. ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“ወደ ዘላለም ሕይወት የሚወስደውን የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ምሕረት ስትጠባበቁ በእግዚአብሔር ፍቅር ራሳችሁን ጠብቁ።”
ይሁዳ 1፥21
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“ወደ ዘላለም ሕይወት የሚወስደውን የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ምሕረት ስትጠባበቁ በእግዚአብሔር ፍቅር ራሳችሁን ጠብቁ።”
ይሁዳ 1፥21
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
🥰6👍4❤1
ዓላማ መር ህይወት- ቀን 1_Purpose driven Life - Day 1 _ alama mer hiywet…
PETERiCH (I am empty without Jesus)
#መጻሕፍትን_በድምጽ
👉ርዕስ፦ ዓላማ መር ሕይወት
✍️ጸሐፊ፦ ሪክ ዋረን
🗣ትርጉም፦ ኢቫንጀሊካል ቴዎሎጂካል ኮሌጅ
🗒ክፍል፦ 1
ይቀጥላል...
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👉ርዕስ፦ ዓላማ መር ሕይወት
✍️ጸሐፊ፦ ሪክ ዋረን
🗣ትርጉም፦ ኢቫንጀሊካል ቴዎሎጂካል ኮሌጅ
🗒ክፍል፦ 1
ይቀጥላል...
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍8❤1🔥1
#የሮሜ_መልእክት_ጥናት
ሮሜ 10
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁵ ሙሴ ከሕግ የሆነውን ጽድቅ የሚያደርገው ሰው በእርሱ በሕይወት እንዲኖር ጽፎአልና።
⁶ ከእምነት የሆነ ጽድቅ ግን እንዲህ ይላል፦ በልብህ፦ ማን ወደ ሰማይ ይወጣል? አትበል፤ ይህ ክርስቶስን ለማውረድ ነው፤
⁷ ወይም፦ በልብህ፦ ወደ ጥልቁ ማን ይወርዳል? አትበል፤ ይህ ክርስቶስን ከሙታን ለማውጣት ነው።
⁸ ነገር ግን ምን ይላል? በአፍህ በልብህም ሆኖ ቃሉ ቀርቦልሃል፤ ይህም የምንሰብከው የእምነት ቃል ነው።
⁹ ኢየሱስ ጌታ እንደ ሆነ በአፍህ ብትመሰክር እግዚአብሔርም ከሙታን እንዳስነሣው በልብህ ብታምን ትድናለህና፤
¹⁰ ሰው በልቡ አምኖ ይጸድቃልና በአፉም መስክሮ ይድናልና።
¹¹ መጽሐፍ፦ በእርሱ የሚያምን ሁሉ አያፍርም ይላልና።
¹² በአይሁዳዊና በግሪክ ሰው መካከል ልዩነት የለምና፤ አንዱ ጌታ የሁሉ ጌታ ነውና፥ ለሚጠሩትም ሁሉ ባለ ጠጋ ነው፤
¹³ የጌታን ስም የሚጠራ ሁሉ ይድናልና።
ሮሜ 10 (አዲሱ መ.ት)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁵ ሙሴ በሕግ በኩል የሆነውን ጽድቅ ሲገልጽ፣ “እነዚህን የሚፈጽም ሰው በእነርሱ ይኖራል” ይላል።
⁶ ከእምነት የሆነው ጽድቅ ግን እንዲህ ይላል፤ “ ‘በልብህ ማን ወደ ሰማይ ይወጣል?’ አትበል”፤ ይህ ክርስቶስን ለማውረድ ነው፤
⁷ “ወይም ‘ወደ ጥልቁስ ማን ይወርዳል?’ አትበል”፤ ይህም ክርስቶስን ከሙታን ለማውጣት ነው።
⁸ ነገር ግን ምን ይላል? “ቃሉ በአጠገብህ ነው፤ በአፍህና በልብህም ውስጥ ነው፤” የምንሰብከውም የእምነት ቃል ይህ ነው፤
⁹ “ኢየሱስ ጌታ ነው” ብለህ በአፍህ ብትመሰክር፣ እግዚአብሔርም ከሙታን እንዳስነሣው በልብህ ብታምን፣ ትድናለህ።
¹⁰ የምትጸድቀው በልብህ አምነህ ነው፤ የምትድነውም በአፍህ መስክረህ ነውና።
¹¹ መጽሐፍ እንደሚለው፣ “በእርሱ የሚያምን ሁሉ አያፍርም።”
¹² በአይሁድና በአሕዛብ መካከል ልዩነት የለም፤ አንዱ ጌታ የሁሉ ጌታ ነውና፤ የሚለምኑትንም አብዝቶ ይባርካል፤
¹³ “የጌታን ስም የሚጠራ ሁሉ ይድናልና።”
ሮሜ 10 (ሕያው ቃል)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁵ ሕግን በመጠበቅ ስለ መጽደቅ ሙሴ፥ «አንድ ሰው ሕግ የሚያዘውን ሁሉ መጠበቅ ከቻለ ፥ ሕግ ራሱ ሕይወት ይሰጠዋል» ሲል ጽፎአል።
⁶ በእምነት የሚገኘው ጽድቅ ግን፥ «ክርስቶስን ወደ ምድር ለማውረድ ወደ ሰማይ መውጣት አያስፈልግህም።
⁷ ወይም ወደ ሲኦል ወርደህ ክርስቶስን ከሙታን መካከል ማስነሣት የለብህም» ይላል።
⁸ ነገር ግን መጽደቅ ስለሚቻልበት መንገድ እንዲህ ይላል። «የእግዚአብሔር ቃል በአጠገብህ ይገኛል ፤ በአፍህና በልብህም ውስጥ ነው።» ይህም የእግዚአብሔር ቃል እኛ የምናስተምራችሁ የእምነት ቃል ነው።
⁹ ኢየሱስ ጌታ እንደሆነ በአፋችሁ ብትመሰክሩ፥ እግዚአብሔርም ከሞት እንዳስነሣው በልባችሁ ብታምኑ ትድናላችሁ።
¹⁰ ምክንያቱም ሰው በልቡ አምኖ ይጸድቃል። ስለ እምነቱም በመመስከሩ ይድናል።
¹¹ ይህ እውነት መሆኑን ለማረጋገጥ እንዲህ የሚል ቃል በመጽሐፍ ተጽፎ ይገኛል ፤ «በእርሱ የሚያምን ሁሉ አያፍርም።»
¹² ይህ ቃል የተጻፈው በአይሁድና በአሕዛብ መካከል ምንም ልዩነት ሳይደረግ ለሁሉ ነው። የሁሉም ጌታ የሆነው ኢየሱስ፥ ለሚለምኑት ሁሉ በረከቱን የሚሰጥ ባለጸጋ አምላክ ነው።
¹³ በቅዱሳት መጻሕፍት ፥ «የጌታን ስም የሚጠራ ሁሉ ይድናል» ተብሏል።
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ሮሜ 10
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁵ ሙሴ ከሕግ የሆነውን ጽድቅ የሚያደርገው ሰው በእርሱ በሕይወት እንዲኖር ጽፎአልና።
⁶ ከእምነት የሆነ ጽድቅ ግን እንዲህ ይላል፦ በልብህ፦ ማን ወደ ሰማይ ይወጣል? አትበል፤ ይህ ክርስቶስን ለማውረድ ነው፤
⁷ ወይም፦ በልብህ፦ ወደ ጥልቁ ማን ይወርዳል? አትበል፤ ይህ ክርስቶስን ከሙታን ለማውጣት ነው።
⁸ ነገር ግን ምን ይላል? በአፍህ በልብህም ሆኖ ቃሉ ቀርቦልሃል፤ ይህም የምንሰብከው የእምነት ቃል ነው።
⁹ ኢየሱስ ጌታ እንደ ሆነ በአፍህ ብትመሰክር እግዚአብሔርም ከሙታን እንዳስነሣው በልብህ ብታምን ትድናለህና፤
¹⁰ ሰው በልቡ አምኖ ይጸድቃልና በአፉም መስክሮ ይድናልና።
¹¹ መጽሐፍ፦ በእርሱ የሚያምን ሁሉ አያፍርም ይላልና።
¹² በአይሁዳዊና በግሪክ ሰው መካከል ልዩነት የለምና፤ አንዱ ጌታ የሁሉ ጌታ ነውና፥ ለሚጠሩትም ሁሉ ባለ ጠጋ ነው፤
¹³ የጌታን ስም የሚጠራ ሁሉ ይድናልና።
ሮሜ 10 (አዲሱ መ.ት)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁵ ሙሴ በሕግ በኩል የሆነውን ጽድቅ ሲገልጽ፣ “እነዚህን የሚፈጽም ሰው በእነርሱ ይኖራል” ይላል።
⁶ ከእምነት የሆነው ጽድቅ ግን እንዲህ ይላል፤ “ ‘በልብህ ማን ወደ ሰማይ ይወጣል?’ አትበል”፤ ይህ ክርስቶስን ለማውረድ ነው፤
⁷ “ወይም ‘ወደ ጥልቁስ ማን ይወርዳል?’ አትበል”፤ ይህም ክርስቶስን ከሙታን ለማውጣት ነው።
⁸ ነገር ግን ምን ይላል? “ቃሉ በአጠገብህ ነው፤ በአፍህና በልብህም ውስጥ ነው፤” የምንሰብከውም የእምነት ቃል ይህ ነው፤
⁹ “ኢየሱስ ጌታ ነው” ብለህ በአፍህ ብትመሰክር፣ እግዚአብሔርም ከሙታን እንዳስነሣው በልብህ ብታምን፣ ትድናለህ።
¹⁰ የምትጸድቀው በልብህ አምነህ ነው፤ የምትድነውም በአፍህ መስክረህ ነውና።
¹¹ መጽሐፍ እንደሚለው፣ “በእርሱ የሚያምን ሁሉ አያፍርም።”
¹² በአይሁድና በአሕዛብ መካከል ልዩነት የለም፤ አንዱ ጌታ የሁሉ ጌታ ነውና፤ የሚለምኑትንም አብዝቶ ይባርካል፤
¹³ “የጌታን ስም የሚጠራ ሁሉ ይድናልና።”
ሮሜ 10 (ሕያው ቃል)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁵ ሕግን በመጠበቅ ስለ መጽደቅ ሙሴ፥ «አንድ ሰው ሕግ የሚያዘውን ሁሉ መጠበቅ ከቻለ ፥ ሕግ ራሱ ሕይወት ይሰጠዋል» ሲል ጽፎአል።
⁶ በእምነት የሚገኘው ጽድቅ ግን፥ «ክርስቶስን ወደ ምድር ለማውረድ ወደ ሰማይ መውጣት አያስፈልግህም።
⁷ ወይም ወደ ሲኦል ወርደህ ክርስቶስን ከሙታን መካከል ማስነሣት የለብህም» ይላል።
⁸ ነገር ግን መጽደቅ ስለሚቻልበት መንገድ እንዲህ ይላል። «የእግዚአብሔር ቃል በአጠገብህ ይገኛል ፤ በአፍህና በልብህም ውስጥ ነው።» ይህም የእግዚአብሔር ቃል እኛ የምናስተምራችሁ የእምነት ቃል ነው።
⁹ ኢየሱስ ጌታ እንደሆነ በአፋችሁ ብትመሰክሩ፥ እግዚአብሔርም ከሞት እንዳስነሣው በልባችሁ ብታምኑ ትድናላችሁ።
¹⁰ ምክንያቱም ሰው በልቡ አምኖ ይጸድቃል። ስለ እምነቱም በመመስከሩ ይድናል።
¹¹ ይህ እውነት መሆኑን ለማረጋገጥ እንዲህ የሚል ቃል በመጽሐፍ ተጽፎ ይገኛል ፤ «በእርሱ የሚያምን ሁሉ አያፍርም።»
¹² ይህ ቃል የተጻፈው በአይሁድና በአሕዛብ መካከል ምንም ልዩነት ሳይደረግ ለሁሉ ነው። የሁሉም ጌታ የሆነው ኢየሱስ፥ ለሚለምኑት ሁሉ በረከቱን የሚሰጥ ባለጸጋ አምላክ ነው።
¹³ በቅዱሳት መጻሕፍት ፥ «የጌታን ስም የሚጠራ ሁሉ ይድናል» ተብሏል።
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍3❤2
በቅዱሳት መጻሕፍት ከብሉይ ኪዳን ነቢያት መካከል “... ጻድቅ ግን በእምነቱ በሕይወት ይኖራል።” በሚለው የሚታወቀው ነቢይ የቱ ነው?
Anonymous Quiz
19%
ሀ. ኢሳይያስ
12%
ለ. ኤርምያስ
9%
ሐ. ሕዝቅኤል
54%
መ. ዕንባቆም
6%
ሠ. ኤልያስ
👍7
. ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“መድኃኒታችንም ከዓመፅ ሁሉ እንዲቤዠን፥ መልካሙንም ለማድረግ የሚቀናውን ገንዘቡም የሚሆነውን ሕዝብ ለራሱ እንዲያነጻ፥ ስለ እኛ ነፍሱን ሰጥቶአል።”
ቲቶ 2፥14
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“መድኃኒታችንም ከዓመፅ ሁሉ እንዲቤዠን፥ መልካሙንም ለማድረግ የሚቀናውን ገንዘቡም የሚሆነውን ሕዝብ ለራሱ እንዲያነጻ፥ ስለ እኛ ነፍሱን ሰጥቶአል።”
ቲቶ 2፥14
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤7👍1😁1
ዓላማ መር ህይወት- ቀን 2_Purpose driven Life - Day 2 _ alama mer hiywet…
PETERiCH (I am empty without Jesus)
#መጻሕፍትን_በድምጽ
👉ርዕስ፦ ዓላማ መር ሕይወት
✍️ጸሐፊ፦ ሪክ ዋረን
🗣ትርጉም፦ ኢቫንጀሊካል ቴዎሎጂካል ኮሌጅ
🗒ክፍል፦ 2 (አጋጣሚ አይደለህም)
ይቀጥላል...
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👉ርዕስ፦ ዓላማ መር ሕይወት
✍️ጸሐፊ፦ ሪክ ዋረን
🗣ትርጉም፦ ኢቫንጀሊካል ቴዎሎጂካል ኮሌጅ
🗒ክፍል፦ 2 (አጋጣሚ አይደለህም)
ይቀጥላል...
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤3👍2
ከቅዱሳት መጻሕፍት መካከል በአዲስ ኪዳን የሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስን በጣም ስሜታዊ እና ግላዊ ጹሑፍ የያዘው መጽሐፍ የትኛው ነው?
Anonymous Quiz
35%
ሀ. 2ኛ ጢሞቴዎስ
25%
ለ. ገላትያ
30%
ሐ. 2ኛ ቆሮንቶስ
11%
መ. ሮሜ
❤4👍4
. ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“የመንፈስ ፍሬ ግን ፍቅር፥ ደስታ፥ ሰላም፥ ትዕግሥት፥ ቸርነት፥ በጎነት፥ እምነት፥ የውሃት፥ ራስን መግዛት ነው።”
ገላትያ 5፥22
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“የመንፈስ ፍሬ ግን ፍቅር፥ ደስታ፥ ሰላም፥ ትዕግሥት፥ ቸርነት፥ በጎነት፥ እምነት፥ የውሃት፥ ራስን መግዛት ነው።”
ገላትያ 5፥22
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍14
ዓላማ መር ህይወት- ቀን 3_Purpose driven Life - Day 3 _ alama mer hiywet…
PETERiCH (I am empty without Jesus)
#መጻሕፍትን_በድምጽ
👉ርዕስ፦ ዓላማ መር ሕይወት
✍️ጸሐፊ፦ ሪክ ዋረን
🗣ትርጉም፦ ኢቫንጀሊካል ቴዎሎጂካል ኮሌጅ
🗒ክፍል፦ 3 (ሕይወትህ የሚመራው በምንድነው?)
ይቀጥላል...
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👉ርዕስ፦ ዓላማ መር ሕይወት
✍️ጸሐፊ፦ ሪክ ዋረን
🗣ትርጉም፦ ኢቫንጀሊካል ቴዎሎጂካል ኮሌጅ
🗒ክፍል፦ 3 (ሕይወትህ የሚመራው በምንድነው?)
ይቀጥላል...
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤2
⏱ቢዚ - ቢዚ፤ ለሁሉ ጊዜ አለው ወይስ አለን?
በጋሽ ንጉሤ ቡልቻ
ጓዙን ጠቅልሎ ወደ ውጪ አገር የሚሄድ ጓደኛውን ለመሸኘት ከተሰበሰቡት መካከል የሽኝት ፕሮግራሙን ማጠቃለያ ጸሎት የሚጸልየው ሰው እንዲህ ብሎ ጸልዮአል አሉ፡፡
“ጌታ ሆይ ይህ ወንድማችን በሚሄድበት አገር ቢዚ ከሚባል ጋኔን እንድትጠብቀው እንለምንሃለሁ፡፡”
“ቢዚ” የሚባል ጋኔን መኖር አለመኖሩን መመራመራችንን ትተን ባተሌነት “ቢዚነት” የውጪ አገር አበሳ መሆኑ ቀርቶ ውስጥ አገርም የሚያስጨንቀን ጉዳይ እንደ ሆነ እንቀበል፡፡
በቀጠሮ ብዛት፣ በእንቅስቃሴ ብዛት፣ በጉዳይ ብዛት፣ በሥራ ብዛት፣ በሥራ ውጣ ውረድ፣ በማኅበራዊ ግንኙነት ብዛት፣ በሽቅብ ቁልቁል ብዛት፣ የአካላችን አውታር እስኪነዝሩ ተወጣጥረናል፤ ነፍሳችን ብን ትን እስክትል እንማስናለን፡፡ ትንፋሽ አጥሮን ስናለከልክ የሚያየን የሌላ ዓለም ፍጡር ቢኖር “ምን ሥራሥር በጥብጠው ቢጠጡ ነው እንዲህ የሚያዛብታቸው፣ የሚያሽከረክራቸው” ብሎ በጠየቀ፡፡ ለመሆኑ ምን እንዲህ ያባትለናል?
የየዕለቱ ውጣ ውረድ ነዋ! የጉረሮ መድፈን ጥሪ፣ የማኅበረ ሰብ ቦታችንን የማስጠበቅ ጥሪ፣ የነገ ምን ይሆናል ጭንቀት፣ ሌሎችም ይህን የመሳሰሉ ሁሉ፡፡ የሰው ልጅ የሚሠራውንና የሚውልበትን ሁነኛ ጉዳይ አግኝቶ በሥራ መጠመዱ በረከት እንጂ ርግማን አይደለም፡፡ ጊዜ እንደ ጅረት በሚንፎለፎልበት ልማዱ ቢነጉድ የሥራ ቦይ እየቀደዱ ጥቅም ላይ የሚያውሉት የታደሉ ናቸው “ዘመኑን ዋጁ” በሚለው ምክር አብነት፡፡ እንዲህ የሚያደርጉ በሥራው ከሚገኘው ጥቃሞት በላይ ስብእናቸው ይለማል፣ ርካታና ደስታም ያገኛሉ፡፡
አሁን ያነሣነው “ጋኔኑ ቢዚነት” ግን ከሚያለማው የሚያጠፋው የበለጠ፣ ከሚያረካው የሚያቅበዘብዘው የበዛ፣ ደስታችንን ቦጥቡጦ የሚበላ መልቲ ነው፡፡
ሮጠን ሮጠን ልባችን ሊፈነዳ ሲል ስንቆም የትም እንዳልደረስን ስንረዳ፣ ከበሬታ ፍለጋ ብዙ የአንቱታ ካባ ደርበን ድንገት ካባው የወደቀ ቀን የነፍሳችን ክሳት ሲጋለጥ የዚህ ዐይነት ቢዚነት ፍሬ ይታወቅ ይሆናል፡፡
መድኃኒታችን ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ “በአጭር ቁመት በጠባብ ደረት ተወስኖ ወደዚህ ምድር ስለመጣ ልክ እንደ እኛ በቀን ውስጥ 24 ሰዓት ብቻ ነበረው፡፡ ያደረገውን ሁሉ ያደረገው በዚሁ በባለ 24 ሰዓት ቀን ነበር፡፡ የምድር እድሜው ጥቂት ነበረ፤ የይፋ አገልግሎቱ ደግሞ ከሦስት ዓመታት እጅግም ያልዘለለ አጭር ነበር፡፡ ይህ ሁሉ ሆኖ ወደ አባቱ መሄጃው ጊዜ ሲደርስ የጸለየው ጸሎት የተዋከበ፣ የተጨነቀ አልነበረም፤ “ምነው አንድ ዐሥር ዓመት ብትጨምርልኝና የጀመርሁትን በጨረስሁ” የሚል የጊዜ ልመና አልነበረበትም፡፡ “የሰጠኸኝን ሥራ በምድር ላይ ፈጽሜ አከበርሁህ” የሚል ደልዳላ ዘገባ ነበር፡፡
እንዴት እንደዚህ ስክን ያለ ሕይወትና አገልግሎት አገኘ? እጅግ ብዙ የእርሱን ርዳታ የሚሹ ፍጡራን ባሉበት ዓለም ውስጥ በቀኝና በግራ ሊያዋክቡት የሚችሉ አስባታሊ ተግባራት በነበሩበት ሁኔታ እንደምን ርጋታ አገኘ? መጽሐፉ ላይ እንደ ተጠቆምን ከሆነ መልሱ ውስብስብ አይደለም፡፡ ጌታችን ዋናውን ጉዳይ ከአስቸኳዩ የለየ፣ የሕይወት ጥሪውን አሳምሮ ያወቀ፣ ቆፍጣና የዓላማ ሰው ስለነበረ ነው፡፡ “የሰጠኸኝን ሥራ” አለ እንጂ በሜዳ ያለውን ተግባር ሁሉ አላለም፤ ወይም ዘመድ ወዳጅ የጠየቀኝን ኀላፊነት ሁሉ ወይም የተገኘውን ሥራ ሁሉ ፈጸምሁ አላለም፡፡ የአባቱ ፈቃድ የሕይወት ጥሪው ነበረና ያንኑ ፈቃድ በመንፈስ ቅዱስ ኀይል ፈጸመው፡፡ በጸሎቱ ዘገባ በዝርዝር እንዳሰፈረው እያንዳንዱን ቅንጣት ተግባር ከነውጤቱ እንደተከናወነ ርግጠኛ ነበር፡፡ በምድር አገልግሎቱ የነካቸው ሰዎች ሁሉ ሕይወታቸው በጥልቅ ተነክቷል፤ የይድረስ ይድረስ በሽታ ሳይጠናወተው የሚሠራውን ሁሉ ወደ ተገቢው ፍጻሜ አደረሰ፡፡ በዓላማ ጽናት፣ በርግጠኛ ርምጃ፣ በታላቅ ማስተዋል ተራመደ፡፡ ስለዚህ ሞቱ የጸጸት አልነበረም የድልና የስኬት እንጂ፡፡ ሕይወቱ አልተጨናገፈም፤ ውጥኑ ባጭር አልቀረም፤ የሰማይ አባቱን ያስከበረ ወርቃማ ፍጻሜ አገኘ፡፡ የሕይወትን ዋና ጥሪ ለመፈጸም ጊዜን በጥበቡ የመጠቀም ጉልህ አርኣያ ሆነ፡፡ ስሙ ይክበር፡፡ ቻርልስ ሁሜል የተባለ አስተዋይ ጸሐፊ “The Tyranny of the Urgent” ብሎ የጻፈውና ቁምላቸው ፈንታሁን የተረጎመው አንድ ጽሑፍ እንዲህ ይላል፦
/ወደ ኋላ መለስ ብለን ስንመለከት፣ያልተጠናቀቁ ሥራዎች፣ ምላሽ ያልተሰጣቸው ደብዳቤዎች፣ ያልተጎበኙ ወዳጆች ያልተጻፉ መጣጥፎችና ያልተነበቡ መጻሕፍት ይታዩናል፡፡ በሥራ እየባተልን ቢሆንም የምናገኝበት ደስታ እያደር የመነመነ ነው፡፡ ሆኖም ችግር የሚፈጥርብን ተግቶ መሥራት ሳይሆን ጥርጣሬና መወላወል ናቸው፡፡ ትልቁ አደጋ ለአስቸኳዩ ጉዳይ መላ ለመፈለግ ስንጣደፍ ዋነኛውን ጉዳይ መዘንጋቱ ነው፡፡ ችግሩ ደግሞ ዋነናው ጉዳይ ዛሬ ወይም በዚህ ሳምንት ይሠራ የሚያሰኝ አጣዳፊነት የሌለው መሆኑ ነው፡፡ ፈጣን ርምጃ የሚጠይቁን አጣዳፊ ጉዳዮች ናቸው፡፡ በጊዜው በጣም አስፈላጊና ወደ ጎን የማይባሉ ስለሚመስሉን ጉልበታችንን ይመጡታል፡፡ ክርስቲያን ፋታ ወስዶ መንፈሳዊ ሁኔታውን በመፈተሸ፣ የሥራ ኀላፊነት ለመቀበል እንዳይችል ሆኖ በሥራ ከተጠመደ፣ ለአስቸኳዩ ጉዳይ ምላሽ ለመስጠት ሎሌ ያድራል፡፡ በራሱና በሌሎች ዐይን ዋጋ የሚሰጠው የሚመስል ነገር፣ ሌት ተቀን ሠርቶ ማከናወን ቢችልም፣ እግዚአብሔር ያቀደለትን ሥራ ግን ሳያጠናቅቅ ይቀራል/
እንግዲያው በባርነት ቀፍድዶ የያዘን “አስቸኳይ” የሚባል አምባ ገነን የፍዳችን አንዱ ዋና ምክንያት መሆኑ ነው፡፡ አስቸኳዩን ከዋናው ጉዳይ እንዴት እንለያለን? የሚለው ጥያቄ ብርቱ ጥያቄ ነው፡፡ ለዚህ መልስ ካገኘን የፍልሚያው እምብርት ታወቀ ማለት ነው፡፡
ይቀጥላል ...
ምንጭ :- semayawithought.com
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
በጋሽ ንጉሤ ቡልቻ
ጓዙን ጠቅልሎ ወደ ውጪ አገር የሚሄድ ጓደኛውን ለመሸኘት ከተሰበሰቡት መካከል የሽኝት ፕሮግራሙን ማጠቃለያ ጸሎት የሚጸልየው ሰው እንዲህ ብሎ ጸልዮአል አሉ፡፡
“ጌታ ሆይ ይህ ወንድማችን በሚሄድበት አገር ቢዚ ከሚባል ጋኔን እንድትጠብቀው እንለምንሃለሁ፡፡”
“ቢዚ” የሚባል ጋኔን መኖር አለመኖሩን መመራመራችንን ትተን ባተሌነት “ቢዚነት” የውጪ አገር አበሳ መሆኑ ቀርቶ ውስጥ አገርም የሚያስጨንቀን ጉዳይ እንደ ሆነ እንቀበል፡፡
በቀጠሮ ብዛት፣ በእንቅስቃሴ ብዛት፣ በጉዳይ ብዛት፣ በሥራ ብዛት፣ በሥራ ውጣ ውረድ፣ በማኅበራዊ ግንኙነት ብዛት፣ በሽቅብ ቁልቁል ብዛት፣ የአካላችን አውታር እስኪነዝሩ ተወጣጥረናል፤ ነፍሳችን ብን ትን እስክትል እንማስናለን፡፡ ትንፋሽ አጥሮን ስናለከልክ የሚያየን የሌላ ዓለም ፍጡር ቢኖር “ምን ሥራሥር በጥብጠው ቢጠጡ ነው እንዲህ የሚያዛብታቸው፣ የሚያሽከረክራቸው” ብሎ በጠየቀ፡፡ ለመሆኑ ምን እንዲህ ያባትለናል?
የየዕለቱ ውጣ ውረድ ነዋ! የጉረሮ መድፈን ጥሪ፣ የማኅበረ ሰብ ቦታችንን የማስጠበቅ ጥሪ፣ የነገ ምን ይሆናል ጭንቀት፣ ሌሎችም ይህን የመሳሰሉ ሁሉ፡፡ የሰው ልጅ የሚሠራውንና የሚውልበትን ሁነኛ ጉዳይ አግኝቶ በሥራ መጠመዱ በረከት እንጂ ርግማን አይደለም፡፡ ጊዜ እንደ ጅረት በሚንፎለፎልበት ልማዱ ቢነጉድ የሥራ ቦይ እየቀደዱ ጥቅም ላይ የሚያውሉት የታደሉ ናቸው “ዘመኑን ዋጁ” በሚለው ምክር አብነት፡፡ እንዲህ የሚያደርጉ በሥራው ከሚገኘው ጥቃሞት በላይ ስብእናቸው ይለማል፣ ርካታና ደስታም ያገኛሉ፡፡
አሁን ያነሣነው “ጋኔኑ ቢዚነት” ግን ከሚያለማው የሚያጠፋው የበለጠ፣ ከሚያረካው የሚያቅበዘብዘው የበዛ፣ ደስታችንን ቦጥቡጦ የሚበላ መልቲ ነው፡፡
ሮጠን ሮጠን ልባችን ሊፈነዳ ሲል ስንቆም የትም እንዳልደረስን ስንረዳ፣ ከበሬታ ፍለጋ ብዙ የአንቱታ ካባ ደርበን ድንገት ካባው የወደቀ ቀን የነፍሳችን ክሳት ሲጋለጥ የዚህ ዐይነት ቢዚነት ፍሬ ይታወቅ ይሆናል፡፡
መድኃኒታችን ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ “በአጭር ቁመት በጠባብ ደረት ተወስኖ ወደዚህ ምድር ስለመጣ ልክ እንደ እኛ በቀን ውስጥ 24 ሰዓት ብቻ ነበረው፡፡ ያደረገውን ሁሉ ያደረገው በዚሁ በባለ 24 ሰዓት ቀን ነበር፡፡ የምድር እድሜው ጥቂት ነበረ፤ የይፋ አገልግሎቱ ደግሞ ከሦስት ዓመታት እጅግም ያልዘለለ አጭር ነበር፡፡ ይህ ሁሉ ሆኖ ወደ አባቱ መሄጃው ጊዜ ሲደርስ የጸለየው ጸሎት የተዋከበ፣ የተጨነቀ አልነበረም፤ “ምነው አንድ ዐሥር ዓመት ብትጨምርልኝና የጀመርሁትን በጨረስሁ” የሚል የጊዜ ልመና አልነበረበትም፡፡ “የሰጠኸኝን ሥራ በምድር ላይ ፈጽሜ አከበርሁህ” የሚል ደልዳላ ዘገባ ነበር፡፡
እንዴት እንደዚህ ስክን ያለ ሕይወትና አገልግሎት አገኘ? እጅግ ብዙ የእርሱን ርዳታ የሚሹ ፍጡራን ባሉበት ዓለም ውስጥ በቀኝና በግራ ሊያዋክቡት የሚችሉ አስባታሊ ተግባራት በነበሩበት ሁኔታ እንደምን ርጋታ አገኘ? መጽሐፉ ላይ እንደ ተጠቆምን ከሆነ መልሱ ውስብስብ አይደለም፡፡ ጌታችን ዋናውን ጉዳይ ከአስቸኳዩ የለየ፣ የሕይወት ጥሪውን አሳምሮ ያወቀ፣ ቆፍጣና የዓላማ ሰው ስለነበረ ነው፡፡ “የሰጠኸኝን ሥራ” አለ እንጂ በሜዳ ያለውን ተግባር ሁሉ አላለም፤ ወይም ዘመድ ወዳጅ የጠየቀኝን ኀላፊነት ሁሉ ወይም የተገኘውን ሥራ ሁሉ ፈጸምሁ አላለም፡፡ የአባቱ ፈቃድ የሕይወት ጥሪው ነበረና ያንኑ ፈቃድ በመንፈስ ቅዱስ ኀይል ፈጸመው፡፡ በጸሎቱ ዘገባ በዝርዝር እንዳሰፈረው እያንዳንዱን ቅንጣት ተግባር ከነውጤቱ እንደተከናወነ ርግጠኛ ነበር፡፡ በምድር አገልግሎቱ የነካቸው ሰዎች ሁሉ ሕይወታቸው በጥልቅ ተነክቷል፤ የይድረስ ይድረስ በሽታ ሳይጠናወተው የሚሠራውን ሁሉ ወደ ተገቢው ፍጻሜ አደረሰ፡፡ በዓላማ ጽናት፣ በርግጠኛ ርምጃ፣ በታላቅ ማስተዋል ተራመደ፡፡ ስለዚህ ሞቱ የጸጸት አልነበረም የድልና የስኬት እንጂ፡፡ ሕይወቱ አልተጨናገፈም፤ ውጥኑ ባጭር አልቀረም፤ የሰማይ አባቱን ያስከበረ ወርቃማ ፍጻሜ አገኘ፡፡ የሕይወትን ዋና ጥሪ ለመፈጸም ጊዜን በጥበቡ የመጠቀም ጉልህ አርኣያ ሆነ፡፡ ስሙ ይክበር፡፡ ቻርልስ ሁሜል የተባለ አስተዋይ ጸሐፊ “The Tyranny of the Urgent” ብሎ የጻፈውና ቁምላቸው ፈንታሁን የተረጎመው አንድ ጽሑፍ እንዲህ ይላል፦
/ወደ ኋላ መለስ ብለን ስንመለከት፣ያልተጠናቀቁ ሥራዎች፣ ምላሽ ያልተሰጣቸው ደብዳቤዎች፣ ያልተጎበኙ ወዳጆች ያልተጻፉ መጣጥፎችና ያልተነበቡ መጻሕፍት ይታዩናል፡፡ በሥራ እየባተልን ቢሆንም የምናገኝበት ደስታ እያደር የመነመነ ነው፡፡ ሆኖም ችግር የሚፈጥርብን ተግቶ መሥራት ሳይሆን ጥርጣሬና መወላወል ናቸው፡፡ ትልቁ አደጋ ለአስቸኳዩ ጉዳይ መላ ለመፈለግ ስንጣደፍ ዋነኛውን ጉዳይ መዘንጋቱ ነው፡፡ ችግሩ ደግሞ ዋነናው ጉዳይ ዛሬ ወይም በዚህ ሳምንት ይሠራ የሚያሰኝ አጣዳፊነት የሌለው መሆኑ ነው፡፡ ፈጣን ርምጃ የሚጠይቁን አጣዳፊ ጉዳዮች ናቸው፡፡ በጊዜው በጣም አስፈላጊና ወደ ጎን የማይባሉ ስለሚመስሉን ጉልበታችንን ይመጡታል፡፡ ክርስቲያን ፋታ ወስዶ መንፈሳዊ ሁኔታውን በመፈተሸ፣ የሥራ ኀላፊነት ለመቀበል እንዳይችል ሆኖ በሥራ ከተጠመደ፣ ለአስቸኳዩ ጉዳይ ምላሽ ለመስጠት ሎሌ ያድራል፡፡ በራሱና በሌሎች ዐይን ዋጋ የሚሰጠው የሚመስል ነገር፣ ሌት ተቀን ሠርቶ ማከናወን ቢችልም፣ እግዚአብሔር ያቀደለትን ሥራ ግን ሳያጠናቅቅ ይቀራል/
እንግዲያው በባርነት ቀፍድዶ የያዘን “አስቸኳይ” የሚባል አምባ ገነን የፍዳችን አንዱ ዋና ምክንያት መሆኑ ነው፡፡ አስቸኳዩን ከዋናው ጉዳይ እንዴት እንለያለን? የሚለው ጥያቄ ብርቱ ጥያቄ ነው፡፡ ለዚህ መልስ ካገኘን የፍልሚያው እምብርት ታወቀ ማለት ነው፡፡
ይቀጥላል ...
ምንጭ :- semayawithought.com
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍10❤8👏1💯1
. ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“ጥቂት ጊዜ ተውሁሽ፥ በታላቅም ምሕረት እሰበስብሻለሁ።”
ኢሳይያስ 54፥7
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“ጥቂት ጊዜ ተውሁሽ፥ በታላቅም ምሕረት እሰበስብሻለሁ።”
ኢሳይያስ 54፥7
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍7
ዓላማ መር ህይወት- ቀን 4_Purpose driven Life - Day 4 _ alama mer hiywet…
PETERiCH (I am empty without Jesus)
#መጻሕፍትን_በድምጽ
👉ርዕስ፦ ዓላማ መር ሕይወት
✍️ጸሐፊ፦ ሪክ ዋረን
🗣ትርጉም፦ ኢቫንጀሊካል ቴዎሎጂካል ኮሌጅ
🗒ክፍል፦ 4 (ለዘላለም ሕይወት ተፈጥረሃል)
ይቀጥላል...
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👉ርዕስ፦ ዓላማ መር ሕይወት
✍️ጸሐፊ፦ ሪክ ዋረን
🗣ትርጉም፦ ኢቫንጀሊካል ቴዎሎጂካል ኮሌጅ
🗒ክፍል፦ 4 (ለዘላለም ሕይወት ተፈጥረሃል)
ይቀጥላል...
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤2
#እራሳችንን_እንመርምር
"ሰው" መሆን ማለት ምን ማለት ነው? ሁለት እግር ያለው የሚንቀሳቀስ፣ የሚያስብ፣ የሚበላ፣ የሚጠጣ ወይስ ሌላ? ሰው አለመሆንስ ይቻላል?
“በርታ ሰውም ሁን፤ የምታደርገውንና የምትሄድበትን ሁሉ ታከናውን ዘንድ፥ በሙሴ ሕግ እንደ ተጻፈ ሥርዓቱንና ትእዛዛቱን ፍርዱንና ምስክሩንም ትጠብቅ ዘንድ፥ በመንገዱም ትሄድ ዘንድ፥ የአምላክህን የእግዚአብሔርን ትእዛዝ ጠብቅ።”
1ኛ ነገሥት 2፥3
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
"ሰው" መሆን ማለት ምን ማለት ነው? ሁለት እግር ያለው የሚንቀሳቀስ፣ የሚያስብ፣ የሚበላ፣ የሚጠጣ ወይስ ሌላ? ሰው አለመሆንስ ይቻላል?
“በርታ ሰውም ሁን፤ የምታደርገውንና የምትሄድበትን ሁሉ ታከናውን ዘንድ፥ በሙሴ ሕግ እንደ ተጻፈ ሥርዓቱንና ትእዛዛቱን ፍርዱንና ምስክሩንም ትጠብቅ ዘንድ፥ በመንገዱም ትሄድ ዘንድ፥ የአምላክህን የእግዚአብሔርን ትእዛዝ ጠብቅ።”
1ኛ ነገሥት 2፥3
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤8👍3
. ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“ለባሪያህ ከሠራኸው ከምሕረትህና ከእውነትህም ሁሉ ትንሽ ስንኳ የማይገባኝ ነኝ፤ በትሬን ብቻ ይዤ ይህን ዮርዳኖስን ተሻግሬ ነበርና፥ አሁን ግን የሁለት ክፍል ሠራዊት ሆንሁ።”
ዘፍጥረት 32፥10
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“ለባሪያህ ከሠራኸው ከምሕረትህና ከእውነትህም ሁሉ ትንሽ ስንኳ የማይገባኝ ነኝ፤ በትሬን ብቻ ይዤ ይህን ዮርዳኖስን ተሻግሬ ነበርና፥ አሁን ግን የሁለት ክፍል ሠራዊት ሆንሁ።”
ዘፍጥረት 32፥10
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤7👍2
ዓላማ መር ህይወት- ቀን 5_Purpose driven Life - Day 5 _ alama mer hiywet…
PETERiCH (I am empty without Jesus)
#መጻሕፍትን_በድምጽ
👉ርዕስ፦ ዓላማ መር ሕይወት
✍️ጸሐፊ፦ ሪክ ዋረን
🗣ትርጉም፦ ኢቫንጀሊካል ቴዎሎጂካል ኮሌጅ
🗒ክፍል፦ 5 (ሕይወትን ከእግዚአብሔር ዕይታ አንጻር መልእክት)
ይቀጥላል...
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👉ርዕስ፦ ዓላማ መር ሕይወት
✍️ጸሐፊ፦ ሪክ ዋረን
🗣ትርጉም፦ ኢቫንጀሊካል ቴዎሎጂካል ኮሌጅ
🗒ክፍል፦ 5 (ሕይወትን ከእግዚአብሔር ዕይታ አንጻር መልእክት)
ይቀጥላል...
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍4❤3
የቀጠለ...
⏱️ቢዚ - ቢዚ፤ ለሁሉ ጊዜ አለው ወይስ አለን?
በጋሽ ንጉሤ ቡልቻ
ይረዳን እንደ ሆነ እስቲ መላ ልምታ፡፡ በጎ ትብብራችሁን ስጡኝና ይህን ጥያቄ በጥሞና መልሱልኝ “ለመሞት አንድ ወር ቀርቶሃል የምትሠራውን ሁሉ በነዚህ ሠላሳ ቀናት ጨርስ” ብትባሉ ቀኖቹንና ሌሊቶቹን ምን ታደርጉባቸው ነበር?
ብጣሽ ወረቀት አውጡና የምታደርጓቸውን ነገሮች በቅደም ተከተል ጻፉዋቸው፡፡ ልምምዱ ምናልባት ዋና የምትሉትን ዋና ካልሆኑት ለመለየት ይረዳችሁ ይሆናል፡፡
የሕይወታችሁ ዋና ዓላማ ምንድን ነው? የደም ግፊታችሁን እየጨመረ፣ ናላችሁን እያዞረ፣ ትንፋሽ አሳጥቶ የሚያስሮጣችሁን ነገር ሁሉ ከዚህ ዋና ዓላማ አንጻር ፈትሹት፡፡ ወደ ዓላማው የሚፈስ ነባር ወንዝ ነው ወይስ በየመስኩ የፈነዳ መድረሻው ያልታወቀ የውሃ ምንጭ? የክርስቶስ ተከታይ ዋና ዓላማ ምንድን ነው የተባለ እንደሆነ ሐዋርያው ጳውሎስ ባጭሩና በግልጽ ከተናገረው ከዚህ ጥቅስ የተሻለ መግለጫ አላገኘሁም፡፡ “አንዱ ስለ ሁሉ ሞተ፣ እንግዲያውስ ሁሉ ሞቱ በሕይወትም ያሉትም ስለ እነርሱ ለሞተውና ለተነሣው እንጂ ወደ ፊት ለራሳቸው እንዳይኖሩ ስለ ሁሉ ሞተ፡፡” 2ኛ ቆሮ 5፡13
የክርስቶስ ተከታይ ግለ ሰብም ሆነ ማኅበረ ሰብ የሕይወት ዓላማው ንድፍ ተሠርቶለት አልቋል፡፡ የምንሠራው ሁሉ የምናስበው ሁሉ የዚህ ዋና ንድፍ (Master Plan) አካል ካልሆነ ሕገ ወጥ ግንባታ ነው፤ ለፍቶ መና ነው፡፡ እያንዳንዱዋ የእንቅስቃሴ ቅንጣት መፈተሸ ዋጋዋም መተመን አለባት፡፡ መሮጥ ብቻውን ዋጋ ቢስ ነው፤ ሕይወት መሮጫ ግብ ይሻል፤ ግቡም በአንጻሩ የመገስገሻ መስመር አለው፡፡ ሐዋርያው ትንፋሽ ሊሰበስብ ሲቃረብ ሩጫ ጨረስኩ ሳይሆን ‹‹ሩጫውን ጨረስኩ›› ማለቱ የተሰመረ መንገድ፣ የሚደረስበት ግብ መኖሩን ሲያመለክተን ነው፡፡
የቢዚነት ጉዳይ ግን ከዓላማ አንጻር ብቻ ሳይሆን በጊዜ አስተዳደር አንጻርም ሊታይ ይገባል፡፡ ጊዜ ከፈጣሪ የተሰጠን ሀብት ነው፡፡ ጊዜ ሀብት ከሆነ እንግዲያው እያንዳንዳችን “መጋቤ ጊዜያት” ሆነን በዚህ ሀብት ላይ ተሹመናል፡፡ የጊዜ መጋቢነት እንዴት ይከወን ስንል ባለ ሙያዎች ከሚመክሩን መካከል ሦስቱን ብቻ ልጥቀስ፡-
ጊዜዬ የት ጠፋ? ምን አደረግሁት? እያልክ የምትጠይቅ ከሆነ ሥራዬ ብለህ የዕለት ዕለት እንቅስቃሴህን ለተከታታይ ሰባት ቀናት ያደረግከውን ነገር ስም እየሰጠህ ልትጽፈው ትችላለህ፡፡ ከሳምንቱ በኋላ የጊዜ አጠቃቀምህን በዐይነቱ ስትሰድረው ጊዜህ ምን ላይ እንደዋለ የጊዜ ምጋቤ ባህርይህን ትረዳዋለህ፡፡ ያኔ ያላግባብ የባከነ ወይም በቂ ጊዜ ያልተሰጠው ምን እንደሆነ ግልጽ ይሆናል፡፡
ይህ የጊዜ ውሎ ግምጋሜ ወደ ሁለተኛው ዋና ነገር ይመራሃል ይህም ጊዜህን የሚሰርቁ የጊዜ መንታፊዎቸን ለይቶ ማወቅ ነው፡፡ ከታወቁት የጊዜ መንታፊዎች መካከል፡-
👉መወላወል (የቱን ላንሳ የቱን ልጣል)
👉ዝርክርክነት (ካርዱን የት ነበር ያደረግኩት)
👉መግቻ የሌላቸው የስልክ ጥሪዎች
👉ነገ ይደርሳል እያሉ መሳነፍ
👉ተራ/ወረፋ ጥበቃ
👉ጥድፊያ (ጥድፊያ ሲበዛ ፍጥነት ይቀንሳል ይባላል)
👉ድንገት የሚከሰቱ መስተጓጉሎች ይገኙበታል፡፡
እነዚህን የጊዜ ሌቦች እንዴት ነቅተህ እንደምትጠብቅ ከራስህ ጋር ተመካከር፡፡
ሦስተኛው ርምጃ ለሕይወትህ ዓላማ መሳካት የሚረዳ ከአንተ ባህርይና ሁናቴ ጋር የሚጣጣም የጊዜ ሰሌዳ መንደፍ ነው፡፡ የጊዜ መርሃ ግብር እንደሚያወጡት ቀላልነት ሳያዛንፉ መከተሉ ቀላል አይደለም፡፡ ላወጣኸው የጊዜ ሰሌዳ መገዛት ቢያቅትህ እንደገና መከለስና ማሻሻል ምንም ነውር የለበትም፡፡
ይህን ሁሉ ስታደርግ ልብ ማለት የሚገባህ ሕይወት ሥራ ብቻ÷ የግል ኑሮ ብቻ እንዳይደለ መገንዘብ ነው፡፡ የሥራና የዕረፍትን ሚዛን፣ የግልና የማኅበር ኑሮን ሚዛን፣ የዕለቱንና የዘላለሙን ሚዛን የሚጠብቅ የሕይወት ስልት መቀየስ ሁሉ ጎናዊ ስምረት እንዲኖረን ይረዳል፡፡
ወገኖቼ ጤናችን እስኪዛባ ደስታችን እስኪጠፋ ቢዚ ከሆንን እየቆየ ወደ ክስመት (burn out) ልንሄድ እንችላለን፡፡ በእምነት እጦት ሰበብ ሩጫ ያበዙትን ሕዝበ እስራኤል እግዚአብሔር እንደገሰጻቸውና እንደመከራቸው እኛንም ያስጠነቅቀናል፡፡
“የእስራኤል ቅዱስ ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላልና በመመለስና በማረፍ ትድናላችሁ፣ በፀጥታና በመታመን ኃይል ይሆንላችኋል፡፡”
(ኢሳ 30፡15)
ቁምላቸው ፈንታሁን ወደ አማርኛ ተርጉሞት በቃለ እግዚአብሔር አንባቢዎች ማኅበር በኩል ከታተመው መጽሐፍ ይህን አስተዋይ ጸሎት ልብ እንድንለው አብረንም እንድንጸልየው እጋብዛለሁ፡፡
ሰከን አርገኝ ጌታ!
ለአእምሮዬ ፀጥታ ለግሰህ፣ የልቤን ድውድውታ ቀንሰው፡፡
በጊዜ ውስጥ የዘላለምን አፅናፍ ራእይ ስጠኝና ጥድፊያዬ ልጓም ይበጅለት፡፡
በቀናት ዑደት ቱማታና ግርግር መካከል፣
የዘላለም ዓለም ኮረብቶች ግርማዊ አርምሞ በኔ ላይ ያርብብ፡፡
የሠራ አካላቴ ውጥረት በትውስታዬ በሚኖሩ
ዘማሪ ጅረቶች የሚያሳርፍ ሙዚቃ ይርገብ፡፡
የእንቅልፍን አስማታዊ አዳሽ ኃይል እንድገነዘብ እርዳኝ፡፡
ጥበብን አካፍለኝና የደቂቃ እርፍቶች በየመካከሉ እየወሰድኩ፡-
አበቦችን ልመልከት፣ ከወዳጅ ጋር ልጫወት፣
በጫካው መካከል ልመላለስ፣ ሸረሪት ድሯን ስትሸምን ልያት
ህፃኗን በፈገግታ ልቀበላት፣ እንባዎቿንም ላብስላት፡፡
ሩጫ ሁልጊዜ ለፈጣኖች እንዳይደለ፣
የኑሮ ሁለንተና ፍጥነት እየጨመሩ መኖጥ እንዳይደለ በየዕለቱ አስታውሰኝ፡፡
ቀና ብዬ ደመኖቹንና ሰማዩን
እንዲሁም ያዘመመን ዛፍ ልመልከታቸው፣
ዛፉ ዛሬ ይህን አክሎ ያደረገው፣ የበረታው በሕይወት ሰጪ ፀሐይህ ሙቀት
በዝግታ በማደጉ መሆኑን ልገንዘብ፡፡
ሰከን አርገኝ ጌታ ከአንተ ጋር ኅብረት በማድረግ በጥልቅ እኔነቴ የሚያሹኝን ሰላምና እረፍት ልጎናጸፍ፡፡
ምንጭ :- semayawithought.com
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
⏱️ቢዚ - ቢዚ፤ ለሁሉ ጊዜ አለው ወይስ አለን?
በጋሽ ንጉሤ ቡልቻ
ይረዳን እንደ ሆነ እስቲ መላ ልምታ፡፡ በጎ ትብብራችሁን ስጡኝና ይህን ጥያቄ በጥሞና መልሱልኝ “ለመሞት አንድ ወር ቀርቶሃል የምትሠራውን ሁሉ በነዚህ ሠላሳ ቀናት ጨርስ” ብትባሉ ቀኖቹንና ሌሊቶቹን ምን ታደርጉባቸው ነበር?
ብጣሽ ወረቀት አውጡና የምታደርጓቸውን ነገሮች በቅደም ተከተል ጻፉዋቸው፡፡ ልምምዱ ምናልባት ዋና የምትሉትን ዋና ካልሆኑት ለመለየት ይረዳችሁ ይሆናል፡፡
የሕይወታችሁ ዋና ዓላማ ምንድን ነው? የደም ግፊታችሁን እየጨመረ፣ ናላችሁን እያዞረ፣ ትንፋሽ አሳጥቶ የሚያስሮጣችሁን ነገር ሁሉ ከዚህ ዋና ዓላማ አንጻር ፈትሹት፡፡ ወደ ዓላማው የሚፈስ ነባር ወንዝ ነው ወይስ በየመስኩ የፈነዳ መድረሻው ያልታወቀ የውሃ ምንጭ? የክርስቶስ ተከታይ ዋና ዓላማ ምንድን ነው የተባለ እንደሆነ ሐዋርያው ጳውሎስ ባጭሩና በግልጽ ከተናገረው ከዚህ ጥቅስ የተሻለ መግለጫ አላገኘሁም፡፡ “አንዱ ስለ ሁሉ ሞተ፣ እንግዲያውስ ሁሉ ሞቱ በሕይወትም ያሉትም ስለ እነርሱ ለሞተውና ለተነሣው እንጂ ወደ ፊት ለራሳቸው እንዳይኖሩ ስለ ሁሉ ሞተ፡፡” 2ኛ ቆሮ 5፡13
የክርስቶስ ተከታይ ግለ ሰብም ሆነ ማኅበረ ሰብ የሕይወት ዓላማው ንድፍ ተሠርቶለት አልቋል፡፡ የምንሠራው ሁሉ የምናስበው ሁሉ የዚህ ዋና ንድፍ (Master Plan) አካል ካልሆነ ሕገ ወጥ ግንባታ ነው፤ ለፍቶ መና ነው፡፡ እያንዳንዱዋ የእንቅስቃሴ ቅንጣት መፈተሸ ዋጋዋም መተመን አለባት፡፡ መሮጥ ብቻውን ዋጋ ቢስ ነው፤ ሕይወት መሮጫ ግብ ይሻል፤ ግቡም በአንጻሩ የመገስገሻ መስመር አለው፡፡ ሐዋርያው ትንፋሽ ሊሰበስብ ሲቃረብ ሩጫ ጨረስኩ ሳይሆን ‹‹ሩጫውን ጨረስኩ›› ማለቱ የተሰመረ መንገድ፣ የሚደረስበት ግብ መኖሩን ሲያመለክተን ነው፡፡
የቢዚነት ጉዳይ ግን ከዓላማ አንጻር ብቻ ሳይሆን በጊዜ አስተዳደር አንጻርም ሊታይ ይገባል፡፡ ጊዜ ከፈጣሪ የተሰጠን ሀብት ነው፡፡ ጊዜ ሀብት ከሆነ እንግዲያው እያንዳንዳችን “መጋቤ ጊዜያት” ሆነን በዚህ ሀብት ላይ ተሹመናል፡፡ የጊዜ መጋቢነት እንዴት ይከወን ስንል ባለ ሙያዎች ከሚመክሩን መካከል ሦስቱን ብቻ ልጥቀስ፡-
ጊዜዬ የት ጠፋ? ምን አደረግሁት? እያልክ የምትጠይቅ ከሆነ ሥራዬ ብለህ የዕለት ዕለት እንቅስቃሴህን ለተከታታይ ሰባት ቀናት ያደረግከውን ነገር ስም እየሰጠህ ልትጽፈው ትችላለህ፡፡ ከሳምንቱ በኋላ የጊዜ አጠቃቀምህን በዐይነቱ ስትሰድረው ጊዜህ ምን ላይ እንደዋለ የጊዜ ምጋቤ ባህርይህን ትረዳዋለህ፡፡ ያኔ ያላግባብ የባከነ ወይም በቂ ጊዜ ያልተሰጠው ምን እንደሆነ ግልጽ ይሆናል፡፡
ይህ የጊዜ ውሎ ግምጋሜ ወደ ሁለተኛው ዋና ነገር ይመራሃል ይህም ጊዜህን የሚሰርቁ የጊዜ መንታፊዎቸን ለይቶ ማወቅ ነው፡፡ ከታወቁት የጊዜ መንታፊዎች መካከል፡-
👉መወላወል (የቱን ላንሳ የቱን ልጣል)
👉ዝርክርክነት (ካርዱን የት ነበር ያደረግኩት)
👉መግቻ የሌላቸው የስልክ ጥሪዎች
👉ነገ ይደርሳል እያሉ መሳነፍ
👉ተራ/ወረፋ ጥበቃ
👉ጥድፊያ (ጥድፊያ ሲበዛ ፍጥነት ይቀንሳል ይባላል)
👉ድንገት የሚከሰቱ መስተጓጉሎች ይገኙበታል፡፡
እነዚህን የጊዜ ሌቦች እንዴት ነቅተህ እንደምትጠብቅ ከራስህ ጋር ተመካከር፡፡
ሦስተኛው ርምጃ ለሕይወትህ ዓላማ መሳካት የሚረዳ ከአንተ ባህርይና ሁናቴ ጋር የሚጣጣም የጊዜ ሰሌዳ መንደፍ ነው፡፡ የጊዜ መርሃ ግብር እንደሚያወጡት ቀላልነት ሳያዛንፉ መከተሉ ቀላል አይደለም፡፡ ላወጣኸው የጊዜ ሰሌዳ መገዛት ቢያቅትህ እንደገና መከለስና ማሻሻል ምንም ነውር የለበትም፡፡
ይህን ሁሉ ስታደርግ ልብ ማለት የሚገባህ ሕይወት ሥራ ብቻ÷ የግል ኑሮ ብቻ እንዳይደለ መገንዘብ ነው፡፡ የሥራና የዕረፍትን ሚዛን፣ የግልና የማኅበር ኑሮን ሚዛን፣ የዕለቱንና የዘላለሙን ሚዛን የሚጠብቅ የሕይወት ስልት መቀየስ ሁሉ ጎናዊ ስምረት እንዲኖረን ይረዳል፡፡
ወገኖቼ ጤናችን እስኪዛባ ደስታችን እስኪጠፋ ቢዚ ከሆንን እየቆየ ወደ ክስመት (burn out) ልንሄድ እንችላለን፡፡ በእምነት እጦት ሰበብ ሩጫ ያበዙትን ሕዝበ እስራኤል እግዚአብሔር እንደገሰጻቸውና እንደመከራቸው እኛንም ያስጠነቅቀናል፡፡
“የእስራኤል ቅዱስ ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላልና በመመለስና በማረፍ ትድናላችሁ፣ በፀጥታና በመታመን ኃይል ይሆንላችኋል፡፡”
(ኢሳ 30፡15)
ቁምላቸው ፈንታሁን ወደ አማርኛ ተርጉሞት በቃለ እግዚአብሔር አንባቢዎች ማኅበር በኩል ከታተመው መጽሐፍ ይህን አስተዋይ ጸሎት ልብ እንድንለው አብረንም እንድንጸልየው እጋብዛለሁ፡፡
ሰከን አርገኝ ጌታ!
ለአእምሮዬ ፀጥታ ለግሰህ፣ የልቤን ድውድውታ ቀንሰው፡፡
በጊዜ ውስጥ የዘላለምን አፅናፍ ራእይ ስጠኝና ጥድፊያዬ ልጓም ይበጅለት፡፡
በቀናት ዑደት ቱማታና ግርግር መካከል፣
የዘላለም ዓለም ኮረብቶች ግርማዊ አርምሞ በኔ ላይ ያርብብ፡፡
የሠራ አካላቴ ውጥረት በትውስታዬ በሚኖሩ
ዘማሪ ጅረቶች የሚያሳርፍ ሙዚቃ ይርገብ፡፡
የእንቅልፍን አስማታዊ አዳሽ ኃይል እንድገነዘብ እርዳኝ፡፡
ጥበብን አካፍለኝና የደቂቃ እርፍቶች በየመካከሉ እየወሰድኩ፡-
አበቦችን ልመልከት፣ ከወዳጅ ጋር ልጫወት፣
በጫካው መካከል ልመላለስ፣ ሸረሪት ድሯን ስትሸምን ልያት
ህፃኗን በፈገግታ ልቀበላት፣ እንባዎቿንም ላብስላት፡፡
ሩጫ ሁልጊዜ ለፈጣኖች እንዳይደለ፣
የኑሮ ሁለንተና ፍጥነት እየጨመሩ መኖጥ እንዳይደለ በየዕለቱ አስታውሰኝ፡፡
ቀና ብዬ ደመኖቹንና ሰማዩን
እንዲሁም ያዘመመን ዛፍ ልመልከታቸው፣
ዛፉ ዛሬ ይህን አክሎ ያደረገው፣ የበረታው በሕይወት ሰጪ ፀሐይህ ሙቀት
በዝግታ በማደጉ መሆኑን ልገንዘብ፡፡
ሰከን አርገኝ ጌታ ከአንተ ጋር ኅብረት በማድረግ በጥልቅ እኔነቴ የሚያሹኝን ሰላምና እረፍት ልጎናጸፍ፡፡
ምንጭ :- semayawithought.com
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍7❤2🙏2💯1
በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ ጌታችን እና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እራሱን በተደጋጋሚ "እኔ...ነኝ" እያለ የገለጸበት መጽሐፍ የቱ ነው?
Anonymous Quiz
11%
ሀ. ማቴዎስ
5%
ለ. ማርቆስ
4%
ሐ. ሉቃስ
80%
መ. ዮሐንስ
❤11
. ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“እናንተ ግን፥ ወንድሞች ሆይ፥ መልካም ሥራን ለመሥራት አትታክቱ።”
2ኛ ተሰሎንቄ 3፥13
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“እናንተ ግን፥ ወንድሞች ሆይ፥ መልካም ሥራን ለመሥራት አትታክቱ።”
2ኛ ተሰሎንቄ 3፥13
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍11❤1
ዓላማ መር ህይወት- ቀን 6_Purpose driven Life - Day 6_ alama mer hiywet…
PETERiCH (I am empty without Jesus)
#መጻሕፍትን_በድምጽ
👉ርዕስ፦ ዓላማ መር ሕይወት
✍️ጸሐፊ፦ ሪክ ዋረን
🗣ትርጉም፦ ኢቫንጀሊካል ቴዎሎጂካል ኮሌጅ
🗒ክፍል፦ 6 (ሕይወት ጊዜያዊ ሥራ ነው)
ይቀጥላል...
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👉ርዕስ፦ ዓላማ መር ሕይወት
✍️ጸሐፊ፦ ሪክ ዋረን
🗣ትርጉም፦ ኢቫንጀሊካል ቴዎሎጂካል ኮሌጅ
🗒ክፍል፦ 6 (ሕይወት ጊዜያዊ ሥራ ነው)
ይቀጥላል...
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤2👍2