. ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“እናንተ በጌታ ጸንታችሁ ብትቆሙ፥ አሁን በሕይወት እንኖራለንና።”
1ኛ ተሰሎንቄ 3፥8
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“እናንተ በጌታ ጸንታችሁ ብትቆሙ፥ አሁን በሕይወት እንኖራለንና።”
1ኛ ተሰሎንቄ 3፥8
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤9🔥1
የአዲስ ኪዳን ማብራሪያ.pdf
55.3 MB
👉ርዕስ፦ የአዲስ ኪዳን ማብራሪያ
The Applied New Testament Commentary by Thomas Hale ከሚለው የተወሰደ
🗣ተርጓሚ፦ መስፍን ተስፋዬ፣ ተስፋዬ መስፍን፣ ምንሊክ አስፋውና ቴዎድሮስ በየነ ናቸው።
✏️ዋና ኦርታኢ፦ ደረጀ በቀለ ሲሆኑ ሰሎሞን ጥላሁንም አግዘዋል።
🖨አሳታሚ፦ ራዕይ አሳታሚ
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
The Applied New Testament Commentary by Thomas Hale ከሚለው የተወሰደ
🗣ተርጓሚ፦ መስፍን ተስፋዬ፣ ተስፋዬ መስፍን፣ ምንሊክ አስፋውና ቴዎድሮስ በየነ ናቸው።
✏️ዋና ኦርታኢ፦ ደረጀ በቀለ ሲሆኑ ሰሎሞን ጥላሁንም አግዘዋል።
🖨አሳታሚ፦ ራዕይ አሳታሚ
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤5👍5
በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ በዮሐንስ ራእይ ከሰባቱ አብያተ ክርስቲያናት መካከል አንድም ነቀፋ ያልቀረበበት ቤተ ክርስቲያን የቱ ነው?
Anonymous Quiz
33%
ሀ. ፊላደልፊያ
8%
ለ. ጴርጋሞን
13%
ሐ. ሰምርኔስ
7%
መ. ሰርዴስ
12%
ሠ. ኤፌሶን
11%
ረ. ሀ እና መ
17%
ሰ. ሀ እና ሐ
👍2🔥2
. ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“ዘመኑ ቀርቦአልና የሚያነበው፥ የትንቢቱን ቃል የሚሰሙትና በውስጡ የተጻፈውን የሚጠብቁት ብፁዓን ናቸው።”
ራእይ 1፥3
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“ዘመኑ ቀርቦአልና የሚያነበው፥ የትንቢቱን ቃል የሚሰሙትና በውስጡ የተጻፈውን የሚጠብቁት ብፁዓን ናቸው።”
ራእይ 1፥3
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤4🔥3👍1
የሐዋርያው ጳውሎስ መልእክቶች የአጻጻፍ ስልት እና ይዘት
5. የግጥም እና የመዝሙር ይዘቶች
ጳውሎስ ሥነ-መለኮታዊ እውነቶችን ለማጉላት መዝሙሮችን ወይም ቅኔያዊ ምንባቦችን አካቷል።
ምሳሌ፡- ፊልጵስዩስ 2፡6-11 ስለ ኢየሱስ ትህትና እና ከፍ ያለ የክርስቶስ መዝሙር ይዟል።
6. የወላጅ እና የዲሲፕሊን ድምጸት ያላቸው መልእክቶች
በአብያተ ክርስቲያናት ውስጥ ያሉ ስህተቶችን ወይም ግጭቶችን ለመፍታት አንዳንድ ጊዜ የማስተካከያ ዘዴ ይጠቀማል።
ምሳሌ፡- 1ኛ ቆሮንቶስ በቤተክርስቲያን ውስጥ መለያየትንና ብልሹ ባህሪይን ይገስጻል።
7. መምሰል እና ምሳሌ
ጳውሎስ የክርስቶስን ምሳሌ በመከተል የእሱን እምነትና ሕይወት እንዲኮርጁ አንባቢዎቹ አበረታቷቸዋል።
ምሳሌ፦ 1ኛ ቆሮንቶስ 11፥1፦ “እኔ ክርስቶስን እንደምመስል እኔን ምሰሉ።”
8. የባህል ማጣቀሻዎች እና ምስለት
ሐዋሪያው ጳውሎስ ለአድማጮቹ የተለመዱ ዘይቤዎችን እና ምሳሌዎችን ተጠቅሟል። ለምሳሌ ከስፖርት ፣ ከግብርና እና ከወታደራዊ ሕይወት ጋር እያነጻጸረ ይጠቀማል።
ምሳሌ፡- 1ኛ ቆሮንቶስ 9፡24-27 የክርስትናን ሕይወት ከሩጫ ጋር ያነጻጽራል።
9. ልባዊ ምክር እና ማበረታቻ
ጳውሎስ አንባቢዎቹን በቅዱስና በጽድቅ ሕይወት እንዲመሩ ደጋግሞ ይመክራል።
ምሳሌ፡- ኤፌሶን 4-6 ግንኙነትን እና መንፈሳዊ ጦርነትን ጨምሮ ለክርስቲያናዊ ኑሮ መመሪያዎችን ይዟል።
ይቀጥላል...
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
5. የግጥም እና የመዝሙር ይዘቶች
ጳውሎስ ሥነ-መለኮታዊ እውነቶችን ለማጉላት መዝሙሮችን ወይም ቅኔያዊ ምንባቦችን አካቷል።
ምሳሌ፡- ፊልጵስዩስ 2፡6-11 ስለ ኢየሱስ ትህትና እና ከፍ ያለ የክርስቶስ መዝሙር ይዟል።
6. የወላጅ እና የዲሲፕሊን ድምጸት ያላቸው መልእክቶች
በአብያተ ክርስቲያናት ውስጥ ያሉ ስህተቶችን ወይም ግጭቶችን ለመፍታት አንዳንድ ጊዜ የማስተካከያ ዘዴ ይጠቀማል።
ምሳሌ፡- 1ኛ ቆሮንቶስ በቤተክርስቲያን ውስጥ መለያየትንና ብልሹ ባህሪይን ይገስጻል።
7. መምሰል እና ምሳሌ
ጳውሎስ የክርስቶስን ምሳሌ በመከተል የእሱን እምነትና ሕይወት እንዲኮርጁ አንባቢዎቹ አበረታቷቸዋል።
ምሳሌ፦ 1ኛ ቆሮንቶስ 11፥1፦ “እኔ ክርስቶስን እንደምመስል እኔን ምሰሉ።”
8. የባህል ማጣቀሻዎች እና ምስለት
ሐዋሪያው ጳውሎስ ለአድማጮቹ የተለመዱ ዘይቤዎችን እና ምሳሌዎችን ተጠቅሟል። ለምሳሌ ከስፖርት ፣ ከግብርና እና ከወታደራዊ ሕይወት ጋር እያነጻጸረ ይጠቀማል።
ምሳሌ፡- 1ኛ ቆሮንቶስ 9፡24-27 የክርስትናን ሕይወት ከሩጫ ጋር ያነጻጽራል።
9. ልባዊ ምክር እና ማበረታቻ
ጳውሎስ አንባቢዎቹን በቅዱስና በጽድቅ ሕይወት እንዲመሩ ደጋግሞ ይመክራል።
ምሳሌ፡- ኤፌሶን 4-6 ግንኙነትን እና መንፈሳዊ ጦርነትን ጨምሮ ለክርስቲያናዊ ኑሮ መመሪያዎችን ይዟል።
ይቀጥላል...
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤8👍2
. ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“አንተ በምሕረትህ ብዛት በምድረ በዳ አልተውሃቸውም፤ በመንገድም ይመራቸው ዘንድ የደመና ዓምድ በቀን፥ የሚሄዱበትንም መንገድ ያበራላቸው ዘንድ የእሳት ዓምድ በሌሊት ከእነርሱ አልራቀም።”
ነህምያ 9፥19
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“አንተ በምሕረትህ ብዛት በምድረ በዳ አልተውሃቸውም፤ በመንገድም ይመራቸው ዘንድ የደመና ዓምድ በቀን፥ የሚሄዱበትንም መንገድ ያበራላቸው ዘንድ የእሳት ዓምድ በሌሊት ከእነርሱ አልራቀም።”
ነህምያ 9፥19
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍7
#የሮሜ_መልእክት_ጥናት
ሮሜ 10፥1-4
የዚህ ምዕራፍ ጭብጥ እስራኤል አሁን እግዚአብሔርን የመግፋቷ ጉዳይ ነው፡፡ ጳውሎስ ከመለኮታዊ ሉዓላዊነት (ምዕራፍ 9) ወደ ሰው ተጠያቂነት ያመራል፡፡ ባለፈው ምዕራፍ (ሮሜ 9:30-33) የጽድቅን ጭብጥ ካስተዋወቀ በኋላ የእስራኤልን የእምቢታ ሦስት ገጽታዎች ያብራራል፡፡
እስራኤል እንደ ሕዝብ የመሢሑን መምጣት በጉጉት እየጠበቁ ሊቀበሉት የተዘጋጁ እንደነበሩ አድርጋችሁ ታስቡ ይሆናል፡፡ ለዘመናት የብሉይ ኪዳን ትንቢቶችን ያውቃሉ፤ ሕጉንም ሲሠሩበት ኖረዋል፣ እርሱም ወደ ክርስቶስ እንዲመራቸው የተሰጠ እንደ «ሥራ መሪ» ነበር (ገላ. 3፡24)፡፡ እግዚአብሔር ሕዝቡን ሊያዘጋጅ ፈልጓል፣ ነገር ግን ኢየሱስ ክርስቶስ በመጣ ጊዜ አልተቀበሉትም፡፡ ‹‹የእርሱ ወደ ሆነው መጣ፣ የገዛ ወገኖቹም አልተቀበሉትም» (ዮሐንስ 1፡11)፡፡ እርግጥ ነው፣ መምጣቱን ሲጠባበቁ የነበሩት ቅሬታዎች ነበሩ፣ ለምሳሌ ስምዖንና ሐና (ሉቃስ 2፡25-38)፤ ነገር ግን አብዛኛው ሕዝብ ክርስቶስ ሲመጣ ዝግጁ አልነበረም፡፡
ይህን አሳዛኝ ነገር እንዴት መግለጽ እንችላለን? እስራኤላውያን መሢሑን ያልተቀበሉበትን ብዙ ምክንያቶች ጳውሎስ አቅርቧል፡፡
ሀ) ደኅንነት እንደሚያስፈልጋቸው አልተሰማቸውም ( 10፥1)
ጳውሎስ ለእስራኤላውያን ወይም ለአይሁዳውያን ወደ እግዚአብሔር የሚጸልየው ለምንድን ነው?
በሮሜ 9÷18 እግዚአብሔር ምሕረት ለሚያደርግለት ምሕረቱን ያሳያል፥ ልቡን ሊያጠነክር የሚፈልገውንም ያጠነክረዋል ብሎ ከጻፈ፤ አሁን ታዲያ ለአይሁዳውያን ደኅንነት ሲጸልይ ምን ጥቅም ያገኝበታል? ጳውሎስ እግዚአብሔርን ለማግባባት ይሞክራልን? ወይስ በጸሎቱ የእግዚአብሔርን አስተሳሰብ ለመለወጥ ይጥራል?
መልሱ አዎን ነው። እጅግ በሚያስደንቅ መንገድ፤ እግዚአብሔር በፀሎታችን እንድናግባባው ይፈቅዳል። ይህን በማስረጃ ለማስደገፍ በመላው መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በጣም ብዙ ምሳሌዎች አሉ። በተጨማሪም በጸሎታችን የሰይጣንን ሥራ ማሰናከል እንችላለን። ከእግዚአብሔር ቃል ቀጥሎ
ጸሎት በጣም ኀይለኛ የሆነ መንፈሳዊ የጦር መሣሪያ ነው (ኤፌ. 6፥17-18)። አንድ ነገር ለማግኘት በኢየሱስ ስም ብንጸልይ፥ እግዚአብሔር ይመልስልናል (ዮሐ. 15፥16)። ስለዚህም ጳውሎስ ለአይሁዳውያን ይጸልያል።
ጳውሎስ ከሕዝቡ ጋር ተስማምቶ ወንጌልን ተቃውሞ ኢየሱስን እንደ አታላይ የቆጠረበት ጊዜ ነበር፡፡ እስራኤላውያን ደኅንነት የሚያስፈልጋቸው አይሁድ ሳይሆኑ አሕዛብ ብቻ እንደሆኑ ቆጠሩ፡፡ በብዙ ምሳሌዎቹ እነዚህን የተሳሳቱ አሳቦች ኢየሱስ አንድ በአንድ አንሥቶአቸዋል፡- ታላቁ ወንድም (ሉቃስ 15፡11- 32) እና ፈሪሳዊው (ሉቃስ 18:9-14) ሁለት ምሳሌዎች ናቸው፡፡ እስራኤላውያን ከሮም ነፃ የሚወጡበት የፖለቲካ አርነት ቢፈልጉም፣ መንፈሳዊ ደኅንነት እንደሚያስፈልጋቸው ግን አልተረዱም ነበር፡፡
ይቀጥላል...
ምንጭ፦ ዋረን ደብልዩ ዌርዝ ቢ፤ ተስማማ፤ ገጽ 104-105፣ የአዲስ ኪዳን ማብራሪያ፤ ገጽ 374
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ሮሜ 10፥1-4
የዚህ ምዕራፍ ጭብጥ እስራኤል አሁን እግዚአብሔርን የመግፋቷ ጉዳይ ነው፡፡ ጳውሎስ ከመለኮታዊ ሉዓላዊነት (ምዕራፍ 9) ወደ ሰው ተጠያቂነት ያመራል፡፡ ባለፈው ምዕራፍ (ሮሜ 9:30-33) የጽድቅን ጭብጥ ካስተዋወቀ በኋላ የእስራኤልን የእምቢታ ሦስት ገጽታዎች ያብራራል፡፡
እስራኤል እንደ ሕዝብ የመሢሑን መምጣት በጉጉት እየጠበቁ ሊቀበሉት የተዘጋጁ እንደነበሩ አድርጋችሁ ታስቡ ይሆናል፡፡ ለዘመናት የብሉይ ኪዳን ትንቢቶችን ያውቃሉ፤ ሕጉንም ሲሠሩበት ኖረዋል፣ እርሱም ወደ ክርስቶስ እንዲመራቸው የተሰጠ እንደ «ሥራ መሪ» ነበር (ገላ. 3፡24)፡፡ እግዚአብሔር ሕዝቡን ሊያዘጋጅ ፈልጓል፣ ነገር ግን ኢየሱስ ክርስቶስ በመጣ ጊዜ አልተቀበሉትም፡፡ ‹‹የእርሱ ወደ ሆነው መጣ፣ የገዛ ወገኖቹም አልተቀበሉትም» (ዮሐንስ 1፡11)፡፡ እርግጥ ነው፣ መምጣቱን ሲጠባበቁ የነበሩት ቅሬታዎች ነበሩ፣ ለምሳሌ ስምዖንና ሐና (ሉቃስ 2፡25-38)፤ ነገር ግን አብዛኛው ሕዝብ ክርስቶስ ሲመጣ ዝግጁ አልነበረም፡፡
ይህን አሳዛኝ ነገር እንዴት መግለጽ እንችላለን? እስራኤላውያን መሢሑን ያልተቀበሉበትን ብዙ ምክንያቶች ጳውሎስ አቅርቧል፡፡
ሀ) ደኅንነት እንደሚያስፈልጋቸው አልተሰማቸውም ( 10፥1)
ጳውሎስ ለእስራኤላውያን ወይም ለአይሁዳውያን ወደ እግዚአብሔር የሚጸልየው ለምንድን ነው?
በሮሜ 9÷18 እግዚአብሔር ምሕረት ለሚያደርግለት ምሕረቱን ያሳያል፥ ልቡን ሊያጠነክር የሚፈልገውንም ያጠነክረዋል ብሎ ከጻፈ፤ አሁን ታዲያ ለአይሁዳውያን ደኅንነት ሲጸልይ ምን ጥቅም ያገኝበታል? ጳውሎስ እግዚአብሔርን ለማግባባት ይሞክራልን? ወይስ በጸሎቱ የእግዚአብሔርን አስተሳሰብ ለመለወጥ ይጥራል?
መልሱ አዎን ነው። እጅግ በሚያስደንቅ መንገድ፤ እግዚአብሔር በፀሎታችን እንድናግባባው ይፈቅዳል። ይህን በማስረጃ ለማስደገፍ በመላው መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በጣም ብዙ ምሳሌዎች አሉ። በተጨማሪም በጸሎታችን የሰይጣንን ሥራ ማሰናከል እንችላለን። ከእግዚአብሔር ቃል ቀጥሎ
ጸሎት በጣም ኀይለኛ የሆነ መንፈሳዊ የጦር መሣሪያ ነው (ኤፌ. 6፥17-18)። አንድ ነገር ለማግኘት በኢየሱስ ስም ብንጸልይ፥ እግዚአብሔር ይመልስልናል (ዮሐ. 15፥16)። ስለዚህም ጳውሎስ ለአይሁዳውያን ይጸልያል።
ጳውሎስ ከሕዝቡ ጋር ተስማምቶ ወንጌልን ተቃውሞ ኢየሱስን እንደ አታላይ የቆጠረበት ጊዜ ነበር፡፡ እስራኤላውያን ደኅንነት የሚያስፈልጋቸው አይሁድ ሳይሆኑ አሕዛብ ብቻ እንደሆኑ ቆጠሩ፡፡ በብዙ ምሳሌዎቹ እነዚህን የተሳሳቱ አሳቦች ኢየሱስ አንድ በአንድ አንሥቶአቸዋል፡- ታላቁ ወንድም (ሉቃስ 15፡11- 32) እና ፈሪሳዊው (ሉቃስ 18:9-14) ሁለት ምሳሌዎች ናቸው፡፡ እስራኤላውያን ከሮም ነፃ የሚወጡበት የፖለቲካ አርነት ቢፈልጉም፣ መንፈሳዊ ደኅንነት እንደሚያስፈልጋቸው ግን አልተረዱም ነበር፡፡
ይቀጥላል...
ምንጭ፦ ዋረን ደብልዩ ዌርዝ ቢ፤ ተስማማ፤ ገጽ 104-105፣ የአዲስ ኪዳን ማብራሪያ፤ ገጽ 374
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍8❤4
. ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“በክርስቶስ በሰማያዊ ስፍራ በመንፈሳዊ በረከት ሁሉ የባረከን የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክና አባት ይባረክ።”
ኤፌሶን 1፥3
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“በክርስቶስ በሰማያዊ ስፍራ በመንፈሳዊ በረከት ሁሉ የባረከን የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክና አባት ይባረክ።”
ኤፌሶን 1፥3
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤6🥰3👍2
ትህትና
ከእግዚአብሔር ጋር ለመኖርና አሸናፊ ለመሆን ትህትና እጅግ አስፈላጊ ባህሪ ነው፡፡ ካለ ትህትና ከእግዚአብሔር ጋር እንጣላለን፡፡ እንዲያውም እግዚአብሄር ትዕቢተኛውን ይቃወማል፡፡
"ነገር ግን ጸጋን አብልጦ ይሰጣል፤ ስለዚህ፦ እግዚአብሔር ትዕቢተኞችን ይቃወማል፥ ለትሑታን ግን ጸጋን ይሰጣል ።" ያዕቆብ 4፡6
ትህትና ይህን ያህል አስፈላጊ ከሆነ ትህትና ግን ምንድነው ብለን መጠየቅ ጥበብ ነው፡፡ ትህትናን በደንብ ልንማረውና ልናጠናው ተግተንም ልንለማመደው የሚገባ የተወደደ ባህሪ ነው፡፡
ትህትና ለሁሉም ሰው ያለ አክብሮት ነው፡፡ ትሁት ሰው ለወገኔ ይጠቅማል በማለት አንዱን ከሌላው ሰው በወገናዊነት አያበላልጥም፡፡ ትሁት ሰው ለሁሉም ከፍ ያለ አክብሮት ያለው ሰው ሲሆን ሁሉንም ለማገልገልና ለመጥቀም የተዘጋጀ ነው፡፡
"ለወገኔ ይጠቅማል በማለት ወይም በከንቱ ውዳሴ ምክንያት አንድ እንኳ አታድርጉ::" ፊልጵስዩስ 2፡3
ትሁት ሰው ሌላው ሰው ከእርሱ እንደሚሻል በቅንነትና በእውነት የሚያምን ነው፡፡ ትሁት ሰው ራሱን ብቻ አስፈላጊ አድርጎ የማይመለከት ሰው ነው፡፡ ትሁት ሰው የሰውን ሁሉ አስፈላጊነት የሚረዳ ሰው ነው፡፡ ትሁት ሰው በሌላው ሰው ስጦታ ጥሪና ጠቃሚነት የሚያምን ነው፡፡
"ነገር ግን እያንዳንዱ ባልንጀራው ከራሱ ይልቅ እንዲሻል በትሕትና ይቍጠር::" ፊልጵስዩስ 2፡3
ትሁት ሰው የራሱን ብቻ የማይፈልግ ሰው ነው፡፡ ትሁት ሰው ሌላውንም የሚጠቅመውን ነገር ለማድረግ የሚፈልግ ሰው ነው፡፡ ትሁት ሰው ራስ ወዳድ አይደለም፡፡ ትሁት ሰው ለሌላው ጥቅም በትጋት የሚሰራ ሰው ነው፡፡
"እያንዳንዱ ለራሱ የሚጠቅመውን አይመልከት፥ ለባልንጀራው ደግሞ እንጂ" ፊልጵስዩስ 2፡4
ትህትና እንደ ክርስቶስ ራስን አዋርዶ መኖር ነው፡፡ የሰው ትህትና የሚጀምረው ከአሳብ ነው፡፡ ሰው ገና በአሳብ ደረጃ ራሱን ካላዋረደ በትህትና ሊመላለስ አይችልም፡፡ ትሁት ሰው የትህትና መልክ ብቻ ሳይሆን የትህትና ሃሳብና ውሳኔ ያለው ነው፡፡
"በክርስቶስ ኢየሱስ የነበረ ይህ አሳብ በእናንተ ዘንድ ደግሞ ይሁን።" ፊልጵስዩስ 2፡5
ከኢየሱስ የምንማረው ትሁት ሰው ለደረጃ ግድ እንደሌለው ነው፡፡ ትሁት ሰው ስለደረጃ አይጣላም አይጨቃጨቅም፡፡ ትሁት ሰው ትኩረቱ ማገልገል ሰውም መጥቀም በሰው ላይ ዋጋን መጨመር ሰውን ማንሳት ላይ እንጂ ስለስምና ስለስልጣን ወይም ጥቅም አይደለም፡፡ ትሁት ሰው የትም ማገልገል ስለሚችል መቼም ለመውረድ የተዘጋጀ ነው፡፡
"እርሱ በእግዚአብሔር መልክ ሲኖር ሳለ ከእግዚአብሔር ጋር መተካከልን መቀማት እንደሚገባ ነገር አልቈጠረውም፥" ፊልጵስዩስ 2፡6
ትሁት ሰው እግዚአብሔርም እንዲያዋርደው የማያደርግ ቀድሞ ራሱን የሚያዋርድ ነው፡፡ ትሁትን ሰው የምናውቀው ሁኔታ ስላልተመቸው በመዋረዱ ሳይሆን ከፍ የሚያደርግ ሁኔታ እያለ በራሱ ፈቃድ ራሱን የሚያዋርድ ሰው ነው፡፡
ትሁት ሰው ሰዎችን ለመጥቀም በምድር ላይ እንዳለ የሚያውቅ ሰው ሲሆን ሰዎች ሲጠቀሙበት እንደ እድል እንጂ እንደ ሽንፈት የማይቆጥር ሰው ነው፡፡ ትሁት ሰው ሰዎች እንደተጠቀሙበት የሚሰማውን አፍራሽ ስሜት የማይቀበል ሰዎች እንዲጠቀሙበት የሚፈቅድ የባሪያ ልብ ያለው ለራሱ የማይሰስት ሰው ነው፡፡
"ነገር ግን የባሪያን መልክ ይዞ በሰውም ምሳሌ ሆኖ ራሱን ባዶ አደረገ፥" ፊልጵስዩስ 2፡7
ትሁት ሰው ነገሮችን ካደረገ በኋላ ክፍያውን የማይተምን በትህትናው የማይመካ ስላደረገው ስራ ዋጋውን ራሱ የማይተምን ሃላፊነቱን ብቻ እንደተወጠ የሚሰማው ሰው ነው፡፡ ትሁት ሰው ምንጩ እግዚአብሔር እንደሆነ የሚረዳ እንካ በእንካ አገልግሎት የሌለው ሰው ነው፡፡
"እንዲሁ እናንተ ደግሞ የታዘዛችሁትን ሁሉ ባደረጋችሁ ጊዜ፦ የማንጠቅም ባሪያዎች ነን፥ ልናደርገው የሚገባንን አድርገናል በሉ።" ሉቃስ 17፡10
ትሁት ሰው ማንነቱን ጠንቅቆ የተረዳ ፣ ክብሩን የሚያውቅ ፣ የእርሱ ዝቅ ብሎ ማገልገል ምንም እንደማያዋርደው የሚያውቅ ሰው ነው፡፡ ትሁት ሰው በእግዚአብሔር ካለው ክብር እርሱን ሊያዋርደው የሚችል ምንም ነገር እንደሌለ የተረዳ ነው፡፡
"ኢየሱስ አብ ሁሉን በልጁ እንደ ሰጠው ከእግዚአብሔርም እንደ ወጣ ወደ እግዚአብሔርም እንዲሄድ አውቆ፥ ከእራት ተነሣ ልብሱንም አኖረ፥ ማበሻም ጨርቅ ወስዶ ታጠቀ፤ በኋላም በመታጠቢያው ውኃ ጨመረ፥ የደቀ መዛሙርቱንም እግር ሊያጥብና በታጠቀበትም ማበሻ ጨርቅ ሊያብስ ጀመረ።" ዮሐንስ 13፡3-5
ምንጭ:- አብይ ዋቁማ
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ከእግዚአብሔር ጋር ለመኖርና አሸናፊ ለመሆን ትህትና እጅግ አስፈላጊ ባህሪ ነው፡፡ ካለ ትህትና ከእግዚአብሔር ጋር እንጣላለን፡፡ እንዲያውም እግዚአብሄር ትዕቢተኛውን ይቃወማል፡፡
"ነገር ግን ጸጋን አብልጦ ይሰጣል፤ ስለዚህ፦ እግዚአብሔር ትዕቢተኞችን ይቃወማል፥ ለትሑታን ግን ጸጋን ይሰጣል ።" ያዕቆብ 4፡6
ትህትና ይህን ያህል አስፈላጊ ከሆነ ትህትና ግን ምንድነው ብለን መጠየቅ ጥበብ ነው፡፡ ትህትናን በደንብ ልንማረውና ልናጠናው ተግተንም ልንለማመደው የሚገባ የተወደደ ባህሪ ነው፡፡
ትህትና ለሁሉም ሰው ያለ አክብሮት ነው፡፡ ትሁት ሰው ለወገኔ ይጠቅማል በማለት አንዱን ከሌላው ሰው በወገናዊነት አያበላልጥም፡፡ ትሁት ሰው ለሁሉም ከፍ ያለ አክብሮት ያለው ሰው ሲሆን ሁሉንም ለማገልገልና ለመጥቀም የተዘጋጀ ነው፡፡
"ለወገኔ ይጠቅማል በማለት ወይም በከንቱ ውዳሴ ምክንያት አንድ እንኳ አታድርጉ::" ፊልጵስዩስ 2፡3
ትሁት ሰው ሌላው ሰው ከእርሱ እንደሚሻል በቅንነትና በእውነት የሚያምን ነው፡፡ ትሁት ሰው ራሱን ብቻ አስፈላጊ አድርጎ የማይመለከት ሰው ነው፡፡ ትሁት ሰው የሰውን ሁሉ አስፈላጊነት የሚረዳ ሰው ነው፡፡ ትሁት ሰው በሌላው ሰው ስጦታ ጥሪና ጠቃሚነት የሚያምን ነው፡፡
"ነገር ግን እያንዳንዱ ባልንጀራው ከራሱ ይልቅ እንዲሻል በትሕትና ይቍጠር::" ፊልጵስዩስ 2፡3
ትሁት ሰው የራሱን ብቻ የማይፈልግ ሰው ነው፡፡ ትሁት ሰው ሌላውንም የሚጠቅመውን ነገር ለማድረግ የሚፈልግ ሰው ነው፡፡ ትሁት ሰው ራስ ወዳድ አይደለም፡፡ ትሁት ሰው ለሌላው ጥቅም በትጋት የሚሰራ ሰው ነው፡፡
"እያንዳንዱ ለራሱ የሚጠቅመውን አይመልከት፥ ለባልንጀራው ደግሞ እንጂ" ፊልጵስዩስ 2፡4
ትህትና እንደ ክርስቶስ ራስን አዋርዶ መኖር ነው፡፡ የሰው ትህትና የሚጀምረው ከአሳብ ነው፡፡ ሰው ገና በአሳብ ደረጃ ራሱን ካላዋረደ በትህትና ሊመላለስ አይችልም፡፡ ትሁት ሰው የትህትና መልክ ብቻ ሳይሆን የትህትና ሃሳብና ውሳኔ ያለው ነው፡፡
"በክርስቶስ ኢየሱስ የነበረ ይህ አሳብ በእናንተ ዘንድ ደግሞ ይሁን።" ፊልጵስዩስ 2፡5
ከኢየሱስ የምንማረው ትሁት ሰው ለደረጃ ግድ እንደሌለው ነው፡፡ ትሁት ሰው ስለደረጃ አይጣላም አይጨቃጨቅም፡፡ ትሁት ሰው ትኩረቱ ማገልገል ሰውም መጥቀም በሰው ላይ ዋጋን መጨመር ሰውን ማንሳት ላይ እንጂ ስለስምና ስለስልጣን ወይም ጥቅም አይደለም፡፡ ትሁት ሰው የትም ማገልገል ስለሚችል መቼም ለመውረድ የተዘጋጀ ነው፡፡
"እርሱ በእግዚአብሔር መልክ ሲኖር ሳለ ከእግዚአብሔር ጋር መተካከልን መቀማት እንደሚገባ ነገር አልቈጠረውም፥" ፊልጵስዩስ 2፡6
ትሁት ሰው እግዚአብሔርም እንዲያዋርደው የማያደርግ ቀድሞ ራሱን የሚያዋርድ ነው፡፡ ትሁትን ሰው የምናውቀው ሁኔታ ስላልተመቸው በመዋረዱ ሳይሆን ከፍ የሚያደርግ ሁኔታ እያለ በራሱ ፈቃድ ራሱን የሚያዋርድ ሰው ነው፡፡
ትሁት ሰው ሰዎችን ለመጥቀም በምድር ላይ እንዳለ የሚያውቅ ሰው ሲሆን ሰዎች ሲጠቀሙበት እንደ እድል እንጂ እንደ ሽንፈት የማይቆጥር ሰው ነው፡፡ ትሁት ሰው ሰዎች እንደተጠቀሙበት የሚሰማውን አፍራሽ ስሜት የማይቀበል ሰዎች እንዲጠቀሙበት የሚፈቅድ የባሪያ ልብ ያለው ለራሱ የማይሰስት ሰው ነው፡፡
"ነገር ግን የባሪያን መልክ ይዞ በሰውም ምሳሌ ሆኖ ራሱን ባዶ አደረገ፥" ፊልጵስዩስ 2፡7
ትሁት ሰው ነገሮችን ካደረገ በኋላ ክፍያውን የማይተምን በትህትናው የማይመካ ስላደረገው ስራ ዋጋውን ራሱ የማይተምን ሃላፊነቱን ብቻ እንደተወጠ የሚሰማው ሰው ነው፡፡ ትሁት ሰው ምንጩ እግዚአብሔር እንደሆነ የሚረዳ እንካ በእንካ አገልግሎት የሌለው ሰው ነው፡፡
"እንዲሁ እናንተ ደግሞ የታዘዛችሁትን ሁሉ ባደረጋችሁ ጊዜ፦ የማንጠቅም ባሪያዎች ነን፥ ልናደርገው የሚገባንን አድርገናል በሉ።" ሉቃስ 17፡10
ትሁት ሰው ማንነቱን ጠንቅቆ የተረዳ ፣ ክብሩን የሚያውቅ ፣ የእርሱ ዝቅ ብሎ ማገልገል ምንም እንደማያዋርደው የሚያውቅ ሰው ነው፡፡ ትሁት ሰው በእግዚአብሔር ካለው ክብር እርሱን ሊያዋርደው የሚችል ምንም ነገር እንደሌለ የተረዳ ነው፡፡
"ኢየሱስ አብ ሁሉን በልጁ እንደ ሰጠው ከእግዚአብሔርም እንደ ወጣ ወደ እግዚአብሔርም እንዲሄድ አውቆ፥ ከእራት ተነሣ ልብሱንም አኖረ፥ ማበሻም ጨርቅ ወስዶ ታጠቀ፤ በኋላም በመታጠቢያው ውኃ ጨመረ፥ የደቀ መዛሙርቱንም እግር ሊያጥብና በታጠቀበትም ማበሻ ጨርቅ ሊያብስ ጀመረ።" ዮሐንስ 13፡3-5
ምንጭ:- አብይ ዋቁማ
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍13❤1
. ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“ሰው እግዚአብሔርን ይሰርቃልን? እናንተ ግን እኔን ሰርቃችኋል። እናንተም፦ የሰረቅንህ በምንድር ነው? ብላችኋል። በአሥራትና በበኵራት ነው።”
ሚልክያስ 3፥8
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“ሰው እግዚአብሔርን ይሰርቃልን? እናንተ ግን እኔን ሰርቃችኋል። እናንተም፦ የሰረቅንህ በምንድር ነው? ብላችኋል። በአሥራትና በበኵራት ነው።”
ሚልክያስ 3፥8
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
🔥4👍3
የሐዋርያው ጳውሎስ መልእክቶች የአጻጻፍ ስልት እና ይዘት
10. የብሉይ ኪዳን ቅዱሳት መጻሕፍትን በብዛት መጠቀም
ሐዋርያው ጳውሎስ የመከራከሪያ ነጥቦቹን ለመደገፍ ብዙ ጊዜ የዕብራይስጥ ቅዱሳን ጽሑፎችን ይጠቅስ ወይም ይጠቀም ነበር።
ምሳሌ፡- ሮሜ 4 በእምነት መጽደቅን ለማስረዳት የአብርሃምን ታሪክ ይጠቀማል።
11. መዘርዘር
ጳውሎስ ዝርዝሮችን ለማጉላት እንደ በጎ ምግባር፣ ስለሥጋ ወይም መንፈሳዊ ስጦታዎች ያሉ ነጥቦችን ለማጉላት ተጠቅሟል።
ምሳሌ፦ ገላትያ 5፥22-23 የመንፈስ ፍሬዎችን ይዘረዝራል።
12. ምስጋና እና ጸሎት
አብዛኞቹ ደብዳቤዎቹ የሚጀምሩት ለተቀባዮቹ በምስጋና እና በጸሎት ነው።
ምሳሌ፡- ፊልጵስዩስ 1፥3-11 የምስጋና እና የማበረታቻ ጸሎትን ይጨምራል።
13. ሁለትነት እና ንፅፅር
ጳውሎስ ሕግን ከጸጋን፣ ሥጋን ከመንፈስን፣ እና ሞትን ከሕይወት ጋር ያነጻጽራል።
ምሳሌ፡- ሮሜ 8 እንደ ሥጋ መኖርን እና እንደ መንፈስ ፈቃድ መኖርን ያነጻጽራል።
14. ኪያስመስ (አንድን በተለየ መንገድ መድገም)
ጳውሎስ አንዳንድ ጊዜ የኪያስመስ መዋቅርን ይጠቀም ነበር፣ እሱም ሃሳቦች በመስታወታዊ ቅደም ተከተል (A-B-B-A) ለአጽንዖት ይቀርባሉ።
ምሳሌ፡- በ2ኛ ቆሮንቶስ 4፥8-9፣ የመከራ እና የነጻነት ምሳሌ ኪያስመስ ይፈጥራል።
15. ኢሻቶሎጂካል(የነገረ ፍጻሜ) ትኩረት
የክርስቶስን መምጣት እና የአማኞች የመጨረሻ ተስፋ ላይ በማተኮር ጽፏል።
ምሳሌ፡- 1ኛ ተሰሎንቄ 4፥13-18 ስለ ትንሣኤና ስለ ክርስቶስ ዳግም ምጽአት ይናገራል።
የጳውሎስ ሁለገብ የአጻጻፍ ስልት የተለያዩ አንባቢዎችን በብቃት እንዲደርስ አስችሎታል። ይህም ምሁራዊ ጥልቀትን ከእረኝነት ሙቀት ጋር በማጣመር። ይህ ጥልቀት ጽሑፎቹን ዘላቂ ተጽዕኖ አላብሷቸዋል።
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
10. የብሉይ ኪዳን ቅዱሳት መጻሕፍትን በብዛት መጠቀም
ሐዋርያው ጳውሎስ የመከራከሪያ ነጥቦቹን ለመደገፍ ብዙ ጊዜ የዕብራይስጥ ቅዱሳን ጽሑፎችን ይጠቅስ ወይም ይጠቀም ነበር።
ምሳሌ፡- ሮሜ 4 በእምነት መጽደቅን ለማስረዳት የአብርሃምን ታሪክ ይጠቀማል።
11. መዘርዘር
ጳውሎስ ዝርዝሮችን ለማጉላት እንደ በጎ ምግባር፣ ስለሥጋ ወይም መንፈሳዊ ስጦታዎች ያሉ ነጥቦችን ለማጉላት ተጠቅሟል።
ምሳሌ፦ ገላትያ 5፥22-23 የመንፈስ ፍሬዎችን ይዘረዝራል።
12. ምስጋና እና ጸሎት
አብዛኞቹ ደብዳቤዎቹ የሚጀምሩት ለተቀባዮቹ በምስጋና እና በጸሎት ነው።
ምሳሌ፡- ፊልጵስዩስ 1፥3-11 የምስጋና እና የማበረታቻ ጸሎትን ይጨምራል።
13. ሁለትነት እና ንፅፅር
ጳውሎስ ሕግን ከጸጋን፣ ሥጋን ከመንፈስን፣ እና ሞትን ከሕይወት ጋር ያነጻጽራል።
ምሳሌ፡- ሮሜ 8 እንደ ሥጋ መኖርን እና እንደ መንፈስ ፈቃድ መኖርን ያነጻጽራል።
14. ኪያስመስ (አንድን በተለየ መንገድ መድገም)
ጳውሎስ አንዳንድ ጊዜ የኪያስመስ መዋቅርን ይጠቀም ነበር፣ እሱም ሃሳቦች በመስታወታዊ ቅደም ተከተል (A-B-B-A) ለአጽንዖት ይቀርባሉ።
ምሳሌ፡- በ2ኛ ቆሮንቶስ 4፥8-9፣ የመከራ እና የነጻነት ምሳሌ ኪያስመስ ይፈጥራል።
15. ኢሻቶሎጂካል(የነገረ ፍጻሜ) ትኩረት
የክርስቶስን መምጣት እና የአማኞች የመጨረሻ ተስፋ ላይ በማተኮር ጽፏል።
ምሳሌ፡- 1ኛ ተሰሎንቄ 4፥13-18 ስለ ትንሣኤና ስለ ክርስቶስ ዳግም ምጽአት ይናገራል።
የጳውሎስ ሁለገብ የአጻጻፍ ስልት የተለያዩ አንባቢዎችን በብቃት እንዲደርስ አስችሎታል። ይህም ምሁራዊ ጥልቀትን ከእረኝነት ሙቀት ጋር በማጣመር። ይህ ጥልቀት ጽሑፎቹን ዘላቂ ተጽዕኖ አላብሷቸዋል።
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍6❤4🔥1
በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ ሐዋርያው ጳውሎስ እስር ቤት በነበረበት ወቅት መልእክት ለእነማን ወይም ለማን ላከ?
Anonymous Quiz
9%
ሀ. ገላትያ፣ ሮሜ እና ቆሮንቶስ
15%
ለ. ጢሞቴዎስ፣ ቲቶ እና ፊልሞና
6%
ሐ. ተሰሎንቄ፣ ጢሞቴዎስ እና ቲቶ
53%
መ. ኤፌሶን፣ ፊልጵስዩስ፣ ቆላስይስ እና ፊልሞና
16%
ሠ. ሁሉም
❤7🔥2
. ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“እናንተ ደግሞ ታገሡ፥ ልባችሁንም አጽኑ፤ የጌታ መምጣት ቀርቦአልና።”
ያዕቆብ 5፥8
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“እናንተ ደግሞ ታገሡ፥ ልባችሁንም አጽኑ፤ የጌታ መምጣት ቀርቦአልና።”
ያዕቆብ 5፥8
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤7🔥4👍1
#እራሳችንን_እንመርምር
የነፍስ ድካም እና ዝለት መድኃኒቱ ምን ይሆን? ነፍስን የሚያዝሉ ነገሮችስ የትኞቹ ናቸው?
“በነፍሳችሁ ዝላችሁ እንዳትደክሙ፥ ከኃጢአተኞች በደረሰበት እንዲህ ባለ መቃወም የጸናውን አስቡ።”
ዕብራውያን 12፥3
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የነፍስ ድካም እና ዝለት መድኃኒቱ ምን ይሆን? ነፍስን የሚያዝሉ ነገሮችስ የትኞቹ ናቸው?
“በነፍሳችሁ ዝላችሁ እንዳትደክሙ፥ ከኃጢአተኞች በደረሰበት እንዲህ ባለ መቃወም የጸናውን አስቡ።”
ዕብራውያን 12፥3
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤6👍4
. ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“ዓለም እናንተን ሊጠላ አይቻለውም፤ እኔ ግን ሥራው ክፉ መሆኑን እመሰክርበታለሁና እኔን ይጠላኛል።”
ዮሐንስ 7፥7
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“ዓለም እናንተን ሊጠላ አይቻለውም፤ እኔ ግን ሥራው ክፉ መሆኑን እመሰክርበታለሁና እኔን ይጠላኛል።”
ዮሐንስ 7፥7
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
🔥4❤2
የሃኪሙ ሉቃስ ጹሑፎች የአጻጻፍ ስልት እና ይዘት
በአዲስ ኪዳን የሉቃስ ወንጌል እና የሐዋርያት ሥራ ጸሐፊ ሃኪሙ ሉቃስ፣ በልዩ የአጻጻፍ ስልትና ዘዴዎች ይታወቃል። ሥራዎቹ በሥነ-ጽሑፋዊ ውስብስብነታቸው (አስደናቂ የግሪክ ቋንቋ እውቀቱ)፣ በታሪካዊ ዝርዝርነታቸው፣ በሥነ-መለኮት ጥልቀት እና በሁለንተናዊ እይታ ተለይተው ይታወቃሉ። ከዚህ በታች የእሱን ዘይቤ እና ስልቶች አጠቃላይ እይታ ከቅዱሳት መጻሕፍት እንመለከታለን፦
1. ታሪካዊ እና የምርምር አቀራረብ ዘዴ
የሉቃስ አጻጻፍ ጥንቃቄ የተሞላበት ታሪካዊ ምርምርን ያንጸባርቃል። ብዙ ጊዜ ምንጮችን እና ምስክሮችን ይጠቅሳል፣ ይህም ለትክክለኛነቱ እና ለምርምር እና ጥናት ያለውን ቁርጠኝነት ያሳያል።
ምሳሌ፡- ሉቃስ በወንጌሉ መግቢያ ላይ ጥልቅ ምርምር እና ጥናት እንዳደረገ በግልጽ ተናግሯል።
“የከበርህ ቴዎፍሎስ ሆይ፥ ከመጀመሪያው በዓይን ያዩትና የቃሉ አገልጋዮች የሆኑት እንዳስተላለፉልን፥ በኛ ዘንድ ስለ ተፈጸመው ነገር ብዙዎች ታሪክን በየተራው ለማዘጋጀት ስለ ሞከሩ፥ እኔ ደግሞ ስለ ተማርኸው ቃል እርግጡን እንድታውቅ በጥንቃቄ ሁሉን ከመጀመሪያው ተከትዬ በየተራው ልጽፍልህ መልካም ሆኖ ታየኝ።”
ሉቃስ 1፥1-4
2. የግሪክ ሥነ-ጽሑፍ ዘይቤ አጠቃቀም ዘዴ
ሐኪሙ ሉቃስ በአዳዲስ ቃላት እና መዋቅር የበለፀገ፣ ትምህርቱን እና አንባቢውን የማሳተፍ ችሎታውን የሚያንፀባርቅ ድንቅ የግሪክ ዘይቤን ይጠቀማል።
ምሳሌ፦ ወቅታዊ አረፍተ ነገሮችን መጠቀሙ፣ እንደ መቅድም (ሉቃስ 1፡1-4)፣ የተራቀቀ ድንቅ የግሪክ የአጻጻፍ ስልት ያሳያል።
ይቀጥላል...
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
በአዲስ ኪዳን የሉቃስ ወንጌል እና የሐዋርያት ሥራ ጸሐፊ ሃኪሙ ሉቃስ፣ በልዩ የአጻጻፍ ስልትና ዘዴዎች ይታወቃል። ሥራዎቹ በሥነ-ጽሑፋዊ ውስብስብነታቸው (አስደናቂ የግሪክ ቋንቋ እውቀቱ)፣ በታሪካዊ ዝርዝርነታቸው፣ በሥነ-መለኮት ጥልቀት እና በሁለንተናዊ እይታ ተለይተው ይታወቃሉ። ከዚህ በታች የእሱን ዘይቤ እና ስልቶች አጠቃላይ እይታ ከቅዱሳት መጻሕፍት እንመለከታለን፦
1. ታሪካዊ እና የምርምር አቀራረብ ዘዴ
የሉቃስ አጻጻፍ ጥንቃቄ የተሞላበት ታሪካዊ ምርምርን ያንጸባርቃል። ብዙ ጊዜ ምንጮችን እና ምስክሮችን ይጠቅሳል፣ ይህም ለትክክለኛነቱ እና ለምርምር እና ጥናት ያለውን ቁርጠኝነት ያሳያል።
ምሳሌ፡- ሉቃስ በወንጌሉ መግቢያ ላይ ጥልቅ ምርምር እና ጥናት እንዳደረገ በግልጽ ተናግሯል።
“የከበርህ ቴዎፍሎስ ሆይ፥ ከመጀመሪያው በዓይን ያዩትና የቃሉ አገልጋዮች የሆኑት እንዳስተላለፉልን፥ በኛ ዘንድ ስለ ተፈጸመው ነገር ብዙዎች ታሪክን በየተራው ለማዘጋጀት ስለ ሞከሩ፥ እኔ ደግሞ ስለ ተማርኸው ቃል እርግጡን እንድታውቅ በጥንቃቄ ሁሉን ከመጀመሪያው ተከትዬ በየተራው ልጽፍልህ መልካም ሆኖ ታየኝ።”
ሉቃስ 1፥1-4
2. የግሪክ ሥነ-ጽሑፍ ዘይቤ አጠቃቀም ዘዴ
ሐኪሙ ሉቃስ በአዳዲስ ቃላት እና መዋቅር የበለፀገ፣ ትምህርቱን እና አንባቢውን የማሳተፍ ችሎታውን የሚያንፀባርቅ ድንቅ የግሪክ ዘይቤን ይጠቀማል።
ምሳሌ፦ ወቅታዊ አረፍተ ነገሮችን መጠቀሙ፣ እንደ መቅድም (ሉቃስ 1፡1-4)፣ የተራቀቀ ድንቅ የግሪክ የአጻጻፍ ስልት ያሳያል።
ይቀጥላል...
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤9👍4
. ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“ሁልጊዜ ስለ ሁሉ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም አምላካችንንና አባታችንን ስለ ሁሉ አመስግኑ።”
ኤፌሶን 5፥20
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“ሁልጊዜ ስለ ሁሉ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም አምላካችንንና አባታችንን ስለ ሁሉ አመስግኑ።”
ኤፌሶን 5፥20
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤5👍1
ቅዱሳት መጻሕፍት
ነቢዩ ኤርምያስ ክፍል-፯ በኤርምያስ ዘመን ግብረ ገባዊ ዝቅጠት በሰፊው የተሠራጨ ሲሆን፣ ኢፍትሓዊነትም በዚያው ልክ ተስፋፍቶ ነበር (5፥1-9፤ 7 ፥ 1-11 ፤ 23 ፥ 10-14)፡፡ ካህናትና ነቢያት እንደ ሌሎቹ አይሁድ ጥፋተኞች ነበሩ (6፥ 13-15)፡፡ ሆኖም ሕዝቡ ሃይማኖታዊ ሥርዐትን ፈጸሙ፡፡ እግዚአብሔር ግን በዚህ ውጫዊ ሥርዐት ከቊጣው የሚመለስ አልነበረም::…
ነቢዩ ኤርምያስ
ክፍል-፰
መሲሓዊ ትንቢትን በተመለከተም ኤርምያስ መሲሓዊውን ጊዜ በዝርዝር አይገልጽም፡፡ የመሲሑ ማንነት በመጽሐፉ ላይ በጒልሕ አልተመለከተም፡፡ ይሁን እንጂ ኤርምያስ አንዳንድ ፋይዳ ያላቸውን መሲሓውያን ምንባቦች ይሰጣል ፡-
1. ከኪዳኑ ታቦት የላቀ የእግዚአብሔር መገለጥ እውን እንድሚሆን መታወጁ (3፥14-17)
2. የዐዲሱ ኪዳን መገለጥ (31፥31-34)
3. የዳዊት ኪዳን ፍጻሜ ላይ ከመድረሱ ጋር ተያይዞ (33 ፥ 14- 26) የሙሴ ውብ ሐሳብ እውን መሆን (ዘፀ 19፥6)፡፡
የትንቢተ ኤርምያስ ዘላቂ ፋይዳ የሚገኘው በዐዲስ ኪዳን ውስጥ ያሉትን ይዘቶች (በአርባና በኀምሳ ቤት ውስጥ ይገኛሉ፤ በዮሐንስ ራእይ ላይ ከግማሽ በላይ ይገኛሉ) ኢርቱዕ በሆነ መልክ በመግለጽ ብቻ ሳይሆን፣ ከእግዚአብሔር ጋር ስላለው ግንኙነት ለማወቅ ድንቅ የሆነ መማሪያ መጽሐፍ በመሆኑ ነው፡፡ በብሉይ ኪዳን ውስጥ ከዚህ ላይ የግል እምነት ከፍተኛ ደረጃ ላይ ደርሶ ይገኛል፤ እንዲሁም በዳዊት ሥርወ መንግሥት ውስጥ (23፥1-8፤ 33፥ 14-18) የካህንነትንና የንጉሥነትን ምንነት ለመረዳት እውነተኛ መንገድ በመሆኑ ነው፡፡ በምዕራፍ 30-33 ላይ ለሕዝቡ ብሩህ ተስፋዎች በብዛት መገኘታቸው የመጽሐፍ ቅዱስ ሊቃውንት ይህን ክፍል “የመጽናናት መጽሐፍ” እስከ ማለት አበቃቸው፡፡ በኤርምያስ ትንቢት ውስጥ በእጅጉ ዝነኛ የሆነው ምንባብ ስለ ዐዲሱ ኪዳን ይናገራል (31፥31-34):: ይህም የሚናገረው እስራኤል በቦታዋ ስለ መመለሷ እንጂ ስለ ግለ ሰባዊ ትንሣኤ አይደለም፡፡
ኤርምያስ እንደ ሌሎቹ የብሉይ ኪዳን ነቢያት ባለመሆኑ፣ ጽሑፉም ከሕይወቱና ከሐሳቡ ጋር የተሳሰረ በመሆኑ፣ የእርሱ ትንቢት ተማሪ የሆነ ሰው የዚህን የእግዚአብሐር ሰው ውስጣዊ ሕይወትና ባሕርያት በጥልቅ ማጤን ይኖርበታል፤ ከእነዚህም አንዳንዶቹ ቀደም ሲል በመጠኑ ተዳስሰዋል፡፡ ከተፈጥሮኣዊ ችሎታዎቹ፣ ከጥልቅ ስሜቶቹ (ውስጣዊ ስሜቶቹ)፣ ከተነሣሽነቱ፣ ከጌታ ጋር ስላለው የግል ግንኙነት ገጽታዎች በተጨማሪ፣ የኤርምያስ ንስሓዎች ተብለው የሚጠሩ፣ ከጌታ ጋር ያደረጋቸው ውይይቶች በጠላቶች ላይ ያወረዳቸው ርግማኖችና በተለይ የጸሎት ሕይወቱ ይገኛሉ፡፡ ልቡንና መንፈሳዊ መሻቶቹን እንደ እርሱ የገለጠ የብሉይ ኪዳን ነቢይ የለም፡፡ ጨዋና ፈሪ ቢሆንም እንኳ (አንዳንዶች በእርሱ ላይ እንደ ለጠፉት ግን ከቶ ሴታሴት አልነበረም፣ ከእግዚአብሔር ጥሪና እግዚአብሔር ከሰጠው ዐደራ የተነሣ ለተግባሩ በጽኑ የቆመ ሰው ነበር፡፡ ከዐላማው ሊነቃነቅ አልቻለም፡፡ በይሁዳ ውስጥ እንደ እርሱ ያለ አገሩን የሚወድ ሰው አልነበረም፤ ይሁን እንጂ የይሁዳን ኀጢአት አይቶ እንዳላየ ለማለፍ አወላውሎ ከቶ አያውቅም᎓᎓ ሕይወቱ የብቸኛና የገለልተኛ ሕይወት ነበር፤ የሰውን ኅብረትና ፍቅር ቢናፍቅም እንኳ በሕይወቱ ዘመን ሁሉ ቤተ ሰውና የቅርብ ወዳጆች አልነበሩትም:: ለወገኞቹ ጥልቅ ፍቅር ቢኖረውም እንኳ ሥቃያቸውንና ብሔራዊ ጥፋታቸውን ይፋ ያደርግ ዘንድ በመለኮት ዐደራ ተሰጥቶት ነበር፡፡ ከእግዚአብሔር ጋር የነበረው ኅብረት የተለየ ጥልቀትና ቅርርብ ነበረው፡፡ አንዳንድ ጊዜ ይህን ያህል ግልጽ በመሆኑ፣ በዘመናችን የሚገኙት አያሌ የእርሱ መጽሐፍ ተማሪዎች ይህማ እግዚአብሔርን እንደ መሳደብ ወይም ተገቢውን ክብር እንደ መንፈግ የሚቈጠር ነው ከማለት አድርሷቸዋል፡፡
ይቀጥላል...
ምንጭ፦ የብሉይ ኪዳን ማብራሪያ፤ ገጽ 827-828
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ክፍል-፰
መሲሓዊ ትንቢትን በተመለከተም ኤርምያስ መሲሓዊውን ጊዜ በዝርዝር አይገልጽም፡፡ የመሲሑ ማንነት በመጽሐፉ ላይ በጒልሕ አልተመለከተም፡፡ ይሁን እንጂ ኤርምያስ አንዳንድ ፋይዳ ያላቸውን መሲሓውያን ምንባቦች ይሰጣል ፡-
1. ከኪዳኑ ታቦት የላቀ የእግዚአብሔር መገለጥ እውን እንድሚሆን መታወጁ (3፥14-17)
2. የዐዲሱ ኪዳን መገለጥ (31፥31-34)
3. የዳዊት ኪዳን ፍጻሜ ላይ ከመድረሱ ጋር ተያይዞ (33 ፥ 14- 26) የሙሴ ውብ ሐሳብ እውን መሆን (ዘፀ 19፥6)፡፡
የትንቢተ ኤርምያስ ዘላቂ ፋይዳ የሚገኘው በዐዲስ ኪዳን ውስጥ ያሉትን ይዘቶች (በአርባና በኀምሳ ቤት ውስጥ ይገኛሉ፤ በዮሐንስ ራእይ ላይ ከግማሽ በላይ ይገኛሉ) ኢርቱዕ በሆነ መልክ በመግለጽ ብቻ ሳይሆን፣ ከእግዚአብሔር ጋር ስላለው ግንኙነት ለማወቅ ድንቅ የሆነ መማሪያ መጽሐፍ በመሆኑ ነው፡፡ በብሉይ ኪዳን ውስጥ ከዚህ ላይ የግል እምነት ከፍተኛ ደረጃ ላይ ደርሶ ይገኛል፤ እንዲሁም በዳዊት ሥርወ መንግሥት ውስጥ (23፥1-8፤ 33፥ 14-18) የካህንነትንና የንጉሥነትን ምንነት ለመረዳት እውነተኛ መንገድ በመሆኑ ነው፡፡ በምዕራፍ 30-33 ላይ ለሕዝቡ ብሩህ ተስፋዎች በብዛት መገኘታቸው የመጽሐፍ ቅዱስ ሊቃውንት ይህን ክፍል “የመጽናናት መጽሐፍ” እስከ ማለት አበቃቸው፡፡ በኤርምያስ ትንቢት ውስጥ በእጅጉ ዝነኛ የሆነው ምንባብ ስለ ዐዲሱ ኪዳን ይናገራል (31፥31-34):: ይህም የሚናገረው እስራኤል በቦታዋ ስለ መመለሷ እንጂ ስለ ግለ ሰባዊ ትንሣኤ አይደለም፡፡
ኤርምያስ እንደ ሌሎቹ የብሉይ ኪዳን ነቢያት ባለመሆኑ፣ ጽሑፉም ከሕይወቱና ከሐሳቡ ጋር የተሳሰረ በመሆኑ፣ የእርሱ ትንቢት ተማሪ የሆነ ሰው የዚህን የእግዚአብሐር ሰው ውስጣዊ ሕይወትና ባሕርያት በጥልቅ ማጤን ይኖርበታል፤ ከእነዚህም አንዳንዶቹ ቀደም ሲል በመጠኑ ተዳስሰዋል፡፡ ከተፈጥሮኣዊ ችሎታዎቹ፣ ከጥልቅ ስሜቶቹ (ውስጣዊ ስሜቶቹ)፣ ከተነሣሽነቱ፣ ከጌታ ጋር ስላለው የግል ግንኙነት ገጽታዎች በተጨማሪ፣ የኤርምያስ ንስሓዎች ተብለው የሚጠሩ፣ ከጌታ ጋር ያደረጋቸው ውይይቶች በጠላቶች ላይ ያወረዳቸው ርግማኖችና በተለይ የጸሎት ሕይወቱ ይገኛሉ፡፡ ልቡንና መንፈሳዊ መሻቶቹን እንደ እርሱ የገለጠ የብሉይ ኪዳን ነቢይ የለም፡፡ ጨዋና ፈሪ ቢሆንም እንኳ (አንዳንዶች በእርሱ ላይ እንደ ለጠፉት ግን ከቶ ሴታሴት አልነበረም፣ ከእግዚአብሔር ጥሪና እግዚአብሔር ከሰጠው ዐደራ የተነሣ ለተግባሩ በጽኑ የቆመ ሰው ነበር፡፡ ከዐላማው ሊነቃነቅ አልቻለም፡፡ በይሁዳ ውስጥ እንደ እርሱ ያለ አገሩን የሚወድ ሰው አልነበረም፤ ይሁን እንጂ የይሁዳን ኀጢአት አይቶ እንዳላየ ለማለፍ አወላውሎ ከቶ አያውቅም᎓᎓ ሕይወቱ የብቸኛና የገለልተኛ ሕይወት ነበር፤ የሰውን ኅብረትና ፍቅር ቢናፍቅም እንኳ በሕይወቱ ዘመን ሁሉ ቤተ ሰውና የቅርብ ወዳጆች አልነበሩትም:: ለወገኞቹ ጥልቅ ፍቅር ቢኖረውም እንኳ ሥቃያቸውንና ብሔራዊ ጥፋታቸውን ይፋ ያደርግ ዘንድ በመለኮት ዐደራ ተሰጥቶት ነበር፡፡ ከእግዚአብሔር ጋር የነበረው ኅብረት የተለየ ጥልቀትና ቅርርብ ነበረው፡፡ አንዳንድ ጊዜ ይህን ያህል ግልጽ በመሆኑ፣ በዘመናችን የሚገኙት አያሌ የእርሱ መጽሐፍ ተማሪዎች ይህማ እግዚአብሔርን እንደ መሳደብ ወይም ተገቢውን ክብር እንደ መንፈግ የሚቈጠር ነው ከማለት አድርሷቸዋል፡፡
ይቀጥላል...
ምንጭ፦ የብሉይ ኪዳን ማብራሪያ፤ ገጽ 827-828
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍5❤1