በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ “...እሳትን እሰድዳለሁ፥ ... አዳራሾች ትበላለች።” በሚለው ዓረፍተ ነገር የሚታወቀው መጽሐፍ የቱ ነው?
Anonymous Quiz
24%
ሀ. ኢሳይያስ
7%
ለ. ዮናስ
32%
ሐ. አሞጽ
7%
መ. ናሆም
19%
ሠ. ኤርምያስ
10%
ረ. ሕዝቅኤል
❤4👍2
. ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“አንተም ከሕዝቡ ሁሉ አዋቂዎችን፥ እግዚአብሔርን የሚፈሩትን፥ የታመኑ፥ የግፍንም ረብ የሚጠሉትን ሰዎች ምረጥ፤ ከእነርሱም የሺህ አለቆችን፥ የመቶ አለቆችን፥ የአምሳ አለቆችን፥ የአሥርም አለቆችን ሹምላቸው።”
ዘጸአት 18፥21
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“አንተም ከሕዝቡ ሁሉ አዋቂዎችን፥ እግዚአብሔርን የሚፈሩትን፥ የታመኑ፥ የግፍንም ረብ የሚጠሉትን ሰዎች ምረጥ፤ ከእነርሱም የሺህ አለቆችን፥ የመቶ አለቆችን፥ የአምሳ አለቆችን፥ የአሥርም አለቆችን ሹምላቸው።”
ዘጸአት 18፥21
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍4🔥2
Audio
#መጻሕፍትን_በድምጽ
👉ርዕስ፦ ዓላማ መር ሕይወት
✍️ጸሐፊ፦ ሪክ ዋረን
🗣ትርጉም፦ ኢቫንጀሊካል ቴዎሎጂካል ኮሌጅ
🗒ክፍል፦ 8 (ለእግዚአብሔር ደስታ የታቀድህ ነህ)
ይቀጥላል...
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👉ርዕስ፦ ዓላማ መር ሕይወት
✍️ጸሐፊ፦ ሪክ ዋረን
🗣ትርጉም፦ ኢቫንጀሊካል ቴዎሎጂካል ኮሌጅ
🗒ክፍል፦ 8 (ለእግዚአብሔር ደስታ የታቀድህ ነህ)
ይቀጥላል...
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍2❤1
ቅዱሳት መጻሕፍት
#እምነት ውድ የቻናላችን ቤተሰቦች ጌታ ቢፈቃድ በቅርብ ቀን ". . . ነገር ግን የሰው ልጅ በመጣ ጊዜ በምድር እምነትን ያገኝ ይሆንን?” ሉቃስ 18፥8 በሚል ርዕስ ተከታታይ ትምህርት እንጀምራል። በዚህም መሠረት ስለእምነት ሊነሱ ይገባል የምትሉትን አሳቦች በአሳብ መስጫው ላይ በነጻነት እንድታሰፍሩልን ስንል እንጠይቃለን። ጸልዩልን! ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
#እምነት
እምነት
ክፍል-1
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ያለው "እምነት" ትርጉም
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ "እምነት" የሚለው ቃል በእግዚአብሔር መታመንን፣ ማመንን እና መደገፍን ያመለክታል። በእግዚአብሔር ተስፋዎች፣ ባህሪ እና ሃይል ላይ ጽኑ እምነትን የሚያስተላልፍ በብሉይም ሆነ በአዲስ ኪዳን ውስጥ ማዕከላዊ ጽንሰ-ሀሳብ ነው።
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ "እምነት" ስንት ጊዜ ተጠቀሰ?
"እምነት" የሚለው ቃል በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ብዙ ጊዜ ተጠቅሷል፣ ነገር ግን ትክክለኛው ቁጥሩ እንደ መጽሐፍ ቅዱስ ትርጉሙ ይለያያል።
ለምሳሌ፦
👉KJV፦ 247 ጊዜ
👉NIV፦ 458 ጊዜ
👉ESV፦ 378 ጊዜ
በዕብራይስጥ (ብሉይ ኪዳን) የ"እምነት" ትርጉም
በዕብራይስጥ "እምነት" የሚለው ቃል "ኢሙናህ (אֱמוּנָה)" ሲሆን ትርጉሙም በዋናነት ታማኝነት፣ ጽናት እና . . . ወ.ዘ.ተ ማለት እንጂ በአሁን ጊዜ "እምነት" ብለን እንደምንጠራው ብቻ አይደለም። የመተማመን እና አስተማማኝነት ሀሳብንም ያስተላልፋል።
“እነሆ፥ ነፍሱ ኰርታለች፥ በውስጡም ቅን አይደለችም፤ ጻድቅ ግን በእምነቱ (ኤሙና) በሕይወት ይኖራል።”
ዕንባቆም 2፥4
በግሪክ (አዲስ ኪዳን) የ"እምነት" ትርጉም
እምነት ለሚለው የግሪክ ቃል "ፒስቲስ (πίστις)" ሲሆን ትርጉሙም በእግዚአብሔር እውነት እና ተስፋዎች ላይ መደገፍ፣ የሙጥኝ እና መጣበቅ ማለት ነው። በአዲስ ኪዳን አማኙ ከእግዚአብሔር እና ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር ያለውን ግንኙነት ለመግለጽ በሰፊው ጥቅም ላይ ውሏል።
“እምነትም (ጲስጢስ) ተስፋ ስለምናደርገው ነገር የሚያስረግጥ፥ የማናየውንም ነገር የሚያስረዳ ነው።”
ይቀጥላል...
ምንጭ፦ Harris, R. L., Archer, G. L., & Waltke, B. K. (1980). Theological Wordbook of the Old Testament (Vol. 1). Moody Press.
Balz, H. R., & Schneider, G. (1990). Exegetical Dictionary of the New Testament (Vol. 3). Eerdmans.
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
እምነት
ክፍል-1
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ያለው "እምነት" ትርጉም
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ "እምነት" የሚለው ቃል በእግዚአብሔር መታመንን፣ ማመንን እና መደገፍን ያመለክታል። በእግዚአብሔር ተስፋዎች፣ ባህሪ እና ሃይል ላይ ጽኑ እምነትን የሚያስተላልፍ በብሉይም ሆነ በአዲስ ኪዳን ውስጥ ማዕከላዊ ጽንሰ-ሀሳብ ነው።
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ "እምነት" ስንት ጊዜ ተጠቀሰ?
"እምነት" የሚለው ቃል በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ብዙ ጊዜ ተጠቅሷል፣ ነገር ግን ትክክለኛው ቁጥሩ እንደ መጽሐፍ ቅዱስ ትርጉሙ ይለያያል።
ለምሳሌ፦
👉KJV፦ 247 ጊዜ
👉NIV፦ 458 ጊዜ
👉ESV፦ 378 ጊዜ
በዕብራይስጥ (ብሉይ ኪዳን) የ"እምነት" ትርጉም
በዕብራይስጥ "እምነት" የሚለው ቃል "ኢሙናህ (אֱמוּנָה)" ሲሆን ትርጉሙም በዋናነት ታማኝነት፣ ጽናት እና . . . ወ.ዘ.ተ ማለት እንጂ በአሁን ጊዜ "እምነት" ብለን እንደምንጠራው ብቻ አይደለም። የመተማመን እና አስተማማኝነት ሀሳብንም ያስተላልፋል።
“እነሆ፥ ነፍሱ ኰርታለች፥ በውስጡም ቅን አይደለችም፤ ጻድቅ ግን በእምነቱ (ኤሙና) በሕይወት ይኖራል።”
ዕንባቆም 2፥4
በግሪክ (አዲስ ኪዳን) የ"እምነት" ትርጉም
እምነት ለሚለው የግሪክ ቃል "ፒስቲስ (πίστις)" ሲሆን ትርጉሙም በእግዚአብሔር እውነት እና ተስፋዎች ላይ መደገፍ፣ የሙጥኝ እና መጣበቅ ማለት ነው። በአዲስ ኪዳን አማኙ ከእግዚአብሔር እና ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር ያለውን ግንኙነት ለመግለጽ በሰፊው ጥቅም ላይ ውሏል።
“እምነትም (ጲስጢስ) ተስፋ ስለምናደርገው ነገር የሚያስረግጥ፥ የማናየውንም ነገር የሚያስረዳ ነው።”
ይቀጥላል...
ምንጭ፦ Harris, R. L., Archer, G. L., & Waltke, B. K. (1980). Theological Wordbook of the Old Testament (Vol. 1). Moody Press.
Balz, H. R., & Schneider, G. (1990). Exegetical Dictionary of the New Testament (Vol. 3). Eerdmans.
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍10❤8🔥3
. ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“ጽድቅንና ፍርድን በማድረግ የእግዚአብሔርን መንገድ ይጠብቁ ዘንድ ልጆቹንና ከእርሱ በኋላ ቤቱን እንዲያዝዝ አውቃለሁና፤ ይህም እግዚአብሔር በአብርሃም ላይ የተናገረውን ነገር ሁሉ ያመጣ ዘንድ ነው።”
ዘፍጥረት 18፥19
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“ጽድቅንና ፍርድን በማድረግ የእግዚአብሔርን መንገድ ይጠብቁ ዘንድ ልጆቹንና ከእርሱ በኋላ ቤቱን እንዲያዝዝ አውቃለሁና፤ ይህም እግዚአብሔር በአብርሃም ላይ የተናገረውን ነገር ሁሉ ያመጣ ዘንድ ነው።”
ዘፍጥረት 18፥19
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
Audio
#መጻሕፍትን_በድምጽ
👉ርዕስ፦ ዓላማ መር ሕይወት
✍️ጸሐፊ፦ ሪክ ዋረን
🗣ትርጉም፦ ኢቫንጀሊካል ቴዎሎጂካል ኮሌጅ
🗒ክፍል፦ 9 (እግዚአብሔርን ፈገግ የሚያሰኘው ነገር ምንድነው?)
ይቀጥላል...
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👉ርዕስ፦ ዓላማ መር ሕይወት
✍️ጸሐፊ፦ ሪክ ዋረን
🗣ትርጉም፦ ኢቫንጀሊካል ቴዎሎጂካል ኮሌጅ
🗒ክፍል፦ 9 (እግዚአብሔርን ፈገግ የሚያሰኘው ነገር ምንድነው?)
ይቀጥላል...
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍5❤1
የሕሊና ዓይነቶች
በቅዱሳት መጻሕፍት በተለይም በአዲስ ኪዳን ይባስ ብሎም ደግሞ በሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ትምህርት "#ሕሊና" የሚለው አሳብ ተደጋግሞ ይነሳል። ለምሳሌ ሐዋርያው እንዲህ ይላል፦
“ስለዚህ እኔ ደግሞ በእግዚአብሔርና በሰው ፊት ሁልጊዜ ነውር የሌለባት ሕሊና ትኖረኝ ዘንድ እተጋለሁ።”
ሐዋርያት 24፥16
ከታች ከተዘረዘሩት ለአንድ ክርስቲያን የሚያስፈልገውና የግሉ ሊያደርገው ሊጋደልበት የሚገባው የቱ ነው? ለምን?
1. ክፉ ሕሊና
ክፉ ሕሊና ተበላሽቶ ወደ ሥነ ምግባር ዝቅጠት የሚመራ ነው። ይህ ሕሊና የእግዚአብሔርን ፈቃድ የሚጻረር እና የኃጢያት ባህሪን የሚያበረታታ ነው። (ዕብ. 10፥22)
2. የረከሰ ሕሊና
የረከሰ ሕሊና በኃጢአት የረከሰና ግልጽ የሆነ የሞራል ልዩነት ማድረግ የማይችል ነው። ትክክል እና
ስህተት መካከል ወደ ግራ መጋባት ይመራል። (ቲቶ. 1፥15)
3. የደነዘዘ ሕሊና
የደነዘዘ ሕሊና ማለት በድግግሞሽ ኃጢአት የተዳከመ ወይም የደነደነ ነው። ከጊዜ በኋላ
ሰውየው ለጥፋተኝነት ወይም ለጥፋተኝነት ግድየለሽ ይሆናል። ኃጢአትን እንደ ስህተት አይገነዘብም። (1ኛ ጢሞ.
4፥2)
4. ደካማ ሕሊና
ደካማ ሕሊና የሚያመለክተው ኃጢአት በሌለበት አካባቢም እንኳ በቀላሉ ሊኮነን የሚችል ያልበሰለ
ወይም ከልክ ያለፈ ስስ ሕሊና ነው። ይህ ሊሆን የሚችለው አንድ ሰው በተፈጥሮ ኃጢአተኛ ያልሆኑ የሥነ ምግባር ጉዳዮች ላይ እርግጠኛ ካልሆነ ነው። (1ኛ ቆሮ. 8፥7)
5. ንጹሕ ሕሊና
ንፁህ ህሊና ማለት ከጥፋተኝነት እና ከነቀፋ በጸዳ መልኩ በእግዚአብሔርና በሰው ፊት መኖር ፣ በታማኝነት እና በመታዘዝ መመላለስ ማለት ነው። (ሐዋ. 24፥16)
6. በጎ ሕሊና
በጎ ሕሊና ከእግዚአብሔር እውነት ጋር የሚስማማ እና ወደ ጽድቅ ሕይወት የሚመራ ነው። ግለሰቡ
ይቅርታን እንዲጠይቅ እና የሞራል ህይወት እንዲጠብቅ የሚገፋፋው ለኃጢያት እና የጥፋተኝነትን ድንበር በማወቅ ለእነዚህ ነገሮች ንቁ የሆነ ነው። (1 ጢሞ. 1፥19)
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
በቅዱሳት መጻሕፍት በተለይም በአዲስ ኪዳን ይባስ ብሎም ደግሞ በሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ትምህርት "#ሕሊና" የሚለው አሳብ ተደጋግሞ ይነሳል። ለምሳሌ ሐዋርያው እንዲህ ይላል፦
“ስለዚህ እኔ ደግሞ በእግዚአብሔርና በሰው ፊት ሁልጊዜ ነውር የሌለባት ሕሊና ትኖረኝ ዘንድ እተጋለሁ።”
ሐዋርያት 24፥16
ከታች ከተዘረዘሩት ለአንድ ክርስቲያን የሚያስፈልገውና የግሉ ሊያደርገው ሊጋደልበት የሚገባው የቱ ነው? ለምን?
1. ክፉ ሕሊና
ክፉ ሕሊና ተበላሽቶ ወደ ሥነ ምግባር ዝቅጠት የሚመራ ነው። ይህ ሕሊና የእግዚአብሔርን ፈቃድ የሚጻረር እና የኃጢያት ባህሪን የሚያበረታታ ነው። (ዕብ. 10፥22)
2. የረከሰ ሕሊና
የረከሰ ሕሊና በኃጢአት የረከሰና ግልጽ የሆነ የሞራል ልዩነት ማድረግ የማይችል ነው። ትክክል እና
ስህተት መካከል ወደ ግራ መጋባት ይመራል። (ቲቶ. 1፥15)
3. የደነዘዘ ሕሊና
የደነዘዘ ሕሊና ማለት በድግግሞሽ ኃጢአት የተዳከመ ወይም የደነደነ ነው። ከጊዜ በኋላ
ሰውየው ለጥፋተኝነት ወይም ለጥፋተኝነት ግድየለሽ ይሆናል። ኃጢአትን እንደ ስህተት አይገነዘብም። (1ኛ ጢሞ.
4፥2)
4. ደካማ ሕሊና
ደካማ ሕሊና የሚያመለክተው ኃጢአት በሌለበት አካባቢም እንኳ በቀላሉ ሊኮነን የሚችል ያልበሰለ
ወይም ከልክ ያለፈ ስስ ሕሊና ነው። ይህ ሊሆን የሚችለው አንድ ሰው በተፈጥሮ ኃጢአተኛ ያልሆኑ የሥነ ምግባር ጉዳዮች ላይ እርግጠኛ ካልሆነ ነው። (1ኛ ቆሮ. 8፥7)
5. ንጹሕ ሕሊና
ንፁህ ህሊና ማለት ከጥፋተኝነት እና ከነቀፋ በጸዳ መልኩ በእግዚአብሔርና በሰው ፊት መኖር ፣ በታማኝነት እና በመታዘዝ መመላለስ ማለት ነው። (ሐዋ. 24፥16)
6. በጎ ሕሊና
በጎ ሕሊና ከእግዚአብሔር እውነት ጋር የሚስማማ እና ወደ ጽድቅ ሕይወት የሚመራ ነው። ግለሰቡ
ይቅርታን እንዲጠይቅ እና የሞራል ህይወት እንዲጠብቅ የሚገፋፋው ለኃጢያት እና የጥፋተኝነትን ድንበር በማወቅ ለእነዚህ ነገሮች ንቁ የሆነ ነው። (1 ጢሞ. 1፥19)
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍13❤7
. ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“ቃልህ ተገኝቶአል እኔም በልቼዋለሁ አቤቱ፥ የሠራዊት አምላክ ሆይ፥ በስምህ ተጠርቻለሁና ቃልህ ሐሤትና የልብ ደስታ ሆነኝ።”
ኤርምያስ 15፥16
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“ቃልህ ተገኝቶአል እኔም በልቼዋለሁ አቤቱ፥ የሠራዊት አምላክ ሆይ፥ በስምህ ተጠርቻለሁና ቃልህ ሐሤትና የልብ ደስታ ሆነኝ።”
ኤርምያስ 15፥16
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤7
Audio
#መጻሕፍትን_በድምጽ
👉ርዕስ፦ ዓላማ መር ሕይወት
✍️ጸሐፊ፦ ሪክ ዋረን
🗣ትርጉም፦ ኢቫንጀሊካል ቴዎሎጂካል ኮሌጅ
🗒ክፍል፦ 10 (የአምልኮ ልብ)
ይቀጥላል...
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👉ርዕስ፦ ዓላማ መር ሕይወት
✍️ጸሐፊ፦ ሪክ ዋረን
🗣ትርጉም፦ ኢቫንጀሊካል ቴዎሎጂካል ኮሌጅ
🗒ክፍል፦ 10 (የአምልኮ ልብ)
ይቀጥላል...
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍7❤1🥰1
#እምነት
እምነት
ክፍል-2
አሁን ስለእምነት ባነሳነው ትምህርት ሁለተኛ ክፍል ላይ እንገኛለን። በመጀመሪያው ክፍል ላይ "እምነት" የሚለው ቃል በብሉይ እና በአዲስ ኪዳን፣ በዕብራይስጥ እና በግሪክ ቋንቋ በአጠቃላይ የትኛውን አሳብ እንደሚሸከም አጠር ባለ መልኩ አይተናል። ከዚህ ክፍል ጀምሮ የጥናታችን መሪ ጥቅስ ከሆነው በመነሳት "እምነት" የሚለውን መጽሐፍ ቅዱሳዊ አሳብ በጥልቀት እንመለከተዋለን። እስቲ እንጀምር።
ሉቃስ ምዕራፍ 18 ሲጀምር ጌታችን እና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንዴት መጸለይ እንደሚገባን በምሳሌ ሲያስረዳን እንዲህ ሲል ይጀምራል፦
“ሳይታክቱም ዘወትር ሊጸልዩ እንዲገባቸው የሚል ምሳሌን ነገራቸው፥”
ሉቃስ 18፥1
ምሳሌውን ሲጨርስ ደግሞ አንድ የሚያሳስበውን አሳብ በጥያቄ መልክ በማንሳት ያጠቃልላል እንዲህ ሲል፦
“. . . ነገር ግን የሰው ልጅ በመጣ ጊዜ በምድር እምነትን ያገኝ ይሆንን?”
ሉቃስ 18፥8
". . . ይሁንና፥ እኔ ተመልሼ በምመጣበት ጊዜ በእምነት ጸንተው የሚኖሩ ሰዎች አገኝ ይሆን?”
ሉቃስ 18፥8 (ሕያው ቃል)
እና የጌታችንን ጥያቄ ጆሮ ዳባ ልበስ ብለን ካለፍን አጉል የዋህነት እና ስንፍና ተጠናወተን ከማለት ውጪ ምን ይባላል?
የኢየሱስ ጥያቄ ምናልባት የመምጫው ጊዜ እየተቃረበ ሲመጣ፣ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ብዙዎች ከእውነተኛው እምነት ወደ ኋላ እስከሚሉ ድረስ ክፋት እያየለ እንደሚሄድ ያመለክታል (ማቴ 24፥11-13፣24፤ 1ጢሞ)፡፡ ምን ይሄ ብቻ ጌታችን እና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ መስቀል ሞት ከመሄዱ በፊት ሐዋርያት ከእርሱ እንደማይለዩ ሲምሉና ሲገዘቱ እርሱ ከዲያቢሎስ ጋር ግብግብ የገጠመበትንና ዲያቢሎስም ትኩረት ያደረገበትን አንድ ትልቅ የክርስቲያን ሀብት እንዲህ በማለት ገልጾታል፦
"ጌታም፦ ስምዖን ስምዖን ሆይ፥ እነሆ፥ ሰይጣን እንደ ስንዴ ሊያበጥራችሁ ለመነ፤ እኔ ግን እምነትህ እንዳይጠፋ ስለ አንተ አማለድሁ፤ አንተም በተመለስህ ጊዜ ወንድሞችህን አጽና አለ።"
ሉቃስ 22፥31-32
ኢየሱስ ተመልሶ ሲመጣ እየተሰደዱና እየተገደሉ ነገር ግን፥ ሳያሰልሱና ሳያቋርጡ የሚጸልዩ ሰዎችን ያገኝ ይሆን? በመጨረሻው ዘመን ማለትም ክርስቶስ ተመልሶ ከመምጣቱ በፊት፥ ስደትና መከራ በሰዎች ሁሉ ላይ ይመጣል። «በዚያን ጊዜ ብዙዎች ሃይማኖታቸውን በመካድ ይሰናከላሉ» (ማቴ. 24፥10)። ታዲያ ክርስቶስ ታማኝ ሆነው የሚቆዩ ሰዎችን ያገኝ ይሆን?
የጌታችንን ጥያቄ ልብ ብለን ልንጠይቅ ይገባል። አልፎ ተርፎም እያንዳንዱ አማኝ እራሱን የሚከተለውን ጥያቄ መጠየቅ አለበት እምነቴ ጽኑ ነውን፣ ፍትሕ እንዲሰፍንና የእርሱ ጽድቅ ሙሉ በሙሉ ለዘላለም እንዲያሸንፍ፣ በመጸለይና ወደ እግዚአብሔር በመጮኸ እየተጋሁ ነኝን? ወይስ ስለ ክርስቶስ መመለስና ስለ ዘላለማዊ መንግሥቱ ናፍቆትና ጕጕት እስከማይኖረኝ ድረስ ሐሳቤ በዚህ ዓለም የኑሮ ጕዳይ ተይዞአል?” (ራእ 19—22)። የዚህ ትምህርትም ዓላማ ራስን ለመመርመር እድል ለመስጠት ነው። ለዚህም እንዲያመቸን የእውነተኛ እምነት ምንነት፣ ባህሪያት፣ በእምነት እንዴት ማደግ እንደምንችል ወይንም ደግሞ እምነታችንን እንዴት ማሳደግ እንደምንችል. . . ወ.ዘ.ተ በአሁኑ ዘመን "እምነት" የሚባለው ነገር ከቅዱሳት መጻሕፍት አንጻር እንፈትሻለን። በእያንዳንዱ ትምህርት ላይም አስተያየት እና ጥያቄ ይበረታታል። ውይይት ማድረግም እንዲሁ የተፈቀደና የሚበረታታ ነው።
ይቀጥላል...
ምንጭ፦ ምሉእ ሕይወት፤ ገጽ 1575፣ የአዲስ ኪዳን ማብራሪያ፤ ገጽ 216
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
እምነት
ክፍል-2
አሁን ስለእምነት ባነሳነው ትምህርት ሁለተኛ ክፍል ላይ እንገኛለን። በመጀመሪያው ክፍል ላይ "እምነት" የሚለው ቃል በብሉይ እና በአዲስ ኪዳን፣ በዕብራይስጥ እና በግሪክ ቋንቋ በአጠቃላይ የትኛውን አሳብ እንደሚሸከም አጠር ባለ መልኩ አይተናል። ከዚህ ክፍል ጀምሮ የጥናታችን መሪ ጥቅስ ከሆነው በመነሳት "እምነት" የሚለውን መጽሐፍ ቅዱሳዊ አሳብ በጥልቀት እንመለከተዋለን። እስቲ እንጀምር።
ሉቃስ ምዕራፍ 18 ሲጀምር ጌታችን እና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንዴት መጸለይ እንደሚገባን በምሳሌ ሲያስረዳን እንዲህ ሲል ይጀምራል፦
“ሳይታክቱም ዘወትር ሊጸልዩ እንዲገባቸው የሚል ምሳሌን ነገራቸው፥”
ሉቃስ 18፥1
ምሳሌውን ሲጨርስ ደግሞ አንድ የሚያሳስበውን አሳብ በጥያቄ መልክ በማንሳት ያጠቃልላል እንዲህ ሲል፦
“. . . ነገር ግን የሰው ልጅ በመጣ ጊዜ በምድር እምነትን ያገኝ ይሆንን?”
ሉቃስ 18፥8
". . . ይሁንና፥ እኔ ተመልሼ በምመጣበት ጊዜ በእምነት ጸንተው የሚኖሩ ሰዎች አገኝ ይሆን?”
ሉቃስ 18፥8 (ሕያው ቃል)
እና የጌታችንን ጥያቄ ጆሮ ዳባ ልበስ ብለን ካለፍን አጉል የዋህነት እና ስንፍና ተጠናወተን ከማለት ውጪ ምን ይባላል?
የኢየሱስ ጥያቄ ምናልባት የመምጫው ጊዜ እየተቃረበ ሲመጣ፣ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ብዙዎች ከእውነተኛው እምነት ወደ ኋላ እስከሚሉ ድረስ ክፋት እያየለ እንደሚሄድ ያመለክታል (ማቴ 24፥11-13፣24፤ 1ጢሞ)፡፡ ምን ይሄ ብቻ ጌታችን እና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ መስቀል ሞት ከመሄዱ በፊት ሐዋርያት ከእርሱ እንደማይለዩ ሲምሉና ሲገዘቱ እርሱ ከዲያቢሎስ ጋር ግብግብ የገጠመበትንና ዲያቢሎስም ትኩረት ያደረገበትን አንድ ትልቅ የክርስቲያን ሀብት እንዲህ በማለት ገልጾታል፦
"ጌታም፦ ስምዖን ስምዖን ሆይ፥ እነሆ፥ ሰይጣን እንደ ስንዴ ሊያበጥራችሁ ለመነ፤ እኔ ግን እምነትህ እንዳይጠፋ ስለ አንተ አማለድሁ፤ አንተም በተመለስህ ጊዜ ወንድሞችህን አጽና አለ።"
ሉቃስ 22፥31-32
ኢየሱስ ተመልሶ ሲመጣ እየተሰደዱና እየተገደሉ ነገር ግን፥ ሳያሰልሱና ሳያቋርጡ የሚጸልዩ ሰዎችን ያገኝ ይሆን? በመጨረሻው ዘመን ማለትም ክርስቶስ ተመልሶ ከመምጣቱ በፊት፥ ስደትና መከራ በሰዎች ሁሉ ላይ ይመጣል። «በዚያን ጊዜ ብዙዎች ሃይማኖታቸውን በመካድ ይሰናከላሉ» (ማቴ. 24፥10)። ታዲያ ክርስቶስ ታማኝ ሆነው የሚቆዩ ሰዎችን ያገኝ ይሆን?
የጌታችንን ጥያቄ ልብ ብለን ልንጠይቅ ይገባል። አልፎ ተርፎም እያንዳንዱ አማኝ እራሱን የሚከተለውን ጥያቄ መጠየቅ አለበት እምነቴ ጽኑ ነውን፣ ፍትሕ እንዲሰፍንና የእርሱ ጽድቅ ሙሉ በሙሉ ለዘላለም እንዲያሸንፍ፣ በመጸለይና ወደ እግዚአብሔር በመጮኸ እየተጋሁ ነኝን? ወይስ ስለ ክርስቶስ መመለስና ስለ ዘላለማዊ መንግሥቱ ናፍቆትና ጕጕት እስከማይኖረኝ ድረስ ሐሳቤ በዚህ ዓለም የኑሮ ጕዳይ ተይዞአል?” (ራእ 19—22)። የዚህ ትምህርትም ዓላማ ራስን ለመመርመር እድል ለመስጠት ነው። ለዚህም እንዲያመቸን የእውነተኛ እምነት ምንነት፣ ባህሪያት፣ በእምነት እንዴት ማደግ እንደምንችል ወይንም ደግሞ እምነታችንን እንዴት ማሳደግ እንደምንችል. . . ወ.ዘ.ተ በአሁኑ ዘመን "እምነት" የሚባለው ነገር ከቅዱሳት መጻሕፍት አንጻር እንፈትሻለን። በእያንዳንዱ ትምህርት ላይም አስተያየት እና ጥያቄ ይበረታታል። ውይይት ማድረግም እንዲሁ የተፈቀደና የሚበረታታ ነው።
ይቀጥላል...
ምንጭ፦ ምሉእ ሕይወት፤ ገጽ 1575፣ የአዲስ ኪዳን ማብራሪያ፤ ገጽ 216
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍8👏1
. ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“የጌታውንም ፈቃድ አውቆ ያልተዘጋጀ እንደ ፈቃዱም ያላደረገ ያ ባሪያ እጅግ ይገረፋል፤”
ሉቃስ 12፥47
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“የጌታውንም ፈቃድ አውቆ ያልተዘጋጀ እንደ ፈቃዱም ያላደረገ ያ ባሪያ እጅግ ይገረፋል፤”
ሉቃስ 12፥47
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍4❤1
Audio
#መጻሕፍትን_በድምጽ
👉ርዕስ፦ ዓላማ መር ሕይወት
✍️ጸሐፊ፦ ሪክ ዋረን
🗣ትርጉም፦ ኢቫንጀሊካል ቴዎሎጂካል ኮሌጅ
🗒ክፍል፦ 11 (የእግዚአብሔር የቅርብ ወዳጅ መሆን)
ይቀጥላል...
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👉ርዕስ፦ ዓላማ መር ሕይወት
✍️ጸሐፊ፦ ሪክ ዋረን
🗣ትርጉም፦ ኢቫንጀሊካል ቴዎሎጂካል ኮሌጅ
🗒ክፍል፦ 11 (የእግዚአብሔር የቅርብ ወዳጅ መሆን)
ይቀጥላል...
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤1
#እራሳችንን_እንመርምር
የራሳችንን ዘመን ፍጻሜ ብናውቅና ምን እየሰራን፣ ከፍጻሜያችን አንጻር ምን ያህል ጊዜ እንደቀረን መጥኖ ማወቅ ብንችል ምንኛ ጥበብ ነው? ምን እየሠራ ነው? ለማን፣ ለምን? እሺ፣ አሁን ምን ላድርግ? ቀጥሎስ?
"እግዚአብሔር ሆይ ፥ የሕይወቴ ፍጻሜ መቼ እንደ ሆነና የዕድሜዬ ልክ ስንት እንደ ሆነ ግለጽልኝ፤ በዚህ ዓለም የምኖረው ዘመን ፈጥኖ የሚያልፍ መሆኑን ለማወቅ አስችለኝ።"
መዝሙር 39፥4 (ሕያው ቃል)
“እስራኤልም የሚገባውን ያደርግ ዘንድ ዘመኑን የሚያውቁ ጥበበኞች ሰዎች የይሳኮር ልጆች አለቆች ሁለት መቶ ነበሩ፤ ወንድሞቻቸውም ሁሉ ይታዘዙአቸው ነበር።”
1 ዜና 12፥32
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የራሳችንን ዘመን ፍጻሜ ብናውቅና ምን እየሰራን፣ ከፍጻሜያችን አንጻር ምን ያህል ጊዜ እንደቀረን መጥኖ ማወቅ ብንችል ምንኛ ጥበብ ነው? ምን እየሠራ ነው? ለማን፣ ለምን? እሺ፣ አሁን ምን ላድርግ? ቀጥሎስ?
"እግዚአብሔር ሆይ ፥ የሕይወቴ ፍጻሜ መቼ እንደ ሆነና የዕድሜዬ ልክ ስንት እንደ ሆነ ግለጽልኝ፤ በዚህ ዓለም የምኖረው ዘመን ፈጥኖ የሚያልፍ መሆኑን ለማወቅ አስችለኝ።"
መዝሙር 39፥4 (ሕያው ቃል)
“እስራኤልም የሚገባውን ያደርግ ዘንድ ዘመኑን የሚያውቁ ጥበበኞች ሰዎች የይሳኮር ልጆች አለቆች ሁለት መቶ ነበሩ፤ ወንድሞቻቸውም ሁሉ ይታዘዙአቸው ነበር።”
1 ዜና 12፥32
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
🙏5👍2
. ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“እግዚአብሔርም ጌታንም አስነሣ እኛንም በኃይሉ ያስነሣናል።”
1ኛ ቆሮንቶስ 6፥14
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“እግዚአብሔርም ጌታንም አስነሣ እኛንም በኃይሉ ያስነሣናል።”
1ኛ ቆሮንቶስ 6፥14
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍2
Audio
#መጻሕፍትን_በድምጽ
👉ርዕስ፦ ዓላማ መር ሕይወት
✍️ጸሐፊ፦ ሪክ ዋረን
🗣ትርጉም፦ ኢቫንጀሊካል ቴዎሎጂካል ኮሌጅ
🗒ክፍል፦ 12 (ከእግዚአብሔር ጋር ወዳጅነትህን ማሳደግ)
ይቀጥላል...
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👉ርዕስ፦ ዓላማ መር ሕይወት
✍️ጸሐፊ፦ ሪክ ዋረን
🗣ትርጉም፦ ኢቫንጀሊካል ቴዎሎጂካል ኮሌጅ
🗒ክፍል፦ 12 (ከእግዚአብሔር ጋር ወዳጅነትህን ማሳደግ)
ይቀጥላል...
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍2
ዐብይ ጾም የሚጀምረው መቼ ነው? ጾሙስ ስንት ቀን ነው?
ጾም ነገ ይገባል፤ ዐቢይ ጾም የሚጀምረው ግን በሚቀጥለው ሰኞ ዕለት ነው። (ዝርዝሩን ዝቅ ብዬ አስረዳለሁ።) የካቶሊክ፣ የአንግሊካን፣ የምስራቅ ኦርቶዶክስ እና የተለያዩ የፕሮቴስታንት አብያተ ክርስቲያናት ይህን የ40 ቀናት ጾም (Lent) ያካሄዳሉ። (የኢትዮጵያ ፕሬቴስታንቶች ግን ከኦርቶዶክሳዊነት ጋር የተለያዩ መሆናቸው እንዲያሳይላቸው ነው መሰለኝ ይህን ትውፊት አይከተሉም።) የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ይህን “ጾመ አርብዓ” (ሁዳዴ) እንዲጾሙ ታዛለች፤ ይህንን ቤተ ክርስቲያኒቱ ሕጓ አድርጋ በተቀበለችው መጽሐፈ ሲኖዶስ (ዘሐዋርያት ተደንግጓል)። 40 ቀናት የተመረጡት ጌታ "በገዳመ ቆሮንቶስ" ለአርባ ቀናት መጾሙንና በብሉይ ኪዳንም ሙሴና ኤልያስ የጾሙት በመሆኑ ነው። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ጾም በተግባር ሲታይ ግን የአርባ ቀን ጾም ሳይሆን፣ የ54 ቀናት ነው። (አንዳንዶች 55 ያደርጉታል።) ለምን?
ፕሮፌሰር ጌታቸው ኃይሌ በግለ ታሪካቸው እንዳሰፈሩት ከሆነ፣ ይህ የሆነበት ምክንያት በ40 ቀናቱ ጾም ላይ “ሁለት ባለሰባት ቀን ጾሞች፣ አንዱ ጾመ አርባ ከመጀመሩ በፊት፣ አንዱ ካለቀ በኋላ ተጨምረው፣ እነዚህ ሦስት ጾሞች ተርታውን ስለሚመጡ ነው። ከጾመ አርባ በፊት የሚመጣው (የመጀመሪያው) ጾም “ጾመ ሕርቃል” ይባላል። ጾመ ሕርቃልና ጾመ አርባ እንዳለቁ የሚመጣው (የመጨረሻው) ጾም ደግሞ “ጾመ ሕማማት” ይባላል። ሦስቱ ጾሞች በተለያየ ጊዜ ከመምጣት ይልቅ ተከታትለው የመጡት በአበው ውሳኔ እንጂ፣ ታሪካቸው ተከታታይ ሆኖ አይደለም። ጾመ አርባ የሚጾመው የጌታን ጾም ለማስታወስና ከጌታ ጋር ተባባሪ ለመሆን ነው፤ ጾመ ሕማማት የሚጾመውና የሚሰገደው የጌታን ሥቃይ ለማስታወስና ስርየት ኀጢአት ለማግኘት ነው። ጾመ ሕርቃል የሚጾመው ሕርቃል ላፈረሰው መሐላ ፍዳ ለመክፈል ነው።”
ሕርቃል ማነው?
ሕርቃል (Heraclius) ከ610-641 ባይዛንታይንን የገዛ ንጉሠ ነገሥት ነው። ዋና ከተማው ቁስጥንጥንያ ነበረች። በግዛቱም ውስጥ ኦርቶዶክሳውያን፣ ካቶሊኮች እና አይሁድ ነበሩ። እነዚህም ሦስት ወገኖች በየጊዜው ጠብ የሚፈጥሩና አዲስ ወራሪ በመጣ ቁጥር ከመካከላቸው አንዱ ወራሪውን አስቀድሞ በመቀበል ሌሎቹን ለማስመታት የሚጥሩ ነበሩ። ሕርቃል በፊት የነበረው ንጉሥ ፎቃ በሚገዛበት ጊዜ የፋርስ ንጉሥ ቁስጥንጥንያን ከብቦ ማስጨነቅ ጀመሩ። ያኔ ክርስቲያኖቹ የፋሲካን በዓል በሚያደርጉበት ጊዜ በየአገሩ ያሉ አይሁድ ተጠራርተው ወረሯቸውና አብያተ ክርስቲያናትን ዘረፉ። መዘበሩ።
ወዲያው ሕርቃል የጦር መኮንን ነበረና የፋርስን ንጉሥ አሸንፎ ሕዝቡን ነጻ ሲያወጣ የቁስጥንጥንያ ነዋሪዎች የገዛ ንጉሣቸውን ገድለው እርሱን አነገሡት። እርሱም ከአገር አገር በውጊያ እየዞረ ኢየሩሳሌም ሲደርስ በዚያን ወቅት አይሁድም ብዙ እጅ መንሻ አመጡለትና እንዳይገድላቸው ቃል አስገቡት፤ አይሁድ ያደረጉት የማያውቀው ሕርቃልም ቃል ኪዳን ገባላቸው። ኢየሩሳሌም ሲገባ ደግሞ የክርስቲያኖቹ ካህናት በዝማሬ ተቀበሉት። የፈራረሱትን አብያተ ክርስቲያናት ያየው ሕርቃል የሆነውን ነገር ቢጠይቅ የአይሁድን ክፋት አጫወቱትና እንዲበቀልላቸው ጥያቄ አቀረቡለት።
እርሱ ግን ለአይሁድ ቃል ኪዳን እንደገባላቸውና ቃል ኪዳኑን ቢያፈርስ እግዚአብሔር እንደሚቀጣው ነገራቸው። ካህናቱ ግን “አይሁድን ተበቀልልን እንጂ ቃል ኪዳኑ አያሳስብህ፤ ንስሓ እንዲሆንህ እኛ ክርስቲያኖቹ ዓለም እስክታልፍ ድረስ ስላንተ በየዓመቱ አንድ ሳምንት እንጾምልሃለን” አሉት። በዚያ ጊዜ ሠራዊቱ አይሁድን እንዲገድሏቸው ትእዛዝ ሰጠ። ብዙዎቹን ፈጇቸው። እነዚያም ኤጴስ ቆጶሳት ስለ ሕርቃል መሓላ መጣስ በየዓመቱ አንድ ሳምንት የንስሓ ጾም እንዲጾሙ ለክርስቲያኖች ሁሉ ላኩባቸው።
እናም “ጾመ ሕርቃል” የንሥሐ ጾም ነው። Encyclopaedia Aethiopica ይህን አሳምሮ ይገልጸዋል፤ “Heraclius was also the Emperor whose repentance for the massacre of Jews in Jerusalem in 630/31 became the alleged reason for adding an (eighth) extra week to the Lent.” በማለት። ጾሙ ራሱን የቻለ ሳምንት ስላስፈለገው፣ በሰባቱ ሳምንታት ጾም ላይ ተጨምሮ ጾሙን የስምንት ሳምንታት አድርጎታል። “ፍትሐ ነገሥት ንባቡና ትርጓሜው” የሚለውን ኦርቶዶክሳዊ መጽሐፍም፣ “ከዐቢይ ጾም አስቀድማ የምትሆን የሕርቃል ጾም ናት” ይላል (ገጽ 150)።
እናላችሁ የዚህ ሳምንት ጾም ከዐቢይ ጾም ቀድማ የምትመጣ ጾመ ሕርቃል ናት። ጾመ ሕርቃልን ፍትሓ ነግሥቱ ቢጠቅሰውም ዝርዝሩን አይናገርም። ትርጓሜ ፍትሐ ነገሥትም መንፈሳዊ አንድምታው ላይ ያተኩራል እንጂ ታሪኩን አይናገርም፤ እንደ ፕሮፌሰር ጌታቸው አገላለጽ። እሳቸውም ታሪኩን ያገኙት አባቶች ወደ ግዕዝ ከተተረጎመው የጊዮርጊስ ወልደ ዓሚድ የዓለም ታሪክ መጽሐፍ ላይ ነው። ስለዚህም አብዛኛው ጿሚ የዐቢይ ጾምን የመጀመሪያ ሳምንት ጾም ታሪክ ሳያውቅ ነው የሚጾመው። ለኢትዮጵያ ጾሙን የሰጠችው የግብፅ ቤ/ክ ታሪኩ በሕይወት ያሉ ወገኖችን የሚያቃቅር ሆኖ ስላገኘችው ታሪኩን መካድ ወይም ለጾሙ ሌላ ምክንያት መስጠትን የተሻለ ሆና ያገኘችው ይመስላል። በእኔ ውስን ንባብ መሠረት የግብፅ ኦርቶዶክስ ቤት ክርስቲያን የዚህን ሳምንት ጾም “የዝግጅት ሳምንት” በሚል ስያሜ ነው የምትጾመው፤ የዐቢይ ጾም ዝግጅት መሆኑ ነው። በተለያዩ አጋጣሚዎች እንደ ታዘብሁት ከሆነ ደግሞ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ አማኞች ዘንድ ግን ይህ ታሪክ በቅጡ የሚታወቅ አይመስለኝም።
ጾመ ሕርቃል የአንድ ሳምንት ጾም ነው፤ ከዚያ የ40 ቀን ዐቢይ ጾም ይቀጥላል። ከዚያም የጌታን ሕማማት መነሻው የሚያደርገው የሐዋርያት ጾም ለአንድ ሳምንት ይቀጥላል። ስለዚህ 7 + 40 + 7 = 54። ከዚያም ይፈሰካል!
ዛሬ ዛሬ ዐቢይ ጾምን የሚጾሙ ጥቂት ወንጌላውያን ክርስቲያኖችን ዐውቃለሁ፤ እኔም ስተባበራቸው ነበር። ታዲያ ከአርባው ቀን በፊት (በዚህ ሳምንት) የሚካሄደውን “ጾመ ሕርቃል” መጾም አለባቸው? ይህስ ምን ያህል መጽሐፍ ቅዱሳዊ ነው?
ምንጭ፦ @PaulosFekadu
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ጾም ነገ ይገባል፤ ዐቢይ ጾም የሚጀምረው ግን በሚቀጥለው ሰኞ ዕለት ነው። (ዝርዝሩን ዝቅ ብዬ አስረዳለሁ።) የካቶሊክ፣ የአንግሊካን፣ የምስራቅ ኦርቶዶክስ እና የተለያዩ የፕሮቴስታንት አብያተ ክርስቲያናት ይህን የ40 ቀናት ጾም (Lent) ያካሄዳሉ። (የኢትዮጵያ ፕሬቴስታንቶች ግን ከኦርቶዶክሳዊነት ጋር የተለያዩ መሆናቸው እንዲያሳይላቸው ነው መሰለኝ ይህን ትውፊት አይከተሉም።) የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ይህን “ጾመ አርብዓ” (ሁዳዴ) እንዲጾሙ ታዛለች፤ ይህንን ቤተ ክርስቲያኒቱ ሕጓ አድርጋ በተቀበለችው መጽሐፈ ሲኖዶስ (ዘሐዋርያት ተደንግጓል)። 40 ቀናት የተመረጡት ጌታ "በገዳመ ቆሮንቶስ" ለአርባ ቀናት መጾሙንና በብሉይ ኪዳንም ሙሴና ኤልያስ የጾሙት በመሆኑ ነው። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ጾም በተግባር ሲታይ ግን የአርባ ቀን ጾም ሳይሆን፣ የ54 ቀናት ነው። (አንዳንዶች 55 ያደርጉታል።) ለምን?
ፕሮፌሰር ጌታቸው ኃይሌ በግለ ታሪካቸው እንዳሰፈሩት ከሆነ፣ ይህ የሆነበት ምክንያት በ40 ቀናቱ ጾም ላይ “ሁለት ባለሰባት ቀን ጾሞች፣ አንዱ ጾመ አርባ ከመጀመሩ በፊት፣ አንዱ ካለቀ በኋላ ተጨምረው፣ እነዚህ ሦስት ጾሞች ተርታውን ስለሚመጡ ነው። ከጾመ አርባ በፊት የሚመጣው (የመጀመሪያው) ጾም “ጾመ ሕርቃል” ይባላል። ጾመ ሕርቃልና ጾመ አርባ እንዳለቁ የሚመጣው (የመጨረሻው) ጾም ደግሞ “ጾመ ሕማማት” ይባላል። ሦስቱ ጾሞች በተለያየ ጊዜ ከመምጣት ይልቅ ተከታትለው የመጡት በአበው ውሳኔ እንጂ፣ ታሪካቸው ተከታታይ ሆኖ አይደለም። ጾመ አርባ የሚጾመው የጌታን ጾም ለማስታወስና ከጌታ ጋር ተባባሪ ለመሆን ነው፤ ጾመ ሕማማት የሚጾመውና የሚሰገደው የጌታን ሥቃይ ለማስታወስና ስርየት ኀጢአት ለማግኘት ነው። ጾመ ሕርቃል የሚጾመው ሕርቃል ላፈረሰው መሐላ ፍዳ ለመክፈል ነው።”
ሕርቃል ማነው?
ሕርቃል (Heraclius) ከ610-641 ባይዛንታይንን የገዛ ንጉሠ ነገሥት ነው። ዋና ከተማው ቁስጥንጥንያ ነበረች። በግዛቱም ውስጥ ኦርቶዶክሳውያን፣ ካቶሊኮች እና አይሁድ ነበሩ። እነዚህም ሦስት ወገኖች በየጊዜው ጠብ የሚፈጥሩና አዲስ ወራሪ በመጣ ቁጥር ከመካከላቸው አንዱ ወራሪውን አስቀድሞ በመቀበል ሌሎቹን ለማስመታት የሚጥሩ ነበሩ። ሕርቃል በፊት የነበረው ንጉሥ ፎቃ በሚገዛበት ጊዜ የፋርስ ንጉሥ ቁስጥንጥንያን ከብቦ ማስጨነቅ ጀመሩ። ያኔ ክርስቲያኖቹ የፋሲካን በዓል በሚያደርጉበት ጊዜ በየአገሩ ያሉ አይሁድ ተጠራርተው ወረሯቸውና አብያተ ክርስቲያናትን ዘረፉ። መዘበሩ።
ወዲያው ሕርቃል የጦር መኮንን ነበረና የፋርስን ንጉሥ አሸንፎ ሕዝቡን ነጻ ሲያወጣ የቁስጥንጥንያ ነዋሪዎች የገዛ ንጉሣቸውን ገድለው እርሱን አነገሡት። እርሱም ከአገር አገር በውጊያ እየዞረ ኢየሩሳሌም ሲደርስ በዚያን ወቅት አይሁድም ብዙ እጅ መንሻ አመጡለትና እንዳይገድላቸው ቃል አስገቡት፤ አይሁድ ያደረጉት የማያውቀው ሕርቃልም ቃል ኪዳን ገባላቸው። ኢየሩሳሌም ሲገባ ደግሞ የክርስቲያኖቹ ካህናት በዝማሬ ተቀበሉት። የፈራረሱትን አብያተ ክርስቲያናት ያየው ሕርቃል የሆነውን ነገር ቢጠይቅ የአይሁድን ክፋት አጫወቱትና እንዲበቀልላቸው ጥያቄ አቀረቡለት።
እርሱ ግን ለአይሁድ ቃል ኪዳን እንደገባላቸውና ቃል ኪዳኑን ቢያፈርስ እግዚአብሔር እንደሚቀጣው ነገራቸው። ካህናቱ ግን “አይሁድን ተበቀልልን እንጂ ቃል ኪዳኑ አያሳስብህ፤ ንስሓ እንዲሆንህ እኛ ክርስቲያኖቹ ዓለም እስክታልፍ ድረስ ስላንተ በየዓመቱ አንድ ሳምንት እንጾምልሃለን” አሉት። በዚያ ጊዜ ሠራዊቱ አይሁድን እንዲገድሏቸው ትእዛዝ ሰጠ። ብዙዎቹን ፈጇቸው። እነዚያም ኤጴስ ቆጶሳት ስለ ሕርቃል መሓላ መጣስ በየዓመቱ አንድ ሳምንት የንስሓ ጾም እንዲጾሙ ለክርስቲያኖች ሁሉ ላኩባቸው።
እናም “ጾመ ሕርቃል” የንሥሐ ጾም ነው። Encyclopaedia Aethiopica ይህን አሳምሮ ይገልጸዋል፤ “Heraclius was also the Emperor whose repentance for the massacre of Jews in Jerusalem in 630/31 became the alleged reason for adding an (eighth) extra week to the Lent.” በማለት። ጾሙ ራሱን የቻለ ሳምንት ስላስፈለገው፣ በሰባቱ ሳምንታት ጾም ላይ ተጨምሮ ጾሙን የስምንት ሳምንታት አድርጎታል። “ፍትሐ ነገሥት ንባቡና ትርጓሜው” የሚለውን ኦርቶዶክሳዊ መጽሐፍም፣ “ከዐቢይ ጾም አስቀድማ የምትሆን የሕርቃል ጾም ናት” ይላል (ገጽ 150)።
እናላችሁ የዚህ ሳምንት ጾም ከዐቢይ ጾም ቀድማ የምትመጣ ጾመ ሕርቃል ናት። ጾመ ሕርቃልን ፍትሓ ነግሥቱ ቢጠቅሰውም ዝርዝሩን አይናገርም። ትርጓሜ ፍትሐ ነገሥትም መንፈሳዊ አንድምታው ላይ ያተኩራል እንጂ ታሪኩን አይናገርም፤ እንደ ፕሮፌሰር ጌታቸው አገላለጽ። እሳቸውም ታሪኩን ያገኙት አባቶች ወደ ግዕዝ ከተተረጎመው የጊዮርጊስ ወልደ ዓሚድ የዓለም ታሪክ መጽሐፍ ላይ ነው። ስለዚህም አብዛኛው ጿሚ የዐቢይ ጾምን የመጀመሪያ ሳምንት ጾም ታሪክ ሳያውቅ ነው የሚጾመው። ለኢትዮጵያ ጾሙን የሰጠችው የግብፅ ቤ/ክ ታሪኩ በሕይወት ያሉ ወገኖችን የሚያቃቅር ሆኖ ስላገኘችው ታሪኩን መካድ ወይም ለጾሙ ሌላ ምክንያት መስጠትን የተሻለ ሆና ያገኘችው ይመስላል። በእኔ ውስን ንባብ መሠረት የግብፅ ኦርቶዶክስ ቤት ክርስቲያን የዚህን ሳምንት ጾም “የዝግጅት ሳምንት” በሚል ስያሜ ነው የምትጾመው፤ የዐቢይ ጾም ዝግጅት መሆኑ ነው። በተለያዩ አጋጣሚዎች እንደ ታዘብሁት ከሆነ ደግሞ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ አማኞች ዘንድ ግን ይህ ታሪክ በቅጡ የሚታወቅ አይመስለኝም።
ጾመ ሕርቃል የአንድ ሳምንት ጾም ነው፤ ከዚያ የ40 ቀን ዐቢይ ጾም ይቀጥላል። ከዚያም የጌታን ሕማማት መነሻው የሚያደርገው የሐዋርያት ጾም ለአንድ ሳምንት ይቀጥላል። ስለዚህ 7 + 40 + 7 = 54። ከዚያም ይፈሰካል!
ዛሬ ዛሬ ዐቢይ ጾምን የሚጾሙ ጥቂት ወንጌላውያን ክርስቲያኖችን ዐውቃለሁ፤ እኔም ስተባበራቸው ነበር። ታዲያ ከአርባው ቀን በፊት (በዚህ ሳምንት) የሚካሄደውን “ጾመ ሕርቃል” መጾም አለባቸው? ይህስ ምን ያህል መጽሐፍ ቅዱሳዊ ነው?
ምንጭ፦ @PaulosFekadu
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍8❤3
በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ ለአርባ ቀንና ለአርባ ሌሊት የጾመው ሰው ማን ነው?
Anonymous Quiz
19%
ሀ. ሙሴ
2%
ለ. ኤልያስ
37%
ሐ. ጌታችን እና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ
42%
መ. ሁሉም
👍8🙏2
. ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“ኢዮሣፍጥም ፈራ፥ እግዚአብሔርንም ሊፈልግ ፊቱን አቀና፤ በይሁዳም ሁሉ ጾም አወጀ።”
2 ዜና 20፥3
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“ኢዮሣፍጥም ፈራ፥ እግዚአብሔርንም ሊፈልግ ፊቱን አቀና፤ በይሁዳም ሁሉ ጾም አወጀ።”
2 ዜና 20፥3
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤8👍1👏1
Audio
#መጻሕፍትን_በድምጽ
👉ርዕስ፦ ዓላማ መር ሕይወት
✍️ጸሐፊ፦ ሪክ ዋረን
🗣ትርጉም፦ ኢቫንጀሊካል ቴዎሎጂካል ኮሌጅ
🗒ክፍል፦ 13 (እግዚአብሔርን የሚያስደስት አምልኮ)
ይቀጥላል...
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👉ርዕስ፦ ዓላማ መር ሕይወት
✍️ጸሐፊ፦ ሪክ ዋረን
🗣ትርጉም፦ ኢቫንጀሊካል ቴዎሎጂካል ኮሌጅ
🗒ክፍል፦ 13 (እግዚአብሔርን የሚያስደስት አምልኮ)
ይቀጥላል...
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍4
👍4