የሃኪሙ ሉቃስ ጹሑፎች የአጻጻፍ ስልት እና ይዘት
3. ዓለም አቀፋዊ ትኩረት
ሉቃስ የኢየሱስን ተልእኮ ዓለም አቀፋዊ እንደሆነ አጽንዖት ሰጥቷል፣ ይህም ለሁሉም ሰዎች ማለትም አሕዛብን፣ ሴቶችን፣ ድሆችን እና የተገለሉ ቡድኖችን ጨምሮ መቀላቀልን ያሳያል።
ምሳሌ፦ በሉቃስ ውስጥ ያለው የዘር ሐረግ የኢየሱስን የዘር ሐረግ ከአዳም ጀምሮ ያሳያል (ሉቃስ 3፥23-38)። ይህም ጌታችን እና መድኋኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የመጣው አይሁዳዊያንን ብቻ ሳይሆን የሰውን ዘር በሙሉ ለማዳን እንደመጣ ለማስገንዘብ ነው።
4. ለተገለሉ ቡድኖች ትኩረት መስጠት
ሉቃስ ስለሴቶች፣ ሳምራውያን፣ ቀራጮች እና ኃጢአተኞች ታሪኮችን በልዩ ሁኔታ አጉልቶ ያሳያል።
ምሳሌዎች፡- የደጉ ሳምራዊ ምሳሌ (ሉቃስ 10፥25–37)። ኃጢአተኛዋ ሴት ኢየሱስን ሽቶ ስለቀባችው ታሪክ (ሉቃስ 7፥36–50)።
5. በጸሎት እና በመንፈስ ቅዱስ ላይ ማተኮር
ሉቃስ ጸሎትን እና የመንፈስ ቅዱስን ሥራ በኢየሱስ ክርስቶስ ሕይወት እና በቀደመችው ቤተክርስቲያን ውስጥ በተደጋጋሚ ሁኔታ ትኩረት ሰጥቶ ያነሳዋል።
ምሳሌ፡- የኢየሱስ ጸሎት (ሉቃስ 3፥21፣ 5፥16፣ 6፥12፣ 22፥39–46)። በጰንጠቆስጤ የመንፈስ ቅዱስ መውረድ (ሐዋ. 2፡1-4)።
ይቀጥላል...
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
3. ዓለም አቀፋዊ ትኩረት
ሉቃስ የኢየሱስን ተልእኮ ዓለም አቀፋዊ እንደሆነ አጽንዖት ሰጥቷል፣ ይህም ለሁሉም ሰዎች ማለትም አሕዛብን፣ ሴቶችን፣ ድሆችን እና የተገለሉ ቡድኖችን ጨምሮ መቀላቀልን ያሳያል።
ምሳሌ፦ በሉቃስ ውስጥ ያለው የዘር ሐረግ የኢየሱስን የዘር ሐረግ ከአዳም ጀምሮ ያሳያል (ሉቃስ 3፥23-38)። ይህም ጌታችን እና መድኋኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የመጣው አይሁዳዊያንን ብቻ ሳይሆን የሰውን ዘር በሙሉ ለማዳን እንደመጣ ለማስገንዘብ ነው።
4. ለተገለሉ ቡድኖች ትኩረት መስጠት
ሉቃስ ስለሴቶች፣ ሳምራውያን፣ ቀራጮች እና ኃጢአተኞች ታሪኮችን በልዩ ሁኔታ አጉልቶ ያሳያል።
ምሳሌዎች፡- የደጉ ሳምራዊ ምሳሌ (ሉቃስ 10፥25–37)። ኃጢአተኛዋ ሴት ኢየሱስን ሽቶ ስለቀባችው ታሪክ (ሉቃስ 7፥36–50)።
5. በጸሎት እና በመንፈስ ቅዱስ ላይ ማተኮር
ሉቃስ ጸሎትን እና የመንፈስ ቅዱስን ሥራ በኢየሱስ ክርስቶስ ሕይወት እና በቀደመችው ቤተክርስቲያን ውስጥ በተደጋጋሚ ሁኔታ ትኩረት ሰጥቶ ያነሳዋል።
ምሳሌ፡- የኢየሱስ ጸሎት (ሉቃስ 3፥21፣ 5፥16፣ 6፥12፣ 22፥39–46)። በጰንጠቆስጤ የመንፈስ ቅዱስ መውረድ (ሐዋ. 2፡1-4)።
ይቀጥላል...
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍3❤1
#የእግዚአብሔር_ቃል_ምን_ይላል?
ኤርምያስ 23
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
³³ ይህ ሕዝብ ወይም ነቢይ ወይም ካህን፦ የእግዚአብሔር ሸክም ምንድር ነው? ብሎ ቢጠይቅህ፥ አንተ፦ ሸክሙ እናንተ ናችሁ፥ እጥላችሁማለህ፥ ይላል እግዚአብሔር ትላቸዋለህ።
³⁴ የእግዚአብሔር ሸክም የሚለውን ነቢይንና ካህንን ሕዝብንም ያን ሰውና ቤቱን እቀጣለሁ።
³⁵ አንዱም አንዱ ለባልንጀራው፥ አንዱም አንዱ ለወንድሙ እንዲህ ይበል፦ እግዚአብሔር የመለሰው ምንድር ነው? እግዚአብሔርስ ምን ነገር ተናገረ?
³⁶ ለሰው ሁሉ ቃሉ ሸክም ይሆንበታልና የእግዚአብሔር ሸክም ብላችሁ ከእንግዲህ ወዲህ አትጥሩ፤ የሠራዊትን ጌታ የአምላካችንን የእግዚአብሔርን የሕያውን አምላክ ቃል ለውጣችኋልና።
³⁷ ለነቢዩ፦ እግዚአብሔር ምን መለሰልህ? እግዚአብሔርስ የተናገረው ምንድር ነው? ትላለህ።
³⁸ ነገር ግን፦ የእግዚአብሔር ሸክም ብትሉ፥ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ እኔ፦ የእግዚአብሔር ሸክም አትበሉ ብዬ ልኬባችኋለሁና፥ እናንተም ይህን ቃል፦
³⁹ የእግዚአብሔር ሸክም ብላችኋልና ስለዚህ፥ እነሆ፥ ፈጽሜ እረሳችኋለሁ እናንተንም ለእናንተና ለአባቶቻችሁም የሰጠኋትን ከተማ ከፊቴ እጥላለሁ።
⁴⁰ የዘላለምንም ስድብ ከቶም ተረስቶ የማይጠፋውን የዘላለምን እፍረት አመጣባችኋለሁ።
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ኤርምያስ 23
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
³³ ይህ ሕዝብ ወይም ነቢይ ወይም ካህን፦ የእግዚአብሔር ሸክም ምንድር ነው? ብሎ ቢጠይቅህ፥ አንተ፦ ሸክሙ እናንተ ናችሁ፥ እጥላችሁማለህ፥ ይላል እግዚአብሔር ትላቸዋለህ።
³⁴ የእግዚአብሔር ሸክም የሚለውን ነቢይንና ካህንን ሕዝብንም ያን ሰውና ቤቱን እቀጣለሁ።
³⁵ አንዱም አንዱ ለባልንጀራው፥ አንዱም አንዱ ለወንድሙ እንዲህ ይበል፦ እግዚአብሔር የመለሰው ምንድር ነው? እግዚአብሔርስ ምን ነገር ተናገረ?
³⁶ ለሰው ሁሉ ቃሉ ሸክም ይሆንበታልና የእግዚአብሔር ሸክም ብላችሁ ከእንግዲህ ወዲህ አትጥሩ፤ የሠራዊትን ጌታ የአምላካችንን የእግዚአብሔርን የሕያውን አምላክ ቃል ለውጣችኋልና።
³⁷ ለነቢዩ፦ እግዚአብሔር ምን መለሰልህ? እግዚአብሔርስ የተናገረው ምንድር ነው? ትላለህ።
³⁸ ነገር ግን፦ የእግዚአብሔር ሸክም ብትሉ፥ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ እኔ፦ የእግዚአብሔር ሸክም አትበሉ ብዬ ልኬባችኋለሁና፥ እናንተም ይህን ቃል፦
³⁹ የእግዚአብሔር ሸክም ብላችኋልና ስለዚህ፥ እነሆ፥ ፈጽሜ እረሳችኋለሁ እናንተንም ለእናንተና ለአባቶቻችሁም የሰጠኋትን ከተማ ከፊቴ እጥላለሁ።
⁴⁰ የዘላለምንም ስድብ ከቶም ተረስቶ የማይጠፋውን የዘላለምን እፍረት አመጣባችኋለሁ።
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍5❤1👎1
. ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“በእውነት ኤፍሬም ለእኔ የከበረ ልጅ ነውን? ወይስ የተወደደ ሕፃን ነውን? በእርሱ ላይ በተናገርሁ ቍጥር አስበዋለሁ፤ ስለዚህ አንጀቴ ታወከችለት ርኅራኄም እራራለታለሁ፥ ይላል እግዚአብሔር።”
ኤርምያስ 31፥20
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“በእውነት ኤፍሬም ለእኔ የከበረ ልጅ ነውን? ወይስ የተወደደ ሕፃን ነውን? በእርሱ ላይ በተናገርሁ ቍጥር አስበዋለሁ፤ ስለዚህ አንጀቴ ታወከችለት ርኅራኄም እራራለታለሁ፥ ይላል እግዚአብሔር።”
ኤርምያስ 31፥20
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍6
#ከተማ_ወይም_ቦታ_በቅዱሳት_መጻሕፍት
#ጊብዓ
ጊብዓ፤ ጉብታ ወይም ኮረብታ ማለት ነው።
1. በይሁዳ የነበረ ከተማ። ኢያሱ 15፥57።
2. ከኢየሩሳሌም ወደ ሰሜን አምስት ኪ.ሜ. ያህል ርቆ የሚገኝ የብንያም አገር ከተማ። የብንያም ጊብዓ በአሁን ጊዜ ከኢየሩሳሌም በስተሰሜን የምትገኝ ዘመናዊቷ ቴል ኤል ፉል ላይ እንደነበረች ይገመታል። የአርኪኦሎጂ ቁፋሮዎች የጥንት ምሽግ ቅሪቶችን በቁፋሮ አግኝተዋል፣ ይህም ግምቶችን እውነተኛ ሊሆኑ እንድሚችሉ አረጋግጧል።
የጊብዓ ሰዎች አስጸያፊ ብልግና ስላደረጉ እስራኤላውያን የብንያምን ወገን ለማጥፋት ተነሡ፤ ሆኖም 600 ሰዎች አምልጠዋል፤ መሳ. 19፥11-20፡48። ግን ንጉሥ ሳኦል የጊብዓ ሰው ነበረና መናገሻ ከተማውን በጊብዓ አደረገ፤ 1ሳሙ. 10፥26፤ 22፥6። በብሉይ ኪዳን ዘመን ጊብዓ ምሽግ ከተማ ነበረ፤ ከክርስቶስ ልደት ወዲህ ግን ባድማ ሆኗል።
ጊብዓ የምትታወቅባቸው ዋና ዋና የታሪክ ሁነቶች፦
👉የሌዋዊው ቁባት በጊብዓ ሰዎች በተፈጸመባት አሳቃቂ ግፍ የደረሰው ቁጣና ያስከተለው መዘዝ (መሳ. ምዕራፍ 19-21)
👉ጊብዓ የእስራኤል የመጀመሪያው ንጉሥ የንጉሥ ሳኦል የትውልድ ከተማ ነበረች። (1ኛ ሳሙኤል 10፥26፤ 1ሳሙ 15፥34-35)
👉የጊብዓ ትንቢታዊ ውግዘቶች፡- ነብያት ከጊዜ በኋላ ጊብዓን በመሳፍንት ውስጥ በተመዘገቡት ድርጊቶች ምክንያት የእስራኤል የሥነ ምግባር ውድቀት ምልክት እንደሆነች ጠቅሰዋል። (ሆሴዕ 9፥9፤ ሆሴዕ 10፥9።
ምንጭ፦ የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት፤ ገጽ 242
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
#ጊብዓ
ጊብዓ፤ ጉብታ ወይም ኮረብታ ማለት ነው።
1. በይሁዳ የነበረ ከተማ። ኢያሱ 15፥57።
2. ከኢየሩሳሌም ወደ ሰሜን አምስት ኪ.ሜ. ያህል ርቆ የሚገኝ የብንያም አገር ከተማ። የብንያም ጊብዓ በአሁን ጊዜ ከኢየሩሳሌም በስተሰሜን የምትገኝ ዘመናዊቷ ቴል ኤል ፉል ላይ እንደነበረች ይገመታል። የአርኪኦሎጂ ቁፋሮዎች የጥንት ምሽግ ቅሪቶችን በቁፋሮ አግኝተዋል፣ ይህም ግምቶችን እውነተኛ ሊሆኑ እንድሚችሉ አረጋግጧል።
የጊብዓ ሰዎች አስጸያፊ ብልግና ስላደረጉ እስራኤላውያን የብንያምን ወገን ለማጥፋት ተነሡ፤ ሆኖም 600 ሰዎች አምልጠዋል፤ መሳ. 19፥11-20፡48። ግን ንጉሥ ሳኦል የጊብዓ ሰው ነበረና መናገሻ ከተማውን በጊብዓ አደረገ፤ 1ሳሙ. 10፥26፤ 22፥6። በብሉይ ኪዳን ዘመን ጊብዓ ምሽግ ከተማ ነበረ፤ ከክርስቶስ ልደት ወዲህ ግን ባድማ ሆኗል።
ጊብዓ የምትታወቅባቸው ዋና ዋና የታሪክ ሁነቶች፦
👉የሌዋዊው ቁባት በጊብዓ ሰዎች በተፈጸመባት አሳቃቂ ግፍ የደረሰው ቁጣና ያስከተለው መዘዝ (መሳ. ምዕራፍ 19-21)
👉ጊብዓ የእስራኤል የመጀመሪያው ንጉሥ የንጉሥ ሳኦል የትውልድ ከተማ ነበረች። (1ኛ ሳሙኤል 10፥26፤ 1ሳሙ 15፥34-35)
👉የጊብዓ ትንቢታዊ ውግዘቶች፡- ነብያት ከጊዜ በኋላ ጊብዓን በመሳፍንት ውስጥ በተመዘገቡት ድርጊቶች ምክንያት የእስራኤል የሥነ ምግባር ውድቀት ምልክት እንደሆነች ጠቅሰዋል። (ሆሴዕ 9፥9፤ ሆሴዕ 10፥9።
ምንጭ፦ የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት፤ ገጽ 242
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍3❤1😁1
. ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“በቸርነትህ የተቤዠሃቸውን ሕዝብህን መራህ፤ በኃይልህ ወደ ቅዱስ ማደሪያህ አገባሃቸው።”
ዘጸአት 15፥13
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“በቸርነትህ የተቤዠሃቸውን ሕዝብህን መራህ፤ በኃይልህ ወደ ቅዱስ ማደሪያህ አገባሃቸው።”
ዘጸአት 15፥13
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤4👍1
እየጨመረ የሚሄድ ሕይወት
የጠለቀ መንፈሳዊ ጉዞ ለመጓዝና እየጨመረ የሚሄድ ርካታና እረፍት እንድናይ ካስፈለገ፣የክርስትና ሕይወት ትጋትን ይጠይቀናል(ዕብ 4:11)፡፡ በተለያየ ቦታ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ቃሉ እንደሚያስተምረን ትጋታችን እየጨመረ ሲሄድ፣ የእግዚአብሔር ጸጋም በሕይወታችን እየጨመረ ይሄዳል፡፡ እናም ለመንፈሳዊ ነገር ያለን መሻት እያደገ ይሄዳል፡፡ በእንደዚህ ዓይነት ግሥገሣ ውስጥ ባለማሰለስ ስንገኝ፣ እሱን ለማወቅ ያለን ራብ እየተቀጣጠለ ስለሚመጣ፣እየጨመረ ለሚሄድ ፍለጋ እንጠናከራለን፡፡ ይህንን በእንግሊዝኛው አገላለጽ positive vicious cycle ይሉታል፡፡ ማለትም ትጋቱ የጨመረ መንፈሳዊ ራብን ይወልዳል፤ የጨመረው መንፈሳዊ ራብ ደግሞ ሌላ ከፍ ያለ ትጋትንና ግሥገሣን ይወልዳል፡፡ መቼም ይሄ ኡደት ማቆሚያ የለውም እኛ በሥጋዊ አካሄዶች እስካላጠፋነው ድረስ!
በነገራችን ላይ እየጨመረ የሚሄድ የክርስትና ሕይወት ብዙ ግብዓቶችን ይፈልጋል ፡፡ መልካም የእምነት ውጊያንና ዲያቢሎስን በኃይል ጸንቶ መቃወም ይጠይቃል ፡፡ የእግዚአብሔርን ቃል ሳይታክቱ ማሰላሰልና በፊቱ ጥሩ የሆኑ ጊዜዎችን ማሳለፍ ግድ ይለናል ፡፡ ሁኔታዎችንና ሥጋችንን ሳናዳምጥ የሚከፈሉ ዋጋዎችን እንደ ጌታ ፈቃድ መክፈልን ይጠይቀናል፡፡
ሦስት በተሰናሰለ መንገድ የተቀመጡ ድርጊቶች በውጤት ሂደት እንዲህ ተቀምጠዋል፡-
ድርጊት(Action)-->ልማድ(Habit)-->ጠባይ(character)
ይህንን መርሕ ለመግለጽ ጸሎትን እንደ ምሳሌ ልውሰድ ፡፡ ጸሎትን ደጋግመን ስናደርገው ወደ ልማድነት ይቀየራል ፡፡ በሕይወታችን ልማድ እየሆነ የመጣውን ተግባር እየጨመርን ደጋግመን ስናደርገው፣ ጠባያችን ወይም መገለጫ ባሕርያችን ይሆናል ፡፡ ከዚያማ ውጤቱ እንዲህ ይሆናል፡-
“መጸለይ እንጂ አለመጸለይ አንችልም፡፡”
“በፊቱ መሆን እንጂ አለመሆን ያቅተናል፡፡”
እጅግ ሊጓጓለት የሚገባ ድንቅ ለውጥ!
የላይኛውን ሐሳብ የሚደግፉና የክርስትና ሕይወት እየተቀጣጠለ፣ እያደገና እየጨመረ የሚሄድ ሕይወት እንደ ሆነ የሚጠቁሙ ብዙ ክፍሎች አሉ ፡፡ ለምሳሌ ሦስቱን ልጥቀስ፡-
“እስከ እግዚአብሔር ፍጹም ሙላት ደርሳችሁ ትሞሉ ዘንድ” (ኤፌሶን 3፥19)
“በመንፈስ የምትቃጠሉ ሁኑ” (ሮሜ 12፥11)
“መንፈስ ይሙላባችሁ እንጂ በወይን ጠጅ አትስከሩ ይህ ማባከን ነውና” /ብዙ የሚያሰክሩ ነገሮች እንዳሉ ልብ ይሏል/(ኤፌሶን 5፥16-20)
ስሚዝ ዊግልስዎርዝ እንዲህ ብሎ ነበር፡-“If you are in the same place today as you were yesterday, you are a backslider.”(ትርጉሙ፡-በዛሬው ቀን ትላንትና የነበርክበት ቦታ ላይ ከተገኘህ የኋሊት እየሄድክ ነው)
በተሰጠ ማንነት፣ ልባችን መሉ በሙሉ በጌታ ላይ ሆኖ ከላይ በተጠቀሰው ዓይነት ፍለጋ(craving) እና ትጋት ስንቀጥል፣ የጌታ አብሮሆት ከመቸው በሚበልጥ ሁኔታ በሕይወታችን ዕውን ይሆናል ፡፡ ከዚህም የተነሣ የምናገኘው የመጀመሪያው በረከት በቃላት ልንገልጸው የማንችለው ሰላም፣ መረጋጋትና ደስታ ይሆናል ፡፡ መንፈሳዊ መረዳታችንም እየጨመረ ስለሚሄድ፣ ጌታን በሚገባ እያወቅነው እንመጣለን፡፡ስለዚህ ለውጣችን ወደ ኋላ የማይቀለበስና ዘላቂ ይሆናል ፡፡ መንፈሳዊ ዓይኖቻችን በጨመረ ሁኔታ እየተከፈቱ ስለሚመጡ፣ ብዙ ረብ የሌላቸውን ነገሮች የመጣል መነሣሣትና አቅም እያገኘን እንመጣለን ፡፡
እንደዚህ በጽናት ሳናሰልስ የጌታን ፊት በጨመረ ሁኔታ በፈለግን ቁጥር፣ የእግዚአብሔር ኃይል በውስጣችን እየጨመረ ስለሚሄድ፣ ብዙ ቀንበሮች ከሕይወታችን ይሰበራሉ ፡፡ ስለዚህም “ሸክሙ ከጫንቃህ ቀንበሩም ከትከሻህ ላይ ይሰበራል” የሚለው ቃል በሕይወታችን ይፈጸማል (ኢሳ.10፡27)፡፡ እናም ከበፊቱ ይልቅ በሕልውናው ውስጥ መቆየት አያስቸግረንም፡፡ ቃሉ እንዲህ ይላልና፡-
“እርሱንም ሳታዩት ትወዱታላችሁ፤ አሁንም ምንም ባታዩት በእርሱ አምናችሁ የእምነታችሁን ፍጻሜ እርሱም የነፍሳችሁን መዳን እየተቀበላችሁ በማይነገርና ክብር በሞላበት ሐሤት ደስ ይላችኋል” (1 ጴጥሮስ 1፥8-9)
ለዚህ አሳብ ጥሩ እይታ የሚሰጠን ኢዮብ 28፥1-11 ነው ፡፡ ይህ የምንባብ ክፍል የማዕድን ሠራተኛ ከባዶ ተነሥቶ የሚያደርገውን ግሥገሣ ነው የሚያሳየው ፡፡ “ዓይኑ ዕንቁን እስክታይ ድረስ” ፣ “የተሸፈነው ነገር ወደ ብርሃን እስኪወጣ ድረስ” ይተጋል ፡፡ እጁን ወደ ቡላድ ድንጋይ ይዘረጋል ፡፡ መጨረሻ ላይ ከብዙ እልህ አስጨራሽ ትግልና ጉዞ በኋላ የከበሩ ማዕድናትን ያገኛል፤ክፍሉ የልፋቱን ውጤት እንዲህ ይገልጸዋልና ፡-
“ሰው ወደ ቡላድ ድንጋይ እጁን ይዘረጋል፤ ተራራውንም ከመሠረቱ ይገለብጣል። ከድንጋይ ውስጥ መንዶልዶያ ይወቅራል፤ ዓይኑምዕንቍን ሁሉ ታያለች። ፈሳሹም እንዳይንጠባጠብ ይገድባል፤የተሰወረውንም ነገር ወደ ብርሃን ያወጣል።”(ቁ.9-11)
አዎ ይህ ክፍል ምሳሌያዊ በሆነ አገላለጽ፣ እንደ ማዕድን ሠራተኛው ያለ መታከት እንድንተጋና የጌታን ፊት እንድንፈልግ ያስተምረናል ፡፡
የእግዚአብሔር ቃል ተግተው “የሚሹኝ ምስጉኖች/የተባረኩ ናቸው” (ምሳሌ 8፡34) ይላልና፤ “እናንተም ትጠሩኛለችሁ፤ ሄዳችሁም ወደ እኔ ትጸልያላችሁ፣እኔም እሰማችኋለሁ። እናንተ ትሹኛላችሁ፣በፍጹም ልባችሁም ከሻችሁኝ ታገኙኛላችሁ። ከእናንተም ዘንድ እገኛለሁ፡፡”(ኤር.29፥13-14) ይላልና ጨክኖ የጌታን ፊት የሚፈልግ ሰው ይዋል ይደር እንጂ፣ የእግዚአብሔር በረከት ታገኘዋለች፡፡
አዎ፣ ጌታ አጥብቀው ለሚሹት ሰዎች በእርግጥ ይገለጣል፡፡ የበለጠ እንድናየው፣ የበለጠ በእርሱ ላይ እንድንደገፍና እንድንጠጋው ያደርገናል፡፡ በተጨማሪም ጌታ ተገልጦ ሕይወታችንን ሲጎበኝ የሚመጣው ለውጥ ለሌሎች በረከት ያደርገናልና በትጋትና በጨመረ ሁኔታ ተግተን እንፈልገው!
ምንጭ:- ዶ/ር በቀለ በላቸው፤ ባለጸጋ ክርስትያን መጽሔት
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የጠለቀ መንፈሳዊ ጉዞ ለመጓዝና እየጨመረ የሚሄድ ርካታና እረፍት እንድናይ ካስፈለገ፣የክርስትና ሕይወት ትጋትን ይጠይቀናል(ዕብ 4:11)፡፡ በተለያየ ቦታ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ቃሉ እንደሚያስተምረን ትጋታችን እየጨመረ ሲሄድ፣ የእግዚአብሔር ጸጋም በሕይወታችን እየጨመረ ይሄዳል፡፡ እናም ለመንፈሳዊ ነገር ያለን መሻት እያደገ ይሄዳል፡፡ በእንደዚህ ዓይነት ግሥገሣ ውስጥ ባለማሰለስ ስንገኝ፣ እሱን ለማወቅ ያለን ራብ እየተቀጣጠለ ስለሚመጣ፣እየጨመረ ለሚሄድ ፍለጋ እንጠናከራለን፡፡ ይህንን በእንግሊዝኛው አገላለጽ positive vicious cycle ይሉታል፡፡ ማለትም ትጋቱ የጨመረ መንፈሳዊ ራብን ይወልዳል፤ የጨመረው መንፈሳዊ ራብ ደግሞ ሌላ ከፍ ያለ ትጋትንና ግሥገሣን ይወልዳል፡፡ መቼም ይሄ ኡደት ማቆሚያ የለውም እኛ በሥጋዊ አካሄዶች እስካላጠፋነው ድረስ!
በነገራችን ላይ እየጨመረ የሚሄድ የክርስትና ሕይወት ብዙ ግብዓቶችን ይፈልጋል ፡፡ መልካም የእምነት ውጊያንና ዲያቢሎስን በኃይል ጸንቶ መቃወም ይጠይቃል ፡፡ የእግዚአብሔርን ቃል ሳይታክቱ ማሰላሰልና በፊቱ ጥሩ የሆኑ ጊዜዎችን ማሳለፍ ግድ ይለናል ፡፡ ሁኔታዎችንና ሥጋችንን ሳናዳምጥ የሚከፈሉ ዋጋዎችን እንደ ጌታ ፈቃድ መክፈልን ይጠይቀናል፡፡
ሦስት በተሰናሰለ መንገድ የተቀመጡ ድርጊቶች በውጤት ሂደት እንዲህ ተቀምጠዋል፡-
ድርጊት(Action)-->ልማድ(Habit)-->ጠባይ(character)
ይህንን መርሕ ለመግለጽ ጸሎትን እንደ ምሳሌ ልውሰድ ፡፡ ጸሎትን ደጋግመን ስናደርገው ወደ ልማድነት ይቀየራል ፡፡ በሕይወታችን ልማድ እየሆነ የመጣውን ተግባር እየጨመርን ደጋግመን ስናደርገው፣ ጠባያችን ወይም መገለጫ ባሕርያችን ይሆናል ፡፡ ከዚያማ ውጤቱ እንዲህ ይሆናል፡-
“መጸለይ እንጂ አለመጸለይ አንችልም፡፡”
“በፊቱ መሆን እንጂ አለመሆን ያቅተናል፡፡”
እጅግ ሊጓጓለት የሚገባ ድንቅ ለውጥ!
የላይኛውን ሐሳብ የሚደግፉና የክርስትና ሕይወት እየተቀጣጠለ፣ እያደገና እየጨመረ የሚሄድ ሕይወት እንደ ሆነ የሚጠቁሙ ብዙ ክፍሎች አሉ ፡፡ ለምሳሌ ሦስቱን ልጥቀስ፡-
“እስከ እግዚአብሔር ፍጹም ሙላት ደርሳችሁ ትሞሉ ዘንድ” (ኤፌሶን 3፥19)
“በመንፈስ የምትቃጠሉ ሁኑ” (ሮሜ 12፥11)
“መንፈስ ይሙላባችሁ እንጂ በወይን ጠጅ አትስከሩ ይህ ማባከን ነውና” /ብዙ የሚያሰክሩ ነገሮች እንዳሉ ልብ ይሏል/(ኤፌሶን 5፥16-20)
ስሚዝ ዊግልስዎርዝ እንዲህ ብሎ ነበር፡-“If you are in the same place today as you were yesterday, you are a backslider.”(ትርጉሙ፡-በዛሬው ቀን ትላንትና የነበርክበት ቦታ ላይ ከተገኘህ የኋሊት እየሄድክ ነው)
በተሰጠ ማንነት፣ ልባችን መሉ በሙሉ በጌታ ላይ ሆኖ ከላይ በተጠቀሰው ዓይነት ፍለጋ(craving) እና ትጋት ስንቀጥል፣ የጌታ አብሮሆት ከመቸው በሚበልጥ ሁኔታ በሕይወታችን ዕውን ይሆናል ፡፡ ከዚህም የተነሣ የምናገኘው የመጀመሪያው በረከት በቃላት ልንገልጸው የማንችለው ሰላም፣ መረጋጋትና ደስታ ይሆናል ፡፡ መንፈሳዊ መረዳታችንም እየጨመረ ስለሚሄድ፣ ጌታን በሚገባ እያወቅነው እንመጣለን፡፡ስለዚህ ለውጣችን ወደ ኋላ የማይቀለበስና ዘላቂ ይሆናል ፡፡ መንፈሳዊ ዓይኖቻችን በጨመረ ሁኔታ እየተከፈቱ ስለሚመጡ፣ ብዙ ረብ የሌላቸውን ነገሮች የመጣል መነሣሣትና አቅም እያገኘን እንመጣለን ፡፡
እንደዚህ በጽናት ሳናሰልስ የጌታን ፊት በጨመረ ሁኔታ በፈለግን ቁጥር፣ የእግዚአብሔር ኃይል በውስጣችን እየጨመረ ስለሚሄድ፣ ብዙ ቀንበሮች ከሕይወታችን ይሰበራሉ ፡፡ ስለዚህም “ሸክሙ ከጫንቃህ ቀንበሩም ከትከሻህ ላይ ይሰበራል” የሚለው ቃል በሕይወታችን ይፈጸማል (ኢሳ.10፡27)፡፡ እናም ከበፊቱ ይልቅ በሕልውናው ውስጥ መቆየት አያስቸግረንም፡፡ ቃሉ እንዲህ ይላልና፡-
“እርሱንም ሳታዩት ትወዱታላችሁ፤ አሁንም ምንም ባታዩት በእርሱ አምናችሁ የእምነታችሁን ፍጻሜ እርሱም የነፍሳችሁን መዳን እየተቀበላችሁ በማይነገርና ክብር በሞላበት ሐሤት ደስ ይላችኋል” (1 ጴጥሮስ 1፥8-9)
ለዚህ አሳብ ጥሩ እይታ የሚሰጠን ኢዮብ 28፥1-11 ነው ፡፡ ይህ የምንባብ ክፍል የማዕድን ሠራተኛ ከባዶ ተነሥቶ የሚያደርገውን ግሥገሣ ነው የሚያሳየው ፡፡ “ዓይኑ ዕንቁን እስክታይ ድረስ” ፣ “የተሸፈነው ነገር ወደ ብርሃን እስኪወጣ ድረስ” ይተጋል ፡፡ እጁን ወደ ቡላድ ድንጋይ ይዘረጋል ፡፡ መጨረሻ ላይ ከብዙ እልህ አስጨራሽ ትግልና ጉዞ በኋላ የከበሩ ማዕድናትን ያገኛል፤ክፍሉ የልፋቱን ውጤት እንዲህ ይገልጸዋልና ፡-
“ሰው ወደ ቡላድ ድንጋይ እጁን ይዘረጋል፤ ተራራውንም ከመሠረቱ ይገለብጣል። ከድንጋይ ውስጥ መንዶልዶያ ይወቅራል፤ ዓይኑምዕንቍን ሁሉ ታያለች። ፈሳሹም እንዳይንጠባጠብ ይገድባል፤የተሰወረውንም ነገር ወደ ብርሃን ያወጣል።”(ቁ.9-11)
አዎ ይህ ክፍል ምሳሌያዊ በሆነ አገላለጽ፣ እንደ ማዕድን ሠራተኛው ያለ መታከት እንድንተጋና የጌታን ፊት እንድንፈልግ ያስተምረናል ፡፡
የእግዚአብሔር ቃል ተግተው “የሚሹኝ ምስጉኖች/የተባረኩ ናቸው” (ምሳሌ 8፡34) ይላልና፤ “እናንተም ትጠሩኛለችሁ፤ ሄዳችሁም ወደ እኔ ትጸልያላችሁ፣እኔም እሰማችኋለሁ። እናንተ ትሹኛላችሁ፣በፍጹም ልባችሁም ከሻችሁኝ ታገኙኛላችሁ። ከእናንተም ዘንድ እገኛለሁ፡፡”(ኤር.29፥13-14) ይላልና ጨክኖ የጌታን ፊት የሚፈልግ ሰው ይዋል ይደር እንጂ፣ የእግዚአብሔር በረከት ታገኘዋለች፡፡
አዎ፣ ጌታ አጥብቀው ለሚሹት ሰዎች በእርግጥ ይገለጣል፡፡ የበለጠ እንድናየው፣ የበለጠ በእርሱ ላይ እንድንደገፍና እንድንጠጋው ያደርገናል፡፡ በተጨማሪም ጌታ ተገልጦ ሕይወታችንን ሲጎበኝ የሚመጣው ለውጥ ለሌሎች በረከት ያደርገናልና በትጋትና በጨመረ ሁኔታ ተግተን እንፈልገው!
ምንጭ:- ዶ/ር በቀለ በላቸው፤ ባለጸጋ ክርስትያን መጽሔት
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍23❤2
. ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“በአምላክህም በእግዚአብሔር ፊት እንዲህ ብለህ ተናገር፦ አባቴ የተቅበዘበዘ ሶርያዊ ነበረ፤ በቍጥር ጥቂት ሳለ ወደ ግብፅ ወረደ በዚያም ተቀመጠ፤ ታላቅ የሆነ የበረታም ቍጥሩም የበዛ ሕዝብ ሆነ።”
ዘዳግም 26፥5
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“በአምላክህም በእግዚአብሔር ፊት እንዲህ ብለህ ተናገር፦ አባቴ የተቅበዘበዘ ሶርያዊ ነበረ፤ በቍጥር ጥቂት ሳለ ወደ ግብፅ ወረደ በዚያም ተቀመጠ፤ ታላቅ የሆነ የበረታም ቍጥሩም የበዛ ሕዝብ ሆነ።”
ዘዳግም 26፥5
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤7👎1
የሃኪሙ ሉቃስ ጹሑፎች የአጻጻፍ ስልት እና ይዘት
6. ምሳሌዎች እና ታሪኮች
ሉቃስ በሌሎች ወንጌሎች ውስጥ የማይገኙ በርካታ ምሳሌዎችን ያካትታል፣ ብዙ ጊዜ በጸጋ እና በርኅራኄ ላይ ያተኩራል።
ምሳሌዎች፡-አባካኙ ልጅ (ሉቃስ 15፥11–32)። ባለጠጋው እና አልዓዛር (ሉቃስ 16፥19–31)።
7. የሕክምና ቃላት
እንደ ሃኪም (ቆላስይስ 4፥14) ሉቃስ አልፎ አልፎ የህክምና ቃላትን እና ስለ በሽታዎች እና ፈውሶች ትክክለኛ መግለጫዎችን ይጠቀማል።
ምሳሌ፡- ሆዱ የተነፋ ሰው መፈወስ ሲገልጽ (ሉቃስ 14፥2) ሉቃስ የተለየ የሕክምና ቃል ተጠቅሟል።
8. የዘመን ቅደም ተከተል እና ጭብጥ ማደራጀት
ሃኪሙ ሉቃስ ትረካውን በጊዜ ቅደም ተከተል እና በጭብጥ አዋቅሮታል። ብዙውን ጊዜ የጌታችን እና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ሕይወት ክስተቶች ከሰፋፊ ሥነ-መለኮታዊ ጭብጦች ጋር ያገናኛል።
ምሳሌ፡- በሉቃስ-ሐዋርያት ውስጥ ያለው ሥርዓት ያለው ቅደም ተከተል የኢየሱስን ሕይወት ከጥንቷ ቤተ ክርስቲያን እድገት ጋር ያገናኛል (ሐዋ. 1፥1-2)።
9. የመዝሙር እና የግጥም ውህደት
ሉቃስ በብዛት ዝማሬዎችን እና የቅኔ ምንባባትን አካቷል። የማርያም ውዳሴ፣ ዘካርያስ አድናቆት፣ የመላእክት ክብር እና የስምዖን ቅኔያዊ ምንባቦችን ያካትታል።
ምሳሌዎች፡- (ሉቃስ 1፥46-55)። (ሉቃስ 2፥29–32)።
ይቀጥላል...
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
6. ምሳሌዎች እና ታሪኮች
ሉቃስ በሌሎች ወንጌሎች ውስጥ የማይገኙ በርካታ ምሳሌዎችን ያካትታል፣ ብዙ ጊዜ በጸጋ እና በርኅራኄ ላይ ያተኩራል።
ምሳሌዎች፡-አባካኙ ልጅ (ሉቃስ 15፥11–32)። ባለጠጋው እና አልዓዛር (ሉቃስ 16፥19–31)።
7. የሕክምና ቃላት
እንደ ሃኪም (ቆላስይስ 4፥14) ሉቃስ አልፎ አልፎ የህክምና ቃላትን እና ስለ በሽታዎች እና ፈውሶች ትክክለኛ መግለጫዎችን ይጠቀማል።
ምሳሌ፡- ሆዱ የተነፋ ሰው መፈወስ ሲገልጽ (ሉቃስ 14፥2) ሉቃስ የተለየ የሕክምና ቃል ተጠቅሟል።
8. የዘመን ቅደም ተከተል እና ጭብጥ ማደራጀት
ሃኪሙ ሉቃስ ትረካውን በጊዜ ቅደም ተከተል እና በጭብጥ አዋቅሮታል። ብዙውን ጊዜ የጌታችን እና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ሕይወት ክስተቶች ከሰፋፊ ሥነ-መለኮታዊ ጭብጦች ጋር ያገናኛል።
ምሳሌ፡- በሉቃስ-ሐዋርያት ውስጥ ያለው ሥርዓት ያለው ቅደም ተከተል የኢየሱስን ሕይወት ከጥንቷ ቤተ ክርስቲያን እድገት ጋር ያገናኛል (ሐዋ. 1፥1-2)።
9. የመዝሙር እና የግጥም ውህደት
ሉቃስ በብዛት ዝማሬዎችን እና የቅኔ ምንባባትን አካቷል። የማርያም ውዳሴ፣ ዘካርያስ አድናቆት፣ የመላእክት ክብር እና የስምዖን ቅኔያዊ ምንባቦችን ያካትታል።
ምሳሌዎች፡- (ሉቃስ 1፥46-55)። (ሉቃስ 2፥29–32)።
ይቀጥላል...
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤2👍2
. ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“ወደ ዘላለም ሕይወት የሚወስደውን የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ምሕረት ስትጠባበቁ በእግዚአብሔር ፍቅር ራሳችሁን ጠብቁ።”
ይሁዳ 1፥21
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“ወደ ዘላለም ሕይወት የሚወስደውን የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ምሕረት ስትጠባበቁ በእግዚአብሔር ፍቅር ራሳችሁን ጠብቁ።”
ይሁዳ 1፥21
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍9❤1🔥1🥰1
#እራሳችንን_እንመርምር
ስለ ወንጌል ምን እናደርጋለን? በወንጌል ማኅበረተኛ እንሆን ዘንድስ? ወይስ "ወንጌል ምኔ ነው?" ብለን ለሆነ ወገን አስረክበን እየኖርን ነው?
“በወንጌልም ማኅበረተኛ እሆን ዘንድ ስለ ወንጌል ሁሉን አደርጋለሁ።”
1ኛ ቆሮንቶስ 9፥23
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ስለ ወንጌል ምን እናደርጋለን? በወንጌል ማኅበረተኛ እንሆን ዘንድስ? ወይስ "ወንጌል ምኔ ነው?" ብለን ለሆነ ወገን አስረክበን እየኖርን ነው?
“በወንጌልም ማኅበረተኛ እሆን ዘንድ ስለ ወንጌል ሁሉን አደርጋለሁ።”
1ኛ ቆሮንቶስ 9፥23
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤6👍2
. ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“በጽድቅ መንገድ ላይ ሕይወት አለ በጎዳናዋም ሞት የለም።”
ምሳሌ 12፥28
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“በጽድቅ መንገድ ላይ ሕይወት አለ በጎዳናዋም ሞት የለም።”
ምሳሌ 12፥28
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤4👍2🔥2🥰1
የሃኪሙ ሉቃስ ጹሑፎች የአጻጻፍ ስልት እና ይዘት
10. ድርብ ሥራ፡- ወንጌል እና የሐዋርያት ሥራ
የሉቃስ ባለ ሁለት ጥራዝ ሥራ ከኢየሱስ አገልግሎት ጀምሮ እስከ ቤተ ክርስቲያን ምስረታ ድረስ ያለውን የእግዚአብሔር ዕቅድ ቀጣይነት ያሳያል።
ምሳሌ፦ የሐዋርያት ሥራ የሚጀምረው በኢየሱስ ዕርገት እና በመንፈስ ቅዱስ ተስፋ (ሉቃስ 24፥50–53፤ የሐዋርያት ሥራ 1፥1–11) የሉቃስ ወንጌል በሚያልቅበት ቦታ ነው።
11. የሴቶች ሚና
በሉቃስ ወንጌል ውስጥ ሴቶች ትልቅ ሚና ተሰጥቷቸዋል። ለምሳሌ ማርያም፣ ኤልሳቤጥ፣ ኢየሱስን ሽቶ የቀባችው ኃጢአተኛ ሴት (ሉቃስ 7፥36-50) እና መግደላዊት ማርያም ይገኙበታል።
ሉቃስ በትረካዎቹ ውስጥ ብዙ ጊዜ ወንዶችንና ሴቶችን ያጣምራል፣ ይህም የጾታ እኩልነትን በእግዚአብሔር መንግሥት ውስጥ አጉልቶ ያሳያል (ለምሳሌ፡ ስምዖን እና ሐና በሉቃስ 2፥25-38)።
ምንጭ፦
👉Luke, Gospel of. The Holy Bible (NIV, ESV, KJV, or other preferred translations).
👉Fitzmyer, J. A. (1981). The Gospel According to Luke I–IX. Anchor Bible Commentary.
👉Johnson, L. T. (1992). The Acts of the Apostles. Sacra Pagina Commentary.
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
10. ድርብ ሥራ፡- ወንጌል እና የሐዋርያት ሥራ
የሉቃስ ባለ ሁለት ጥራዝ ሥራ ከኢየሱስ አገልግሎት ጀምሮ እስከ ቤተ ክርስቲያን ምስረታ ድረስ ያለውን የእግዚአብሔር ዕቅድ ቀጣይነት ያሳያል።
ምሳሌ፦ የሐዋርያት ሥራ የሚጀምረው በኢየሱስ ዕርገት እና በመንፈስ ቅዱስ ተስፋ (ሉቃስ 24፥50–53፤ የሐዋርያት ሥራ 1፥1–11) የሉቃስ ወንጌል በሚያልቅበት ቦታ ነው።
11. የሴቶች ሚና
በሉቃስ ወንጌል ውስጥ ሴቶች ትልቅ ሚና ተሰጥቷቸዋል። ለምሳሌ ማርያም፣ ኤልሳቤጥ፣ ኢየሱስን ሽቶ የቀባችው ኃጢአተኛ ሴት (ሉቃስ 7፥36-50) እና መግደላዊት ማርያም ይገኙበታል።
ሉቃስ በትረካዎቹ ውስጥ ብዙ ጊዜ ወንዶችንና ሴቶችን ያጣምራል፣ ይህም የጾታ እኩልነትን በእግዚአብሔር መንግሥት ውስጥ አጉልቶ ያሳያል (ለምሳሌ፡ ስምዖን እና ሐና በሉቃስ 2፥25-38)።
ምንጭ፦
👉Luke, Gospel of. The Holy Bible (NIV, ESV, KJV, or other preferred translations).
👉Fitzmyer, J. A. (1981). The Gospel According to Luke I–IX. Anchor Bible Commentary.
👉Johnson, L. T. (1992). The Acts of the Apostles. Sacra Pagina Commentary.
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤3
. ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“አቤቱ፥ ምሕረትህንና ቸርነትህን አስብ፥ ከጥንት ጀምሮ ናቸውና።”
መዝሙር 25፥6
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“አቤቱ፥ ምሕረትህንና ቸርነትህን አስብ፥ ከጥንት ጀምሮ ናቸውና።”
መዝሙር 25፥6
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤5
. ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“እንግዲህ በእምነት ከጸደቅን በእግዚአብሔር ዘንድ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ሰላምን እንያዝ፤”
ሮሜ 5፥1
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“እንግዲህ በእምነት ከጸደቅን በእግዚአብሔር ዘንድ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ሰላምን እንያዝ፤”
ሮሜ 5፥1
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍6❤3
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
የጌታችንና የመድኃኒታችንን የኢየሱስ ክርስቶስ ልደት ምክንያት በማድረግ ቅዱሳት መጻሕፍት፣ ክርስቶስ ለምን እንደተወለደ እና ለማን እንደ ተወለደ፣ ከአዳም በመነሳት ሕግና ነቢያት ጭምር ምን በስፋት እንደሚያነሱ፣ የክርስቶስ የመጀመሪያው እና ዳግመኛው ምጽአት በብሉያት መጻሕፍት እንዴት ተዳሰሱ የሚሉትን እንመለከታለን?
በቅርብ ቀን በተከታታይ ትምህርቶች ይጠብቁን!
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
በቅርብ ቀን በተከታታይ ትምህርቶች ይጠብቁን!
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍27❤3
በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ በእስራኤል ታሪክ የመጀመሪያው እና የመጨረሻው መስፍን ማን ነው?
Anonymous Quiz
11%
ሀ. ናዖድ እና ኤሊ
27%
ለ. ጎቶንያል እና ሳሙኤል
12%
ሐ. ጎቶንያል እና ኤሊ
32%
መ. ጌዴዎን እና ሳምሶን
17%
ሠ. መልስ የለም
👍2🔥1
. ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“እግዚአብሔር እንደ ሰጠን ሁሉ፥ የእግዚአብሔርን ቸርነትና የእግዚአብሔርን ምስጋና፥ እንደ ምሕረቱና እንደ ቸርነቱም ብዛት ለእስራኤል ቤት የሰጠውን ትልቅ በጎነት አሳስባለሁ።”
ኢሳይያስ 63፥7
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“እግዚአብሔር እንደ ሰጠን ሁሉ፥ የእግዚአብሔርን ቸርነትና የእግዚአብሔርን ምስጋና፥ እንደ ምሕረቱና እንደ ቸርነቱም ብዛት ለእስራኤል ቤት የሰጠውን ትልቅ በጎነት አሳስባለሁ።”
ኢሳይያስ 63፥7
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍6
ቅዱሳት መጻሕፍት
#የሮሜ_መልእክት_ጥናት ሮሜ 10፥1-4 የዚህ ምዕራፍ ጭብጥ እስራኤል አሁን እግዚአብሔርን የመግፋቷ ጉዳይ ነው፡፡ ጳውሎስ ከመለኮታዊ ሉዓላዊነት (ምዕራፍ 9) ወደ ሰው ተጠያቂነት ያመራል፡፡ ባለፈው ምዕራፍ (ሮሜ 9:30-33) የጽድቅን ጭብጥ ካስተዋወቀ በኋላ የእስራኤልን የእምቢታ ሦስት ገጽታዎች ያብራራል፡፡ እስራኤል እንደ ሕዝብ የመሢሑን መምጣት በጉጉት እየጠበቁ ሊቀበሉት የተዘጋጁ እንደነበሩ…
#የሮሜ_መልእክት_ጥናት
ሮሜ 10፥2-3
ለ) ለእግዚአብሔር ይቀኑ ነበር (10:2)
እስራኤላውያን ከባቢሎን ምርኮ መልስ ከጣዖት አምልኮ ተፈውሰው ነበር፡፡ በምኩራብና በቤተ መቅደስ እውነተኛው አምላክ ይመለክና ያገለግሉ ነበር፡፡ እውነተኛውም ሕግ በትምህርት ይሰጥ ነበር፡፡ አይሁድ ከቅናታቸው የተነሣ ‹‹የእግዚአብሔርን ሕግ አሻሽለው» የራሳቸውን ትውፊት በማከል ከሕጉ ጋር እኩል አደረጓቸው፡፡ ጳውሎስ ለሕግና ለትውፊት ቀናተኛ ነበር (የሐዋ. 26፡1-11፤ ገላ. 1:13-14)
ቅናታቸው ግን በእውቀት ላይ የተመሠረተ አልነበረም፤ ብርሃን የሌለበት ሙቀት ነበረ፡፡ ዛሬም ብዙ የሃይማኖት ሰዎች ተመሳሳይ ስሕተት ይፈጽማሉ፡፡ መልካም ሥራቸውና መንፈሳዊ ድርጊታቸው ከመዳን እንደሚያርቋቸው ሳይገነዘቡ፣ ደኅንነት የሚሰጧቸው ይመስላቸዋል፡፡ በእርግጥ አብዛኛዎቹ ቅንና የተሰጡ ናቸው፣ ነገር ግን ቅንነትና መሰጠት ነፍስን አያድንም፡፡ «ይህም የሕግን ሥራ በመሥራት ሥጋ የለበሰ ሁሉ በእርሱ ፊት ስለማይጸድቅ ነው» (ሮሜ 3፡20)፡፡
ብዙ ሰዎች የእግዚአብሔርን ነገር በትጋት ይፈልጋሉ፤ ነገር ግን ትጋታቸው እውነትን በማወቅ ላይ የተመሠረተ ካልሆነ ከንቱ ነው። በሐሰት ላይ የተመሠረተ ትጋት በጣም አደገኛ ነው፤ ብዙውን ጊዜ የሚመራው ወደ ታላቅ ጥፋት
ነው።
ሐ) ኩሩና ራሳቸውን ያጸደቁ ነበሩ (10:3)
ስላልሰሙ ሳይሆን፣ ለመማር ባለመፍቀዳቸው፣ እስራኤላውያን ስለ እግዚአብሔር ጽድቅ የማያውቁ ነበሩ፡፡ ዕድል ከማጣት የሚመጣ አለማወቅ ቢኖርም፣ እስራኤላውያን ግን ለመዳን በጣም ብዙ ዕድል ነበራቸው፡፡ በራሳቸው እልከኝነት የመጣ እውነትን የመቃወም ባሕርይ ኖሮባቸው ለእግዚአብሔር አይገዙም፡፡ በመልካም ሥራቸውና በጽድቃቸው ስለታመኑ፣ ኃጢአተኝነታቸውን አምነው አዳኙን አልታመኑበትም፡፡ ጌታን ከመገናኘቱ በፊት ጳውሎስም ተመሳሳይ ስሕተት ፈጽሟል (ፊልጵ. 3፡1-11)።
አይሁዳውያን ከእግዚአብሔር የሚመጣውን ጽድቅ በክርስቶስ በማመን የሚመጣውን ስለማያውቁ፥ ማለትም ጽድቅ ስለማያውቁ ለእርሱ ሊታዘዙ
አልቻሉም። የእግዚአብሔር ጽድቅ አካል ክርስቶስ ራሱ መሆኑን አልተረዱም።
"አሁን ግን በሕግና በነቢያት የተመሰከረለት የእግዚአብሔር ጽድቅ ያለ ሕግ ተገልጦአል፥ እርሱም፥ ለሚያምኑ ሁሉ የሆነ፥ በኢየሱስ ክርስቶስ በማመን የሚገኘው የእግዚአብሔር ጽድቅ ነው፤ ልዩነት የለምና፤"
ሮሜ. 3፥21-22
ሮበርት ሙሬይ ማክቼኒ የተባለ አንድ ሰው፣ መንፈሳዊ ጽሑፎችን ሲያድል በጥሩ ሁኔታ ልብስ ለለበሰች ሴት ሰጣት፡፡ ሴትየዋም በንቀት አየችውና፣ «ጌታው፣ ማን እንደሆንኩ አታውቅም!›› አለችው፡፡ እርሱም በእርጋታ፣ «የእኔ እመቤት፣ የፍርድ ቀን መጥቷል፣ በዚያ ቀን ማንነትዎ ዋጋ የለውም!›› አላት፡፡
ይቀጥላል...
ምንጭ፦ ዋረን ደብልዩ ዌርዝ ቢ፤ ተስማማ፤ ገጽ 105-106፣ የአዲስ ኪዳን ማብራሪያ፤ ገጽ 374
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ሮሜ 10፥2-3
ለ) ለእግዚአብሔር ይቀኑ ነበር (10:2)
እስራኤላውያን ከባቢሎን ምርኮ መልስ ከጣዖት አምልኮ ተፈውሰው ነበር፡፡ በምኩራብና በቤተ መቅደስ እውነተኛው አምላክ ይመለክና ያገለግሉ ነበር፡፡ እውነተኛውም ሕግ በትምህርት ይሰጥ ነበር፡፡ አይሁድ ከቅናታቸው የተነሣ ‹‹የእግዚአብሔርን ሕግ አሻሽለው» የራሳቸውን ትውፊት በማከል ከሕጉ ጋር እኩል አደረጓቸው፡፡ ጳውሎስ ለሕግና ለትውፊት ቀናተኛ ነበር (የሐዋ. 26፡1-11፤ ገላ. 1:13-14)
ቅናታቸው ግን በእውቀት ላይ የተመሠረተ አልነበረም፤ ብርሃን የሌለበት ሙቀት ነበረ፡፡ ዛሬም ብዙ የሃይማኖት ሰዎች ተመሳሳይ ስሕተት ይፈጽማሉ፡፡ መልካም ሥራቸውና መንፈሳዊ ድርጊታቸው ከመዳን እንደሚያርቋቸው ሳይገነዘቡ፣ ደኅንነት የሚሰጧቸው ይመስላቸዋል፡፡ በእርግጥ አብዛኛዎቹ ቅንና የተሰጡ ናቸው፣ ነገር ግን ቅንነትና መሰጠት ነፍስን አያድንም፡፡ «ይህም የሕግን ሥራ በመሥራት ሥጋ የለበሰ ሁሉ በእርሱ ፊት ስለማይጸድቅ ነው» (ሮሜ 3፡20)፡፡
ብዙ ሰዎች የእግዚአብሔርን ነገር በትጋት ይፈልጋሉ፤ ነገር ግን ትጋታቸው እውነትን በማወቅ ላይ የተመሠረተ ካልሆነ ከንቱ ነው። በሐሰት ላይ የተመሠረተ ትጋት በጣም አደገኛ ነው፤ ብዙውን ጊዜ የሚመራው ወደ ታላቅ ጥፋት
ነው።
ሐ) ኩሩና ራሳቸውን ያጸደቁ ነበሩ (10:3)
ስላልሰሙ ሳይሆን፣ ለመማር ባለመፍቀዳቸው፣ እስራኤላውያን ስለ እግዚአብሔር ጽድቅ የማያውቁ ነበሩ፡፡ ዕድል ከማጣት የሚመጣ አለማወቅ ቢኖርም፣ እስራኤላውያን ግን ለመዳን በጣም ብዙ ዕድል ነበራቸው፡፡ በራሳቸው እልከኝነት የመጣ እውነትን የመቃወም ባሕርይ ኖሮባቸው ለእግዚአብሔር አይገዙም፡፡ በመልካም ሥራቸውና በጽድቃቸው ስለታመኑ፣ ኃጢአተኝነታቸውን አምነው አዳኙን አልታመኑበትም፡፡ ጌታን ከመገናኘቱ በፊት ጳውሎስም ተመሳሳይ ስሕተት ፈጽሟል (ፊልጵ. 3፡1-11)።
አይሁዳውያን ከእግዚአብሔር የሚመጣውን ጽድቅ በክርስቶስ በማመን የሚመጣውን ስለማያውቁ፥ ማለትም ጽድቅ ስለማያውቁ ለእርሱ ሊታዘዙ
አልቻሉም። የእግዚአብሔር ጽድቅ አካል ክርስቶስ ራሱ መሆኑን አልተረዱም።
"አሁን ግን በሕግና በነቢያት የተመሰከረለት የእግዚአብሔር ጽድቅ ያለ ሕግ ተገልጦአል፥ እርሱም፥ ለሚያምኑ ሁሉ የሆነ፥ በኢየሱስ ክርስቶስ በማመን የሚገኘው የእግዚአብሔር ጽድቅ ነው፤ ልዩነት የለምና፤"
ሮሜ. 3፥21-22
ሮበርት ሙሬይ ማክቼኒ የተባለ አንድ ሰው፣ መንፈሳዊ ጽሑፎችን ሲያድል በጥሩ ሁኔታ ልብስ ለለበሰች ሴት ሰጣት፡፡ ሴትየዋም በንቀት አየችውና፣ «ጌታው፣ ማን እንደሆንኩ አታውቅም!›› አለችው፡፡ እርሱም በእርጋታ፣ «የእኔ እመቤት፣ የፍርድ ቀን መጥቷል፣ በዚያ ቀን ማንነትዎ ዋጋ የለውም!›› አላት፡፡
ይቀጥላል...
ምንጭ፦ ዋረን ደብልዩ ዌርዝ ቢ፤ ተስማማ፤ ገጽ 105-106፣ የአዲስ ኪዳን ማብራሪያ፤ ገጽ 374
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍9❤4