ቅዱሳት መጻሕፍት
7.45K subscribers
1.37K photos
61 videos
333 files
808 links
በዚህ ቻናል

👉ቅዱሳት መጻሕፍት ይጠናሉ::
👉መጽሐፍ ቅዱሳዊ ትምህርቶች ይቀርባሉ::
👉 ለቅዱሳት መጽሐፍት ጥናት የሚያግዙ መጻሕፍት ይለቀቃሉ።

⭐️⭐️⭐️⭐️⭐️

@Holy_scriptures
Download Telegram
.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“ስለዚህ በምታደርጉት ሁሉ ትከናወኑ ዘንድ የዚህን ቃል ኪዳን ቃሎች ጠብቁ አድርጉም።”
ዘዳግም 29፥9



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
5👍2👏1
ቅዱሳት መጻሕፍት
በቅዱሳት መጻሕፍት "ቃል" ማን ነው? #ቃልም_ሥጋ_ሆነ 2. “ቃል” በአዲስ ኪዳን (ግሪክ፦ Λόγος – ሎጎስ) ሐዋሪያው ቅዱስ ዮሐንስ፣ በዮሐንስ ወንጌል “ሎጎስ” የሚለውን ቃል (1፥1-14) ኢየሱስን እንደ መለኮታዊ የእግዚአብሔር ቃል ለመወከል ተጠቅሟል። "ሎጎስ" የሚለው ቃል በሁለቱም የግሪክ ፍልስፍና እና የአይሁድ ሥነ-መለኮት ውስጥ ሥር የሰደደ እና በጣም የሚታወቅ አሳብ ነው። እና ቅዱስ…
በቅዱሳት መጻሕፍት "ቃል" ማን ነው?


#ቃልም_ሥጋ_ሆነ


ለ. ቃል እንደ ፈጣሪ እና ጠባቂ


የጳውሎስ ጽሑፎች ክርስቶስን እንደ መለኮታዊ "ሎጎስ" በመግለጽ ፍጥረት ሁሉ የተገኘበት እንደሆነ በመግልጽ የሐዋርያ ዮሐንስን አመለካከት ያስተጋባል።

"እርሱም የማይታይ አምላክ ምሳሌ ነው፤ የሚታዩትና የማይታዩትም፥ ዙፋናት ቢሆኑ ወይም ጌትነት ወይም አለቅነት ወይም ሥልጣናት፥ በሰማይና በምድር ያሉት ሁሉ በእርሱ ተፈጥረዋልና ከፍጥረት ሁሉ በፊት በኵር ነው፤ ሁሉ በእርሱና ለእርሱ ተፈጥሮአል፤ እርሱም ከሁሉ በፊት ነው ሁሉም በእርሱ ተጋጥሞአል።
                ቆላስይስ 1፥15-17

ሐ. ቃል፣ እንደ እግዚአብሔር መገለጥ


ኢየሱስ የብሉይ ኪዳንን መለኮታዊ የሐሳብ ልውውጥ ዘዴዎችን በነቢያት በማሟላት እንደ እግዚአብሔር የመጨረሻ መገለጥ በአዲስ ኪዳን ተገልጿል።

"ከጥንት ጀምሮ እግዚአብሔር በብዙ ዓይነትና በብዙ ጎዳና ለአባቶቻችን በነቢያት ተናግሮ፥ ሁሉን ወራሽ ባደረገው ደግሞም ዓለማትን በፈጠረበት በልጁ በዚህ ዘመን መጨረሻ ለእኛ ተናገረን፤ እርሱም የክብሩ መንጸባረቅና የባሕርዩ ምሳሌ ሆኖ፥ ሁሉን በስልጣኑ ቃል እየደገፈ፥ ኃጢአታችንን በራሱ ካነጻ በኋላ በሰማያት በግርማው ቀኝ ተቀመጠ፤"
              ዕብራውያን 1፥1-3

መ. ቃል፣ በነገረ ፍጻሜ


"ዓይኖቹም እንደ እሳት ነበልባል ናቸው፥ በራሱ ላይም ብዙ ዘውዶች አሉ፥ ከእርሱም በቀር አንድ እንኳ የማያውቀው የተጻፈ ስም አለው፤ በደምም የተረጨ ልብስ ተጐናጽፎአል፥ ስሙም የእግዚአብሔር ቃል ተብሎአል።
                ራእይ 19፥12-13

ይህ የአቡቀለምሲሳዊ ምስል ሥጋ የሆነውን ኢየሱስ ክርስቶስን (ዮሐንስ 1) ከገዢው እና ከአሸናፊው ክርስቶስ ጋር ያገናኛል።


ይቀጥላል...



ምንጭ፦
📜Brown, Raymond E. The Gospel According to John. Anchor Bible Commentary, 1995.
📜Ladd, George Eldon. A Theology of the New Testament. Eerdmans, 1993.
Strong's Concordance (Entries for דָּבָר and Λόγος).
📜Vine, W.E. Vine's Expository Dictionary of New Testament Words. Thomas Nelson, 1996.




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍61
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#ቃልም_ሥጋ_ሆነ


“እርሱም እስራኤልን ከኃጢአቱ ሁሉ ያድነዋል።”
               መዝሙር 130፥8

"ወውእቱ ያድኅኖ ለእስራኤል እምኵሉ ኃጢአቱ።"
መዝሙር 130፥8

"Inni mataan isaa cubbuu isaanii
hundumaa irraa Israaʼelin ni fura."
Faarfannaa 130:8

"ንሱውን ንእስራኤል ካብ ኵሉ ኣበሳኡ ኼድሕኖ እዩ።"
መዝሙር 130፥8




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
7
.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“ከኃጢአተኞች ጋር ነፍሴን፥ ከደም ሰዎችም ጋር ሕይወቴን አታጥፋ።”
መዝሙር 26፥9



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍42
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
#ቃልም_ሥጋ_ሆነ


“የጽዮን ልጅ ሆይ፥ እነሆ፥ መጥቼ በመካከልሽ እኖራለሁና ዘምሪ ደስም ይበልሽ፥ ይላል እግዚአብሔር።”
                 ዘካርያስ 2፥10


"ተፈሥሒ ወተሐሠዪ ወለተ ጽዮን እስመ አነ እመጽእ ወአኀድር ማእከሌኪ፤ ይቤ እግዚአብሔር።"
ዘካርያስ 2፥10

“Yaa Intala Xiyoon gammadii ililchi. Ani dhufee gidduu kee nan jiraadhaatii jedha Waaqayyo."
Zakkaariyaas 2:10


"ኣቲ ጓል ጽዮን፣ እንሆ፣ እመጽእ ኣሎኹ፣ ኣብ ማእከልኪ ኸኣ ክነብር እየ እሞ፣ እልል በሊ ተሐጐሲውን፣ ይብል እግዚኣብሄር።"
ዘካርያስ 2፥10




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍2
#እራሳችንን_እንመርምር


የሰው ልጅ ሕይወት በዚህ ምድር በጥድፊያ፣ ትኩረትን በሚሹና በሚረብሹ ውጥረቶች የተሞላ ነው። ግን እንዴት በዚህ ወጀብ መሃል በእርጋታ እና በስክነት መኖር ይቻላል?


“አንተ ግን ነገርን ሁሉ በልክ አድርግ፥”
2ኛ ጢሞቴዎስ 4፥5

“አንተ ግን በሁኔታዎች ሁሉ የረጋህ ሁን፤”
2ኛ ጢሞቴዎስ 4፥5 (አዲሱ መ.ት)



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
4👍1
.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“ሌሎቹ ደግሞ እንዲፈሩ፥ ኃጢአት የሚሰሩትን በሁሉ ፊት ገሥጻቸው።”
1ኛ ጢሞቴዎስ 5፥20



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
4👍3
በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ የጌታችንንና የመድኃኒታችንን የኢየሱስ ክርስቶስ ውልደት ከዋክብት እንደሚያበስሩ ትንቢት የተናገረው ማን ነው?
Anonymous Quiz
59%
ሀ. ኢሳይያስ
6%
ለ. ኤርምያስ
8%
ሐ. ዘካርያስ
18%
መ. በለዓም
10%
ሠ. ሚክያስ
👍4
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
#ቃልም_ሥጋ_ሆነ


“አየዋለሁ፥ አሁን ግን አይደለም፤ እመለከተዋለሁ፥ በቅርብ ግን አይደለም፤ ከያዕቆብ ኮከብ ይወጣል፥ ከእስራኤል በትር ይነሣል፥ የሞዓብንም ማዕዘኖች ይመታል፥ የሤትንም ልጆች ያጠፋል።”
                ዘኍልቁ 24፥17


"እሬእዮ ወአኮ ይእዜ፡
ወአስተበፅዖ ወአኮ ዘይቀርብ፡
ይሠርቅ ኮከብ እምያዕቆብ፡
ወይትነሣእ እምእስራኤል፡
ወያጠፍኦሙ ለመላእክተ ሞአብ፡
ወይጼውዎሙ ለኵሉ ደቂቀ ሴት።"
            ዘኍልቁ 24፥17


"Ani isa nan arga; garuu amma miti;
ani isa nan ilaala; garuu dhiʼootti miti.
Yaaqoob keessaa urjiin tokko ni baʼa;
Israaʼel keessaa bokkuun tokko ol kaʼa.
Inni adda warra Moʼaab,
buqqee mataa ilmaan Seet hundaas ni caccabsa."
                 Lakkoobsa 24:17


"እርእዮ ኣሎኹ፡ ሕጂ ደኣ ኣይኰነን፡
እጥምቶ ኣሎኹ፡ ግናኸ ቀረባ ኣይኰነን፡
ካብ ያእቆብ ኰዀብ ይወጽእ፡
ካብ እስራኤል ከኣ በትሪ መንግስቲ ትትንስእ፡
ንሳ ንመሳፍንቲ ሞኣብ ትወቕዖም፡
ንዅሎም ደቂ መዕገርገርቲ ትጭፍልቖም።"
               ዘኍልቁ 24፥17




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍6
.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“ካህኑ የሠራዊት ጌታ የእግዚአብሔር መልእክተኛ ነውና ከንፈሮቹ እውቀትን ይጠብቁ ዘንድ ይገባቸዋል፥ ሰዎችም ሕግን ከአፉ ይፈልጉ ዘንድ ይገባቸዋል።”
ሚልክያስ 2፥7




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍4
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍31
የገላትያና የያዕቆብ መልእክት.pdf
8.3 MB
👉ርዕስ፦ የገላትያና የያዕቆብ መልእክት፣
የጥናት መምሪያና ማብራሪያ
ጸሐፊ፦ ቲም ፌሎስ


ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
10
#ቃልም_ሥጋ_ሆነ


የሕግ መጻሕፍት ስለኢየሱስ ምን ይላሉ?



ከቅዱሳት መጻሕፍት መካከል የመጀመሪያዎቹ አምስቱ  መጻሕፍት (ዘፍጥረት፣ ዘጸአት፣ ዘሌዋውያን፣ ዘኍልቍ እና ዘዳግም) ፔንታቱክ በመባል ይታወቃሉ። መጻሕፍቱ ጌታችንንና መድኃኒታችንን ኢየሱስ ክርስቶስን በስም አይጠቅሱም ሆኖም፣ ኢየሱስ ክርስቶስን ለማመልከት በክርስቲያናዊ ሥነ-መለኮት ዘርፍ ውስጥ በቀላሉ ልንገነዘባቸው የምንችላቸው በርካታ ትንቢቶችን እና ምሳሌዎችን ይዘዋል። ከዚህ በታች መጻሕፍቱ ካነሷቸው አሳቦች መካከል ዋና ዋናዎቹን እነሆ፦

1. የሴቲቱ ዘር (ዘፍ 3፥15)

“በአንተና በሴቲቱ መካከል፥ በዘርህና በዘርዋም መካከል ጠላትነትን አደርጋለሁ፤ እርሱ ራስህን ይቀጠቅጣል፥ አንተም ሰኰናውን ትቀጠቅጣለህ።”
       ዘፍጥረት 3፥15

ይህ ክፍል የመጀመሪያው ወንጌል በመባል ይታወቃል፣ ይህ ቁጥር ኢየሱስ በሰይጣን ላይ ስላደረገው ድል ጥላ እንደሆነ ተመላክቷል። “የሴቲቱ ዘር” የሚያመለክተው ክርስቶስን ነው፣ እርሱም በመጨረሻ ክፋትን የሚያሸንፍ ነው።

2. ከአብርሃም ጋር የገባው ቃል ኪዳን (ዘፍ 12፥3፣ 22፥18

“... የምድር ነገዶችም ሁሉ በአንተ ይባረካሉ።” ዘፍጥረት 12፥3

“የምድር አሕዛብ ሁሉም በዘርህ ይባረካሉ፥”
   ዘፍጥረት 22፥18

የአብርሃም ዘር አሕዛብን ሁሉ እንደሚባርክ የተነገረው ተስፋ በኢየሱስ ተፈጽሟል፣ አዲስ ኪዳን (ገላትያ 3፡16) ኢየሱስን የተስፋው ዘር እንደሆነ ይገልጻል።

3. የይስሐቅ መስዋዕት (ዘፍ 22፥1-14)

አብርሃም ልጁን ይስሐቅን እንዲሠዋ ታዝዟል። እግዚአብሔር ግን ምትክ አውራ በግ አዘጋጀ።
ይህ ክስተት ኢየሱስን የኃጢአተኞችን ቦታ የሚወስድ የመሥዋዕቱ በግ እንደሆነ ያሳያል። ይስሐቅ ለመሥዋዕትነት የሚቀርበውን እንጨት ተሸክሞ መስቀሉን ከተሸከመው ኢየሱስ ጋር ሲመሳሰል ይታያል።


ይቀጥላል...



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍10🥰31
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#ቃልም_ሥጋ_ሆነ


“እነሆ፥ መልእክተኛዬን እልካለሁ፥ መንገድንም በፊቴ ያስተካክላል፤ እናንተም የምትፈልጉት ጌታ በድንገት ወደ መቅደሱ ይመጣል፤ የምትወዱትም የቃል ኪዳን መልእክተኛ፥ እነሆ፥ ይመጣል፥ ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር።”
             ሚልክያስ 3፥1


"ናሁ አነ እፌኑ መልእክየ ዘይጸይሕ ወይርኢ ፍኖትየ ቅድመ ገጽከ፡ ወይመጽእ ውስተ ጽርሑ ግብተ እግዚአብሔር ዘአንትሙ ተኀሥሡ መልአከ ሥርዓትየ ዘአንትሙ ትፈቅዱ፤ ናሁ ይመጽእ፡ ይቤ እግዚአብሔር ዘኵሎ ይመልክ።"
                 ሚልክያስ 3፥1

“Kunoo ani ergamaa koo isa fuula koo duraan karaa naaf qopheessu nan erga. Ergasii Gooftaan isin eeggattan akkuma tasaa gara mana qulqullummaa isaa ni dhufa; ergamaan kakuu kan isin hawwitan sun ni dhufa” jedha Waaqayyo Waan Hunda Dandaʼu.
                 Miilkiyaas 3:1

"እንሆ፣ ኣነ ልኡኸይ እልእኽ ኣሎኹ፣ ንሱ ቐቅድመይ መገዲ ኺጸርግ እዩ። ብኡብኡ ኸኣ እቲ እትደልይዎ ጐይታ ናብ መቕደሱ ኺመጽእ እዩ፣ እቲ እትናፍቕዎ መልኣኽ ቃል ኪዳን እንሆ፣ ይመጽእ ኣሎ፣ ይብል እግዚኣብሄር ጐይታ ሰራዊት።"
              ሚልክያስ 3፥1



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
1
.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“ነገር ግን ለዚህ ዓለም ከሚመችና የአሮጊቶችን ሴቶች ጨዋታ ከሚመስለው ተረት ራቅ። እግዚአብሔርን ለመምሰል ግን ራስህን አስለምድ።”
1ኛ ጢሞቴዎስ 4፥7



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
11👍4
በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ ጌታችንንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከግብፅ ተመልሶ ወይም ተጠርቶ በእስራኤል እንደሚኖር ትንቢት የተናገረው ነቢይ ማን ነው?
Anonymous Quiz
13%
ሀ. ኤርምያስ
42%
ለ. ኢሳይያስ
23%
ሐ. ሆሴዕ
13%
መ. ሚክያስ
9%
ሠ. ዘካርያስ
👍52👏2
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#ቃልም_ሥጋ_ሆነ


“ስለዚህ ጌታ ራሱ ምልክት ይሰጣችኋል፤ እነሆ፥ ድንግል ትፀንሳለች፥ ወንድ ልጅም ትወልዳለች፥ ስሙንም አማኑኤል ብላ ትጠራዋለች።”
             ኢሳይያስ 7፥14

"ናሁኬ በእንተ ዝንቱ ይሁበክሙ እግዚአብሔር ትእምርተ፤ ናሁ ድንግል ትፀንስ፡ ወትወልድ ወልደ፡ ወትሰምዮ ስሞ፦ አማኑኤል።"
ኢሳይያስ 7፥14

"Kanaafuu Gooftaan mataan isaa mallattoo isiniif kenna: Kunoo durbi tokko ni ulfoofti; ilma ni deessi; Amaanuʼel jettees isa moggaafti."
Isaayyaas 7:14

"ስለዚ እግዚኣብሄር ባዕሉ ትእምርቲ ኺህበኩም እዩ፡ እንሆ፡ ድንግል ክትጠንስ፡ ወዲ ኸኣ ክትወልድ እያ፡ ስሙውን ኣማኑኤል ክትሰምዮ እያ።"
ኢሳይያስ 7፥14




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍3
የጊዜ ቀመራችሁ እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር ለሆነ የቻናላችን ቤተሰቦች እንኳን ለጌታችን እና ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ!
🎄መልካም በዓል🎄

ከዚህ ጋር በተያያዘ የጌታችን ልደት ለምን ሁለት የተለያዩ ቀናት እንደሚከበር (December 25 እና January 7) ከአፍታ ቆይታ በኋላ እንመለስበታለን።




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍52
.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“አምላክህ እግዚአብሔር መሐሪ አምላክ ነውና አይተውህም፥ አያጠፋህምም፥ ለአባቶችህም የማለላቸውን ቃል ኪዳኑን አይረሳም።”
ዘዳግም 4፥31



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
🔥62
ለምን የጌታችን ልደት በተለያየ ቀን ይከበራል?


በክርስቲያናዊ ቤተ እምነቶች መካከል ባለው የቀን መቁጠሪያ ስርዓት እና ወግ ልዩነት ምክንያት የጌታችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በተለያዩ ቀናቶች ማለትም እ.ኤ.አ ዲሴምበር 25 እና ጃንዋሪ 7 (ታህሳስ 28/29) ይከበራል።

ዲሴምበር 25

የሮማ ካቶሊክ እና የፕሮቴስታንት እምነት ተከታዮችን ጨምሮ አብዛኞቹ የምዕራባውያን አብያተ ክርስቲያናት እንደ ጎርጎሪዮስ አቆጣጠር ዲሴምበር 25 የገናን በዓል ያከብራሉ። ይህ ቀን ለበዓልነት የተወሰነው በክርስትና የመጀመሪያዎቹ ክፍለ ዘመናት ውስጥ ነው፤ ምናልባትም በየክረምቱ አካባቢ ከሚከበሩ አረማዊ በዓላት ጋር ሰው ወደ ክርስትና ሲመጣ እንዳይቸገር ለማስማማት ወይም ለመተካት ሊሆን እንደሚችል ይገመታል። የዲሴምበር 25 የቀን ምርጫ በመጀመሪያ የተጠቀሰው በአራተኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ ላይ በሮም አልማናክ ውስጥ ነው።

ጃንዋሪ 7

እንደ ሩሲያ፣ ጆርጂያ እና ሰርቢያ ያሉ ብዙ የምስራቅ ኦርቶዶክስ አብያተ ክርስቲያናት እና የኢትዮጵያና የኤርትራ አብያተ ክርስቲያናት ገናን ጃንዋሪ 7 ያከብራሉ። በአሁኑ ጊዜ፣ በጁሊያን እና በጎርጎርዮስ አቆጣጠር መካከል የ13 ቀናት ልዩነት አለ፣ ይህም ገናን በጁሊያን ዲሴምበር 25 በጎርጎሪያን ጃንዋሪ 7 ጋር እንዲሆን አድርጎታል።

የዘመን አቆጣጠር ልዩነት

እ.ኤ.አ 1582 ጳጳስ ጎርጎርዮስ 12ኛ ያስተዋወቀው የጎርጎርዮስ አቆጣጠር፣ በጁሊያን አቆጣጠር ከፀሐይ ዓመት ጋር በተሻለ ሁኔታ እንዲጣጣም በጁሊያን አቆጣጠር ውስጥ የተስተዋሉ ስህተቶችን አስተካክሏል። ብዙ አገሮች እና አብያተ ክርስቲያናት የጎርጎሪያንን የቀን አቆጣጠር ሲከተሉ፣ በርካታ የምስራቅ ኦርቶዶክስ አብያተ ክርስቲያናት የጁሊያን የቀን መቁጠሪያን ለሃይማኖታዊ በዓላት ይጠቀማሉ። ይህም አሁን የምንመለከተውን የሚመስል የቀናት ልዩነትን አስከትሏል።

በቀጣይ የጎርጎርዮሳዊን እና የጁሊያን የዘመን አቆጣጠር ዋና ዋና ልዩነቶችን እንመለከታለን


ይቀጥላል...



ምንጭ፦ www.biblicalarchaeology.org


ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
5🔥1👏1
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#ቃልም_ሥጋ_ሆነ


“መልአኩም መልሶ እንዲህ አላት፦ መንፈስ ቅዱስ በአንቺ ላይ ይመጣል፥ የልዑልም ኃይል ይጸልልሻል ስለዚህ ደግሞ ከአንቺ የሚወለደው ቅዱስ የእግዚአብሔር ልጅ ይባላል።”
              ሉቃስ 1፥35


ወአውሥአ መልአክ ወይቤላ፦ “መንፈሰ እግዚአብሔር ቅዱስ ይመጽእ ላዕሌኪ ወኀይለ ልዑል ይጼልለኪ ወዘኒ ይትወለድ እምኔኪ ቅዱስ ውእቱ ወይሰመይ ወልደ እግዚአብሔር ልዑል።
ሉቃስ 1፥35

Ergamaan sunis akkana jedhee deebiseef; “Hafuurri Qulqulluun sirra buʼa; humni Waaqa Waan Hundaa Oliis si golbooba. Kanaaf inni qulqulluun dhalatu sun Ilma Waaqaa ni jedhama.”
Luqaas 1:35


እቲ መልኣኽ ከኣ መሊሱ፡ መንፈስ ቅዱስ ኪወርደኪ ሓይሊ ልዑልውን ኬጽልለኪ እዩ። ስለዚኸኣ እቲ ዚውለድ ቅዱስ፡ ወዲ ኣምላኽ ኪብሃል እዩ።
ሉቃስ 1፥35




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍2