. ──•◈•─────•◈•─
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“ዮቶርም እግዚአብሔር ለእስራኤል ስላደረገው ቸርነት ሁሉ፥ ከግብፃውያንም እጅ ስላዳናቸው ደስ አለው።”
ዘጸአት 18፥9
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“ዮቶርም እግዚአብሔር ለእስራኤል ስላደረገው ቸርነት ሁሉ፥ ከግብፃውያንም እጅ ስላዳናቸው ደስ አለው።”
ዘጸአት 18፥9
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤9
ቅዱሳት መጻሕፍት
የጸጋ ስጦታዎች ውጤታማ አሠራር እንዴት ሊሆን ይገባል? ክፍል-2 በመርዕድ ለማ 3. ሁሉን ፈትኑ፦ መቼም የሰማነውንና ያገኘነውን ሁሉ አግበስብሶ መቀበል ጤናማ ሕይወታችንን ያውካል። ያለንበት ዓለም በብዙ ዓይነት የመናፍስት አሠራር የተሞላ ነው። የእግዚአብሔር መንፈስ አለ፤ የሰይጣን መንፈስ አለ፤ የሰውም መንፈስ…
የጸጋ ስጦታዎች ውጤታማ አሠራር እንዴት ሊሆን ይገባል?
ክፍል-3
(የመጨረሻ ክፍል)
በመርዕድ ለማ
የጸጋ ስጦታዎችና ፍቅር
ሐዋርያው ጳውሎስ ስለ መንፈስ ቅዱስ ሥራና ስጦታዎች በሰፊው የተናገረበት ክፍል ለቆሮንቶስ ሰዎች የጻፈው የመጀመሪያው መልእክቱ ነው። በዚሁ መልእክት በ12ኛው ምዕራፍ ላይ የጸጋ ስጦታዎችን ምንነትና የስጦታዎቹ ምንጭ ማን እንደሆነ የተናገረበት ክፍል ነው። በምዕራፍ 14 ላይ ደግሞ በማህበር፣ በጉባዔ ውስጥ እንዴት መጠቀም እንደሚኖርብን የተናገረበት ክፍል ነው። ምዕራፍ 13 ስጦታዎች አመርቂና ውጤታማ መሆን የሚችሉት በፍቅር ስንጠቀምባቸው ብቻ ነው በማለት ያስረዳል፤ ምዕራፍ 13 ስለ ፍቅር በስፋት የሚናገርበት ምዕራፍ ነው። ከቁጥር 1-3 ካለፍቅር የጸጋ ስጦታዎች ጠቃሚነት እንደሌላቸው ተገልጦአል፤ ከቁጥር 4-7 ደግሞ የፍቅርን የተለያዩ መግለጫዎች እንመለከታለን። ከቁጥር 8-13 የጸጋ ስጦታዎች እስከ ተወሰነ ጊዜ ድረስ ብቻ እንደሚሠሩና እምነት፣ ተስፋ፣ ፍቅር ጸንተው እንደሚኖሩ ገልጦ ከሦስቱም የሚበልጠው ፍቅር እንደ ሆነ ተናግሯል። ብዙውን ጊዜ በዚሁ በምዕራፍ 13 ላይ የተገለጸውን ፍቅር ሰዎች በተሳሳተ መልኩ ይጠቀሙበታል።
አንዳንዶቹ የጸጋ ስጦታንና የመንፈስ ቅዱስን አገልግሎት ላለማጉላት የፈለጉ ሰዎች፦ ፍቅር ነው እንጂ የጸጋ ስጦታ ጠቃሚ አይደለም በማለት ለጸጋ ስጦታዎች ሥፍራ እንዳይሰጡና የመንፈስ ቅዱስን እሳት ለማዳፈኛ ሲጠቀሙበት ይታያል። ይህ ትልቁ ስሕተት ነው። አንድን እውነት ሌላውን እውነት ለማጥፊያ መጠቀም በእግዚአብሔር ዘንድ የሚያስጠይቅ ስለሆነ እንጠንቀቅ። ሌሎች ደግሞ ከመጠን ባለፈ መልኩ የጸጋ ስጦታዎችን ብቻ በመግለጥ ስጦታዎችን ካለፍቅር የሚጠቀሙና የሚያስተምሩ አሉ። እነርሱም የትም አይደርሱም። ያለፍቅር ሁሉ ከንቱ ነውና። ከቁጥር 4-7 ባለው ክፍል 15 የተለያዩ የፍቅርን ባሕርያት እንመለከታለን።
ፍቅር ይታገሳል፦ አገልጋዮች ሰዎች አገልግሎታችንን ባይረዱ ችግር ቢገጥመን በዚህም ብንፈተን በትዕግስት እግዚአብሔርን መጠበቅ ፍቅር ነው።
ፍቅር ቸርነትን ያደርጋል፦ አገልግሎታችን እኛው ለኛው መሆን የለበትም፣ ለሌሎች ሰዎች ጥቅምና መታነጽ ምክንያት መሆን አለበት። ስለዚህ ለሌሎች ቸርነት ማድረግና ርህራሄን ማሳየት ፍቅር ነው።
ፍቅር አይቀናም፦ አገልጋዮች በምናገለግለው የጸጋ አገልግሎት ወደ ቅናት ውስጥ ከገባን ጸጋችንን በተሳሳተ መንገድ ተጠቅመንበታል ማለት ነው። ስለዚህ ከቅናት ነጻ መሆን አለብን።
ፍቅር አይመካም፣ አይታበይም፦ ትምክህተኛነት እግዚአብሔርን ያለማወቅ ነው። ማንም ሰው ትምክህቱ በእግዚአብሔር ላይ እንዲሆን የእግዚአብሔር ቃል ያዛል። “ጠቢብ በጥበቡ አይመካ፣ ኃያልም በኃይሉ አይመካ፤ ባለጠጋም በብልጥግናው አይመካ፤ ነገር ግን የሚመካው፣ ምሕረትንና ፍርድን ጽድቅንም በምድር ላይ የማደርግ እኔ እግዚአብሔር መሆኔን በማወቁና በማስተዋሉ በዚህ ይመካ፤ ደስ የሚያሰኙኝ እነዚህ ናቸውና፣ ይላል እግዚአብሔር።” [ኤርምያስ 9፥23-24]
ፍቅር የማይገባውን አያደርግም፦ አንድ አገልጋይ በአነጋገሩ፣ በአሳቡ፣ በሚያደርገው ነገር ሁሉ ጠንቃቃና አስተዋይ ሊሆን ይገባዋል። ሰዎች በጸጋ ስጦታዎች የምናገለግላቸውን አገልግሎቶች ብቻ ሳይሆን ጠቅላላ ሕይወታችንንም ይከታተላሉ። ስለዚህ ጨዋና የተከበረ ጭምትና ነውር የሌለበት ከክፋትም የራቅን ልንሆን ይገባል።
ፍቅር የራሱን አይፈልግም፦ ከአገልግሎታችን ጋር በተያያዘ መልኩ የተለያዩ ፈተናዎችና ችግሮች ሲገጥሙን፣ ለምን ተነካሁ? በማለት የያዝነውን አደራ መጣል የፍቅር ጉድለት ነው። አገልጋይ ሳይነካ ማገልገል ጨርሶ አይችልም።
ፍቅር አይበሳጭም፦ አገልጋይ ከተበሳጨ በጸጋ አያድግም። ዘወትር በቅርብ ያለውን ብቻ ስለሚያይ በርቀት ያለውን የእግዚአብሔርን አሳብ አይረዳም። ስለዚህ በሆነው ባልሆነው መበሳጨት በአንድ አገልጋይ የሚታይ የፍቅር ጉድለት ነው።
ፍቅር በደልን አይቆጥርም፦ አገልግሎታችን ከተለያዩ ሰዎች ጋር የተያያዘ ነው። በመሆኑም ከሰዎች ጋር እስከ ተያያዘ ድረስ ደግሞ ሰዎችን መጉዳትና በሰዎችም መጎዳት ሊያጋጥም ይችላል። ጎዳንም ተጎዳንም ዘወትር ይቅር ለማለትና በይቅርታ ለማስተካከል ዝግጁ መሆን ይኖርብናል። ይኸን ብናደርግ የፍቅር ሰዎች ሆነናል ማለት ነው።
ፍቅር ከእውነት ጋር ደስ ይለዋል እንጂ ስለ አመጻ ደስ አይለውም፦ የፍቅር ሰው የሌሎች ሰዎች አገልግሎትና የመንፈሳዊ ሕይወት እድገት ያስደስተዋል። እንዲሁም ውድቀታቸውንና ችግራቸውን በራሱ እንደ ደረሰ አድርጎ ይቆጥረዋል፤ ይሰማዋል።
ፍቅር ሁሉን ይታገሳል፦ የሌሎችን ሰዎች ስሕተት ለማጋለጥ አይቸኩልም፤ ወይም ትክክለኛነቱንና ሀቀኛነቱን ለማሳየት አይጥርም። በሚቃወሙትና በሚተቹት ሰዎች ሁሉ ፊት እራሱን ይገዛል። ሁሉን ያምናል፣ የፍቅር ሰው በሚሰማውና በሚያየው ነገር ልቡ አያፈገፍግም፤ ዳሩ ግን በአምላኩ ይታመናል።
ፍቅር ሁሉን ተስፋ ያደርጋል፦ በፍቅር የሚያገለግል ሰው ዛሬ በጨለማ ያለ ቢመስለውም የነገው ብርሃን እንደሚሆንለት በአምላኩ ተስፋ ያደርጋል። በሙሉ ተስፋም ይወጣል ይገባልም።
ፍቅር በሁሉ ይጸናል፦ አንድ የጌታ አገልጋይ ብዙ ሰልፍና ጦር የሚገጥመው ሰው ነው። ከወጀቡና ከማዕበሉ የተነሳ ሥፍራውን በመልቀቅ የሚሸሽ ሳይሆን በአምላኩ ተማምኖ ተደግፎ ቀጥ ብሎ የሚቆም መሆን አለበት። እንግዲያስ እውነትን በፍቅር እየገለጥን ከጌታ የተቀበልነውን አገልግሎት በፍቅር መጠቀም እንድንችል እግዚአብሔር ይርዳን። አሜን።
ምንጭ:- shalomgospel.com
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ክፍል-3
(የመጨረሻ ክፍል)
በመርዕድ ለማ
የጸጋ ስጦታዎችና ፍቅር
ሐዋርያው ጳውሎስ ስለ መንፈስ ቅዱስ ሥራና ስጦታዎች በሰፊው የተናገረበት ክፍል ለቆሮንቶስ ሰዎች የጻፈው የመጀመሪያው መልእክቱ ነው። በዚሁ መልእክት በ12ኛው ምዕራፍ ላይ የጸጋ ስጦታዎችን ምንነትና የስጦታዎቹ ምንጭ ማን እንደሆነ የተናገረበት ክፍል ነው። በምዕራፍ 14 ላይ ደግሞ በማህበር፣ በጉባዔ ውስጥ እንዴት መጠቀም እንደሚኖርብን የተናገረበት ክፍል ነው። ምዕራፍ 13 ስጦታዎች አመርቂና ውጤታማ መሆን የሚችሉት በፍቅር ስንጠቀምባቸው ብቻ ነው በማለት ያስረዳል፤ ምዕራፍ 13 ስለ ፍቅር በስፋት የሚናገርበት ምዕራፍ ነው። ከቁጥር 1-3 ካለፍቅር የጸጋ ስጦታዎች ጠቃሚነት እንደሌላቸው ተገልጦአል፤ ከቁጥር 4-7 ደግሞ የፍቅርን የተለያዩ መግለጫዎች እንመለከታለን። ከቁጥር 8-13 የጸጋ ስጦታዎች እስከ ተወሰነ ጊዜ ድረስ ብቻ እንደሚሠሩና እምነት፣ ተስፋ፣ ፍቅር ጸንተው እንደሚኖሩ ገልጦ ከሦስቱም የሚበልጠው ፍቅር እንደ ሆነ ተናግሯል። ብዙውን ጊዜ በዚሁ በምዕራፍ 13 ላይ የተገለጸውን ፍቅር ሰዎች በተሳሳተ መልኩ ይጠቀሙበታል።
አንዳንዶቹ የጸጋ ስጦታንና የመንፈስ ቅዱስን አገልግሎት ላለማጉላት የፈለጉ ሰዎች፦ ፍቅር ነው እንጂ የጸጋ ስጦታ ጠቃሚ አይደለም በማለት ለጸጋ ስጦታዎች ሥፍራ እንዳይሰጡና የመንፈስ ቅዱስን እሳት ለማዳፈኛ ሲጠቀሙበት ይታያል። ይህ ትልቁ ስሕተት ነው። አንድን እውነት ሌላውን እውነት ለማጥፊያ መጠቀም በእግዚአብሔር ዘንድ የሚያስጠይቅ ስለሆነ እንጠንቀቅ። ሌሎች ደግሞ ከመጠን ባለፈ መልኩ የጸጋ ስጦታዎችን ብቻ በመግለጥ ስጦታዎችን ካለፍቅር የሚጠቀሙና የሚያስተምሩ አሉ። እነርሱም የትም አይደርሱም። ያለፍቅር ሁሉ ከንቱ ነውና። ከቁጥር 4-7 ባለው ክፍል 15 የተለያዩ የፍቅርን ባሕርያት እንመለከታለን።
ፍቅር ይታገሳል፦ አገልጋዮች ሰዎች አገልግሎታችንን ባይረዱ ችግር ቢገጥመን በዚህም ብንፈተን በትዕግስት እግዚአብሔርን መጠበቅ ፍቅር ነው።
ፍቅር ቸርነትን ያደርጋል፦ አገልግሎታችን እኛው ለኛው መሆን የለበትም፣ ለሌሎች ሰዎች ጥቅምና መታነጽ ምክንያት መሆን አለበት። ስለዚህ ለሌሎች ቸርነት ማድረግና ርህራሄን ማሳየት ፍቅር ነው።
ፍቅር አይቀናም፦ አገልጋዮች በምናገለግለው የጸጋ አገልግሎት ወደ ቅናት ውስጥ ከገባን ጸጋችንን በተሳሳተ መንገድ ተጠቅመንበታል ማለት ነው። ስለዚህ ከቅናት ነጻ መሆን አለብን።
ፍቅር አይመካም፣ አይታበይም፦ ትምክህተኛነት እግዚአብሔርን ያለማወቅ ነው። ማንም ሰው ትምክህቱ በእግዚአብሔር ላይ እንዲሆን የእግዚአብሔር ቃል ያዛል። “ጠቢብ በጥበቡ አይመካ፣ ኃያልም በኃይሉ አይመካ፤ ባለጠጋም በብልጥግናው አይመካ፤ ነገር ግን የሚመካው፣ ምሕረትንና ፍርድን ጽድቅንም በምድር ላይ የማደርግ እኔ እግዚአብሔር መሆኔን በማወቁና በማስተዋሉ በዚህ ይመካ፤ ደስ የሚያሰኙኝ እነዚህ ናቸውና፣ ይላል እግዚአብሔር።” [ኤርምያስ 9፥23-24]
ፍቅር የማይገባውን አያደርግም፦ አንድ አገልጋይ በአነጋገሩ፣ በአሳቡ፣ በሚያደርገው ነገር ሁሉ ጠንቃቃና አስተዋይ ሊሆን ይገባዋል። ሰዎች በጸጋ ስጦታዎች የምናገለግላቸውን አገልግሎቶች ብቻ ሳይሆን ጠቅላላ ሕይወታችንንም ይከታተላሉ። ስለዚህ ጨዋና የተከበረ ጭምትና ነውር የሌለበት ከክፋትም የራቅን ልንሆን ይገባል።
ፍቅር የራሱን አይፈልግም፦ ከአገልግሎታችን ጋር በተያያዘ መልኩ የተለያዩ ፈተናዎችና ችግሮች ሲገጥሙን፣ ለምን ተነካሁ? በማለት የያዝነውን አደራ መጣል የፍቅር ጉድለት ነው። አገልጋይ ሳይነካ ማገልገል ጨርሶ አይችልም።
ፍቅር አይበሳጭም፦ አገልጋይ ከተበሳጨ በጸጋ አያድግም። ዘወትር በቅርብ ያለውን ብቻ ስለሚያይ በርቀት ያለውን የእግዚአብሔርን አሳብ አይረዳም። ስለዚህ በሆነው ባልሆነው መበሳጨት በአንድ አገልጋይ የሚታይ የፍቅር ጉድለት ነው።
ፍቅር በደልን አይቆጥርም፦ አገልግሎታችን ከተለያዩ ሰዎች ጋር የተያያዘ ነው። በመሆኑም ከሰዎች ጋር እስከ ተያያዘ ድረስ ደግሞ ሰዎችን መጉዳትና በሰዎችም መጎዳት ሊያጋጥም ይችላል። ጎዳንም ተጎዳንም ዘወትር ይቅር ለማለትና በይቅርታ ለማስተካከል ዝግጁ መሆን ይኖርብናል። ይኸን ብናደርግ የፍቅር ሰዎች ሆነናል ማለት ነው።
ፍቅር ከእውነት ጋር ደስ ይለዋል እንጂ ስለ አመጻ ደስ አይለውም፦ የፍቅር ሰው የሌሎች ሰዎች አገልግሎትና የመንፈሳዊ ሕይወት እድገት ያስደስተዋል። እንዲሁም ውድቀታቸውንና ችግራቸውን በራሱ እንደ ደረሰ አድርጎ ይቆጥረዋል፤ ይሰማዋል።
ፍቅር ሁሉን ይታገሳል፦ የሌሎችን ሰዎች ስሕተት ለማጋለጥ አይቸኩልም፤ ወይም ትክክለኛነቱንና ሀቀኛነቱን ለማሳየት አይጥርም። በሚቃወሙትና በሚተቹት ሰዎች ሁሉ ፊት እራሱን ይገዛል። ሁሉን ያምናል፣ የፍቅር ሰው በሚሰማውና በሚያየው ነገር ልቡ አያፈገፍግም፤ ዳሩ ግን በአምላኩ ይታመናል።
ፍቅር ሁሉን ተስፋ ያደርጋል፦ በፍቅር የሚያገለግል ሰው ዛሬ በጨለማ ያለ ቢመስለውም የነገው ብርሃን እንደሚሆንለት በአምላኩ ተስፋ ያደርጋል። በሙሉ ተስፋም ይወጣል ይገባልም።
ፍቅር በሁሉ ይጸናል፦ አንድ የጌታ አገልጋይ ብዙ ሰልፍና ጦር የሚገጥመው ሰው ነው። ከወጀቡና ከማዕበሉ የተነሳ ሥፍራውን በመልቀቅ የሚሸሽ ሳይሆን በአምላኩ ተማምኖ ተደግፎ ቀጥ ብሎ የሚቆም መሆን አለበት። እንግዲያስ እውነትን በፍቅር እየገለጥን ከጌታ የተቀበልነውን አገልግሎት በፍቅር መጠቀም እንድንችል እግዚአብሔር ይርዳን። አሜን።
ምንጭ:- shalomgospel.com
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤4👍3
. ──•◈•─────•◈•─
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“ፊተኛ ኑሮአችሁን እያሰባችሁ እንደሚያታልል ምኞት የሚጠፋውን አሮጌውን ሰው አስወግዱ፥”
ኤፌሶን 4፥22
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“ፊተኛ ኑሮአችሁን እያሰባችሁ እንደሚያታልል ምኞት የሚጠፋውን አሮጌውን ሰው አስወግዱ፥”
ኤፌሶን 4፥22
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤8
"ጌታው በስብከትህ ውስጥ ክርስቶስ የለም? እንዲያ ከሆነ ወደ ቤትህ ተመለስ፤ የሚረባ ነገር መስበክ እስክትጀምር ድረስ መልሰህ መቼም አትስበክ።"
ቻርለስ ስፐርጅን
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ቻርለስ ስፐርጅን
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍10❤2
. ──•◈•─────•◈•─
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“በልቤ ስላላችሁ፣ ስለ ሁላችሁ እንዲህ ማሰቤ ተገቢ ነው፤ በእስራቴም ሆነ ለወንጌል ስመክትና ሳጸናው ሁላችሁም ከእኔ ጋር የእግዚአብሔር ጸጋ ተካፋዮች ናችሁና።”
ፊልጵስዩስ 1፥7 (አዲሱ መ.ት)
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“በልቤ ስላላችሁ፣ ስለ ሁላችሁ እንዲህ ማሰቤ ተገቢ ነው፤ በእስራቴም ሆነ ለወንጌል ስመክትና ሳጸናው ሁላችሁም ከእኔ ጋር የእግዚአብሔር ጸጋ ተካፋዮች ናችሁና።”
ፊልጵስዩስ 1፥7 (አዲሱ መ.ት)
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤5🔥1
ቅዱሳት መጻሕፍት
#መጻሕፍትን_እንመርምር የኢየሱስ ክርስቶስ ትንሣኤ የአካል ወይስ የመንፈስ? ክፍል-፭ 2. የሐዋርያው ጳውሎስ አስተምህሮ ሐዋርያው ጳውሎስ እጅግ ጥንታዊ ነው የሚባለውን የቤተ ክርስቲያን የእምነት መግለጫ ጠቅሶ በጻፈበት ክፍል ላይ፣ የክርስቶስን ሞት ከገለጸ በኋላ የሃይማኖት…
#መጻሕፍትን_እንመርምር
የኢየሱስ ክርስቶስ ትንሣኤ የአካል ወይስ የመንፈስ?
