ቅዱሳት መጻሕፍት
7.45K subscribers
1.35K photos
61 videos
332 files
797 links
በዚህ ቻናል

👉ቅዱሳት መጻሕፍት ይጠናሉ::
👉መጽሐፍ ቅዱሳዊ ትምህርቶች ይቀርባሉ::
👉 ለቅዱሳት መጽሐፍት ጥናት የሚያግዙ መጻሕፍት ይለቀቃሉ።

⭐️⭐️⭐️⭐️⭐️

@Holy_scriptures
Download Telegram
ዓላማ መር ህይወት- ቀን 38_Purpose driven Life - Day 38_ alama mer hiywet…
PETERiCH (I am empty without Jesus)
#መጻሕፍትን_በድምጽ

👉ርዕስ፦ ዓላማ መር ሕይወት
✍️ጸሐፊ፦ ሪክ ዋረን
🗣ትርጉም፦ ኢቫንጀሊካል ቴዎሎጂካል ኮሌጅ
🗒ክፍል፦ 38 (ለዓለም ጠቃሚ ክርስቲያን መሆን)


ይቀጥላል...


ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍1
.       ──•◈•─────•◈•─
                          የዕለቱ ጥቅስ
        ──•◈•─────•◈•─
“መልካም ቢሆን ወይም ክፉ እንዳደረገ፥ እያንዳንዱ በሥጋው የተሠራውን በብድራት ይቀበል ዘንድ ሁላችን በክርስቶስ በፍርድ ወንበር ፊት ልንገለጥ ይገባናልና።”
2ኛ ቆሮ 5፥10



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
10
Audio
#መጻሕፍትን_በድምጽ

👉ርዕስ፦ ዓላማ መር ሕይወት
✍️ጸሐፊ፦ ሪክ ዋረን
🗣ትርጉም፦ ኢቫንጀሊካል ቴዎሎጂካል ኮሌጅ
🗒ክፍል፦ 39 (የሕይወትህን ሚዛን መጠበቅ)


ይቀጥላል...


ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍3
#እራሳችንን_እንመርምር

የመንፈሳዊ ሕይወት አቅጣጫችን ልክ እንዳልሆነ ሲሰማን ምንድነው የምናደርገው? የቀድሞ ትጋታችን፣ ለእግዚአብሔር እና ለቃሉ ያለን ናፍቆት ከተወሰደብን ምን እናድርግ? ለለውጥ ካልተነሳንስ ምን ይከተለናል?


“እንግዲህ ከወዴት እንደ ወደቅህ አስብ ንስሐም ግባ የቀደመውንም ሥራህን አድርግ፤ አለዚያ እመጣብሃለሁ ንስሐም ባትገባ መቅረዝህን ከስፍራው እወስዳለሁ።”
ራእይ 2፥5



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
12🙏4😢3👍1🔥1
.       ──•◈•─────•◈•─
                          የዕለቱ ጥቅስ
        ──•◈•─────•◈•─
“ኢየሱስም እንዲህ አላቸው፦ የሕይወት እንጀራ እኔ ነኝ፤ ወደ እኔ የሚመጣ ከቶ አይራብም በእኔ የሚያምንም ሁልጊዜ ከቶ አይጠማም።”
ዮሐንስ 6፥35



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍43
ዓላማ መር ህይወት- ቀን 40_Purpose driven Life - Day 40_ alama mer hiywet…
PETERiCH (I am empty without Jesus)
#መጻሕፍትን_በድምጽ

👉ርዕስ፦ ዓላማ መር ሕይወት
✍️ጸሐፊ፦ ሪክ ዋረን
🗣ትርጉም፦ ኢቫንጀሊካል ቴዎሎጂካል ኮሌጅ
🗒ክፍል፦ 40 (በዓላማ መኖር)


፨፨፨፨፨—ተፈጸመ—፨፨፨፨፨፨


ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
3👏1
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
#ትንሣኤ

በቅርብ ቀን ስለ #ፋሲካ እና #ትንሣኤ ተከታታይ ትምህርት ይጠብቁ


ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
🥰127👍1
.       ──•◈•─────•◈•─
                          የዕለቱ ጥቅስ
        ──•◈•─────•◈•─
“ጢሞቴዎስ ሆይ፥ በውሸት እውቀት ከተባለ ለዓለም ከሚመች ከከንቱ መለፍለፍና መከራከር እየራቅህ፥ የተሰጠህን አደራ ጠብቅ፤”
1ኛ ጢሞቴዎስ 6፥20



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
6
ትንሣኤ ሙታን


                            ወ/ዊ ያሬድ ጥላሁን


                 ክፍል-3

  
ሞት፡- የሰውን ልጅ ሁሉ ያንበረከከ፣ ጀግኖችን ያልፈራ፣ ነገሥታትን ያላፈረ፣ አዛውንትን ያላከበረ የሰው ጠላት ከሞት በላይ ማን ይኖር ይሆን!? በኃጢአት በኩል ወደ ዓለም ገብቶ በሥጋ ሁሉ ላይ የነገሠ፣ ከአዳም አንስቶ እስከ ሙሴ ከሕግ በፊትም ሆነ ከሕግ በኃላ የተንሰራፋ፣ የሰውን ልጅ ሁሉ አይሁድ ግሪክ ሳይል አንገት ያስደፋ ከሞት በላይ ማን ይኖር ይሆን? ሰው የፈለገውን ያህል ሃብት ቢያከማች፣ ዲግሪ ቢደረድር፣ ማዕረግ ቢጭን፣ ዝናው ቢናኝ ቀና ብሎ ነገን ሲያስብ አንድ ነገር ተስፋውን ያጨልምበታል። ሞት! ለዚህ ይሆን ያገሬ ሰው ልጁን “ሞት ባይኖር” ብሎ ስም የሚያውጣው? ሞት የሚያስፈራራን ሲገድለን ብቻ ቢሆን ምንኛ መልካም ነበር? ሞት አንዴ ነዋ! ነገር ግን እንደ ዕብራዊያን መልዕክት ጸሐፊ በሕይወታችን ዘመን ሁሉ ያስፈራራናል፡-

“እንግዲህ ልጆቹ በሥጋና በደም ስለሚካፈሉ፣ እርሱ ደግሞ በሞት ላይ ሥልጣን ያለውን በሞት እንዲሽር፣ ይኽውም ዲያቢሎስን ነው፣ በሕይወታቸውም ሁሉ ስለ ሞት ፍርሃት በባርነት ይታሰሩ የነበሩትን ሁሉ ነፃ እንዲያወጣ፣ በሥጋና በደም እንዲሁ ተካፈለ” ዕብ. 2፡14-15።

በዓለም ታሪክ ከሞት ወዲህ በሥጋ ሕይወት ላሉ የሰው ልጅ ችግሮች ሁሉ ሰው መፍትሄ ከማበጀት አልቦዘነም። እስቲ ትራንስፖርት፣ መገናኛ ብዙሃን፣ የህክምና ሳይንስ ወ.ዘ.ተ የደረሰበትን እንመልከት። ችግራችን ገንዘብ ቢሆን፣ ጤና፣ እውቀት ቢሆን ዝና ሰዎች ሊፈቱት ይችላሉ። ችግራችን ሲገለጥ ወዳጅ ዘመድ ይረባረባል፣ የቅርብ የሩቁ የራሱን ድርሻ ይጫወታል። ነገር ግን አንዴ ሞት ጥላውን ካጠላ ሰብዓዊ መፍትሄ ይሟጠጣል፣ ተስፋ ይቆረጣል፣ ከዋይታና ከሰቀቀን በስተቀር ሊዋጣ የሚችል መላ የለም። ሞት ግን ለእግዚአብሔር ብቻ የሚተው ጉዳይ ነው። ለዚህ ነው እግዚአብሔር ለሙታን ሕይወትን የሚሠጥ አምላክ ሆኖ የተገለጠው። እግዚአብሔር የሚፈልገው አንድ ነገር ብቻ ነው። መታመን! የሞቱትን ሰውነታቸው የበሰበሰውንና የፈረሰውን እንደገና የክብር ሕይወት ሰጥቶ እንደሚያነሣ፣ ይህንንም መሢህ ኢየሱስን ከሙታን በማስነሣቱ እንዳረጋገጠ፣ ቀን እንደቀጠረ በዚያም ቀን ሙታንን በእርግጥ እንደሚያነሣ፣ አስቀድሞ የእርሱ የሆኑትን በኃላም ሁሉን አስነስቶ ክብር ለሚገባው ክብርን፣ ውርደት ለሚገባውም እንደ ሥራው ለሁሉ እንደሚከፍል መታመን ይፈልጋል። እምነት ማለት ይህ ነው፣ ለሙታን ሕይውትን በሚሰጥ አምላክ ተደግፎ በሞት ላይ የሚስቅ ሕያው እምነት።

"ሞት ሆይ፥ መውጊያህ የት አለ? ሲኦል ሆይ፥ ድል መንሣትህ የት አለ? የሞት መውጊያ ኃጢአት ነው የኃጢአትም ኃይል ሕግ ነው፤ ነገር ግን በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል ድል መንሣትን ለሚሰጠን ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን።"
1ኛ ቆሮንቶስ 15፥55-57

ይቀጥላል... 


ምንጭ:- semayawithought.com



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍135
.       ──•◈•─────•◈•─
                          የዕለቱ ጥቅስ
        ──•◈•─────•◈•─
“መንፈሱና ሙሽራይቱም፦ ና ይላሉ። የሚሰማም፦ ና ይበል። የተጠማም ይምጣ፥ የወደደም የሕይወትን ውኃ እንዲያው ይውሰድ።”
ራእይ 22፥17



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍94
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
2
መንፈስ ቅዱስ.pdf
9.1 MB
👉ርዕስ፦ መንፈስ ቅዱስ
ጸሐፊ፦ ቢሊ ግሬሃም
🗣ትርጉም፦ ግርማዊ
✏️እርማት፦ ወንድዬ ዓሊ


ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
11🔥3
.       ──•◈•─────•◈•─
                          የዕለቱ ጥቅስ
        ──•◈•─────•◈•─
“እግዚአብሔር ፈራጃችን ነው፥ እግዚአብሔር ሕግን ሰጪያችን ነው፥ እግዚአብሔር ንጉሣችን ነው፤ እርሱ ያድነናል።”
ኢሳይያስ 33፥22



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍84
ቅዱሳት መጻሕፍት
ትንሣኤ ሙታን                             ወ/ዊ ያሬድ ጥላሁን                  ክፍል-3    ሞት፡- የሰውን ልጅ ሁሉ ያንበረከከ፣ ጀግኖችን ያልፈራ፣ ነገሥታትን ያላፈረ፣ አዛውንትን ያላከበረ የሰው ጠላት ከሞት በላይ ማን ይኖር ይሆን!? በኃጢአት በኩል ወደ ዓለም ገብቶ በሥጋ ሁሉ ላይ የነገሠ፣ ከአዳም አንስቶ እስከ ሙሴ ከሕግ በፊትም ሆነ ከሕግ በኃላ የተንሰራፋ፣ የሰውን…
ትንሣኤ ሙታን


                            ወ/ዊ ያሬድ ጥላሁን


                 ክፍል-4

ተስፋ፡- ጌታ ኢየሱስ ከሙታን እንደተነሣ ምንም ያህል አስቀድሞ፣ ደጋግሞ የነገራቸው ቢሆንም ትንሣኤን ለማመን ልባቸው የዘገየውን ደቀመዛሙርቱን ለማስረዳት ያደረገው ነገር ቢኖር መጽሐፍትን ያስተውሉ ዘንድ አዕምሯቸውን መክፈት ነው። ይህም ትንሣኤው አስቀድሞ የተሰጠ መለኮታዊ ተስፋ መሆኑኑ ያረጋግጥልናል።

እግዚአብሔር የተስፋ አምላክ ነው። ታዲያ ተስፋ መስጠት የጀመረው የተስፋው ወራሽ የሆነው ሰው ከተፈጠረ በኃላ ብቻ አልነበረም። ሐዋርያው ጳውሎስ በመንፈስ ቅዱስ መረዳት ወደ ዘላለም መጥቆ ዐለም ሳይፈጠር ስለተከናወነ አንድ ተግባር ይተርክልናል፡-

“ስለዚህም ሕይወት የማይዋሽ እግዚአብሔር ከዘላለም ዘመናት በፊት ተስፋን ሰጠ” ቲቶ 1፥2

“በክርስቶስ ኢየሱስ እንደሚሆን የሕይወት ተስፋ በእግዚአብሔር ፈቃድ የኢየሱስ ክርስቶስ ሐዋርያ የሆነ ጳውሎስ” 2ጢሞ. 1፥1

“… ይህም ፀጋ ከዘላለም ዘመናት በፊት በክርስቶስ ኢየሱስ ተሰጠን፣ አሁን ግን በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ መገለጥ ታይቷል። እርሱ ሞትን ሽሯልና … በወንጌል ሕይወትንና አለመጥፋትን ወደ ብርሃን አውጥቷል” 2ጢሞ. 1፥9-11
 
ይህ የዘላለም ተስፋ ነው በዘመናት ውስጥ ከእግዚአብሔር ዘንድ ለአባቶች የተሰጠው። ተስፋው በሙሉ ከትንሳኤ ጋር የተያያዘ ነው። እግዚአብሔር በዘመናት ውስጥ ከተለያዩ ሰዎች ጋር ኪዳን የገባ ቢሆንም “ቅዱስ” ተብሎ የተጠራ ኪዳን እግዚአብሔር ከአብርሃምና ከዳዊት ጋር የገባው “የተስፋ ኪዳን” ነው። ተስፋችን ስንሞት ሥጋችን ወደ አፈር፣ ነፍሳችን ወደ እግዚአብሔር ሄዳ በዚያ ለዘላለም መኖራችን አይደለም። በፍፁም አይደለ! ምንም እንክዋ ነፍሳችን ከሥጋችን ከምትለይበት አንስቶ ጌታ ዳግመኛ እስኪመጣና የአካል ትንሣኤ እስኪሆን ድረስ ሕያው የሆነች ነፍሳችን በጌታ ዘንድ የምትቆይ ቢሆንም ያ ተስፋችን አይደለም። እዚያም ሆነን በናፍቆት የምንጠብቀው ተስፋ የሥጋ ትንሣኤን ይመሥለኛል። ለዚህ አይደል የጌታን ዳግም መምጣት ሲያወሳ ጳውሎስ “የተባረከው ተስፋችን የታላቁ የአምላካችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ መገለጥ” ቲቶ 2፥11-13 በማለት የሚጠራው? ስለዚህ እኛም መገለጡን ከሚጠባበቁ አዕላፋት ቅዱሳን ጋር ተጨምረን “ማራናታ፡- አሜን ጌታ ኢየሱስ ሆይ ቶሎ ና!” እንበል። በቅድስና በመኖር ወንጌልንም በማሰራጨት መምጣቱን እናፋጥን። 



ምንጭ:- semayawithought.com



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍8
በቤተክርስቲያን ታሪክ የተካሄደው የኤፌሶን ጉባኤ (431) የትኛውን ኑፋቄ አውግዟል?
Anonymous Quiz
28%
ሀ. ኖስትሲዝም
32%
ለ. ንስጥሮሳዊነት
32%
ሐ. አርዮሳዊነት
8%
መ. ሴባልዮሳዊነት
.       ──•◈•─────•◈•─
                          የዕለቱ ጥቅስ
        ──•◈•─────•◈•─
“እግዚአብሔርም እነዚያን የአገር ከተሞች ባጠፋ ጊዜ አብርሃምን አሰበው፤ ሎጥ ተቀምጦበት የነበረውንም ከተማ ባጠፋ ጊዜ ከዚያ ጥፋት መካከል ሎጥን አወጣው።”
ዘፍጥረት 19፥29



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
8👍6
ቅዱሳት መጻሕፍት
#እምነት                    ክፍል-7 እግዚአብሔርን እንዴት እንመን? ወይንም ለማመን ምን እናድርግ? 2. በፍጹም ልብ እግዚአብሔርን መፈለግ “እናንተ ትሹኛላችሁ፥ በፍጹም ልባችሁም ከሻችሁኝ ታገኙኛላችሁ።”         ኤርምያስ 29፥13 3. በቅዱሳት መጻሕፍት ተአማኒነት ላይ ማመን “የእግዚአብሔር ሰው ፍጹምና ለበጎ ሥራ ሁሉ የተዘጋጀ ይሆን ዘንድ፥ የእግዚአብሔር መንፈስ ያለበት…
#እምነት


                   ክፍል-8


በቅዱሳት መጻሕፍት መሠረት እምነታችንን ለመጠበቅ ምን እናድረግ?


1. ጸሎት እና በእግዚአብሔር ላይ መደገፍ

“እኔ ግን እምነትህ እንዳይጠፋ ስለ አንተ ጸለይሁ፤ አንተም በተመለስህ ጊዜ ወንድሞችህን አበርታ።””
         ሉቃስ 22፥32 (አዲሱ መ.ት)

ኢየሱስ እምነታችንን ለመጠበቅ ጸሎት አስፈላጊ እንደሆነ ያስተምራል። በጸሎት የእግዚአብሔርን ብርታት መፈለግ እንዳለብን በማሳየት በግል ለጴጥሮስ አማለደ።

2. በእግዚአብሔር ቃል መበርታት

“እንግዲያስ እምነት ከመስማት ነው መስማትም በእግዚአብሔር ቃል ነው።”
             ሮሜ 10፥17

ቅዱሳት መጻሕፍትን አዘውትሮ ማጥናት እና ማሰላሰል እምነታችንን ያጠናክራል እናም ከጥርጣሬ ይጠብቀናል (መዝ. 119፡105)።

3. በፈተና ውስጥ መጽናት

“ወንድሞቼ ሆይ፥ የእምነታችሁ መፈተን ትዕግሥትን እንዲያደርግላችሁ አውቃችሁ፥ ልዩ ልዩ ፈተና ሲደርስባችሁ እንደ ሙሉ ደስታ ቍጠሩት”
            ያዕቆብ 1፥2-3

4. ከቅዱሳን ጋር ሕብረት ማድረግ

"ለፍቅርና ለመልካምም ሥራ እንድንነቃቃ እርስ በርሳችን እንተያይ፤ በአንዳንዶችም ዘንድ ልማድ እንደ ሆነው፥ መሰብሰባችንን አንተው እርስ በርሳችን እንመካከር እንጂ፤ ይልቁንም ቀኑ ሲቀርብ እያያችሁ አብልጣችሁ ይህን አድርጉ።
            ዕብራውያን 10፥24-25

በአማኞች ማህበረሰብ ውስጥ መሆን እምነትን በጋራ ለመበረታታት ይረዳል።

“በሐዋርያትም ትምህርትና በኅብረት እንጀራውንም በመቍረስ በየጸሎቱም ይተጉ ነበር።”
                 ሐዋርያት 2፥42

5. ከኃጢአትና ከፈተና መጠበቅ

"በመጠን ኑሩ ንቁም፥ ባላጋራችሁ ዲያብሎስ የሚውጠውን ፈልጎ እንደሚያገሣ አንበሳ ይዞራልና፤ በዓለም ያሉት ወንድሞቻችሁ ያን መከራ በሙሉ እንዲቀበሉ እያወቃችሁ በእምነት ጸንታችሁ ተቃወሙት።"
              1ኛ ጴጥሮስ 5፥8-9

እምነትን ለመጠበቅ ንቁ መሆን እና ኃጢአትን መቃወም አስፈላጊ ነው (ኤፌሶን 6፥10-11)።

6. በመንፈስ ቅዱስ ላይ መደገፍ

"እናንተ ግን፥ ወዳጆች ሆይ፥ ከሁሉ ይልቅ በተቀደሰ ሃይማኖታችሁ ራሳችሁን ለማነጽ እየተጋችሁ በመንፈስ ቅዱስም እየጸለያችሁ፥ ወደ ዘላለም ሕይወት የሚወስደውን የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ምሕረት ስትጠባበቁ በእግዚአብሔር ፍቅር ራሳችሁን ጠብቁ።"
               ይሁዳ 1፥20-21

መንፈስ ቅዱስ አማኞችን በእምነት ያጠነክራል እና ይመራል (ዮሐ. 14፡26)።


ይቀጥላል...


ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍171
.       ──•◈•─────•◈•─
                          የዕለቱ ጥቅስ
        ──•◈•─────•◈•─
“ስለ ሥጋችሁ ድካም እንደ ሰው ልማድ እላለሁ። ብልቶቻችሁ ዓመፃ ሊያደርጉ ለርኵስነትና ለዓመፃ ባሪያዎች አድርጋችሁ እንዳቀረባችሁ፥ እንደዚሁ ብልቶቻችሁ ሊቀደሱ ለጽድቅ ባሪያዎች አድርጋችሁ አሁን አቅርቡ።”
ሮሜ 6፥19



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
7👍3
መንፈስ ቅዱስ Holy Spirit
BibleProject - Amharic / አማርኛ
👉ርዕስ፦ መንፈስ ቅዱስ
በባይብል ፕሮጀክት፣ በአማርኛ ቋንቋ የተዘጋጀ


ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍32
.       ──•◈•─────•◈•─
                          የዕለቱ ጥቅስ
        ──•◈•─────•◈•─
“ለሰው ፊትም ሳያደላ በእያንዳንዱ ላይ እንደ ሥራው የሚፈርደውን አባት ብላችሁ ብትጠሩ በእንግድነታችሁ ዘመን በፍርሃት ኑሩ።”
1ኛ ጴጥሮስ 1፥17



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍6