ወንጌልን ይጠብቃል (2ጢሞ 1፥14)፤ የጽድቅንም ሕይወት እንዲስፋፋ ያደርጋል (ዮሐ 16፥8፡ዘ፥1ቆሮ 3፥16፤ 6፥18-20)፡፡
ሠ. የመንፈስ ቅዱስ ልዩ ልዩ አገልግሎቶች እርስ በርስ የሚደጋገፉ እንጂ የሚቃረኑ አይደሉም፡፡
እንደዚሁም የመንፈስ ቅዱስ ሥራ ልዩ ልዩ ገጽታዎች እርስ በርስ የተያያዙ ናቸው፤ ፈጽሞም ሊለያዩ አይችሉም፡፡ ስለዚህ
ሀ. በክርስቶስ ያለውን የአዲስ ሕይወት ሙላትን፣
ለ. ጽድቅን የኑሮ መርሕ ማድረግን፣
ሐ) ለጌታችን የመመስከር ኀይል መቀበልን ወይም
መ. በአካሉ ውስጥ ያለንን አንድነት በተናጥል መለማመድ አንችልም፡፡
ለምሳሌ የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀት፣ መንፈስ ቅዱስ ጽድቅን በውስጣችን ለማፍራት ከሚሠራው ሥራ እንዲሁም ወደ መጽሐፍ ቅዱሳዊ እውነት በመምራትና ራሳችንን እንድንሰጥ በማድረግ ከሚፈጽመው ሥራ ተለይቶ በዘላቂነት ሊጠበቅ አይችልም።
ይቀጥላል ...
ምንጭ፦ ምሉእ ሕይወት፤ ገጽ 1679-1680
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
#ጰራቅሊጦስ
የቀጠለ...
ሐ. መንፈስ ቅዱስ አማኞችን ለአገልግሎትና ለምስክርነት የሚያስታጥቅ የአገልግሎት ብርትት ነው፡፡
ይህ የመንፈስ ቅዱስ ሥራ በመንፈስ ቅዱስ ከመጠመቅ ወይም በመንፈስ ቅዱስ ከመሞላት ጋር የተያያዘ ነው፡፡ በመንፈስ ቅዱስ ስንጠመቅ፣ ለክርስቶስ ለመመስከር እንዲሁም በቤተ ክርስቲያንና በዓለም ፊት ውጤታማ ሥራ ለመሥራት የሚያስችለንን ኀይል እንቀበላለን (ሐሥ 1፥8)። የእግዚአብሔርን ቃል እንድንናገርና (ሐሥ 1፥8፡4፥31) ታምራትን እንድናደርግ (ሐሥ 2፥43፣ 3፥2-8፤ 5፥15፤ 6፥8፡ 10፥38) የሚያስችለንን በደቀ መዛሙርትና (ሐ 2፥4፤ 1፥5 ይመ) በክርስቶስ (ዮሐ 1፥32-33) ላይ የወረደውን ዐይነት መለኮታዊ ቅባት እንቀበላለን፡፡ በዚህ ዘመን ያሉ ክርስቲያኖች በሙሉ በመንፈስ ቅዱስ እንዲጠመቁ ማድረግ እግዚአብሔር አስቀድሞ ያሰበው ዐላማ ነው (ሐሥ 2፥39):: በአገልግሎት ረገድ መንፈስ ቅዱስ በቤተ ክርስቲያን ያሉ ግለሰብ አባላት ቤተ ክርስቲያንን ለማነጽ ወይም ለማጠንከር የሚያስችሉአቸውን የመንፈስ ቅዱስ ስጦታዎችን ይሰጣቸዋል (1ቆሮ 12-14)፡፡ እነዚህ ስጦታዎች መንፈስ ቅዱስ በግለሰብ አማኞች ሕይወት ውስጥ የሚገለጥባቸው ምልክቶች ሲሆኑ፣ የክርስቶስ ሀልዎት፣ ፍቅር፣ እውነትና ጻድቅ መለኪያዎች ለጋራ ጥቅም (1ቆሮ 12፥7-10) በአማኞች ኅብረት ውስጥ እውን እንዲሆኑ የሚያደርጉ ናቸው::
መ. መንፈስ ቅዱስ አማኞች በአንዱ በክርስቶስ አካል ውስጥ እንዲተባበሩ የሚያደርግ ኀይል ነው (1ቆሮ 12፥13)፤
እርሱ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ይኖራል (1ቆሮ 3፥16)፤ ቤተ ክርስቲያንን ይገነባል (ኤፌ 2፥22)፣ የቤተ ክርስቲያንን አምልኮ ያንቀሳቅሳል (ፊል 3፥3 ) ፤ ተልእኮዋን ይመራል (ሐሥ 13፥2፡4)፡ ሠራተኞቿን ይሾማል (ሐሥ 20፥28)፣ ለቤተ ክርስቲያን ስጦታን ይሰጣል (ቆሮ 12፥1-11)፤ ሰባኪዎቿን ይቀባል (ሐሥ 2፥4፤ 1ቆሮ 2፥4)፡ ወንጌልን ይጠብቃል (2ጢሞ 1፥14)፤ የጽድቅንም ሕይወት እንዲስፋፋ ያደርጋል (ዮሐ 16፥8፡ዘ፥1ቆሮ 3፥16፤ 6፥18-20)፡፡
ሠ. የመንፈስ ቅዱስ ልዩ ልዩ አገልግሎቶች እርስ በርስ የሚደጋገፉ እንጂ የሚቃረኑ አይደሉም፡፡
እንደዚሁም የመንፈስ ቅዱስ ሥራ ልዩ ልዩ ገጽታዎች እርስ በርስ የተያያዙ ናቸው፤ ፈጽሞም ሊለያዩ አይችሉም፡፡ ስለዚህ
ሀ. በክርስቶስ ያለውን የአዲስ ሕይወት ሙላትን፣
ለ. ጽድቅን የኑሮ መርሕ ማድረግን፣
ሐ) ለጌታችን የመመስከር ኀይል መቀበልን ወይም
መ. በአካሉ ውስጥ ያለንን አንድነት በተናጥል መለማመድ አንችልም፡፡
ለምሳሌ የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀት፣ መንፈስ ቅዱስ ጽድቅን በውስጣችን ለማፍራት ከሚሠራው ሥራ እንዲሁም ወደ መጽሐፍ ቅዱሳዊ እውነት በመምራትና ራሳችንን እንድንሰጥ በማድረግ ከሚፈጽመው ሥራ ተለይቶ በዘላቂነት ሊጠበቅ አይችልም።
ይቀጥላል ...
ምንጭ፦ ምሉእ ሕይወት፤ ገጽ 1679-1680
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤6👏1
በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ በሐዋርያው ጳውሎስ የመጀመሪያው የወንጌል ጉዞ (ሐዋ. 13፥1-14፥28) ወንጌል የሰሙ ከተሞች የትኞቹ ናቸው?
Anonymous Quiz
26%
ሀ. ቆጵሮስ
12%
ለ. ተሰሎንቄ
19%
ሐ. ኤፌሶን
15%
መ. መቄዶንያ
27%
ሠ. ሁሉም
👍6❤1
. ──•◈•─────•◈•─
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“አሁን ግን እናንተ በፊት ርቃችሁ የነበራችሁ በክርስቶስ ኢየሱስ ሆናችሁ በክርስቶስ ደም ቀርባችኋል።”
ኤፌሶን 2፥13
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“አሁን ግን እናንተ በፊት ርቃችሁ የነበራችሁ በክርስቶስ ኢየሱስ ሆናችሁ በክርስቶስ ደም ቀርባችኋል።”
ኤፌሶን 2፥13
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤14
ምሉእ ሕይወት.pdf
108.8 MB
ምሉእ ሕይወት መጽሐፍ ቅዱስ
አዲሱ መደበኛ ትርጉም
ዋና አርታኢ፦ DONALD C. STAMPS
ተባባሪ አርታኢ፦ J. WESLEY ADAMS
LIFE PUBLISHERS INTERNATIONAL
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
አዲሱ መደበኛ ትርጉም
ዋና አርታኢ፦ DONALD C. STAMPS
ተባባሪ አርታኢ፦ J. WESLEY ADAMS
LIFE PUBLISHERS INTERNATIONAL
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤23🥰3
#እራሳችንን_እንመርምር
አማኝ ክርስቲያን ስንሆን በተለይ በእግዚአብሔር ቤት ውስጥ በቤተክርስቲያን ስንኖር እና ስናገለግል ከሰው የምናገኘውን ጥቅም የምናሰላና ከሰው እጅ ያለውን ለመንጠቅ የምንቋምጥ ከሆነ ምንኛ ምስኪን ነን? እንዴትስ መልእክታችን የተዛባ ነው?
“ሙሴም እጅግ ተቈጣ፥ እግዚአብሔርንም፦ ወደ ቍርባናቸው አትመልከት፤ እኔ ከእነርሱ አንድ አህያ ስንኳ አልወሰድሁም፥ ከእነርሱም አንድ ሰው አልበደልሁም አለው።”
ዘኍልቁ 16፥15
“እነሆኝ በእግዚአብሔርና እርሱ በቀባው ፊት መስክሩብኝ የማንን በሬ ወሰድሁ? የማንንስ አህያ ወሰድሁ? ማንንስ ሸነገልሁ? በማንስ ላይ ግፍ አደረግሁ? ዓይኖቼንስ ለማሳወር ከማን ጋር እጅ ጉቦ ተቀበልሁ? እኔም እመልስላችኋለሁ።”
1ኛ ሳሙኤል 12፥3
“ከማንም ብር ወይም ወርቅ ወይም ልብስ አልተመኘሁም፤”
ሐዋርያት 20፥33
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
አማኝ ክርስቲያን ስንሆን በተለይ በእግዚአብሔር ቤት ውስጥ በቤተክርስቲያን ስንኖር እና ስናገለግል ከሰው የምናገኘውን ጥቅም የምናሰላና ከሰው እጅ ያለውን ለመንጠቅ የምንቋምጥ ከሆነ ምንኛ ምስኪን ነን? እንዴትስ መልእክታችን የተዛባ ነው?
“ሙሴም እጅግ ተቈጣ፥ እግዚአብሔርንም፦ ወደ ቍርባናቸው አትመልከት፤ እኔ ከእነርሱ አንድ አህያ ስንኳ አልወሰድሁም፥ ከእነርሱም አንድ ሰው አልበደልሁም አለው።”
ዘኍልቁ 16፥15
“እነሆኝ በእግዚአብሔርና እርሱ በቀባው ፊት መስክሩብኝ የማንን በሬ ወሰድሁ? የማንንስ አህያ ወሰድሁ? ማንንስ ሸነገልሁ? በማንስ ላይ ግፍ አደረግሁ? ዓይኖቼንስ ለማሳወር ከማን ጋር እጅ ጉቦ ተቀበልሁ? እኔም እመልስላችኋለሁ።”
1ኛ ሳሙኤል 12፥3
“ከማንም ብር ወይም ወርቅ ወይም ልብስ አልተመኘሁም፤”
ሐዋርያት 20፥33
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍4❤1
. ──•◈•─────•◈•─
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“ያን መንፈስም፥ በጸጋው ጸድቀን በዘላለም ሕይወት ተስፋ ወራሾች እንድንሆን፥ በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ በእኛ ላይ አትርፎ አፈሰሰው።”
ቲቶ 3፥6-7
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“ያን መንፈስም፥ በጸጋው ጸድቀን በዘላለም ሕይወት ተስፋ ወራሾች እንድንሆን፥ በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ በእኛ ላይ አትርፎ አፈሰሰው።”
ቲቶ 3፥6-7
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤8
ጰራቅሊጦስ.pdf
2.1 MB
❤7👍2👏1
. ──•◈•─────•◈•─
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“አምላክህን መፍራትህ መጽናናትህ፥ የቅንነትህም መንገድ ተስፋህ አይደለምን?”
ኢዮብ 4፥6
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“አምላክህን መፍራትህ መጽናናትህ፥ የቅንነትህም መንገድ ተስፋህ አይደለምን?”
ኢዮብ 4፥6
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
🔥5❤3
Pligrem
Nigusse Denano
🥰2❤1👏1
ቅዱሳት መጻሕፍት
#በዓለ_ኀምሳ #ጰራቅሊጦስ የቀጠለ... ሐ. መንፈስ ቅዱስ አማኞችን ለአገልግሎትና ለምስክርነት የሚያስታጥቅ የአገልግሎት ብርትት ነው፡፡ ይህ የመንፈስ ቅዱስ ሥራ በመንፈስ ቅዱስ ከመጠመቅ ወይም በመንፈስ ቅዱስ ከመሞላት ጋር የተያያዘ ነው፡፡ በመንፈስ ቅዱስ ስንጠመቅ፣ ለክርስቶስ ለመመስከር እንዲሁም በቤተ ክርስቲያንና በዓለም ፊት ውጤታማ ሥራ ለመሥራት የሚያስችለንን ኀይል እንቀበላለን (ሐሥ…
#በዓለ_ኀምሳ
#ጰራቅሊጦስ
የቀጠለ...
መንፈስ ቅዱስ በታሪክ ውስጥ
በዘመናችን የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ምስባኮች ላይ መንፈስ ቅዱስ የሚለው ስም መጥራት የተለመደ ቢሆንም፣ ሕዝበ ክርስትያኑ ስለ መንፈስ ቅዱስ ማንነት ጠንቅቆ ያውቃል ለማለት አስቸጋሪ ይመስላል። መንፈስ ቅዱስን አስመልክቶ ግልጽ አስተምህሮ ያለም አይመስልም። ለአንዳንዶች መንፈስ ቅዱስ ተአምራት ማድረጊያ ኀይል፣ እንዲሁም በጨርቅ ተደርጎ እና በጠርሙስ ታሽጎ የሚወሰድ ትንግርት መፍጠሪያ ሲሆን፣ ለሌሎች ደግሞ ማነቃቂያ እና ተሃድሶ የሚያመጣ እሳት ወዘተ. ነው።
የክርስትና እምነት መሠረት የአሓዱ ሥሉስ አምላክ አምልኮ መሆኑ እሙን ነው። መንፈስ ቅዱስ ደግሞ የዚህ አሓዱ ሥሉስ አምላክ አንዱ አካል ነው። ይሁን እንጂ የማንነቱን ያህል በቤተ ክርስቲያን ታሪክ ውስጥ ተገቢውን ስፍራ አልተሰጠውም፣ አሊያም ብዙዎች በመንፈስ ቅዱስ ስም ብዙ አስደንጋጭ እና አስነዋሪ ነገሮችን ፈጽመዋል። በዚህች አጭር መጣጥፍ በቤተ ክርስቲያን ታሪክ ውስጥ መንፈስ ቅዱስ የነበረውን ሚና፣ በተለያዩ ዘመናት በመንፈስ ቅዱስ አስተምህሮ እና ልምምድ ላይ የተነሡ የተለያዩ ኑፋቄዎችን በወፍ በረር ተመልክተን፣ በዘመናችን ያሉትን በመንፈስ ቅዱስ ስም የሚደረጉ እንቅስቃሴዎች በእግዚአብሔር ቃል እንገመግማለን።
በቤተ ክርስቲያን ታሪክ ውስጥ በእግዚአብሔር አብ እና በእግዚአብሔር ወልድ አስተምህሮዎች ዙሪያ ከፍተኛ ትኩረት የተሰጠ እና ብዙ ውይይቶች የተካሄዱባቸው መሆኑ ግልጽ ነው። በደፈናው ለተመለከተው የእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ አስተምህሮ በቤተ ክርስቲያን ጉባኤዎች እና ታሪክ የተዘነጋ ይመስላል። ይሁን እንጂ የቤተ ክርስቲያን አባቶች ስለ እግዚአብሔር ወልድ የተለያዩ ጉባኤዎችን ሲያካሄዱ፣ አጽንዖት ሰጥተውትም ባይሆን በእግረ መንገዳቸው የመንፈስ ቅዱስ አስተምህሮን ነካክተው ዐልፈዋል።
ቅድመ ኒቂያ ዘመን
በቅድመ ኒቂያ የቤተ ክርስቲያን አባቶች ከሆኑት ከአሌክሳንድሪያው ቀሌመንጦስ እና ከአንጾኪያው ቴዎፍሎስ ጽሑፎች መረዳት እንደሚቻለው የእግዚአብሔር አብን፣ የእግዚአብሔር ወልድን እና የእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስን መለኮትነት የተረዱ መሆናቸውን መመልከት ይቻላል። እግዚአብሔር አብ፣ እግዚአብሔር ወልድ እና እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ በአካል ሦስትነታቸው፣ እንዲህ በባሕርይ አንድነታቸውን ለማሳየት “ሥላሴ” የሚለውን ቃል ለመጀመሪያ ጊዜ የተጠቀመው በቅድመ ኒቂያ ዘመን የኖረው ጠርጠሉስ (ተርቱልያን) የተባለ የቤተ ክርስቲያን አባት ነው። ጠርጠሉስ በዚህ ቃል አማካይነት የክርስትና እምነት የአሓዱ አምላክ አምልኮት እንጂ የብዝኀ አምላክ አምልኮ አለመሆኑን አሳይቷል።
ይቀጥላል...
ምንጭ:- hintset.org
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
#ጰራቅሊጦስ
የቀጠለ...
መንፈስ ቅዱስ በታሪክ ውስጥ
በዘመናችን የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ምስባኮች ላይ መንፈስ ቅዱስ የሚለው ስም መጥራት የተለመደ ቢሆንም፣ ሕዝበ ክርስትያኑ ስለ መንፈስ ቅዱስ ማንነት ጠንቅቆ ያውቃል ለማለት አስቸጋሪ ይመስላል። መንፈስ ቅዱስን አስመልክቶ ግልጽ አስተምህሮ ያለም አይመስልም። ለአንዳንዶች መንፈስ ቅዱስ ተአምራት ማድረጊያ ኀይል፣ እንዲሁም በጨርቅ ተደርጎ እና በጠርሙስ ታሽጎ የሚወሰድ ትንግርት መፍጠሪያ ሲሆን፣ ለሌሎች ደግሞ ማነቃቂያ እና ተሃድሶ የሚያመጣ እሳት ወዘተ. ነው።
የክርስትና እምነት መሠረት የአሓዱ ሥሉስ አምላክ አምልኮ መሆኑ እሙን ነው። መንፈስ ቅዱስ ደግሞ የዚህ አሓዱ ሥሉስ አምላክ አንዱ አካል ነው። ይሁን እንጂ የማንነቱን ያህል በቤተ ክርስቲያን ታሪክ ውስጥ ተገቢውን ስፍራ አልተሰጠውም፣ አሊያም ብዙዎች በመንፈስ ቅዱስ ስም ብዙ አስደንጋጭ እና አስነዋሪ ነገሮችን ፈጽመዋል። በዚህች አጭር መጣጥፍ በቤተ ክርስቲያን ታሪክ ውስጥ መንፈስ ቅዱስ የነበረውን ሚና፣ በተለያዩ ዘመናት በመንፈስ ቅዱስ አስተምህሮ እና ልምምድ ላይ የተነሡ የተለያዩ ኑፋቄዎችን በወፍ በረር ተመልክተን፣ በዘመናችን ያሉትን በመንፈስ ቅዱስ ስም የሚደረጉ እንቅስቃሴዎች በእግዚአብሔር ቃል እንገመግማለን።
በቤተ ክርስቲያን ታሪክ ውስጥ በእግዚአብሔር አብ እና በእግዚአብሔር ወልድ አስተምህሮዎች ዙሪያ ከፍተኛ ትኩረት የተሰጠ እና ብዙ ውይይቶች የተካሄዱባቸው መሆኑ ግልጽ ነው። በደፈናው ለተመለከተው የእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ አስተምህሮ በቤተ ክርስቲያን ጉባኤዎች እና ታሪክ የተዘነጋ ይመስላል። ይሁን እንጂ የቤተ ክርስቲያን አባቶች ስለ እግዚአብሔር ወልድ የተለያዩ ጉባኤዎችን ሲያካሄዱ፣ አጽንዖት ሰጥተውትም ባይሆን በእግረ መንገዳቸው የመንፈስ ቅዱስ አስተምህሮን ነካክተው ዐልፈዋል።
ቅድመ ኒቂያ ዘመን
በቅድመ ኒቂያ የቤተ ክርስቲያን አባቶች ከሆኑት ከአሌክሳንድሪያው ቀሌመንጦስ እና ከአንጾኪያው ቴዎፍሎስ ጽሑፎች መረዳት እንደሚቻለው የእግዚአብሔር አብን፣ የእግዚአብሔር ወልድን እና የእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስን መለኮትነት የተረዱ መሆናቸውን መመልከት ይቻላል። እግዚአብሔር አብ፣ እግዚአብሔር ወልድ እና እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ በአካል ሦስትነታቸው፣ እንዲህ በባሕርይ አንድነታቸውን ለማሳየት “ሥላሴ” የሚለውን ቃል ለመጀመሪያ ጊዜ የተጠቀመው በቅድመ ኒቂያ ዘመን የኖረው ጠርጠሉስ (ተርቱልያን) የተባለ የቤተ ክርስቲያን አባት ነው። ጠርጠሉስ በዚህ ቃል አማካይነት የክርስትና እምነት የአሓዱ አምላክ አምልኮት እንጂ የብዝኀ አምላክ አምልኮ አለመሆኑን አሳይቷል።
ይቀጥላል...
ምንጭ:- hintset.org
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
🔥4
#እንወያይ
#በዓለ_ኀምሳ
ከከቤተክርስቲያን አባቶች አንዱ ቅዱስ ኢራኔዎስ (የፖሊካርፕ ደቀ መዝሙር ነው። ፖሊካርፕ ደግሞ የሐዋርያው ዮሐንስ ደቀ መዝሙር ነው) ስለ ቤተክርስቲያን እና መንፈስ ቅዱስ ትስስር የሚከተለውን ብሏል። በአሁን ዘመን ያለቺውን ቤተክርስቲያን እንዴት ታዩያታላችሁ? እስቲ እንወያይበት።
"
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
#በዓለ_ኀምሳ
ከከቤተክርስቲያን አባቶች አንዱ ቅዱስ ኢራኔዎስ (የፖሊካርፕ ደቀ መዝሙር ነው። ፖሊካርፕ ደግሞ የሐዋርያው ዮሐንስ ደቀ መዝሙር ነው) ስለ ቤተክርስቲያን እና መንፈስ ቅዱስ ትስስር የሚከተለውን ብሏል። በአሁን ዘመን ያለቺውን ቤተክርስቲያን እንዴት ታዩያታላችሁ? እስቲ እንወያይበት።
"
ቤተ ክርስቲያን ባለችበት የእግዚአብሔር መንፈስ አለ የእግዚአብሔርም መንፈስ ባለበት ቤተ ክርስቲያንና ፀጋ ሁሉ አሉ።"ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤11
. ──•◈•─────•◈•─
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“ለፍጥረቱ የበኵራት ዓይነት እንድንሆን በእውነት ቃል አስቦ ወለደን።”
ያዕቆብ 1፥18
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“ለፍጥረቱ የበኵራት ዓይነት እንድንሆን በእውነት ቃል አስቦ ወለደን።”
ያዕቆብ 1፥18
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤5👍4
#የእግዚአብሔር_ቃል_ምን_ይላል?
ሕዝቅኤል 36
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
²⁴ ከአሕዛብም መካከል አወጣችኋለሁ ከየአገሩም ሁሉ እሰበስባችኋለሁ ወደ ገዛ ምድራችሁም አመጣችኋለሁ።
²⁵ ጥሩ ውኃንም እረጭባችኋለሁ እናንተም ትጠራላችሁ፥ ከርኵሰታችሁም ሁሉ ከጣዖቶቻችሁም ሁሉ አጠራችኋለሁ።
²⁶ አዲስም ልብ እሰጣችኋለሁ አዲስም መንፈስ በውስጣችሁ አኖራለሁ፤ የድንጋዩንም ልብ ከሥጋችሁ አወጣለሁ የሥጋንም ልብ እሰጣችኋለሁ።
²⁷ መንፈሴንም በውስጣችሁ አኖራለሁ በትእዛዜም አስሄዳችኋለሁ፥ ፍርዴንም ትጠብቃላችሁ ታደርጉትማላችሁ።
²⁸ ለአባቶቻችሁም በሰጠኋት ምድር ትኖራላችሁ፤ ሕዝብም ትሆኑኛላችሁ እኔም አምላክ እሆናችኋለሁ።
²⁹ ከርኵሰታችሁም ሁሉ አድናችኋለሁ፤ እህልንም እጠራዋለሁ አበዛውማለሁ ራብንም አላመጣባችሁም።
³⁰ ደግሞም የራብን ስድብ ከአሕዛብ ዘንድ እንዳትሸከሙ የዛፍን ፍሬና የእርሻውን ቡቃያ አበዛለሁ።
³¹ ክፉውን መንገዳችሁንና መልካም ያይደለውን ሥራችሁንም ታስባላችሁ፥ ስለ በደላችሁና ስለ ርኵሰታችሁም ራሳችሁን ትጸየፋላችሁ።
³² ይህን የሠራሁ ስለ እናንተ እንዳይደለ በእናንተ ዘንድ የታወቀ ይሁን፥ ይላል ጌታ እግዚአብሔር፤ የእስራኤል ቤት ሆይ፥ ስለ መንገዳችሁ እፈሩና ተዋረዱ።
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ሕዝቅኤል 36
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
²⁴ ከአሕዛብም መካከል አወጣችኋለሁ ከየአገሩም ሁሉ እሰበስባችኋለሁ ወደ ገዛ ምድራችሁም አመጣችኋለሁ።
²⁵ ጥሩ ውኃንም እረጭባችኋለሁ እናንተም ትጠራላችሁ፥ ከርኵሰታችሁም ሁሉ ከጣዖቶቻችሁም ሁሉ አጠራችኋለሁ።
²⁶ አዲስም ልብ እሰጣችኋለሁ አዲስም መንፈስ በውስጣችሁ አኖራለሁ፤ የድንጋዩንም ልብ ከሥጋችሁ አወጣለሁ የሥጋንም ልብ እሰጣችኋለሁ።
²⁷ መንፈሴንም በውስጣችሁ አኖራለሁ በትእዛዜም አስሄዳችኋለሁ፥ ፍርዴንም ትጠብቃላችሁ ታደርጉትማላችሁ።
²⁸ ለአባቶቻችሁም በሰጠኋት ምድር ትኖራላችሁ፤ ሕዝብም ትሆኑኛላችሁ እኔም አምላክ እሆናችኋለሁ።
²⁹ ከርኵሰታችሁም ሁሉ አድናችኋለሁ፤ እህልንም እጠራዋለሁ አበዛውማለሁ ራብንም አላመጣባችሁም።
³⁰ ደግሞም የራብን ስድብ ከአሕዛብ ዘንድ እንዳትሸከሙ የዛፍን ፍሬና የእርሻውን ቡቃያ አበዛለሁ።
³¹ ክፉውን መንገዳችሁንና መልካም ያይደለውን ሥራችሁንም ታስባላችሁ፥ ስለ በደላችሁና ስለ ርኵሰታችሁም ራሳችሁን ትጸየፋላችሁ።
³² ይህን የሠራሁ ስለ እናንተ እንዳይደለ በእናንተ ዘንድ የታወቀ ይሁን፥ ይላል ጌታ እግዚአብሔር፤ የእስራኤል ቤት ሆይ፥ ስለ መንገዳችሁ እፈሩና ተዋረዱ።
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤11🙏6