ትምህርተ እግዚአብሔር.pdf
18.9 MB
👉ርዕስ፦ ትምህርተ እግዚአብሔር
✍ጸሐፊ፦ በቄስ ኮሊንስ ማንሰል
ስለ መጽሐፉ፦
አጠቃላይ የነገረ መለኮት ትምህርት
ትምህርተ እግዚአብሔር 1ኛ መጽሐፍ
በውስጡ ያሉ ጥናቶች፦
👉ጥናት 1. ትምህርተ አስተርእዮ
👉ጥናት 2. ትምህርተ ባሕርየ እግዚአብሔር
👉ጥናት 3. ትምህርተ ፍጥረት
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
✍ጸሐፊ፦ በቄስ ኮሊንስ ማንሰል
ስለ መጽሐፉ፦
አጠቃላይ የነገረ መለኮት ትምህርት
ትምህርተ እግዚአብሔር 1ኛ መጽሐፍ
በውስጡ ያሉ ጥናቶች፦
👉ጥናት 1. ትምህርተ አስተርእዮ
👉ጥናት 2. ትምህርተ ባሕርየ እግዚአብሔር
👉ጥናት 3. ትምህርተ ፍጥረት
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍4❤1
በእስራኤል ነገሥታት ታሪክ ብቸኛዋ ሴት ገዢ ንግሥት ማን ናት?
Anonymous Quiz
59%
ሀ. ዲቦራ
5%
ለ. ኢያዔል
19%
ሐ. ጎቶልያ
9%
መ. ቤርሳቤህ
8%
ሠ. አቢግያ
👍4
. ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“ስለዚህ የተወደዳችሁ ወንድሞቼ ሆይ፤ ጸንታችሁ ቁሙ፤ በምንም ነገር አትናወጡ። ለጌታ ሥራ ዘወትር የምትተጉ ሁኑ፤ ምክንያቱም ለጌታ የምትደክሙት በከንቱ እንዳልሆነ ታውቃላችሁ።”
1ኛ ቆሮንቶስ 15፥58 (አዲሱ መ.ት)
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“ስለዚህ የተወደዳችሁ ወንድሞቼ ሆይ፤ ጸንታችሁ ቁሙ፤ በምንም ነገር አትናወጡ። ለጌታ ሥራ ዘወትር የምትተጉ ሁኑ፤ ምክንያቱም ለጌታ የምትደክሙት በከንቱ እንዳልሆነ ታውቃላችሁ።”
1ኛ ቆሮንቶስ 15፥58 (አዲሱ መ.ት)
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍4❤1
ቅዱሳት መጻሕፍት
ነቢዩ ኤርምያስ ክፍል-፭ በኢዮአቄም የዐሥራ አንድ ዓመት ዘመነ መንግሥት ውስጥ የከርከሚሽ ጦርነት ተካሄደ (ከ46 ፥ 2 ጋር ያነጻ)፡፡ በመካከለኛው ምሥራቅ የኀይል ሚዛን ከግብፅ ወደ ባቢሎን መተላለፉን ያመላከተ ስለ ሆነ፣ ዘላቂ ፋይዳ ያለው ሁኔታ (ክሥተት) ነበር፡፡ ይህ ሽንፈት በግብፅ የመስፋፋት ምኞት ላይ የመጨረሻ በትር ሲሆን፤ ከለዳውያን በምዕራቡ…
ነቢዩ ኤርምያስ
ክፍል-፮
ነገር ግን መጨረሻው ሩቅ አልነበረም:: በዘጠነኛው የአገዛዝ ዘመኑ (588)፣ ሴዴቅያስ ከፈርዖን ኡፍራ ጋር ግምባር በመግጠም በናቡከደነፆር ላይ ዐመፀ:: ባቢሎን ይሁዳን በመውረር ምላሽ ሰጥታ በ586 ከተማዋ በእጇ ስትወድቅ ወረራው ፍጻሜ ላይ ደረሰ (2ነገ 36፥17፤ ኤር 38 ፥ 28-39፥ 10)፡፡ በወረራው ዘመን ሁሉ ሴዴቅያስ እጁን ይሰጥ ዘንድ ኤርምያስ አደፋፈረው (21 ፥ 1-10 ፤ 34፥ 1-5፤ 17-22 37 ፥ 3-10፤ 16-17 ፤ 38፥ 14-23)፡፡ በአንድ ወቅት የግብፅ ሰራዊት እየገፋ መምጣት፣ የባቢሎንን ተዋጊ ሰራዊት ያፈገፍግ ዘንድ አስገደደው፤ ይሁን እንጂ ወረራው ተመልሶ ቀጠለ (37 ፥ 1-10)፡፡ በዚህም ጊዜ ሴዴቅያስ ፍርሀት ያደረበት ሰው ስለ ነበር፣ ኤርምያስ በይሁዳ በሚገኙት ጠላቶቹ ግፍ ደረሰበት (37 ፥ 11-21፤ ምዕ 38)፡፡ በዚህ ወቅት ኢየሩሳሌም የወደቀችበት ዕለት፣ በዓለም ዙሪያ በሚገኙ አይሁድ ዘንድ፣ በአቢብ ወር በዘጠነኛው ቀን በሐዘን የሚታሰብ ሲሆን፣ በብሉይ ኪዳን ውስጥ በእስራኤል ላይ ከፍተኛው የእግዚአብሔር ፍርድ ነበር፡፡ ሴዴቅያስ ለማምለጥ ሲሞክር ተያዘ፤ ወንዶች ልጆቹም ዐይኑ እያየ በፊቱ ታረዱ፤ ዐይኑም ወጣ፤ ከዚያም ከተከታዮቹ ጋር ወደ ባቢሎን ተጋዘ፡፡
ከከተማዪቱና ከቤተ መቅደሱ ውድመት በኋላ የባቢሎን ንጉሥ፣ ጎዶልያስን የይሁዳ ገዥ አድርጎ ሾመው፡፡ ከጥቂት ጊዜ በኋላ (በቂ ማስረጃ በሌለበት ሦስት ወር ወይም ጥቂት ዓመታት ሊሆን ይችላል)፣ ጎዶልያስ ከዳዊት ቤት በሆነው ወገን ተገደለ፤ ይህም አፍቃሬ ግብፅ በሆኑት ሰዎች ቀስቃሽነት ሳይፈጸም አልቀረም፡፡ የብርቱው መከራ ሰለባዎች የሆኑት የባቢሎንን የዐመፅ ምላሽ በመፍራት ኤርምያስንና ባሮክን ዐብረዋቸው እንዲሸሹ በማስገደድ ወደ ግብፅ ወረዱ፡፡ ስለዚህ ከምእት ዓመታት በፊት በሙሴ አማካይነት ከፈርዖን ትድግና የተገኘበት ዑደት በዚህ ጊዜ ፍጻሜ ላይ ደረሰ፡፡ ሌላው የሚያስገርመው ጒዳይ ደግሞ በአገልግሎቱ ዘመን ሁሉ በግብፅ ላይ እንዳይታመኑ ሲመክር የነበረው ኤርምያስ ያለፈቃዱ የምድር ሕይወቱን በዚያ እንዲጨርስ መደረጉ ነው፡፡ ስለዚህ በእስራኤል ውስጥ ዐይነተኛ ዘመን የነበረው መለኮታዊ አገዛዝ አከተመ፡፡ በሴሎ የማደሪያው ድንኳን መውደሙም የመሳፍንትን ዘመን ደመደመው፡፡ የሰሎሞን ቤተ መቅደስ መውደም በእስራኤል ዘንድ የንጉሣዊ አገዛዝ ዘመን ማክተሙን አመለከተ፡፡ በቲቶ (ጥጦስ) ዘመን (70 ዓ.ም.) ሁለተኛው ቤተ መቅደስ መውደሙ እስከ ዐዲሱ ዘመን ድረስ እስራኤል በምድሯ ላይ የምትኖርበት ዘመን በአደገኛ ሁኔታ ማክተሙን አመላካች ነበር፡፡
ነገረ መለኮታዊ አጽንዖት
የኤርምያስ መልእክት ጒሉሓን ባሕርያት፣ ለእርሱ ዘመንና ለእኛ ዘመን ዐቢይ ፋይዳ አላቸው፡፡ ኤርምያስ በዕድሜ ዘመኑ ሁሉ የደረሰበትን ሐዘንና ተቃውሞ ለመዝለቅ የበቃው በእግዚአብሔርና እግዚአብሔር በሰጠው ተስፋ ጽኑ እምነት ስለ ነበረው ነው (18+7! 29:14: 32:1-5):: የሕይወቱም የአገልግሎቱም ሁለት ትኲረቶች እግዚአብሔር (ማለት ቸርነቱ፣ በሰው ዘር ላይ ያለው ባለቤትነቱ፣ ንስሓና እምነት እውን ይሆኑ ዘንድ ግድ መሰኘቱ) እና ተንከራታች ሕዝቡ ሲሆኑ፣ ይህም የሥጋዊና የመንፈሳዊ ሕይወታቸውን ደኅንነት ያካትታል፡፡
ኤርምያስ እግዚአብሔር የፍጥረት ሁሉ አምላክ መሆኑን በማመን (27፥5)፣ ስለ እግዚአብሔር ከፍ ያለ ሐሳብ አለው፡፡ የአሕዛብ አማልክት ህልውና የላቸውም (10፥11 (በአራማይስጥ ቋንቋ መጽሐፍ ውስጥ ብቸኛ ጥቅስ ነው)፤ 14 14፥ 22)፡፡ እግዚአብሔር የሰውን ልብ ክፋት ያውቃል (17፥9-10)፤ ይሁን እንጂ በእርሱ ላይ የሚታመኑትን ለመባረክ በመናፈቅ (17 ፥ 7) ሕዝቡን በጥልቅ ይወዳል (31፥1-3)፡፡ የጣዖት አምልኮና ልበ ደንዳናነት እንዲሁም ንስሓ አልባ አገልግሎት በእርሱ ፊት አስጸያፊዎች ናቸው (19:4-6 14፥12)፡፡ እግዚአብሔርን ሕይወት በሌላቸው ጣዖታት ከመወከል የበለጠ በእርሱ ላይ የሚሰነዘር ስድብ የለም፡፡ ኤርምያስ ያለመታከት በመቃወም ስብከት ያቀረበበት ልዩ ኀጢአት የጣዖት አምልኮ ነበር፡፡ ሦስት ዐይነት ሐሰት አስቈጣው፡-
(1) ንስሓ ይገባ ዘንድ የተደረገውን ጥሪ ሁሉ አልቀበልም እያለ ምንም አልሆንም የሚል ዐመፀኛ የሆነ ከንቱ ዋስትና፣
(2) ሕዝቡን በአደገኛ አስተማማኝነት እንዲሸፈኑ ያደረጉ የሐሰት ነቢያት፣
(3) ጣዖታትን በከንቱ ማምለክ፡፡ አምልኮ ለበኣል፣ ለሞሎክና ለሰማይ ንግሥት (ለኢሽታር) ይደረግ ነበር፡፡ የእነዚህ አማልክት ምስል በቤተ መቅደስ ውስጥ ሳይቀር ተቀምጦ ነበር (32፥34፤ ከ7፥31 ፤ ከ19፥5፤ ከ32 ፥ 35፤ ከ44፥18-19)፡፡
ይቀጥላል...
🚨ማሳሰቢያ የጊዜ አቆጣጠር ካልተጠቀሰ በቀር ዓመተ ቅድመ ክርስቶስ ነው።
ምንጭ፦ የብሉይ ኪዳን ማብራሪያ፤ ገጽ 826
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ክፍል-፮
ነገር ግን መጨረሻው ሩቅ አልነበረም:: በዘጠነኛው የአገዛዝ ዘመኑ (588)፣ ሴዴቅያስ ከፈርዖን ኡፍራ ጋር ግምባር በመግጠም በናቡከደነፆር ላይ ዐመፀ:: ባቢሎን ይሁዳን በመውረር ምላሽ ሰጥታ በ586 ከተማዋ በእጇ ስትወድቅ ወረራው ፍጻሜ ላይ ደረሰ (2ነገ 36፥17፤ ኤር 38 ፥ 28-39፥ 10)፡፡ በወረራው ዘመን ሁሉ ሴዴቅያስ እጁን ይሰጥ ዘንድ ኤርምያስ አደፋፈረው (21 ፥ 1-10 ፤ 34፥ 1-5፤ 17-22 37 ፥ 3-10፤ 16-17 ፤ 38፥ 14-23)፡፡ በአንድ ወቅት የግብፅ ሰራዊት እየገፋ መምጣት፣ የባቢሎንን ተዋጊ ሰራዊት ያፈገፍግ ዘንድ አስገደደው፤ ይሁን እንጂ ወረራው ተመልሶ ቀጠለ (37 ፥ 1-10)፡፡ በዚህም ጊዜ ሴዴቅያስ ፍርሀት ያደረበት ሰው ስለ ነበር፣ ኤርምያስ በይሁዳ በሚገኙት ጠላቶቹ ግፍ ደረሰበት (37 ፥ 11-21፤ ምዕ 38)፡፡ በዚህ ወቅት ኢየሩሳሌም የወደቀችበት ዕለት፣ በዓለም ዙሪያ በሚገኙ አይሁድ ዘንድ፣ በአቢብ ወር በዘጠነኛው ቀን በሐዘን የሚታሰብ ሲሆን፣ በብሉይ ኪዳን ውስጥ በእስራኤል ላይ ከፍተኛው የእግዚአብሔር ፍርድ ነበር፡፡ ሴዴቅያስ ለማምለጥ ሲሞክር ተያዘ፤ ወንዶች ልጆቹም ዐይኑ እያየ በፊቱ ታረዱ፤ ዐይኑም ወጣ፤ ከዚያም ከተከታዮቹ ጋር ወደ ባቢሎን ተጋዘ፡፡
ከከተማዪቱና ከቤተ መቅደሱ ውድመት በኋላ የባቢሎን ንጉሥ፣ ጎዶልያስን የይሁዳ ገዥ አድርጎ ሾመው፡፡ ከጥቂት ጊዜ በኋላ (በቂ ማስረጃ በሌለበት ሦስት ወር ወይም ጥቂት ዓመታት ሊሆን ይችላል)፣ ጎዶልያስ ከዳዊት ቤት በሆነው ወገን ተገደለ፤ ይህም አፍቃሬ ግብፅ በሆኑት ሰዎች ቀስቃሽነት ሳይፈጸም አልቀረም፡፡ የብርቱው መከራ ሰለባዎች የሆኑት የባቢሎንን የዐመፅ ምላሽ በመፍራት ኤርምያስንና ባሮክን ዐብረዋቸው እንዲሸሹ በማስገደድ ወደ ግብፅ ወረዱ፡፡ ስለዚህ ከምእት ዓመታት በፊት በሙሴ አማካይነት ከፈርዖን ትድግና የተገኘበት ዑደት በዚህ ጊዜ ፍጻሜ ላይ ደረሰ፡፡ ሌላው የሚያስገርመው ጒዳይ ደግሞ በአገልግሎቱ ዘመን ሁሉ በግብፅ ላይ እንዳይታመኑ ሲመክር የነበረው ኤርምያስ ያለፈቃዱ የምድር ሕይወቱን በዚያ እንዲጨርስ መደረጉ ነው፡፡ ስለዚህ በእስራኤል ውስጥ ዐይነተኛ ዘመን የነበረው መለኮታዊ አገዛዝ አከተመ፡፡ በሴሎ የማደሪያው ድንኳን መውደሙም የመሳፍንትን ዘመን ደመደመው፡፡ የሰሎሞን ቤተ መቅደስ መውደም በእስራኤል ዘንድ የንጉሣዊ አገዛዝ ዘመን ማክተሙን አመለከተ፡፡ በቲቶ (ጥጦስ) ዘመን (70 ዓ.ም.) ሁለተኛው ቤተ መቅደስ መውደሙ እስከ ዐዲሱ ዘመን ድረስ እስራኤል በምድሯ ላይ የምትኖርበት ዘመን በአደገኛ ሁኔታ ማክተሙን አመላካች ነበር፡፡
ነገረ መለኮታዊ አጽንዖት
የኤርምያስ መልእክት ጒሉሓን ባሕርያት፣ ለእርሱ ዘመንና ለእኛ ዘመን ዐቢይ ፋይዳ አላቸው፡፡ ኤርምያስ በዕድሜ ዘመኑ ሁሉ የደረሰበትን ሐዘንና ተቃውሞ ለመዝለቅ የበቃው በእግዚአብሔርና እግዚአብሔር በሰጠው ተስፋ ጽኑ እምነት ስለ ነበረው ነው (18+7! 29:14: 32:1-5):: የሕይወቱም የአገልግሎቱም ሁለት ትኲረቶች እግዚአብሔር (ማለት ቸርነቱ፣ በሰው ዘር ላይ ያለው ባለቤትነቱ፣ ንስሓና እምነት እውን ይሆኑ ዘንድ ግድ መሰኘቱ) እና ተንከራታች ሕዝቡ ሲሆኑ፣ ይህም የሥጋዊና የመንፈሳዊ ሕይወታቸውን ደኅንነት ያካትታል፡፡
ኤርምያስ እግዚአብሔር የፍጥረት ሁሉ አምላክ መሆኑን በማመን (27፥5)፣ ስለ እግዚአብሔር ከፍ ያለ ሐሳብ አለው፡፡ የአሕዛብ አማልክት ህልውና የላቸውም (10፥11 (በአራማይስጥ ቋንቋ መጽሐፍ ውስጥ ብቸኛ ጥቅስ ነው)፤ 14 14፥ 22)፡፡ እግዚአብሔር የሰውን ልብ ክፋት ያውቃል (17፥9-10)፤ ይሁን እንጂ በእርሱ ላይ የሚታመኑትን ለመባረክ በመናፈቅ (17 ፥ 7) ሕዝቡን በጥልቅ ይወዳል (31፥1-3)፡፡ የጣዖት አምልኮና ልበ ደንዳናነት እንዲሁም ንስሓ አልባ አገልግሎት በእርሱ ፊት አስጸያፊዎች ናቸው (19:4-6 14፥12)፡፡ እግዚአብሔርን ሕይወት በሌላቸው ጣዖታት ከመወከል የበለጠ በእርሱ ላይ የሚሰነዘር ስድብ የለም፡፡ ኤርምያስ ያለመታከት በመቃወም ስብከት ያቀረበበት ልዩ ኀጢአት የጣዖት አምልኮ ነበር፡፡ ሦስት ዐይነት ሐሰት አስቈጣው፡-
(1) ንስሓ ይገባ ዘንድ የተደረገውን ጥሪ ሁሉ አልቀበልም እያለ ምንም አልሆንም የሚል ዐመፀኛ የሆነ ከንቱ ዋስትና፣
(2) ሕዝቡን በአደገኛ አስተማማኝነት እንዲሸፈኑ ያደረጉ የሐሰት ነቢያት፣
(3) ጣዖታትን በከንቱ ማምለክ፡፡ አምልኮ ለበኣል፣ ለሞሎክና ለሰማይ ንግሥት (ለኢሽታር) ይደረግ ነበር፡፡ የእነዚህ አማልክት ምስል በቤተ መቅደስ ውስጥ ሳይቀር ተቀምጦ ነበር (32፥34፤ ከ7፥31 ፤ ከ19፥5፤ ከ32 ፥ 35፤ ከ44፥18-19)፡፡
ይቀጥላል...
🚨ማሳሰቢያ የጊዜ አቆጣጠር ካልተጠቀሰ በቀር ዓመተ ቅድመ ክርስቶስ ነው።
ምንጭ፦ የብሉይ ኪዳን ማብራሪያ፤ ገጽ 826
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤3👍3👏1
በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ "ነቢይ" ተብሎ የተጠራው ሰው ማን?
Anonymous Quiz
15%
ሀ. ኤልያስ
31%
ለ. አብርሃም
8%
ሐ. ኖኅ
36%
መ. ሙሴ
8%
ሠ. ኢሳይያስ
2%
ረ. ዳዊት
👍7
. ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“እርሱ ግን ስለ ኃጢአት አንድን መሥዋዕት ለዘላለም አቅርቦ በእግዚአብሔር ቀኝ ተቀመጠ፥”
ዕብራውያን 10፥12
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“እርሱ ግን ስለ ኃጢአት አንድን መሥዋዕት ለዘላለም አቅርቦ በእግዚአብሔር ቀኝ ተቀመጠ፥”
ዕብራውያን 10፥12
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍4
በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ ንጉሡ ዳዊት ሲነግስ ለመጀመሪያ ጊዜ የነገሰው የት ነበር?
Anonymous Quiz
15%
ሀ. ኢየሩሳሌም
18%
ለ. ቤተልሔም
17%
ሐ. ሴሎ
41%
መ. ኬብሮን
9%
ሠ. ቤቴል
👍4
#እራሳችንን_እንመርምር
ነገ ስናስብ ተራራ የሚያሳክልብንና በጭንቅ የሚወረን ለነገ ያለን መመካት ነው። ዛሬ ነገ ላይ ይኖራሉ ያልናቸው ነገሮች ላይኖሩ እንደሚችሉ ምን ያክሎቻችን በእርግጥ እናውቀዋለን? ዛሬ ላይ ሆነን፣ ነገ አልታየኝም ማለት ነገ ይጨልማል ያለው ማን ነው?
“ቀን የሚያመጣውን ምን እንደ ሆነ አታውቅምና ነገ በሚሆነው አትመካ።”
ምሳሌ 27፥1
“ራሳችሁን ከፍቅረ ንዋይ ጠብቁ፤ ባላችሁ ነገር ረክታችሁ ኑሩ፤ ምክንያቱም እግዚአብሔር፣ “ከቶ አልተውህም፤ በፍጹም አልጥልህም” ብሎአል።”
ዕብራውያን 13፥5 (አዲሱ መ.ት)
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ነገ ስናስብ ተራራ የሚያሳክልብንና በጭንቅ የሚወረን ለነገ ያለን መመካት ነው። ዛሬ ነገ ላይ ይኖራሉ ያልናቸው ነገሮች ላይኖሩ እንደሚችሉ ምን ያክሎቻችን በእርግጥ እናውቀዋለን? ዛሬ ላይ ሆነን፣ ነገ አልታየኝም ማለት ነገ ይጨልማል ያለው ማን ነው?
“ቀን የሚያመጣውን ምን እንደ ሆነ አታውቅምና ነገ በሚሆነው አትመካ።”
ምሳሌ 27፥1
“ራሳችሁን ከፍቅረ ንዋይ ጠብቁ፤ ባላችሁ ነገር ረክታችሁ ኑሩ፤ ምክንያቱም እግዚአብሔር፣ “ከቶ አልተውህም፤ በፍጹም አልጥልህም” ብሎአል።”
ዕብራውያን 13፥5 (አዲሱ መ.ት)
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍4
. ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“ቅጥር እንደሌላት እንደ ፈረሰች ከተማ፥ መንፈሱን የማይከለክል ሰው እንዲሁ ነው።”
ምሳሌ 25፥28
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“ቅጥር እንደሌላት እንደ ፈረሰች ከተማ፥ መንፈሱን የማይከለክል ሰው እንዲሁ ነው።”
ምሳሌ 25፥28
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤2
የጠጣር ልብ አደገኛ ውጤቶች
የምንኖርበት ጊዜ ልባችንን ልያጠጥር ስለሚችል ከመቼውም ጊዜ በበለጠ ልባችንን በትኩረት መከታተል አለብን ፡፡
በአንድ ሌሊት አይከሰትም። አንድ ሰው ከእግዚአብሔር ጋር በንቁ ጉዞ ሊኖር ይችላል ከዚያም ቀስ በቀስ ወደ ደረቅነት ወደ ሚቀዘቅዘው ይሸጋገራል፡፡ ትክክል የሆነውን ያውቃሉ ፡፡ ግን ከእንግዲህ ግድ የላቸውም ፡፡ ግዴለሽነት ልባቸውን ይገዛል። የሌላውን ችግር እንደራስ በቀላሉ ማግኘት አይቻልም። በአንድ ወቅት እምነት ጠንካራ እና ንቁ ነበር ፣ መቀዝቀዝ ፣ ጥርጣሬ እና ነቀፋ ወረረዉ፡፡ ልጅ-መሰል እምነት ይቀልጣል እናም እንቅፋትን ይታገሱታል።
ልብን መለወጥ እንዴት ከባድ ነው ጠንካራ ልብን ማዳበር የምንችልባቸው የተለያዩ መንገዶች አሉ ፣ ግን ሁለት ዋናዎች መጥቀስ ተገቢ ነው-
1. እዉነትን መስማት ግን ተግባራዊ አለማድረግ፡፡
ጠንካራ ልብ በቀላሉ ሊያድግ ከሚችልበት አንድ ትልቁ መንገድ ምን ማድረግ እንዳለብን ስናውቅ እርምጃ ሳንወስድ ስንቀር ነው፡፡ የምንኖረው ከማንኛውም የበለጠ እውቀት እና ማስተዋል በሚገኝበት ትውልድ ውስጥ ነው። ሁልጊዜ እውነትን ለመስማት እድል አለን ፡፡ ችግሩ ፣ ብዙ እንሰማለን ፣ ግን በጣም ትንሽ ነገር ላይ እርምጃ እንወስዳለን፡፡
እኛ በታላላቅ አስተማሪዎች ተከብበናል ፣ ግን ብዙዎች ስለእሱ ምንም አያደርጉም ፣ ይህም ውሎ አድሮ ጠንካራ እና ቀዝቃዛ ወደ ሆነው ልብ እንዲያድጉ ያደርጋቸዋል ፡፡
ብዙዎች የሆነ ነገር በመስማታቸው ምክንያት “እናዉቃለን” ብለው በማሰብ ተታለዋል ። ግን ያ እውነት በዕለት ተዕለት ኑሯቸው ውስጥ ንቁ እውነታ አይደለም ፡፡እውነት በእዉነታዉ ላይ ተግባራዊ ካልተደረገ እና በውሳኔዎችም ውስጥ እንዲታይ እስካልተፈቀደ ድረስ እውነት ትርጉም የለውም። ሌሎች ትክክል የሆነውን ነገር በትክክል ያውቃሉ ፣ ግን እርምጃ ላለመውሰድ ይመርጣሉ። የክርስትና ሕይወት ግቡ የሰማችሁትን መውሰድ ነው ፣ ያዕቆብ 1፥22 እንደሚናገረው “ቃሉን የምታደርጉ እንጂ የምትሰሙ ብቻ አትሁኑ” ፡፡
በአንዳንድ መንገዶች ፣ አንድ ጠንካራ ልብ ለመጽሐፍ ቅዱስ እውነት የተጋለጠ ሰው ግን በነገሩ ምንም ባለማድረግ ሊገለፅ ይችላል፡፡
2. የልብዎ ችግር በጊዜ መፍትሄ አለማግኘቱ፡፡
ጠንካራ ልብ የሚያዳብርበት ዋነኛው ምክንያት የተሰበሩ ልምዶች እና የተሰበሩ ጉዳዮች ሁልጊዜ የሚያስፈልገውን ፈውስ የማይቀበሉ ከሆነ ነው። አሁን ሰዎች በብዛት ከባድ እየሆኑ ነው ምክንያቱም እግዚአብሔር የሕይወታቸውን ጥልቅ ሥቃይ እንዲፈውስ ስላልፈቀዱ ነው ፡፡
ቅሬታ፣ ለሌሎች አለማሰብ ጠንካራ ልብ ሊያዳብሩ ከሚችሉ ዋና ነገሮች ነገሮች አንዱ ነው፡፡ ጠንካራ ልብን ካሸናፊዎቹ የሚለየው ቅሬታን እንዴት መወጣት አለመቻሉ ነው፡፡
በስህተት የተያዘ እና ጥልቅ ቅሬታ የልብ ገዳይ ሊሆን ይችላል ፡፡ጥልቅ የህመማችን ቅሬታ ለማከም ካልሞከርን ወደ ቂም መያዝ ፣ መለያየት እና ወደ የከፋ መቀዝቀዝ ያመራናል፡፡ የልብ ጡንቻዎቻችን ያላቅቅብናል፡፡
ሁሉም ሰው ለብስጭት እና ለችግሮች የራሱ ድርሻ አለው። ብዙዎች በሥቃይ ውስጥ እግዚአብሔርን መጋበዝ ይመርጣሉ ፡፡ ምንም እንኳን እጅግ በጣም ከባድ ቢሆንም ፣ ከዚህ በፊት የማያውቋቸውን የእግዚአብሔር ተፈጥሮ ገጽታዎችን ያያሉ ፡፡ በመከራ ፣ በማጣት በብስጭት ጊዜያት ታላቅ ጥንካሬ እና ብስለት ያገኛሉ። ሆኖም በተመሳሳይ ጊዜ ፣ ብዙዎች በመንፈስ እና በስሜት ይወሰዳሉ፡፡
በተጎዳን ወይም በተቃጠልንባቸው ወቅቶች ውስጥ ማለፍ እንችላለን እናም እግዚአብሔር ጠንካራ ቦታዎችን በማለስለስ ልባችንን መፈወስ ይፈልጋል ፡፡ ለጥንካሬ ተስፋ አለ ፡፡ነገር ግን ያ ጥንካሬ የማይጣስበት ጊዜ ይመጣል ፡፡ እግዚአብሔር ራሱ በፊትህ ሊወጣ ይችላል እናም ምንም ነገር አይለውጠዉም ፡፡
ይቀጥላል...
ምንጭ:- www.hiyawkal.org
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የምንኖርበት ጊዜ ልባችንን ልያጠጥር ስለሚችል ከመቼውም ጊዜ በበለጠ ልባችንን በትኩረት መከታተል አለብን ፡፡
በአንድ ሌሊት አይከሰትም። አንድ ሰው ከእግዚአብሔር ጋር በንቁ ጉዞ ሊኖር ይችላል ከዚያም ቀስ በቀስ ወደ ደረቅነት ወደ ሚቀዘቅዘው ይሸጋገራል፡፡ ትክክል የሆነውን ያውቃሉ ፡፡ ግን ከእንግዲህ ግድ የላቸውም ፡፡ ግዴለሽነት ልባቸውን ይገዛል። የሌላውን ችግር እንደራስ በቀላሉ ማግኘት አይቻልም። በአንድ ወቅት እምነት ጠንካራ እና ንቁ ነበር ፣ መቀዝቀዝ ፣ ጥርጣሬ እና ነቀፋ ወረረዉ፡፡ ልጅ-መሰል እምነት ይቀልጣል እናም እንቅፋትን ይታገሱታል።
ልብን መለወጥ እንዴት ከባድ ነው ጠንካራ ልብን ማዳበር የምንችልባቸው የተለያዩ መንገዶች አሉ ፣ ግን ሁለት ዋናዎች መጥቀስ ተገቢ ነው-
1. እዉነትን መስማት ግን ተግባራዊ አለማድረግ፡፡
ጠንካራ ልብ በቀላሉ ሊያድግ ከሚችልበት አንድ ትልቁ መንገድ ምን ማድረግ እንዳለብን ስናውቅ እርምጃ ሳንወስድ ስንቀር ነው፡፡ የምንኖረው ከማንኛውም የበለጠ እውቀት እና ማስተዋል በሚገኝበት ትውልድ ውስጥ ነው። ሁልጊዜ እውነትን ለመስማት እድል አለን ፡፡ ችግሩ ፣ ብዙ እንሰማለን ፣ ግን በጣም ትንሽ ነገር ላይ እርምጃ እንወስዳለን፡፡
እኛ በታላላቅ አስተማሪዎች ተከብበናል ፣ ግን ብዙዎች ስለእሱ ምንም አያደርጉም ፣ ይህም ውሎ አድሮ ጠንካራ እና ቀዝቃዛ ወደ ሆነው ልብ እንዲያድጉ ያደርጋቸዋል ፡፡
ብዙዎች የሆነ ነገር በመስማታቸው ምክንያት “እናዉቃለን” ብለው በማሰብ ተታለዋል ። ግን ያ እውነት በዕለት ተዕለት ኑሯቸው ውስጥ ንቁ እውነታ አይደለም ፡፡እውነት በእዉነታዉ ላይ ተግባራዊ ካልተደረገ እና በውሳኔዎችም ውስጥ እንዲታይ እስካልተፈቀደ ድረስ እውነት ትርጉም የለውም። ሌሎች ትክክል የሆነውን ነገር በትክክል ያውቃሉ ፣ ግን እርምጃ ላለመውሰድ ይመርጣሉ። የክርስትና ሕይወት ግቡ የሰማችሁትን መውሰድ ነው ፣ ያዕቆብ 1፥22 እንደሚናገረው “ቃሉን የምታደርጉ እንጂ የምትሰሙ ብቻ አትሁኑ” ፡፡
በአንዳንድ መንገዶች ፣ አንድ ጠንካራ ልብ ለመጽሐፍ ቅዱስ እውነት የተጋለጠ ሰው ግን በነገሩ ምንም ባለማድረግ ሊገለፅ ይችላል፡፡
2. የልብዎ ችግር በጊዜ መፍትሄ አለማግኘቱ፡፡
ጠንካራ ልብ የሚያዳብርበት ዋነኛው ምክንያት የተሰበሩ ልምዶች እና የተሰበሩ ጉዳዮች ሁልጊዜ የሚያስፈልገውን ፈውስ የማይቀበሉ ከሆነ ነው። አሁን ሰዎች በብዛት ከባድ እየሆኑ ነው ምክንያቱም እግዚአብሔር የሕይወታቸውን ጥልቅ ሥቃይ እንዲፈውስ ስላልፈቀዱ ነው ፡፡
ቅሬታ፣ ለሌሎች አለማሰብ ጠንካራ ልብ ሊያዳብሩ ከሚችሉ ዋና ነገሮች ነገሮች አንዱ ነው፡፡ ጠንካራ ልብን ካሸናፊዎቹ የሚለየው ቅሬታን እንዴት መወጣት አለመቻሉ ነው፡፡
በስህተት የተያዘ እና ጥልቅ ቅሬታ የልብ ገዳይ ሊሆን ይችላል ፡፡ጥልቅ የህመማችን ቅሬታ ለማከም ካልሞከርን ወደ ቂም መያዝ ፣ መለያየት እና ወደ የከፋ መቀዝቀዝ ያመራናል፡፡ የልብ ጡንቻዎቻችን ያላቅቅብናል፡፡
ሁሉም ሰው ለብስጭት እና ለችግሮች የራሱ ድርሻ አለው። ብዙዎች በሥቃይ ውስጥ እግዚአብሔርን መጋበዝ ይመርጣሉ ፡፡ ምንም እንኳን እጅግ በጣም ከባድ ቢሆንም ፣ ከዚህ በፊት የማያውቋቸውን የእግዚአብሔር ተፈጥሮ ገጽታዎችን ያያሉ ፡፡ በመከራ ፣ በማጣት በብስጭት ጊዜያት ታላቅ ጥንካሬ እና ብስለት ያገኛሉ። ሆኖም በተመሳሳይ ጊዜ ፣ ብዙዎች በመንፈስ እና በስሜት ይወሰዳሉ፡፡
በተጎዳን ወይም በተቃጠልንባቸው ወቅቶች ውስጥ ማለፍ እንችላለን እናም እግዚአብሔር ጠንካራ ቦታዎችን በማለስለስ ልባችንን መፈወስ ይፈልጋል ፡፡ ለጥንካሬ ተስፋ አለ ፡፡ነገር ግን ያ ጥንካሬ የማይጣስበት ጊዜ ይመጣል ፡፡ እግዚአብሔር ራሱ በፊትህ ሊወጣ ይችላል እናም ምንም ነገር አይለውጠዉም ፡፡
ይቀጥላል...
ምንጭ:- www.hiyawkal.org
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍1
በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ በንጉሡ ዳዊት ዘመን ካህን ማን ነበር?
Anonymous Quiz
9%
ሀ. ሳዶቅ
28%
ለ. ሳሙኤል
21%
ሐ. አብያታር
9%
መ. ኢዮአብ
3%
ሠ. አኪጦፌል
30%
ረ. ሀ እና ሐ
. ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“በዚያም ኢየሱስ እንደ መልከ ጼዴቅ ሹመት ለዘላለም ሊቀ ካህናት የሆነው፥ ስለ እኛ ቀዳሚ ሆኖ ገባ።”
ዕብራውያን 6፥20
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“በዚያም ኢየሱስ እንደ መልከ ጼዴቅ ሹመት ለዘላለም ሊቀ ካህናት የሆነው፥ ስለ እኛ ቀዳሚ ሆኖ ገባ።”
ዕብራውያን 6፥20
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍9
ቅዱሳት መጻሕፍት
የጠጣር ልብ አደገኛ ውጤቶች የምንኖርበት ጊዜ ልባችንን ልያጠጥር ስለሚችል ከመቼውም ጊዜ በበለጠ ልባችንን በትኩረት መከታተል አለብን ፡፡ በአንድ ሌሊት አይከሰትም። አንድ ሰው ከእግዚአብሔር ጋር በንቁ ጉዞ ሊኖር ይችላል ከዚያም ቀስ በቀስ ወደ ደረቅነት ወደ ሚቀዘቅዘው ይሸጋገራል፡፡ ትክክል የሆነውን ያውቃሉ ፡፡ ግን ከእንግዲህ ግድ የላቸውም ፡፡ ግዴለሽነት ልባቸውን ይገዛል። የሌላውን ችግር እንደራስ…
የቀጠለ...
የጠጣር ልብ አደገኛ ውጤቶች
የጠጣር ልብ የሚያስከትሉት ውጤቶች ግለሰቡ ላይ ብቻ አይደለም። በአጠገቡ ያሉትን ሰዎች ይጎዳል። ግትር የሆነው ልበ ቅንነት በቤተሰብ ፣ በቤተክርስቲያን አመራር እና በአጠቃላይ ድርጅት ላይ ተጽዕኖ ይሳድራል ፡፡ልበ ጠጣርነት አንድ ሰዉን ብቻ አይጎዳም በዙሪያው ያሉትን ሁሉ ይነካል ፡፡
“እኔ እስከዚ ድረስ ብቻ ነው መግዋዝ የምችለው” የሚለው ይህ አስተሳሰብ ነው ፡፡ እነሱ ልክ እንደበፊቱ አያምኑም ፡፡ የእነሱ የዓለም አመለካከት ሊቆጣጠሩት ለሚችሉት ነገር ቀንሷል። በዚህ ምክንያት ፣ ጠጣር ልብ ከሚያስከትላቸው መዘዞች አንዱ በአካባቢዎ ያሉ ሰዎችን መጉዳቱ ነው፡፡ ሰዎች ይጎዳሉ ፣ ቤተሰቦች ይጎዳሉ ፡፡ ጋብቻ፣ በአካባቢዎ ያሉ ግንኙነቶች አሉታዊ ተፅኖንው ያጠቃዋል፡፡
2. የሚጎዳቸውን ነገር አይተውም፡፡
ምንም እንኳን እነዚህ የማምለጫ መሳሪያዎች አሉታዊ ተፅእኖን ቢያስከትሉም ጠጣር ልቦች ብዙውን ጊዜ ሱስ የሚያስይዝ ልምምዶችን ይፈልጋሉ።
እናም እነሱን ትጠይቃቸዋለህ “ለምን ይህን መጥፎ ልማድ ትሰራላችሁ? ለምን ይህን ታደርጋለህ?” ብዙ ጊዜ መለወጥ እንደማይፈልጉ የሚገልጽ ቀዝቃዛ ምላሽ ያገኛሉ።
ምንም እንኳን ልምዳቸው ስሜታቸውን እና አካላዊ ጤንነታቸውን እንኳን የሚጎዳ ቢሆንም ምንም እንኳን በቤተሰቡ ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ ቢኖረውም ለእነሱ ግድ አይሰጥም ፡፡
ከባድ ሲሆንብዎ ጊዜ ከዚ በኋላ ከሚያስከትላቸው ውጤቶች ጋር ከእንግዲህ አይገናኙም ፡፡ ጠጣር ልብ ያላቸው ሰዎች በሚያስደንቅ ሁኔታ ግትር ይሆናሉ ፡፡ እነሱ እንደዚህ ይላሉ ፣ “እኔ እንደዚ ነኝ፡፡ ይቀበሉት ወይም ይተዉት፡፡”
3. የእግዚአብሔርን እንቅስቃሴ እና የአቅጣጫ ፍሰት ያግዳሉ፡፡
የእግዚአብሔር ሥራ ሁሉ የሚከናወነው በመንፈስ ቅዱሱ መሪነት ፣ ተነሳሽነት እና ኃይል ሰጪነት ነው ፡፡ነገር ግን ጠንካርነት በሚኖርበት ጊዜ ወደ እርስዎ የሚመጡ የገነት ምልክቶችን አይለዩም። በእውነቱ ፣ እግዚአብሔር ሩቅ ነው ብለው ያስባሉ እርሱ ሩቅ ስለሆነ አይደለም ፣ ነገር ግን ልብዎ በዚያ የትስስር ግንኙነት ስለጠነከረ ነው ፡፡
የትኛውም ቡድን ቢሆኑ ፣ ጠጣርነቶ በቡድኑ ውስጥ ያሉትን ይጎዳል ፡፡ የእግዚአብሔር አቅም ይታገዳል ፡፡ የእርስዎ ጠጣርነት በሌሎች ላይ ተጽዕኖ እያሳደረ ነው።
4. ሊያንቀሳቅሳቸው በሚችሉ ነገሮች ላይ ስሜት አልባ እና ቀዝቃዛ ይሆናሉ፡፡
ጠጣር ልብ ሲኖርዎት ፣ የበለጠ እንዳይነቁ እና ከህይወትዎ ተለይተዉ እንዲወጡ ያደርግዎታል። ይህ ከእግዚአብሔር የፍቅር እና ግንዛቤ ፀጋ መውጣት አይደለም ፣ ነገር ግን የአከባቢያዊ ግንኙነቶችዎ ላይ ተፅህኖ ማምጣትም ነው ፡፡
በተለምዶ ፣ የተወሰኑ ነገሮች ልብዎን ያንቀሳቅሱ እና ወደ መለወጥ ይመራዎታል ፡፡ አሁን ፣ እነዚያ ቀስቃሾች ከእንግዲህ እንኳን አይነክዋችሁም።
እግዚአብሔር ወደ ፍላጎቶችዎ ያስገባዎታል ፡፡ እግዚአብሔር ተዛማጅ ስለሆነ ፍላጎቱን በእናንተ ላይ አይጭንም። በችግር ቦታ ውስጥ ቢሆኑም እንኳን በትዕግስት ይወዳችኋል ፡፡ እርሱ ግን ጠንካራነትህ ወደ ሚወስድህ እንድትሄድ ያደርግሃል ፡፡ እራሳችንን ለማነቃቃት ልባችን እንዲቀልልልን አንዳንድ ግዜ አስቸጋሪ ጊዜዎችን ማለፍ አለብን ፡፡
ምንጭ፦ www.hiyawkal.org
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የጠጣር ልብ አደገኛ ውጤቶች
የጠጣር ልብ የሚያስከትሉት ውጤቶች ግለሰቡ ላይ ብቻ አይደለም። በአጠገቡ ያሉትን ሰዎች ይጎዳል። ግትር የሆነው ልበ ቅንነት በቤተሰብ ፣ በቤተክርስቲያን አመራር እና በአጠቃላይ ድርጅት ላይ ተጽዕኖ ይሳድራል ፡፡ልበ ጠጣርነት አንድ ሰዉን ብቻ አይጎዳም በዙሪያው ያሉትን ሁሉ ይነካል ፡፡
“እኔ እስከዚ ድረስ ብቻ ነው መግዋዝ የምችለው” የሚለው ይህ አስተሳሰብ ነው ፡፡ እነሱ ልክ እንደበፊቱ አያምኑም ፡፡ የእነሱ የዓለም አመለካከት ሊቆጣጠሩት ለሚችሉት ነገር ቀንሷል። በዚህ ምክንያት ፣ ጠጣር ልብ ከሚያስከትላቸው መዘዞች አንዱ በአካባቢዎ ያሉ ሰዎችን መጉዳቱ ነው፡፡ ሰዎች ይጎዳሉ ፣ ቤተሰቦች ይጎዳሉ ፡፡ ጋብቻ፣ በአካባቢዎ ያሉ ግንኙነቶች አሉታዊ ተፅኖንው ያጠቃዋል፡፡
2. የሚጎዳቸውን ነገር አይተውም፡፡
ምንም እንኳን እነዚህ የማምለጫ መሳሪያዎች አሉታዊ ተፅእኖን ቢያስከትሉም ጠጣር ልቦች ብዙውን ጊዜ ሱስ የሚያስይዝ ልምምዶችን ይፈልጋሉ።
እናም እነሱን ትጠይቃቸዋለህ “ለምን ይህን መጥፎ ልማድ ትሰራላችሁ? ለምን ይህን ታደርጋለህ?” ብዙ ጊዜ መለወጥ እንደማይፈልጉ የሚገልጽ ቀዝቃዛ ምላሽ ያገኛሉ።
ምንም እንኳን ልምዳቸው ስሜታቸውን እና አካላዊ ጤንነታቸውን እንኳን የሚጎዳ ቢሆንም ምንም እንኳን በቤተሰቡ ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ ቢኖረውም ለእነሱ ግድ አይሰጥም ፡፡
ከባድ ሲሆንብዎ ጊዜ ከዚ በኋላ ከሚያስከትላቸው ውጤቶች ጋር ከእንግዲህ አይገናኙም ፡፡ ጠጣር ልብ ያላቸው ሰዎች በሚያስደንቅ ሁኔታ ግትር ይሆናሉ ፡፡ እነሱ እንደዚህ ይላሉ ፣ “እኔ እንደዚ ነኝ፡፡ ይቀበሉት ወይም ይተዉት፡፡”
3. የእግዚአብሔርን እንቅስቃሴ እና የአቅጣጫ ፍሰት ያግዳሉ፡፡
የእግዚአብሔር ሥራ ሁሉ የሚከናወነው በመንፈስ ቅዱሱ መሪነት ፣ ተነሳሽነት እና ኃይል ሰጪነት ነው ፡፡ነገር ግን ጠንካርነት በሚኖርበት ጊዜ ወደ እርስዎ የሚመጡ የገነት ምልክቶችን አይለዩም። በእውነቱ ፣ እግዚአብሔር ሩቅ ነው ብለው ያስባሉ እርሱ ሩቅ ስለሆነ አይደለም ፣ ነገር ግን ልብዎ በዚያ የትስስር ግንኙነት ስለጠነከረ ነው ፡፡
የትኛውም ቡድን ቢሆኑ ፣ ጠጣርነቶ በቡድኑ ውስጥ ያሉትን ይጎዳል ፡፡ የእግዚአብሔር አቅም ይታገዳል ፡፡ የእርስዎ ጠጣርነት በሌሎች ላይ ተጽዕኖ እያሳደረ ነው።
4. ሊያንቀሳቅሳቸው በሚችሉ ነገሮች ላይ ስሜት አልባ እና ቀዝቃዛ ይሆናሉ፡፡
ጠጣር ልብ ሲኖርዎት ፣ የበለጠ እንዳይነቁ እና ከህይወትዎ ተለይተዉ እንዲወጡ ያደርግዎታል። ይህ ከእግዚአብሔር የፍቅር እና ግንዛቤ ፀጋ መውጣት አይደለም ፣ ነገር ግን የአከባቢያዊ ግንኙነቶችዎ ላይ ተፅህኖ ማምጣትም ነው ፡፡
በተለምዶ ፣ የተወሰኑ ነገሮች ልብዎን ያንቀሳቅሱ እና ወደ መለወጥ ይመራዎታል ፡፡ አሁን ፣ እነዚያ ቀስቃሾች ከእንግዲህ እንኳን አይነክዋችሁም።
እግዚአብሔር ወደ ፍላጎቶችዎ ያስገባዎታል ፡፡ እግዚአብሔር ተዛማጅ ስለሆነ ፍላጎቱን በእናንተ ላይ አይጭንም። በችግር ቦታ ውስጥ ቢሆኑም እንኳን በትዕግስት ይወዳችኋል ፡፡ እርሱ ግን ጠንካራነትህ ወደ ሚወስድህ እንድትሄድ ያደርግሃል ፡፡ እራሳችንን ለማነቃቃት ልባችን እንዲቀልልልን አንዳንድ ግዜ አስቸጋሪ ጊዜዎችን ማለፍ አለብን ፡፡
ምንጭ፦ www.hiyawkal.org
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍4
#የሮሜ_መልእክት_ጥናት
ሮሜ 10
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ ወንድሞች ሆይ፥ የልቤ በጎ ፈቃድና ስለ እስራኤል ወደ እግዚአብሔር ልመናዬ እንዲድኑ ነው።
² በእውቀት አይቅኑ እንጂ ለእግዚአብሔር እንዲቀኑ እመሰክርላቸዋለሁና።
³ የእግዚአብሔርን ጽድቅ ሳያውቁ የራሳቸውንም ጽድቅ ሊያቆሙ ሲፈልጉ፥ ለእግዚአብሔር ጽድቅ አልተገዙም።
⁴ የሚያምኑ ሁሉ ይጸድቁ ዘንድ ክርስቶስ የሕግ ፍጻሜ ነውና።
ሮሜ 10 (አዲሱ መ.ት)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ ወንድሞች ሆይ፤ ስለ እስራኤላውያን የልቤ ምኞት፣ እግዚአብሔርንም የምለምነው እንዲድኑ ነው።
² ለእግዚአብሔር ቀናተኞች እንደሆኑ ስለ እነርሱ መመስከር እችላለሁና፤ ቅናታቸው ግን ከዕውቀት የተነሣ አይደለም።
³ ከእግዚአብሔር የሚመጣውን ጽድቅ ስላላወቁና የራሳቸውን ጽድቅ ለመመሥረት ስለ ፈለጉ፣ ለእግዚአብሔር ጽድቅ አልተገዙም።
⁴ ለሚያምን ሁሉ ጽድቅ ይሆን ዘንድ ክርስቶስ የሕግ ፍጻሜ ነውና።
ሮሜ 10 (ሕያው ቃል)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ ወንድሞቼ ሆይ፥እሥራኤላውያን እንዲድኑ ያለኝ ምኞትና ጉጉት ይህ ነው አይባልም። ጌታ እንዲያድናቸውም የዘወትር ጸሎቴ ነው።
² እነርሱም ስለ እግዚአብሔር ከፍ ያለ ቅንዓት እንዳላቸው አውቃለሁ። ነገር ግን ይህ ቅንዓታቸው በትክክለኛ እውቀት ላይ የተመሠረተ አይደለም።
³ ከእግዚአብሔር የሚሰጠውን ጽድቅ ንቀው፥ ሕግን በመጠበቅና በበጎ ሥራ ላይ የተመሠረተውን የራሳቸውን የጽድቅ መንገድ በመከተል እውነተኛውን ጽድቅ እምቢ አሉ።
⁴ በእርሱ የሚያምኑ ሁሉ እንዲጸድቁ ክርስቶስ ሕግን ፈጽሞላቸዋል። ስለዚህ ሕግን በመጠበቅ ለመጽደቅ አይቻልም።
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ሮሜ 10
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ ወንድሞች ሆይ፥ የልቤ በጎ ፈቃድና ስለ እስራኤል ወደ እግዚአብሔር ልመናዬ እንዲድኑ ነው።
² በእውቀት አይቅኑ እንጂ ለእግዚአብሔር እንዲቀኑ እመሰክርላቸዋለሁና።
³ የእግዚአብሔርን ጽድቅ ሳያውቁ የራሳቸውንም ጽድቅ ሊያቆሙ ሲፈልጉ፥ ለእግዚአብሔር ጽድቅ አልተገዙም።
⁴ የሚያምኑ ሁሉ ይጸድቁ ዘንድ ክርስቶስ የሕግ ፍጻሜ ነውና።
ሮሜ 10 (አዲሱ መ.ት)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ ወንድሞች ሆይ፤ ስለ እስራኤላውያን የልቤ ምኞት፣ እግዚአብሔርንም የምለምነው እንዲድኑ ነው።
² ለእግዚአብሔር ቀናተኞች እንደሆኑ ስለ እነርሱ መመስከር እችላለሁና፤ ቅናታቸው ግን ከዕውቀት የተነሣ አይደለም።
³ ከእግዚአብሔር የሚመጣውን ጽድቅ ስላላወቁና የራሳቸውን ጽድቅ ለመመሥረት ስለ ፈለጉ፣ ለእግዚአብሔር ጽድቅ አልተገዙም።
⁴ ለሚያምን ሁሉ ጽድቅ ይሆን ዘንድ ክርስቶስ የሕግ ፍጻሜ ነውና።
ሮሜ 10 (ሕያው ቃል)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ ወንድሞቼ ሆይ፥እሥራኤላውያን እንዲድኑ ያለኝ ምኞትና ጉጉት ይህ ነው አይባልም። ጌታ እንዲያድናቸውም የዘወትር ጸሎቴ ነው።
² እነርሱም ስለ እግዚአብሔር ከፍ ያለ ቅንዓት እንዳላቸው አውቃለሁ። ነገር ግን ይህ ቅንዓታቸው በትክክለኛ እውቀት ላይ የተመሠረተ አይደለም።
³ ከእግዚአብሔር የሚሰጠውን ጽድቅ ንቀው፥ ሕግን በመጠበቅና በበጎ ሥራ ላይ የተመሠረተውን የራሳቸውን የጽድቅ መንገድ በመከተል እውነተኛውን ጽድቅ እምቢ አሉ።
⁴ በእርሱ የሚያምኑ ሁሉ እንዲጸድቁ ክርስቶስ ሕግን ፈጽሞላቸዋል። ስለዚህ ሕግን በመጠበቅ ለመጽደቅ አይቻልም።
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍6
ከቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ ስለሮሜ መጽሐፍ ታሪካዊ ዳራ ትክክል ያልሆነው የቱ ነው?
Anonymous Quiz
26%
ሀ. መጽሐፉ የተጻፈው ቆሮንቶስ ከተማ ውስጥ ነው።
17%
ለ. በዘመኑ ቀላውዴዎስ ቄሳር አይሁድን ከሮም እንዲወጡ አዞ ነበር።
31%
ሐ. መልእክቱን ለሮም ቤተክርስቲያን ያመጣችሁ ዲያቆኗ ፌቨን ናት
25%
መ. መልእክቱ የተጻፈ በጳውሎስ በሁለተኛው የወንጌል ጉዞ ነው
. ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“በእሽቅድምድም ስፍራ የሚሮጡት፥ ሁሉ እንዲሮጡ ነገር ግን አንዱ ብቻ ዋጋውን እንዲቀበል አታውቁምን? እንዲሁም ታገኙ ዘንድ ሩጡ።”
1ኛ ቆሮንቶስ 9፥24
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“በእሽቅድምድም ስፍራ የሚሮጡት፥ ሁሉ እንዲሮጡ ነገር ግን አንዱ ብቻ ዋጋውን እንዲቀበል አታውቁምን? እንዲሁም ታገኙ ዘንድ ሩጡ።”
1ኛ ቆሮንቶስ 9፥24
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍5
#ከተማ_ወይም_ቦታ_በቅዱሳት_መጻሕፍት
#ሰሊሆም
ሰሊሆም ማለት የተላከ ማለት ነው። ኢየሱስ የዕውሩን ዓይን በጭቃ ከቀባ በኋላ «ሂድና ታጠብ» ብሎ ወደ ሰሊሆም ላከው፤ ዮሐ 9፡6-7። ለመጠመቂያ የሚሆን ውሃ የተጠራቀመበት ኩሬ። ከኢየሩሳሌም በደቡብ በኩል ዖፊል በተባለው ጎጥ ሥር ይገኛል። ሕዝቅያስ ውሃውን ከግዮን ምንጭ በቦይ ወደዚህ አስገብቶታል። በፊት በኢየሩሳሌም ቅጥር ውስጥ ነበር። ዛሬ ግን በኋላ ከተሠራው ቅጥር ውጭ ነው፤ ኢሳ. 22፥9-11። በብሉይ ኪዳን በተለይም በኢሳይያስ 8፥6 መሠረት ሰሊሆም ጸጥ ብለው በሚፈሱ ምንጮች የተከማቹ ሲሆኑ፣ እነዚህ ምንጮች ኢየሩሳሌም በጠላት በምትከበብበት ጊዜ ሁሉ የሚያገለግሉ በመሬት ውስጥ የሚሄዱ ስውር ውሆች ናቸው፡፡ እነዚህም ወኪሎች በሆኑት ነገሥታት ማለትም ፈሪሃ እግዚአብሔር የነበራቸው ከዳዊት ዘር በሆኑት ነገሥታት በኩል እግዚአብሔር በቸርነቱና በበረከቱ እስራኤልን በሰላምና በጸጥታ የሚገዛበትን ሁኔታ በምሳሌነት የሚገልጹ ናቸው፡፡
ምንጭ፦ የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት፤ ገጽ 71፣ ምሉእ ሕይወት፤ ገጽ 1014
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
#ሰሊሆም
ሰሊሆም ማለት የተላከ ማለት ነው። ኢየሱስ የዕውሩን ዓይን በጭቃ ከቀባ በኋላ «ሂድና ታጠብ» ብሎ ወደ ሰሊሆም ላከው፤ ዮሐ 9፡6-7። ለመጠመቂያ የሚሆን ውሃ የተጠራቀመበት ኩሬ። ከኢየሩሳሌም በደቡብ በኩል ዖፊል በተባለው ጎጥ ሥር ይገኛል። ሕዝቅያስ ውሃውን ከግዮን ምንጭ በቦይ ወደዚህ አስገብቶታል። በፊት በኢየሩሳሌም ቅጥር ውስጥ ነበር። ዛሬ ግን በኋላ ከተሠራው ቅጥር ውጭ ነው፤ ኢሳ. 22፥9-11። በብሉይ ኪዳን በተለይም በኢሳይያስ 8፥6 መሠረት ሰሊሆም ጸጥ ብለው በሚፈሱ ምንጮች የተከማቹ ሲሆኑ፣ እነዚህ ምንጮች ኢየሩሳሌም በጠላት በምትከበብበት ጊዜ ሁሉ የሚያገለግሉ በመሬት ውስጥ የሚሄዱ ስውር ውሆች ናቸው፡፡ እነዚህም ወኪሎች በሆኑት ነገሥታት ማለትም ፈሪሃ እግዚአብሔር የነበራቸው ከዳዊት ዘር በሆኑት ነገሥታት በኩል እግዚአብሔር በቸርነቱና በበረከቱ እስራኤልን በሰላምና በጸጥታ የሚገዛበትን ሁኔታ በምሳሌነት የሚገልጹ ናቸው፡፡
ምንጭ፦ የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት፤ ገጽ 71፣ ምሉእ ሕይወት፤ ገጽ 1014
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤7👍3
. ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“እንደ ሥጋ ፈቃድ የሚኖሩ የሥጋን ነገር ያስባሉና፥ እንደ መንፈስ ፈቃድ የሚኖሩ ግን የመንፈስን ነገር ያስባሉ።”
ሮሜ 8፥5
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“እንደ ሥጋ ፈቃድ የሚኖሩ የሥጋን ነገር ያስባሉና፥ እንደ መንፈስ ፈቃድ የሚኖሩ ግን የመንፈስን ነገር ያስባሉ።”
ሮሜ 8፥5
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍8❤2
የብሉይ ኪዳን ማብራሪያ.pdf
23.3 MB
👉ርዕስ፦ የብሉይ ኪዳን ማብራሪያ፣
ከ "ZONDERVAN NIV
BIBLE COMMENTARY VOLUME 1: Old Testamen" የተተረጎመ
🗣ተርጓሚዎች፦ ምንሊክ አስፋው፣ ንጉሤ ቡልቻ፣ ተጋፋው ትርፌ፣ ሰሎሞን ጥላሁን፣ ናሁሠናይ አፈወርቅ፣ ፍትሐ አምላክ እንየው፣ ደርበው አዱኛ፣ መስፍን ታዬ፣ ቁምላቸው ፋንታሁን፣ ዮናስ አስፋው፣ ፍሥሓ ፈይሣ፣ ተስፋዬ መስፍን፣ ወርቁ ኤጀሬ እና ቴዎፍሎስ ቀነዓ ናቸው፡፡
✍አርታዕያን፦ ንጉሤ ቡልቻ፣ ናሁሠናይ አፈወርቅ፣ ሰሎሞን ጥላሁን፣ ደርበው አዱኛ፣ ምንሊክ አስፋው እና ፍሥሓ ፈይሣ
📝ዋና አርታዒ ፦ ፍትሐ አምላክ እንየው ናቸው፡፡
🖨አሳታሚ፦ ራዕይ አሳታሚ
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ከ "ZONDERVAN NIV
BIBLE COMMENTARY VOLUME 1: Old Testamen" የተተረጎመ
🗣ተርጓሚዎች፦ ምንሊክ አስፋው፣ ንጉሤ ቡልቻ፣ ተጋፋው ትርፌ፣ ሰሎሞን ጥላሁን፣ ናሁሠናይ አፈወርቅ፣ ፍትሐ አምላክ እንየው፣ ደርበው አዱኛ፣ መስፍን ታዬ፣ ቁምላቸው ፋንታሁን፣ ዮናስ አስፋው፣ ፍሥሓ ፈይሣ፣ ተስፋዬ መስፍን፣ ወርቁ ኤጀሬ እና ቴዎፍሎስ ቀነዓ ናቸው፡፡
✍አርታዕያን፦ ንጉሤ ቡልቻ፣ ናሁሠናይ አፈወርቅ፣ ሰሎሞን ጥላሁን፣ ደርበው አዱኛ፣ ምንሊክ አስፋው እና ፍሥሓ ፈይሣ
📝ዋና አርታዒ ፦ ፍትሐ አምላክ እንየው ናቸው፡፡
🖨አሳታሚ፦ ራዕይ አሳታሚ
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤5👍5