ቅዱሳት መጻሕፍት
7.46K subscribers
1.37K photos
61 videos
332 files
808 links
በዚህ ቻናል

👉ቅዱሳት መጻሕፍት ይጠናሉ::
👉መጽሐፍ ቅዱሳዊ ትምህርቶች ይቀርባሉ::
👉 ለቅዱሳት መጽሐፍት ጥናት የሚያግዙ መጻሕፍት ይለቀቃሉ።

⭐️⭐️⭐️⭐️⭐️

@Holy_scriptures
Download Telegram
.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“ዓለም እናንተን ሊጠላ አይቻለውም፤ እኔ ግን ሥራው ክፉ መሆኑን እመሰክርበታለሁና እኔን ይጠላኛል።”
ዮሐንስ 7፥7



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
🔥42
የሃኪሙ ሉቃስ ጹሑፎች የአጻጻፍ ስልት እና ይዘት


በአዲስ ኪዳን የሉቃስ ወንጌል እና የሐዋርያት ሥራ ጸሐፊ ሃኪሙ ሉቃስ፣ በልዩ የአጻጻፍ ስልትና ዘዴዎች ይታወቃል። ሥራዎቹ በሥነ-ጽሑፋዊ ውስብስብነታቸው (አስደናቂ የግሪክ ቋንቋ እውቀቱ)፣ በታሪካዊ ዝርዝርነታቸው፣ በሥነ-መለኮት ጥልቀት እና በሁለንተናዊ እይታ ተለይተው ይታወቃሉ። ከዚህ በታች የእሱን ዘይቤ እና ስልቶች አጠቃላይ እይታ ከቅዱሳት መጻሕፍት እንመለከታለን፦

1. ታሪካዊ እና የምርምር አቀራረብ ዘዴ

የሉቃስ አጻጻፍ ጥንቃቄ የተሞላበት ታሪካዊ ምርምርን ያንጸባርቃል። ብዙ ጊዜ ምንጮችን እና ምስክሮችን ይጠቅሳል፣ ይህም ለትክክለኛነቱ እና ለምርምር እና ጥናት ያለውን ቁርጠኝነት ያሳያል።

ምሳሌ፡- ሉቃስ በወንጌሉ መግቢያ ላይ ጥልቅ ምርምር እና ጥናት እንዳደረገ በግልጽ ተናግሯል።

“የከበርህ ቴዎፍሎስ ሆይ፥ ከመጀመሪያው በዓይን ያዩትና የቃሉ አገልጋዮች የሆኑት እንዳስተላለፉልን፥ በኛ ዘንድ ስለ ተፈጸመው ነገር ብዙዎች ታሪክን በየተራው ለማዘጋጀት ስለ ሞከሩ፥ እኔ ደግሞ ስለ ተማርኸው ቃል እርግጡን እንድታውቅ በጥንቃቄ ሁሉን ከመጀመሪያው ተከትዬ በየተራው ልጽፍልህ መልካም ሆኖ ታየኝ።”
ሉቃስ 1፥1-4


2. የግሪክ ሥነ-ጽሑፍ ዘይቤ አጠቃቀም ዘዴ

ሐኪሙ ሉቃስ በአዳዲስ ቃላት እና መዋቅር የበለፀገ፣ ትምህርቱን እና አንባቢውን የማሳተፍ ችሎታውን የሚያንፀባርቅ ድንቅ የግሪክ ዘይቤን ይጠቀማል።

ምሳሌ፦ ወቅታዊ አረፍተ ነገሮችን መጠቀሙ፣ እንደ መቅድም (ሉቃስ 1፡1-4)፣ የተራቀቀ ድንቅ የግሪክ የአጻጻፍ ስልት ያሳያል።


ይቀጥላል...



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
9👍4
.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“ሁልጊዜ ስለ ሁሉ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም አምላካችንንና አባታችንን ስለ ሁሉ አመስግኑ።”
ኤፌሶን 5፥20




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
5👍1
ቅዱሳት መጻሕፍት
ነቢዩ ኤርምያስ                         ክፍል-፯ በኤርምያስ ዘመን ግብረ ገባዊ ዝቅጠት በሰፊው የተሠራጨ ሲሆን፣ ኢፍትሓዊነትም በዚያው ልክ ተስፋፍቶ ነበር (5፥1-9፤ 7 ፥ 1-11 ፤ 23 ፥ 10-14)፡፡ ካህናትና ነቢያት እንደ ሌሎቹ አይሁድ ጥፋተኞች ነበሩ (6፥ 13-15)፡፡ ሆኖም ሕዝቡ ሃይማኖታዊ ሥርዐትን ፈጸሙ፡፡ እግዚአብሔር ግን በዚህ ውጫዊ ሥርዐት ከቊጣው የሚመለስ አልነበረም::…
ነቢዩ ኤርምያስ