ክፍል-፮
ሀ. “ከእናንተ አንዳንዶቹ ትንሣኤ ሙታን የለም እንዴት ይላሉ?” (ቊጥር 12)
ጳውሎስ ይህን መልእክት የጻፈው ከአቴና ትንሽ ኪሎ ሜትር ወረድ ብላ በምትገኘው ቆሮንቶስ ነው:: በዚያ የሞቱ ሰዎች ዳግም ሕይወት ያገኛሉ የሚለው ትምህርት ተረት ነበር (ሐዋርያት ሥራ 17÷32)፡፡ አንድ ግሪካዊ ወደ ፊት ሕይወት በመንፈሳዊው ዓለም ውስጥ ይቀጥላል የሚለው ትምህርት የሚቀበለው እንጂ የሚሰናከልበት ጒዳይ አይደለም፤ ግሪካውያንን የሚያሰናክላቸው የአካል ትንሣኤ ወይም በዚሁ አካል ዳግም ሕይወት ያገኛል የሚለው ትምህርት ነው።
ለ. “የምትዘራው የሚሆነውን አካል አይደለም” (ቊጥር 37)
የዘር ፍሬ ከሚበቅለው ፍሬ እንደሚለይ የትንሣኤም አካል ከሚሞተው አካል የተለየ ነው:: ነገር ግን በተዘራው ማለትም በሞተው ዘርና በበቀለው ዘር መካከል በክፍለ ህዋስ ወይም በመሠረታዊ ተፈጥሮአቸውም ሆነ በታሪካቸው ልዩነት እንደሌላቸው ሁሉ የትንሣኤ አካል ከሞተው አካል ያለው አንድነት እንደዚሁ ነው::
ሐ. “የሙታን ትንሣኤ ደግሞ እንዲሁ ነው፡፡ በመበስበስ ይዘራል፣ ባለመበስበስ ይነሣል፤ በውርደት ይዘራል፣ በክብር ይነሣል፤ በድካም ይዘራል፤ በኀይል ይነሣል፤ ፍጥረታዊ አካል ይዘራል፣ መንፈሳዊ አካል ይነሣል፡፡ ፍጥረታዊ አካል ካለ መንፈሳዊ አካል ደግሞ አለ” (ቊጥር 42-44)
በክፍሉ አራት ጥንድ ነገሮች አብረው ተነጻጽረዋል፡፡ በመበስበስ፣ ባለመበስበስ፤ በውርደት፣ በክብር፤ በድካም፣ በኀይል፤ ፍጥረታዊ፣ መንፈሳዊ፡፡ በመጀመሪያዎቹ ሦስት ጥንዶች ስለሚሞተው አካል የተሰጡት አሉታዊ ገለጻዎች ናቸው። መበስበስ፣ ውርደት፣ ድካም ከመጀመሪያው አካል የተገኙ አሉታዊ ውርሶች ናቸው:: በመጀመሪያዎቹ ሦስት ጥንዶች ውስጥ ስለ ትንሣኤ አካል የቀረቡት ገለጻዎች የሚጠቁሙት አሉታዊ የሆኑት የውድቀት ውጤቶች እንደሚለወጡ ነው:: በክፍሉ ላይ የቀረቡት የጳውሎስ ማስረጃዎች የሐሳብ ፍሰታቸው ወጥነት ያለው ነው:: አራተኛው ጥንድ እንደ ላይኞቹ ሦስቱ አብረው በንጽጽር የቀረበ ነው:: ይኸውም ለውድቀት መንሥኤ ስለሆነው አካልና ከውድቀት ለመነሣት ምክንያት ስለሆነው አካል ነው፡፡
“ፍጥረታዊ አካል” የተባለው የኀጢአት አሉታዊ ውጤት የሆነው ነው፡፡ በኦሪት ዘፍጥረት መጽሐፍ ላይ እግዚአብሔር አምላክ አዳምን ከምድር ዐፈር እንዳበጀው፣ ይህንንም አካል፣ “መልካም ነው” እንዳለ እንመለከታለን (ዘፍጥረት 1÷26-31)።
አንደኛ ቆሮንቶስ 2፥14-15 ስለ መንፈሳዊ ሰው ይናገራል:: “መንፈሳዊ ሰው” ማለት ግን ቊሳዊ አካል የሌለው መንፈስ ብቻ የሆነ ማለት አይደለም፡፡ ነገር ግን በመንፈስ ቅዱስ ቊጥጥር ሥር ያለ ማለት ነው:: በአጠቃላይ “ፍጥረታዊ አካል” በእግዚአብሔር ቢፈጠርም፣ እግዚአብሔር በመጀመሪያ “መልካም ነው” ቢለውም እንኳ፣ በኀጢአት አማካይነት ግን ይህ አካል ተበላሽቶአል፡፡
ይቀጥላል...
ምንጭ፦ ዶ/ር ተስፋዬ ሮበሌ፤ በሥጋ ትንሣኤ አምናለሁ! የአስተምህሮተ ትንሣኤ መጽሐፍ ቅዱሳዊ፣ ታሪካዊና ሥነ አመክንዮአዊ ትንታኔ፤ ከምእራፍ ሰባት የተወሰደ
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የኢየሱስ ክርስቶስ ትንሣኤ የአካል ወይስ የመንፈስ?
ክፍል-፮
ሀ. “ከእናንተ አንዳንዶቹ ትንሣኤ ሙታን የለም እንዴት ይላሉ?” (ቊጥር 12)
ጳውሎስ ይህን መልእክት የጻፈው ከአቴና ትንሽ ኪሎ ሜትር ወረድ ብላ በምትገኘው ቆሮንቶስ ነው:: በዚያ የሞቱ ሰዎች ዳግም ሕይወት ያገኛሉ የሚለው ትምህርት ተረት ነበር (ሐዋርያት ሥራ 17÷32)፡፡ አንድ ግሪካዊ ወደ ፊት ሕይወት በመንፈሳዊው ዓለም ውስጥ ይቀጥላል የሚለው ትምህርት የሚቀበለው እንጂ የሚሰናከልበት ጒዳይ አይደለም፤ ግሪካውያንን የሚያሰናክላቸው የአካል ትንሣኤ ወይም በዚሁ አካል ዳግም ሕይወት ያገኛል የሚለው ትምህርት ነው።
ለ. “የምትዘራው የሚሆነውን አካል አይደለም” (ቊጥር 37)
የዘር ፍሬ ከሚበቅለው ፍሬ እንደሚለይ የትንሣኤም አካል ከሚሞተው አካል የተለየ ነው:: ነገር ግን በተዘራው ማለትም በሞተው ዘርና በበቀለው ዘር መካከል በክፍለ ህዋስ ወይም በመሠረታዊ ተፈጥሮአቸውም ሆነ በታሪካቸው ልዩነት እንደሌላቸው ሁሉ የትንሣኤ አካል ከሞተው አካል ያለው አንድነት እንደዚሁ ነው::
ሐ. “የሙታን ትንሣኤ ደግሞ እንዲሁ ነው፡፡ በመበስበስ ይዘራል፣ ባለመበስበስ ይነሣል፤ በውርደት ይዘራል፣ በክብር ይነሣል፤ በድካም ይዘራል፤ በኀይል ይነሣል፤ ፍጥረታዊ አካል ይዘራል፣ መንፈሳዊ አካል ይነሣል፡፡ ፍጥረታዊ አካል ካለ መንፈሳዊ አካል ደግሞ አለ” (ቊጥር 42-44)
በክፍሉ አራት ጥንድ ነገሮች አብረው ተነጻጽረዋል፡፡ በመበስበስ፣ ባለመበስበስ፤ በውርደት፣ በክብር፤ በድካም፣ በኀይል፤ ፍጥረታዊ፣ መንፈሳዊ፡፡ በመጀመሪያዎቹ ሦስት ጥንዶች ስለሚሞተው አካል የተሰጡት አሉታዊ ገለጻዎች ናቸው። መበስበስ፣ ውርደት፣ ድካም ከመጀመሪያው አካል የተገኙ አሉታዊ ውርሶች ናቸው:: በመጀመሪያዎቹ ሦስት ጥንዶች ውስጥ ስለ ትንሣኤ አካል የቀረቡት ገለጻዎች የሚጠቁሙት አሉታዊ የሆኑት የውድቀት ውጤቶች እንደሚለወጡ ነው:: በክፍሉ ላይ የቀረቡት የጳውሎስ ማስረጃዎች የሐሳብ ፍሰታቸው ወጥነት ያለው ነው:: አራተኛው ጥንድ እንደ ላይኞቹ ሦስቱ አብረው በንጽጽር የቀረበ ነው:: ይኸውም ለውድቀት መንሥኤ ስለሆነው አካልና ከውድቀት ለመነሣት ምክንያት ስለሆነው አካል ነው፡፡
“ፍጥረታዊ አካል” የተባለው የኀጢአት አሉታዊ ውጤት የሆነው ነው፡፡ በኦሪት ዘፍጥረት መጽሐፍ ላይ እግዚአብሔር አምላክ አዳምን ከምድር ዐፈር እንዳበጀው፣ ይህንንም አካል፣ “መልካም ነው” እንዳለ እንመለከታለን (ዘፍጥረት 1÷26-31)።
አንደኛ ቆሮንቶስ 2፥14-15 ስለ መንፈሳዊ ሰው ይናገራል:: “መንፈሳዊ ሰው” ማለት ግን ቊሳዊ አካል የሌለው መንፈስ ብቻ የሆነ ማለት አይደለም፡፡ ነገር ግን በመንፈስ ቅዱስ ቊጥጥር ሥር ያለ ማለት ነው:: በአጠቃላይ “ፍጥረታዊ አካል” በእግዚአብሔር ቢፈጠርም፣ እግዚአብሔር በመጀመሪያ “መልካም ነው” ቢለውም እንኳ፣ በኀጢአት አማካይነት ግን ይህ አካል ተበላሽቶአል፡፡
ይቀጥላል...
ምንጭ፦ ዶ/ር ተስፋዬ ሮበሌ፤ በሥጋ ትንሣኤ አምናለሁ! የአስተምህሮተ ትንሣኤ መጽሐፍ ቅዱሳዊ፣ ታሪካዊና ሥነ አመክንዮአዊ ትንታኔ፤ ከምእራፍ ሰባት የተወሰደ
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍8❤3
. ──•◈•─────•◈•─
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“ሕዝቤ ሰንፈዋልና አላወቁኝም ሰነፎች ልጆች ናቸው፥ ማስተዋልም የላቸውም፤ ክፉ ነገርን ለማድረግ ብልሃተኞች ናቸው፥ በጎ ነገርን ማድረግ ግን አያውቁም።”
ኤርምያስ 4፥22
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“ሕዝቤ ሰንፈዋልና አላወቁኝም ሰነፎች ልጆች ናቸው፥ ማስተዋልም የላቸውም፤ ክፉ ነገርን ለማድረግ ብልሃተኞች ናቸው፥ በጎ ነገርን ማድረግ ግን አያውቁም።”
ኤርምያስ 4፥22
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤4😢3👍1
#የእግዚአብሔር_ቃል_ምን_ይላል?
መዝሙር 25
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ አቤቱ፥ ወደ አንተ ነፍሴን አነሣለሁ።
² አምላኬ፥ አንተን ታመንሁ፤ አልፈር፥ ጠላቶቼ በእኔ አይሣቁብኝ።
³ አንተን ተስፋ የሚያደርጉ አያፍሩም፤ በከንቱ የሚገበዙ ያፍራሉ።
⁴ አቤቱ፥ መንገድህን አመልክተኝ፥ ፍለጋህንም አስተምረኝ።
⁵ አንተ የመድኃኒቴ አምላክ ነህና በእውነትህ ምራኝ፥ አስተምረኝም፤ ቀኑን ሁሉ አንተን ተስፋ አድርጌአለሁ።
⁶ አቤቱ፥ ምሕረትህንና ቸርነትህን አስብ፥ ከጥንት ጀምሮ ናቸውና።
⁷ የልጅነቴን ኃጢአትና መተላለፍ አታስብብኝ፤ አቤቱ፥ ስለ ቸርነትህ ብዛት እንደ ምሕረትህ አስበኝ።
⁸ እግዚአብሔር ቸር ቅንም ነው፤ ስለዚህ ኃጢአተኞችን በመንገድ ይመራቸዋል።
⁹ ገሮችን በፍርድ ይመራል፥ ለገሮችም መንገድን ያስተምራቸዋል።
¹⁰ የእግዚአብሔር መንገድ ሁሉ ቸርነትና እውነት ነው። ቃል ኪዳኑንና ምስክሩን ለሚጠብቁ።
¹¹ አቤቱ፥ ኃጢአቴ እጅግ ነውና ስለ ስምህ ይቅር በለኝ።
¹² እግዚአብሔርን የሚፈራ ሰው ማን ነው? በሚመርጠው መንገድ ያስተምረዋል።
¹³ ነፍሱ በመልካም ታድራለች፥ ዘሩም ምድርን ይወርሳል።
¹⁴ እግዚአብሔር ለሚፈሩት ኃይላቸው ነው፥ ቃል ኪዳኑንም ያስታውቃቸዋል።
¹⁵ እርሱ እግሮቼን ከወጥመድ ያወጣቸዋልና ዓይኖቼ ሁልጊዜ ወደ እግዚአብሔር ናቸው።
¹⁶ እኔ ብቻዬንና ችግረኛ ነኝና ፊትህን ወደ እኔ አድርግ ማረኝም።
¹⁷ የልቤ ችግር ብዙ ነው፤ ከጭንቀቴ አውጣኝ።
¹⁸ ድካሜንና መከራዬን እይ፥ ኃጢአቴንም ሁሉ ይቅር በለኝ።
¹⁹ ጠላቶቼ እንደ በዙ እይ፥ የግፍም ጥል ጠልተውኛል።
²⁰ ነፍሴን ጠብቅና አድነኝ፤ አንተን ታምኛለሁና አልፈር።
²¹ አንተን ተስፋ አድርጌአለሁና የውሃትና ቅንነት ይጠብቁኝ።
²² አቤቱ፥ እስራኤልን ከመከራው ሁሉ አድነው።
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
መዝሙር 25
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ አቤቱ፥ ወደ አንተ ነፍሴን አነሣለሁ።
² አምላኬ፥ አንተን ታመንሁ፤ አልፈር፥ ጠላቶቼ በእኔ አይሣቁብኝ።
³ አንተን ተስፋ የሚያደርጉ አያፍሩም፤ በከንቱ የሚገበዙ ያፍራሉ።
⁴ አቤቱ፥ መንገድህን አመልክተኝ፥ ፍለጋህንም አስተምረኝ።
⁵ አንተ የመድኃኒቴ አምላክ ነህና በእውነትህ ምራኝ፥ አስተምረኝም፤ ቀኑን ሁሉ አንተን ተስፋ አድርጌአለሁ።
⁶ አቤቱ፥ ምሕረትህንና ቸርነትህን አስብ፥ ከጥንት ጀምሮ ናቸውና።
⁷ የልጅነቴን ኃጢአትና መተላለፍ አታስብብኝ፤ አቤቱ፥ ስለ ቸርነትህ ብዛት እንደ ምሕረትህ አስበኝ።
⁸ እግዚአብሔር ቸር ቅንም ነው፤ ስለዚህ ኃጢአተኞችን በመንገድ ይመራቸዋል።
⁹ ገሮችን በፍርድ ይመራል፥ ለገሮችም መንገድን ያስተምራቸዋል።
¹⁰ የእግዚአብሔር መንገድ ሁሉ ቸርነትና እውነት ነው። ቃል ኪዳኑንና ምስክሩን ለሚጠብቁ።
¹¹ አቤቱ፥ ኃጢአቴ እጅግ ነውና ስለ ስምህ ይቅር በለኝ።
¹² እግዚአብሔርን የሚፈራ ሰው ማን ነው? በሚመርጠው መንገድ ያስተምረዋል።
¹³ ነፍሱ በመልካም ታድራለች፥ ዘሩም ምድርን ይወርሳል።
¹⁴ እግዚአብሔር ለሚፈሩት ኃይላቸው ነው፥ ቃል ኪዳኑንም ያስታውቃቸዋል።
¹⁵ እርሱ እግሮቼን ከወጥመድ ያወጣቸዋልና ዓይኖቼ ሁልጊዜ ወደ እግዚአብሔር ናቸው።
¹⁶ እኔ ብቻዬንና ችግረኛ ነኝና ፊትህን ወደ እኔ አድርግ ማረኝም።
¹⁷ የልቤ ችግር ብዙ ነው፤ ከጭንቀቴ አውጣኝ።
¹⁸ ድካሜንና መከራዬን እይ፥ ኃጢአቴንም ሁሉ ይቅር በለኝ።
¹⁹ ጠላቶቼ እንደ በዙ እይ፥ የግፍም ጥል ጠልተውኛል።
²⁰ ነፍሴን ጠብቅና አድነኝ፤ አንተን ታምኛለሁና አልፈር።
²¹ አንተን ተስፋ አድርጌአለሁና የውሃትና ቅንነት ይጠብቁኝ።
²² አቤቱ፥ እስራኤልን ከመከራው ሁሉ አድነው።
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍5❤4
. ──•◈•─────•◈•─
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“ሰው ሆይ፥ መልካሙን ነግሮሃል፤ እግዚአብሔርም ከአንተ ዘንድ የሚሻው ምንድር ነው? ፍርድን ታደርግ ዘንድ፥ ምሕረትንም ትወድድ ዘንድ፥ ከአምላክህም ጋር በትሕትና ትሄድ ዘንድ አይደለምን?”
ሚክያስ 6፥8
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“ሰው ሆይ፥ መልካሙን ነግሮሃል፤ እግዚአብሔርም ከአንተ ዘንድ የሚሻው ምንድር ነው? ፍርድን ታደርግ ዘንድ፥ ምሕረትንም ትወድድ ዘንድ፥ ከአምላክህም ጋር በትሕትና ትሄድ ዘንድ አይደለምን?”
ሚክያስ 6፥8
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤7
#እራሳችንን_እንመርምር
መንፈሣችንን መቆጣጠር ላይ እንዴት ነን? መንፈሣችን ቅጥር ከሌለው የክርስትና ሕይወታችን ተጠብቆ ለጌታ ቀን የምንበቃውስ በየትኛው መንገድ ነው?
“ቅጥር እንደሌላት እንደ ፈረሰች ከተማ፥ መንፈሱን የማይከለክል ሰው እንዲሁ ነው።”
ምሳሌ 25፥28
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
መንፈሣችንን መቆጣጠር ላይ እንዴት ነን? መንፈሣችን ቅጥር ከሌለው የክርስትና ሕይወታችን ተጠብቆ ለጌታ ቀን የምንበቃውስ በየትኛው መንገድ ነው?
“ቅጥር እንደሌላት እንደ ፈረሰች ከተማ፥ መንፈሱን የማይከለክል ሰው እንዲሁ ነው።”
ምሳሌ 25፥28
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍1🙏1
. ──•◈•─────•◈•─
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“እግዚአብሔር የላከው የእግዚአብሔርን ቃል ይናገራልና፤ እግዚአብሔር መንፈሱን ሰፍሮ አይሰጥምና።”
ዮሐንስ 3፥34
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“እግዚአብሔር የላከው የእግዚአብሔርን ቃል ይናገራልና፤ እግዚአብሔር መንፈሱን ሰፍሮ አይሰጥምና።”
ዮሐንስ 3፥34
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍2
#መጻሕፍትን_በድምጽ
📔ርዕስ፦ የመጽሐፍ ቅዱስ አስተምህሮ
👤ጸሐፊ፦ ዶ/ር ቻርልስ ሲ.ራይሪ
🗣ተርጓሚ፦ ሲሳይ ደሳለኝ
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📔ርዕስ፦ የመጽሐፍ ቅዱስ አስተምህሮ
👤ጸሐፊ፦ ዶ/ር ቻርልስ ሲ.ራይሪ
🗣ተርጓሚ፦ ሲሳይ ደሳለኝ
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍4
ቅዱሳት መጻሕፍት
#እምነት ክፍል-8 በቅዱሳት መጻሕፍት መሠረት እምነታችንን ለመጠበቅ ምን እናድረግ? 1. ጸሎት እና በእግዚአብሔር ላይ መደገፍ “እኔ ግን እምነትህ እንዳይጠፋ ስለ አንተ ጸለይሁ፤ አንተም በተመለስህ ጊዜ ወንድሞችህን አበርታ።”” ሉቃስ 22፥32 (አዲሱ መ.ት) ኢየሱስ እምነታችንን ለመጠበቅ ጸሎት አስፈላጊ እንደሆነ ያስተምራል። በጸሎት የእግዚአብሔርን…
#እምነት
ክፍል-9
እምነት እና ሥራ
በመጽሐፍ ቅዱስ መሠረት ሰው የሚድነው ወይም የሚጸድቀው በእምነት እንጂ በሥራ እንዳልሆነ እርግጥ ነው፤ ይህ በእምነት የመጽደቅ ጉዳይም በሰው ዘንድ ሳይሆን በእግዚአብሔር ዘንድ የሚታየው ነው፡፡
በሮሜ 4፥1‐8 የምናገኘው የእግዚአብሔር ቃል ይህን የሚያረጋግጥ ነው፤ በቊ.1 ላይ «በሥጋ አባታችን የሆነ አብርሃም ምን አገኘ እንላለን? አብርሃም በሥራ ጸድቆ ቢሆን የሚመካበት አለውና፤ ነገር ግን በእግዚአብሔር ዘንድ አይደለም» ይላል፤ «በእግዚአብሔር ዘንድ አይደለም» የሚለው ይህ ቃል በእግዚአብሔር ዘንድ በሥራ መጽደቅ እንደሌለ የሚገልጽ ነው፡፡
በዚህ ክፍል ሰው ያለ ሥራ በእምነት እንደሚጸድቅ ለማሳየት ሁለት ሰዎች በምሳሌነት ተጠቅሰዋል፤ እነርሱም አብርሃምና ዳዊት ናቸው፡፡ እነዚህ ሁለት ሰዎች በአንድነት መጠቀሳቸው በመጽሐፍ ቅዱስ የተለመደ ሲሆን (ማቴ.1፥1፤ የሐ.ሥ.13፥26‐36) ይህንንም ታላቅ ርእሰ ጉዳይ ለማብራራት አብረው መጠቀሳቸው ወሳኝ ነው፡፡ አብርሃም የነበረው ሕግ ከመሰጠቱ በፊት ሲሆን ዳዊት ደግሞ በሕጉ ዘመን የነበረ ሰው ነው፤ ከሁለቱም ሰዎች አንጻር ሲታይ ግን በእግዚአብሔር ዘንድ ጽድቅ የሚቈጠረው በሥራ ሳይሆን በእምነት እንደሆነ ተብራርቷል፡፡
በቊ.3 ላይ አብርሃምን በተመለከተ ሲገልጽ «መጽሐፍስ ምን አለ? አብርሃም እግዚአብሔርን አመነ ጽድቅም ሆኖ ተቈጠረለት፤ ለሚሠራ ደመወዝ እንደ ዕዳ ነው እንጂ እንደ ጸጋ አይቈጠርለትም፤ ነገር ግን ለማይሠራ ኃጢአተኛውን በሚያጸድቅ ለሚያምን ሰው እምነቱ ጽድቅ ሆኖ ይቈጠርለታል» ይላል፡፡ በዚህም ቃል ውስጥ አብርሃም ጽድቅን ያገኘው እግዚአብሔርን ስላመነ ተቈጥሮለት እንጂ ጽድቅ ሠርቶ እንዳልሆነ እንገነዘባለን፡፡ ይህም ለሚያምን ሰው ሁሉ እግዚአብሔር የሚያደርገው መሆኑ ተገልጿል፡፡ በመቀጠል ደግሞ ዳዊት ይህን ጉዳይ በተመለከተ የተናገረው ተጠቅሷል፡፡ ይኸውም «እንደዚህም ደግሞ እግዚአብሔር ያለ ሥራ ጽድቅን ስለሚቈጥርለት ሰው ብፅዕና ይናገራል እንዲህ ሲል፤ ‘ዓመፃቸው የተሰረየላቸው ኃጢአታቸውም የተከደነላቸው ብፁዓን ናቸው፤ ጌታ ኃጢአቱን የማይቈጥርበት ሰው ብፁዕ ነው»(ቊ.6‐8)፤ በአብርሃም ሕይወት እንዳየነው እግዚአብሔር ሊቈጠርልን የማይገባውን ጽድቅ በእምነት ሲቈጥርልን እናያለን፤ በዚህ ዳዊት በተናገረው ቃል ውስጥ ደግሞ እግዚአብሔር ሊቈጥርብን የሚገባውን ኃጢአት ባለመቊጠር ጸጋውን ሲያሳይ እንመለከታለን፡፡ ይህም «እግዚአብሔር ያለ ሥራ ጽድቅን ስለሚቈጥርለት ሰው ብፅዕና» የተነገረ መሆኑ ተገልጿል፡፡ ስለዚህ በሮሜ 4 ውስጥ የተሰጠው ትምህርት ሰው በእግዚአብሔር ዘንድ የሚጸድቀው ያለ ሥራ በእምነት መሆኑን የሚያሳይ ነው፤ ይህ እምነት በሥራ ሊገለጥ የሚችል እውነተኛ መሆኑን እግዚአብሔር ማወቅ ይችላልና፡፡
በያዕ.2 ውስጥ የምናገኘው ትምህርት ግን ጽድቅ ወይም መዳን በሰው ዘንድ የሚታየው ወይም የሚረጋገጠው በእምነት ብቻ ሳይሆን በሥራም እንደሆነ የሚገልጽ ነው፡፡ በሰው ዘንድ የአንድ ሰው እምነት እውነተኛ እምነት መሆኑ ሊታይ የሚችለው በሥራ ነው፤ በቊ.14 ላይ «ወንድሞች ሆይ እምነት አለኝ የሚል ሥራ ግን የሌለው ሰው ቢኖር ምን ይጠቅመዋል፤ እምነቱስ ሊያድነው ይችላልን?» በማለት ያዕቆብ ጥያቄ ያነሳል፤ እዚህ ላይ «እምነት አለኝ» የሚለው ያ ሰው ራሱ ነው፡፡
ይቀጥላል...
ምንጭ፦ 1bible.page
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ክፍል-9
እምነት እና ሥራ
በመጽሐፍ ቅዱስ መሠረት ሰው የሚድነው ወይም የሚጸድቀው በእምነት እንጂ በሥራ እንዳልሆነ እርግጥ ነው፤ ይህ በእምነት የመጽደቅ ጉዳይም በሰው ዘንድ ሳይሆን በእግዚአብሔር ዘንድ የሚታየው ነው፡፡
በሮሜ 4፥1‐8 የምናገኘው የእግዚአብሔር ቃል ይህን የሚያረጋግጥ ነው፤ በቊ.1 ላይ «በሥጋ አባታችን የሆነ አብርሃም ምን አገኘ እንላለን? አብርሃም በሥራ ጸድቆ ቢሆን የሚመካበት አለውና፤ ነገር ግን በእግዚአብሔር ዘንድ አይደለም» ይላል፤ «በእግዚአብሔር ዘንድ አይደለም» የሚለው ይህ ቃል በእግዚአብሔር ዘንድ በሥራ መጽደቅ እንደሌለ የሚገልጽ ነው፡፡
በዚህ ክፍል ሰው ያለ ሥራ በእምነት እንደሚጸድቅ ለማሳየት ሁለት ሰዎች በምሳሌነት ተጠቅሰዋል፤ እነርሱም አብርሃምና ዳዊት ናቸው፡፡ እነዚህ ሁለት ሰዎች በአንድነት መጠቀሳቸው በመጽሐፍ ቅዱስ የተለመደ ሲሆን (ማቴ.1፥1፤ የሐ.ሥ.13፥26‐36) ይህንንም ታላቅ ርእሰ ጉዳይ ለማብራራት አብረው መጠቀሳቸው ወሳኝ ነው፡፡ አብርሃም የነበረው ሕግ ከመሰጠቱ በፊት ሲሆን ዳዊት ደግሞ በሕጉ ዘመን የነበረ ሰው ነው፤ ከሁለቱም ሰዎች አንጻር ሲታይ ግን በእግዚአብሔር ዘንድ ጽድቅ የሚቈጠረው በሥራ ሳይሆን በእምነት እንደሆነ ተብራርቷል፡፡
በቊ.3 ላይ አብርሃምን በተመለከተ ሲገልጽ «መጽሐፍስ ምን አለ? አብርሃም እግዚአብሔርን አመነ ጽድቅም ሆኖ ተቈጠረለት፤ ለሚሠራ ደመወዝ እንደ ዕዳ ነው እንጂ እንደ ጸጋ አይቈጠርለትም፤ ነገር ግን ለማይሠራ ኃጢአተኛውን በሚያጸድቅ ለሚያምን ሰው እምነቱ ጽድቅ ሆኖ ይቈጠርለታል» ይላል፡፡ በዚህም ቃል ውስጥ አብርሃም ጽድቅን ያገኘው እግዚአብሔርን ስላመነ ተቈጥሮለት እንጂ ጽድቅ ሠርቶ እንዳልሆነ እንገነዘባለን፡፡ ይህም ለሚያምን ሰው ሁሉ እግዚአብሔር የሚያደርገው መሆኑ ተገልጿል፡፡ በመቀጠል ደግሞ ዳዊት ይህን ጉዳይ በተመለከተ የተናገረው ተጠቅሷል፡፡ ይኸውም «እንደዚህም ደግሞ እግዚአብሔር ያለ ሥራ ጽድቅን ስለሚቈጥርለት ሰው ብፅዕና ይናገራል እንዲህ ሲል፤ ‘ዓመፃቸው የተሰረየላቸው ኃጢአታቸውም የተከደነላቸው ብፁዓን ናቸው፤ ጌታ ኃጢአቱን የማይቈጥርበት ሰው ብፁዕ ነው»(ቊ.6‐8)፤ በአብርሃም ሕይወት እንዳየነው እግዚአብሔር ሊቈጠርልን የማይገባውን ጽድቅ በእምነት ሲቈጥርልን እናያለን፤ በዚህ ዳዊት በተናገረው ቃል ውስጥ ደግሞ እግዚአብሔር ሊቈጥርብን የሚገባውን ኃጢአት ባለመቊጠር ጸጋውን ሲያሳይ እንመለከታለን፡፡ ይህም «እግዚአብሔር ያለ ሥራ ጽድቅን ስለሚቈጥርለት ሰው ብፅዕና» የተነገረ መሆኑ ተገልጿል፡፡ ስለዚህ በሮሜ 4 ውስጥ የተሰጠው ትምህርት ሰው በእግዚአብሔር ዘንድ የሚጸድቀው ያለ ሥራ በእምነት መሆኑን የሚያሳይ ነው፤ ይህ እምነት በሥራ ሊገለጥ የሚችል እውነተኛ መሆኑን እግዚአብሔር ማወቅ ይችላልና፡፡
በያዕ.2 ውስጥ የምናገኘው ትምህርት ግን ጽድቅ ወይም መዳን በሰው ዘንድ የሚታየው ወይም የሚረጋገጠው በእምነት ብቻ ሳይሆን በሥራም እንደሆነ የሚገልጽ ነው፡፡ በሰው ዘንድ የአንድ ሰው እምነት እውነተኛ እምነት መሆኑ ሊታይ የሚችለው በሥራ ነው፤ በቊ.14 ላይ «ወንድሞች ሆይ እምነት አለኝ የሚል ሥራ ግን የሌለው ሰው ቢኖር ምን ይጠቅመዋል፤ እምነቱስ ሊያድነው ይችላልን?» በማለት ያዕቆብ ጥያቄ ያነሳል፤ እዚህ ላይ «እምነት አለኝ» የሚለው ያ ሰው ራሱ ነው፡፡
ይቀጥላል...
ምንጭ፦ 1bible.page
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍9❤2🔥1😁1
. ──•◈•─────•◈•─
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“ተመልሶ ይምረናል፤ ክፋታችንንም ይጠቀጥቃል፥ ኃጢአታችንንም በባሕሩ ጥልቅ ይጥለዋል።”
ሚክያስ 7፥19
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“ተመልሶ ይምረናል፤ ክፋታችንንም ይጠቀጥቃል፥ ኃጢአታችንንም በባሕሩ ጥልቅ ይጥለዋል።”
ሚክያስ 7፥19
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤7🙏2
Audio
#መጻሕፍትን_በድምጽ
📔ርዕስ፦ የመጽሐፍ ቅዱስ አስተምህሮ
👤ጸሐፊ፦ ዶ/ር ቻርልስ ሲ.ራይሪ
🗣ተርጓሚ፦ ሲሳይ ደሳለኝ
👉መግቢያ
ይቀጥላል...
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📔ርዕስ፦ የመጽሐፍ ቅዱስ አስተምህሮ
👤ጸሐፊ፦ ዶ/ር ቻርልስ ሲ.ራይሪ
🗣ተርጓሚ፦ ሲሳይ ደሳለኝ
👉መግቢያ
ይቀጥላል...
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍8❤1
ክርስቲያናዊ ዓቅብተ እምነት – CHRISTIAN APOLOGETICS
ክፍል-1
መግቢያ
“ዳሩ ግን ጌታን እርሱም ክርስቶስ በልባችሁ ቀድሱት። በእናንተ ስላለ ተስፋ ምክንያትን ለሚጠይቁዋችሁ ሁሉ መልስ ለመስጠት ዘወትር የተዘጋጃችሁ ሁኑ፥ ነገር ግን በየዋህነትና በፍርሃት ይሁን።” 1ጴጥ. 3፥15
የክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ያለ ተግዳሮት የኖረችበት ዘመን የለም፡፡ በየዘመናቱ የነበሩት ተግዳሮቶች አንድ መልክ ባይኖራቸውም ነገር ግን አንድ ዓላማና ግብ ያላቸው ሆነው እናገኛቸዋለን፡፡ እርሱም ቤተ ክርስቲያንን ማዳክም ብሎም ማጥፋት ነው፡፡ ነገር ግን በተለያዩ ዘመናት የኖሩት ክርስቲያኖች መሠረታዊውን የክርስትና አስተምሕሮ ከውስጣዊና ውጫዊ ተግዳሮቶች ተከላክሎ በማቆየቱ ረገድ በመንፈስ ቅዱስ እርዳታ ከፍተኛውን ሚና ተጫውተዋል፡፡
የምንኖረው መንፈሳዊ ውጊያ ባለበት ዓለም ውስጥ ነው፡፡ ውጊያው ደግሞ የሚደረገው በሰዎች አዕምሮ ውስጥ ነው፡፡ ይህንን ውጊያ ለማሸነፍ የተዘጋጀንና የታጠቅን መሆን ያስፈልገናል፡፡ የዚህ ጽሑፍ ዓላማ ስለ ክርስቲያናዊ ዓቅብተ እምነት ታሪካዊ አመጣጥና መጽሐፍ ቅዱሳዊነት መሠረታዊ ግንዛቤን ማስጨበጥ ነው። መጽሐፍ ቅዱስ 1ቆሮ 10፥4-6 ላይ በተናገረው መሠረት በእግዚአብሔር ሐሳብ ላይ የሚነሳውን ከፍ ያለውን የሰውን ሐሳብ በማፍረስ አዕምሮን ሁሉ ለክርስቶስ እንዴት መማረክ እንደምንችል ክርስቲያናዊውን መንገድ ያመላክታል፡፡ አንባቢያንም ስለ ክርስቲያናዊ ዓቅብተ እምነት የበለጠ ጥናት እንዲያደርጉ እንደሚያነሳሳና አቅጣጫን እንደሚጠቁም ይታመናል።
1.የክርስቲያናዊ ዓቅብተ እምነት ትርጉምና ታሪክ
1.1. ትርጉም
“አፖሎጀቲክስ” የሚለው የእንግሊዘኛ ቃል አፖሎጊያ ከሚል የግሪክ ቃል የመጣ ሲሆን ትርጓሜውም “በመከላከል መናገር” እንደ ማለት ነው፡፡ በጥንታዊቷ ግሪክ የሕግ ስርኣት ውስጥ ሁለት ቁልፍ የሆኑ ቃላት ጥቅም ላይ ይውሉ ነበር፤ የከሳሽ ወገን ንግግር “ካታጎሪያ” በመባል የሚታወቅ ሲሆን የተከሳሽ ወገን ምላሽ ደግሞ “አፖሎጊያ” በመባል ይታወቃል፡፡ “አፖሎጊያ’ የሚለው ቃል በአዲስ ኪዳን ውስጥ በተደጋጋሚ ተጠቅሷል። በሐዋርያት ሥራ 26፥2 ላይ ሐዋርው ጳውሎስ ተከሶ በፊስጦስና አግሪጳ ፊት በቀረበ ጊዜ ተጠቅሞበታል፤ እንዲሁም በፊልጵስዩስ 1፥7፣ 1፥16 እና 1ጴጥሮስ 3፥15 ላይ እናገኘዋለን፡፡
ዓቅብተ እምነት ከነገረ መለኮት የጥናት ዘርፎች መካከል አንዱ ሲሆን መረጃዎችን በተቀናበረ ሁኔታ በመጠቀም ለሃይማኖታዊ አስተምህሮ ጥብቅና መቆም ነው፡፡ የአንድ ሃይማኖት አስተምህሮ ትክክል መሆኑንና እምነቱን መምረጥ ከሰው አመክንዮአዊ አስተሳሰብ ጋር የማይጣረስ መሆኑን ለማሳየት የሚደረግ ጥረትም ነው፡፡ ስለዚህ ዓቅብተ እምነት ሰዎች አስተሳሰባቸውን እንዲለውጡ የማሳመን ሥራ ነው፡፡ ክርስቲያናዊ ዓቅብተ እምነት ክርስቲያናዊ ሥነ መለኮት (Christian Theology)፣ ተፈጥሯዊ ሥነ መለኮት (Natural Theology) እና ፍልስፍናን በማጣመር ክርስቲያናዊውን አስተምህሮ ከውጪያዊ ጥቃቶችና የተሳሳቱ ትርጓሜዎች ለመከላከል ይጥራል፣ እንዲሁም የሌሎች ንፅረተ ዓለማት አስተምሕሮዎችን ይመረምራል፡፡
ይቀጥላል...
ምንጭ:- ewnetlehulu.org
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ክፍል-1
መግቢያ
“ዳሩ ግን ጌታን እርሱም ክርስቶስ በልባችሁ ቀድሱት። በእናንተ ስላለ ተስፋ ምክንያትን ለሚጠይቁዋችሁ ሁሉ መልስ ለመስጠት ዘወትር የተዘጋጃችሁ ሁኑ፥ ነገር ግን በየዋህነትና በፍርሃት ይሁን።” 1ጴጥ. 3፥15
የክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ያለ ተግዳሮት የኖረችበት ዘመን የለም፡፡ በየዘመናቱ የነበሩት ተግዳሮቶች አንድ መልክ ባይኖራቸውም ነገር ግን አንድ ዓላማና ግብ ያላቸው ሆነው እናገኛቸዋለን፡፡ እርሱም ቤተ ክርስቲያንን ማዳክም ብሎም ማጥፋት ነው፡፡ ነገር ግን በተለያዩ ዘመናት የኖሩት ክርስቲያኖች መሠረታዊውን የክርስትና አስተምሕሮ ከውስጣዊና ውጫዊ ተግዳሮቶች ተከላክሎ በማቆየቱ ረገድ በመንፈስ ቅዱስ እርዳታ ከፍተኛውን ሚና ተጫውተዋል፡፡
የምንኖረው መንፈሳዊ ውጊያ ባለበት ዓለም ውስጥ ነው፡፡ ውጊያው ደግሞ የሚደረገው በሰዎች አዕምሮ ውስጥ ነው፡፡ ይህንን ውጊያ ለማሸነፍ የተዘጋጀንና የታጠቅን መሆን ያስፈልገናል፡፡ የዚህ ጽሑፍ ዓላማ ስለ ክርስቲያናዊ ዓቅብተ እምነት ታሪካዊ አመጣጥና መጽሐፍ ቅዱሳዊነት መሠረታዊ ግንዛቤን ማስጨበጥ ነው። መጽሐፍ ቅዱስ 1ቆሮ 10፥4-6 ላይ በተናገረው መሠረት በእግዚአብሔር ሐሳብ ላይ የሚነሳውን ከፍ ያለውን የሰውን ሐሳብ በማፍረስ አዕምሮን ሁሉ ለክርስቶስ እንዴት መማረክ እንደምንችል ክርስቲያናዊውን መንገድ ያመላክታል፡፡ አንባቢያንም ስለ ክርስቲያናዊ ዓቅብተ እምነት የበለጠ ጥናት እንዲያደርጉ እንደሚያነሳሳና አቅጣጫን እንደሚጠቁም ይታመናል።
1.የክርስቲያናዊ ዓቅብተ እምነት ትርጉምና ታሪክ
1.1. ትርጉም
“አፖሎጀቲክስ” የሚለው የእንግሊዘኛ ቃል አፖሎጊያ ከሚል የግሪክ ቃል የመጣ ሲሆን ትርጓሜውም “በመከላከል መናገር” እንደ ማለት ነው፡፡ በጥንታዊቷ ግሪክ የሕግ ስርኣት ውስጥ ሁለት ቁልፍ የሆኑ ቃላት ጥቅም ላይ ይውሉ ነበር፤ የከሳሽ ወገን ንግግር “ካታጎሪያ” በመባል የሚታወቅ ሲሆን የተከሳሽ ወገን ምላሽ ደግሞ “አፖሎጊያ” በመባል ይታወቃል፡፡ “አፖሎጊያ’ የሚለው ቃል በአዲስ ኪዳን ውስጥ በተደጋጋሚ ተጠቅሷል። በሐዋርያት ሥራ 26፥2 ላይ ሐዋርው ጳውሎስ ተከሶ በፊስጦስና አግሪጳ ፊት በቀረበ ጊዜ ተጠቅሞበታል፤ እንዲሁም በፊልጵስዩስ 1፥7፣ 1፥16 እና 1ጴጥሮስ 3፥15 ላይ እናገኘዋለን፡፡
ዓቅብተ እምነት ከነገረ መለኮት የጥናት ዘርፎች መካከል አንዱ ሲሆን መረጃዎችን በተቀናበረ ሁኔታ በመጠቀም ለሃይማኖታዊ አስተምህሮ ጥብቅና መቆም ነው፡፡ የአንድ ሃይማኖት አስተምህሮ ትክክል መሆኑንና እምነቱን መምረጥ ከሰው አመክንዮአዊ አስተሳሰብ ጋር የማይጣረስ መሆኑን ለማሳየት የሚደረግ ጥረትም ነው፡፡ ስለዚህ ዓቅብተ እምነት ሰዎች አስተሳሰባቸውን እንዲለውጡ የማሳመን ሥራ ነው፡፡ ክርስቲያናዊ ዓቅብተ እምነት ክርስቲያናዊ ሥነ መለኮት (Christian Theology)፣ ተፈጥሯዊ ሥነ መለኮት (Natural Theology) እና ፍልስፍናን በማጣመር ክርስቲያናዊውን አስተምህሮ ከውጪያዊ ጥቃቶችና የተሳሳቱ ትርጓሜዎች ለመከላከል ይጥራል፣ እንዲሁም የሌሎች ንፅረተ ዓለማት አስተምሕሮዎችን ይመረምራል፡፡
ይቀጥላል...
ምንጭ:- ewnetlehulu.org
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍5
. ──•◈•─────•◈•─
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“ምድርም በእግዚአብሔር ፊት ተበላሸች፤ ምድርም ግፍን ተሞላች።”
ዘፍጥረት 6፥11
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“ምድርም በእግዚአብሔር ፊት ተበላሸች፤ ምድርም ግፍን ተሞላች።”
ዘፍጥረት 6፥11
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍5😢1
Audio
#መጻሕፍትን_በድምጽ
📔ርዕስ፦ የመጽሐፍ ቅዱስ አስተምህሮ
👤ጸሐፊ፦ ዶ/ር ቻርልስ ሲ.ራይሪ
🗣ተርጓሚ፦ ሲሳይ ደሳለኝ
👉ክፍል-1
ይቀጥላል...
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📔ርዕስ፦ የመጽሐፍ ቅዱስ አስተምህሮ
👤ጸሐፊ፦ ዶ/ር ቻርልስ ሲ.ራይሪ
🗣ተርጓሚ፦ ሲሳይ ደሳለኝ
👉ክፍል-1
ይቀጥላል...
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍5
ንስር
ንስር የአእዋፍ ንጉስ በመባል የሚታወቅ የወፍ ዘር ነው ታላላቅ ነገስታት ንስርን ለተለያዩ ነገሮች መግለጫነት እንደ ምሳሌ ተጠቅመዋል ለነጻነት ለሥልጣን ለግርማና ለመሳሰሉት በዚህ ጹሑፍ ግን የምናተኩረው አስገራሚ የሆነ መመሳሰል በንስር ባሕሪና በክርስቲያን ሕይወት ውስጥ መኖሩን ነው በዚህች አጭር ጹሑፍ ውስጥ አምስት ነጥቦችን ብቻ እንመልከታለን፡፡
1. ንስር ስፍራውን አይለቅም
የተለያ አዕዋፍና አራዊት ከአየር ንብረት ለውጥ ጋር በተዛመደ መልኩ ጎጆዋቸውንና ስፍራቸውን በመተው ወደሌላ ቦታ ይሰደዳሉ ይህም ፍልሰት በመባል ይታወቃል ኀይለኛ ፍልሰት በመባል ይታወቃል ኃይለኛ የክረምት ወቅት ሲመጣ ብዙዎቹ ወደ ሌላ አካባቢ እስከ እረጅም እርቀት ድረስ በመጓዝ ሀገር ሁሉ አቋርጠው ይሰደዳሉ ንስር ግን እንደዚህ አይደለም ክረምት አልፎ በጋም እንደሚመጣ ያውቃል በመሆኑም በብዙ ድካምና ጥረት የሠራውን ጎጆውን ጥሎ አይሸሽም እንደምንም ብሎ በጎጆው ውስጥ በመሆን ያን የክረምትን ወራት ያሳልፋል ንስር የክረምት ወራት ያሳልፋል ንስር ክርስቲያኖችም እንደዚህ ናቸው ወጀብ አውሎ ንፋስ ስለበዛባቸው ብቻ እግዚአብሔርን ካስቀመጣቸው ቦታና ከሰጣቸው ስፍራ ተነስተው አይሄዱም ጌታ ወጀቡን ጸጥ በማድረግ እንደሚያሻግራቸው ያውቃሉ በሆኑም በስፍራቸው ጸንተው ይቆያሉ(ናሆም 1፡3)
2. የንስር ጠላት
ንሰር አንድ ጠላት ብቻ አለው ያም እባብ ነው ንስር ቤቱን የሚሰራው ከፍ ባለ አለት ላይ ስለሆነ ከእባብ ሌላ ምንም ሊደርስበት አይችልም እባብ ግን ተስታኮ ወደ ጎጆው ሊያመራና የንስርን እንቁላሎች ወይም ጫጩቶችን ሊጎዳ ይችላል ከዚህም የተነሳ ሴቷ ንስር እንቁላሎች ወይም ጫቹቶችን ሊጎዳ ይችላል ከዚህም የተነሳ ሴቷ ንስር እንቁላሎችዋንም ሆነ ጫጩቶቿን በትጋት ነው የምትጠብቀው እባቡ ወደ ጎጆዋ ሲመጣ በከፍተኛ ፍጥነት በአፏ እና በጥፍሮቿ ትይዘውና ወደላይ ትበራለች ከዚያም አለት ፈልጋ በአለቱ ላይ እባቡን ትለቀዋለች እባቡም በአለቱ ላይ ተፈጥፍጦ ይሞታል የክርስቲያን ጠላት የቀደመው እባብ የተባለው ዲያብሎስን ነው ራእይ 12፡9 ክርስቲያንም ዲያብሎስን የሚቀጠቅጠው በአለቱ በክርስቶስ ነው በክርስቶስ ዲያብሎስ ድል ተነስቷልና
3. ንስር ሲታመም
ንስር አንዳንድ ጊዜ ይታመማል በተለይ የተበከለ ምግብ ከበላ ይታመማል በሚታመምበትም ጊዜ ተዘርግቶ በደረቱ ይተኛና ዓይኑን ወደ ፀሐይ ቀና በማድረግ ፀሐይን በቀጥታ በዓይኖቹ ይመለከታል ፈውስንም ከፀሐይ ብርሃን ያገኛል ንስር የተለየ ዓይን ስላለው ፀሐይን በቀጥታ አይቶ ሳይታወር የሚቀር የተለየ ፍጥረት ቢሆን ነው የዓይኑ አፈጣጠር የተለየ እስከ 40 ኪ.ሜ ድረስም አሻግሮ ማየት ይችላል ንስር ክርስቲያኖችንም በሕይወታቸው ችግር ሲገጥማቸው ድካም ሲይዛቸውና ፈተና ሲያንገላታቸው በቀጥታ ወደ ክርስቶስ በመመልከትና እርሱን ደጅ በመጥናት እንደ ፀሐይ ከሚያበራው ፊቱ ፈውስን ብርታትና ኃይልን ይቀበላሉ ንስር አንዳንድ ጊዜ ካልተፈወሰ እዚያው ፀሐይን እያየ ሞቶ ይቀራል ክርስቲያን የመጣው ቢመጣ ጌታውን እያየ ይሞታታል እንጂ ጌታውን ትቶ አይሄድም ሮሜ 8፡38-39 ንስር እስከ 40 ኪሜ ድረስ ከርቀት አሻግሮ እንደሚያይ ሁሉ ንስር አስቀድሞ ከርቀት የሚያዩበትና የሚያስተውሉበትን መንፈስ ከጌታ ተቀብለዋል፡፡
