ትህትና
ከእግዚአብሔር ጋር ለመኖርና አሸናፊ ለመሆን ትህትና እጅግ አስፈላጊ ባህሪ ነው፡፡ ካለ ትህትና ከእግዚአብሔር ጋር እንጣላለን፡፡ እንዲያውም እግዚአብሄር ትዕቢተኛውን ይቃወማል፡፡
"ነገር ግን ጸጋን አብልጦ ይሰጣል፤ ስለዚህ፦ እግዚአብሔር ትዕቢተኞችን ይቃወማል፥ ለትሑታን ግን ጸጋን ይሰጣል ።" ያዕቆብ 4፡6
ትህትና ይህን ያህል አስፈላጊ ከሆነ ትህትና ግን ምንድነው ብለን መጠየቅ ጥበብ ነው፡፡ ትህትናን በደንብ ልንማረውና ልናጠናው ተግተንም ልንለማመደው የሚገባ የተወደደ ባህሪ ነው፡፡
ትህትና ለሁሉም ሰው ያለ አክብሮት ነው፡፡ ትሁት ሰው ለወገኔ ይጠቅማል በማለት አንዱን ከሌላው ሰው በወገናዊነት አያበላልጥም፡፡ ትሁት ሰው ለሁሉም ከፍ ያለ አክብሮት ያለው ሰው ሲሆን ሁሉንም ለማገልገልና ለመጥቀም የተዘጋጀ ነው፡፡
"ለወገኔ ይጠቅማል በማለት ወይም በከንቱ ውዳሴ ምክንያት አንድ እንኳ አታድርጉ::" ፊልጵስዩስ 2፡3
ትሁት ሰው ሌላው ሰው ከእርሱ እንደሚሻል በቅንነትና በእውነት የሚያምን ነው፡፡ ትሁት ሰው ራሱን ብቻ አስፈላጊ አድርጎ የማይመለከት ሰው ነው፡፡ ትሁት ሰው የሰውን ሁሉ አስፈላጊነት የሚረዳ ሰው ነው፡፡ ትሁት ሰው በሌላው ሰው ስጦታ ጥሪና ጠቃሚነት የሚያምን ነው፡፡
"ነገር ግን እያንዳንዱ ባልንጀራው ከራሱ ይልቅ እንዲሻል በትሕትና ይቍጠር::" ፊልጵስዩስ 2፡3
ትሁት ሰው የራሱን ብቻ የማይፈልግ ሰው ነው፡፡ ትሁት ሰው ሌላውንም የሚጠቅመውን ነገር ለማድረግ የሚፈልግ ሰው ነው፡፡ ትሁት ሰው ራስ ወዳድ አይደለም፡፡ ትሁት ሰው ለሌላው ጥቅም በትጋት የሚሰራ ሰው ነው፡፡
"እያንዳንዱ ለራሱ የሚጠቅመውን አይመልከት፥ ለባልንጀራው ደግሞ እንጂ" ፊልጵስዩስ 2፡4
ትህትና እንደ ክርስቶስ ራስን አዋርዶ መኖር ነው፡፡ የሰው ትህትና የሚጀምረው ከአሳብ ነው፡፡ ሰው ገና በአሳብ ደረጃ ራሱን ካላዋረደ በትህትና ሊመላለስ አይችልም፡፡ ትሁት ሰው የትህትና መልክ ብቻ ሳይሆን የትህትና ሃሳብና ውሳኔ ያለው ነው፡፡
"በክርስቶስ ኢየሱስ የነበረ ይህ አሳብ በእናንተ ዘንድ ደግሞ ይሁን።" ፊልጵስዩስ 2፡5
ከኢየሱስ የምንማረው ትሁት ሰው ለደረጃ ግድ እንደሌለው ነው፡፡ ትሁት ሰው ስለደረጃ አይጣላም አይጨቃጨቅም፡፡ ትሁት ሰው ትኩረቱ ማገልገል ሰውም መጥቀም በሰው ላይ ዋጋን መጨመር ሰውን ማንሳት ላይ እንጂ ስለስምና ስለስልጣን ወይም ጥቅም አይደለም፡፡ ትሁት ሰው የትም ማገልገል ስለሚችል መቼም ለመውረድ የተዘጋጀ ነው፡፡
"እርሱ በእግዚአብሔር መልክ ሲኖር ሳለ ከእግዚአብሔር ጋር መተካከልን መቀማት እንደሚገባ ነገር አልቈጠረውም፥" ፊልጵስዩስ 2፡6
ትሁት ሰው እግዚአብሔርም እንዲያዋርደው የማያደርግ ቀድሞ ራሱን የሚያዋርድ ነው፡፡ ትሁትን ሰው የምናውቀው ሁኔታ ስላልተመቸው በመዋረዱ ሳይሆን ከፍ የሚያደርግ ሁኔታ እያለ በራሱ ፈቃድ ራሱን የሚያዋርድ ሰው ነው፡፡
ትሁት ሰው ሰዎችን ለመጥቀም በምድር ላይ እንዳለ የሚያውቅ ሰው ሲሆን ሰዎች ሲጠቀሙበት እንደ እድል እንጂ እንደ ሽንፈት የማይቆጥር ሰው ነው፡፡ ትሁት ሰው ሰዎች እንደተጠቀሙበት የሚሰማውን አፍራሽ ስሜት የማይቀበል ሰዎች እንዲጠቀሙበት የሚፈቅድ የባሪያ ልብ ያለው ለራሱ የማይሰስት ሰው ነው፡፡
"ነገር ግን የባሪያን መልክ ይዞ በሰውም ምሳሌ ሆኖ ራሱን ባዶ አደረገ፥" ፊልጵስዩስ 2፡7
ትሁት ሰው ነገሮችን ካደረገ በኋላ ክፍያውን የማይተምን በትህትናው የማይመካ ስላደረገው ስራ ዋጋውን ራሱ የማይተምን ሃላፊነቱን ብቻ እንደተወጠ የሚሰማው ሰው ነው፡፡ ትሁት ሰው ምንጩ እግዚአብሔር እንደሆነ የሚረዳ እንካ በእንካ አገልግሎት የሌለው ሰው ነው፡፡
"እንዲሁ እናንተ ደግሞ የታዘዛችሁትን ሁሉ ባደረጋችሁ ጊዜ፦ የማንጠቅም ባሪያዎች ነን፥ ልናደርገው የሚገባንን አድርገናል በሉ።" ሉቃስ 17፡10
ትሁት ሰው ማንነቱን ጠንቅቆ የተረዳ ፣ ክብሩን የሚያውቅ ፣ የእርሱ ዝቅ ብሎ ማገልገል ምንም እንደማያዋርደው የሚያውቅ ሰው ነው፡፡ ትሁት ሰው በእግዚአብሔር ካለው ክብር እርሱን ሊያዋርደው የሚችል ምንም ነገር እንደሌለ የተረዳ ነው፡፡
"ኢየሱስ አብ ሁሉን በልጁ እንደ ሰጠው ከእግዚአብሔርም እንደ ወጣ ወደ እግዚአብሔርም እንዲሄድ አውቆ፥ ከእራት ተነሣ ልብሱንም አኖረ፥ ማበሻም ጨርቅ ወስዶ ታጠቀ፤ በኋላም በመታጠቢያው ውኃ ጨመረ፥ የደቀ መዛሙርቱንም እግር ሊያጥብና በታጠቀበትም ማበሻ ጨርቅ ሊያብስ ጀመረ።" ዮሐንስ 13፡3-5
ምንጭ:- አብይ ዋቁማ
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ከእግዚአብሔር ጋር ለመኖርና አሸናፊ ለመሆን ትህትና እጅግ አስፈላጊ ባህሪ ነው፡፡ ካለ ትህትና ከእግዚአብሔር ጋር እንጣላለን፡፡ እንዲያውም እግዚአብሄር ትዕቢተኛውን ይቃወማል፡፡
"ነገር ግን ጸጋን አብልጦ ይሰጣል፤ ስለዚህ፦ እግዚአብሔር ትዕቢተኞችን ይቃወማል፥ ለትሑታን ግን ጸጋን ይሰጣል ።" ያዕቆብ 4፡6
ትህትና ይህን ያህል አስፈላጊ ከሆነ ትህትና ግን ምንድነው ብለን መጠየቅ ጥበብ ነው፡፡ ትህትናን በደንብ ልንማረውና ልናጠናው ተግተንም ልንለማመደው የሚገባ የተወደደ ባህሪ ነው፡፡
ትህትና ለሁሉም ሰው ያለ አክብሮት ነው፡፡ ትሁት ሰው ለወገኔ ይጠቅማል በማለት አንዱን ከሌላው ሰው በወገናዊነት አያበላልጥም፡፡ ትሁት ሰው ለሁሉም ከፍ ያለ አክብሮት ያለው ሰው ሲሆን ሁሉንም ለማገልገልና ለመጥቀም የተዘጋጀ ነው፡፡
"ለወገኔ ይጠቅማል በማለት ወይም በከንቱ ውዳሴ ምክንያት አንድ እንኳ አታድርጉ::" ፊልጵስዩስ 2፡3
ትሁት ሰው ሌላው ሰው ከእርሱ እንደሚሻል በቅንነትና በእውነት የሚያምን ነው፡፡ ትሁት ሰው ራሱን ብቻ አስፈላጊ አድርጎ የማይመለከት ሰው ነው፡፡ ትሁት ሰው የሰውን ሁሉ አስፈላጊነት የሚረዳ ሰው ነው፡፡ ትሁት ሰው በሌላው ሰው ስጦታ ጥሪና ጠቃሚነት የሚያምን ነው፡፡
"ነገር ግን እያንዳንዱ ባልንጀራው ከራሱ ይልቅ እንዲሻል በትሕትና ይቍጠር::" ፊልጵስዩስ 2፡3
ትሁት ሰው የራሱን ብቻ የማይፈልግ ሰው ነው፡፡ ትሁት ሰው ሌላውንም የሚጠቅመውን ነገር ለማድረግ የሚፈልግ ሰው ነው፡፡ ትሁት ሰው ራስ ወዳድ አይደለም፡፡ ትሁት ሰው ለሌላው ጥቅም በትጋት የሚሰራ ሰው ነው፡፡
"እያንዳንዱ ለራሱ የሚጠቅመውን አይመልከት፥ ለባልንጀራው ደግሞ እንጂ" ፊልጵስዩስ 2፡4
ትህትና እንደ ክርስቶስ ራስን አዋርዶ መኖር ነው፡፡ የሰው ትህትና የሚጀምረው ከአሳብ ነው፡፡ ሰው ገና በአሳብ ደረጃ ራሱን ካላዋረደ በትህትና ሊመላለስ አይችልም፡፡ ትሁት ሰው የትህትና መልክ ብቻ ሳይሆን የትህትና ሃሳብና ውሳኔ ያለው ነው፡፡
"በክርስቶስ ኢየሱስ የነበረ ይህ አሳብ በእናንተ ዘንድ ደግሞ ይሁን።" ፊልጵስዩስ 2፡5
ከኢየሱስ የምንማረው ትሁት ሰው ለደረጃ ግድ እንደሌለው ነው፡፡ ትሁት ሰው ስለደረጃ አይጣላም አይጨቃጨቅም፡፡ ትሁት ሰው ትኩረቱ ማገልገል ሰውም መጥቀም በሰው ላይ ዋጋን መጨመር ሰውን ማንሳት ላይ እንጂ ስለስምና ስለስልጣን ወይም ጥቅም አይደለም፡፡ ትሁት ሰው የትም ማገልገል ስለሚችል መቼም ለመውረድ የተዘጋጀ ነው፡፡
"እርሱ በእግዚአብሔር መልክ ሲኖር ሳለ ከእግዚአብሔር ጋር መተካከልን መቀማት እንደሚገባ ነገር አልቈጠረውም፥" ፊልጵስዩስ 2፡6
ትሁት ሰው እግዚአብሔርም እንዲያዋርደው የማያደርግ ቀድሞ ራሱን የሚያዋርድ ነው፡፡ ትሁትን ሰው የምናውቀው ሁኔታ ስላልተመቸው በመዋረዱ ሳይሆን ከፍ የሚያደርግ ሁኔታ እያለ በራሱ ፈቃድ ራሱን የሚያዋርድ ሰው ነው፡፡
ትሁት ሰው ሰዎችን ለመጥቀም በምድር ላይ እንዳለ የሚያውቅ ሰው ሲሆን ሰዎች ሲጠቀሙበት እንደ እድል እንጂ እንደ ሽንፈት የማይቆጥር ሰው ነው፡፡ ትሁት ሰው ሰዎች እንደተጠቀሙበት የሚሰማውን አፍራሽ ስሜት የማይቀበል ሰዎች እንዲጠቀሙበት የሚፈቅድ የባሪያ ልብ ያለው ለራሱ የማይሰስት ሰው ነው፡፡
"ነገር ግን የባሪያን መልክ ይዞ በሰውም ምሳሌ ሆኖ ራሱን ባዶ አደረገ፥" ፊልጵስዩስ 2፡7
ትሁት ሰው ነገሮችን ካደረገ በኋላ ክፍያውን የማይተምን በትህትናው የማይመካ ስላደረገው ስራ ዋጋውን ራሱ የማይተምን ሃላፊነቱን ብቻ እንደተወጠ የሚሰማው ሰው ነው፡፡ ትሁት ሰው ምንጩ እግዚአብሔር እንደሆነ የሚረዳ እንካ በእንካ አገልግሎት የሌለው ሰው ነው፡፡
"እንዲሁ እናንተ ደግሞ የታዘዛችሁትን ሁሉ ባደረጋችሁ ጊዜ፦ የማንጠቅም ባሪያዎች ነን፥ ልናደርገው የሚገባንን አድርገናል በሉ።" ሉቃስ 17፡10
ትሁት ሰው ማንነቱን ጠንቅቆ የተረዳ ፣ ክብሩን የሚያውቅ ፣ የእርሱ ዝቅ ብሎ ማገልገል ምንም እንደማያዋርደው የሚያውቅ ሰው ነው፡፡ ትሁት ሰው በእግዚአብሔር ካለው ክብር እርሱን ሊያዋርደው የሚችል ምንም ነገር እንደሌለ የተረዳ ነው፡፡
"ኢየሱስ አብ ሁሉን በልጁ እንደ ሰጠው ከእግዚአብሔርም እንደ ወጣ ወደ እግዚአብሔርም እንዲሄድ አውቆ፥ ከእራት ተነሣ ልብሱንም አኖረ፥ ማበሻም ጨርቅ ወስዶ ታጠቀ፤ በኋላም በመታጠቢያው ውኃ ጨመረ፥ የደቀ መዛሙርቱንም እግር ሊያጥብና በታጠቀበትም ማበሻ ጨርቅ ሊያብስ ጀመረ።" ዮሐንስ 13፡3-5
ምንጭ:- አብይ ዋቁማ
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍13❤1
. ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“ሰው እግዚአብሔርን ይሰርቃልን? እናንተ ግን እኔን ሰርቃችኋል። እናንተም፦ የሰረቅንህ በምንድር ነው? ብላችኋል። በአሥራትና በበኵራት ነው።”
ሚልክያስ 3፥8
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“ሰው እግዚአብሔርን ይሰርቃልን? እናንተ ግን እኔን ሰርቃችኋል። እናንተም፦ የሰረቅንህ በምንድር ነው? ብላችኋል። በአሥራትና በበኵራት ነው።”
ሚልክያስ 3፥8
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
🔥4👍3
የሐዋርያው ጳውሎስ መልእክቶች የአጻጻፍ ስልት እና ይዘት
10. የብሉይ ኪዳን ቅዱሳት መጻሕፍትን በብዛት መጠቀም
ሐዋርያው ጳውሎስ የመከራከሪያ ነጥቦቹን ለመደገፍ ብዙ ጊዜ የዕብራይስጥ ቅዱሳን ጽሑፎችን ይጠቅስ ወይም ይጠቀም ነበር።
ምሳሌ፡- ሮሜ 4 በእምነት መጽደቅን ለማስረዳት የአብርሃምን ታሪክ ይጠቀማል።
11. መዘርዘር
ጳውሎስ ዝርዝሮችን ለማጉላት እንደ በጎ ምግባር፣ ስለሥጋ ወይም መንፈሳዊ ስጦታዎች ያሉ ነጥቦችን ለማጉላት ተጠቅሟል።
ምሳሌ፦ ገላትያ 5፥22-23 የመንፈስ ፍሬዎችን ይዘረዝራል።
12. ምስጋና እና ጸሎት
አብዛኞቹ ደብዳቤዎቹ የሚጀምሩት ለተቀባዮቹ በምስጋና እና በጸሎት ነው።
ምሳሌ፡- ፊልጵስዩስ 1፥3-11 የምስጋና እና የማበረታቻ ጸሎትን ይጨምራል።
13. ሁለትነት እና ንፅፅር
ጳውሎስ ሕግን ከጸጋን፣ ሥጋን ከመንፈስን፣ እና ሞትን ከሕይወት ጋር ያነጻጽራል።
ምሳሌ፡- ሮሜ 8 እንደ ሥጋ መኖርን እና እንደ መንፈስ ፈቃድ መኖርን ያነጻጽራል።
14. ኪያስመስ (አንድን በተለየ መንገድ መድገም)
ጳውሎስ አንዳንድ ጊዜ የኪያስመስ መዋቅርን ይጠቀም ነበር፣ እሱም ሃሳቦች በመስታወታዊ ቅደም ተከተል (A-B-B-A) ለአጽንዖት ይቀርባሉ።
ምሳሌ፡- በ2ኛ ቆሮንቶስ 4፥8-9፣ የመከራ እና የነጻነት ምሳሌ ኪያስመስ ይፈጥራል።
15. ኢሻቶሎጂካል(የነገረ ፍጻሜ) ትኩረት
የክርስቶስን መምጣት እና የአማኞች የመጨረሻ ተስፋ ላይ በማተኮር ጽፏል።
ምሳሌ፡- 1ኛ ተሰሎንቄ 4፥13-18 ስለ ትንሣኤና ስለ ክርስቶስ ዳግም ምጽአት ይናገራል።
የጳውሎስ ሁለገብ የአጻጻፍ ስልት የተለያዩ አንባቢዎችን በብቃት እንዲደርስ አስችሎታል። ይህም ምሁራዊ ጥልቀትን ከእረኝነት ሙቀት ጋር በማጣመር። ይህ ጥልቀት ጽሑፎቹን ዘላቂ ተጽዕኖ አላብሷቸዋል።
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
10. የብሉይ ኪዳን ቅዱሳት መጻሕፍትን በብዛት መጠቀም
ሐዋርያው ጳውሎስ የመከራከሪያ ነጥቦቹን ለመደገፍ ብዙ ጊዜ የዕብራይስጥ ቅዱሳን ጽሑፎችን ይጠቅስ ወይም ይጠቀም ነበር።
ምሳሌ፡- ሮሜ 4 በእምነት መጽደቅን ለማስረዳት የአብርሃምን ታሪክ ይጠቀማል።
11. መዘርዘር
ጳውሎስ ዝርዝሮችን ለማጉላት እንደ በጎ ምግባር፣ ስለሥጋ ወይም መንፈሳዊ ስጦታዎች ያሉ ነጥቦችን ለማጉላት ተጠቅሟል።
ምሳሌ፦ ገላትያ 5፥22-23 የመንፈስ ፍሬዎችን ይዘረዝራል።
12. ምስጋና እና ጸሎት
አብዛኞቹ ደብዳቤዎቹ የሚጀምሩት ለተቀባዮቹ በምስጋና እና በጸሎት ነው።
ምሳሌ፡- ፊልጵስዩስ 1፥3-11 የምስጋና እና የማበረታቻ ጸሎትን ይጨምራል።
13. ሁለትነት እና ንፅፅር
ጳውሎስ ሕግን ከጸጋን፣ ሥጋን ከመንፈስን፣ እና ሞትን ከሕይወት ጋር ያነጻጽራል።
ምሳሌ፡- ሮሜ 8 እንደ ሥጋ መኖርን እና እንደ መንፈስ ፈቃድ መኖርን ያነጻጽራል።
14. ኪያስመስ (አንድን በተለየ መንገድ መድገም)
ጳውሎስ አንዳንድ ጊዜ የኪያስመስ መዋቅርን ይጠቀም ነበር፣ እሱም ሃሳቦች በመስታወታዊ ቅደም ተከተል (A-B-B-A) ለአጽንዖት ይቀርባሉ።
ምሳሌ፡- በ2ኛ ቆሮንቶስ 4፥8-9፣ የመከራ እና የነጻነት ምሳሌ ኪያስመስ ይፈጥራል።
15. ኢሻቶሎጂካል(የነገረ ፍጻሜ) ትኩረት
የክርስቶስን መምጣት እና የአማኞች የመጨረሻ ተስፋ ላይ በማተኮር ጽፏል።
ምሳሌ፡- 1ኛ ተሰሎንቄ 4፥13-18 ስለ ትንሣኤና ስለ ክርስቶስ ዳግም ምጽአት ይናገራል።
የጳውሎስ ሁለገብ የአጻጻፍ ስልት የተለያዩ አንባቢዎችን በብቃት እንዲደርስ አስችሎታል። ይህም ምሁራዊ ጥልቀትን ከእረኝነት ሙቀት ጋር በማጣመር። ይህ ጥልቀት ጽሑፎቹን ዘላቂ ተጽዕኖ አላብሷቸዋል።
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍6❤4🔥1
በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ ሐዋርያው ጳውሎስ እስር ቤት በነበረበት ወቅት መልእክት ለእነማን ወይም ለማን ላከ?
Anonymous Quiz
9%
ሀ. ገላትያ፣ ሮሜ እና ቆሮንቶስ
15%
ለ. ጢሞቴዎስ፣ ቲቶ እና ፊልሞና
6%
ሐ. ተሰሎንቄ፣ ጢሞቴዎስ እና ቲቶ
53%
መ. ኤፌሶን፣ ፊልጵስዩስ፣ ቆላስይስ እና ፊልሞና
16%
ሠ. ሁሉም
❤7🔥2
. ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“እናንተ ደግሞ ታገሡ፥ ልባችሁንም አጽኑ፤ የጌታ መምጣት ቀርቦአልና።”
ያዕቆብ 5፥8
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“እናንተ ደግሞ ታገሡ፥ ልባችሁንም አጽኑ፤ የጌታ መምጣት ቀርቦአልና።”
ያዕቆብ 5፥8
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤7🔥4👍1
#እራሳችንን_እንመርምር
የነፍስ ድካም እና ዝለት መድኃኒቱ ምን ይሆን? ነፍስን የሚያዝሉ ነገሮችስ የትኞቹ ናቸው?
“በነፍሳችሁ ዝላችሁ እንዳትደክሙ፥ ከኃጢአተኞች በደረሰበት እንዲህ ባለ መቃወም የጸናውን አስቡ።”
ዕብራውያን 12፥3
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የነፍስ ድካም እና ዝለት መድኃኒቱ ምን ይሆን? ነፍስን የሚያዝሉ ነገሮችስ የትኞቹ ናቸው?
“በነፍሳችሁ ዝላችሁ እንዳትደክሙ፥ ከኃጢአተኞች በደረሰበት እንዲህ ባለ መቃወም የጸናውን አስቡ።”
ዕብራውያን 12፥3
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤6👍4
. ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“ዓለም እናንተን ሊጠላ አይቻለውም፤ እኔ ግን ሥራው ክፉ መሆኑን እመሰክርበታለሁና እኔን ይጠላኛል።”
ዮሐንስ 7፥7
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“ዓለም እናንተን ሊጠላ አይቻለውም፤ እኔ ግን ሥራው ክፉ መሆኑን እመሰክርበታለሁና እኔን ይጠላኛል።”
ዮሐንስ 7፥7
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
🔥4❤2
የሃኪሙ ሉቃስ ጹሑፎች የአጻጻፍ ስልት እና ይዘት
በአዲስ ኪዳን የሉቃስ ወንጌል እና የሐዋርያት ሥራ ጸሐፊ ሃኪሙ ሉቃስ፣ በልዩ የአጻጻፍ ስልትና ዘዴዎች ይታወቃል። ሥራዎቹ በሥነ-ጽሑፋዊ ውስብስብነታቸው (አስደናቂ የግሪክ ቋንቋ እውቀቱ)፣ በታሪካዊ ዝርዝርነታቸው፣ በሥነ-መለኮት ጥልቀት እና በሁለንተናዊ እይታ ተለይተው ይታወቃሉ። ከዚህ በታች የእሱን ዘይቤ እና ስልቶች አጠቃላይ እይታ ከቅዱሳት መጻሕፍት እንመለከታለን፦
1. ታሪካዊ እና የምርምር አቀራረብ ዘዴ
የሉቃስ አጻጻፍ ጥንቃቄ የተሞላበት ታሪካዊ ምርምርን ያንጸባርቃል። ብዙ ጊዜ ምንጮችን እና ምስክሮችን ይጠቅሳል፣ ይህም ለትክክለኛነቱ እና ለምርምር እና ጥናት ያለውን ቁርጠኝነት ያሳያል።
ምሳሌ፡- ሉቃስ በወንጌሉ መግቢያ ላይ ጥልቅ ምርምር እና ጥናት እንዳደረገ በግልጽ ተናግሯል።
“የከበርህ ቴዎፍሎስ ሆይ፥ ከመጀመሪያው በዓይን ያዩትና የቃሉ አገልጋዮች የሆኑት እንዳስተላለፉልን፥ በኛ ዘንድ ስለ ተፈጸመው ነገር ብዙዎች ታሪክን በየተራው ለማዘጋጀት ስለ ሞከሩ፥ እኔ ደግሞ ስለ ተማርኸው ቃል እርግጡን እንድታውቅ በጥንቃቄ ሁሉን ከመጀመሪያው ተከትዬ በየተራው ልጽፍልህ መልካም ሆኖ ታየኝ።”
ሉቃስ 1፥1-4
2. የግሪክ ሥነ-ጽሑፍ ዘይቤ አጠቃቀም ዘዴ
ሐኪሙ ሉቃስ በአዳዲስ ቃላት እና መዋቅር የበለፀገ፣ ትምህርቱን እና አንባቢውን የማሳተፍ ችሎታውን የሚያንፀባርቅ ድንቅ የግሪክ ዘይቤን ይጠቀማል።
ምሳሌ፦ ወቅታዊ አረፍተ ነገሮችን መጠቀሙ፣ እንደ መቅድም (ሉቃስ 1፡1-4)፣ የተራቀቀ ድንቅ የግሪክ የአጻጻፍ ስልት ያሳያል።
ይቀጥላል...
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
በአዲስ ኪዳን የሉቃስ ወንጌል እና የሐዋርያት ሥራ ጸሐፊ ሃኪሙ ሉቃስ፣ በልዩ የአጻጻፍ ስልትና ዘዴዎች ይታወቃል። ሥራዎቹ በሥነ-ጽሑፋዊ ውስብስብነታቸው (አስደናቂ የግሪክ ቋንቋ እውቀቱ)፣ በታሪካዊ ዝርዝርነታቸው፣ በሥነ-መለኮት ጥልቀት እና በሁለንተናዊ እይታ ተለይተው ይታወቃሉ። ከዚህ በታች የእሱን ዘይቤ እና ስልቶች አጠቃላይ እይታ ከቅዱሳት መጻሕፍት እንመለከታለን፦
1. ታሪካዊ እና የምርምር አቀራረብ ዘዴ
የሉቃስ አጻጻፍ ጥንቃቄ የተሞላበት ታሪካዊ ምርምርን ያንጸባርቃል። ብዙ ጊዜ ምንጮችን እና ምስክሮችን ይጠቅሳል፣ ይህም ለትክክለኛነቱ እና ለምርምር እና ጥናት ያለውን ቁርጠኝነት ያሳያል።
ምሳሌ፡- ሉቃስ በወንጌሉ መግቢያ ላይ ጥልቅ ምርምር እና ጥናት እንዳደረገ በግልጽ ተናግሯል።
“የከበርህ ቴዎፍሎስ ሆይ፥ ከመጀመሪያው በዓይን ያዩትና የቃሉ አገልጋዮች የሆኑት እንዳስተላለፉልን፥ በኛ ዘንድ ስለ ተፈጸመው ነገር ብዙዎች ታሪክን በየተራው ለማዘጋጀት ስለ ሞከሩ፥ እኔ ደግሞ ስለ ተማርኸው ቃል እርግጡን እንድታውቅ በጥንቃቄ ሁሉን ከመጀመሪያው ተከትዬ በየተራው ልጽፍልህ መልካም ሆኖ ታየኝ።”
ሉቃስ 1፥1-4
2. የግሪክ ሥነ-ጽሑፍ ዘይቤ አጠቃቀም ዘዴ
ሐኪሙ ሉቃስ በአዳዲስ ቃላት እና መዋቅር የበለፀገ፣ ትምህርቱን እና አንባቢውን የማሳተፍ ችሎታውን የሚያንፀባርቅ ድንቅ የግሪክ ዘይቤን ይጠቀማል።
ምሳሌ፦ ወቅታዊ አረፍተ ነገሮችን መጠቀሙ፣ እንደ መቅድም (ሉቃስ 1፡1-4)፣ የተራቀቀ ድንቅ የግሪክ የአጻጻፍ ስልት ያሳያል።
ይቀጥላል...
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤9👍4
. ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“ሁልጊዜ ስለ ሁሉ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም አምላካችንንና አባታችንን ስለ ሁሉ አመስግኑ።”
ኤፌሶን 5፥20
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“ሁልጊዜ ስለ ሁሉ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም አምላካችንንና አባታችንን ስለ ሁሉ አመስግኑ።”
ኤፌሶን 5፥20
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤5👍1
ቅዱሳት መጻሕፍት
ነቢዩ ኤርምያስ ክፍል-፯ በኤርምያስ ዘመን ግብረ ገባዊ ዝቅጠት በሰፊው የተሠራጨ ሲሆን፣ ኢፍትሓዊነትም በዚያው ልክ ተስፋፍቶ ነበር (5፥1-9፤ 7 ፥ 1-11 ፤ 23 ፥ 10-14)፡፡ ካህናትና ነቢያት እንደ ሌሎቹ አይሁድ ጥፋተኞች ነበሩ (6፥ 13-15)፡፡ ሆኖም ሕዝቡ ሃይማኖታዊ ሥርዐትን ፈጸሙ፡፡ እግዚአብሔር ግን በዚህ ውጫዊ ሥርዐት ከቊጣው የሚመለስ አልነበረም::…
ነቢዩ ኤርምያስ
ክፍል-፰
መሲሓዊ ትንቢትን በተመለከተም ኤርምያስ መሲሓዊውን ጊዜ በዝርዝር አይገልጽም፡፡ የመሲሑ ማንነት በመጽሐፉ ላይ በጒልሕ አልተመለከተም፡፡ ይሁን እንጂ ኤርምያስ አንዳንድ ፋይዳ ያላቸውን መሲሓውያን ምንባቦች ይሰጣል ፡-
1. ከኪዳኑ ታቦት የላቀ የእግዚአብሔር መገለጥ እውን እንድሚሆን መታወጁ (3፥14-17)
2. የዐዲሱ ኪዳን መገለጥ (31፥31-34)
3. የዳዊት ኪዳን ፍጻሜ ላይ ከመድረሱ ጋር ተያይዞ (33 ፥ 14- 26) የሙሴ ውብ ሐሳብ እውን መሆን (ዘፀ 19፥6)፡፡
የትንቢተ ኤርምያስ ዘላቂ ፋይዳ የሚገኘው በዐዲስ ኪዳን ውስጥ ያሉትን ይዘቶች (በአርባና በኀምሳ ቤት ውስጥ ይገኛሉ፤ በዮሐንስ ራእይ ላይ ከግማሽ በላይ ይገኛሉ) ኢርቱዕ በሆነ መልክ በመግለጽ ብቻ ሳይሆን፣ ከእግዚአብሔር ጋር ስላለው ግንኙነት ለማወቅ ድንቅ የሆነ መማሪያ መጽሐፍ በመሆኑ ነው፡፡ በብሉይ ኪዳን ውስጥ ከዚህ ላይ የግል እምነት ከፍተኛ ደረጃ ላይ ደርሶ ይገኛል፤ እንዲሁም በዳዊት ሥርወ መንግሥት ውስጥ (23፥1-8፤ 33፥ 14-18) የካህንነትንና የንጉሥነትን ምንነት ለመረዳት እውነተኛ መንገድ በመሆኑ ነው፡፡ በምዕራፍ 30-33 ላይ ለሕዝቡ ብሩህ ተስፋዎች በብዛት መገኘታቸው የመጽሐፍ ቅዱስ ሊቃውንት ይህን ክፍል “የመጽናናት መጽሐፍ” እስከ ማለት አበቃቸው፡፡ በኤርምያስ ትንቢት ውስጥ በእጅጉ ዝነኛ የሆነው ምንባብ ስለ ዐዲሱ ኪዳን ይናገራል (31፥31-34):: ይህም የሚናገረው እስራኤል በቦታዋ ስለ መመለሷ እንጂ ስለ ግለ ሰባዊ ትንሣኤ አይደለም፡፡
ኤርምያስ እንደ ሌሎቹ የብሉይ ኪዳን ነቢያት ባለመሆኑ፣ ጽሑፉም ከሕይወቱና ከሐሳቡ ጋር የተሳሰረ በመሆኑ፣ የእርሱ ትንቢት ተማሪ የሆነ ሰው የዚህን የእግዚአብሐር ሰው ውስጣዊ ሕይወትና ባሕርያት በጥልቅ ማጤን ይኖርበታል፤ ከእነዚህም አንዳንዶቹ ቀደም ሲል በመጠኑ ተዳስሰዋል፡፡ ከተፈጥሮኣዊ ችሎታዎቹ፣ ከጥልቅ ስሜቶቹ (ውስጣዊ ስሜቶቹ)፣ ከተነሣሽነቱ፣ ከጌታ ጋር ስላለው የግል ግንኙነት ገጽታዎች በተጨማሪ፣ የኤርምያስ ንስሓዎች ተብለው የሚጠሩ፣ ከጌታ ጋር ያደረጋቸው ውይይቶች በጠላቶች ላይ ያወረዳቸው ርግማኖችና በተለይ የጸሎት ሕይወቱ ይገኛሉ፡፡ ልቡንና መንፈሳዊ መሻቶቹን እንደ እርሱ የገለጠ የብሉይ ኪዳን ነቢይ የለም፡፡ ጨዋና ፈሪ ቢሆንም እንኳ (አንዳንዶች በእርሱ ላይ እንደ ለጠፉት ግን ከቶ ሴታሴት አልነበረም፣ ከእግዚአብሔር ጥሪና እግዚአብሔር ከሰጠው ዐደራ የተነሣ ለተግባሩ በጽኑ የቆመ ሰው ነበር፡፡ ከዐላማው ሊነቃነቅ አልቻለም፡፡ በይሁዳ ውስጥ እንደ እርሱ ያለ አገሩን የሚወድ ሰው አልነበረም፤ ይሁን እንጂ የይሁዳን ኀጢአት አይቶ እንዳላየ ለማለፍ አወላውሎ ከቶ አያውቅም᎓᎓ ሕይወቱ የብቸኛና የገለልተኛ ሕይወት ነበር፤ የሰውን ኅብረትና ፍቅር ቢናፍቅም እንኳ በሕይወቱ ዘመን ሁሉ ቤተ ሰውና የቅርብ ወዳጆች አልነበሩትም:: ለወገኞቹ ጥልቅ ፍቅር ቢኖረውም እንኳ ሥቃያቸውንና ብሔራዊ ጥፋታቸውን ይፋ ያደርግ ዘንድ በመለኮት ዐደራ ተሰጥቶት ነበር፡፡ ከእግዚአብሔር ጋር የነበረው ኅብረት የተለየ ጥልቀትና ቅርርብ ነበረው፡፡ አንዳንድ ጊዜ ይህን ያህል ግልጽ በመሆኑ፣ በዘመናችን የሚገኙት አያሌ የእርሱ መጽሐፍ ተማሪዎች ይህማ እግዚአብሔርን እንደ መሳደብ ወይም ተገቢውን ክብር እንደ መንፈግ የሚቈጠር ነው ከማለት አድርሷቸዋል፡፡
ይቀጥላል...
ምንጭ፦ የብሉይ ኪዳን ማብራሪያ፤ ገጽ 827-828
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ክፍል-፰
መሲሓዊ ትንቢትን በተመለከተም ኤርምያስ መሲሓዊውን ጊዜ በዝርዝር አይገልጽም፡፡ የመሲሑ ማንነት በመጽሐፉ ላይ በጒልሕ አልተመለከተም፡፡ ይሁን እንጂ ኤርምያስ አንዳንድ ፋይዳ ያላቸውን መሲሓውያን ምንባቦች ይሰጣል ፡-
1. ከኪዳኑ ታቦት የላቀ የእግዚአብሔር መገለጥ እውን እንድሚሆን መታወጁ (3፥14-17)
2. የዐዲሱ ኪዳን መገለጥ (31፥31-34)
3. የዳዊት ኪዳን ፍጻሜ ላይ ከመድረሱ ጋር ተያይዞ (33 ፥ 14- 26) የሙሴ ውብ ሐሳብ እውን መሆን (ዘፀ 19፥6)፡፡
የትንቢተ ኤርምያስ ዘላቂ ፋይዳ የሚገኘው በዐዲስ ኪዳን ውስጥ ያሉትን ይዘቶች (በአርባና በኀምሳ ቤት ውስጥ ይገኛሉ፤ በዮሐንስ ራእይ ላይ ከግማሽ በላይ ይገኛሉ) ኢርቱዕ በሆነ መልክ በመግለጽ ብቻ ሳይሆን፣ ከእግዚአብሔር ጋር ስላለው ግንኙነት ለማወቅ ድንቅ የሆነ መማሪያ መጽሐፍ በመሆኑ ነው፡፡ በብሉይ ኪዳን ውስጥ ከዚህ ላይ የግል እምነት ከፍተኛ ደረጃ ላይ ደርሶ ይገኛል፤ እንዲሁም በዳዊት ሥርወ መንግሥት ውስጥ (23፥1-8፤ 33፥ 14-18) የካህንነትንና የንጉሥነትን ምንነት ለመረዳት እውነተኛ መንገድ በመሆኑ ነው፡፡ በምዕራፍ 30-33 ላይ ለሕዝቡ ብሩህ ተስፋዎች በብዛት መገኘታቸው የመጽሐፍ ቅዱስ ሊቃውንት ይህን ክፍል “የመጽናናት መጽሐፍ” እስከ ማለት አበቃቸው፡፡ በኤርምያስ ትንቢት ውስጥ በእጅጉ ዝነኛ የሆነው ምንባብ ስለ ዐዲሱ ኪዳን ይናገራል (31፥31-34):: ይህም የሚናገረው እስራኤል በቦታዋ ስለ መመለሷ እንጂ ስለ ግለ ሰባዊ ትንሣኤ አይደለም፡፡
ኤርምያስ እንደ ሌሎቹ የብሉይ ኪዳን ነቢያት ባለመሆኑ፣ ጽሑፉም ከሕይወቱና ከሐሳቡ ጋር የተሳሰረ በመሆኑ፣ የእርሱ ትንቢት ተማሪ የሆነ ሰው የዚህን የእግዚአብሐር ሰው ውስጣዊ ሕይወትና ባሕርያት በጥልቅ ማጤን ይኖርበታል፤ ከእነዚህም አንዳንዶቹ ቀደም ሲል በመጠኑ ተዳስሰዋል፡፡ ከተፈጥሮኣዊ ችሎታዎቹ፣ ከጥልቅ ስሜቶቹ (ውስጣዊ ስሜቶቹ)፣ ከተነሣሽነቱ፣ ከጌታ ጋር ስላለው የግል ግንኙነት ገጽታዎች በተጨማሪ፣ የኤርምያስ ንስሓዎች ተብለው የሚጠሩ፣ ከጌታ ጋር ያደረጋቸው ውይይቶች በጠላቶች ላይ ያወረዳቸው ርግማኖችና በተለይ የጸሎት ሕይወቱ ይገኛሉ፡፡ ልቡንና መንፈሳዊ መሻቶቹን እንደ እርሱ የገለጠ የብሉይ ኪዳን ነቢይ የለም፡፡ ጨዋና ፈሪ ቢሆንም እንኳ (አንዳንዶች በእርሱ ላይ እንደ ለጠፉት ግን ከቶ ሴታሴት አልነበረም፣ ከእግዚአብሔር ጥሪና እግዚአብሔር ከሰጠው ዐደራ የተነሣ ለተግባሩ በጽኑ የቆመ ሰው ነበር፡፡ ከዐላማው ሊነቃነቅ አልቻለም፡፡ በይሁዳ ውስጥ እንደ እርሱ ያለ አገሩን የሚወድ ሰው አልነበረም፤ ይሁን እንጂ የይሁዳን ኀጢአት አይቶ እንዳላየ ለማለፍ አወላውሎ ከቶ አያውቅም᎓᎓ ሕይወቱ የብቸኛና የገለልተኛ ሕይወት ነበር፤ የሰውን ኅብረትና ፍቅር ቢናፍቅም እንኳ በሕይወቱ ዘመን ሁሉ ቤተ ሰውና የቅርብ ወዳጆች አልነበሩትም:: ለወገኞቹ ጥልቅ ፍቅር ቢኖረውም እንኳ ሥቃያቸውንና ብሔራዊ ጥፋታቸውን ይፋ ያደርግ ዘንድ በመለኮት ዐደራ ተሰጥቶት ነበር፡፡ ከእግዚአብሔር ጋር የነበረው ኅብረት የተለየ ጥልቀትና ቅርርብ ነበረው፡፡ አንዳንድ ጊዜ ይህን ያህል ግልጽ በመሆኑ፣ በዘመናችን የሚገኙት አያሌ የእርሱ መጽሐፍ ተማሪዎች ይህማ እግዚአብሔርን እንደ መሳደብ ወይም ተገቢውን ክብር እንደ መንፈግ የሚቈጠር ነው ከማለት አድርሷቸዋል፡፡
ይቀጥላል...
ምንጭ፦ የብሉይ ኪዳን ማብራሪያ፤ ገጽ 827-828
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍5❤1
የሮሜ_መልእክት_የጥናት_መምሪያ_እና_ማብራሪያ.pdf
19 MB
👉ርዕስ፦ የሮሜ መልእክት የጥናት መምሪያ እና ማብራሪያ፣
በትምህርተ መለኮት ማስፋፊያ (ት.መ.ማ) መልክ የተዘጋጀ
✍ጸሐፊ፦ ስቲቭ ስትራውስ
🗣ትርጉም፦ ጌቱ ግዛው
✏️እርማት፦ ኃይሌ ጀናይና ግርማይ
🖨አሳታሚ፦ ኤስ. አይ. ኤም
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
በትምህርተ መለኮት ማስፋፊያ (ት.መ.ማ) መልክ የተዘጋጀ
✍ጸሐፊ፦ ስቲቭ ስትራውስ
🗣ትርጉም፦ ጌቱ ግዛው
✏️እርማት፦ ኃይሌ ጀናይና ግርማይ
🖨አሳታሚ፦ ኤስ. አይ. ኤም
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍4
. ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“ጌታ ኃጢአቱን የማይቆጥርበት ሰው ብፁዕ ነው።”
ሮሜ 4፥8
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“ጌታ ኃጢአቱን የማይቆጥርበት ሰው ብፁዕ ነው።”
ሮሜ 4፥8
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍4
የሃኪሙ ሉቃስ ጹሑፎች የአጻጻፍ ስልት እና ይዘት
3. ዓለም አቀፋዊ ትኩረት
ሉቃስ የኢየሱስን ተልእኮ ዓለም አቀፋዊ እንደሆነ አጽንዖት ሰጥቷል፣ ይህም ለሁሉም ሰዎች ማለትም አሕዛብን፣ ሴቶችን፣ ድሆችን እና የተገለሉ ቡድኖችን ጨምሮ መቀላቀልን ያሳያል።
ምሳሌ፦ በሉቃስ ውስጥ ያለው የዘር ሐረግ የኢየሱስን የዘር ሐረግ ከአዳም ጀምሮ ያሳያል (ሉቃስ 3፥23-38)። ይህም ጌታችን እና መድኋኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የመጣው አይሁዳዊያንን ብቻ ሳይሆን የሰውን ዘር በሙሉ ለማዳን እንደመጣ ለማስገንዘብ ነው።
4. ለተገለሉ ቡድኖች ትኩረት መስጠት
ሉቃስ ስለሴቶች፣ ሳምራውያን፣ ቀራጮች እና ኃጢአተኞች ታሪኮችን በልዩ ሁኔታ አጉልቶ ያሳያል።
ምሳሌዎች፡- የደጉ ሳምራዊ ምሳሌ (ሉቃስ 10፥25–37)። ኃጢአተኛዋ ሴት ኢየሱስን ሽቶ ስለቀባችው ታሪክ (ሉቃስ 7፥36–50)።
5. በጸሎት እና በመንፈስ ቅዱስ ላይ ማተኮር
ሉቃስ ጸሎትን እና የመንፈስ ቅዱስን ሥራ በኢየሱስ ክርስቶስ ሕይወት እና በቀደመችው ቤተክርስቲያን ውስጥ በተደጋጋሚ ሁኔታ ትኩረት ሰጥቶ ያነሳዋል።
ምሳሌ፡- የኢየሱስ ጸሎት (ሉቃስ 3፥21፣ 5፥16፣ 6፥12፣ 22፥39–46)። በጰንጠቆስጤ የመንፈስ ቅዱስ መውረድ (ሐዋ. 2፡1-4)።
ይቀጥላል...
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
3. ዓለም አቀፋዊ ትኩረት
ሉቃስ የኢየሱስን ተልእኮ ዓለም አቀፋዊ እንደሆነ አጽንዖት ሰጥቷል፣ ይህም ለሁሉም ሰዎች ማለትም አሕዛብን፣ ሴቶችን፣ ድሆችን እና የተገለሉ ቡድኖችን ጨምሮ መቀላቀልን ያሳያል።
ምሳሌ፦ በሉቃስ ውስጥ ያለው የዘር ሐረግ የኢየሱስን የዘር ሐረግ ከአዳም ጀምሮ ያሳያል (ሉቃስ 3፥23-38)። ይህም ጌታችን እና መድኋኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የመጣው አይሁዳዊያንን ብቻ ሳይሆን የሰውን ዘር በሙሉ ለማዳን እንደመጣ ለማስገንዘብ ነው።
4. ለተገለሉ ቡድኖች ትኩረት መስጠት
ሉቃስ ስለሴቶች፣ ሳምራውያን፣ ቀራጮች እና ኃጢአተኞች ታሪኮችን በልዩ ሁኔታ አጉልቶ ያሳያል።
ምሳሌዎች፡- የደጉ ሳምራዊ ምሳሌ (ሉቃስ 10፥25–37)። ኃጢአተኛዋ ሴት ኢየሱስን ሽቶ ስለቀባችው ታሪክ (ሉቃስ 7፥36–50)።
5. በጸሎት እና በመንፈስ ቅዱስ ላይ ማተኮር
ሉቃስ ጸሎትን እና የመንፈስ ቅዱስን ሥራ በኢየሱስ ክርስቶስ ሕይወት እና በቀደመችው ቤተክርስቲያን ውስጥ በተደጋጋሚ ሁኔታ ትኩረት ሰጥቶ ያነሳዋል።
ምሳሌ፡- የኢየሱስ ጸሎት (ሉቃስ 3፥21፣ 5፥16፣ 6፥12፣ 22፥39–46)። በጰንጠቆስጤ የመንፈስ ቅዱስ መውረድ (ሐዋ. 2፡1-4)።
ይቀጥላል...
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍3❤1
#የእግዚአብሔር_ቃል_ምን_ይላል?
ኤርምያስ 23
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
³³ ይህ ሕዝብ ወይም ነቢይ ወይም ካህን፦ የእግዚአብሔር ሸክም ምንድር ነው? ብሎ ቢጠይቅህ፥ አንተ፦ ሸክሙ እናንተ ናችሁ፥ እጥላችሁማለህ፥ ይላል እግዚአብሔር ትላቸዋለህ።
³⁴ የእግዚአብሔር ሸክም የሚለውን ነቢይንና ካህንን ሕዝብንም ያን ሰውና ቤቱን እቀጣለሁ።
³⁵ አንዱም አንዱ ለባልንጀራው፥ አንዱም አንዱ ለወንድሙ እንዲህ ይበል፦ እግዚአብሔር የመለሰው ምንድር ነው? እግዚአብሔርስ ምን ነገር ተናገረ?
³⁶ ለሰው ሁሉ ቃሉ ሸክም ይሆንበታልና የእግዚአብሔር ሸክም ብላችሁ ከእንግዲህ ወዲህ አትጥሩ፤ የሠራዊትን ጌታ የአምላካችንን የእግዚአብሔርን የሕያውን አምላክ ቃል ለውጣችኋልና።
³⁷ ለነቢዩ፦ እግዚአብሔር ምን መለሰልህ? እግዚአብሔርስ የተናገረው ምንድር ነው? ትላለህ።
³⁸ ነገር ግን፦ የእግዚአብሔር ሸክም ብትሉ፥ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ እኔ፦ የእግዚአብሔር ሸክም አትበሉ ብዬ ልኬባችኋለሁና፥ እናንተም ይህን ቃል፦
³⁹ የእግዚአብሔር ሸክም ብላችኋልና ስለዚህ፥ እነሆ፥ ፈጽሜ እረሳችኋለሁ እናንተንም ለእናንተና ለአባቶቻችሁም የሰጠኋትን ከተማ ከፊቴ እጥላለሁ።
⁴⁰ የዘላለምንም ስድብ ከቶም ተረስቶ የማይጠፋውን የዘላለምን እፍረት አመጣባችኋለሁ።
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ኤርምያስ 23
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
³³ ይህ ሕዝብ ወይም ነቢይ ወይም ካህን፦ የእግዚአብሔር ሸክም ምንድር ነው? ብሎ ቢጠይቅህ፥ አንተ፦ ሸክሙ እናንተ ናችሁ፥ እጥላችሁማለህ፥ ይላል እግዚአብሔር ትላቸዋለህ።
³⁴ የእግዚአብሔር ሸክም የሚለውን ነቢይንና ካህንን ሕዝብንም ያን ሰውና ቤቱን እቀጣለሁ።
³⁵ አንዱም አንዱ ለባልንጀራው፥ አንዱም አንዱ ለወንድሙ እንዲህ ይበል፦ እግዚአብሔር የመለሰው ምንድር ነው? እግዚአብሔርስ ምን ነገር ተናገረ?
³⁶ ለሰው ሁሉ ቃሉ ሸክም ይሆንበታልና የእግዚአብሔር ሸክም ብላችሁ ከእንግዲህ ወዲህ አትጥሩ፤ የሠራዊትን ጌታ የአምላካችንን የእግዚአብሔርን የሕያውን አምላክ ቃል ለውጣችኋልና።
³⁷ ለነቢዩ፦ እግዚአብሔር ምን መለሰልህ? እግዚአብሔርስ የተናገረው ምንድር ነው? ትላለህ።
³⁸ ነገር ግን፦ የእግዚአብሔር ሸክም ብትሉ፥ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ እኔ፦ የእግዚአብሔር ሸክም አትበሉ ብዬ ልኬባችኋለሁና፥ እናንተም ይህን ቃል፦
³⁹ የእግዚአብሔር ሸክም ብላችኋልና ስለዚህ፥ እነሆ፥ ፈጽሜ እረሳችኋለሁ እናንተንም ለእናንተና ለአባቶቻችሁም የሰጠኋትን ከተማ ከፊቴ እጥላለሁ።
⁴⁰ የዘላለምንም ስድብ ከቶም ተረስቶ የማይጠፋውን የዘላለምን እፍረት አመጣባችኋለሁ።
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍5❤1👎1
. ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“በእውነት ኤፍሬም ለእኔ የከበረ ልጅ ነውን? ወይስ የተወደደ ሕፃን ነውን? በእርሱ ላይ በተናገርሁ ቍጥር አስበዋለሁ፤ ስለዚህ አንጀቴ ታወከችለት ርኅራኄም እራራለታለሁ፥ ይላል እግዚአብሔር።”
ኤርምያስ 31፥20
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“በእውነት ኤፍሬም ለእኔ የከበረ ልጅ ነውን? ወይስ የተወደደ ሕፃን ነውን? በእርሱ ላይ በተናገርሁ ቍጥር አስበዋለሁ፤ ስለዚህ አንጀቴ ታወከችለት ርኅራኄም እራራለታለሁ፥ ይላል እግዚአብሔር።”
ኤርምያስ 31፥20
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍6
#ከተማ_ወይም_ቦታ_በቅዱሳት_መጻሕፍት
#ጊብዓ
ጊብዓ፤ ጉብታ ወይም ኮረብታ ማለት ነው።
1. በይሁዳ የነበረ ከተማ። ኢያሱ 15፥57።
2. ከኢየሩሳሌም ወደ ሰሜን አምስት ኪ.ሜ. ያህል ርቆ የሚገኝ የብንያም አገር ከተማ። የብንያም ጊብዓ በአሁን ጊዜ ከኢየሩሳሌም በስተሰሜን የምትገኝ ዘመናዊቷ ቴል ኤል ፉል ላይ እንደነበረች ይገመታል። የአርኪኦሎጂ ቁፋሮዎች የጥንት ምሽግ ቅሪቶችን በቁፋሮ አግኝተዋል፣ ይህም ግምቶችን እውነተኛ ሊሆኑ እንድሚችሉ አረጋግጧል።
የጊብዓ ሰዎች አስጸያፊ ብልግና ስላደረጉ እስራኤላውያን የብንያምን ወገን ለማጥፋት ተነሡ፤ ሆኖም 600 ሰዎች አምልጠዋል፤ መሳ. 19፥11-20፡48። ግን ንጉሥ ሳኦል የጊብዓ ሰው ነበረና መናገሻ ከተማውን በጊብዓ አደረገ፤ 1ሳሙ. 10፥26፤ 22፥6። በብሉይ ኪዳን ዘመን ጊብዓ ምሽግ ከተማ ነበረ፤ ከክርስቶስ ልደት ወዲህ ግን ባድማ ሆኗል።
ጊብዓ የምትታወቅባቸው ዋና ዋና የታሪክ ሁነቶች፦
👉የሌዋዊው ቁባት በጊብዓ ሰዎች በተፈጸመባት አሳቃቂ ግፍ የደረሰው ቁጣና ያስከተለው መዘዝ (መሳ. ምዕራፍ 19-21)
👉ጊብዓ የእስራኤል የመጀመሪያው ንጉሥ የንጉሥ ሳኦል የትውልድ ከተማ ነበረች። (1ኛ ሳሙኤል 10፥26፤ 1ሳሙ 15፥34-35)
👉የጊብዓ ትንቢታዊ ውግዘቶች፡- ነብያት ከጊዜ በኋላ ጊብዓን በመሳፍንት ውስጥ በተመዘገቡት ድርጊቶች ምክንያት የእስራኤል የሥነ ምግባር ውድቀት ምልክት እንደሆነች ጠቅሰዋል። (ሆሴዕ 9፥9፤ ሆሴዕ 10፥9።
ምንጭ፦ የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት፤ ገጽ 242
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
#ጊብዓ
ጊብዓ፤ ጉብታ ወይም ኮረብታ ማለት ነው።
1. በይሁዳ የነበረ ከተማ። ኢያሱ 15፥57።
2. ከኢየሩሳሌም ወደ ሰሜን አምስት ኪ.ሜ. ያህል ርቆ የሚገኝ የብንያም አገር ከተማ። የብንያም ጊብዓ በአሁን ጊዜ ከኢየሩሳሌም በስተሰሜን የምትገኝ ዘመናዊቷ ቴል ኤል ፉል ላይ እንደነበረች ይገመታል። የአርኪኦሎጂ ቁፋሮዎች የጥንት ምሽግ ቅሪቶችን በቁፋሮ አግኝተዋል፣ ይህም ግምቶችን እውነተኛ ሊሆኑ እንድሚችሉ አረጋግጧል።
የጊብዓ ሰዎች አስጸያፊ ብልግና ስላደረጉ እስራኤላውያን የብንያምን ወገን ለማጥፋት ተነሡ፤ ሆኖም 600 ሰዎች አምልጠዋል፤ መሳ. 19፥11-20፡48። ግን ንጉሥ ሳኦል የጊብዓ ሰው ነበረና መናገሻ ከተማውን በጊብዓ አደረገ፤ 1ሳሙ. 10፥26፤ 22፥6። በብሉይ ኪዳን ዘመን ጊብዓ ምሽግ ከተማ ነበረ፤ ከክርስቶስ ልደት ወዲህ ግን ባድማ ሆኗል።
ጊብዓ የምትታወቅባቸው ዋና ዋና የታሪክ ሁነቶች፦
👉የሌዋዊው ቁባት በጊብዓ ሰዎች በተፈጸመባት አሳቃቂ ግፍ የደረሰው ቁጣና ያስከተለው መዘዝ (መሳ. ምዕራፍ 19-21)
👉ጊብዓ የእስራኤል የመጀመሪያው ንጉሥ የንጉሥ ሳኦል የትውልድ ከተማ ነበረች። (1ኛ ሳሙኤል 10፥26፤ 1ሳሙ 15፥34-35)
👉የጊብዓ ትንቢታዊ ውግዘቶች፡- ነብያት ከጊዜ በኋላ ጊብዓን በመሳፍንት ውስጥ በተመዘገቡት ድርጊቶች ምክንያት የእስራኤል የሥነ ምግባር ውድቀት ምልክት እንደሆነች ጠቅሰዋል። (ሆሴዕ 9፥9፤ ሆሴዕ 10፥9።
ምንጭ፦ የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት፤ ገጽ 242
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍3❤1😁1
. ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“በቸርነትህ የተቤዠሃቸውን ሕዝብህን መራህ፤ በኃይልህ ወደ ቅዱስ ማደሪያህ አገባሃቸው።”
ዘጸአት 15፥13
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“በቸርነትህ የተቤዠሃቸውን ሕዝብህን መራህ፤ በኃይልህ ወደ ቅዱስ ማደሪያህ አገባሃቸው።”
ዘጸአት 15፥13
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤4👍1
እየጨመረ የሚሄድ ሕይወት
የጠለቀ መንፈሳዊ ጉዞ ለመጓዝና እየጨመረ የሚሄድ ርካታና እረፍት እንድናይ ካስፈለገ፣የክርስትና ሕይወት ትጋትን ይጠይቀናል(ዕብ 4:11)፡፡ በተለያየ ቦታ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ቃሉ እንደሚያስተምረን ትጋታችን እየጨመረ ሲሄድ፣ የእግዚአብሔር ጸጋም በሕይወታችን እየጨመረ ይሄዳል፡፡ እናም ለመንፈሳዊ ነገር ያለን መሻት እያደገ ይሄዳል፡፡ በእንደዚህ ዓይነት ግሥገሣ ውስጥ ባለማሰለስ ስንገኝ፣ እሱን ለማወቅ ያለን ራብ እየተቀጣጠለ ስለሚመጣ፣እየጨመረ ለሚሄድ ፍለጋ እንጠናከራለን፡፡ ይህንን በእንግሊዝኛው አገላለጽ positive vicious cycle ይሉታል፡፡ ማለትም ትጋቱ የጨመረ መንፈሳዊ ራብን ይወልዳል፤ የጨመረው መንፈሳዊ ራብ ደግሞ ሌላ ከፍ ያለ ትጋትንና ግሥገሣን ይወልዳል፡፡ መቼም ይሄ ኡደት ማቆሚያ የለውም እኛ በሥጋዊ አካሄዶች እስካላጠፋነው ድረስ!
በነገራችን ላይ እየጨመረ የሚሄድ የክርስትና ሕይወት ብዙ ግብዓቶችን ይፈልጋል ፡፡ መልካም የእምነት ውጊያንና ዲያቢሎስን በኃይል ጸንቶ መቃወም ይጠይቃል ፡፡ የእግዚአብሔርን ቃል ሳይታክቱ ማሰላሰልና በፊቱ ጥሩ የሆኑ ጊዜዎችን ማሳለፍ ግድ ይለናል ፡፡ ሁኔታዎችንና ሥጋችንን ሳናዳምጥ የሚከፈሉ ዋጋዎችን እንደ ጌታ ፈቃድ መክፈልን ይጠይቀናል፡፡
ሦስት በተሰናሰለ መንገድ የተቀመጡ ድርጊቶች በውጤት ሂደት እንዲህ ተቀምጠዋል፡-
ድርጊት(Action)-->ልማድ(Habit)-->ጠባይ(character)
ይህንን መርሕ ለመግለጽ ጸሎትን እንደ ምሳሌ ልውሰድ ፡፡ ጸሎትን ደጋግመን ስናደርገው ወደ ልማድነት ይቀየራል ፡፡ በሕይወታችን ልማድ እየሆነ የመጣውን ተግባር እየጨመርን ደጋግመን ስናደርገው፣ ጠባያችን ወይም መገለጫ ባሕርያችን ይሆናል ፡፡ ከዚያማ ውጤቱ እንዲህ ይሆናል፡-
“መጸለይ እንጂ አለመጸለይ አንችልም፡፡”
“በፊቱ መሆን እንጂ አለመሆን ያቅተናል፡፡”
እጅግ ሊጓጓለት የሚገባ ድንቅ ለውጥ!
የላይኛውን ሐሳብ የሚደግፉና የክርስትና ሕይወት እየተቀጣጠለ፣ እያደገና እየጨመረ የሚሄድ ሕይወት እንደ ሆነ የሚጠቁሙ ብዙ ክፍሎች አሉ ፡፡ ለምሳሌ ሦስቱን ልጥቀስ፡-
“እስከ እግዚአብሔር ፍጹም ሙላት ደርሳችሁ ትሞሉ ዘንድ” (ኤፌሶን 3፥19)
“በመንፈስ የምትቃጠሉ ሁኑ” (ሮሜ 12፥11)
“መንፈስ ይሙላባችሁ እንጂ በወይን ጠጅ አትስከሩ ይህ ማባከን ነውና” /ብዙ የሚያሰክሩ ነገሮች እንዳሉ ልብ ይሏል/(ኤፌሶን 5፥16-20)
ስሚዝ ዊግልስዎርዝ እንዲህ ብሎ ነበር፡-“If you are in the same place today as you were yesterday, you are a backslider.”(ትርጉሙ፡-በዛሬው ቀን ትላንትና የነበርክበት ቦታ ላይ ከተገኘህ የኋሊት እየሄድክ ነው)
በተሰጠ ማንነት፣ ልባችን መሉ በሙሉ በጌታ ላይ ሆኖ ከላይ በተጠቀሰው ዓይነት ፍለጋ(craving) እና ትጋት ስንቀጥል፣ የጌታ አብሮሆት ከመቸው በሚበልጥ ሁኔታ በሕይወታችን ዕውን ይሆናል ፡፡ ከዚህም የተነሣ የምናገኘው የመጀመሪያው በረከት በቃላት ልንገልጸው የማንችለው ሰላም፣ መረጋጋትና ደስታ ይሆናል ፡፡ መንፈሳዊ መረዳታችንም እየጨመረ ስለሚሄድ፣ ጌታን በሚገባ እያወቅነው እንመጣለን፡፡ስለዚህ ለውጣችን ወደ ኋላ የማይቀለበስና ዘላቂ ይሆናል ፡፡ መንፈሳዊ ዓይኖቻችን በጨመረ ሁኔታ እየተከፈቱ ስለሚመጡ፣ ብዙ ረብ የሌላቸውን ነገሮች የመጣል መነሣሣትና አቅም እያገኘን እንመጣለን ፡፡
እንደዚህ በጽናት ሳናሰልስ የጌታን ፊት በጨመረ ሁኔታ በፈለግን ቁጥር፣ የእግዚአብሔር ኃይል በውስጣችን እየጨመረ ስለሚሄድ፣ ብዙ ቀንበሮች ከሕይወታችን ይሰበራሉ ፡፡ ስለዚህም “ሸክሙ ከጫንቃህ ቀንበሩም ከትከሻህ ላይ ይሰበራል” የሚለው ቃል በሕይወታችን ይፈጸማል (ኢሳ.10፡27)፡፡ እናም ከበፊቱ ይልቅ በሕልውናው ውስጥ መቆየት አያስቸግረንም፡፡ ቃሉ እንዲህ ይላልና፡-
“እርሱንም ሳታዩት ትወዱታላችሁ፤ አሁንም ምንም ባታዩት በእርሱ አምናችሁ የእምነታችሁን ፍጻሜ እርሱም የነፍሳችሁን መዳን እየተቀበላችሁ በማይነገርና ክብር በሞላበት ሐሤት ደስ ይላችኋል” (1 ጴጥሮስ 1፥8-9)
ለዚህ አሳብ ጥሩ እይታ የሚሰጠን ኢዮብ 28፥1-11 ነው ፡፡ ይህ የምንባብ ክፍል የማዕድን ሠራተኛ ከባዶ ተነሥቶ የሚያደርገውን ግሥገሣ ነው የሚያሳየው ፡፡ “ዓይኑ ዕንቁን እስክታይ ድረስ” ፣ “የተሸፈነው ነገር ወደ ብርሃን እስኪወጣ ድረስ” ይተጋል ፡፡ እጁን ወደ ቡላድ ድንጋይ ይዘረጋል ፡፡ መጨረሻ ላይ ከብዙ እልህ አስጨራሽ ትግልና ጉዞ በኋላ የከበሩ ማዕድናትን ያገኛል፤ክፍሉ የልፋቱን ውጤት እንዲህ ይገልጸዋልና ፡-
“ሰው ወደ ቡላድ ድንጋይ እጁን ይዘረጋል፤ ተራራውንም ከመሠረቱ ይገለብጣል። ከድንጋይ ውስጥ መንዶልዶያ ይወቅራል፤ ዓይኑምዕንቍን ሁሉ ታያለች። ፈሳሹም እንዳይንጠባጠብ ይገድባል፤የተሰወረውንም ነገር ወደ ብርሃን ያወጣል።”(ቁ.9-11)
አዎ ይህ ክፍል ምሳሌያዊ በሆነ አገላለጽ፣ እንደ ማዕድን ሠራተኛው ያለ መታከት እንድንተጋና የጌታን ፊት እንድንፈልግ ያስተምረናል ፡፡
የእግዚአብሔር ቃል ተግተው “የሚሹኝ ምስጉኖች/የተባረኩ ናቸው” (ምሳሌ 8፡34) ይላልና፤ “እናንተም ትጠሩኛለችሁ፤ ሄዳችሁም ወደ እኔ ትጸልያላችሁ፣እኔም እሰማችኋለሁ። እናንተ ትሹኛላችሁ፣በፍጹም ልባችሁም ከሻችሁኝ ታገኙኛላችሁ። ከእናንተም ዘንድ እገኛለሁ፡፡”(ኤር.29፥13-14) ይላልና ጨክኖ የጌታን ፊት የሚፈልግ ሰው ይዋል ይደር እንጂ፣ የእግዚአብሔር በረከት ታገኘዋለች፡፡
አዎ፣ ጌታ አጥብቀው ለሚሹት ሰዎች በእርግጥ ይገለጣል፡፡ የበለጠ እንድናየው፣ የበለጠ በእርሱ ላይ እንድንደገፍና እንድንጠጋው ያደርገናል፡፡ በተጨማሪም ጌታ ተገልጦ ሕይወታችንን ሲጎበኝ የሚመጣው ለውጥ ለሌሎች በረከት ያደርገናልና በትጋትና በጨመረ ሁኔታ ተግተን እንፈልገው!
ምንጭ:- ዶ/ር በቀለ በላቸው፤ ባለጸጋ ክርስትያን መጽሔት
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የጠለቀ መንፈሳዊ ጉዞ ለመጓዝና እየጨመረ የሚሄድ ርካታና እረፍት እንድናይ ካስፈለገ፣የክርስትና ሕይወት ትጋትን ይጠይቀናል(ዕብ 4:11)፡፡ በተለያየ ቦታ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ቃሉ እንደሚያስተምረን ትጋታችን እየጨመረ ሲሄድ፣ የእግዚአብሔር ጸጋም በሕይወታችን እየጨመረ ይሄዳል፡፡ እናም ለመንፈሳዊ ነገር ያለን መሻት እያደገ ይሄዳል፡፡ በእንደዚህ ዓይነት ግሥገሣ ውስጥ ባለማሰለስ ስንገኝ፣ እሱን ለማወቅ ያለን ራብ እየተቀጣጠለ ስለሚመጣ፣እየጨመረ ለሚሄድ ፍለጋ እንጠናከራለን፡፡ ይህንን በእንግሊዝኛው አገላለጽ positive vicious cycle ይሉታል፡፡ ማለትም ትጋቱ የጨመረ መንፈሳዊ ራብን ይወልዳል፤ የጨመረው መንፈሳዊ ራብ ደግሞ ሌላ ከፍ ያለ ትጋትንና ግሥገሣን ይወልዳል፡፡ መቼም ይሄ ኡደት ማቆሚያ የለውም እኛ በሥጋዊ አካሄዶች እስካላጠፋነው ድረስ!
በነገራችን ላይ እየጨመረ የሚሄድ የክርስትና ሕይወት ብዙ ግብዓቶችን ይፈልጋል ፡፡ መልካም የእምነት ውጊያንና ዲያቢሎስን በኃይል ጸንቶ መቃወም ይጠይቃል ፡፡ የእግዚአብሔርን ቃል ሳይታክቱ ማሰላሰልና በፊቱ ጥሩ የሆኑ ጊዜዎችን ማሳለፍ ግድ ይለናል ፡፡ ሁኔታዎችንና ሥጋችንን ሳናዳምጥ የሚከፈሉ ዋጋዎችን እንደ ጌታ ፈቃድ መክፈልን ይጠይቀናል፡፡
ሦስት በተሰናሰለ መንገድ የተቀመጡ ድርጊቶች በውጤት ሂደት እንዲህ ተቀምጠዋል፡-
ድርጊት(Action)-->ልማድ(Habit)-->ጠባይ(character)
ይህንን መርሕ ለመግለጽ ጸሎትን እንደ ምሳሌ ልውሰድ ፡፡ ጸሎትን ደጋግመን ስናደርገው ወደ ልማድነት ይቀየራል ፡፡ በሕይወታችን ልማድ እየሆነ የመጣውን ተግባር እየጨመርን ደጋግመን ስናደርገው፣ ጠባያችን ወይም መገለጫ ባሕርያችን ይሆናል ፡፡ ከዚያማ ውጤቱ እንዲህ ይሆናል፡-
“መጸለይ እንጂ አለመጸለይ አንችልም፡፡”
“በፊቱ መሆን እንጂ አለመሆን ያቅተናል፡፡”
እጅግ ሊጓጓለት የሚገባ ድንቅ ለውጥ!
የላይኛውን ሐሳብ የሚደግፉና የክርስትና ሕይወት እየተቀጣጠለ፣ እያደገና እየጨመረ የሚሄድ ሕይወት እንደ ሆነ የሚጠቁሙ ብዙ ክፍሎች አሉ ፡፡ ለምሳሌ ሦስቱን ልጥቀስ፡-
“እስከ እግዚአብሔር ፍጹም ሙላት ደርሳችሁ ትሞሉ ዘንድ” (ኤፌሶን 3፥19)
“በመንፈስ የምትቃጠሉ ሁኑ” (ሮሜ 12፥11)
“መንፈስ ይሙላባችሁ እንጂ በወይን ጠጅ አትስከሩ ይህ ማባከን ነውና” /ብዙ የሚያሰክሩ ነገሮች እንዳሉ ልብ ይሏል/(ኤፌሶን 5፥16-20)
ስሚዝ ዊግልስዎርዝ እንዲህ ብሎ ነበር፡-“If you are in the same place today as you were yesterday, you are a backslider.”(ትርጉሙ፡-በዛሬው ቀን ትላንትና የነበርክበት ቦታ ላይ ከተገኘህ የኋሊት እየሄድክ ነው)
በተሰጠ ማንነት፣ ልባችን መሉ በሙሉ በጌታ ላይ ሆኖ ከላይ በተጠቀሰው ዓይነት ፍለጋ(craving) እና ትጋት ስንቀጥል፣ የጌታ አብሮሆት ከመቸው በሚበልጥ ሁኔታ በሕይወታችን ዕውን ይሆናል ፡፡ ከዚህም የተነሣ የምናገኘው የመጀመሪያው በረከት በቃላት ልንገልጸው የማንችለው ሰላም፣ መረጋጋትና ደስታ ይሆናል ፡፡ መንፈሳዊ መረዳታችንም እየጨመረ ስለሚሄድ፣ ጌታን በሚገባ እያወቅነው እንመጣለን፡፡ስለዚህ ለውጣችን ወደ ኋላ የማይቀለበስና ዘላቂ ይሆናል ፡፡ መንፈሳዊ ዓይኖቻችን በጨመረ ሁኔታ እየተከፈቱ ስለሚመጡ፣ ብዙ ረብ የሌላቸውን ነገሮች የመጣል መነሣሣትና አቅም እያገኘን እንመጣለን ፡፡
እንደዚህ በጽናት ሳናሰልስ የጌታን ፊት በጨመረ ሁኔታ በፈለግን ቁጥር፣ የእግዚአብሔር ኃይል በውስጣችን እየጨመረ ስለሚሄድ፣ ብዙ ቀንበሮች ከሕይወታችን ይሰበራሉ ፡፡ ስለዚህም “ሸክሙ ከጫንቃህ ቀንበሩም ከትከሻህ ላይ ይሰበራል” የሚለው ቃል በሕይወታችን ይፈጸማል (ኢሳ.10፡27)፡፡ እናም ከበፊቱ ይልቅ በሕልውናው ውስጥ መቆየት አያስቸግረንም፡፡ ቃሉ እንዲህ ይላልና፡-
“እርሱንም ሳታዩት ትወዱታላችሁ፤ አሁንም ምንም ባታዩት በእርሱ አምናችሁ የእምነታችሁን ፍጻሜ እርሱም የነፍሳችሁን መዳን እየተቀበላችሁ በማይነገርና ክብር በሞላበት ሐሤት ደስ ይላችኋል” (1 ጴጥሮስ 1፥8-9)
ለዚህ አሳብ ጥሩ እይታ የሚሰጠን ኢዮብ 28፥1-11 ነው ፡፡ ይህ የምንባብ ክፍል የማዕድን ሠራተኛ ከባዶ ተነሥቶ የሚያደርገውን ግሥገሣ ነው የሚያሳየው ፡፡ “ዓይኑ ዕንቁን እስክታይ ድረስ” ፣ “የተሸፈነው ነገር ወደ ብርሃን እስኪወጣ ድረስ” ይተጋል ፡፡ እጁን ወደ ቡላድ ድንጋይ ይዘረጋል ፡፡ መጨረሻ ላይ ከብዙ እልህ አስጨራሽ ትግልና ጉዞ በኋላ የከበሩ ማዕድናትን ያገኛል፤ክፍሉ የልፋቱን ውጤት እንዲህ ይገልጸዋልና ፡-
“ሰው ወደ ቡላድ ድንጋይ እጁን ይዘረጋል፤ ተራራውንም ከመሠረቱ ይገለብጣል። ከድንጋይ ውስጥ መንዶልዶያ ይወቅራል፤ ዓይኑምዕንቍን ሁሉ ታያለች። ፈሳሹም እንዳይንጠባጠብ ይገድባል፤የተሰወረውንም ነገር ወደ ብርሃን ያወጣል።”(ቁ.9-11)
አዎ ይህ ክፍል ምሳሌያዊ በሆነ አገላለጽ፣ እንደ ማዕድን ሠራተኛው ያለ መታከት እንድንተጋና የጌታን ፊት እንድንፈልግ ያስተምረናል ፡፡
የእግዚአብሔር ቃል ተግተው “የሚሹኝ ምስጉኖች/የተባረኩ ናቸው” (ምሳሌ 8፡34) ይላልና፤ “እናንተም ትጠሩኛለችሁ፤ ሄዳችሁም ወደ እኔ ትጸልያላችሁ፣እኔም እሰማችኋለሁ። እናንተ ትሹኛላችሁ፣በፍጹም ልባችሁም ከሻችሁኝ ታገኙኛላችሁ። ከእናንተም ዘንድ እገኛለሁ፡፡”(ኤር.29፥13-14) ይላልና ጨክኖ የጌታን ፊት የሚፈልግ ሰው ይዋል ይደር እንጂ፣ የእግዚአብሔር በረከት ታገኘዋለች፡፡
አዎ፣ ጌታ አጥብቀው ለሚሹት ሰዎች በእርግጥ ይገለጣል፡፡ የበለጠ እንድናየው፣ የበለጠ በእርሱ ላይ እንድንደገፍና እንድንጠጋው ያደርገናል፡፡ በተጨማሪም ጌታ ተገልጦ ሕይወታችንን ሲጎበኝ የሚመጣው ለውጥ ለሌሎች በረከት ያደርገናልና በትጋትና በጨመረ ሁኔታ ተግተን እንፈልገው!
ምንጭ:- ዶ/ር በቀለ በላቸው፤ ባለጸጋ ክርስትያን መጽሔት
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍23❤2
. ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“በአምላክህም በእግዚአብሔር ፊት እንዲህ ብለህ ተናገር፦ አባቴ የተቅበዘበዘ ሶርያዊ ነበረ፤ በቍጥር ጥቂት ሳለ ወደ ግብፅ ወረደ በዚያም ተቀመጠ፤ ታላቅ የሆነ የበረታም ቍጥሩም የበዛ ሕዝብ ሆነ።”
ዘዳግም 26፥5
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“በአምላክህም በእግዚአብሔር ፊት እንዲህ ብለህ ተናገር፦ አባቴ የተቅበዘበዘ ሶርያዊ ነበረ፤ በቍጥር ጥቂት ሳለ ወደ ግብፅ ወረደ በዚያም ተቀመጠ፤ ታላቅ የሆነ የበረታም ቍጥሩም የበዛ ሕዝብ ሆነ።”
ዘዳግም 26፥5
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤7👎1