                        ክፍል-



መሲሓዊ ትንቢትን በተመለከተም ኤርምያስ መሲሓዊውን ጊዜ በዝርዝር አይገልጽም፡፡ የመሲሑ ማንነት በመጽሐፉ ላይ በጒልሕ አልተመለከተም፡፡ ይሁን እንጂ ኤርምያስ አንዳንድ ፋይዳ ያላቸውን መሲሓውያን ምንባቦች ይሰጣል ፡-

1. ከኪዳኑ ታቦት የላቀ የእግዚአብሔር መገለጥ እውን እንድሚሆን መታወጁ (3፥14-17)

2. የዐዲሱ ኪዳን መገለጥ (31፥31-34)

3. የዳዊት ኪዳን ፍጻሜ ላይ ከመድረሱ ጋር ተያይዞ (33 ፥ 14- 26) የሙሴ ውብ ሐሳብ እውን መሆን (ዘፀ 19፥6)፡፡

የትንቢተ ኤርምያስ ዘላቂ ፋይዳ የሚገኘው በዐዲስ ኪዳን ውስጥ ያሉትን ይዘቶች (በአርባና በኀምሳ ቤት ውስጥ ይገኛሉ፤ በዮሐንስ ራእይ ላይ ከግማሽ በላይ ይገኛሉ) ኢርቱዕ በሆነ መልክ በመግለጽ ብቻ ሳይሆን፣ ከእግዚአብሔር ጋር ስላለው ግንኙነት ለማወቅ ድንቅ የሆነ መማሪያ መጽሐፍ በመሆኑ ነው፡፡ በብሉይ ኪዳን ውስጥ ከዚህ ላይ የግል እምነት ከፍተኛ ደረጃ ላይ ደርሶ ይገኛል፤ እንዲሁም በዳዊት ሥርወ መንግሥት ውስጥ (23፥1-8፤ 33፥ 14-18) የካህንነትንና የንጉሥነትን ምንነት ለመረዳት እውነተኛ መንገድ በመሆኑ ነው፡፡ በምዕራፍ 30-33 ላይ ለሕዝቡ ብሩህ ተስፋዎች በብዛት መገኘታቸው የመጽሐፍ ቅዱስ ሊቃውንት ይህን ክፍል “የመጽናናት መጽሐፍ” እስከ ማለት አበቃቸው፡፡ በኤርምያስ ትንቢት ውስጥ በእጅጉ ዝነኛ የሆነው ምንባብ ስለ ዐዲሱ ኪዳን ይናገራል (31፥31-34):: ይህም የሚናገረው እስራኤል በቦታዋ ስለ መመለሷ እንጂ ስለ ግለ ሰባዊ ትንሣኤ አይደለም፡፡

ኤርምያስ እንደ ሌሎቹ የብሉይ ኪዳን ነቢያት ባለመሆኑ፣ ጽሑፉም ከሕይወቱና ከሐሳቡ ጋር የተሳሰረ በመሆኑ፣ የእርሱ ትንቢት ተማሪ የሆነ ሰው የዚህን የእግዚአብሐር ሰው ውስጣዊ ሕይወትና ባሕርያት በጥልቅ ማጤን ይኖርበታል፤ ከእነዚህም አንዳንዶቹ ቀደም ሲል በመጠኑ ተዳስሰዋል፡፡ ከተፈጥሮኣዊ ችሎታዎቹ፣ ከጥልቅ ስሜቶቹ (ውስጣዊ ስሜቶቹ)፣ ከተነሣሽነቱ፣ ከጌታ ጋር ስላለው የግል ግንኙነት ገጽታዎች በተጨማሪ፣ የኤርምያስ ንስሓዎች ተብለው የሚጠሩ፣ ከጌታ ጋር ያደረጋቸው ውይይቶች በጠላቶች ላይ ያወረዳቸው ርግማኖችና በተለይ የጸሎት ሕይወቱ ይገኛሉ፡፡ ልቡንና መንፈሳዊ መሻቶቹን እንደ እርሱ የገለጠ የብሉይ ኪዳን ነቢይ የለም፡፡ ጨዋና ፈሪ ቢሆንም እንኳ (አንዳንዶች በእርሱ ላይ እንደ ለጠፉት ግን ከቶ ሴታሴት አልነበረም፣ ከእግዚአብሔር ጥሪና እግዚአብሔር ከሰጠው ዐደራ የተነሣ ለተግባሩ በጽኑ የቆመ ሰው ነበር፡፡ ከዐላማው ሊነቃነቅ አልቻለም፡፡ በይሁዳ ውስጥ እንደ እርሱ ያለ አገሩን የሚወድ ሰው አልነበረም፤ ይሁን እንጂ የይሁዳን ኀጢአት አይቶ እንዳላየ ለማለፍ አወላውሎ ከቶ አያውቅም᎓᎓ ሕይወቱ የብቸኛና የገለልተኛ ሕይወት ነበር፤ የሰውን ኅብረትና ፍቅር ቢናፍቅም እንኳ በሕይወቱ ዘመን ሁሉ ቤተ ሰውና የቅርብ ወዳጆች አልነበሩትም:: ለወገኞቹ ጥልቅ ፍቅር ቢኖረውም እንኳ ሥቃያቸውንና ብሔራዊ ጥፋታቸውን ይፋ ያደርግ ዘንድ በመለኮት ዐደራ ተሰጥቶት ነበር፡፡ ከእግዚአብሔር ጋር የነበረው ኅብረት የተለየ ጥልቀትና ቅርርብ ነበረው፡፡ አንዳንድ ጊዜ ይህን ያህል ግልጽ በመሆኑ፣ በዘመናችን የሚገኙት አያሌ የእርሱ መጽሐፍ ተማሪዎች ይህማ እግዚአብሔርን እንደ መሳደብ ወይም ተገቢውን ክብር እንደ መንፈግ የሚቈጠር ነው ከማለት አድርሷቸዋል፡፡



ይቀጥላል...



ምንጭ፦ የብሉይ ኪዳን ማብራሪያ፤ ገጽ 827-828



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍51
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍1
የሮሜ_መልእክት_የጥናት_መምሪያ_እና_ማብራሪያ.pdf
19 MB
👉ርዕስ፦ የሮሜ መልእክት የጥናት መምሪያ እና ማብራሪያ፣
በትምህርተ መለኮት ማስፋፊያ (ት.መ.ማ) መልክ የተዘጋጀ
ጸሐፊ፦ ስቲቭ ስትራውስ
🗣ትርጉም፦ ጌቱ ግዛው
✏️እርማት፦ ኃይሌ ጀናይና ግርማይ
🖨አሳታሚ፦ ኤስ. አይ. ኤም


ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍4
.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“ጌታ ኃጢአቱን የማይቆጥርበት ሰው ብፁዕ ነው።”
ሮሜ 4፥8




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍4
የሃኪሙ ሉቃስ ጹሑፎች የአጻጻፍ ስልት እና ይዘት


3. ዓለም አቀፋዊ ትኩረት

ሉቃስ የኢየሱስን ተልእኮ ዓለም አቀፋዊ እንደሆነ አጽንዖት ሰጥቷል፣ ይህም ለሁሉም ሰዎች ማለትም አሕዛብን፣ ሴቶችን፣ ድሆችን እና የተገለሉ ቡድኖችን ጨምሮ መቀላቀልን ያሳያል።

ምሳሌ፦ በሉቃስ ውስጥ ያለው የዘር ሐረግ የኢየሱስን የዘር ሐረግ ከአዳም ጀምሮ ያሳያል (ሉቃስ 3፥23-38)። ይህም ጌታችን እና መድኋኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የመጣው አይሁዳዊያንን ብቻ ሳይሆን የሰውን ዘር በሙሉ ለማዳን እንደመጣ ለማስገንዘብ ነው።

4. ለተገለሉ ቡድኖች ትኩረት መስጠት

ሉቃስ ስለሴቶች፣ ሳምራውያን፣ ቀራጮች እና ኃጢአተኞች ታሪኮችን በልዩ ሁኔታ አጉልቶ ያሳያል።
 
ምሳሌዎች፡- የደጉ ሳምራዊ ምሳሌ (ሉቃስ 10፥25–37)። ኃጢአተኛዋ ሴት ኢየሱስን ሽቶ ስለቀባችው ታሪክ (ሉቃስ 7፥36–50)።

5. በጸሎት እና በመንፈስ ቅዱስ ላይ ማተኮር 

ሉቃስ ጸሎትን እና የመንፈስ ቅዱስን ሥራ በኢየሱስ ክርስቶስ ሕይወት እና በቀደመችው ቤተክርስቲያን ውስጥ በተደጋጋሚ ሁኔታ ትኩረት ሰጥቶ ያነሳዋል። 

ምሳሌ፡- የኢየሱስ ጸሎት (ሉቃስ 3፥21፣ 5፥16፣ 6፥12፣ 22፥39–46)። በጰንጠቆስጤ የመንፈስ ቅዱስ መውረድ (ሐዋ. 2፡1-4)።


ይቀጥላል...



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍31
#የእግዚአብሔር_ቃል_ምን_ይላል?


ኤርምያስ 23
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
³³ ይህ ሕዝብ ወይም ነቢይ ወይም ካህን፦ የእግዚአብሔር ሸክም ምንድር ነው? ብሎ ቢጠይቅህ፥ አንተ፦ ሸክሙ እናንተ ናችሁ፥ እጥላችሁማለህ፥ ይላል እግዚአብሔር ትላቸዋለህ።
³⁴ የእግዚአብሔር ሸክም የሚለውን ነቢይንና ካህንን ሕዝብንም ያን ሰውና ቤቱን እቀጣለሁ።
³⁵ አንዱም አንዱ ለባልንጀራው፥ አንዱም አንዱ ለወንድሙ እንዲህ ይበል፦ እግዚአብሔር የመለሰው ምንድር ነው? እግዚአብሔርስ ምን ነገር ተናገረ?
³⁶ ለሰው ሁሉ ቃሉ ሸክም ይሆንበታልና የእግዚአብሔር ሸክም ብላችሁ ከእንግዲህ ወዲህ አትጥሩ፤ የሠራዊትን ጌታ የአምላካችንን የእግዚአብሔርን የሕያውን አምላክ ቃል ለውጣችኋልና።
³⁷ ለነቢዩ፦ እግዚአብሔር ምን መለሰልህ? እግዚአብሔርስ የተናገረው ምንድር ነው? ትላለህ።
³⁸ ነገር ግን፦ የእግዚአብሔር ሸክም ብትሉ፥ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ እኔ፦ የእግዚአብሔር ሸክም አትበሉ ብዬ ልኬባችኋለሁና፥ እናንተም ይህን ቃል፦
³⁹ የእግዚአብሔር ሸክም ብላችኋልና ስለዚህ፥ እነሆ፥ ፈጽሜ እረሳችኋለሁ እናንተንም ለእናንተና ለአባቶቻችሁም የሰጠኋትን ከተማ ከፊቴ እጥላለሁ።
⁴⁰ የዘላለምንም ስድብ ከቶም ተረስቶ የማይጠፋውን የዘላለምን እፍረት አመጣባችኋለሁ።




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍51👎1
.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“በእውነት ኤፍሬም ለእኔ የከበረ ልጅ ነውን? ወይስ የተወደደ ሕፃን ነውን? በእርሱ ላይ በተናገርሁ ቍጥር አስበዋለሁ፤ ስለዚህ አንጀቴ ታወከችለት ርኅራኄም እራራለታለሁ፥ ይላል እግዚአብሔር።”
ኤርምያስ 31፥20



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍6
#ከተማ_ወይም_ቦታ_በቅዱሳት_መጻሕፍት


#ጊብዓ

ጊብዓ፤ ጉብታ ወይም ኮረብታ ማለት ነው።
1. በይሁዳ የነበረ ከተማ።  ኢያሱ 15፥57።
2. ከኢየሩሳሌም ወደ ሰሜን አምስት ኪ.ሜ. ያህል ርቆ የሚገኝ የብንያም አገር ከተማ። የብንያም ጊብዓ በአሁን ጊዜ ከኢየሩሳሌም በስተሰሜን የምትገኝ ዘመናዊቷ ቴል ኤል ፉል ላይ እንደነበረች ይገመታል። የአርኪኦሎጂ ቁፋሮዎች የጥንት ምሽግ ቅሪቶችን በቁፋሮ አግኝተዋል፣ ይህም ግምቶችን እውነተኛ ሊሆኑ እንድሚችሉ አረጋግጧል።
የጊብዓ ሰዎች አስጸያፊ ብልግና ስላደረጉ እስራኤላውያን የብንያምን ወገን ለማጥፋት ተነሡ፤ ሆኖም 600 ሰዎች አምልጠዋል፤ መሳ. 19፥11-20፡48። ግን ንጉሥ ሳኦል የጊብዓ ሰው ነበረና መናገሻ ከተማውን በጊብዓ አደረገ፤ 1ሳሙ. 10፥26፤ 22፥6። በብሉይ ኪዳን ዘመን ጊብዓ ምሽግ ከተማ ነበረ፤ ከክርስቶስ ልደት ወዲህ ግን ባድማ ሆኗል።

ጊብዓ የምትታወቅባቸው ዋና ዋና የታሪክ ሁነቶች፦

👉የሌዋዊው ቁባት በጊብዓ ሰዎች በተፈጸመባት አሳቃቂ ግፍ የደረሰው ቁጣና ያስከተለው መዘዝ (መሳ. ምዕራፍ 19-21)

👉ጊብዓ የእስራኤል የመጀመሪያው ንጉሥ የንጉሥ ሳኦል የትውልድ ከተማ ነበረች። (1ኛ ሳሙኤል 10፥26፤ 1ሳሙ 15፥34-35)

👉የጊብዓ ትንቢታዊ ውግዘቶች፡- ነብያት ከጊዜ በኋላ ጊብዓን በመሳፍንት ውስጥ በተመዘገቡት ድርጊቶች ምክንያት የእስራኤል የሥነ ምግባር ውድቀት ምልክት እንደሆነች ጠቅሰዋል። (ሆሴዕ 9፥9፤ ሆሴዕ 10፥9።


ምንጭ፦ የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት፤ ገጽ 242




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍31😁1
.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“በቸርነትህ የተቤዠሃቸውን ሕዝብህን መራህ፤ በኃይልህ ወደ ቅዱስ ማደሪያህ አገባሃቸው።”
ዘጸአት 15፥13



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
4👍1
እየጨመረ የሚሄድ ሕይወት
                
         


የጠለቀ መንፈሳዊ ጉዞ ለመጓዝና እየጨመረ የሚሄድ ርካታና እረፍት እንድናይ ካስፈለገ፣የክርስትና ሕይወት ትጋትን ይጠይቀናል(ዕብ 4:11)፡፡ በተለያየ ቦታ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ቃሉ እንደሚያስተምረን ትጋታችን እየጨመረ ሲሄድ፣ የእግዚአብሔር ጸጋም በሕይወታችን እየጨመረ ይሄዳል፡፡ እናም ለመንፈሳዊ ነገር ያለን መሻት እያደገ ይሄዳል፡፡ በእንደዚህ ዓይነት ግሥገሣ ውስጥ ባለማሰለስ ስንገኝ፣ እሱን ለማወቅ ያለን ራብ እየተቀጣጠለ ስለሚመጣ፣እየጨመረ ለሚሄድ ፍለጋ እንጠናከራለን፡፡ ይህንን በእንግሊዝኛው አገላለጽ positive vicious cycle ይሉታል፡፡ ማለትም ትጋቱ የጨመረ መንፈሳዊ ራብን ይወልዳል፤ የጨመረው መንፈሳዊ ራብ ደግሞ ሌላ ከፍ ያለ ትጋትንና ግሥገሣን ይወልዳል፡፡ መቼም ይሄ ኡደት ማቆሚያ የለውም እኛ በሥጋዊ አካሄዶች እስካላጠፋነው ድረስ!

በነገራችን ላይ እየጨመረ የሚሄድ የክርስትና ሕይወት ብዙ ግብዓቶችን ይፈልጋል ፡፡ መልካም የእምነት ውጊያንና ዲያቢሎስን በኃይል ጸንቶ መቃወም ይጠይቃል ፡፡ የእግዚአብሔርን ቃል ሳይታክቱ ማሰላሰልና በፊቱ ጥሩ የሆኑ ጊዜዎችን ማሳለፍ ግድ ይለናል ፡፡ ሁኔታዎችንና ሥጋችንን ሳናዳምጥ የሚከፈሉ ዋጋዎችን እንደ ጌታ ፈቃድ መክፈልን ይጠይቀናል፡፡

ሦስት በተሰናሰለ መንገድ የተቀመጡ ድርጊቶች በውጤት ሂደት እንዲህ ተቀምጠዋል፡-

ድርጊት(Action)-->ልማድ(Habit)-->ጠባይ(character)

ይህንን መርሕ ለመግለጽ ጸሎትን እንደ ምሳሌ ልውሰድ ፡፡ ጸሎትን ደጋግመን ስናደርገው ወደ ልማድነት ይቀየራል ፡፡ በሕይወታችን ልማድ እየሆነ የመጣውን ተግባር እየጨመርን ደጋግመን ስናደርገው፣ ጠባያችን ወይም መገለጫ ባሕርያችን ይሆናል ፡፡ ከዚያማ ውጤቱ እንዲህ ይሆናል፡-

“መጸለይ እንጂ አለመጸለይ አንችልም፡፡”
“በፊቱ መሆን እንጂ አለመሆን ያቅተናል፡፡”
እጅግ ሊጓጓለት የሚገባ ድንቅ ለውጥ!

የላይኛውን ሐሳብ የሚደግፉና የክርስትና ሕይወት እየተቀጣጠለ፣ እያደገና እየጨመረ የሚሄድ ሕይወት እንደ ሆነ የሚጠቁሙ ብዙ ክፍሎች አሉ ፡፡ ለምሳሌ ሦስቱን ልጥቀስ፡-

“እስከ እግዚአብሔር ፍጹም ሙላት ደርሳችሁ ትሞሉ ዘንድ” (ኤፌሶን 3፥19)

“በመንፈስ የምትቃጠሉ ሁኑ” (ሮሜ 12፥11)

“መንፈስ ይሙላባችሁ እንጂ በወይን ጠጅ አትስከሩ ይህ ማባከን ነውና” /ብዙ የሚያሰክሩ ነገሮች እንዳሉ ልብ ይሏል/(ኤፌሶን 5፥16-20)

ስሚዝ ዊግልስዎርዝ እንዲህ ብሎ ነበር፡-“If you are in the same place today as you were yesterday, you are a backslider.”(ትርጉሙ፡-በዛሬው ቀን ትላንትና የነበርክበት ቦታ ላይ ከተገኘህ የኋሊት እየሄድክ ነው)

በተሰጠ ማንነት፣ ልባችን መሉ በሙሉ በጌታ ላይ ሆኖ ከላይ በተጠቀሰው ዓይነት ፍለጋ(craving) እና ትጋት ስንቀጥል፣ የጌታ አብሮሆት ከመቸው በሚበልጥ ሁኔታ በሕይወታችን ዕውን ይሆናል ፡፡ ከዚህም የተነሣ የምናገኘው የመጀመሪያው በረከት በቃላት ልንገልጸው የማንችለው ሰላም፣ መረጋጋትና ደስታ ይሆናል ፡፡ መንፈሳዊ መረዳታችንም እየጨመረ ስለሚሄድ፣ ጌታን በሚገባ እያወቅነው እንመጣለን፡፡ስለዚህ ለውጣችን ወደ ኋላ የማይቀለበስና ዘላቂ ይሆናል ፡፡ መንፈሳዊ ዓይኖቻችን በጨመረ ሁኔታ እየተከፈቱ ስለሚመጡ፣ ብዙ ረብ የሌላቸውን ነገሮች የመጣል መነሣሣትና አቅም እያገኘን እንመጣለን ፡፡

እንደዚህ በጽናት ሳናሰልስ የጌታን ፊት በጨመረ ሁኔታ በፈለግን ቁጥር፣ የእግዚአብሔር ኃይል በውስጣችን እየጨመረ ስለሚሄድ፣ ብዙ ቀንበሮች ከሕይወታችን ይሰበራሉ ፡፡ ስለዚህም “ሸክሙ ከጫንቃህ ቀንበሩም ከትከሻህ ላይ ይሰበራል” የሚለው ቃል በሕይወታችን ይፈጸማል (ኢሳ.10፡27)፡፡ እናም ከበፊቱ ይልቅ በሕልውናው ውስጥ መቆየት አያስቸግረንም፡፡ ቃሉ እንዲህ ይላልና፡-

“እርሱንም ሳታዩት ትወዱታላችሁ፤ አሁንም ምንም ባታዩት በእርሱ አምናችሁ የእምነታችሁን ፍጻሜ እርሱም የነፍሳችሁን መዳን እየተቀበላችሁ በማይነገርና ክብር በሞላበት ሐሤት ደስ ይላችኋል” (1 ጴጥሮስ 1፥8-9)

ለዚህ አሳብ ጥሩ እይታ የሚሰጠን ኢዮብ 28፥1-11 ነው ፡፡ ይህ የምንባብ ክፍል የማዕድን ሠራተኛ ከባዶ ተነሥቶ የሚያደርገውን ግሥገሣ ነው የሚያሳየው ፡፡ “ዓይኑ ዕንቁን እስክታይ ድረስ” ፣ “የተሸፈነው ነገር ወደ ብርሃን እስኪወጣ ድረስ” ይተጋል ፡፡ እጁን ወደ ቡላድ ድንጋይ ይዘረጋል ፡፡ መጨረሻ ላይ ከብዙ እልህ አስጨራሽ ትግልና ጉዞ በኋላ የከበሩ ማዕድናትን ያገኛል፤ክፍሉ የልፋቱን ውጤት እንዲህ ይገልጸዋልና ፡-

“ሰው ወደ ቡላድ ድንጋይ እጁን ይዘረጋል፤ ተራራውንም ከመሠረቱ ይገለብጣል። ከድንጋይ ውስጥ መንዶልዶያ ይወቅራል፤ ዓይኑምዕንቍን ሁሉ ታያለች።   ፈሳሹም እንዳይንጠባጠብ ይገድባል፤የተሰወረውንም ነገር ወደ ብርሃን ያወጣል።”(ቁ.9-11)

አዎ ይህ ክፍል ምሳሌያዊ በሆነ አገላለጽ፣ እንደ ማዕድን ሠራተኛው ያለ መታከት እንድንተጋና የጌታን ፊት እንድንፈልግ ያስተምረናል ፡፡

የእግዚአብሔር ቃል ተግተው “የሚሹኝ ምስጉኖች/የተባረኩ ናቸው” (ምሳሌ 8፡34) ይላልና፤ “እናንተም ትጠሩኛለችሁ፤ ሄዳችሁም ወደ እኔ ትጸልያላችሁ፣እኔም እሰማችኋለሁ። እናንተ ትሹኛላችሁ፣በፍጹም ልባችሁም ከሻችሁኝ ታገኙኛላችሁ። ከእናንተም ዘንድ እገኛለሁ፡፡”(ኤር.29፥13-14) ይላልና ጨክኖ የጌታን ፊት የሚፈልግ ሰው ይዋል ይደር እንጂ፣ የእግዚአብሔር በረከት ታገኘዋለች፡፡

አዎ፣ ጌታ አጥብቀው ለሚሹት ሰዎች በእርግጥ ይገለጣል፡፡ የበለጠ እንድናየው፣ የበለጠ በእርሱ ላይ እንድንደገፍና እንድንጠጋው ያደርገናል፡፡ በተጨማሪም ጌታ ተገልጦ ሕይወታችንን ሲጎበኝ የሚመጣው ለውጥ ለሌሎች በረከት ያደርገናልና በትጋትና በጨመረ ሁኔታ ተግተን እንፈልገው!



ምንጭ:- ዶ/ር በቀለ በላቸው፤ ባለጸጋ ክርስትያን መጽሔት




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍232
.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“በአምላክህም በእግዚአብሔር ፊት እንዲህ ብለህ ተናገር፦ አባቴ የተቅበዘበዘ ሶርያዊ ነበረ፤ በቍጥር ጥቂት ሳለ ወደ ግብፅ ወረደ በዚያም ተቀመጠ፤ ታላቅ የሆነ የበረታም ቍጥሩም የበዛ ሕዝብ ሆነ።”
ዘዳግም 26፥5



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
7👎1
የሃኪሙ ሉቃስ ጹሑፎች የአጻጻፍ ስልት እና ይዘት


6. ምሳሌዎች እና ታሪኮች

ሉቃስ በሌሎች ወንጌሎች ውስጥ የማይገኙ በርካታ ምሳሌዎችን ያካትታል፣ ብዙ ጊዜ በጸጋ እና በርኅራኄ ላይ ያተኩራል።

ምሳሌዎች፡-አባካኙ ልጅ (ሉቃስ 15፥11–32)። ባለጠጋው እና አልዓዛር (ሉቃስ 16፥19–31)።

7. የሕክምና ቃላት

እንደ ሃኪም (ቆላስይስ 4፥14) ሉቃስ አልፎ አልፎ የህክምና ቃላትን እና ስለ በሽታዎች እና ፈውሶች ትክክለኛ መግለጫዎችን ይጠቀማል።

ምሳሌ፡- ሆዱ የተነፋ ሰው መፈወስ ሲገልጽ (ሉቃስ 14፥2) ሉቃስ የተለየ የሕክምና ቃል ተጠቅሟል።

8. የዘመን ቅደም ተከተል እና ጭብጥ ማደራጀት

ሃኪሙ ሉቃስ ትረካውን በጊዜ ቅደም ተከተል እና በጭብጥ አዋቅሮታል። ብዙውን ጊዜ የጌታችን እና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ሕይወት ክስተቶች ከሰፋፊ ሥነ-መለኮታዊ ጭብጦች ጋር ያገናኛል።

ምሳሌ፡- በሉቃስ-ሐዋርያት ውስጥ ያለው ሥርዓት ያለው ቅደም ተከተል የኢየሱስን ሕይወት ከጥንቷ ቤተ ክርስቲያን እድገት ጋር ያገናኛል (ሐዋ. 1፥1-2)።

9. የመዝሙር እና የግጥም ውህደት

ሉቃስ በብዛት ዝማሬዎችን እና የቅኔ ምንባባትን አካቷል። የማርያም ውዳሴ፣ ዘካርያስ አድናቆት፣ የመላእክት ክብር እና የስምዖን ቅኔያዊ ምንባቦችን ያካትታል።

ምሳሌዎች፡- (ሉቃስ 1፥46-55)። (ሉቃስ 2፥29–32)።


ይቀጥላል...



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
2👍2
.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“ወደ ዘላለም ሕይወት የሚወስደውን የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ምሕረት ስትጠባበቁ በእግዚአብሔር ፍቅር ራሳችሁን ጠብቁ።”
ይሁዳ 1፥21



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍91🔥1🥰1
#እራሳችንን_እንመርምር



ስለ ወንጌል ምን እናደርጋለን? በወንጌል ማኅበረተኛ እንሆን ዘንድስ? ወይስ "ወንጌል ምኔ ነው?" ብለን ለሆነ ወገን አስረክበን እየኖርን ነው?


“በወንጌልም ማኅበረተኛ እሆን ዘንድ ስለ ወንጌል ሁሉን አደርጋለሁ።”
1ኛ ቆሮንቶስ 9፥23




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
6👍2
.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“በጽድቅ መንገድ ላይ ሕይወት አለ በጎዳናዋም ሞት የለም።”
ምሳሌ 12፥28



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
4👍2🔥2🥰1
የሃኪሙ ሉቃስ ጹሑፎች የአጻጻፍ ስልት እና ይዘት


10. ድርብ ሥራ፡- ወንጌል እና የሐዋርያት ሥራ

የሉቃስ ባለ ሁለት ጥራዝ ሥራ ከኢየሱስ አገልግሎት ጀምሮ እስከ ቤተ ክርስቲያን ምስረታ ድረስ ያለውን የእግዚአብሔር ዕቅድ ቀጣይነት ያሳያል።

ምሳሌ፦ የሐዋርያት ሥራ የሚጀምረው በኢየሱስ ዕርገት እና በመንፈስ ቅዱስ ተስፋ (ሉቃስ 24፥50–53፤ የሐዋርያት ሥራ 1፥1–11) የሉቃስ ወንጌል በሚያልቅበት ቦታ ነው።

11. የሴቶች ሚና

በሉቃስ ወንጌል ውስጥ ሴቶች ትልቅ ሚና ተሰጥቷቸዋል። ለምሳሌ ማርያም፣ ኤልሳቤጥ፣ ኢየሱስን ሽቶ የቀባችው ኃጢአተኛ ሴት (ሉቃስ 7፥36-50) እና መግደላዊት ማርያም ይገኙበታል።
ሉቃስ በትረካዎቹ ውስጥ ብዙ ጊዜ ወንዶችንና ሴቶችን ያጣምራል፣ ይህም የጾታ እኩልነትን በእግዚአብሔር መንግሥት ውስጥ አጉልቶ ያሳያል (ለምሳሌ፡ ስምዖን እና ሐና በሉቃስ 2፥25-38)።



ምንጭ፦
👉Luke, Gospel of. The Holy Bible (NIV, ESV, KJV, or other preferred translations).
👉Fitzmyer, J. A. (1981). The Gospel According to Luke I–IX. Anchor Bible Commentary.
👉Johnson, L. T. (1992). The Acts of the Apostles. Sacra Pagina Commentary.



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
3
.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“አቤቱ፥ ምሕረትህንና ቸርነትህን አስብ፥ ከጥንት ጀምሮ ናቸውና።”
መዝሙር 25፥6



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
5
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍1