Audio
#መጻሕፍትን_በድምጽ
👉ርዕስ፦ የካታኮምቡ ሰማዕት
🗣ትርጉም፦ በአማረ ማሞ
መካነ ኢየሱስ ሥነ ጽሑፍ ክፍል።
📻ክፍል-5
ይቀጥላል...
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👉ርዕስ፦ የካታኮምቡ ሰማዕት
🗣ትርጉም፦ በአማረ ማሞ
መካነ ኢየሱስ ሥነ ጽሑፍ ክፍል።
📻ክፍል-5
ይቀጥላል...
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
🥰3👍1
. ──•◈•─────•◈•─
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“እግዚአብሔር ሁሉን ይምር ዘንድ ሁሉን በአለመታዘዝ ዘግቶታልና።”
ሮሜ 11፥32
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“እግዚአብሔር ሁሉን ይምር ዘንድ ሁሉን በአለመታዘዝ ዘግቶታልና።”
ሮሜ 11፥32
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤2👏1
Audio
#መጻሕፍትን_በድምጽ
👉ርዕስ፦ የካታኮምቡ ሰማዕት
🗣ትርጉም፦ በአማረ ማሞ
መካነ ኢየሱስ ሥነ ጽሑፍ ክፍል።
📻ክፍል-6
ይቀጥላል...
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👉ርዕስ፦ የካታኮምቡ ሰማዕት
🗣ትርጉም፦ በአማረ ማሞ
መካነ ኢየሱስ ሥነ ጽሑፍ ክፍል።
📻ክፍል-6
ይቀጥላል...
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤3
ቅዱሳት መጻሕፍት
#መጻሕፍትን_እንመርምር የኢየሱስ ክርስቶስ ትንሣኤ የአካል ወይስ የመንፈስ? ክፍል-፫ (1) በሞተው ሰውና ከሙታን በተነሣው ሰው መካከል ልዩነት የለም፡፡ ከሞት የሚነሣው የሞተው ሰው ራሱ ነው (የሞተው አካል ከሞት የሚነሣው አካል አያቋርጤ ነው:: ለምሳሌ— ኢየሱስ ከትንሣኤውም በኋላ ራሱን፣ “እኔው ራሴው ነኝ” (ሉቃስ 24÷39) ብሏል። አስታውሴው፣ ጠባዩ፣…
#መጻሕፍትን_እንመርምር
የኢየሱስ ክርስቶስ ትንሣኤ የአካል ወይስ የመንፈስ?
ክፍል-፬
"ለዘብተኛ አቋም" አላቸው በመባል የሚታወቁት ሰዱቃውያን በሙታን ትንሣኤ አያምኑም ነበር (ማቴዎስ 22÷23):: በአንጻሩ ደግሞ ፈሪሳውያን በሙታን ትንሣኤ ያምናሉ (ሐዋርያት ሥራ 23÷8)፡፡ ሰዱቃውያን ትንሣኤ ሙታን ላለመኖሩ እንደ ምክንያት ያቀረቡት ጒዳይ ስለማግባትና ስለመጋባት ነበር፤ ይህም ትንሣኤ ሙታን የአካል እንደ ሆነ ታሳቢ ያደረገ ንግግር መሆኑ ብቻ ሳይሆን ኢየሱስም የመለሰው መልስ ትንሣኤ ሙታን የአካል እንደ ሆነ ነገር ግን ከትንሣኤ በኋላ ማግባትና መጋባት እንደማይኖር የሚያስረዳ ነው (ማቴዎስ 22÷28)። ከግማሽ በላይ የሚሆኑት የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት የተጻፉት ቀድሞ ፈሪሳዊ በነበሩ ሰዎች ነው:: አይሁዶች በተለይ ደግሞ ፈሪሳውያን ሰው የተፈጠረው ከምድር ዐፈር እንደ ሆነ (ዘፍጥረት 2÷7)፣ ወደ ዐፈርም እንደሚመለስ (መክብብ 12÷7)፣ በትንሣኤም ቀን ወደ ዐፈርነት ከተለወጠው አካሉ በእግዚአብሔር ኪነ ጥበብ ሕያው ሆኖ ከሙታን እንደሚነሣ (ዘዳግም 32÷39፤ 1ሳሙኤል 2፥6፤ ኢዮብ 19÷25-27፤ መዝሙር 49÷14-15) ያምናሉ፡፡
የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት አስተምህሮ ንጉሥ ዳዊት የእግዚአብሔር ቅዱስ የሆነው ኢየሱስ መበስበስን እንማያይ ተንብዮ ነበር (መዝሙር 16÷10):: ጴጥሮስ የንጉሥ ዳዊትን ትንቢት በተመለከተ እንዲህ በሏል፣ "ይህንን አስቀድሞ በማየቱ እርሱ በሲኦል እንደማይቀርና ሥጋውም እንማይበሰብስ ስለ ክርስቶስ ትንሣኤ ተነገረ" (ሐዋርያት ሥራ 2÷31):: በዚህ ቦታ “ሥጋ” ተብሎ የተተረጐመው የግሪክ ቃል (ሳርክ) ሊበሰብስ እንደሚችል ነገር ግን በእግዚአብሔር ከሃሌ ኲሉነት በመስበስን ሳያይ እንደማይበሰብስ ሆነ ከሙታን እንደ ተነሣ ያስተምራል:: ሐዋርያው ጳውሎስም ይህን የዳዊት ትንቢት በመጥቀስ ኢየሱስ፣ “እንዳልበሰበሰና እግዚአብሔርም ከሙታን እንዳስነሣው ለማረጋገጥ ...ቅዱስህ መበስበስን እንዲያይ አትፈቅድም' ይላል” (ሐዋርያት ሥራ 13፥34:35)።
ኢየሱስ ሰዱቃውያን በሙታን ትንሣኤ ባለማመናቸው፣ “ቅዱሳት መጻሕፍትንና የእግዚአብሔርን ኀይል ስለማታውቁ ትስታላችሁ” (ማቴዎስ 23÷29) ሲል ተናግሯቸዋል: እንዲሁም ዘፀአት 3፥6:15 በመጥቀስ፣ “እኔ የአብርሃም አምላክ፣ የይስሐቅ አምላክ፣ የያዕቀብ አምላክ ነኝ፡፡ እግዚአብሔር የሕያዋን እንጂ የሙታን አምላክ አይደለም” (ማቴዎስ 23÷32) ሲል አስተምሯል፡፡
ነቢዩ ኢሳይያስ፣ “ነገር ግን ሙታን ሕያዋን ይሆናሉ፤ በድናቸውም ይነሣል፡፡ እናንት በዐፈር ውስጥ የምትኖሩ፣ ተነሡ፤ በደስታም ዘመሩ፡፡ ጠልህ እንደ ንጋት ጠል ነው፤ ምድር ሙታንን ትወልዳለች” (ኢሳይያስ 26÷19) የሚለው ትምህርቱ የሞተው አካል እንደሚነሣ ይህም የሙታን ትንሣኤ የአካል እንደ ሆነ የሚያስተምር ነው፡፡
ዳንኤል፣ “በምድር ዐፈር ውስጥ ካንቀላፉት ብዙዎች ይነቃሉ፤ አንዳንዶቹ ለዘላለም ሕይወት፣ ሌሎቹም ለውርደትና ለዘላለም ጒስቊልና ይነሣሉ” (ዳንኤል 12፥2) የሚለው ትንቢቱ ትንሣኤ ሙታን የአካል እንደ ሆነ የሚያስተምር ነው:: በተመሳሳይ መልኩ ኢየሱስ ትንሣኤ ሙታን ከሚያገኙ ሰዎች ግማሹ ወደ ዘላለም ሕይወት ግማሾቹ ደግሞ ወደ ዘላለም ሞት እንደሚሄዱ አስተምሮአል (ዮሐንስ 5÷28)፡፡
ማርያምና ማርታ ወንድማቸው አልዓዛር በትንሣኤ ቀን እንደሚነሣ ተስፋ እንደሚያደርጉ በተጨማሪ ኢየሱስ በትንሣኤ ቀን ብቻ ሳይሆን ዛሬም ሙታንን የማስነሣት ኀይል ከገለጸ በኋላ አልዓዛርን ከሙታን ማስነሣቱ ትንሣኤ ሙታን የአካል እንደ ሆነ በግልጽ የሚያስተምር ነው (ዮሐንስ 11÷38-44)፡፡
ከእነዚህም ሆኑ ከእነዚህ ጋር ተዛማጅነት ካላቸው የብሉይና የሐዲስ ኪዳን ምንባባት በግልጽ የምንረዳው እውነት፣ ብሉያትም ሆኑ ሐዲሳት ስለ ትንሣኤ የሚያስተምሩት ትምህርት ተደጋጋፊ እንዲሁም እርስ በእርሱ የሚጣጣም መሆኑን ነው፡፡ ይኸውም መጽሐፍ ቅዱስ ትንሣኤ የሚለውን ቃል የሚጠቀመው ቊሳዊ አካል ከሙታን መነሣቱን ለማመልከት ብቻ ነው:: ዕብራውያን በተለይ ፈሪሳውያን የጻድቃን የወደፊት ሁኔታ አስመልክቶ የተለያየ አመለካከት ቢኖራቸውም፣ ሁሉም ግን ትንሣኤን ቊሳዊ አካል በጊዜዩዊነትም ሆነ በቋሚነት ከመነሣት ጋር ብቻ ነበር የሚያያይዙት፡፡
ምንም እንኳ ኢየሱስ ክርስቶስ በፈሪሳውያን ግብዝነት ደስተኛ ባይሆንም፣ ሰዱቃውያን የሙታን ትንሣኤ ባለመቀበላቸው ቢነቅፋቸውም፣ ትንሣኤ በሚለው የቃል ፍቺ ላይ ግን ተመሳሳይ አቋም ነበራቸው (ማቴዎስ 22÷23-32)፡፡ ጳውሎስ ቀድሞውኑ ፈሪሳዊ ስለነበር ሥቃይ የደረሰብኝ በሙታን ትንሣኤ በማመኔ ነው ብሎ ነበር (ሐዋርያት ሥራ 23÷6-8)፡፡
በአጠቃላይ ትንሣኤ የሚለው ቃል ያለው ትርጒም የሞተ ሰው አካል በቋሚነትም ሆነ በጊዜያዊነት ሕይወት ማግኘት ማለት ነው፡፡
ይቀጥላል...
ምንጭ፦ ዶ/ር ተስፋዬ ሮበሌ፤ በሥጋ ትንሣኤ አምናለሁ! የአስተምህሮተ ትንሣኤ መጽሐፍ ቅዱሳዊ፣ ታሪካዊና ሥነ አመክንዮአዊ ትንታኔ፤ ከምእራፍ ሰባት የተወሰደ
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የኢየሱስ ክርስቶስ ትንሣኤ የአካል ወይስ የመንፈስ?
ክፍል-፬
"ለዘብተኛ አቋም" አላቸው በመባል የሚታወቁት ሰዱቃውያን በሙታን ትንሣኤ አያምኑም ነበር (ማቴዎስ 22÷23):: በአንጻሩ ደግሞ ፈሪሳውያን በሙታን ትንሣኤ ያምናሉ (ሐዋርያት ሥራ 23÷8)፡፡ ሰዱቃውያን ትንሣኤ ሙታን ላለመኖሩ እንደ ምክንያት ያቀረቡት ጒዳይ ስለማግባትና ስለመጋባት ነበር፤ ይህም ትንሣኤ ሙታን የአካል እንደ ሆነ ታሳቢ ያደረገ ንግግር መሆኑ ብቻ ሳይሆን ኢየሱስም የመለሰው መልስ ትንሣኤ ሙታን የአካል እንደ ሆነ ነገር ግን ከትንሣኤ በኋላ ማግባትና መጋባት እንደማይኖር የሚያስረዳ ነው (ማቴዎስ 22÷28)። ከግማሽ በላይ የሚሆኑት የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት የተጻፉት ቀድሞ ፈሪሳዊ በነበሩ ሰዎች ነው:: አይሁዶች በተለይ ደግሞ ፈሪሳውያን ሰው የተፈጠረው ከምድር ዐፈር እንደ ሆነ (ዘፍጥረት 2÷7)፣ ወደ ዐፈርም እንደሚመለስ (መክብብ 12÷7)፣ በትንሣኤም ቀን ወደ ዐፈርነት ከተለወጠው አካሉ በእግዚአብሔር ኪነ ጥበብ ሕያው ሆኖ ከሙታን እንደሚነሣ (ዘዳግም 32÷39፤ 1ሳሙኤል 2፥6፤ ኢዮብ 19÷25-27፤ መዝሙር 49÷14-15) ያምናሉ፡፡
የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት አስተምህሮ ንጉሥ ዳዊት የእግዚአብሔር ቅዱስ የሆነው ኢየሱስ መበስበስን እንማያይ ተንብዮ ነበር (መዝሙር 16÷10):: ጴጥሮስ የንጉሥ ዳዊትን ትንቢት በተመለከተ እንዲህ በሏል፣ "ይህንን አስቀድሞ በማየቱ እርሱ በሲኦል እንደማይቀርና ሥጋውም እንማይበሰብስ ስለ ክርስቶስ ትንሣኤ ተነገረ" (ሐዋርያት ሥራ 2÷31):: በዚህ ቦታ “ሥጋ” ተብሎ የተተረጐመው የግሪክ ቃል (ሳርክ) ሊበሰብስ እንደሚችል ነገር ግን በእግዚአብሔር ከሃሌ ኲሉነት በመስበስን ሳያይ እንደማይበሰብስ ሆነ ከሙታን እንደ ተነሣ ያስተምራል:: ሐዋርያው ጳውሎስም ይህን የዳዊት ትንቢት በመጥቀስ ኢየሱስ፣ “እንዳልበሰበሰና እግዚአብሔርም ከሙታን እንዳስነሣው ለማረጋገጥ ...ቅዱስህ መበስበስን እንዲያይ አትፈቅድም' ይላል” (ሐዋርያት ሥራ 13፥34:35)።
ኢየሱስ ሰዱቃውያን በሙታን ትንሣኤ ባለማመናቸው፣ “ቅዱሳት መጻሕፍትንና የእግዚአብሔርን ኀይል ስለማታውቁ ትስታላችሁ” (ማቴዎስ 23÷29) ሲል ተናግሯቸዋል: እንዲሁም ዘፀአት 3፥6:15 በመጥቀስ፣ “እኔ የአብርሃም አምላክ፣ የይስሐቅ አምላክ፣ የያዕቀብ አምላክ ነኝ፡፡ እግዚአብሔር የሕያዋን እንጂ የሙታን አምላክ አይደለም” (ማቴዎስ 23÷32) ሲል አስተምሯል፡፡
ነቢዩ ኢሳይያስ፣ “ነገር ግን ሙታን ሕያዋን ይሆናሉ፤ በድናቸውም ይነሣል፡፡ እናንት በዐፈር ውስጥ የምትኖሩ፣ ተነሡ፤ በደስታም ዘመሩ፡፡ ጠልህ እንደ ንጋት ጠል ነው፤ ምድር ሙታንን ትወልዳለች” (ኢሳይያስ 26÷19) የሚለው ትምህርቱ የሞተው አካል እንደሚነሣ ይህም የሙታን ትንሣኤ የአካል እንደ ሆነ የሚያስተምር ነው፡፡
ዳንኤል፣ “በምድር ዐፈር ውስጥ ካንቀላፉት ብዙዎች ይነቃሉ፤ አንዳንዶቹ ለዘላለም ሕይወት፣ ሌሎቹም ለውርደትና ለዘላለም ጒስቊልና ይነሣሉ” (ዳንኤል 12፥2) የሚለው ትንቢቱ ትንሣኤ ሙታን የአካል እንደ ሆነ የሚያስተምር ነው:: በተመሳሳይ መልኩ ኢየሱስ ትንሣኤ ሙታን ከሚያገኙ ሰዎች ግማሹ ወደ ዘላለም ሕይወት ግማሾቹ ደግሞ ወደ ዘላለም ሞት እንደሚሄዱ አስተምሮአል (ዮሐንስ 5÷28)፡፡
ማርያምና ማርታ ወንድማቸው አልዓዛር በትንሣኤ ቀን እንደሚነሣ ተስፋ እንደሚያደርጉ በተጨማሪ ኢየሱስ በትንሣኤ ቀን ብቻ ሳይሆን ዛሬም ሙታንን የማስነሣት ኀይል ከገለጸ በኋላ አልዓዛርን ከሙታን ማስነሣቱ ትንሣኤ ሙታን የአካል እንደ ሆነ በግልጽ የሚያስተምር ነው (ዮሐንስ 11÷38-44)፡፡
ከእነዚህም ሆኑ ከእነዚህ ጋር ተዛማጅነት ካላቸው የብሉይና የሐዲስ ኪዳን ምንባባት በግልጽ የምንረዳው እውነት፣ ብሉያትም ሆኑ ሐዲሳት ስለ ትንሣኤ የሚያስተምሩት ትምህርት ተደጋጋፊ እንዲሁም እርስ በእርሱ የሚጣጣም መሆኑን ነው፡፡ ይኸውም መጽሐፍ ቅዱስ ትንሣኤ የሚለውን ቃል የሚጠቀመው ቊሳዊ አካል ከሙታን መነሣቱን ለማመልከት ብቻ ነው:: ዕብራውያን በተለይ ፈሪሳውያን የጻድቃን የወደፊት ሁኔታ አስመልክቶ የተለያየ አመለካከት ቢኖራቸውም፣ ሁሉም ግን ትንሣኤን ቊሳዊ አካል በጊዜዩዊነትም ሆነ በቋሚነት ከመነሣት ጋር ብቻ ነበር የሚያያይዙት፡፡
ምንም እንኳ ኢየሱስ ክርስቶስ በፈሪሳውያን ግብዝነት ደስተኛ ባይሆንም፣ ሰዱቃውያን የሙታን ትንሣኤ ባለመቀበላቸው ቢነቅፋቸውም፣ ትንሣኤ በሚለው የቃል ፍቺ ላይ ግን ተመሳሳይ አቋም ነበራቸው (ማቴዎስ 22÷23-32)፡፡ ጳውሎስ ቀድሞውኑ ፈሪሳዊ ስለነበር ሥቃይ የደረሰብኝ በሙታን ትንሣኤ በማመኔ ነው ብሎ ነበር (ሐዋርያት ሥራ 23÷6-8)፡፡
በአጠቃላይ ትንሣኤ የሚለው ቃል ያለው ትርጒም የሞተ ሰው አካል በቋሚነትም ሆነ በጊዜያዊነት ሕይወት ማግኘት ማለት ነው፡፡
ይቀጥላል...
ምንጭ፦ ዶ/ር ተስፋዬ ሮበሌ፤ በሥጋ ትንሣኤ አምናለሁ! የአስተምህሮተ ትንሣኤ መጽሐፍ ቅዱሳዊ፣ ታሪካዊና ሥነ አመክንዮአዊ ትንታኔ፤ ከምእራፍ ሰባት የተወሰደ
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍4
በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ "የትንሣኤ ምዕራፍ" በመባል የሚታወቀው ምዕራፍ የቱ ነው?
Anonymous Quiz
36%
ሀ. ዮሐንስ ወንጌል፣ ምዕራፍ 20
24%
ለ. ሉቃስ ወንጌል፣ ምዕራፍ 24
33%
ሐ. 1 ቆሮንቶስ፣ ምዕራፍ 15
7%
መ. የዮሐንስ ራእይ፣ ምዕራፍ 20
🥰4👍2
. ──•◈•─────•◈•─
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“ሕፃንነትና ጕብዝና ከንቱዎች ናቸውና ከልብህ ኀዘንን አርቅ፥ ከሰውነትህም ክፉን ነገር አስወግድ።”
መክብብ 11፥10
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“ሕፃንነትና ጕብዝና ከንቱዎች ናቸውና ከልብህ ኀዘንን አርቅ፥ ከሰውነትህም ክፉን ነገር አስወግድ።”
መክብብ 11፥10
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤4👍1
Audio
#መጻሕፍትን_በድምጽ
👉ርዕስ፦ የካታኮምቡ ሰማዕት
🗣ትርጉም፦ በአማረ ማሞ
መካነ ኢየሱስ ሥነ ጽሑፍ ክፍል።
📻ክፍል-7
ይቀጥላል...
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👉ርዕስ፦ የካታኮምቡ ሰማዕት
🗣ትርጉም፦ በአማረ ማሞ
መካነ ኢየሱስ ሥነ ጽሑፍ ክፍል።
📻ክፍል-7
ይቀጥላል...
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍2
#እራሳችንን_እንመርምር
ብዙ ጸሎታችንም ሆነ ከእግዚአብሔር ጋር የምንገጥመው ክርክር እግዚአብሔር እኛን ወይንም የእኛን ነገር ቸል እንዳለ የሚያሳብቅ እና የሚያሳይ ነው። ግን አንድ ነገር ቆም ብለን እራሳችንን ብንፈትሽ ጥሩ ነው። ምን ከተባለ እኛስ ምን ያህል ስለ እግዚአብሔር እና ስለእግዚአብሔር ቤት ጉዳይ ግድ ይለናል? እስቲ ግድ የለውም በዚህ ጉዳይ ላይ እራሳችንን እንመርምር።
“በውኑ ይህ ቤት ፈርሶ ሳለ እናንተ ራሳችሁ በተሸለሙ ቤቶቻችሁ ለመኖር ጊዜው ነውን?”
ሐጌ 1፥4
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ብዙ ጸሎታችንም ሆነ ከእግዚአብሔር ጋር የምንገጥመው ክርክር እግዚአብሔር እኛን ወይንም የእኛን ነገር ቸል እንዳለ የሚያሳብቅ እና የሚያሳይ ነው። ግን አንድ ነገር ቆም ብለን እራሳችንን ብንፈትሽ ጥሩ ነው። ምን ከተባለ እኛስ ምን ያህል ስለ እግዚአብሔር እና ስለእግዚአብሔር ቤት ጉዳይ ግድ ይለናል? እስቲ ግድ የለውም በዚህ ጉዳይ ላይ እራሳችንን እንመርምር።
“በውኑ ይህ ቤት ፈርሶ ሳለ እናንተ ራሳችሁ በተሸለሙ ቤቶቻችሁ ለመኖር ጊዜው ነውን?”
ሐጌ 1፥4
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍7🙏2🥰1
. ──•◈•─────•◈•─
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“ኖኅ ግን በእግዚአብሔር ፊት ሞገስን አገኘ።”
ዘፍጥረት 6፥8
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“ኖኅ ግን በእግዚአብሔር ፊት ሞገስን አገኘ።”
ዘፍጥረት 6፥8
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
🔥11👍4
Audio
#መጻሕፍትን_በድምጽ
👉ርዕስ፦ የካታኮምቡ ሰማዕት
🗣ትርጉም፦ በአማረ ማሞ
መካነ ኢየሱስ ሥነ ጽሑፍ ክፍል።
📻ክፍል-8
ይቀጥላል...
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👉ርዕስ፦ የካታኮምቡ ሰማዕት
🗣ትርጉም፦ በአማረ ማሞ
መካነ ኢየሱስ ሥነ ጽሑፍ ክፍል።
📻ክፍል-8
ይቀጥላል...
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ቅዱሳት መጻሕፍት
#መጻሕፍትን_እንመርምር የኢየሱስ ክርስቶስ ትንሣኤ የአካል ወይስ የመንፈስ? ክፍል-፬ "ለዘብተኛ አቋም" አላቸው በመባል የሚታወቁት ሰዱቃውያን በሙታን ትንሣኤ አያምኑም ነበር (ማቴዎስ 22÷23):: በአንጻሩ ደግሞ ፈሪሳውያን በሙታን ትንሣኤ ያምናሉ (ሐዋርያት ሥራ 23÷8)፡፡ ሰዱቃውያን ትንሣኤ ሙታን ላለመኖሩ እንደ ምክንያት ያቀረቡት ጒዳይ ስለማግባትና ስለመጋባት…
#መጻሕፍትን_እንመርምር
የኢየሱስ ክርስቶስ ትንሣኤ የአካል ወይስ የመንፈስ?
ክፍል-፭
2. የሐዋርያው ጳውሎስ አስተምህሮ
ሐዋርያው ጳውሎስ እጅግ ጥንታዊ ነው የሚባለውን የቤተ ክርስቲያን የእምነት መግለጫ ጠቅሶ በጻፈበት ክፍል ላይ፣ የክርስቶስን ሞት ከገለጸ በኋላ የሃይማኖት መግለጫው እንዲህ ያላል፣ “ቅዱሳት መጻሕፈት እንደሚሉት ክርስቶስ ስለ ኀጢአታችን ሞተ፤ ተቀበረ፤ በቅዱሳት መጻሕፍት እንደ ተጻፈውም በሦስተኛው ቀን ተነሣ” (1ቆሮንቶስ 15÷3-4)፡፡ ከዚህ ክፍል በግልጽ የምንማረው እውነት፣ ሞቶ የተቀበረው አካል ከሙታን እንደ ተነሣ ነው፡፡ ይህም የሞተው፣ የተቀበረውና ሞትን ድል አድርጎ የተነሣው አካል አንድ መሆኑን አመላካች ነው፡፡ በዚሁ ምዕራፍ ሐዋርያው የስንዴ ቅንጣትን በምሳሌነት በመጠቀም አራት ጊዜ የተዘራው የስንዴ ቅንጣት እንደ በቀለ ይገልጻል፣ “…ይዘራል ይነሣል ይዘራል ይነሣል ይዘራል ይነሣል ይዘራል…ይነሣል” (1ቆሮንቶስ 15÷42-44)። ልክ እንደዚሁ ሁሉ ሞቶ የተቀበረው የክርስቶስ አካል በትንሣኤ እንደ ተነሣ የሚያስተምር ነው፡፡
ክርስቶስ ዳግም ተመልሶ ሲመጣ፣ “ክቡር ሥጋውን እንዲመስል የተዋረደውን ሥጋችንን ይለውጣል” (ፊልጵስዩስ 3÷21) የሚለው የሐዋርያው አነጋገር የተዋረደው የእኛ ሥጋ ልክ እንደ እርሱ ሥጋ እንደሚለወጥ ሲገልጽ፣ እርሱ ራሱ “በተለወጠ ሥጋ” እንዳለ የሚያስተምር ነው፡፡ በዚህ ክፍል የቅዱሳኑንም ሆነ የክርስቶስን አካል ለማመልከት ጥቅም ላይ የዋለውና የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ ቅጆች “ሥጋ” ብለው የተረጐሙት “ሶማ” የሚለው የሐዲስ ኪዳን ግሪክ፣ ዘወትር የሚጨበጠውን የሚዳሰሰውን አካል የሚያመለክት ነው፡፡ የክርስቶስ ትንሣኤ በመንፈስ ቢሆን ኖሮ፣ ሐዋርያው “ሥጋ” ከሚለው ቃል ይልቅ መንፈስ የሚለውን ቃል ይጠቀም ነበር፡፡ የጻድቃን ዕጣ ፈንታቸው በትንሣኤ ሥጋ ከሙታን መነሣት ከሆነ፣ ክርስቶስም ከሙታን የተነሣው በትንሣኤ ሥጋ ነው ማለት ነው፡፡ ጻድቃን ከመሞት ወደ አለመሞት የመለወጣቸው ሂደት ቊሳዊ እንደ ሆነው ሁሉ፣ የክርስቶስም ትንሣኤ በቊሳዊ አካል እንደ ሆነ በንጽጽር የሚያሳይ ነው::
ሐዋርያው፣ “ኢየሱስን ከሙታን ያስነሣው የእርሱ መንፈስ በእናንተ የሚኖር ከሆነ፣ ክርስቶስን ከሙታን ያስነሣው፣ በውስጣችሁ በሚኖረው በመንፈሱ ሟች ለሆነው ሰውነታችሁ ሕይወትን ይሰጣል” (ሮሜ 8÷11) በዚህ ክፍል ሐዋርያው በክርስቶስ አካል ላይ መታደስ እንደ ተካሄደ እንጂ፣ አካሉ በመቃብር እንዳልቀረ ታሳቢ ያደረገ ንግግር ነው::
ሐዋርያው ጳውሎስ በቈላስይስ 2፥9፣ “የመለኮት ሙላት ሁሉ በአካል በእርሱ ይኖራልና" ሲል “ይኖራል” (ካቶይኬ) የሚለውን ቃል የተጠቀመው የአሁን ጊዜ ግሥ ነው፤ ይህም አምላክ የመሆን ባሕርዩ (“የመለኮት ሙላት” “ቴዎቴቶስ” ) በሰውነቱ/በሥጋው (“ሶማቲኮስ”) የሚኖረው፣ ሐዋርያው ይህን መልእክት እስከሚጽፍበት ጊዜ ድረስ ኢየሱስ አካል/ሥጋ እንዳለው የሚያሳይ ነው፡፡
ሉቃስ፣ በሐዋርያት ሥራ መጽሐፉ ላይ ባቀረበው ዘገባ ጳውሎስ፣ የኢየሱስ ክርስቶስ ሥጋ እንደ ንጉሥ ዳዊት ሥጋ በመቃብር ውስጥ እንዳልበሰበሰ፣ ነገር ግን እግዚአብሔር የሞትን ጣር አጥፍቶ አንዳስነሣው ገልጾአል (ሐዋርያት ሥራ 13÷34-37)፡፡ በተጨማሪም ይህ የክርስቶስ ኢየሱስ የአካል ትንሣኤ የትንቢት ፍጻሜ እንደ ሆነ ተገልጾአል (መዝሙር 16÷10)። የክርስቶስ አካል ከንጉሥ ዳዊት አካል ጋር ተነጻጽሮ መቅረቡ እንዲሁም የንጉሥ ዳዊት መቃብር ዛሬም ድረስ እንዳለና የኢየሱስ መቃብር ግን ባዶ መሆኑ፣ የአካል ትንሣኤን አያመለክትም ብሎ ማሰብ እጅግ ሲበዛ አስቸጋሪ ነው፡፡
በአንደኛ ቆሮንቶስ ምዕራፍ ዐሥራ አምስት በዝርዝር የቀረበው መረጃ የኢየሱስ ክርስቶስ ትንሣኤ የአካል መሆኑን በግልጽ የሚያስተምር ነው:: ዋና የሚባሉትን ነጥቦች እንመልከት
ይቀጥላል...
ምንጭ፦ ዶ/ር ተስፋዬ ሮበሌ፤ በሥጋ ትንሣኤ አምናለሁ! የአስተምህሮተ ትንሣኤ መጽሐፍ ቅዱሳዊ፣ ታሪካዊና ሥነ አመክንዮአዊ ትንታኔ፤ ከምእራፍ ሰባት የተወሰደ
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የኢየሱስ ክርስቶስ ትንሣኤ የአካል ወይስ የመንፈስ?
ክፍል-፭
2. የሐዋርያው ጳውሎስ አስተምህሮ
ሐዋርያው ጳውሎስ እጅግ ጥንታዊ ነው የሚባለውን የቤተ ክርስቲያን የእምነት መግለጫ ጠቅሶ በጻፈበት ክፍል ላይ፣ የክርስቶስን ሞት ከገለጸ በኋላ የሃይማኖት መግለጫው እንዲህ ያላል፣ “ቅዱሳት መጻሕፈት እንደሚሉት ክርስቶስ ስለ ኀጢአታችን ሞተ፤ ተቀበረ፤ በቅዱሳት መጻሕፍት እንደ ተጻፈውም በሦስተኛው ቀን ተነሣ” (1ቆሮንቶስ 15÷3-4)፡፡ ከዚህ ክፍል በግልጽ የምንማረው እውነት፣ ሞቶ የተቀበረው አካል ከሙታን እንደ ተነሣ ነው፡፡ ይህም የሞተው፣ የተቀበረውና ሞትን ድል አድርጎ የተነሣው አካል አንድ መሆኑን አመላካች ነው፡፡ በዚሁ ምዕራፍ ሐዋርያው የስንዴ ቅንጣትን በምሳሌነት በመጠቀም አራት ጊዜ የተዘራው የስንዴ ቅንጣት እንደ በቀለ ይገልጻል፣ “…ይዘራል ይነሣል ይዘራል ይነሣል ይዘራል ይነሣል ይዘራል…ይነሣል” (1ቆሮንቶስ 15÷42-44)። ልክ እንደዚሁ ሁሉ ሞቶ የተቀበረው የክርስቶስ አካል በትንሣኤ እንደ ተነሣ የሚያስተምር ነው፡፡
ክርስቶስ ዳግም ተመልሶ ሲመጣ፣ “ክቡር ሥጋውን እንዲመስል የተዋረደውን ሥጋችንን ይለውጣል” (ፊልጵስዩስ 3÷21) የሚለው የሐዋርያው አነጋገር የተዋረደው የእኛ ሥጋ ልክ እንደ እርሱ ሥጋ እንደሚለወጥ ሲገልጽ፣ እርሱ ራሱ “በተለወጠ ሥጋ” እንዳለ የሚያስተምር ነው፡፡ በዚህ ክፍል የቅዱሳኑንም ሆነ የክርስቶስን አካል ለማመልከት ጥቅም ላይ የዋለውና የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ ቅጆች “ሥጋ” ብለው የተረጐሙት “ሶማ” የሚለው የሐዲስ ኪዳን ግሪክ፣ ዘወትር የሚጨበጠውን የሚዳሰሰውን አካል የሚያመለክት ነው፡፡ የክርስቶስ ትንሣኤ በመንፈስ ቢሆን ኖሮ፣ ሐዋርያው “ሥጋ” ከሚለው ቃል ይልቅ መንፈስ የሚለውን ቃል ይጠቀም ነበር፡፡ የጻድቃን ዕጣ ፈንታቸው በትንሣኤ ሥጋ ከሙታን መነሣት ከሆነ፣ ክርስቶስም ከሙታን የተነሣው በትንሣኤ ሥጋ ነው ማለት ነው፡፡ ጻድቃን ከመሞት ወደ አለመሞት የመለወጣቸው ሂደት ቊሳዊ እንደ ሆነው ሁሉ፣ የክርስቶስም ትንሣኤ በቊሳዊ አካል እንደ ሆነ በንጽጽር የሚያሳይ ነው::
ሐዋርያው፣ “ኢየሱስን ከሙታን ያስነሣው የእርሱ መንፈስ በእናንተ የሚኖር ከሆነ፣ ክርስቶስን ከሙታን ያስነሣው፣ በውስጣችሁ በሚኖረው በመንፈሱ ሟች ለሆነው ሰውነታችሁ ሕይወትን ይሰጣል” (ሮሜ 8÷11) በዚህ ክፍል ሐዋርያው በክርስቶስ አካል ላይ መታደስ እንደ ተካሄደ እንጂ፣ አካሉ በመቃብር እንዳልቀረ ታሳቢ ያደረገ ንግግር ነው::
ሐዋርያው ጳውሎስ በቈላስይስ 2፥9፣ “የመለኮት ሙላት ሁሉ በአካል በእርሱ ይኖራልና" ሲል “ይኖራል” (ካቶይኬ) የሚለውን ቃል የተጠቀመው የአሁን ጊዜ ግሥ ነው፤ ይህም አምላክ የመሆን ባሕርዩ (“የመለኮት ሙላት” “ቴዎቴቶስ” ) በሰውነቱ/በሥጋው (“ሶማቲኮስ”) የሚኖረው፣ ሐዋርያው ይህን መልእክት እስከሚጽፍበት ጊዜ ድረስ ኢየሱስ አካል/ሥጋ እንዳለው የሚያሳይ ነው፡፡
ሉቃስ፣ በሐዋርያት ሥራ መጽሐፉ ላይ ባቀረበው ዘገባ ጳውሎስ፣ የኢየሱስ ክርስቶስ ሥጋ እንደ ንጉሥ ዳዊት ሥጋ በመቃብር ውስጥ እንዳልበሰበሰ፣ ነገር ግን እግዚአብሔር የሞትን ጣር አጥፍቶ አንዳስነሣው ገልጾአል (ሐዋርያት ሥራ 13÷34-37)፡፡ በተጨማሪም ይህ የክርስቶስ ኢየሱስ የአካል ትንሣኤ የትንቢት ፍጻሜ እንደ ሆነ ተገልጾአል (መዝሙር 16÷10)። የክርስቶስ አካል ከንጉሥ ዳዊት አካል ጋር ተነጻጽሮ መቅረቡ እንዲሁም የንጉሥ ዳዊት መቃብር ዛሬም ድረስ እንዳለና የኢየሱስ መቃብር ግን ባዶ መሆኑ፣ የአካል ትንሣኤን አያመለክትም ብሎ ማሰብ እጅግ ሲበዛ አስቸጋሪ ነው፡፡
በአንደኛ ቆሮንቶስ ምዕራፍ ዐሥራ አምስት በዝርዝር የቀረበው መረጃ የኢየሱስ ክርስቶስ ትንሣኤ የአካል መሆኑን በግልጽ የሚያስተምር ነው:: ዋና የሚባሉትን ነጥቦች እንመልከት
ይቀጥላል...
ምንጭ፦ ዶ/ር ተስፋዬ ሮበሌ፤ በሥጋ ትንሣኤ አምናለሁ! የአስተምህሮተ ትንሣኤ መጽሐፍ ቅዱሳዊ፣ ታሪካዊና ሥነ አመክንዮአዊ ትንታኔ፤ ከምእራፍ ሰባት የተወሰደ
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤7👍2
. ──•◈•─────•◈•─
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“ኢየሱስም ከዚያ አልፎ በመቅረጫው ተቀምጦ የነበረ ማቴዎስ የሚባል አንድ ሰው አየና፦ ተከተለኝ አለው። ተነሥቶም ተከተለው።”
ማቴዎስ 9፥9
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“ኢየሱስም ከዚያ አልፎ በመቅረጫው ተቀምጦ የነበረ ማቴዎስ የሚባል አንድ ሰው አየና፦ ተከተለኝ አለው። ተነሥቶም ተከተለው።”
ማቴዎስ 9፥9
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍7
Audio
#መጻሕፍትን_በድምጽ
👉ርዕስ፦ የካታኮምቡ ሰማዕት
🗣ትርጉም፦ በአማረ ማሞ
መካነ ኢየሱስ ሥነ ጽሑፍ ክፍል።
📻ክፍል-9
ይቀጥላል...
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👉ርዕስ፦ የካታኮምቡ ሰማዕት
🗣ትርጉም፦ በአማረ ማሞ
መካነ ኢየሱስ ሥነ ጽሑፍ ክፍል።
📻ክፍል-9
ይቀጥላል...
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
#የእግዚአብሔር_ቃል_ምን_ይላል?
ሮሜ 8
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ እንግዲህ በክርስቶስ ኢየሱስ ላሉት አሁን ኵነኔ የለባቸውም።
² በክርስቶስ ኢየሱስ ያለው የሕይወት መንፈስ ሕግ ከኃጢአትና ከሞት ሕግ አርነት አውጥቶኛልና።
³-⁴ ከሥጋ የተነሣ ስለ ደከመ ለሕግ ያልተቻለውን፥ እግዚአብሔር የገዛ ልጁን በኃጢአተኛ ሥጋ ምሳሌ በኃጢአትም ምክንያት ልኮ አድርጎአልና፤ እንደ መንፈስ ፈቃድ እንጂ እንደ ሥጋ ፈቃድ በማንመላለስ በእኛ የሕግ ትእዛዝ ይፈጸም ዘንድ ኃጢአትን በሥጋ ኰነነ።
⁵ እንደ ሥጋ ፈቃድ የሚኖሩ የሥጋን ነገር ያስባሉና፥ እንደ መንፈስ ፈቃድ የሚኖሩ ግን የመንፈስን ነገር ያስባሉ።
⁶ ስለ ሥጋ ማሰብ ሞት ነውና፥ ስለ መንፈስ ማሰብ ግን ሕይወትና ሰላም ነው።
⁷ ስለ ሥጋ ማሰብ በእግዚአብሔር ዘንድ ጥል ነውና፤ ለእግዚአብሔር ሕግ አይገዛምና፥ መገዛትም ተስኖታል፤
⁸ በሥጋ ያሉትም እግዚአብሔርን ደስ ሊያሰኙት አይችሉም።
⁹ እናንተ ግን የእግዚአብሔር መንፈስ በእናንተ ዘንድ ቢኖር፥ በመንፈስ እንጂ በሥጋ አይደላችሁም። የክርስቶስ መንፈስ የሌለው ከሆነ ግን ይኸው የእርሱ ወገን አይደለም።
¹⁰ ክርስቶስ በእናንተ ውስጥ ቢሆን ሰውነታችሁ በኃጢአት ምክንያት የሞተ ነው፥ መንፈሳችሁ ግን በጽድቅ ምክንያት ሕያው ነው።
¹¹ ነገር ግን ኢየሱስን ከሙታን ያስነሣው የእርሱ መንፈስ በእናንተ ዘንድ ቢኖር፥ ክርስቶስ ኢየሱስን ከሙታን ያስነሣው እርሱ በእናንተ በሚኖረው በመንፈሱ፥ ለሚሞተው ሰውነታችሁ ደግሞ ሕይወትን ይሰጠዋል።
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ሮሜ 8
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ እንግዲህ በክርስቶስ ኢየሱስ ላሉት አሁን ኵነኔ የለባቸውም።
² በክርስቶስ ኢየሱስ ያለው የሕይወት መንፈስ ሕግ ከኃጢአትና ከሞት ሕግ አርነት አውጥቶኛልና።
³-⁴ ከሥጋ የተነሣ ስለ ደከመ ለሕግ ያልተቻለውን፥ እግዚአብሔር የገዛ ልጁን በኃጢአተኛ ሥጋ ምሳሌ በኃጢአትም ምክንያት ልኮ አድርጎአልና፤ እንደ መንፈስ ፈቃድ እንጂ እንደ ሥጋ ፈቃድ በማንመላለስ በእኛ የሕግ ትእዛዝ ይፈጸም ዘንድ ኃጢአትን በሥጋ ኰነነ።
⁵ እንደ ሥጋ ፈቃድ የሚኖሩ የሥጋን ነገር ያስባሉና፥ እንደ መንፈስ ፈቃድ የሚኖሩ ግን የመንፈስን ነገር ያስባሉ።
⁶ ስለ ሥጋ ማሰብ ሞት ነውና፥ ስለ መንፈስ ማሰብ ግን ሕይወትና ሰላም ነው።
⁷ ስለ ሥጋ ማሰብ በእግዚአብሔር ዘንድ ጥል ነውና፤ ለእግዚአብሔር ሕግ አይገዛምና፥ መገዛትም ተስኖታል፤
⁸ በሥጋ ያሉትም እግዚአብሔርን ደስ ሊያሰኙት አይችሉም።
⁹ እናንተ ግን የእግዚአብሔር መንፈስ በእናንተ ዘንድ ቢኖር፥ በመንፈስ እንጂ በሥጋ አይደላችሁም። የክርስቶስ መንፈስ የሌለው ከሆነ ግን ይኸው የእርሱ ወገን አይደለም።
¹⁰ ክርስቶስ በእናንተ ውስጥ ቢሆን ሰውነታችሁ በኃጢአት ምክንያት የሞተ ነው፥ መንፈሳችሁ ግን በጽድቅ ምክንያት ሕያው ነው።
¹¹ ነገር ግን ኢየሱስን ከሙታን ያስነሣው የእርሱ መንፈስ በእናንተ ዘንድ ቢኖር፥ ክርስቶስ ኢየሱስን ከሙታን ያስነሣው እርሱ በእናንተ በሚኖረው በመንፈሱ፥ ለሚሞተው ሰውነታችሁ ደግሞ ሕይወትን ይሰጠዋል።
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤3👍1
. ──•◈•─────•◈•─
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“ነገር ግን፦ ቃሌን ስሙ፥ እኔም አምላክ እሆናችኋለሁ እናንተም ሕዝብ ትሆኑኛላችሁ፤ መልካምም ይሆንላችሁ ዘንድ ባዘዝኋችሁ መንገድ ሁሉ ሂዱ ብዬ በዚህ ነገር አዘዝኋቸው።”
ኤርምያስ 7፥23
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“ነገር ግን፦ ቃሌን ስሙ፥ እኔም አምላክ እሆናችኋለሁ እናንተም ሕዝብ ትሆኑኛላችሁ፤ መልካምም ይሆንላችሁ ዘንድ ባዘዝኋችሁ መንገድ ሁሉ ሂዱ ብዬ በዚህ ነገር አዘዝኋቸው።”
ኤርምያስ 7፥23
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
🔥4👍1
የካታኮቡ ሰማእታት ክፍል አሥር catacombs part 10
ታላቁ ተስፋ - Great Hope - Official
#መጻሕፍትን_በድምጽ
👉ርዕስ፦ የካታኮምቡ ሰማዕት
🗣ትርጉም፦ በአማረ ማሞ
መካነ ኢየሱስ ሥነ ጽሑፍ ክፍል።
📻ክፍል-10
ይቀጥላል...
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👉ርዕስ፦ የካታኮምቡ ሰማዕት
🗣ትርጉም፦ በአማረ ማሞ
መካነ ኢየሱስ ሥነ ጽሑፍ ክፍል።
📻ክፍል-10
ይቀጥላል...
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍2🔥2
#ከተማ_ወይም_ቦታ_በቅዱሳት_መጻሕፍት
#ደማስቆ
ሁለት ሺህ ዓመት ከክርስቶስ ልደት በፊት የተሠራ እስከ ዛሬ ድረስ የሶርያ መናገሻ ከተማ የሆነ። «ቅን» የተባለው ጥንታዊ መንገድ እስከ አሁን ይገኝበታል፤ ሐ.ሥ. 9፥11። በአቅራቢያው አባናና ፋርፋ የተባሉ ሁለት ወንዞች ይፈሳሉ፤ 2ነገ. 5፥12። ከምሥራቅ ወደ ታላቁ ባሕር፥ ከሰሜንም ወደ ግብጽ የሚሄዱ መንገዶች የሚገናኙበት ስለሆነ፥ ብዙ ነጋዴዎች የሚመላለሱበት መናኸሪያ ከተማ ነበር።
አብርሃም በአቅራቢያው ይኖር ነበር፣ ዘፍ. 14፥15። እነዳዊት የደማስቆን ሰዎች ድል ነሡ፤ 2ሳሙ. 8፥5:6። በእስራኤል ታሪክ ውስጥ ስማቸው ተጽፎ የምናገኛቸው የሶርያ ገዥዎች የሚከተሉት ናቸው ፦
👉ሬዞን (1ነገ. 11፥23-25)፥
👉ወልደ አዴር (1ነገ. 15፥18)፥
👉አዛሄል (2ነገ. 13፥22)፥
👉ወልደ አዴር 2ኛ (2ነገ. 13፥24)፥
👉ረአሶን (2ነገ. 16፥5፤ ኢሳ. 7፥1)።
ጳውሎስ ወደ ደማስቆ ሲሄድ ሳለ ክርስቶስ ተገለጠለት፤ ወንጌልን ማስተማር በደማስቆ ጀመረ፤ ሐ.ሥ. 9። በ628 ዓ.ም. የእስልምና ሃይማኖት ተከታዮች ከተማውን ማረኩና የእስልምና ትምህርት ማስፋፊያ አደረጉት።
ምንጭ፦ የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት፤ ገጽ 227-228
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
#ደማስቆ
ሁለት ሺህ ዓመት ከክርስቶስ ልደት በፊት የተሠራ እስከ ዛሬ ድረስ የሶርያ መናገሻ ከተማ የሆነ። «ቅን» የተባለው ጥንታዊ መንገድ እስከ አሁን ይገኝበታል፤ ሐ.ሥ. 9፥11። በአቅራቢያው አባናና ፋርፋ የተባሉ ሁለት ወንዞች ይፈሳሉ፤ 2ነገ. 5፥12። ከምሥራቅ ወደ ታላቁ ባሕር፥ ከሰሜንም ወደ ግብጽ የሚሄዱ መንገዶች የሚገናኙበት ስለሆነ፥ ብዙ ነጋዴዎች የሚመላለሱበት መናኸሪያ ከተማ ነበር።
አብርሃም በአቅራቢያው ይኖር ነበር፣ ዘፍ. 14፥15። እነዳዊት የደማስቆን ሰዎች ድል ነሡ፤ 2ሳሙ. 8፥5:6። በእስራኤል ታሪክ ውስጥ ስማቸው ተጽፎ የምናገኛቸው የሶርያ ገዥዎች የሚከተሉት ናቸው ፦
👉ሬዞን (1ነገ. 11፥23-25)፥
👉ወልደ አዴር (1ነገ. 15፥18)፥
👉አዛሄል (2ነገ. 13፥22)፥
👉ወልደ አዴር 2ኛ (2ነገ. 13፥24)፥
👉ረአሶን (2ነገ. 16፥5፤ ኢሳ. 7፥1)።
ጳውሎስ ወደ ደማስቆ ሲሄድ ሳለ ክርስቶስ ተገለጠለት፤ ወንጌልን ማስተማር በደማስቆ ጀመረ፤ ሐ.ሥ. 9። በ628 ዓ.ም. የእስልምና ሃይማኖት ተከታዮች ከተማውን ማረኩና የእስልምና ትምህርት ማስፋፊያ አደረጉት።
ምንጭ፦ የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት፤ ገጽ 227-228
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤5👍1
. ──•◈•─────•◈•─
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“ድሆችን እናስብ ዘንድ ብቻ ለመኑን፥ ይህንም ደግሞ ላደርግ ተጋሁ።”
ገላትያ 2፥10
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“ድሆችን እናስብ ዘንድ ብቻ ለመኑን፥ ይህንም ደግሞ ላደርግ ተጋሁ።”
ገላትያ 2፥10
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍2❤1
Audio
#መጻሕፍትን_በድምጽ
👉ርዕስ፦ የካታኮምቡ ሰማዕት
🗣ትርጉም፦ በአማረ ማሞ
መካነ ኢየሱስ ሥነ ጽሑፍ ክፍል።
📻ክፍል-11
ይቀጥላል...
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👉ርዕስ፦ የካታኮምቡ ሰማዕት
🗣ትርጉም፦ በአማረ ማሞ
መካነ ኢየሱስ ሥነ ጽሑፍ ክፍል።
📻ክፍል-11
ይቀጥላል...
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤3👍3
ንቃ.pdf
6.1 MB
ርዕስ፦ ንቃ
ከአስመሳይ ሃይማኖተኞች ተጠንቀቁ
2ኛ ጴጥሮስ፣ 2ኛ እና 3ኛ ዮሐንስና ይሁዳ መልእክቶች
ጸሐፊ፦ ዋረን ደብልዩ ዌርዝቢ
ትርጉም፦ መስፍን ታዬ
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ከአስመሳይ ሃይማኖተኞች ተጠንቀቁ
2ኛ ጴጥሮስ፣ 2ኛ እና 3ኛ ዮሐንስና ይሁዳ መልእክቶች
ጸሐፊ፦ ዋረን ደብልዩ ዌርዝቢ
ትርጉም፦ መስፍን ታዬ
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤10👏1🙏1