4. ንስር በማለዳ
ንስር በማለዳ ተነስቶ ሁልጊዜ ከአፉ በሚወጣ ፈሳሽ ቅባት መሰል ነገር የክንፎቹን ላባዎች ይቀባል ይህም ቀን በሚበርበት ጊዜ ክንፎቹን የንፋሱን ግፊት ለመቋቋም ጥንካሬ እንዲያገኙ ያደርጋቸዋል ይህንንም ተግባር ባለማቋረጥ በማለዳ ተነስቶ ያደርጋል ንስር ክርስቲያኖችም ዕለት ዕለት በማለዳ በመንቃት በጸሎት ቃሉን በማንበብ ለየዕለቱ ፈተናን ውጣ ውረድ የሚያስፈልጋቸውን ኃይልና ብረታት ከጌታ ይቀበላሉ ይህንን ያልተለማመዱ ክርስቲያኖች ግን ብዙ ጊዜ ሽንፈት ቢገጥማቸው አያስደንቅም ንስር ክርስቲያኖች ግን እንደዚህ አይደሉም ከእንቅልፍ ይልቅ የጌታቸውን ፊት ይናፍቃሉ በማለዳም ወደእርሱ ይገሰግሳሉ ፊቱንም ይፈልጋሉ ጌታም ፊቱን በላያቸው ላይ ያበራል የቀኑንም ክፋት ሁሉ በድል ይወጣሉ፡፡
5. የንስር ፍቅር
ንስር ለጫጩቶቿ የምታደርገው ፍቅር በጣም አስደናቂ ነው ጫጩቶቿ በሚፈለፍሉበት ጊዜ የጎጆው እንጨት እንዳይጎረብጣቸው በደረቷ አካባቢ የሚገኘውን ስስ የገላዋን ክፍል በመንጨት ትጎዘጉዝላቸዋለች ጫጩቶቿም በምቾት ደስ ብሏቸው አካሏ ቁራጭ ላይ ይተኛሉ ይሞቃቸዋልም የክርስቶስ የሆኑትም ተመሳሳይ ፍቅር ለሌሎች እንዲያሳዩ ይጠበቅባቸዋል ለአዳዲሶችም የምናሳየው እንክብካቤ ፍቅርን የተላበሰ ሊሆን ይገባል፡፡
"እግዚአብሔርን በመተማመን የሚጠባበቁ ግን ኃይላቸውን ያድሳሉ እንደ ንስር በክንፍ ይወጣሉ ይሮጣሉ አይታክቱም ይሄዳሉ አይደክሙም"
(ኢሳ 40፡31)
ምንጭ፦ ትርጉም ተድላ ሲማ፣ ብርሃን መፅሔት፣ 1989 ቁጥር 29
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ንስር የአእዋፍ ንጉስ በመባል የሚታወቅ የወፍ ዘር ነው ታላላቅ ነገስታት ንስርን ለተለያዩ ነገሮች መግለጫነት እንደ ምሳሌ ተጠቅመዋል ለነጻነት ለሥልጣን ለግርማና ለመሳሰሉት በዚህ ጹሑፍ ግን የምናተኩረው አስገራሚ የሆነ መመሳሰል በንስር ባሕሪና በክርስቲያን ሕይወት ውስጥ መኖሩን ነው በዚህች አጭር ጹሑፍ ውስጥ አምስት ነጥቦችን ብቻ እንመልከታለን፡፡
1. ንስር ስፍራውን አይለቅም
የተለያ አዕዋፍና አራዊት ከአየር ንብረት ለውጥ ጋር በተዛመደ መልኩ ጎጆዋቸውንና ስፍራቸውን በመተው ወደሌላ ቦታ ይሰደዳሉ ይህም ፍልሰት በመባል ይታወቃል ኀይለኛ ፍልሰት በመባል ይታወቃል ኃይለኛ የክረምት ወቅት ሲመጣ ብዙዎቹ ወደ ሌላ አካባቢ እስከ እረጅም እርቀት ድረስ በመጓዝ ሀገር ሁሉ አቋርጠው ይሰደዳሉ ንስር ግን እንደዚህ አይደለም ክረምት አልፎ በጋም እንደሚመጣ ያውቃል በመሆኑም በብዙ ድካምና ጥረት የሠራውን ጎጆውን ጥሎ አይሸሽም እንደምንም ብሎ በጎጆው ውስጥ በመሆን ያን የክረምትን ወራት ያሳልፋል ንስር የክረምት ወራት ያሳልፋል ንስር ክርስቲያኖችም እንደዚህ ናቸው ወጀብ አውሎ ንፋስ ስለበዛባቸው ብቻ እግዚአብሔርን ካስቀመጣቸው ቦታና ከሰጣቸው ስፍራ ተነስተው አይሄዱም ጌታ ወጀቡን ጸጥ በማድረግ እንደሚያሻግራቸው ያውቃሉ በሆኑም በስፍራቸው ጸንተው ይቆያሉ(ናሆም 1፡3)
2. የንስር ጠላት
ንሰር አንድ ጠላት ብቻ አለው ያም እባብ ነው ንስር ቤቱን የሚሰራው ከፍ ባለ አለት ላይ ስለሆነ ከእባብ ሌላ ምንም ሊደርስበት አይችልም እባብ ግን ተስታኮ ወደ ጎጆው ሊያመራና የንስርን እንቁላሎች ወይም ጫጩቶችን ሊጎዳ ይችላል ከዚህም የተነሳ ሴቷ ንስር እንቁላሎች ወይም ጫቹቶችን ሊጎዳ ይችላል ከዚህም የተነሳ ሴቷ ንስር እንቁላሎችዋንም ሆነ ጫጩቶቿን በትጋት ነው የምትጠብቀው እባቡ ወደ ጎጆዋ ሲመጣ በከፍተኛ ፍጥነት በአፏ እና በጥፍሮቿ ትይዘውና ወደላይ ትበራለች ከዚያም አለት ፈልጋ በአለቱ ላይ እባቡን ትለቀዋለች እባቡም በአለቱ ላይ ተፈጥፍጦ ይሞታል የክርስቲያን ጠላት የቀደመው እባብ የተባለው ዲያብሎስን ነው ራእይ 12፡9 ክርስቲያንም ዲያብሎስን የሚቀጠቅጠው በአለቱ በክርስቶስ ነው በክርስቶስ ዲያብሎስ ድል ተነስቷልና
3. ንስር ሲታመም
ንስር አንዳንድ ጊዜ ይታመማል በተለይ የተበከለ ምግብ ከበላ ይታመማል በሚታመምበትም ጊዜ ተዘርግቶ በደረቱ ይተኛና ዓይኑን ወደ ፀሐይ ቀና በማድረግ ፀሐይን በቀጥታ በዓይኖቹ ይመለከታል ፈውስንም ከፀሐይ ብርሃን ያገኛል ንስር የተለየ ዓይን ስላለው ፀሐይን በቀጥታ አይቶ ሳይታወር የሚቀር የተለየ ፍጥረት ቢሆን ነው የዓይኑ አፈጣጠር የተለየ እስከ 40 ኪ.ሜ ድረስም አሻግሮ ማየት ይችላል ንስር ክርስቲያኖችንም በሕይወታቸው ችግር ሲገጥማቸው ድካም ሲይዛቸውና ፈተና ሲያንገላታቸው በቀጥታ ወደ ክርስቶስ በመመልከትና እርሱን ደጅ በመጥናት እንደ ፀሐይ ከሚያበራው ፊቱ ፈውስን ብርታትና ኃይልን ይቀበላሉ ንስር አንዳንድ ጊዜ ካልተፈወሰ እዚያው ፀሐይን እያየ ሞቶ ይቀራል ክርስቲያን የመጣው ቢመጣ ጌታውን እያየ ይሞታታል እንጂ ጌታውን ትቶ አይሄድም ሮሜ 8፡38-39 ንስር እስከ 40 ኪሜ ድረስ ከርቀት አሻግሮ እንደሚያይ ሁሉ ንስር አስቀድሞ ከርቀት የሚያዩበትና የሚያስተውሉበትን መንፈስ ከጌታ ተቀብለዋል፡፡
4. ንስር በማለዳ
ንስር በማለዳ ተነስቶ ሁልጊዜ ከአፉ በሚወጣ ፈሳሽ ቅባት መሰል ነገር የክንፎቹን ላባዎች ይቀባል ይህም ቀን በሚበርበት ጊዜ ክንፎቹን የንፋሱን ግፊት ለመቋቋም ጥንካሬ እንዲያገኙ ያደርጋቸዋል ይህንንም ተግባር ባለማቋረጥ በማለዳ ተነስቶ ያደርጋል ንስር ክርስቲያኖችም ዕለት ዕለት በማለዳ በመንቃት በጸሎት ቃሉን በማንበብ ለየዕለቱ ፈተናን ውጣ ውረድ የሚያስፈልጋቸውን ኃይልና ብረታት ከጌታ ይቀበላሉ ይህንን ያልተለማመዱ ክርስቲያኖች ግን ብዙ ጊዜ ሽንፈት ቢገጥማቸው አያስደንቅም ንስር ክርስቲያኖች ግን እንደዚህ አይደሉም ከእንቅልፍ ይልቅ የጌታቸውን ፊት ይናፍቃሉ በማለዳም ወደእርሱ ይገሰግሳሉ ፊቱንም ይፈልጋሉ ጌታም ፊቱን በላያቸው ላይ ያበራል የቀኑንም ክፋት ሁሉ በድል ይወጣሉ፡፡
5. የንስር ፍቅር
ንስር ለጫጩቶቿ የምታደርገው ፍቅር በጣም አስደናቂ ነው ጫጩቶቿ በሚፈለፍሉበት ጊዜ የጎጆው እንጨት እንዳይጎረብጣቸው በደረቷ አካባቢ የሚገኘውን ስስ የገላዋን ክፍል በመንጨት ትጎዘጉዝላቸዋለች ጫጩቶቿም በምቾት ደስ ብሏቸው አካሏ ቁራጭ ላይ ይተኛሉ ይሞቃቸዋልም የክርስቶስ የሆኑትም ተመሳሳይ ፍቅር ለሌሎች እንዲያሳዩ ይጠበቅባቸዋል ለአዳዲሶችም የምናሳየው እንክብካቤ ፍቅርን የተላበሰ ሊሆን ይገባል፡፡
"እግዚአብሔርን በመተማመን የሚጠባበቁ ግን ኃይላቸውን ያድሳሉ እንደ ንስር በክንፍ ይወጣሉ ይሮጣሉ አይታክቱም ይሄዳሉ አይደክሙም"
(ኢሳ 40፡31)
ምንጭ፦ ትርጉም ተድላ ሲማ፣ ብርሃን መፅሔት፣ 1989 ቁጥር 29
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍21🔥6❤1👏1
. ──•◈•─────•◈•─
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“ንስር ጫጩቶቹን እንደሚያወጣ፥ በእነርሱም ላይ እንደሚሰፍፍ፥ ክንፎቹን ዘርግቶ ወሰዳቸው፥ በክንፎቹም አዘላቸው።”
ዘዳግም 32፥11
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“ንስር ጫጩቶቹን እንደሚያወጣ፥ በእነርሱም ላይ እንደሚሰፍፍ፥ ክንፎቹን ዘርግቶ ወሰዳቸው፥ በክንፎቹም አዘላቸው።”
ዘዳግም 32፥11
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤9