#መጻሕፍትን_እንመርምር
የኢየሱስ ክርስቶስ ትንሣኤ የአካል ወይስ የመንፈስ?
ክፍል-፫
(1) በሞተው ሰውና ከሙታን በተነሣው ሰው መካከል ልዩነት የለም፡፡
ከሞት የሚነሣው የሞተው ሰው ራሱ ነው (የሞተው አካል ከሞት የሚነሣው አካል አያቋርጤ ነው:: ለምሳሌ— ኢየሱስ ከትንሣኤውም በኋላ ራሱን፣ “እኔው ራሴው ነኝ” (ሉቃስ 24÷39) ብሏል። አስታውሴው፣ ጠባዩ፣ አካላዊ ቅርጹ (ለምሳሌ ከትንሣኤ በፊት በአካሉ ላይ የነበረው ጠባሳ/ዕትራት ከትንሣኤውም በኋላ አብሮት ነበር) ወዘተ አልተቀየረም፡፡
(2) ቅድመ ትንሣኤና ድኅረ ትንሣኤ ያለው አካል ቊሳዊ ይዘቱም ሆነ አያቋርጤነቱን በጠበቀ መልኩ ዕድሳት ይደረግለታል
(ለምሳሌ የሚከተሉትን ክፍሎች ይመለከቷል ሮሜ 8÷11፤ 1ቆሮንቶስ 15÷53፤ ፊልጵስዩስ 3÷20- 21)።
“አንተ ሞኝ የምትዘራው ካልሞተ ሕይወት አያገኝም፡፡ የምትዘራውም የስንዴ ወይም የሌላ ዐይነት ዘር ቅንጣት ብቻ እንጂ ወደ ፊት የምታገኘውን አካል አይደለም፡፡ እግዚአብሔር ግን እንደ ፈቀደ አካልን ይሰጠዋል፤ ለእያንዳንዱም የዘር ዐይነት የራሱን አካል ይሰጠዋል” (1ቆሮንቶስ 15÷36-38)፣
ሐዋርያው ጳውሎስ በዚህ ክፍል የስንዴን ቅንጣት በመውሰድ የሚያስተምረው ትምህርት፣ ቅድመ ትንሣኤና ድኅረ ትንሣኤ አካል ቊሳዊ አያቋርጤነት እንዳለው የተዘራውን ዐይነት ዘር ከተዘራው ዘር ላይ እንደሚበቅል ነው:: አንዱ በሌላው እንደሚተካ ወይም አንዱ በሌላው እንደሚቀየር ሳይሆን፣ ይኸው አካል በትንሣኤ ሂደት ውስጥ እንደሚታደስ ነው:: ቅድመ ትንሣኤ አካል ይበሰብሳል፣ ይሞታል፣ ክብር የሌለው እንዲሁም ፍጥረታዊ ሲሆን ድኅረ ትንሣኤ አካል ግን የማይበሰብስ፣ ክብርንና ኀይልን የተሞላ እንዲሁም መንፈሳዊ ነው (1ቆሮንቶስ 15÷42-44)፡፡
“በሥጋ ትንሣኤ አምናለሁ!”
ኢየሱስ ክርስቶስ ከሙታን የተነሣው በአካለ ሥጋ መሆኑን የሚየስተምሩትን የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች በጥሙና እንመልከት:—
1. ትንሣኤ የሚለው ቃል ቊሳዊ የሆነ አካልን ብቻ የሚያመለክት ነው
የሐዲስ ኪዳንን የትንሣኤ ትምህርት በጠለለ መልኩ ለመረዳት አይሁዶች ስለ ሙታን ትንሣኤ ያላቸውን ትምህርት በትክክል ማወቅ ያስፈልጋል፡፡ ምክንያቱም ከሉቃስ በስተቀር ሁሉም የሐዲስ ኪዳን ጸሓፍያን አይሁዶች ስለሆኑ (ቈላስይስ 4÷11:14) እንዲሁም ሐዲስ ኪዳን ስለ ትንሣኤ ሙታን የሚያስተምረው ትምህርት፣ ከብሉያት አስተምህሮ ጋር ተያያዥነት ያለው ስለሆነ፡፡
ይቀጥላል...
ምንጭ፦ ዶ/ር ተስፋዬ ሮበሌ፤ በሥጋ ትንሣኤ አምናለሁ! የአስተምህሮተ ትንሣኤ መጽሐፍ ቅዱሳዊ፣ ታሪካዊና ሥነ አመክንዮአዊ ትንታኔ፤ ከምእራፍ ሰባት የተወሰደ
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የኢየሱስ ክርስቶስ ትንሣኤ የአካል ወይስ የመንፈስ?
ክፍል-፫
(1) በሞተው ሰውና ከሙታን በተነሣው ሰው መካከል ልዩነት የለም፡፡
ከሞት የሚነሣው የሞተው ሰው ራሱ ነው (የሞተው አካል ከሞት የሚነሣው አካል አያቋርጤ ነው:: ለምሳሌ— ኢየሱስ ከትንሣኤውም በኋላ ራሱን፣ “እኔው ራሴው ነኝ” (ሉቃስ 24÷39) ብሏል። አስታውሴው፣ ጠባዩ፣ አካላዊ ቅርጹ (ለምሳሌ ከትንሣኤ በፊት በአካሉ ላይ የነበረው ጠባሳ/ዕትራት ከትንሣኤውም በኋላ አብሮት ነበር) ወዘተ አልተቀየረም፡፡
(2) ቅድመ ትንሣኤና ድኅረ ትንሣኤ ያለው አካል ቊሳዊ ይዘቱም ሆነ አያቋርጤነቱን በጠበቀ መልኩ ዕድሳት ይደረግለታል
(ለምሳሌ የሚከተሉትን ክፍሎች ይመለከቷል ሮሜ 8÷11፤ 1ቆሮንቶስ 15÷53፤ ፊልጵስዩስ 3÷20- 21)።
“አንተ ሞኝ የምትዘራው ካልሞተ ሕይወት አያገኝም፡፡ የምትዘራውም የስንዴ ወይም የሌላ ዐይነት ዘር ቅንጣት ብቻ እንጂ ወደ ፊት የምታገኘውን አካል አይደለም፡፡ እግዚአብሔር ግን እንደ ፈቀደ አካልን ይሰጠዋል፤ ለእያንዳንዱም የዘር ዐይነት የራሱን አካል ይሰጠዋል” (1ቆሮንቶስ 15÷36-38)፣
ሐዋርያው ጳውሎስ በዚህ ክፍል የስንዴን ቅንጣት በመውሰድ የሚያስተምረው ትምህርት፣ ቅድመ ትንሣኤና ድኅረ ትንሣኤ አካል ቊሳዊ አያቋርጤነት እንዳለው የተዘራውን ዐይነት ዘር ከተዘራው ዘር ላይ እንደሚበቅል ነው:: አንዱ በሌላው እንደሚተካ ወይም አንዱ በሌላው እንደሚቀየር ሳይሆን፣ ይኸው አካል በትንሣኤ ሂደት ውስጥ እንደሚታደስ ነው:: ቅድመ ትንሣኤ አካል ይበሰብሳል፣ ይሞታል፣ ክብር የሌለው እንዲሁም ፍጥረታዊ ሲሆን ድኅረ ትንሣኤ አካል ግን የማይበሰብስ፣ ክብርንና ኀይልን የተሞላ እንዲሁም መንፈሳዊ ነው (1ቆሮንቶስ 15÷42-44)፡፡
“በሥጋ ትንሣኤ አምናለሁ!”
ኢየሱስ ክርስቶስ ከሙታን የተነሣው በአካለ ሥጋ መሆኑን የሚየስተምሩትን የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች በጥሙና እንመልከት:—
1. ትንሣኤ የሚለው ቃል ቊሳዊ የሆነ አካልን ብቻ የሚያመለክት ነው
የሐዲስ ኪዳንን የትንሣኤ ትምህርት በጠለለ መልኩ ለመረዳት አይሁዶች ስለ ሙታን ትንሣኤ ያላቸውን ትምህርት በትክክል ማወቅ ያስፈልጋል፡፡ ምክንያቱም ከሉቃስ በስተቀር ሁሉም የሐዲስ ኪዳን ጸሓፍያን አይሁዶች ስለሆኑ (ቈላስይስ 4÷11:14) እንዲሁም ሐዲስ ኪዳን ስለ ትንሣኤ ሙታን የሚያስተምረው ትምህርት፣ ከብሉያት አስተምህሮ ጋር ተያያዥነት ያለው ስለሆነ፡፡
ይቀጥላል...
ምንጭ፦ ዶ/ር ተስፋዬ ሮበሌ፤ በሥጋ ትንሣኤ አምናለሁ! የአስተምህሮተ ትንሣኤ መጽሐፍ ቅዱሳዊ፣ ታሪካዊና ሥነ አመክንዮአዊ ትንታኔ፤ ከምእራፍ ሰባት የተወሰደ
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤5👍3
. ──•◈•─────•◈•─
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“ሞትን ለዘላለም ይውጣል፥ ጌታ እግዚአብሔርም ከፊት ሁሉ እንባን ያብሳል፥ የሕዝቡን ስድብ ከምድር ሁሉ ላይ ያስወግዳል፤ እግዚአብሔር ተናግሮአልና።”
ኢሳይያስ 25፥8
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“ሞትን ለዘላለም ይውጣል፥ ጌታ እግዚአብሔርም ከፊት ሁሉ እንባን ያብሳል፥ የሕዝቡን ስድብ ከምድር ሁሉ ላይ ያስወግዳል፤ እግዚአብሔር ተናግሮአልና።”
ኢሳይያስ 25፥8
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤2👏1
Audio
#መጻሕፍትን_በድምጽ
👉ርዕስ፦ የካታኮምቡ ሰማዕት
🗣ትርጉም፦ በአማረ ማሞ
መካነ ኢየሱስ ሥነ ጽሑፍ ክፍል።
📻ክፍል-3
ይቀጥላል...
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👉ርዕስ፦ የካታኮምቡ ሰማዕት
🗣ትርጉም፦ በአማረ ማሞ
መካነ ኢየሱስ ሥነ ጽሑፍ ክፍል።
📻ክፍል-3
ይቀጥላል...
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
🔥1
የካታኮንቡ ሰማዕት.pdf
30.5 MB
👍5❤1🔥1
. ──•◈•─────•◈•─
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“የክርስቶስ ኢየሱስም የሆኑቱ ሥጋን ከክፉ መሻቱና ከምኞቱ ጋር ሰቀሉ።”
ገላትያ 5፥24
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“የክርስቶስ ኢየሱስም የሆኑቱ ሥጋን ከክፉ መሻቱና ከምኞቱ ጋር ሰቀሉ።”
ገላትያ 5፥24
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤12👍1
የካታኮምቦ ሰማዕታት ክፍል 4 Catacombs part 4
ታላቁ ተስፋ - Great Hope - Official
#መጻሕፍትን_በድምጽ
👉ርዕስ፦ የካታኮምቡ ሰማዕት
🗣ትርጉም፦ በአማረ ማሞ
መካነ ኢየሱስ ሥነ ጽሑፍ ክፍል።
📻ክፍል-4
ይቀጥላል...
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👉ርዕስ፦ የካታኮምቡ ሰማዕት
🗣ትርጉም፦ በአማረ ማሞ
መካነ ኢየሱስ ሥነ ጽሑፍ ክፍል።
📻ክፍል-4
ይቀጥላል...
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤2🥰2👍1
ቅዱሳት መጻሕፍት
የጥንት ቤተክርስቲያን ጉባዔዎች ክፍል-፫ የኬልቄዶን ጉባዔ 451 በ451 ዓ.ም የተካሄደው የኬልቄዶን ጉባኤ የቤተክርስቲያን አራተኛው ጉባኤ ሲሆን በክርስትና ታሪክ ውስጥ ትልቅ ቦታ ከሚሰጣቸው ጉባኤዎች አንዱ ተደርጎ ይወሰዳል። ነገረ ክርስቶሳዊ አስተምህሮ በመቅረጽ እና የጥንቷ ቤተክርስቲያንን ያከፋፈሉትን ስነ-መለኮታዊ አለመግባባቶችን ለመፍታት ማዕከላዊ ሚና ተጫውቷል። ታሪካዊ…
የጥንት ቤተክርስቲያን ጉባዔዎች
ክፍል-፬
ከኬልቄዶን ጉባኤ (451 ዓ.ም.) ከተካሄደ በኋላ፣ በርካታ ዋና ዋና የቤተክርስቲያን ጉባዔዎች ተካሂደዋል። ነገር ግን፣ እነዚህ ሁሉ ጉባኤዎች በሁሉም አብያተ ክርስቲያናት ዘንድ ተቀባይነት አላገኙም። ለዚህም ዋናው ምክንያት በተለይም ከኬልቄዶን በኋላ በተፈጠሩ ጥልቅ ሥነ-መለኮታዊ አለመግባባቶች እና ፖለቲካዊ ልዩነቶች የተነሳ ነው።
ከኬልቄዶን ጉባኤ በኋላ ያሉ ቁልፍ ክስተቶች፡-
1. የምስራቅ ኦርቶዶክስ አብያተ ክርስቲያናት ጋር በኬልቄዶን ጉባዔ ውሳኔ አለመስማማት
ይህ ጉባዔ በብዙ የምስራቅ አብያተ ክርስቲያናት ውድቅ ተደርጓል፣ በተለይም በግብፅ፣ በሶሪያ እና በአርሜኒያ። እነዚህ አብያተ ክርስቲያናት ከጊዜ በኋላ የምስራቅ ኦርቶዶክስ አብያተ ክርስቲያናት በመባል ይታወቃሉ። ይህም ጉልህ እና ዘላቂ የሆነ መከፋፈል አስከትሏል።
2. የኬልቄዶንያ እና የኬልቄዶንያ ያልሆኑ ካምፖች ምስረታ፡-
የኬልቄዶን ጉባዔ ውሳኔ በምዕራቡ ቤተ ክርስቲያን (ሮምን ጨምሮ) እና በባይዛንታይን (ምሥራቃዊ ኦርቶዶክስ) ቤተ ክርስቲያን ጸንቷል። ሆኖም፣ የኬልቄዶንያ ያልሆኑ አብያተ ክርስቲያናት ራሳቸውን ችለው ቀጥለዋል፣ እያንዳንዱም የየራሱን ወጎች፣ ተዋረዶች እና ሥነ-መለኮታዊ ማዕቀፎችን እያዳበረ ቀጥለዋል።
3. የኮፕቲክ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን መነሳት እና ሌሎች፦
የአሌክሳንደሪያ ኮፕቲክ(የግብፅ) ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን፣ የሶርያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን እና የአርመን ሐዋርያዊት ቤተ ክርስቲያን ኬልቄዶንን ያልተቀበሉት ዋና ዋና አብያተ ክርስቲያናት ናቸው። በአካባቢያቸውም ሀይማኖታዊ እና ሀገራዊ ተቋማት ሆኑ።
4. በምስራቅ-ምእራብ ቤተክርስቲያን ላይ ያመጣው ተጽእኖ፦
በኬልቄዶን የተጀመረው መከፋፈል በክርስትና ውስጥ የአስተምህሮ፣ የፖለቲካ እና የባህል መለያየት እንዲጨምር አስተዋጽኦ አድርጓል፣ ይህም ከጊዜ በኋላ በ1054 ዓ.ም በምስራቅ ኦርቶዶክስ እና በሮማ ካቶሊካዊነት መካከል በተከሰተው መለያየት ተጠናቀቀ።
ምንጭ፦ Chadwick, H. (1993). The early Church (Revised ed.). Penguin Books.
Pelikan, J. (1971). The Christian tradition: A history of the development of doctrine, Volume 1: The emergence of the Catholic tradition (100-600). University of Chicago Press.
Meyendorff, J. (1989). Imperial unity and Christian divisions: The Church 450–680 A.D. St. Vladimir's Seminary Press.
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ክፍል-፬
ከኬልቄዶን ጉባኤ (451 ዓ.ም.) ከተካሄደ በኋላ፣ በርካታ ዋና ዋና የቤተክርስቲያን ጉባዔዎች ተካሂደዋል። ነገር ግን፣ እነዚህ ሁሉ ጉባኤዎች በሁሉም አብያተ ክርስቲያናት ዘንድ ተቀባይነት አላገኙም። ለዚህም ዋናው ምክንያት በተለይም ከኬልቄዶን በኋላ በተፈጠሩ ጥልቅ ሥነ-መለኮታዊ አለመግባባቶች እና ፖለቲካዊ ልዩነቶች የተነሳ ነው።
ከኬልቄዶን ጉባኤ በኋላ ያሉ ቁልፍ ክስተቶች፡-
1. የምስራቅ ኦርቶዶክስ አብያተ ክርስቲያናት ጋር በኬልቄዶን ጉባዔ ውሳኔ አለመስማማት
ይህ ጉባዔ በብዙ የምስራቅ አብያተ ክርስቲያናት ውድቅ ተደርጓል፣ በተለይም በግብፅ፣ በሶሪያ እና በአርሜኒያ። እነዚህ አብያተ ክርስቲያናት ከጊዜ በኋላ የምስራቅ ኦርቶዶክስ አብያተ ክርስቲያናት በመባል ይታወቃሉ። ይህም ጉልህ እና ዘላቂ የሆነ መከፋፈል አስከትሏል።
2. የኬልቄዶንያ እና የኬልቄዶንያ ያልሆኑ ካምፖች ምስረታ፡-
የኬልቄዶን ጉባዔ ውሳኔ በምዕራቡ ቤተ ክርስቲያን (ሮምን ጨምሮ) እና በባይዛንታይን (ምሥራቃዊ ኦርቶዶክስ) ቤተ ክርስቲያን ጸንቷል። ሆኖም፣ የኬልቄዶንያ ያልሆኑ አብያተ ክርስቲያናት ራሳቸውን ችለው ቀጥለዋል፣ እያንዳንዱም የየራሱን ወጎች፣ ተዋረዶች እና ሥነ-መለኮታዊ ማዕቀፎችን እያዳበረ ቀጥለዋል።
3. የኮፕቲክ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን መነሳት እና ሌሎች፦
የአሌክሳንደሪያ ኮፕቲክ(የግብፅ) ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን፣ የሶርያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን እና የአርመን ሐዋርያዊት ቤተ ክርስቲያን ኬልቄዶንን ያልተቀበሉት ዋና ዋና አብያተ ክርስቲያናት ናቸው። በአካባቢያቸውም ሀይማኖታዊ እና ሀገራዊ ተቋማት ሆኑ።
4. በምስራቅ-ምእራብ ቤተክርስቲያን ላይ ያመጣው ተጽእኖ፦
በኬልቄዶን የተጀመረው መከፋፈል በክርስትና ውስጥ የአስተምህሮ፣ የፖለቲካ እና የባህል መለያየት እንዲጨምር አስተዋጽኦ አድርጓል፣ ይህም ከጊዜ በኋላ በ1054 ዓ.ም በምስራቅ ኦርቶዶክስ እና በሮማ ካቶሊካዊነት መካከል በተከሰተው መለያየት ተጠናቀቀ።
ምንጭ፦ Chadwick, H. (1993). The early Church (Revised ed.). Penguin Books.
Pelikan, J. (1971). The Christian tradition: A history of the development of doctrine, Volume 1: The emergence of the Catholic tradition (100-600). University of Chicago Press.
Meyendorff, J. (1989). Imperial unity and Christian divisions: The Church 450–680 A.D. St. Vladimir's Seminary Press.
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍10❤4👏1😢1
. ──•◈•─────•◈•─
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“የቀረውንም ነገር ሳልቆጥር፥ ዕለት ዕለት የሚከብድብኝ የአብያተ ክርስቲያናት ሁሉ አሳብ ነው።”
2ኛ ቆሮ 11፥28
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“የቀረውንም ነገር ሳልቆጥር፥ ዕለት ዕለት የሚከብድብኝ የአብያተ ክርስቲያናት ሁሉ አሳብ ነው።”
2ኛ ቆሮ 11፥28
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍7❤1
Audio
#መጻሕፍትን_በድምጽ
👉ርዕስ፦ የካታኮምቡ ሰማዕት
🗣ትርጉም፦ በአማረ ማሞ
መካነ ኢየሱስ ሥነ ጽሑፍ ክፍል።
📻ክፍል-5
ይቀጥላል...
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👉ርዕስ፦ የካታኮምቡ ሰማዕት
🗣ትርጉም፦ በአማረ ማሞ
መካነ ኢየሱስ ሥነ ጽሑፍ ክፍል።
📻ክፍል-5
ይቀጥላል...
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
🥰3👍1
. ──•◈•─────•◈•─
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“እግዚአብሔር ሁሉን ይምር ዘንድ ሁሉን በአለመታዘዝ ዘግቶታልና።”
ሮሜ 11፥32
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“እግዚአብሔር ሁሉን ይምር ዘንድ ሁሉን በአለመታዘዝ ዘግቶታልና።”
ሮሜ 11፥32
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤2👏1
Audio
#መጻሕፍትን_በድምጽ
👉ርዕስ፦ የካታኮምቡ ሰማዕት
🗣ትርጉም፦ በአማረ ማሞ
መካነ ኢየሱስ ሥነ ጽሑፍ ክፍል።
📻ክፍል-6
ይቀጥላል...
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👉ርዕስ፦ የካታኮምቡ ሰማዕት
🗣ትርጉም፦ በአማረ ማሞ
መካነ ኢየሱስ ሥነ ጽሑፍ ክፍል።
📻ክፍል-6
ይቀጥላል...
