ከቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ ስለሮሜ መጽሐፍ ታሪካዊ ዳራ ትክክል ያልሆነው የቱ ነው?
Anonymous Quiz
26%
ሀ. መጽሐፉ የተጻፈው ቆሮንቶስ ከተማ ውስጥ ነው።
17%
ለ. በዘመኑ ቀላውዴዎስ ቄሳር አይሁድን ከሮም እንዲወጡ አዞ ነበር።
31%
ሐ. መልእክቱን ለሮም ቤተክርስቲያን ያመጣችሁ ዲያቆኗ ፌቨን ናት
25%
መ. መልእክቱ የተጻፈ በጳውሎስ በሁለተኛው የወንጌል ጉዞ ነው
. ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“በእሽቅድምድም ስፍራ የሚሮጡት፥ ሁሉ እንዲሮጡ ነገር ግን አንዱ ብቻ ዋጋውን እንዲቀበል አታውቁምን? እንዲሁም ታገኙ ዘንድ ሩጡ።”
1ኛ ቆሮንቶስ 9፥24
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“በእሽቅድምድም ስፍራ የሚሮጡት፥ ሁሉ እንዲሮጡ ነገር ግን አንዱ ብቻ ዋጋውን እንዲቀበል አታውቁምን? እንዲሁም ታገኙ ዘንድ ሩጡ።”
1ኛ ቆሮንቶስ 9፥24
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍5
#ከተማ_ወይም_ቦታ_በቅዱሳት_መጻሕፍት
#ሰሊሆም
ሰሊሆም ማለት የተላከ ማለት ነው። ኢየሱስ የዕውሩን ዓይን በጭቃ ከቀባ በኋላ «ሂድና ታጠብ» ብሎ ወደ ሰሊሆም ላከው፤ ዮሐ 9፡6-7። ለመጠመቂያ የሚሆን ውሃ የተጠራቀመበት ኩሬ። ከኢየሩሳሌም በደቡብ በኩል ዖፊል በተባለው ጎጥ ሥር ይገኛል። ሕዝቅያስ ውሃውን ከግዮን ምንጭ በቦይ ወደዚህ አስገብቶታል። በፊት በኢየሩሳሌም ቅጥር ውስጥ ነበር። ዛሬ ግን በኋላ ከተሠራው ቅጥር ውጭ ነው፤ ኢሳ. 22፥9-11። በብሉይ ኪዳን በተለይም በኢሳይያስ 8፥6 መሠረት ሰሊሆም ጸጥ ብለው በሚፈሱ ምንጮች የተከማቹ ሲሆኑ፣ እነዚህ ምንጮች ኢየሩሳሌም በጠላት በምትከበብበት ጊዜ ሁሉ የሚያገለግሉ በመሬት ውስጥ የሚሄዱ ስውር ውሆች ናቸው፡፡ እነዚህም ወኪሎች በሆኑት ነገሥታት ማለትም ፈሪሃ እግዚአብሔር የነበራቸው ከዳዊት ዘር በሆኑት ነገሥታት በኩል እግዚአብሔር በቸርነቱና በበረከቱ እስራኤልን በሰላምና በጸጥታ የሚገዛበትን ሁኔታ በምሳሌነት የሚገልጹ ናቸው፡፡
ምንጭ፦ የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት፤ ገጽ 71፣ ምሉእ ሕይወት፤ ገጽ 1014
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
#ሰሊሆም
ሰሊሆም ማለት የተላከ ማለት ነው። ኢየሱስ የዕውሩን ዓይን በጭቃ ከቀባ በኋላ «ሂድና ታጠብ» ብሎ ወደ ሰሊሆም ላከው፤ ዮሐ 9፡6-7። ለመጠመቂያ የሚሆን ውሃ የተጠራቀመበት ኩሬ። ከኢየሩሳሌም በደቡብ በኩል ዖፊል በተባለው ጎጥ ሥር ይገኛል። ሕዝቅያስ ውሃውን ከግዮን ምንጭ በቦይ ወደዚህ አስገብቶታል። በፊት በኢየሩሳሌም ቅጥር ውስጥ ነበር። ዛሬ ግን በኋላ ከተሠራው ቅጥር ውጭ ነው፤ ኢሳ. 22፥9-11። በብሉይ ኪዳን በተለይም በኢሳይያስ 8፥6 መሠረት ሰሊሆም ጸጥ ብለው በሚፈሱ ምንጮች የተከማቹ ሲሆኑ፣ እነዚህ ምንጮች ኢየሩሳሌም በጠላት በምትከበብበት ጊዜ ሁሉ የሚያገለግሉ በመሬት ውስጥ የሚሄዱ ስውር ውሆች ናቸው፡፡ እነዚህም ወኪሎች በሆኑት ነገሥታት ማለትም ፈሪሃ እግዚአብሔር የነበራቸው ከዳዊት ዘር በሆኑት ነገሥታት በኩል እግዚአብሔር በቸርነቱና በበረከቱ እስራኤልን በሰላምና በጸጥታ የሚገዛበትን ሁኔታ በምሳሌነት የሚገልጹ ናቸው፡፡
ምንጭ፦ የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት፤ ገጽ 71፣ ምሉእ ሕይወት፤ ገጽ 1014
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤7👍3
. ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“እንደ ሥጋ ፈቃድ የሚኖሩ የሥጋን ነገር ያስባሉና፥ እንደ መንፈስ ፈቃድ የሚኖሩ ግን የመንፈስን ነገር ያስባሉ።”
ሮሜ 8፥5
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“እንደ ሥጋ ፈቃድ የሚኖሩ የሥጋን ነገር ያስባሉና፥ እንደ መንፈስ ፈቃድ የሚኖሩ ግን የመንፈስን ነገር ያስባሉ።”
ሮሜ 8፥5
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍8❤2
የብሉይ ኪዳን ማብራሪያ.pdf
23.3 MB
👉ርዕስ፦ የብሉይ ኪዳን ማብራሪያ፣
ከ "ZONDERVAN NIV
BIBLE COMMENTARY VOLUME 1: Old Testamen" የተተረጎመ
🗣ተርጓሚዎች፦ ምንሊክ አስፋው፣ ንጉሤ ቡልቻ፣ ተጋፋው ትርፌ፣ ሰሎሞን ጥላሁን፣ ናሁሠናይ አፈወርቅ፣ ፍትሐ አምላክ እንየው፣ ደርበው አዱኛ፣ መስፍን ታዬ፣ ቁምላቸው ፋንታሁን፣ ዮናስ አስፋው፣ ፍሥሓ ፈይሣ፣ ተስፋዬ መስፍን፣ ወርቁ ኤጀሬ እና ቴዎፍሎስ ቀነዓ ናቸው፡፡
✍አርታዕያን፦ ንጉሤ ቡልቻ፣ ናሁሠናይ አፈወርቅ፣ ሰሎሞን ጥላሁን፣ ደርበው አዱኛ፣ ምንሊክ አስፋው እና ፍሥሓ ፈይሣ
📝ዋና አርታዒ ፦ ፍትሐ አምላክ እንየው ናቸው፡፡
🖨አሳታሚ፦ ራዕይ አሳታሚ
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ከ "ZONDERVAN NIV
BIBLE COMMENTARY VOLUME 1: Old Testamen" የተተረጎመ
🗣ተርጓሚዎች፦ ምንሊክ አስፋው፣ ንጉሤ ቡልቻ፣ ተጋፋው ትርፌ፣ ሰሎሞን ጥላሁን፣ ናሁሠናይ አፈወርቅ፣ ፍትሐ አምላክ እንየው፣ ደርበው አዱኛ፣ መስፍን ታዬ፣ ቁምላቸው ፋንታሁን፣ ዮናስ አስፋው፣ ፍሥሓ ፈይሣ፣ ተስፋዬ መስፍን፣ ወርቁ ኤጀሬ እና ቴዎፍሎስ ቀነዓ ናቸው፡፡
✍አርታዕያን፦ ንጉሤ ቡልቻ፣ ናሁሠናይ አፈወርቅ፣ ሰሎሞን ጥላሁን፣ ደርበው አዱኛ፣ ምንሊክ አስፋው እና ፍሥሓ ፈይሣ
📝ዋና አርታዒ ፦ ፍትሐ አምላክ እንየው ናቸው፡፡
🖨አሳታሚ፦ ራዕይ አሳታሚ
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤5👍5
ከቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ ብዙ ቁጥሮችን የያዘው መጽሐፍ የቱ ነው? (ጥያቄው ስለምዕራፍ ቁጥር አይደለም)
Anonymous Quiz
6%
ሀ. ኦሪት ዘፍጥረት
3%
ለ. ኦሪት ዘኁልቊ
72%
ሐ. መዝሙረ ዳዊት
2%
መ. የዮሐንስ ራእይ
15%
ሠ. ትንቢተ ኢሳይያስ
2%
ረ. ኦሪት ዘጸአት
👍4❤1
. ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“አካሄድን እንደ ቃልህ አቅና፤ ኃጢአትም ሁሉ አይግዛኝ።”
መዝሙር 119፥133
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“አካሄድን እንደ ቃልህ አቅና፤ ኃጢአትም ሁሉ አይግዛኝ።”
መዝሙር 119፥133
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍3
ቅዱሳት መጻሕፍት
ነቢዩ ኤርምያስ ክፍል-፮ ነገር ግን መጨረሻው ሩቅ አልነበረም:: በዘጠነኛው የአገዛዝ ዘመኑ (588)፣ ሴዴቅያስ ከፈርዖን ኡፍራ ጋር ግምባር በመግጠም በናቡከደነፆር ላይ ዐመፀ:: ባቢሎን ይሁዳን በመውረር ምላሽ ሰጥታ በ586 ከተማዋ በእጇ ስትወድቅ ወረራው ፍጻሜ ላይ ደረሰ (2ነገ 36፥17፤ ኤር 38 ፥ 28-39፥ 10)፡፡ በወረራው ዘመን ሁሉ ሴዴቅያስ…
ነቢዩ ኤርምያስ
ክፍል-፯
በኤርምያስ ዘመን ግብረ ገባዊ ዝቅጠት በሰፊው የተሠራጨ ሲሆን፣ ኢፍትሓዊነትም በዚያው ልክ ተስፋፍቶ ነበር (5፥1-9፤ 7 ፥ 1-11 ፤ 23 ፥ 10-14)፡፡ ካህናትና ነቢያት እንደ ሌሎቹ አይሁድ ጥፋተኞች ነበሩ (6፥ 13-15)፡፡ ሆኖም ሕዝቡ ሃይማኖታዊ ሥርዐትን ፈጸሙ፡፡ እግዚአብሔር ግን በዚህ ውጫዊ ሥርዐት ከቊጣው የሚመለስ አልነበረም:: ኤርምያስ ከፍርድ ሊያመልጡ እንደማይችሉ ሰበከ፡፡ እግዚአብሔር ድርቅን፣ ረኃብንና የውጭ ወራሪዎችን ቀደም ሲል ተጠቅሞአል (14፥1-6፤ 4 ፥ 11-22) ፤ ከዚያም በናቡከደነፆር በኩል የመጨረሻ ጒብኝቱን ያካሂዳል (25፥9)፡፡ ይሁን እንጂ የእግዚአብሔር ፍቅርና ለኪዳኑ ያለው ታማኝነት ፍርዱ አጥፊ ወይም የመጨረሻ እንዲሆን አያደርጉም:: የወደፊት ተስፋ ነበር፡፡ ከባቢሎን ምርኮ መመለስ እውን እንደሚሆንና (25፥11፤ 29፥10) ባቢሎን ራሷ እንደምትጠፋ (ምዕራፍ 50-51) ኤርምያስ አስቀድሞ ተናገረ፡፡ የእስራኤልን ተስፋ ተጨባጭ መገለጥ ለመስጠት አለወላወለም (32፥1-5)::
ኤርምያስ ለአሕዛብም አገልግሎት ነበረው፡፡ በዚያ ዘመን ለነበሩት ሁናቴዎች ናቡከደነፆር የእግዚአብሔር መሣሪያ መሆኑን አየ (27፥ 6)፡ ፤ ሌሎች ሕዝቦች ናቡከደነፆርን እንዳይቃወሙትም አስጠነቀቀ (27፥1-11)፡፡ ሕዝቡ ሁሉ በጽድቅ እንዲጓዝ በእግዚአብሔር ስም ጥሪ አቀረበ (ምዕራፍ 46-51)፡፡ እግዚአብሔር ለሰዎች ሁሉ ደኅንነት ግድ ያለው መሆኑን በመግለጽም ድምፁን አሰማ (29፥ 1-14 በተለይ ቊጥር 7)፡፡
በኤርምያስ አገልግሎት ውስጥ የነበረው ዐቢይ አጽንዖት፣ ከማንኛውም ነገር ይልቅ መንፈሳዊ ጒዳዩ የላቀ መሆኑ ነው፡፡ የይሁዳ እምነት ጊዜያዊ ገጽታ የቱን ያህል ዝቅተኛ መሆኑን አስተዋለ፡፡ የእምነት ብጤዎቹ ቀጥሎ የተመለከቱትን ይበጅ ብለው መያዛቸውንም አየ፤
(1) የጌታን ኪዳን በአፍኣዊ መልኩ መቀበል (11፥1-5)፣
(2) ግዝረት (9 ፥ 25-26)
(3) ቤተ መቅደሱ (7፥1-15)፣
(4) የመሥዋዕት ሥርዐት (6፥20፤ 7፥21-23)፣
(5) የሙሴን ሕግ በውጫዊ መልኩ መቀበል (8፥8)፣
(6) የሐሰት ትንቢት (2 ፥ 39-40)፣
(7) ጸሎት (11 ፥ 14 ፤ 15፥ 1)፣
(8) ዙፋኑ (22 ፥ 1-9)፣ እናም
(9) ታቦቱ (3፥16)፡፡
ከማንኛውም ነቢይ ይልቅ ኤርምያስ ስለ ንስሓ አብዝቶ ሰበከ፡፡ በማንኛውም ጊዜ ያሳስበው የነበረ ዋና ጒዳይ የእያንዳንዱ ሰው (የግለሰቡ) የልብ ሁናቴ ነበር፡፡ የዐዲሱ ኪዳን ገለጻው (ትንታኔው) በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ በእጅጉ ድንቅ ነው (31 ፥ 31-34)፡፡ ይህ እውነት በጌታችን ሥራ ላይ የቱን ያህል ዘልቆ እንደ ገባ ዐዲስ ኪዳን ያሳያል፡፡
ኤርምያስ በሩቅ ስላለው ስለ ወደፊቱ ወቅት የተነበየው እስራኤል በንስሓ ወደ ጌታ እንደምትመለስ ነው (32 ፥ 37-40)፡፡ መሲሕ በፍትሕና በጽድቅ በእርሷ ላይ ይነግሣል (23፥5-8)፡፡ በዚያን ጊዜ የሕዝቡ ትሩፋን በረከትን ያገኛሉ (3፥17፤ 16፥19)፡፡
ይቀጥላል...
ምንጭ፦ የብሉይ ኪዳን ማብራሪያ፤ ገጽ 827
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ክፍል-፯
በኤርምያስ ዘመን ግብረ ገባዊ ዝቅጠት በሰፊው የተሠራጨ ሲሆን፣ ኢፍትሓዊነትም በዚያው ልክ ተስፋፍቶ ነበር (5፥1-9፤ 7 ፥ 1-11 ፤ 23 ፥ 10-14)፡፡ ካህናትና ነቢያት እንደ ሌሎቹ አይሁድ ጥፋተኞች ነበሩ (6፥ 13-15)፡፡ ሆኖም ሕዝቡ ሃይማኖታዊ ሥርዐትን ፈጸሙ፡፡ እግዚአብሔር ግን በዚህ ውጫዊ ሥርዐት ከቊጣው የሚመለስ አልነበረም:: ኤርምያስ ከፍርድ ሊያመልጡ እንደማይችሉ ሰበከ፡፡ እግዚአብሔር ድርቅን፣ ረኃብንና የውጭ ወራሪዎችን ቀደም ሲል ተጠቅሞአል (14፥1-6፤ 4 ፥ 11-22) ፤ ከዚያም በናቡከደነፆር በኩል የመጨረሻ ጒብኝቱን ያካሂዳል (25፥9)፡፡ ይሁን እንጂ የእግዚአብሔር ፍቅርና ለኪዳኑ ያለው ታማኝነት ፍርዱ አጥፊ ወይም የመጨረሻ እንዲሆን አያደርጉም:: የወደፊት ተስፋ ነበር፡፡ ከባቢሎን ምርኮ መመለስ እውን እንደሚሆንና (25፥11፤ 29፥10) ባቢሎን ራሷ እንደምትጠፋ (ምዕራፍ 50-51) ኤርምያስ አስቀድሞ ተናገረ፡፡ የእስራኤልን ተስፋ ተጨባጭ መገለጥ ለመስጠት አለወላወለም (32፥1-5)::
ኤርምያስ ለአሕዛብም አገልግሎት ነበረው፡፡ በዚያ ዘመን ለነበሩት ሁናቴዎች ናቡከደነፆር የእግዚአብሔር መሣሪያ መሆኑን አየ (27፥ 6)፡ ፤ ሌሎች ሕዝቦች ናቡከደነፆርን እንዳይቃወሙትም አስጠነቀቀ (27፥1-11)፡፡ ሕዝቡ ሁሉ በጽድቅ እንዲጓዝ በእግዚአብሔር ስም ጥሪ አቀረበ (ምዕራፍ 46-51)፡፡ እግዚአብሔር ለሰዎች ሁሉ ደኅንነት ግድ ያለው መሆኑን በመግለጽም ድምፁን አሰማ (29፥ 1-14 በተለይ ቊጥር 7)፡፡
በኤርምያስ አገልግሎት ውስጥ የነበረው ዐቢይ አጽንዖት፣ ከማንኛውም ነገር ይልቅ መንፈሳዊ ጒዳዩ የላቀ መሆኑ ነው፡፡ የይሁዳ እምነት ጊዜያዊ ገጽታ የቱን ያህል ዝቅተኛ መሆኑን አስተዋለ፡፡ የእምነት ብጤዎቹ ቀጥሎ የተመለከቱትን ይበጅ ብለው መያዛቸውንም አየ፤
(1) የጌታን ኪዳን በአፍኣዊ መልኩ መቀበል (11፥1-5)፣
(2) ግዝረት (9 ፥ 25-26)
(3) ቤተ መቅደሱ (7፥1-15)፣
(4) የመሥዋዕት ሥርዐት (6፥20፤ 7፥21-23)፣
(5) የሙሴን ሕግ በውጫዊ መልኩ መቀበል (8፥8)፣
(6) የሐሰት ትንቢት (2 ፥ 39-40)፣
(7) ጸሎት (11 ፥ 14 ፤ 15፥ 1)፣
(8) ዙፋኑ (22 ፥ 1-9)፣ እናም
(9) ታቦቱ (3፥16)፡፡
ከማንኛውም ነቢይ ይልቅ ኤርምያስ ስለ ንስሓ አብዝቶ ሰበከ፡፡ በማንኛውም ጊዜ ያሳስበው የነበረ ዋና ጒዳይ የእያንዳንዱ ሰው (የግለሰቡ) የልብ ሁናቴ ነበር፡፡ የዐዲሱ ኪዳን ገለጻው (ትንታኔው) በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ በእጅጉ ድንቅ ነው (31 ፥ 31-34)፡፡ ይህ እውነት በጌታችን ሥራ ላይ የቱን ያህል ዘልቆ እንደ ገባ ዐዲስ ኪዳን ያሳያል፡፡
ኤርምያስ በሩቅ ስላለው ስለ ወደፊቱ ወቅት የተነበየው እስራኤል በንስሓ ወደ ጌታ እንደምትመለስ ነው (32 ፥ 37-40)፡፡ መሲሕ በፍትሕና በጽድቅ በእርሷ ላይ ይነግሣል (23፥5-8)፡፡ በዚያን ጊዜ የሕዝቡ ትሩፋን በረከትን ያገኛሉ (3፥17፤ 16፥19)፡፡
ይቀጥላል...
ምንጭ፦ የብሉይ ኪዳን ማብራሪያ፤ ገጽ 827
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍8❤1
. ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“ጌታ እግዚአብሔር ሆይ፥ ታላቅነትህን የጸናችውንም እጅህን ለእኔ ለባሪያህ ማሳየት ጀምረሃል፤ በሰማይና በምድርም እንደ ሥራህ እንደ ኃይልህም ይሠራ ዘንድ የሚችል አምላክ ማን ነው?”
ዘዳግም 3፥24
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“ጌታ እግዚአብሔር ሆይ፥ ታላቅነትህን የጸናችውንም እጅህን ለእኔ ለባሪያህ ማሳየት ጀምረሃል፤ በሰማይና በምድርም እንደ ሥራህ እንደ ኃይልህም ይሠራ ዘንድ የሚችል አምላክ ማን ነው?”
ዘዳግም 3፥24
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤3👍2
#የእግዚአብሔር_ቃል_ምን_ይላል?
ሉቃስ 12
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
³⁵ ወገባችሁ የታጠቀ መብራታችሁም የበራ ይሁን፤
³⁶ እናንተም ጌታቸው መጥቶ ደጁን ሲያንኳኳ ወዲያው እንዲከፍቱለት ከሰርግ እስኪመለስ ድረስ የሚጠብቁ ሰዎችን ምሰሉ፤
³⁷ ጌታቸው በመጣ ጊዜ ሲተጉ የሚያገኛቸው እነዚያ ባሪያዎች ብፁዓን ናቸው፤ እውነት እላችኋለሁ፥ ታጥቆ በማዕድ ያስቀምጣቸዋል ቀርቦም ያገለግላቸዋል።
³⁸ ከሌሊቱም በሁለተኛው ወይም በሦስተኛው ክፍል መጥቶ እንዲሁ ቢያገኛቸው፥ እነዚያ ባሪያዎች ብፁዓን ናቸው።
³⁹ ይህን ግን እወቁ ባለቤት በምን ሰዓት ሌባ እንዲመጣ ቢያውቅ ኖሮ፥ በነቃ፥ ቤቱም እንዲቆፈር ባልፈቀደም ነበር።
⁴⁰ እናንተ ደግሞ ተዘጋጅታችሁ ኑሩ፥ የሰው ልጅ በማታስቡበት ሰዓት ይመጣልና።
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ሉቃስ 12
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
³⁵ ወገባችሁ የታጠቀ መብራታችሁም የበራ ይሁን፤
³⁶ እናንተም ጌታቸው መጥቶ ደጁን ሲያንኳኳ ወዲያው እንዲከፍቱለት ከሰርግ እስኪመለስ ድረስ የሚጠብቁ ሰዎችን ምሰሉ፤
³⁷ ጌታቸው በመጣ ጊዜ ሲተጉ የሚያገኛቸው እነዚያ ባሪያዎች ብፁዓን ናቸው፤ እውነት እላችኋለሁ፥ ታጥቆ በማዕድ ያስቀምጣቸዋል ቀርቦም ያገለግላቸዋል።
³⁸ ከሌሊቱም በሁለተኛው ወይም በሦስተኛው ክፍል መጥቶ እንዲሁ ቢያገኛቸው፥ እነዚያ ባሪያዎች ብፁዓን ናቸው።
³⁹ ይህን ግን እወቁ ባለቤት በምን ሰዓት ሌባ እንዲመጣ ቢያውቅ ኖሮ፥ በነቃ፥ ቤቱም እንዲቆፈር ባልፈቀደም ነበር።
⁴⁰ እናንተ ደግሞ ተዘጋጅታችሁ ኑሩ፥ የሰው ልጅ በማታስቡበት ሰዓት ይመጣልና።
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍6❤1
በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ ጳውሎስ እና ሲላስ በእስር ቤት ሆነው እግዚአብሔርን ሲያመሰግኑ የወኅኒው መሠረት የተናወጠበት ከተማ የት ነበር?
Anonymous Quiz
15%
ሀ. ኤፌሶን
30%
ለ. ፊልጵስዩስ
11%
ሐ. ቆሮንቶስ
7%
መ. ተሰሎንቄ
37%
ሠ. አቴና
👍9
. ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“ጽድቅን የሚያደርገውን በመንገዶችህም የሚያስቡህን ትገናኛቸዋለህ። እነሆ፥ አንተ ተቈጣህ እኛም ኃጢአት ሠራን ስለዚህም ተሳሳትን።”
ኢሳይያስ 64፥5
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“ጽድቅን የሚያደርገውን በመንገዶችህም የሚያስቡህን ትገናኛቸዋለህ። እነሆ፥ አንተ ተቈጣህ እኛም ኃጢአት ሠራን ስለዚህም ተሳሳትን።”
ኢሳይያስ 64፥5
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤4🔥2👍1
#እራሳችንን_እንመርምር
በሕይወት ዘመናችን መመካታችን እና እምነታችን ምን ላይ እንዲሆን እንሻለን? ምንደሰተው እና ልባችን በሐሴት የሚሞላው ምን አይነት ሰው ስናይ ነው?
“ነፍሴ በእግዚአብሔር ትከብራለች፥ ገሮችም ሰምተው ደስ ይላቸዋል።”
መዝሙር 34፥2
“በቃልህ ታምኛለሁና የሚፈሩህ እኔን አይተው ደስ ይላቸዋል።”
መዝሙር 119፥74
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
በሕይወት ዘመናችን መመካታችን እና እምነታችን ምን ላይ እንዲሆን እንሻለን? ምንደሰተው እና ልባችን በሐሴት የሚሞላው ምን አይነት ሰው ስናይ ነው?
“ነፍሴ በእግዚአብሔር ትከብራለች፥ ገሮችም ሰምተው ደስ ይላቸዋል።”
መዝሙር 34፥2
“በቃልህ ታምኛለሁና የሚፈሩህ እኔን አይተው ደስ ይላቸዋል።”
መዝሙር 119፥74
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍2👏1😁1
. ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“የሥጋንም ሰውነት በመገፈፍ፥ በክርስቶስ መገረዝ፥ በእጅ ባልተደረገ መገረዝ በእርሱ ሆናችሁ ደግሞ ተገረዛችሁ፤”
ቆላስይስ 2፥11
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“የሥጋንም ሰውነት በመገፈፍ፥ በክርስቶስ መገረዝ፥ በእጅ ባልተደረገ መገረዝ በእርሱ ሆናችሁ ደግሞ ተገረዛችሁ፤”
ቆላስይስ 2፥11
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍6
የሐዋርያው ጳውሎስ መልእክቶች የአጻጻፍ ስልት እና ይዘት
ሐዋርያው ጳውሎስ የተለያዩ የአጻጻፍ ስልቶችን እና ቴክኒኮችን በመልእክቶቹ ውስጥ ተጠቅሟል፣ ይህም ትምህርቱን፣ የራሱን ባህላዊ ነባራዊ ሁኔታ እና የጻፈላቸውን የተለያዩ የመልእክቱ ተቀባዮቹን ሁኔታ የሚያንጸባርቅ ነበር። የተጠቀመባቸው ቁልፍ መንገዶች እና ዘዴዎች እነሆ፦
1. ዶክትሪን እና ሥነ-መለኮታዊ ጹሑፍ
ጳውሎስ ውስብስብ ሥነ-መለኮታዊ ሃሳቦችን በተለይም ስለ ድነት፣ ጸጋ፣ መጽደቅ እና እምነት ለማብራራት ብዙ ጊዜ ጽፏል።
ምሳሌ፡- ሮሜ ስለ ኃጢአት፣ ድነት እና የእግዚአብሔር ጽድቅ ስልታዊ ሥነ-መለኮታዊ ሙግቶችን ይዟል።
2. የግል እና መጋቢያዊ ቃና ያለው ድምጽ
ለአንባቢዎቹ እውነተኛ እንክብካቤ እና ፍቅር አሳይቷል፣ ብዙ ጊዜ “ወንድሞች እና እህቶች” ብሎ ይጠራቸዋል።
ምሳሌ፡- በ1ኛ ተሰሎንቄ ውስጥ፣ ጳውሎስ አማኞችን አመስግኗል እናም እነርሱን ለመጎብኘት ያለውን ጉጉት ገልጿል።
3. ሪቶሪካል ጥያቄዎች
ሪቶሪካል ጥያቄዎች "rhetorical question" ማለት መልሱ ምን እንደሆነ እየታወቀ መልስ እንዲመለስ ሳይሆን በአንባቢው ወይንም በሰሚዎቹ አእምሮ ውስጥ ጥያቄ ከስቶ ለማሰላሰል የሚገፋፋ ነው። ሀሳብን ለመቀስቀስ እና አንባቢዎችን ለማሳተፍ የአጻጻፍ ጥያቄዎችን ተጠቅሟል።
ምሳሌ፦ ሮሜ 6፡1፡ "እንግዲህ ምን እንላለን? ጸጋ እንዲበዛ በኃጢአት እንኑርን?"
4. አመክንዮአዊ ሙግት
ጳውሎስ አድማጮቹን ለማሳመን አመክንዮ በመጠቀም ሙግቶቹን በጥንቃቄ አዘጋጀ።
ምሳሌ፦ ገላትያ በዘዴ ይሟገታል በህግ ላይ ለድነት መታመንን እና በክርስቶስ ያለውን እምነት አጽንዖት ይሰጣል።
ይቀጥላል...
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ሐዋርያው ጳውሎስ የተለያዩ የአጻጻፍ ስልቶችን እና ቴክኒኮችን በመልእክቶቹ ውስጥ ተጠቅሟል፣ ይህም ትምህርቱን፣ የራሱን ባህላዊ ነባራዊ ሁኔታ እና የጻፈላቸውን የተለያዩ የመልእክቱ ተቀባዮቹን ሁኔታ የሚያንጸባርቅ ነበር። የተጠቀመባቸው ቁልፍ መንገዶች እና ዘዴዎች እነሆ፦
1. ዶክትሪን እና ሥነ-መለኮታዊ ጹሑፍ
ጳውሎስ ውስብስብ ሥነ-መለኮታዊ ሃሳቦችን በተለይም ስለ ድነት፣ ጸጋ፣ መጽደቅ እና እምነት ለማብራራት ብዙ ጊዜ ጽፏል።
ምሳሌ፡- ሮሜ ስለ ኃጢአት፣ ድነት እና የእግዚአብሔር ጽድቅ ስልታዊ ሥነ-መለኮታዊ ሙግቶችን ይዟል።
2. የግል እና መጋቢያዊ ቃና ያለው ድምጽ
ለአንባቢዎቹ እውነተኛ እንክብካቤ እና ፍቅር አሳይቷል፣ ብዙ ጊዜ “ወንድሞች እና እህቶች” ብሎ ይጠራቸዋል።
ምሳሌ፡- በ1ኛ ተሰሎንቄ ውስጥ፣ ጳውሎስ አማኞችን አመስግኗል እናም እነርሱን ለመጎብኘት ያለውን ጉጉት ገልጿል።
3. ሪቶሪካል ጥያቄዎች
ሪቶሪካል ጥያቄዎች "rhetorical question" ማለት መልሱ ምን እንደሆነ እየታወቀ መልስ እንዲመለስ ሳይሆን በአንባቢው ወይንም በሰሚዎቹ አእምሮ ውስጥ ጥያቄ ከስቶ ለማሰላሰል የሚገፋፋ ነው። ሀሳብን ለመቀስቀስ እና አንባቢዎችን ለማሳተፍ የአጻጻፍ ጥያቄዎችን ተጠቅሟል።
ምሳሌ፦ ሮሜ 6፡1፡ "እንግዲህ ምን እንላለን? ጸጋ እንዲበዛ በኃጢአት እንኑርን?"
4. አመክንዮአዊ ሙግት
ጳውሎስ አድማጮቹን ለማሳመን አመክንዮ በመጠቀም ሙግቶቹን በጥንቃቄ አዘጋጀ።
ምሳሌ፦ ገላትያ በዘዴ ይሟገታል በህግ ላይ ለድነት መታመንን እና በክርስቶስ ያለውን እምነት አጽንዖት ይሰጣል።
ይቀጥላል...
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍9❤1
. ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“እናንተ በጌታ ጸንታችሁ ብትቆሙ፥ አሁን በሕይወት እንኖራለንና።”
1ኛ ተሰሎንቄ 3፥8
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“እናንተ በጌታ ጸንታችሁ ብትቆሙ፥ አሁን በሕይወት እንኖራለንና።”
1ኛ ተሰሎንቄ 3፥8
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤9🔥1
የአዲስ ኪዳን ማብራሪያ.pdf
55.3 MB
👉ርዕስ፦ የአዲስ ኪዳን ማብራሪያ
The Applied New Testament Commentary by Thomas Hale ከሚለው የተወሰደ
🗣ተርጓሚ፦ መስፍን ተስፋዬ፣ ተስፋዬ መስፍን፣ ምንሊክ አስፋውና ቴዎድሮስ በየነ ናቸው።
✏️ዋና ኦርታኢ፦ ደረጀ በቀለ ሲሆኑ ሰሎሞን ጥላሁንም አግዘዋል።
🖨አሳታሚ፦ ራዕይ አሳታሚ
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
The Applied New Testament Commentary by Thomas Hale ከሚለው የተወሰደ
🗣ተርጓሚ፦ መስፍን ተስፋዬ፣ ተስፋዬ መስፍን፣ ምንሊክ አስፋውና ቴዎድሮስ በየነ ናቸው።
✏️ዋና ኦርታኢ፦ ደረጀ በቀለ ሲሆኑ ሰሎሞን ጥላሁንም አግዘዋል።
🖨አሳታሚ፦ ራዕይ አሳታሚ
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤5👍5
በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ በዮሐንስ ራእይ ከሰባቱ አብያተ ክርስቲያናት መካከል አንድም ነቀፋ ያልቀረበበት ቤተ ክርስቲያን የቱ ነው?
Anonymous Quiz
33%
ሀ. ፊላደልፊያ
8%
ለ. ጴርጋሞን
13%
ሐ. ሰምርኔስ
7%
መ. ሰርዴስ
12%
ሠ. ኤፌሶን
11%
ረ. ሀ እና መ
17%
ሰ. ሀ እና ሐ
👍2🔥2
. ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“ዘመኑ ቀርቦአልና የሚያነበው፥ የትንቢቱን ቃል የሚሰሙትና በውስጡ የተጻፈውን የሚጠብቁት ብፁዓን ናቸው።”
ራእይ 1፥3
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“ዘመኑ ቀርቦአልና የሚያነበው፥ የትንቢቱን ቃል የሚሰሙትና በውስጡ የተጻፈውን የሚጠብቁት ብፁዓን ናቸው።”
ራእይ 1፥3
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤4🔥3👍1