. ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“አምላክህ እግዚአብሔር፥ ታላቅና የሚያስፈራ አምላክ፥ በመካከልህ ነውና ከእነርሱ የተነሣ አትደንግጥ።”
ዘዳግም 7፥21
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“አምላክህ እግዚአብሔር፥ ታላቅና የሚያስፈራ አምላክ፥ በመካከልህ ነውና ከእነርሱ የተነሣ አትደንግጥ።”
ዘዳግም 7፥21
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤8👍2🔥1
ቅዱሳት መጻሕፍት
ነቢዩ ኤርምያስ ክፍል-፰ መሲሓዊ ትንቢትን በተመለከተም ኤርምያስ መሲሓዊውን ጊዜ በዝርዝር አይገልጽም፡፡ የመሲሑ ማንነት በመጽሐፉ ላይ በጒልሕ አልተመለከተም፡፡ ይሁን እንጂ ኤርምያስ አንዳንድ ፋይዳ ያላቸውን መሲሓውያን ምንባቦች ይሰጣል ፡- 1. ከኪዳኑ ታቦት የላቀ የእግዚአብሔር መገለጥ እውን እንድሚሆን መታወጁ (3፥14-17) 2. የዐዲሱ ኪዳን መገለጥ…
ነቢዩ ኤርምያስ
ክፍል-፱
መላው ሕዝብ ቢቃወመውም እንኳ፣ ኤርምያስ የተለየ የድፍረት ሰው እንደ ነበርና ሳያወለውል የእግዚአብሔርን እውነት ለማወጅ የቈረጠ ጀግና እንደ ነበር ብዙ ጊዜ እንዘነጋለን፡፡ ይህን አቋሙን ጠብቆ የኖረው ከፍተኛ የሆነ አእምሮኣዊና አካላዊ ዋጋ በመክፈል ነው፡፡ ሕዝቡ ሳያውላውሉ ወደ አደጋ ሲጣደፉ፣ እርሱ ሁኔታውን ለመለወጥ ዐቅመ ቢስ መሆኑ ሲሰማው ለጥቅማቸው ሲል ትንቢት ከሚናገርላቸው ወገኖች ዘንድ በሚመጣውና በማያቋርጠው ተቃውሞአቸው ውስጥ ሲያልፍ፣ የልቡና የአእምሮው ሥቃይ የቱን ያህል ከባድ እንደሚሆን እንግዲህ ዐስቡት፡፡ እነዚህ ተግዳሮቶችና ፈተናዎች ምንጊዜም ከታላላቅ መንፈሳውያን ጀግኖች ውስጥ እንዲታይ አድርገው ቀረጹት፡፡ ፈሪ ሰው ስለ ነበር ተስፋ ለመቊረጥና አበቃልኝ ለማለት ተጋልጦ ነበር፡፡ ጌታ ትንቢቱ የቱን ያህል ፋይዳ እንዳለው ለማሳየት አንዳች ምልክት ወይም ታምር አልሰጠውም፡፡ በሕይወቱ ዘመን በአንድ ወቅት ኤርምያስ ዐደራውን ለመተው ወስኖ ነበር (20፥8-9)። ነገር ግን በውስጡ የሚሰማው መለኮታዊ አስገዳጅነት ይህን እንዲፈጽም አልፈቀደለትም፡፡ እግዚአብሔር የብረት ዐምድና (ምሰሶና) የነሐስ ቅጥር እንደሚያደርገው ቃል ገብቶለታል፤ እርሱ ደግሞ ቃሉን አያጥፍም፡፡
ከእግዚአብሔር ጋር ረዘም ያለ ውይይት ማካሄድ ለኤርምያስ የተለመደ ባሕርይ ነበር፡፡ እነዚህ ውይይቶች በመርሕ ደረጃ ዋጋ ያላቸው ናቸው፤ ምክንያቱም ውይይቶቹ ኤርምያስ (በተመሳሳይ ሁኔታ የነበሩት ሌሎች ነቢያትም) የግል ግንዛቤውንና የእግዚአብሔርን መልእክት እንዴት ለይቶ እንዳስቀመጠ ያሳያሉና (ከ12፥1-6፤ ከ1፥47 ፤ ከ15፥21 ጋር ያነጻ)፡፡
ኤርምያስ በጠላቶቹ ላይ የበቀል ርምጃ እንዲወስድ ወደ እግዚአብሔር ልመና በማቅረቡ አንዳንድ ተንታኞች ድንጋጤያቸውን ገልጸዋል፤ በእነርሱ ዐይን ይህ በሕይወቱ ላይ ጒልሕ ጒድለት ነው፡፡ እነዚህ ልመናዎች ግን በመዝሙረ ዳዊት ላይ እንደሚገኙት ያሉ ናቸውና የሚብራሩት በዚሁ መልክ ነው፤ ስለዚህ የግል በቀልን እንደሚመለከቱ ሆነው መታየት የለባቸውም፡፡ የእግዚአብሔር መልእክተኛ እንደ ነበር ኤርምያስ ያውቃል፤ ስለዚህ እርሱን የሚያጠቁ ሁሉ የእግዚአብሔር ጠላቶች በመሆን ራሳቸውን ያደራጁ ነበር፡፡ ኤርምያስ ለአምላኩ የነበረው ጥብቅ ታማኝነትና የመለኮት ጽድቅ አሸናፊ ሆኖ እንዲታይ የነበረው ናፍቆት፣ የጌታ ክብር ይገለጥ ዘንድ እነዚህ ርግማኖች ከአፉ በወጡ ጊዜ፣ ነቢዩ ግላዊ ፍላጎት እንዳልነበረው ያሳያሉ፤ ከዚህም በላይ የብሉይ ኪዳን ቅዱሳን ስለሚመጣው ተገቢ ቅጣት ግልጽ የሆነ ራእይ አልነበራቸውም፡፡
የእግዚአብሔርን ሰው እንደ ጸሎት ሕይወቱ ማንነቱን ገልጦ የሚያሳይ ሌላ ነገር የለም፡፡ በጸሎትና በጌታ ፊት ግልጽ በመሆን ዐውድ ውስጥ ኤርምያስ ኖረ፤ ሥራውን አከናወነ፤ አለቀሰም፡፡ መንገዳቸውን ለሳቱት ወገኖቹ አጥብቆ ይማልድ ነበርና እግዚአብሔር እንዲህ ያለውን ድርጊቱን ነቀፈበት (7 ፥ 16፤ 11፥14፤ 14፥11)፡፡ በጸሎቱም ውስጥ ራሱን ጨምሮአል፦ 11 ፥ 18-20 12 ፥ 1-4 ፤ 15፥ 10:15-18፤ 17፥14- 18: 18-19-23 20:7-11: 14-18 ላይ ያሉት ምንባቦች የኤርምያስ ኑዛዜዎች በመባል ይታወቃሉ፡፡ በእነዚህ ውስጥ የማንኛውም የእስራኤል ነቢይ ግልጥልጥ ያሉ ሐሳቦች ይገኛሉ፡፡ ሌሎች ነቢያት ተመክሮአቸውን ይተርካሉ፤ ይሁን እንጂ ብሉይ ኪዳን እንደዚህ ራስን የሚያጋልጡ ጸሎቶች ያሉት በቊጥር ነው:: በእነዚህ ኑዛዜዎች ውስጥ ተሰባሪ ሰውነቱ ይታያል፤ ለሕዝቡ ያለው ፍቅር፣ ለእግዚአብሔር ፈቃድና ጥሪ ያለው ታማኝነትም በእነዚህ ኑዛዜዎች ውስጥ ይታያሉ፡፡
ይቀጥላል...
ምንጭ፦ የብሉይ ኪዳን ማብራሪያ፤ ገጽ 828
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ክፍል-፱
መላው ሕዝብ ቢቃወመውም እንኳ፣ ኤርምያስ የተለየ የድፍረት ሰው እንደ ነበርና ሳያወለውል የእግዚአብሔርን እውነት ለማወጅ የቈረጠ ጀግና እንደ ነበር ብዙ ጊዜ እንዘነጋለን፡፡ ይህን አቋሙን ጠብቆ የኖረው ከፍተኛ የሆነ አእምሮኣዊና አካላዊ ዋጋ በመክፈል ነው፡፡ ሕዝቡ ሳያውላውሉ ወደ አደጋ ሲጣደፉ፣ እርሱ ሁኔታውን ለመለወጥ ዐቅመ ቢስ መሆኑ ሲሰማው ለጥቅማቸው ሲል ትንቢት ከሚናገርላቸው ወገኖች ዘንድ በሚመጣውና በማያቋርጠው ተቃውሞአቸው ውስጥ ሲያልፍ፣ የልቡና የአእምሮው ሥቃይ የቱን ያህል ከባድ እንደሚሆን እንግዲህ ዐስቡት፡፡ እነዚህ ተግዳሮቶችና ፈተናዎች ምንጊዜም ከታላላቅ መንፈሳውያን ጀግኖች ውስጥ እንዲታይ አድርገው ቀረጹት፡፡ ፈሪ ሰው ስለ ነበር ተስፋ ለመቊረጥና አበቃልኝ ለማለት ተጋልጦ ነበር፡፡ ጌታ ትንቢቱ የቱን ያህል ፋይዳ እንዳለው ለማሳየት አንዳች ምልክት ወይም ታምር አልሰጠውም፡፡ በሕይወቱ ዘመን በአንድ ወቅት ኤርምያስ ዐደራውን ለመተው ወስኖ ነበር (20፥8-9)። ነገር ግን በውስጡ የሚሰማው መለኮታዊ አስገዳጅነት ይህን እንዲፈጽም አልፈቀደለትም፡፡ እግዚአብሔር የብረት ዐምድና (ምሰሶና) የነሐስ ቅጥር እንደሚያደርገው ቃል ገብቶለታል፤ እርሱ ደግሞ ቃሉን አያጥፍም፡፡
ከእግዚአብሔር ጋር ረዘም ያለ ውይይት ማካሄድ ለኤርምያስ የተለመደ ባሕርይ ነበር፡፡ እነዚህ ውይይቶች በመርሕ ደረጃ ዋጋ ያላቸው ናቸው፤ ምክንያቱም ውይይቶቹ ኤርምያስ (በተመሳሳይ ሁኔታ የነበሩት ሌሎች ነቢያትም) የግል ግንዛቤውንና የእግዚአብሔርን መልእክት እንዴት ለይቶ እንዳስቀመጠ ያሳያሉና (ከ12፥1-6፤ ከ1፥47 ፤ ከ15፥21 ጋር ያነጻ)፡፡
ኤርምያስ በጠላቶቹ ላይ የበቀል ርምጃ እንዲወስድ ወደ እግዚአብሔር ልመና በማቅረቡ አንዳንድ ተንታኞች ድንጋጤያቸውን ገልጸዋል፤ በእነርሱ ዐይን ይህ በሕይወቱ ላይ ጒልሕ ጒድለት ነው፡፡ እነዚህ ልመናዎች ግን በመዝሙረ ዳዊት ላይ እንደሚገኙት ያሉ ናቸውና የሚብራሩት በዚሁ መልክ ነው፤ ስለዚህ የግል በቀልን እንደሚመለከቱ ሆነው መታየት የለባቸውም፡፡ የእግዚአብሔር መልእክተኛ እንደ ነበር ኤርምያስ ያውቃል፤ ስለዚህ እርሱን የሚያጠቁ ሁሉ የእግዚአብሔር ጠላቶች በመሆን ራሳቸውን ያደራጁ ነበር፡፡ ኤርምያስ ለአምላኩ የነበረው ጥብቅ ታማኝነትና የመለኮት ጽድቅ አሸናፊ ሆኖ እንዲታይ የነበረው ናፍቆት፣ የጌታ ክብር ይገለጥ ዘንድ እነዚህ ርግማኖች ከአፉ በወጡ ጊዜ፣ ነቢዩ ግላዊ ፍላጎት እንዳልነበረው ያሳያሉ፤ ከዚህም በላይ የብሉይ ኪዳን ቅዱሳን ስለሚመጣው ተገቢ ቅጣት ግልጽ የሆነ ራእይ አልነበራቸውም፡፡
የእግዚአብሔርን ሰው እንደ ጸሎት ሕይወቱ ማንነቱን ገልጦ የሚያሳይ ሌላ ነገር የለም፡፡ በጸሎትና በጌታ ፊት ግልጽ በመሆን ዐውድ ውስጥ ኤርምያስ ኖረ፤ ሥራውን አከናወነ፤ አለቀሰም፡፡ መንገዳቸውን ለሳቱት ወገኖቹ አጥብቆ ይማልድ ነበርና እግዚአብሔር እንዲህ ያለውን ድርጊቱን ነቀፈበት (7 ፥ 16፤ 11፥14፤ 14፥11)፡፡ በጸሎቱም ውስጥ ራሱን ጨምሮአል፦ 11 ፥ 18-20 12 ፥ 1-4 ፤ 15፥ 10:15-18፤ 17፥14- 18: 18-19-23 20:7-11: 14-18 ላይ ያሉት ምንባቦች የኤርምያስ ኑዛዜዎች በመባል ይታወቃሉ፡፡ በእነዚህ ውስጥ የማንኛውም የእስራኤል ነቢይ ግልጥልጥ ያሉ ሐሳቦች ይገኛሉ፡፡ ሌሎች ነቢያት ተመክሮአቸውን ይተርካሉ፤ ይሁን እንጂ ብሉይ ኪዳን እንደዚህ ራስን የሚያጋልጡ ጸሎቶች ያሉት በቊጥር ነው:: በእነዚህ ኑዛዜዎች ውስጥ ተሰባሪ ሰውነቱ ይታያል፤ ለሕዝቡ ያለው ፍቅር፣ ለእግዚአብሔር ፈቃድና ጥሪ ያለው ታማኝነትም በእነዚህ ኑዛዜዎች ውስጥ ይታያሉ፡፡
ይቀጥላል...
ምንጭ፦ የብሉይ ኪዳን ማብራሪያ፤ ገጽ 828
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍9❤2👏1
በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ በብሉይ ኪዳን ካሉት ነቢያቶች መካከል "የእግዚአብሔር ቀን" የሚለውን ሐረግ በተደጋጋሚ በመጠቀም የሚታወቀው ነቢይ የቱ ነው?
Anonymous Quiz
6%
ሀ. ዮናስ
30%
ለ. ኤርምያስ
14%
ሐ. ሐጌ
41%
መ. ኢዩኤል
9%
ሠ. ናሆም
👍7
. ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“ስለዚህ የምወደውንና የታመነውን በጌታ ልጄ የሆነውን ጢሞቴዎስን ልኬላችኋለሁ፥ እኔም በየስፍራው በአብያተ ክርስቲያናት ሁሉ እንደማስተምር በክርስቶስ ኢየሱስ የሚሆነውን መንገዴን እርሱ ያሳስባችኋል።”
1ኛ ቆሮንቶስ 4፥17
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“ስለዚህ የምወደውንና የታመነውን በጌታ ልጄ የሆነውን ጢሞቴዎስን ልኬላችኋለሁ፥ እኔም በየስፍራው በአብያተ ክርስቲያናት ሁሉ እንደማስተምር በክርስቶስ ኢየሱስ የሚሆነውን መንገዴን እርሱ ያሳስባችኋል።”
1ኛ ቆሮንቶስ 4፥17
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍6❤3
#እራሳችንን_እንመርምር
በሕይወት ውጣውረድ ነፍሳችን ስትናወጥ፣ የሕይወት ውሉ ሲጠፋ በአእምሯችን ውልብ ከማለት አልፎ ሰቅዘው የሚይዙን ጥያቄዎች ይበዛሉ። ከእነዚህ አንዱ "በዚህ ሁኔታ ውስጥ እግዚአብሔር አለ ወይ"፣ "እግዚአብሔር ለምን ዝም ይላል"፣ "ለምን እንደዚህ አይነት ነገር በሕይወቴ መጣ?"፣ "የእግዚአብሔር አሳብ ምንድነው"... እያልን በጥያቄዎች እንኳትናለን። ታዲህ ለዚህ ምስቅልቅል መፍትሄው ምን ይሆን? ቅዱሳት መጻሕፍትስ ምን ይላሉ?
“ሁሉን ታደርግ ዘንድ ቻይ እንደ ሆንህ፥ አሳብህም ይከለከል ዘንድ ከቶ እንደማይቻል አወቅሁ።”
ኢዮብ 42፥2
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
በሕይወት ውጣውረድ ነፍሳችን ስትናወጥ፣ የሕይወት ውሉ ሲጠፋ በአእምሯችን ውልብ ከማለት አልፎ ሰቅዘው የሚይዙን ጥያቄዎች ይበዛሉ። ከእነዚህ አንዱ "በዚህ ሁኔታ ውስጥ እግዚአብሔር አለ ወይ"፣ "እግዚአብሔር ለምን ዝም ይላል"፣ "ለምን እንደዚህ አይነት ነገር በሕይወቴ መጣ?"፣ "የእግዚአብሔር አሳብ ምንድነው"... እያልን በጥያቄዎች እንኳትናለን። ታዲህ ለዚህ ምስቅልቅል መፍትሄው ምን ይሆን? ቅዱሳት መጻሕፍትስ ምን ይላሉ?
“ሁሉን ታደርግ ዘንድ ቻይ እንደ ሆንህ፥ አሳብህም ይከለከል ዘንድ ከቶ እንደማይቻል አወቅሁ።”
ኢዮብ 42፥2
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤10👍5
. ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“እንደ ፈቃዱ ምክር ሁሉን የሚሠራ እንደ እርሱ አሳብ፥ አስቀድመን የተወሰንን በክርስቶስ ደግሞ ርስትን ተቀበልን።”
ኤፌሶን 1፥11
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“እንደ ፈቃዱ ምክር ሁሉን የሚሠራ እንደ እርሱ አሳብ፥ አስቀድመን የተወሰንን በክርስቶስ ደግሞ ርስትን ተቀበልን።”
ኤፌሶን 1፥11
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍8❤1🔥1
#ቃልም_ሥጋ_ሆነ
በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ፣ ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ፣ መሲሁ (የተቀባው) እና የዓለም አዳኝ እንደሆነ ማመን የክርስትና ዋና መሠረት እና ምሰሶ ነው። ከዚህ በታች የኢየሱስ ክርስቶስ ቁልፍ መግለጫዎች ከቅዱሳት መጻሕፍት በጥቂቱ እንመለከታለን፦
1. የእግዚአብሔር ልጅ
ኢየሱስ መለኮታዊ ማንነቱን በማሳየት የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ መጻሕፍት ይናገራሉ።
“... በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው አለ።”
ማቴዎስ 3፥17
2. መሲሕ (ክርስቶስ)
መጻሕፍት ኢየሱስ የብሉይ ኪዳንን ትንቢቶች የሚፈጽም ተስፋ የተደረገለት መሲሕ እንደሆነ ይገልጻሉ።
"ሴቲቱ፦ ክርስቶስ የሚባል መሲሕ እንዲመጣ አውቃለሁ፤ እርሱ ሲመጣ ሁሉን ይነግረናል አለችው። ኢየሱስ፦ የምናገርሽ እኔ እርሱ ነኝ አላት።"
ዮሐንስ 4፥25-26
3. የአለም አዳኝ
ኢየሱስ የሰውን ልጅ ከኃጢአት ለማዳን እና ከእግዚአብሔር ጋር ለማስታረቅ የመጣ አዳኝ እንደሆነ ቅዱሳት መጻሕፍት ይመሰክራሉ።
“በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ እግዚአብሔር አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ ወዶአልና።”
ዮሐንስ 3፥16
ይቀጥላል...
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ፣ ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ፣ መሲሁ (የተቀባው) እና የዓለም አዳኝ እንደሆነ ማመን የክርስትና ዋና መሠረት እና ምሰሶ ነው። ከዚህ በታች የኢየሱስ ክርስቶስ ቁልፍ መግለጫዎች ከቅዱሳት መጻሕፍት በጥቂቱ እንመለከታለን፦
1. የእግዚአብሔር ልጅ
ኢየሱስ መለኮታዊ ማንነቱን በማሳየት የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ መጻሕፍት ይናገራሉ።
“... በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው አለ።”
ማቴዎስ 3፥17
2. መሲሕ (ክርስቶስ)
መጻሕፍት ኢየሱስ የብሉይ ኪዳንን ትንቢቶች የሚፈጽም ተስፋ የተደረገለት መሲሕ እንደሆነ ይገልጻሉ።
"ሴቲቱ፦ ክርስቶስ የሚባል መሲሕ እንዲመጣ አውቃለሁ፤ እርሱ ሲመጣ ሁሉን ይነግረናል አለችው። ኢየሱስ፦ የምናገርሽ እኔ እርሱ ነኝ አላት።"
ዮሐንስ 4፥25-26
3. የአለም አዳኝ
ኢየሱስ የሰውን ልጅ ከኃጢአት ለማዳን እና ከእግዚአብሔር ጋር ለማስታረቅ የመጣ አዳኝ እንደሆነ ቅዱሳት መጻሕፍት ይመሰክራሉ።
“በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ እግዚአብሔር አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ ወዶአልና።”
ዮሐንስ 3፥16
ይቀጥላል...
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤19👍12😱1
. ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“ስለዚህ ወደ አምላክህ ተመለስ፤ ምሕረትንና ፍርድን ጠብቅ፥ ዘወትርም በአምላክህ ታመን።”
ሆሴዕ 12፥7
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“ስለዚህ ወደ አምላክህ ተመለስ፤ ምሕረትንና ፍርድን ጠብቅ፥ ዘወትርም በአምላክህ ታመን።”
ሆሴዕ 12፥7
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍11
የአዲስ_ኪዳን_የጥናት_መምሪያና_ማብራሪያ_1ኛ_መጽሐፍ.pdf
28.1 MB
👉ርዕስ፦ የአዲስ ኪዳን የጥናት መምሪያና ማብራሪያ 1ኛ መጽሐፍ፣
በትምህርተ መለኮት ማስፋፊያ (ት.መ.ማ) መልክ የተዘጋጀ
✍ጸሐፊ፦ ቲም ፌሎስ
🗣ትርጉም፦ ግርማዊ
🖨አሳታሚ፦ ኤስ.አይ.ኤም
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
በትምህርተ መለኮት ማስፋፊያ (ት.መ.ማ) መልክ የተዘጋጀ
✍ጸሐፊ፦ ቲም ፌሎስ
🗣ትርጉም፦ ግርማዊ
🖨አሳታሚ፦ ኤስ.አይ.ኤም
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍11❤7
በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ ጌታችን እና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሲወለድ በየእርከኑ መሪዎች እነማን ነበሩ?
Anonymous Quiz
39%
ሀ. የሮም ንጉሥ፦ ጲላጦስ ፣ የይሁዳ ገዢ፦ ታላቁ ሄሮድስ፣ ሊቀ ካህን፦ ቀያፋ
26%
ለ. የሮም ንጉሥ፦ አውግስጦስ ፣ የይሁዳ ገዢ፦ ታላቁ ሄሮድስ፣ ሊቀ ካህን፦ ሐና
16%
ሐ. የሮም ንጉሥ፦ ቀላውዴዎስ፣ የይሁዳ ገዢ፦ ታላቁ ሄሮድስ፣ ሊቀ ካህን፦ ዘካርያስ
19%
መ. የሮም ንጉሥ፦ ጢባርዮስ ፣ የይሁዳ ገዢ፦ ጲላጦስ ፣ ሊቀ ካህን፦ ሐናና ቀያፋ
👍8
. ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“በእምነት በኩል ሁላችሁ በክርስቶስ ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጆች ናችሁና፤”
ገላትያ 3፥26
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“በእምነት በኩል ሁላችሁ በክርስቶስ ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጆች ናችሁና፤”
ገላትያ 3፥26
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍7❤5
#ቃልም_ሥጋ_ሆነ
የኢየሱስ ክርስቶስ የማስተማር ዘይቤ እና ዘዴዎች
መቼስ ስለጌታችን ልደት ከማንሳታችን በፊት ስለማስተማሩ እና ምክሩ ቀድመን ማንሳት ግድ ይለናል።
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ያሉት የጌታችን እና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ትምህርቶች ቀለል በማለት፣ በሥልጣን እና በተዛምዶነታቸው ተለይተው የሚታወቁበትን ልዩ አቀራረብ ያሳያሉ። ጌታችን የተጠቀመባቸው ዘይቤዎችና ዘዴዎች እነሆ፡-
1. ምሳሌዎች
ኢየሱስ ብዙ ጊዜ ምሳሌዎችን ይጠቀም ነበር፤ እነዚህም ጥልቅ መንፈሳዊ እውነቶች ያሏቸው ቀላልና ተዛማጅ ታሪኮች ናቸው። ምሳሌዎች ውስብስብ ትምህርቶችን ተደራሽ እና የማይረሱ ያደረጓቸው ሲሆን እውነቶችን ለመቀበል ለማይፈልጉትንም ይጋርዱባቸው ነበር።
ምሳሌ፡-
👉የዘሪው ምሳሌ (ማቴዎስ 13፥3-9)
👉የደጉ ሳምራዊ ምሳሌ (ሉቃስ 10፥25–37)
2. ማብራሪያዎች እና ከዕለት ተዕለት ነገሮች ጋር የተያያዙ ትምህርቶች
ኢየሱስ ነጥቦቹን በምሳሌ ለማስረዳት የዕለት ተዕለት ነገሮችን ወይም ሁኔታዎችን ተጠቅሟል። ይህ ዘዴ በእይታ ቶሎ የሚገባቸውን ተማሪዎችን ይስባል ይህም ትምህርቶቹን ተግባራዊ የመሆን አቅማቸውንም ጨምሯል።
ምሳሌ፡-
👉የበለስ ዛፍ፣ እንደ እምነት እና የፍሬያማነት ትምህርት (ማር. 11፥12–14፥20–25)
👉"እኔ የወይኑ ግንድ ነኝ እናንተም ቅርንጫፎች ናችሁ" (ዮሐ. 15፥1-8)
3. ውይይት እና ጥያቄዎች
ኢየሱስ በጥልቅ እንዲያስቡ እና ራሳቸውን እንዲመረምሩ በማነሳሳት ጥያቄዎችን በመጠየቅ አድማጮቹን አሳትፏል።
ምሳሌ፡-
👉“እናንተስ እኔን ማን እንደ ሆንሁ ትላላችሁ?” (ማቴ. 16፥15)
👉"ሰው ዓለሙን ሁሉ ቢያተርፍ ነፍሱን ግን ቢያጐድል ምን ይጠቅመዋል?" (ማር. 8፥36 )
ይቀጥላል...
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የኢየሱስ ክርስቶስ የማስተማር ዘይቤ እና ዘዴዎች
መቼስ ስለጌታችን ልደት ከማንሳታችን በፊት ስለማስተማሩ እና ምክሩ ቀድመን ማንሳት ግድ ይለናል።
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ያሉት የጌታችን እና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ትምህርቶች ቀለል በማለት፣ በሥልጣን እና በተዛምዶነታቸው ተለይተው የሚታወቁበትን ልዩ አቀራረብ ያሳያሉ። ጌታችን የተጠቀመባቸው ዘይቤዎችና ዘዴዎች እነሆ፡-
1. ምሳሌዎች
ኢየሱስ ብዙ ጊዜ ምሳሌዎችን ይጠቀም ነበር፤ እነዚህም ጥልቅ መንፈሳዊ እውነቶች ያሏቸው ቀላልና ተዛማጅ ታሪኮች ናቸው። ምሳሌዎች ውስብስብ ትምህርቶችን ተደራሽ እና የማይረሱ ያደረጓቸው ሲሆን እውነቶችን ለመቀበል ለማይፈልጉትንም ይጋርዱባቸው ነበር።
ምሳሌ፡-
👉የዘሪው ምሳሌ (ማቴዎስ 13፥3-9)
👉የደጉ ሳምራዊ ምሳሌ (ሉቃስ 10፥25–37)
2. ማብራሪያዎች እና ከዕለት ተዕለት ነገሮች ጋር የተያያዙ ትምህርቶች
ኢየሱስ ነጥቦቹን በምሳሌ ለማስረዳት የዕለት ተዕለት ነገሮችን ወይም ሁኔታዎችን ተጠቅሟል። ይህ ዘዴ በእይታ ቶሎ የሚገባቸውን ተማሪዎችን ይስባል ይህም ትምህርቶቹን ተግባራዊ የመሆን አቅማቸውንም ጨምሯል።
ምሳሌ፡-
👉የበለስ ዛፍ፣ እንደ እምነት እና የፍሬያማነት ትምህርት (ማር. 11፥12–14፥20–25)
👉"እኔ የወይኑ ግንድ ነኝ እናንተም ቅርንጫፎች ናችሁ" (ዮሐ. 15፥1-8)
3. ውይይት እና ጥያቄዎች
ኢየሱስ በጥልቅ እንዲያስቡ እና ራሳቸውን እንዲመረምሩ በማነሳሳት ጥያቄዎችን በመጠየቅ አድማጮቹን አሳትፏል።
ምሳሌ፡-
👉“እናንተስ እኔን ማን እንደ ሆንሁ ትላላችሁ?” (ማቴ. 16፥15)
👉"ሰው ዓለሙን ሁሉ ቢያተርፍ ነፍሱን ግን ቢያጐድል ምን ይጠቅመዋል?" (ማር. 8፥36 )
ይቀጥላል...
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍7❤6🔥1
. ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“በመካከልሽም የዋህና ትሑት ሕዝብን አስቀራለሁ፤ በእግዚአብሔርም ስም ይታመናሉ።”
ሶፎንያስ 3፥12
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“በመካከልሽም የዋህና ትሑት ሕዝብን አስቀራለሁ፤ በእግዚአብሔርም ስም ይታመናሉ።”
ሶፎንያስ 3፥12
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤5👏1
#ቃልም_ሥጋ_ሆነ
የኢየሱስ ክርስቶስ የማስተማር ዘይቤ እና ዘዴዎች
4. በአጽንዖት መደጋገም
ኢየሱስ ተመልካቾቹ መልእክቱን እንዲገነዘቡ ለማድረግ አስፈላጊነት ያላቸውን ነገሮች ለማጉላት ብዙ ጊዜ ቁልፍ ጭብጦችን ይደጋግማል።
ምሳሌ፡-
👉“አትፍሩ” (ማቴ. 14፥27፣ ማር. 5፥36)
👉“መንግሥተ ሰማያት” የሚለው በወንጌሎች ውስጥ ተደጋግሟል
5. ግነትን
ኢየሱስ አንድን አሳብ የማይረሳ ለማድረግ አንዳንድ ጊዜ ግነትን ይጠቀም ነበር።
ምሳሌ፡-
👉“ቀኝ ዓይንህም ብታሰናክልህ አውጥተህ ከአንተ ጣላት” (ማቴ. 5፥29)
👉“ባለጠጋ ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ከሚገባ ግመል በመርፌ ቀዳዳ ቢገባ ይቀላል” (ማቴ. 19፥24)
6. ስልጣን እና የትንቢት ፍጻሜ
ኢየሱስ ያስተማረው በመለኮታዊ ሥልጣን ነው፣ ብዙውን ጊዜ ትምህርቶቹን ከሌሎች በመለየት “እውነት፣ እውነት” ወይም “እላችኋለሁ” በማለት መግለጫዎችን አስቀምጧል። እንዲሁም ትምህርቶቹን ከብሉይ ኪዳን ትንቢቶች ፍጻሜ ጋር ይያያዛሉ።
ምሳሌ፡-
👉" እንደ ተባለ ሰምታችኋል... እኔ ግን እላችኋለሁ..." (ማቴዎስ 5፥21-48)
👉" ዛሬ ይህ መጽሐፍ በጆሮአችሁ ተፈጸመ" (ሉቃስ 4፥21)
7. ርህራሄ እና አድማጮችን መረዳት
ኢየሱስ ጥልቅ ርኅራኄ እና መረዳትን በማሳየት ትምህርቱን ለተመልካቾች አድርሷል። ለግለሰቦችን እና ለቡድን ተደራሽ ለመሆን በተለየ ሁኔታ ጥሯል።
ምሳሌ፡-
👉ዳግመኛ መወለድን አስመልክቶ ለኒቆዲሞስ ሲናገር (ዮሐ. 3፡1-21)
👉ለሳምራዊቷ ሴት የሕይወትን ውኃ አቀረበ (ዮሐ. 4፡1-26)
ይቀጥላል...
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የኢየሱስ ክርስቶስ የማስተማር ዘይቤ እና ዘዴዎች
4. በአጽንዖት መደጋገም
ኢየሱስ ተመልካቾቹ መልእክቱን እንዲገነዘቡ ለማድረግ አስፈላጊነት ያላቸውን ነገሮች ለማጉላት ብዙ ጊዜ ቁልፍ ጭብጦችን ይደጋግማል።
ምሳሌ፡-
👉“አትፍሩ” (ማቴ. 14፥27፣ ማር. 5፥36)
👉“መንግሥተ ሰማያት” የሚለው በወንጌሎች ውስጥ ተደጋግሟል
5. ግነትን
ኢየሱስ አንድን አሳብ የማይረሳ ለማድረግ አንዳንድ ጊዜ ግነትን ይጠቀም ነበር።
ምሳሌ፡-
👉“ቀኝ ዓይንህም ብታሰናክልህ አውጥተህ ከአንተ ጣላት” (ማቴ. 5፥29)
👉“ባለጠጋ ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ከሚገባ ግመል በመርፌ ቀዳዳ ቢገባ ይቀላል” (ማቴ. 19፥24)
6. ስልጣን እና የትንቢት ፍጻሜ
ኢየሱስ ያስተማረው በመለኮታዊ ሥልጣን ነው፣ ብዙውን ጊዜ ትምህርቶቹን ከሌሎች በመለየት “እውነት፣ እውነት” ወይም “እላችኋለሁ” በማለት መግለጫዎችን አስቀምጧል። እንዲሁም ትምህርቶቹን ከብሉይ ኪዳን ትንቢቶች ፍጻሜ ጋር ይያያዛሉ።
ምሳሌ፡-
👉" እንደ ተባለ ሰምታችኋል... እኔ ግን እላችኋለሁ..." (ማቴዎስ 5፥21-48)
👉" ዛሬ ይህ መጽሐፍ በጆሮአችሁ ተፈጸመ" (ሉቃስ 4፥21)
7. ርህራሄ እና አድማጮችን መረዳት
ኢየሱስ ጥልቅ ርኅራኄ እና መረዳትን በማሳየት ትምህርቱን ለተመልካቾች አድርሷል። ለግለሰቦችን እና ለቡድን ተደራሽ ለመሆን በተለየ ሁኔታ ጥሯል።
ምሳሌ፡-
👉ዳግመኛ መወለድን አስመልክቶ ለኒቆዲሞስ ሲናገር (ዮሐ. 3፡1-21)
👉ለሳምራዊቷ ሴት የሕይወትን ውኃ አቀረበ (ዮሐ. 4፡1-26)
ይቀጥላል...
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍7❤5😁2
በቅዱሳት መጻሕፍት፣ በማቴዎስ እና በሉቃስ ወንጌል ውስጥ የጌታችን የዘረ ሐረግ ሲዘረዘር የዮሴፍ (የማርያም እጮኛ) አባት ማን ነበር?
Anonymous Quiz
23%
ሀ. በሁለቱም ወንጌላት ያዕቆብ
26%
ለ. በማቴዎስ፣ ያዕቆብ እና በሉቃስ፣ ኤሊ
7%
ሐ. በሁለቱ ወንጌላት ኤሊ
16%
መ. በማቴዎስ፣ ኤሊ እና በሉቃስ፣ ያዕቆብ
27%
ሠ. መልስ የለም
👍8
. ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“ወይም ይህ ወይም ያ ማናቸው እንዲበቅል ወይም ሁለቱ መልካም እንዲሆኑ አታውቅምና በማለዳ ዘርህን ዝራ፥ በማታም እጅህን አትተው።”
መክብብ 11፥6
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“ወይም ይህ ወይም ያ ማናቸው እንዲበቅል ወይም ሁለቱ መልካም እንዲሆኑ አታውቅምና በማለዳ ዘርህን ዝራ፥ በማታም እጅህን አትተው።”
መክብብ 11፥6
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
🔥3👏1
የአዲስ_ኪዳን_የጥናት_መምሪያና_ማብራሪያ_2ኛ_መጽሐፍ.pdf
42.8 MB
👉ርዕስ፦ የአዲስ ኪዳን የጥናት መምሪያና ማብራሪያ 2ኛ መጽሐፍ፣
በትምህርተ መለኮት ማስፋፊያ (ት.መ.ማ) መልክ የተዘጋጀ
✍ጸሐፊ፦ ቲም ፌሎስ
🗣ትርጉም፦ ግርማዊ
✏️እርማት፦ ፈቃዱ ገብሬ፣ ሰላመ አብ አሰፋ እና ይግረም ረታ
🖨አሳታሚ፦ ኤስ.አይ.ኤም
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
በትምህርተ መለኮት ማስፋፊያ (ት.መ.ማ) መልክ የተዘጋጀ
✍ጸሐፊ፦ ቲም ፌሎስ
🗣ትርጉም፦ ግርማዊ
✏️እርማት፦ ፈቃዱ ገብሬ፣ ሰላመ አብ አሰፋ እና ይግረም ረታ
🖨አሳታሚ፦ ኤስ.አይ.ኤም
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
🔥6❤3👍3
#የእግዚአብሔር_ቃል_ምን_ይላል?
መክብብ 11
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ እንጀራህን በውኃ ፊት ላይ ጣለው፥ ከብዙ ቀን በኋላ ታገኛዋለህና።
² ለሰባት ደግሞም ለስምንት እድል ፈንታን ክፈል፥ በምድር ላይ የሚሆነውን ክፉ ነገር ምን እንደሆነ አታውቅምና።
³ ደመናት ዝናብ በሞሉ ጊዜ በምድር ላይ ያፈስሱታል፤ ዛፍም ወደ ደቡብ ወይም ወደ ሰሜን ቢወድቅ፥ ዛፉ በወደቀበት ስፍራ በዚያ ይኖራል።
⁴ ነፋስን የሚጠባበቅ አይዘራም፥ ደመናንም የሚመለከት አያጭድም።
⁵ የነፋስ መንገድ እንዴት እንደ ሆነች አጥንትም በእርጉዝ ሆድ እንዴት እንድትዋደድ እንደማታውቅ፥ እንዲሁም ሁሉን የሚሠራውን የእግዚአብሔርን ሥራ አታውቅም።
⁶ ወይም ይህ ወይም ያ ማናቸው እንዲበቅል ወይም ሁለቱ መልካም እንዲሆኑ አታውቅምና በማለዳ ዘርህን ዝራ፥ በማታም እጅህን አትተው።
⁷ ብርሃን ጣፋጭ ነው ፀሐይንም ማየት ለዓይን መልካም ነው።
⁸ ሰው ብዙ ዘመን በሕይወት ቢኖር በሁሉም ደስ ይበለው፤ ሆኖም የጨለማውን ዘመን ያስብ፥ ብዙ ቀን ይሆናልና። የሚመጣው ነገር ሁሉ ከንቱ ነው።
⁹ አንተ ጐበዝ፥ በጕብዝናህ ደስ ይበልህ፥ በጕብዝናህም ወራት ልብህን ደስ ይበለው፥ በልብህም መንገድ ዓይኖችህም በሚያዩት ሂድ፤ ዳሩ ግን ስለዚህ ነገር ሁሉ እግዚአብሔር ወደ ፍርድ እንዲያመጣህ እወቅ።
¹⁰ ሕፃንነትና ጕብዝና ከንቱዎች ናቸውና ከልብህ ኀዘንን አርቅ፥ ከሰውነትህም ክፉን ነገር አስወግድ።
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
መክብብ 11
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ እንጀራህን በውኃ ፊት ላይ ጣለው፥ ከብዙ ቀን በኋላ ታገኛዋለህና።
² ለሰባት ደግሞም ለስምንት እድል ፈንታን ክፈል፥ በምድር ላይ የሚሆነውን ክፉ ነገር ምን እንደሆነ አታውቅምና።
³ ደመናት ዝናብ በሞሉ ጊዜ በምድር ላይ ያፈስሱታል፤ ዛፍም ወደ ደቡብ ወይም ወደ ሰሜን ቢወድቅ፥ ዛፉ በወደቀበት ስፍራ በዚያ ይኖራል።
⁴ ነፋስን የሚጠባበቅ አይዘራም፥ ደመናንም የሚመለከት አያጭድም።
⁵ የነፋስ መንገድ እንዴት እንደ ሆነች አጥንትም በእርጉዝ ሆድ እንዴት እንድትዋደድ እንደማታውቅ፥ እንዲሁም ሁሉን የሚሠራውን የእግዚአብሔርን ሥራ አታውቅም።
⁶ ወይም ይህ ወይም ያ ማናቸው እንዲበቅል ወይም ሁለቱ መልካም እንዲሆኑ አታውቅምና በማለዳ ዘርህን ዝራ፥ በማታም እጅህን አትተው።
⁷ ብርሃን ጣፋጭ ነው ፀሐይንም ማየት ለዓይን መልካም ነው።
⁸ ሰው ብዙ ዘመን በሕይወት ቢኖር በሁሉም ደስ ይበለው፤ ሆኖም የጨለማውን ዘመን ያስብ፥ ብዙ ቀን ይሆናልና። የሚመጣው ነገር ሁሉ ከንቱ ነው።
⁹ አንተ ጐበዝ፥ በጕብዝናህ ደስ ይበልህ፥ በጕብዝናህም ወራት ልብህን ደስ ይበለው፥ በልብህም መንገድ ዓይኖችህም በሚያዩት ሂድ፤ ዳሩ ግን ስለዚህ ነገር ሁሉ እግዚአብሔር ወደ ፍርድ እንዲያመጣህ እወቅ።
¹⁰ ሕፃንነትና ጕብዝና ከንቱዎች ናቸውና ከልብህ ኀዘንን አርቅ፥ ከሰውነትህም ክፉን ነገር አስወግድ።
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍5❤2