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤3
ቅዱሳት መጻሕፍት
#መጻሕፍትን_እንመርምር የኢየሱስ ክርስቶስ ትንሣኤ የአካል ወይስ የመንፈስ? ክፍል-፫ (1) በሞተው ሰውና ከሙታን በተነሣው ሰው መካከል ልዩነት የለም፡፡ ከሞት የሚነሣው የሞተው ሰው ራሱ ነው (የሞተው አካል ከሞት የሚነሣው አካል አያቋርጤ ነው:: ለምሳሌ— ኢየሱስ ከትንሣኤውም በኋላ ራሱን፣ “እኔው ራሴው ነኝ” (ሉቃስ 24÷39) ብሏል። አስታውሴው፣ ጠባዩ፣…
#መጻሕፍትን_እንመርምር
የኢየሱስ ክርስቶስ ትንሣኤ የአካል ወይስ የመንፈስ?
ክፍል-፬
"ለዘብተኛ አቋም" አላቸው በመባል የሚታወቁት ሰዱቃውያን በሙታን ትንሣኤ አያምኑም ነበር (ማቴዎስ 22÷23):: በአንጻሩ ደግሞ ፈሪሳውያን በሙታን ትንሣኤ ያምናሉ (ሐዋርያት ሥራ 23÷8)፡፡ ሰዱቃውያን ትንሣኤ ሙታን ላለመኖሩ እንደ ምክንያት ያቀረቡት ጒዳይ ስለማግባትና ስለመጋባት ነበር፤ ይህም ትንሣኤ ሙታን የአካል እንደ ሆነ ታሳቢ ያደረገ ንግግር መሆኑ ብቻ ሳይሆን ኢየሱስም የመለሰው መልስ ትንሣኤ ሙታን የአካል እንደ ሆነ ነገር ግን ከትንሣኤ በኋላ ማግባትና መጋባት እንደማይኖር የሚያስረዳ ነው (ማቴዎስ 22÷28)። ከግማሽ በላይ የሚሆኑት የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት የተጻፉት ቀድሞ ፈሪሳዊ በነበሩ ሰዎች ነው:: አይሁዶች በተለይ ደግሞ ፈሪሳውያን ሰው የተፈጠረው ከምድር ዐፈር እንደ ሆነ (ዘፍጥረት 2÷7)፣ ወደ ዐፈርም እንደሚመለስ (መክብብ 12÷7)፣ በትንሣኤም ቀን ወደ ዐፈርነት ከተለወጠው አካሉ በእግዚአብሔር ኪነ ጥበብ ሕያው ሆኖ ከሙታን እንደሚነሣ (ዘዳግም 32÷39፤ 1ሳሙኤል 2፥6፤ ኢዮብ 19÷25-27፤ መዝሙር 49÷14-15) ያምናሉ፡፡
የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት አስተምህሮ ንጉሥ ዳዊት የእግዚአብሔር ቅዱስ የሆነው ኢየሱስ መበስበስን እንማያይ ተንብዮ ነበር (መዝሙር 16÷10):: ጴጥሮስ የንጉሥ ዳዊትን ትንቢት በተመለከተ እንዲህ በሏል፣ "ይህንን አስቀድሞ በማየቱ እርሱ በሲኦል እንደማይቀርና ሥጋውም እንማይበሰብስ ስለ ክርስቶስ ትንሣኤ ተነገረ" (ሐዋርያት ሥራ 2÷31):: በዚህ ቦታ “ሥጋ” ተብሎ የተተረጐመው የግሪክ ቃል (ሳርክ) ሊበሰብስ እንደሚችል ነገር ግን በእግዚአብሔር ከሃሌ ኲሉነት በመስበስን ሳያይ እንደማይበሰብስ ሆነ ከሙታን እንደ ተነሣ ያስተምራል:: ሐዋርያው ጳውሎስም ይህን የዳዊት ትንቢት በመጥቀስ ኢየሱስ፣ “እንዳልበሰበሰና እግዚአብሔርም ከሙታን እንዳስነሣው ለማረጋገጥ ...ቅዱስህ መበስበስን እንዲያይ አትፈቅድም' ይላል” (ሐዋርያት ሥራ 13፥34:35)።
ኢየሱስ ሰዱቃውያን በሙታን ትንሣኤ ባለማመናቸው፣ “ቅዱሳት መጻሕፍትንና የእግዚአብሔርን ኀይል ስለማታውቁ ትስታላችሁ” (ማቴዎስ 23÷29) ሲል ተናግሯቸዋል: እንዲሁም ዘፀአት 3፥6:15 በመጥቀስ፣ “እኔ የአብርሃም አምላክ፣ የይስሐቅ አምላክ፣ የያዕቀብ አምላክ ነኝ፡፡ እግዚአብሔር የሕያዋን እንጂ የሙታን አምላክ አይደለም” (ማቴዎስ 23÷32) ሲል አስተምሯል፡፡
ነቢዩ ኢሳይያስ፣ “ነገር ግን ሙታን ሕያዋን ይሆናሉ፤ በድናቸውም ይነሣል፡፡ እናንት በዐፈር ውስጥ የምትኖሩ፣ ተነሡ፤ በደስታም ዘመሩ፡፡ ጠልህ እንደ ንጋት ጠል ነው፤ ምድር ሙታንን ትወልዳለች” (ኢሳይያስ 26÷19) የሚለው ትምህርቱ የሞተው አካል እንደሚነሣ ይህም የሙታን ትንሣኤ የአካል እንደ ሆነ የሚያስተምር ነው፡፡
ዳንኤል፣ “በምድር ዐፈር ውስጥ ካንቀላፉት ብዙዎች ይነቃሉ፤ አንዳንዶቹ ለዘላለም ሕይወት፣ ሌሎቹም ለውርደትና ለዘላለም ጒስቊልና ይነሣሉ” (ዳንኤል 12፥2) የሚለው ትንቢቱ ትንሣኤ ሙታን የአካል እንደ ሆነ የሚያስተምር ነው:: በተመሳሳይ መልኩ ኢየሱስ ትንሣኤ ሙታን ከሚያገኙ ሰዎች ግማሹ ወደ ዘላለም ሕይወት ግማሾቹ ደግሞ ወደ ዘላለም ሞት እንደሚሄዱ አስተምሮአል (ዮሐንስ 5÷28)፡፡
ማርያምና ማርታ ወንድማቸው አልዓዛር በትንሣኤ ቀን እንደሚነሣ ተስፋ እንደሚያደርጉ በተጨማሪ ኢየሱስ በትንሣኤ ቀን ብቻ ሳይሆን ዛሬም ሙታንን የማስነሣት ኀይል ከገለጸ በኋላ አልዓዛርን ከሙታን ማስነሣቱ ትንሣኤ ሙታን የአካል እንደ ሆነ በግልጽ የሚያስተምር ነው (ዮሐንስ 11÷38-44)፡፡
ከእነዚህም ሆኑ ከእነዚህ ጋር ተዛማጅነት ካላቸው የብሉይና የሐዲስ ኪዳን ምንባባት በግልጽ የምንረዳው እውነት፣ ብሉያትም ሆኑ ሐዲሳት ስለ ትንሣኤ የሚያስተምሩት ትምህርት ተደጋጋፊ እንዲሁም እርስ በእርሱ የሚጣጣም መሆኑን ነው፡፡ ይኸውም መጽሐፍ ቅዱስ ትንሣኤ የሚለውን ቃል የሚጠቀመው ቊሳዊ አካል ከሙታን መነሣቱን ለማመልከት ብቻ ነው:: ዕብራውያን በተለይ ፈሪሳውያን የጻድቃን የወደፊት ሁኔታ አስመልክቶ የተለያየ አመለካከት ቢኖራቸውም፣ ሁሉም ግን ትንሣኤን ቊሳዊ አካል በጊዜዩዊነትም ሆነ በቋሚነት ከመነሣት ጋር ብቻ ነበር የሚያያይዙት፡፡
ምንም እንኳ ኢየሱስ ክርስቶስ በፈሪሳውያን ግብዝነት ደስተኛ ባይሆንም፣ ሰዱቃውያን የሙታን ትንሣኤ ባለመቀበላቸው ቢነቅፋቸውም፣ ትንሣኤ በሚለው የቃል ፍቺ ላይ ግን ተመሳሳይ አቋም ነበራቸው (ማቴዎስ 22÷23-32)፡፡ ጳውሎስ ቀድሞውኑ ፈሪሳዊ ስለነበር ሥቃይ የደረሰብኝ በሙታን ትንሣኤ በማመኔ ነው ብሎ ነበር (ሐዋርያት ሥራ 23÷6-8)፡፡
በአጠቃላይ ትንሣኤ የሚለው ቃል ያለው ትርጒም የሞተ ሰው አካል በቋሚነትም ሆነ በጊዜያዊነት ሕይወት ማግኘት ማለት ነው፡፡
ይቀጥላል...
ምንጭ፦ ዶ/ር ተስፋዬ ሮበሌ፤ በሥጋ ትንሣኤ አምናለሁ! የአስተምህሮተ ትንሣኤ መጽሐፍ ቅዱሳዊ፣ ታሪካዊና ሥነ አመክንዮአዊ ትንታኔ፤ ከምእራፍ ሰባት የተወሰደ
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የኢየሱስ ክርስቶስ ትንሣኤ የአካል ወይስ የመንፈስ?
ክፍል-፬
"ለዘብተኛ አቋም" አላቸው በመባል የሚታወቁት ሰዱቃውያን በሙታን ትንሣኤ አያምኑም ነበር (ማቴዎስ 22÷23):: በአንጻሩ ደግሞ ፈሪሳውያን በሙታን ትንሣኤ ያምናሉ (ሐዋርያት ሥራ 23÷8)፡፡ ሰዱቃውያን ትንሣኤ ሙታን ላለመኖሩ እንደ ምክንያት ያቀረቡት ጒዳይ ስለማግባትና ስለመጋባት ነበር፤ ይህም ትንሣኤ ሙታን የአካል እንደ ሆነ ታሳቢ ያደረገ ንግግር መሆኑ ብቻ ሳይሆን ኢየሱስም የመለሰው መልስ ትንሣኤ ሙታን የአካል እንደ ሆነ ነገር ግን ከትንሣኤ በኋላ ማግባትና መጋባት እንደማይኖር የሚያስረዳ ነው (ማቴዎስ 22÷28)። ከግማሽ በላይ የሚሆኑት የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት የተጻፉት ቀድሞ ፈሪሳዊ በነበሩ ሰዎች ነው:: አይሁዶች በተለይ ደግሞ ፈሪሳውያን ሰው የተፈጠረው ከምድር ዐፈር እንደ ሆነ (ዘፍጥረት 2÷7)፣ ወደ ዐፈርም እንደሚመለስ (መክብብ 12÷7)፣ በትንሣኤም ቀን ወደ ዐፈርነት ከተለወጠው አካሉ በእግዚአብሔር ኪነ ጥበብ ሕያው ሆኖ ከሙታን እንደሚነሣ (ዘዳግም 32÷39፤ 1ሳሙኤል 2፥6፤ ኢዮብ 19÷25-27፤ መዝሙር 49÷14-15) ያምናሉ፡፡
የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት አስተምህሮ ንጉሥ ዳዊት የእግዚአብሔር ቅዱስ የሆነው ኢየሱስ መበስበስን እንማያይ ተንብዮ ነበር (መዝሙር 16÷10):: ጴጥሮስ የንጉሥ ዳዊትን ትንቢት በተመለከተ እንዲህ በሏል፣ "ይህንን አስቀድሞ በማየቱ እርሱ በሲኦል እንደማይቀርና ሥጋውም እንማይበሰብስ ስለ ክርስቶስ ትንሣኤ ተነገረ" (ሐዋርያት ሥራ 2÷31):: በዚህ ቦታ “ሥጋ” ተብሎ የተተረጐመው የግሪክ ቃል (ሳርክ) ሊበሰብስ እንደሚችል ነገር ግን በእግዚአብሔር ከሃሌ ኲሉነት በመስበስን ሳያይ እንደማይበሰብስ ሆነ ከሙታን እንደ ተነሣ ያስተምራል:: ሐዋርያው ጳውሎስም ይህን የዳዊት ትንቢት በመጥቀስ ኢየሱስ፣ “እንዳልበሰበሰና እግዚአብሔርም ከሙታን እንዳስነሣው ለማረጋገጥ ...ቅዱስህ መበስበስን እንዲያይ አትፈቅድም' ይላል” (ሐዋርያት ሥራ 13፥34:35)።
ኢየሱስ ሰዱቃውያን በሙታን ትንሣኤ ባለማመናቸው፣ “ቅዱሳት መጻሕፍትንና የእግዚአብሔርን ኀይል ስለማታውቁ ትስታላችሁ” (ማቴዎስ 23÷29) ሲል ተናግሯቸዋል: እንዲሁም ዘፀአት 3፥6:15 በመጥቀስ፣ “እኔ የአብርሃም አምላክ፣ የይስሐቅ አምላክ፣ የያዕቀብ አምላክ ነኝ፡፡ እግዚአብሔር የሕያዋን እንጂ የሙታን አምላክ አይደለም” (ማቴዎስ 23÷32) ሲል አስተምሯል፡፡
ነቢዩ ኢሳይያስ፣ “ነገር ግን ሙታን ሕያዋን ይሆናሉ፤ በድናቸውም ይነሣል፡፡ እናንት በዐፈር ውስጥ የምትኖሩ፣ ተነሡ፤ በደስታም ዘመሩ፡፡ ጠልህ እንደ ንጋት ጠል ነው፤ ምድር ሙታንን ትወልዳለች” (ኢሳይያስ 26÷19) የሚለው ትምህርቱ የሞተው አካል እንደሚነሣ ይህም የሙታን ትንሣኤ የአካል እንደ ሆነ የሚያስተምር ነው፡፡
ዳንኤል፣ “በምድር ዐፈር ውስጥ ካንቀላፉት ብዙዎች ይነቃሉ፤ አንዳንዶቹ ለዘላለም ሕይወት፣ ሌሎቹም ለውርደትና ለዘላለም ጒስቊልና ይነሣሉ” (ዳንኤል 12፥2) የሚለው ትንቢቱ ትንሣኤ ሙታን የአካል እንደ ሆነ የሚያስተምር ነው:: በተመሳሳይ መልኩ ኢየሱስ ትንሣኤ ሙታን ከሚያገኙ ሰዎች ግማሹ ወደ ዘላለም ሕይወት ግማሾቹ ደግሞ ወደ ዘላለም ሞት እንደሚሄዱ አስተምሮአል (ዮሐንስ 5÷28)፡፡
ማርያምና ማርታ ወንድማቸው አልዓዛር በትንሣኤ ቀን እንደሚነሣ ተስፋ እንደሚያደርጉ በተጨማሪ ኢየሱስ በትንሣኤ ቀን ብቻ ሳይሆን ዛሬም ሙታንን የማስነሣት ኀይል ከገለጸ በኋላ አልዓዛርን ከሙታን ማስነሣቱ ትንሣኤ ሙታን የአካል እንደ ሆነ በግልጽ የሚያስተምር ነው (ዮሐንስ 11÷38-44)፡፡
ከእነዚህም ሆኑ ከእነዚህ ጋር ተዛማጅነት ካላቸው የብሉይና የሐዲስ ኪዳን ምንባባት በግልጽ የምንረዳው እውነት፣ ብሉያትም ሆኑ ሐዲሳት ስለ ትንሣኤ የሚያስተምሩት ትምህርት ተደጋጋፊ እንዲሁም እርስ በእርሱ የሚጣጣም መሆኑን ነው፡፡ ይኸውም መጽሐፍ ቅዱስ ትንሣኤ የሚለውን ቃል የሚጠቀመው ቊሳዊ አካል ከሙታን መነሣቱን ለማመልከት ብቻ ነው:: ዕብራውያን በተለይ ፈሪሳውያን የጻድቃን የወደፊት ሁኔታ አስመልክቶ የተለያየ አመለካከት ቢኖራቸውም፣ ሁሉም ግን ትንሣኤን ቊሳዊ አካል በጊዜዩዊነትም ሆነ በቋሚነት ከመነሣት ጋር ብቻ ነበር የሚያያይዙት፡፡
ምንም እንኳ ኢየሱስ ክርስቶስ በፈሪሳውያን ግብዝነት ደስተኛ ባይሆንም፣ ሰዱቃውያን የሙታን ትንሣኤ ባለመቀበላቸው ቢነቅፋቸውም፣ ትንሣኤ በሚለው የቃል ፍቺ ላይ ግን ተመሳሳይ አቋም ነበራቸው (ማቴዎስ 22÷23-32)፡፡ ጳውሎስ ቀድሞውኑ ፈሪሳዊ ስለነበር ሥቃይ የደረሰብኝ በሙታን ትንሣኤ በማመኔ ነው ብሎ ነበር (ሐዋርያት ሥራ 23÷6-8)፡፡
በአጠቃላይ ትንሣኤ የሚለው ቃል ያለው ትርጒም የሞተ ሰው አካል በቋሚነትም ሆነ በጊዜያዊነት ሕይወት ማግኘት ማለት ነው፡፡
ይቀጥላል...
ምንጭ፦ ዶ/ር ተስፋዬ ሮበሌ፤ በሥጋ ትንሣኤ አምናለሁ! የአስተምህሮተ ትንሣኤ መጽሐፍ ቅዱሳዊ፣ ታሪካዊና ሥነ አመክንዮአዊ ትንታኔ፤ ከምእራፍ ሰባት የተወሰደ
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍4
በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ "የትንሣኤ ምዕራፍ" በመባል የሚታወቀው ምዕራፍ የቱ ነው?
Anonymous Quiz
36%
ሀ. ዮሐንስ ወንጌል፣ ምዕራፍ 20
24%
ለ. ሉቃስ ወንጌል፣ ምዕራፍ 24
33%
ሐ. 1 ቆሮንቶስ፣ ምዕራፍ 15
7%
መ. የዮሐንስ ራእይ፣ ምዕራፍ 20
🥰4👍2
. ──•◈•─────•◈•─
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“ሕፃንነትና ጕብዝና ከንቱዎች ናቸውና ከልብህ ኀዘንን አርቅ፥ ከሰውነትህም ክፉን ነገር አስወግድ።”
መክብብ 11፥10
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“ሕፃንነትና ጕብዝና ከንቱዎች ናቸውና ከልብህ ኀዘንን አርቅ፥ ከሰውነትህም ክፉን ነገር አስወግድ።”
መክብብ 11፥10
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤4👍1
Audio
#መጻሕፍትን_በድምጽ
👉ርዕስ፦ የካታኮምቡ ሰማዕት
🗣ትርጉም፦ በአማረ ማሞ
መካነ ኢየሱስ ሥነ ጽሑፍ ክፍል።
📻ክፍል-7
ይቀጥላል...
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👉ርዕስ፦ የካታኮምቡ ሰማዕት
🗣ትርጉም፦ በአማረ ማሞ
መካነ ኢየሱስ ሥነ ጽሑፍ ክፍል።
📻ክፍል-7
ይቀጥላል...
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍2
#እራሳችንን_እንመርምር
ብዙ ጸሎታችንም ሆነ ከእግዚአብሔር ጋር የምንገጥመው ክርክር እግዚአብሔር እኛን ወይንም የእኛን ነገር ቸል እንዳለ የሚያሳብቅ እና የሚያሳይ ነው። ግን አንድ ነገር ቆም ብለን እራሳችንን ብንፈትሽ ጥሩ ነው። ምን ከተባለ እኛስ ምን ያህል ስለ እግዚአብሔር እና ስለእግዚአብሔር ቤት ጉዳይ ግድ ይለናል? እስቲ ግድ የለውም በዚህ ጉዳይ ላይ እራሳችንን እንመርምር።
“በውኑ ይህ ቤት ፈርሶ ሳለ እናንተ ራሳችሁ በተሸለሙ ቤቶቻችሁ ለመኖር ጊዜው ነውን?”
ሐጌ 1፥4
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ብዙ ጸሎታችንም ሆነ ከእግዚአብሔር ጋር የምንገጥመው ክርክር እግዚአብሔር እኛን ወይንም የእኛን ነገር ቸል እንዳለ የሚያሳብቅ እና የሚያሳይ ነው። ግን አንድ ነገር ቆም ብለን እራሳችንን ብንፈትሽ ጥሩ ነው። ምን ከተባለ እኛስ ምን ያህል ስለ እግዚአብሔር እና ስለእግዚአብሔር ቤት ጉዳይ ግድ ይለናል? እስቲ ግድ የለውም በዚህ ጉዳይ ላይ እራሳችንን እንመርምር።
“በውኑ ይህ ቤት ፈርሶ ሳለ እናንተ ራሳችሁ በተሸለሙ ቤቶቻችሁ ለመኖር ጊዜው ነውን?”
ሐጌ 1፥4
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍7🙏2🥰1
. ──•◈•─────•◈•─
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“ኖኅ ግን በእግዚአብሔር ፊት ሞገስን አገኘ።”
ዘፍጥረት 6፥8
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“ኖኅ ግን በእግዚአብሔር ፊት ሞገስን አገኘ።”
ዘፍጥረት 6፥8
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
🔥11👍4
Audio
#መጻሕፍትን_በድምጽ
👉ርዕስ፦ የካታኮምቡ ሰማዕት
🗣ትርጉም፦ በአማረ ማሞ
መካነ ኢየሱስ ሥነ ጽሑፍ ክፍል።
📻ክፍል-8
ይቀጥላል...
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👉ርዕስ፦ የካታኮምቡ ሰማዕት
🗣ትርጉም፦ በአማረ ማሞ
መካነ ኢየሱስ ሥነ ጽሑፍ ክፍል።
📻ክፍል-8
ይቀጥላል...
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ቅዱሳት መጻሕፍት
#መጻሕፍትን_እንመርምር የኢየሱስ ክርስቶስ ትንሣኤ የአካል ወይስ የመንፈስ? ክፍል-፬ "ለዘብተኛ አቋም" አላቸው በመባል የሚታወቁት ሰዱቃውያን በሙታን ትንሣኤ አያምኑም ነበር (ማቴዎስ 22÷23):: በአንጻሩ ደግሞ ፈሪሳውያን በሙታን ትንሣኤ ያምናሉ (ሐዋርያት ሥራ 23÷8)፡፡ ሰዱቃውያን ትንሣኤ ሙታን ላለመኖሩ እንደ ምክንያት ያቀረቡት ጒዳይ ስለማግባትና ስለመጋባት…
#መጻሕፍትን_እንመርምር
የኢየሱስ ክርስቶስ ትንሣኤ የአካል ወይስ የመንፈስ?
ክፍል-፭
2. የሐዋርያው ጳውሎስ አስተምህሮ
ሐዋርያው ጳውሎስ እጅግ ጥንታዊ ነው የሚባለውን የቤተ ክርስቲያን የእምነት መግለጫ ጠቅሶ በጻፈበት ክፍል ላይ፣ የክርስቶስን ሞት ከገለጸ በኋላ የሃይማኖት መግለጫው እንዲህ ያላል፣ “ቅዱሳት መጻሕፈት እንደሚሉት ክርስቶስ ስለ ኀጢአታችን ሞተ፤ ተቀበረ፤ በቅዱሳት መጻሕፍት እንደ ተጻፈውም በሦስተኛው ቀን ተነሣ” (1ቆሮንቶስ 15÷3-4)፡፡ ከዚህ ክፍል በግልጽ የምንማረው እውነት፣ ሞቶ የተቀበረው አካል ከሙታን እንደ ተነሣ ነው፡፡ ይህም የሞተው፣ የተቀበረውና ሞትን ድል አድርጎ የተነሣው አካል አንድ መሆኑን አመላካች ነው፡፡ በዚሁ ምዕራፍ ሐዋርያው የስንዴ ቅንጣትን በምሳሌነት በመጠቀም አራት ጊዜ የተዘራው የስንዴ ቅንጣት እንደ በቀለ ይገልጻል፣ “…ይዘራል ይነሣል ይዘራል ይነሣል ይዘራል ይነሣል ይዘራል…ይነሣል” (1ቆሮንቶስ 15÷42-44)። ልክ እንደዚሁ ሁሉ ሞቶ የተቀበረው የክርስቶስ አካል በትንሣኤ እንደ ተነሣ የሚያስተምር ነው፡፡
ክርስቶስ ዳግም ተመልሶ ሲመጣ፣ “ክቡር ሥጋውን እንዲመስል የተዋረደውን ሥጋችንን ይለውጣል” (ፊልጵስዩስ 3÷21) የሚለው የሐዋርያው አነጋገር የተዋረደው የእኛ ሥጋ ልክ እንደ እርሱ ሥጋ እንደሚለወጥ ሲገልጽ፣ እርሱ ራሱ “በተለወጠ ሥጋ” እንዳለ የሚያስተምር ነው፡፡ በዚህ ክፍል የቅዱሳኑንም ሆነ የክርስቶስን አካል ለማመልከት ጥቅም ላይ የዋለውና የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ ቅጆች “ሥጋ” ብለው የተረጐሙት “ሶማ” የሚለው የሐዲስ ኪዳን ግሪክ፣ ዘወትር የሚጨበጠውን የሚዳሰሰውን አካል የሚያመለክት ነው፡፡ የክርስቶስ ትንሣኤ በመንፈስ ቢሆን ኖሮ፣ ሐዋርያው “ሥጋ” ከሚለው ቃል ይልቅ መንፈስ የሚለውን ቃል ይጠቀም ነበር፡፡ የጻድቃን ዕጣ ፈንታቸው በትንሣኤ ሥጋ ከሙታን መነሣት ከሆነ፣ ክርስቶስም ከሙታን የተነሣው በትንሣኤ ሥጋ ነው ማለት ነው፡፡ ጻድቃን ከመሞት ወደ አለመሞት የመለወጣቸው ሂደት ቊሳዊ እንደ ሆነው ሁሉ፣ የክርስቶስም ትንሣኤ በቊሳዊ አካል እንደ ሆነ በንጽጽር የሚያሳይ ነው::
ሐዋርያው፣ “ኢየሱስን ከሙታን ያስነሣው የእርሱ መንፈስ በእናንተ የሚኖር ከሆነ፣ ክርስቶስን ከሙታን ያስነሣው፣ በውስጣችሁ በሚኖረው በመንፈሱ ሟች ለሆነው ሰውነታችሁ ሕይወትን ይሰጣል” (ሮሜ 8÷11) በዚህ ክፍል ሐዋርያው በክርስቶስ አካል ላይ መታደስ እንደ ተካሄደ እንጂ፣ አካሉ በመቃብር እንዳልቀረ ታሳቢ ያደረገ ንግግር ነው::
ሐዋርያው ጳውሎስ በቈላስይስ 2፥9፣ “የመለኮት ሙላት ሁሉ በአካል በእርሱ ይኖራልና" ሲል “ይኖራል” (ካቶይኬ) የሚለውን ቃል የተጠቀመው የአሁን ጊዜ ግሥ ነው፤ ይህም አምላክ የመሆን ባሕርዩ (“የመለኮት ሙላት” “ቴዎቴቶስ” ) በሰውነቱ/በሥጋው (“ሶማቲኮስ”) የሚኖረው፣ ሐዋርያው ይህን መልእክት እስከሚጽፍበት ጊዜ ድረስ ኢየሱስ አካል/ሥጋ እንዳለው የሚያሳይ ነው፡፡
ሉቃስ፣ በሐዋርያት ሥራ መጽሐፉ ላይ ባቀረበው ዘገባ ጳውሎስ፣ የኢየሱስ ክርስቶስ ሥጋ እንደ ንጉሥ ዳዊት ሥጋ በመቃብር ውስጥ እንዳልበሰበሰ፣ ነገር ግን እግዚአብሔር የሞትን ጣር አጥፍቶ አንዳስነሣው ገልጾአል (ሐዋርያት ሥራ 13÷34-37)፡፡ በተጨማሪም ይህ የክርስቶስ ኢየሱስ የአካል ትንሣኤ የትንቢት ፍጻሜ እንደ ሆነ ተገልጾአል (መዝሙር 16÷10)። የክርስቶስ አካል ከንጉሥ ዳዊት አካል ጋር ተነጻጽሮ መቅረቡ እንዲሁም የንጉሥ ዳዊት መቃብር ዛሬም ድረስ እንዳለና የኢየሱስ መቃብር ግን ባዶ መሆኑ፣ የአካል ትንሣኤን አያመለክትም ብሎ ማሰብ እጅግ ሲበዛ አስቸጋሪ ነው፡፡
በአንደኛ ቆሮንቶስ ምዕራፍ ዐሥራ አምስት በዝርዝር የቀረበው መረጃ የኢየሱስ ክርስቶስ ትንሣኤ የአካል መሆኑን በግልጽ የሚያስተምር ነው:: ዋና የሚባሉትን ነጥቦች እንመልከት
ይቀጥላል...
ምንጭ፦ ዶ/ር ተስፋዬ ሮበሌ፤ በሥጋ ትንሣኤ አምናለሁ! የአስተምህሮተ ትንሣኤ መጽሐፍ ቅዱሳዊ፣ ታሪካዊና ሥነ አመክንዮአዊ ትንታኔ፤ ከምእራፍ ሰባት የተወሰደ
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የኢየሱስ ክርስቶስ ትንሣኤ የአካል ወይስ የመንፈስ?
ክፍል-፭
2. የሐዋርያው ጳውሎስ አስተምህሮ
ሐዋርያው ጳውሎስ እጅግ ጥንታዊ ነው የሚባለውን የቤተ ክርስቲያን የእምነት መግለጫ ጠቅሶ በጻፈበት ክፍል ላይ፣ የክርስቶስን ሞት ከገለጸ በኋላ የሃይማኖት መግለጫው እንዲህ ያላል፣ “ቅዱሳት መጻሕፈት እንደሚሉት ክርስቶስ ስለ ኀጢአታችን ሞተ፤ ተቀበረ፤ በቅዱሳት መጻሕፍት እንደ ተጻፈውም በሦስተኛው ቀን ተነሣ” (1ቆሮንቶስ 15÷3-4)፡፡ ከዚህ ክፍል በግልጽ የምንማረው እውነት፣ ሞቶ የተቀበረው አካል ከሙታን እንደ ተነሣ ነው፡፡ ይህም የሞተው፣ የተቀበረውና ሞትን ድል አድርጎ የተነሣው አካል አንድ መሆኑን አመላካች ነው፡፡ በዚሁ ምዕራፍ ሐዋርያው የስንዴ ቅንጣትን በምሳሌነት በመጠቀም አራት ጊዜ የተዘራው የስንዴ ቅንጣት እንደ በቀለ ይገልጻል፣ “…ይዘራል ይነሣል ይዘራል ይነሣል ይዘራል ይነሣል ይዘራል…ይነሣል” (1ቆሮንቶስ 15÷42-44)። ልክ እንደዚሁ ሁሉ ሞቶ የተቀበረው የክርስቶስ አካል በትንሣኤ እንደ ተነሣ የሚያስተምር ነው፡፡
ክርስቶስ ዳግም ተመልሶ ሲመጣ፣ “ክቡር ሥጋውን እንዲመስል የተዋረደውን ሥጋችንን ይለውጣል” (ፊልጵስዩስ 3÷21) የሚለው የሐዋርያው አነጋገር የተዋረደው የእኛ ሥጋ ልክ እንደ እርሱ ሥጋ እንደሚለወጥ ሲገልጽ፣ እርሱ ራሱ “በተለወጠ ሥጋ” እንዳለ የሚያስተምር ነው፡፡ በዚህ ክፍል የቅዱሳኑንም ሆነ የክርስቶስን አካል ለማመልከት ጥቅም ላይ የዋለውና የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ ቅጆች “ሥጋ” ብለው የተረጐሙት “ሶማ” የሚለው የሐዲስ ኪዳን ግሪክ፣ ዘወትር የሚጨበጠውን የሚዳሰሰውን አካል የሚያመለክት ነው፡፡ የክርስቶስ ትንሣኤ በመንፈስ ቢሆን ኖሮ፣ ሐዋርያው “ሥጋ” ከሚለው ቃል ይልቅ መንፈስ የሚለውን ቃል ይጠቀም ነበር፡፡ የጻድቃን ዕጣ ፈንታቸው በትንሣኤ ሥጋ ከሙታን መነሣት ከሆነ፣ ክርስቶስም ከሙታን የተነሣው በትንሣኤ ሥጋ ነው ማለት ነው፡፡ ጻድቃን ከመሞት ወደ አለመሞት የመለወጣቸው ሂደት ቊሳዊ እንደ ሆነው ሁሉ፣ የክርስቶስም ትንሣኤ በቊሳዊ አካል እንደ ሆነ በንጽጽር የሚያሳይ ነው::
ሐዋርያው፣ “ኢየሱስን ከሙታን ያስነሣው የእርሱ መንፈስ በእናንተ የሚኖር ከሆነ፣ ክርስቶስን ከሙታን ያስነሣው፣ በውስጣችሁ በሚኖረው በመንፈሱ ሟች ለሆነው ሰውነታችሁ ሕይወትን ይሰጣል” (ሮሜ 8÷11) በዚህ ክፍል ሐዋርያው በክርስቶስ አካል ላይ መታደስ እንደ ተካሄደ እንጂ፣ አካሉ በመቃብር እንዳልቀረ ታሳቢ ያደረገ ንግግር ነው::
ሐዋርያው ጳውሎስ በቈላስይስ 2፥9፣ “የመለኮት ሙላት ሁሉ በአካል በእርሱ ይኖራልና" ሲል “ይኖራል” (ካቶይኬ) የሚለውን ቃል የተጠቀመው የአሁን ጊዜ ግሥ ነው፤ ይህም አምላክ የመሆን ባሕርዩ (“የመለኮት ሙላት” “ቴዎቴቶስ” ) በሰውነቱ/በሥጋው (“ሶማቲኮስ”) የሚኖረው፣ ሐዋርያው ይህን መልእክት እስከሚጽፍበት ጊዜ ድረስ ኢየሱስ አካል/ሥጋ እንዳለው የሚያሳይ ነው፡፡
ሉቃስ፣ በሐዋርያት ሥራ መጽሐፉ ላይ ባቀረበው ዘገባ ጳውሎስ፣ የኢየሱስ ክርስቶስ ሥጋ እንደ ንጉሥ ዳዊት ሥጋ በመቃብር ውስጥ እንዳልበሰበሰ፣ ነገር ግን እግዚአብሔር የሞትን ጣር አጥፍቶ አንዳስነሣው ገልጾአል (ሐዋርያት ሥራ 13÷34-37)፡፡ በተጨማሪም ይህ የክርስቶስ ኢየሱስ የአካል ትንሣኤ የትንቢት ፍጻሜ እንደ ሆነ ተገልጾአል (መዝሙር 16÷10)። የክርስቶስ አካል ከንጉሥ ዳዊት አካል ጋር ተነጻጽሮ መቅረቡ እንዲሁም የንጉሥ ዳዊት መቃብር ዛሬም ድረስ እንዳለና የኢየሱስ መቃብር ግን ባዶ መሆኑ፣ የአካል ትንሣኤን አያመለክትም ብሎ ማሰብ እጅግ ሲበዛ አስቸጋሪ ነው፡፡
በአንደኛ ቆሮንቶስ ምዕራፍ ዐሥራ አምስት በዝርዝር የቀረበው መረጃ የኢየሱስ ክርስቶስ ትንሣኤ የአካል መሆኑን በግልጽ የሚያስተምር ነው:: ዋና የሚባሉትን ነጥቦች እንመልከት
ይቀጥላል...
ምንጭ፦ ዶ/ር ተስፋዬ ሮበሌ፤ በሥጋ ትንሣኤ አምናለሁ! የአስተምህሮተ ትንሣኤ መጽሐፍ ቅዱሳዊ፣ ታሪካዊና ሥነ አመክንዮአዊ ትንታኔ፤ ከምእራፍ ሰባት የተወሰደ
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤7👍2
. ──•◈•─────•◈•─
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“ኢየሱስም ከዚያ አልፎ በመቅረጫው ተቀምጦ የነበረ ማቴዎስ የሚባል አንድ ሰው አየና፦ ተከተለኝ አለው። ተነሥቶም ተከተለው።”
ማቴዎስ 9፥9
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“ኢየሱስም ከዚያ አልፎ በመቅረጫው ተቀምጦ የነበረ ማቴዎስ የሚባል አንድ ሰው አየና፦ ተከተለኝ አለው። ተነሥቶም ተከተለው።”
ማቴዎስ 9፥9
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍7