. ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“ያን መንፈስም፥ በጸጋው ጸድቀን በዘላለም ሕይወት ተስፋ ወራሾች እንድንሆን፥ በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ በእኛ ላይ አትርፎ አፈሰሰው።”
ቲቶ 3፥6-7
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“ያን መንፈስም፥ በጸጋው ጸድቀን በዘላለም ሕይወት ተስፋ ወራሾች እንድንሆን፥ በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ በእኛ ላይ አትርፎ አፈሰሰው።”
ቲቶ 3፥6-7
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤3👍3🔥1
Audio
❤1👍1🥰1
#ከተማ_ወይም_ቦታ_በቅዱሳት_መጻሕፍት
#ቀርጤስ
ቀርጤስ ከግሪክ ደሴቶች ትልቁ እና ከዋናው ግሪክ በደቡብ ምስራቅ የምትገኝ ከተማ ናት። በጥንት ጊዜ፣ በአውሮፓ ውስጥ ከመጀመሪያዎቹ የላቁ ባህሎች አንዱ ተደርጎ በሚቆጠር ኃይለኛ በሚኖአን ሥልጣኔ (2700-1420 ከክርስቶስ ልደት በፊት) ትታወቅ ነበር። በአዲስ ኪዳን ዘመን፣ ቀርጤስ የአይሁድ ማህበረሰቦችን ጨምሮ በባህሏ እና በተለያዩ ህዝቦቿ የምትታወቅ የሮማ ግዛት አካል ነበረች።
ከሊታውያን የቀርጤስ ሰዎች ነበሩ፤ 1ሳሙ. 30፥14። በጰንጠቆስጤ ቀን ከቀርጤስ የመጡ አንዳንድ ሰዎች በኢየሩሳሌም ነበሩ፤ ሐሥ. 2፥11። ጳውሎስና ቲቶ በቀርጤስ ቤተ ክርስቲያንን መሠረቱ ቲቶ 1፥5-14።
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ስለ ቀርጤስ ቁልፍ ነጥቦች፡-
ስትራቴጂካዊ ቦታ፦ የቀርጤስ መገኛ በሜዲትራኒያን ባህር ውስጥ ለንግድ እና ለጉዞ አስፈላጊ መስቀለኛ መንገድ አድርጎታል።
የባህል ጠቀሜታ፦ ደሴቲቱ ተረት እና ፍልስፍናን ጨምሮ የበለጸገ ባህላዊ ቅርስ ነበራት።
የሥነ ምግባር ዝና፡- የቀርጤስ ሰዎች የሚታወቁት በመዋሸትና በሥነ ምግባር ብልሹነት ነበር (ቲቶ 1፥12)
ክርስቲያናዊ ተልእኮ፡- የጳውሎስ የቀርጤስ ጉብኝት እና ቲቶ መሪ አድርጎ መሾሙ ክርስትና ወደ ደሴቲቱ መስፋፋቱን ያመለክታል።
ምንጭ፦ የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት፤ ገጽ 89፣ The Book of Titus: A Counter-Cultural Gospel for Cretans: https://bibleproject.com/articles/titus/
Crete Meaning - Bible Definition and References:
https://www.biblestudytools.com/dictionary/crete/
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
#ቀርጤስ
ቀርጤስ ከግሪክ ደሴቶች ትልቁ እና ከዋናው ግሪክ በደቡብ ምስራቅ የምትገኝ ከተማ ናት። በጥንት ጊዜ፣ በአውሮፓ ውስጥ ከመጀመሪያዎቹ የላቁ ባህሎች አንዱ ተደርጎ በሚቆጠር ኃይለኛ በሚኖአን ሥልጣኔ (2700-1420 ከክርስቶስ ልደት በፊት) ትታወቅ ነበር። በአዲስ ኪዳን ዘመን፣ ቀርጤስ የአይሁድ ማህበረሰቦችን ጨምሮ በባህሏ እና በተለያዩ ህዝቦቿ የምትታወቅ የሮማ ግዛት አካል ነበረች።
ከሊታውያን የቀርጤስ ሰዎች ነበሩ፤ 1ሳሙ. 30፥14። በጰንጠቆስጤ ቀን ከቀርጤስ የመጡ አንዳንድ ሰዎች በኢየሩሳሌም ነበሩ፤ ሐሥ. 2፥11። ጳውሎስና ቲቶ በቀርጤስ ቤተ ክርስቲያንን መሠረቱ ቲቶ 1፥5-14።
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ስለ ቀርጤስ ቁልፍ ነጥቦች፡-
ስትራቴጂካዊ ቦታ፦ የቀርጤስ መገኛ በሜዲትራኒያን ባህር ውስጥ ለንግድ እና ለጉዞ አስፈላጊ መስቀለኛ መንገድ አድርጎታል።
የባህል ጠቀሜታ፦ ደሴቲቱ ተረት እና ፍልስፍናን ጨምሮ የበለጸገ ባህላዊ ቅርስ ነበራት።
የሥነ ምግባር ዝና፡- የቀርጤስ ሰዎች የሚታወቁት በመዋሸትና በሥነ ምግባር ብልሹነት ነበር (ቲቶ 1፥12)
ክርስቲያናዊ ተልእኮ፡- የጳውሎስ የቀርጤስ ጉብኝት እና ቲቶ መሪ አድርጎ መሾሙ ክርስትና ወደ ደሴቲቱ መስፋፋቱን ያመለክታል።
ምንጭ፦ የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት፤ ገጽ 89፣ The Book of Titus: A Counter-Cultural Gospel for Cretans: https://bibleproject.com/articles/titus/
Crete Meaning - Bible Definition and References:
https://www.biblestudytools.com/dictionary/crete/
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍11❤1
. ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“ያም እድል ፈንታው ነውና ሰው በሥራው ደስ ከሚለው በቀር ሌላ መልካም ነገር እንደሌለው አየሁ፤ ከእርሱ በኋላስ የሚሆነውን ያይ ዘንድ የሚያመጣው ማን ነው?”
መክብብ 3፥22
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“ያም እድል ፈንታው ነውና ሰው በሥራው ደስ ከሚለው በቀር ሌላ መልካም ነገር እንደሌለው አየሁ፤ ከእርሱ በኋላስ የሚሆነውን ያይ ዘንድ የሚያመጣው ማን ነው?”
መክብብ 3፥22
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍6❤1
ከቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ በሚከተለው ዑደት የተሞላው መጽሐፍ የቱ ነው? እስራኤላውያን ኃጢአት ይሰራሉ ----❯ እግዚአብሔር አስጨናቂ የአሕዛብ ገዢዎች ይሰድባቸዋል ---❯ ሕዝቡ ወደ እግዚአብሔር ይጮኻል ----❯ተለምኖም ነጻ ያወጣቸዋል። ---❯ ተመልሰው ወደ ኃጢአት ይገባሉ...
Anonymous Quiz
12%
ሀ. 2ኛ ነገሥት
5%
ለ. 2ኛ ዜና
68%
ሐ. መጽሐፈ መሳፍንት
14%
መ. ትንቢተ ኤርምያስ
1%
ሠ. መጽሐፈ ሩት
👍4
ለቃሉ መታዘዝ
መጽሐፍ ቅዱስ የተጻፈው፡ ለታሪክ፡ለምርምር፡ ለጠቅላላ ዕውቀት፡ ለግንዛቤ፡ ወይም ለመረጃ አይደለም። የተጻፈበት ቀዳሚ ዓላማ ለሕይወት ነው።
"የእግዚአብሔር ቃል ሕያው ነውና፥ የሚሠራም፥ ሁለትም አፍ ካለው ሰይፍ ሁሉ ይልቅ የተሳለ ነው፥ ነፍስንና መንፈስንም ጅማትንና ቅልጥምንም እስኪለይ ድረስ ይወጋል፥ የልብንም ስሜትና አሳብ ይመረምራል፤" ዕብ ፬፡፲፪
መጽሐፍ ቅዱስን መታዘዝ አለብን ስንል መጽሐፉ ከዳር እስከ ዳር ይህን አድርግ ይህን አታድርግ በሚሉ ትእዛዛት የተሞላ መጽሐፍ ነው ማለታችን አይደለም። እግዚአብሔር እንድንታዘዘው የሚፈልገውን ሃሳብ በቃሉ ውስጥ በተለያየ መንገድ አስቀምጧል። ይህንንም ማስተዋል የኛ ድርሻ ይሆናል።
« እግዚአብሔር በአንድ መንገድ በሌላም ይናገራል ሰው ግን አያስተውለውም።» ኢዮ ፴፫፥፲፬፤
እግዚአብሔር ከሚያስተምርባቸው መንገዶች የሚከተሉት ዋናዎቹ ናቸው።
፩. በቀጥተኛ ትዕዛዝ
መጽሐፍ ቅዱስ አድርግ፣ አታድርግ የሚሉ ቀጥተኛ ትእዛዛት አሉት፤ ለምሳሌ እንደ አሥርቱ ቃላት እና ትእዛዛተ-ወንጌል፤ እነዚህንም በቀጥታ መፈጸም ይጠበቅብናል።
«አትግደል፤ አትስረቅ፤ አታመንዝር…. በሰማይ መዝገብ ሰብስቡ፤ አትጨነቁ፤ ጽድቁን ፈልጉ።…» ዘጸ ፳፤ ማቴ ፮።
፪. በምክር መልክ
በቅኔ እና በጥበብ መጻሕፍት ውስጥ በምሳሌ፣ በምስጋና፣ በግጥም፣ በጸሎት መልክ በተጻፉት በምክር ያስተምራል። እነዚህም በመከራ ጊዜ ድጋፍ፣ መጽናኛ የሚሆኑ ኃይል ያላቸው ቃላት ናቸው።
«እግዚአብሔር ብርሃኔና መድኃኒቴ ነው የሚያስፈራኝ ማን ነው? እግዚአብሔር የሕይወቴ መታመኛዋ ነው የሚያስደነግጠኝ ማን ነው?» መዝ ፳፯፥፩
፫. በሰዎች ታሪክ
ደካማም ይሁኑ ብርቱ፣ ከድካማቸው እንድንማር፣ ብርታታቸውን እንድንከተል በመላው መጽሐፍ ቅዱስ ታሪካቸው የተጻፈላቸው ሰዎች ሁሉ ምንጊዜም ለኛ የሚያስተምሩት ነገር አለ። ለምሳሌ አብርሃም የእግዚአብሔር ወዳጅ ለመባል የበቃው በእምነት ባሳየው መታዘዝ በመሆኑ እኛም እንደ አብርሃም በእምነት እግዚአብሔርን ብንታዘዝ የበረከቱ ተካፋዮች እንደምንሆን እግዚአብሔር ተናግሯል።
«መጽሐፍም እግዚአብሔር አሕዛብን በእምነት እንዲያጸድቅ አስቀድሞ አይቶ። በአንተ አሕዛብ ሁሉ ይባረካሉ ብሎ ወንጌልን ለአብርሃም አስቀድሞ ሰበከ። እንደዚህ ከእምነት የሆኑት ካመነው ከአብርሃም ጋር ይባረካሉ። » ገላ ፫፣፰
፬. በኢየሱስ ክርስቶስ ሕይወት
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ዚች ምድር የመጣው አንደኛ ለቤዛነት (ዓለምን ሁሉ ለማዳን) ሲሆን በሁለተኛ ደረጃ ለአርአያነት ወይም በኑሮአችን እንድንመስለው በተግባር ለማስተማር ነው። ከልደቱ እስከ ሞቱ መላው የክርስቶስ ሕይወቱ ለእኛ አስተማሪ ነው።
« የተጠራችሁለት ለዚህ ነውና፤ ክርስቶስ ደግሞ ፍለጋውን እንድትከተሉ ምሳሌ ትቶላችሁ ስለ እናንተ መከራን ተቀብሎአልና።» ፩ ጴጥ ፪፣፳፩።
ልጆች ለወላጆቻቸው እንዲታዘዙ መጀመሪያ በቃል በ፲ቱ ትዕዛዛት በኋላም ሰው ሆኖ በተግባር እየታዘዘ አስተማረን - የሕይወት መምህር ኢየሱስ ክርሰቶስ። ይህን በማስታወስ ቅዱስ ጳውሎስ ልጆች ለወላጆች እንዲታዘዙ ይመክራል።
« ልጆች ሆይ፥ ለወላጆቻችሁ በጌታ ታዘዙ፥ ይህ የሚገባ ነውና። መልካም እንዲሆንልህ ዕድሜህም በምድር ላይ እንዲረዝም አባትህንና እናትህን አክብር፤ እርስዋም የተስፋ ቃል ያላት ፊተኛይቱ ትእዛዝ ናት።» ኤፌ ፮፣፩
የአዳም አለመታዘዝ ለሰዎች ሁሉ ሞትን እንዳመጣ የክርስቶስ መታዘዝ ደግሞ ሕይወትን አስገኝቷል። ሮሜ ፭፣ ፲፱ ይመልከቱ።
መታዘዝ የበረከት ብቻ ሳይሆን የሕይወትም ጉዳይ ነው። ክርስቶስ እንደታዘዘ የሕይወትንም መንገድ እንዳመጣ እኛም በእርሱ በማመን፣ እምነታችንንም በመልካም ሥራ በመግለጽ ስንታዘዝ የዘላላም ሕይወትን እናገኛለን።
ሐዋርያት ኢየሱስ ክርስቶስን መጀመሪያ በእግር ቀጥሎም በግብር ተከተሉት ሲባል ሕይወታቸው በሙሉ እርሱን የሚመስል ሆኖ ለእግዚአብሔር በመታዘዝ ኖሩ ማለት ነው። እኛም በክርስቶስ በስሙ ተጠርተን ክርስቲያኖች (የክርስቶስ) ስንባል ሕይወታችንም እርሱን የሚመስል ሊሆን ይገባዋል ማለት ነው።
ለእግዚአብሔር ከምናቀርብለት ከየትኛውም መሥዋዕታችን ይልቅ ለእግዚአብሔር እንደመታዘዝ ያለ ነገር የለም።
"በውኑ የእግዚአብሔርን ቃል በመስማት ደስ እንደሚለው እግዚአብሔር በሚቃጠልና በሚታረድ መሥዋዕት ደስ ይለዋልን? እነሆ፥ መታዘዝ ከመሥዋዕት፥ ማዳመጥም የአውራ በግ ስብ ከማቅረብ ይበልጣል።" ፩ሳሙ ፲፭፣፳፪።
በብሉይ ኪዳን ለእግዚአብሔር ይቀርብ የነበረው መሥዋዕት የአውራ በግ፣ ዋኖስ፣…. ነበር። በሐዲስ ኪዳን እነዚህን አናቀርብም፤ የቀረበ አንድ መሥዋዕት አለ። እርሱም የእግዚአብሔር በግ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። እንግዲህ እኛ የምናቀርበው መሥዋዕት ምስጋና ነው። ጸሎትም ወደ እግዚአብሔር እናደርሳለን። ምጽዋት በእግዚአብሔር ስም ለተቸገሩት እንሰጣለን። ወደ እግዚአብሔር ከሚደርሱት ምስጋና፣ ጸሎት፣ ጾም፣ ምጽዋት….ከእነዚህ ሁሉ በላይ/በፊት ለእግዚአብሔር መታዘዝ እንደሚቀድም ቃሉ ያስተምረናል።
እንግዲህ በመጽሐፍ ቅዱስ የሚገኘው የእግዚአብሔር ቃል እያንዳንዳችን አድራሻ ያደረገ የሰማያዊ አባታችን መልእክት ስለሆነ በእምነት ስንቀበለው፣ በተግባርም ስንታዘዘው ያን ጊዜ የበረከቱ ተካፋዮች እንሆናለን። የእግዚአብሔር ቃል ከወተት እስከ አጥንት በተለያየ ደረጃ የሚገኝ በመሆኑ እኛም በመጀመሪያ በመንፈስ ሕጻናት ሆነን የቃሉን ወተት እየተመገብን በእርሱ ስናድግ እየተገለጠልን፣ እየተረዳነው እንመጣለን።
« ከጊዜው የተነሳ አስተማሪዎች ልትሆኑ ሲገባችሁ፥ አንድ ሰው ስለ እግዚአብሔር ቃላት መጀመሪያ ያለውን የሕፃንነትን ትምህርት እንዲያስተምራችሁ እንደ ገና ያስፈልጋችኋልና፤ የሚያስፈልጋችሁም ወተት ነው እንጂ ጠንካራ ምግብ አይደለም። » ዕብ ፭፣፲፪
ቃሉ እንዲሠራብን ከኛ ግንዛቤን ሳይሆን ተግባራዊ ምላሽን ይፈልጋል። ስለዚህ ለቃሉ እንታዘዝ።
«ቃሉን የምታደርጉ ሁኑ እንጂ ራሳችሁን እያሳታችሁ የምትሰሙ ብቻ አትሁኑ።» ያዕ ፩፣፳፪
ቃሉን ሰምተን እንድንታዘዝ ጸጋውን ያብዛልን!!!
ምንጭ:- abrhamha.blogspot.com
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
መጽሐፍ ቅዱስ የተጻፈው፡ ለታሪክ፡ለምርምር፡ ለጠቅላላ ዕውቀት፡ ለግንዛቤ፡ ወይም ለመረጃ አይደለም። የተጻፈበት ቀዳሚ ዓላማ ለሕይወት ነው።
"የእግዚአብሔር ቃል ሕያው ነውና፥ የሚሠራም፥ ሁለትም አፍ ካለው ሰይፍ ሁሉ ይልቅ የተሳለ ነው፥ ነፍስንና መንፈስንም ጅማትንና ቅልጥምንም እስኪለይ ድረስ ይወጋል፥ የልብንም ስሜትና አሳብ ይመረምራል፤" ዕብ ፬፡፲፪
መጽሐፍ ቅዱስን መታዘዝ አለብን ስንል መጽሐፉ ከዳር እስከ ዳር ይህን አድርግ ይህን አታድርግ በሚሉ ትእዛዛት የተሞላ መጽሐፍ ነው ማለታችን አይደለም። እግዚአብሔር እንድንታዘዘው የሚፈልገውን ሃሳብ በቃሉ ውስጥ በተለያየ መንገድ አስቀምጧል። ይህንንም ማስተዋል የኛ ድርሻ ይሆናል።
« እግዚአብሔር በአንድ መንገድ በሌላም ይናገራል ሰው ግን አያስተውለውም።» ኢዮ ፴፫፥፲፬፤
እግዚአብሔር ከሚያስተምርባቸው መንገዶች የሚከተሉት ዋናዎቹ ናቸው።
፩. በቀጥተኛ ትዕዛዝ
መጽሐፍ ቅዱስ አድርግ፣ አታድርግ የሚሉ ቀጥተኛ ትእዛዛት አሉት፤ ለምሳሌ እንደ አሥርቱ ቃላት እና ትእዛዛተ-ወንጌል፤ እነዚህንም በቀጥታ መፈጸም ይጠበቅብናል።
«አትግደል፤ አትስረቅ፤ አታመንዝር…. በሰማይ መዝገብ ሰብስቡ፤ አትጨነቁ፤ ጽድቁን ፈልጉ።…» ዘጸ ፳፤ ማቴ ፮።
፪. በምክር መልክ
በቅኔ እና በጥበብ መጻሕፍት ውስጥ በምሳሌ፣ በምስጋና፣ በግጥም፣ በጸሎት መልክ በተጻፉት በምክር ያስተምራል። እነዚህም በመከራ ጊዜ ድጋፍ፣ መጽናኛ የሚሆኑ ኃይል ያላቸው ቃላት ናቸው።
«እግዚአብሔር ብርሃኔና መድኃኒቴ ነው የሚያስፈራኝ ማን ነው? እግዚአብሔር የሕይወቴ መታመኛዋ ነው የሚያስደነግጠኝ ማን ነው?» መዝ ፳፯፥፩
፫. በሰዎች ታሪክ
ደካማም ይሁኑ ብርቱ፣ ከድካማቸው እንድንማር፣ ብርታታቸውን እንድንከተል በመላው መጽሐፍ ቅዱስ ታሪካቸው የተጻፈላቸው ሰዎች ሁሉ ምንጊዜም ለኛ የሚያስተምሩት ነገር አለ። ለምሳሌ አብርሃም የእግዚአብሔር ወዳጅ ለመባል የበቃው በእምነት ባሳየው መታዘዝ በመሆኑ እኛም እንደ አብርሃም በእምነት እግዚአብሔርን ብንታዘዝ የበረከቱ ተካፋዮች እንደምንሆን እግዚአብሔር ተናግሯል።
«መጽሐፍም እግዚአብሔር አሕዛብን በእምነት እንዲያጸድቅ አስቀድሞ አይቶ። በአንተ አሕዛብ ሁሉ ይባረካሉ ብሎ ወንጌልን ለአብርሃም አስቀድሞ ሰበከ። እንደዚህ ከእምነት የሆኑት ካመነው ከአብርሃም ጋር ይባረካሉ። » ገላ ፫፣፰
፬. በኢየሱስ ክርስቶስ ሕይወት
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ዚች ምድር የመጣው አንደኛ ለቤዛነት (ዓለምን ሁሉ ለማዳን) ሲሆን በሁለተኛ ደረጃ ለአርአያነት ወይም በኑሮአችን እንድንመስለው በተግባር ለማስተማር ነው። ከልደቱ እስከ ሞቱ መላው የክርስቶስ ሕይወቱ ለእኛ አስተማሪ ነው።
« የተጠራችሁለት ለዚህ ነውና፤ ክርስቶስ ደግሞ ፍለጋውን እንድትከተሉ ምሳሌ ትቶላችሁ ስለ እናንተ መከራን ተቀብሎአልና።» ፩ ጴጥ ፪፣፳፩።
ልጆች ለወላጆቻቸው እንዲታዘዙ መጀመሪያ በቃል በ፲ቱ ትዕዛዛት በኋላም ሰው ሆኖ በተግባር እየታዘዘ አስተማረን - የሕይወት መምህር ኢየሱስ ክርሰቶስ። ይህን በማስታወስ ቅዱስ ጳውሎስ ልጆች ለወላጆች እንዲታዘዙ ይመክራል።
« ልጆች ሆይ፥ ለወላጆቻችሁ በጌታ ታዘዙ፥ ይህ የሚገባ ነውና። መልካም እንዲሆንልህ ዕድሜህም በምድር ላይ እንዲረዝም አባትህንና እናትህን አክብር፤ እርስዋም የተስፋ ቃል ያላት ፊተኛይቱ ትእዛዝ ናት።» ኤፌ ፮፣፩
የአዳም አለመታዘዝ ለሰዎች ሁሉ ሞትን እንዳመጣ የክርስቶስ መታዘዝ ደግሞ ሕይወትን አስገኝቷል። ሮሜ ፭፣ ፲፱ ይመልከቱ።
መታዘዝ የበረከት ብቻ ሳይሆን የሕይወትም ጉዳይ ነው። ክርስቶስ እንደታዘዘ የሕይወትንም መንገድ እንዳመጣ እኛም በእርሱ በማመን፣ እምነታችንንም በመልካም ሥራ በመግለጽ ስንታዘዝ የዘላላም ሕይወትን እናገኛለን።
ሐዋርያት ኢየሱስ ክርስቶስን መጀመሪያ በእግር ቀጥሎም በግብር ተከተሉት ሲባል ሕይወታቸው በሙሉ እርሱን የሚመስል ሆኖ ለእግዚአብሔር በመታዘዝ ኖሩ ማለት ነው። እኛም በክርስቶስ በስሙ ተጠርተን ክርስቲያኖች (የክርስቶስ) ስንባል ሕይወታችንም እርሱን የሚመስል ሊሆን ይገባዋል ማለት ነው።
ለእግዚአብሔር ከምናቀርብለት ከየትኛውም መሥዋዕታችን ይልቅ ለእግዚአብሔር እንደመታዘዝ ያለ ነገር የለም።
"በውኑ የእግዚአብሔርን ቃል በመስማት ደስ እንደሚለው እግዚአብሔር በሚቃጠልና በሚታረድ መሥዋዕት ደስ ይለዋልን? እነሆ፥ መታዘዝ ከመሥዋዕት፥ ማዳመጥም የአውራ በግ ስብ ከማቅረብ ይበልጣል።" ፩ሳሙ ፲፭፣፳፪።
በብሉይ ኪዳን ለእግዚአብሔር ይቀርብ የነበረው መሥዋዕት የአውራ በግ፣ ዋኖስ፣…. ነበር። በሐዲስ ኪዳን እነዚህን አናቀርብም፤ የቀረበ አንድ መሥዋዕት አለ። እርሱም የእግዚአብሔር በግ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። እንግዲህ እኛ የምናቀርበው መሥዋዕት ምስጋና ነው። ጸሎትም ወደ እግዚአብሔር እናደርሳለን። ምጽዋት በእግዚአብሔር ስም ለተቸገሩት እንሰጣለን። ወደ እግዚአብሔር ከሚደርሱት ምስጋና፣ ጸሎት፣ ጾም፣ ምጽዋት….ከእነዚህ ሁሉ በላይ/በፊት ለእግዚአብሔር መታዘዝ እንደሚቀድም ቃሉ ያስተምረናል።
እንግዲህ በመጽሐፍ ቅዱስ የሚገኘው የእግዚአብሔር ቃል እያንዳንዳችን አድራሻ ያደረገ የሰማያዊ አባታችን መልእክት ስለሆነ በእምነት ስንቀበለው፣ በተግባርም ስንታዘዘው ያን ጊዜ የበረከቱ ተካፋዮች እንሆናለን። የእግዚአብሔር ቃል ከወተት እስከ አጥንት በተለያየ ደረጃ የሚገኝ በመሆኑ እኛም በመጀመሪያ በመንፈስ ሕጻናት ሆነን የቃሉን ወተት እየተመገብን በእርሱ ስናድግ እየተገለጠልን፣ እየተረዳነው እንመጣለን።
« ከጊዜው የተነሳ አስተማሪዎች ልትሆኑ ሲገባችሁ፥ አንድ ሰው ስለ እግዚአብሔር ቃላት መጀመሪያ ያለውን የሕፃንነትን ትምህርት እንዲያስተምራችሁ እንደ ገና ያስፈልጋችኋልና፤ የሚያስፈልጋችሁም ወተት ነው እንጂ ጠንካራ ምግብ አይደለም። » ዕብ ፭፣፲፪
ቃሉ እንዲሠራብን ከኛ ግንዛቤን ሳይሆን ተግባራዊ ምላሽን ይፈልጋል። ስለዚህ ለቃሉ እንታዘዝ።
«ቃሉን የምታደርጉ ሁኑ እንጂ ራሳችሁን እያሳታችሁ የምትሰሙ ብቻ አትሁኑ።» ያዕ ፩፣፳፪
ቃሉን ሰምተን እንድንታዘዝ ጸጋውን ያብዛልን!!!
ምንጭ:- abrhamha.blogspot.com
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤5👍4👏1
. ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“እናንተ ደግሞ እንደ ሕያዋን ድንጋዮች ሆናችሁ፥ በኢየሱስ ክርስቶስ ለእግዚአብሔር ደስ የሚያሰኝ መንፈሳዊ መሥዋዕትን ታቀርቡ ዘንድ ቅዱሳን ካህናት እንድትሆኑ መንፈሳዊ ቤት ለመሆን ተሠሩ።”
1ኛ ጴጥሮስ 2፥5
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“እናንተ ደግሞ እንደ ሕያዋን ድንጋዮች ሆናችሁ፥ በኢየሱስ ክርስቶስ ለእግዚአብሔር ደስ የሚያሰኝ መንፈሳዊ መሥዋዕትን ታቀርቡ ዘንድ ቅዱሳን ካህናት እንድትሆኑ መንፈሳዊ ቤት ለመሆን ተሠሩ።”
1ኛ ጴጥሮስ 2፥5
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤4🔥4👍3
ትምህርተ እግዚአብሔር.pdf
18.9 MB
👉ርዕስ፦ ትምህርተ እግዚአብሔር
✍ጸሐፊ፦ በቄስ ኮሊንስ ማንሰል
ስለ መጽሐፉ፦
አጠቃላይ የነገረ መለኮት ትምህርት
ትምህርተ እግዚአብሔር 1ኛ መጽሐፍ
በውስጡ ያሉ ጥናቶች፦
👉ጥናት 1. ትምህርተ አስተርእዮ
👉ጥናት 2. ትምህርተ ባሕርየ እግዚአብሔር
👉ጥናት 3. ትምህርተ ፍጥረት
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
✍ጸሐፊ፦ በቄስ ኮሊንስ ማንሰል
ስለ መጽሐፉ፦
አጠቃላይ የነገረ መለኮት ትምህርት
ትምህርተ እግዚአብሔር 1ኛ መጽሐፍ
በውስጡ ያሉ ጥናቶች፦
👉ጥናት 1. ትምህርተ አስተርእዮ
👉ጥናት 2. ትምህርተ ባሕርየ እግዚአብሔር
👉ጥናት 3. ትምህርተ ፍጥረት
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍4❤1
በእስራኤል ነገሥታት ታሪክ ብቸኛዋ ሴት ገዢ ንግሥት ማን ናት?
Anonymous Quiz
59%
ሀ. ዲቦራ
5%
ለ. ኢያዔል
19%
ሐ. ጎቶልያ
9%
መ. ቤርሳቤህ
8%
ሠ. አቢግያ
👍4
. ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“ስለዚህ የተወደዳችሁ ወንድሞቼ ሆይ፤ ጸንታችሁ ቁሙ፤ በምንም ነገር አትናወጡ። ለጌታ ሥራ ዘወትር የምትተጉ ሁኑ፤ ምክንያቱም ለጌታ የምትደክሙት በከንቱ እንዳልሆነ ታውቃላችሁ።”
1ኛ ቆሮንቶስ 15፥58 (አዲሱ መ.ት)
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“ስለዚህ የተወደዳችሁ ወንድሞቼ ሆይ፤ ጸንታችሁ ቁሙ፤ በምንም ነገር አትናወጡ። ለጌታ ሥራ ዘወትር የምትተጉ ሁኑ፤ ምክንያቱም ለጌታ የምትደክሙት በከንቱ እንዳልሆነ ታውቃላችሁ።”
1ኛ ቆሮንቶስ 15፥58 (አዲሱ መ.ት)
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍4❤1
ቅዱሳት መጻሕፍት
ነቢዩ ኤርምያስ ክፍል-፭ በኢዮአቄም የዐሥራ አንድ ዓመት ዘመነ መንግሥት ውስጥ የከርከሚሽ ጦርነት ተካሄደ (ከ46 ፥ 2 ጋር ያነጻ)፡፡ በመካከለኛው ምሥራቅ የኀይል ሚዛን ከግብፅ ወደ ባቢሎን መተላለፉን ያመላከተ ስለ ሆነ፣ ዘላቂ ፋይዳ ያለው ሁኔታ (ክሥተት) ነበር፡፡ ይህ ሽንፈት በግብፅ የመስፋፋት ምኞት ላይ የመጨረሻ በትር ሲሆን፤ ከለዳውያን በምዕራቡ…
ነቢዩ ኤርምያስ
ክፍል-፮
ነገር ግን መጨረሻው ሩቅ አልነበረም:: በዘጠነኛው የአገዛዝ ዘመኑ (588)፣ ሴዴቅያስ ከፈርዖን ኡፍራ ጋር ግምባር በመግጠም በናቡከደነፆር ላይ ዐመፀ:: ባቢሎን ይሁዳን በመውረር ምላሽ ሰጥታ በ586 ከተማዋ በእጇ ስትወድቅ ወረራው ፍጻሜ ላይ ደረሰ (2ነገ 36፥17፤ ኤር 38 ፥ 28-39፥ 10)፡፡ በወረራው ዘመን ሁሉ ሴዴቅያስ እጁን ይሰጥ ዘንድ ኤርምያስ አደፋፈረው (21 ፥ 1-10 ፤ 34፥ 1-5፤ 17-22 37 ፥ 3-10፤ 16-17 ፤ 38፥ 14-23)፡፡ በአንድ ወቅት የግብፅ ሰራዊት እየገፋ መምጣት፣ የባቢሎንን ተዋጊ ሰራዊት ያፈገፍግ ዘንድ አስገደደው፤ ይሁን እንጂ ወረራው ተመልሶ ቀጠለ (37 ፥ 1-10)፡፡ በዚህም ጊዜ ሴዴቅያስ ፍርሀት ያደረበት ሰው ስለ ነበር፣ ኤርምያስ በይሁዳ በሚገኙት ጠላቶቹ ግፍ ደረሰበት (37 ፥ 11-21፤ ምዕ 38)፡፡ በዚህ ወቅት ኢየሩሳሌም የወደቀችበት ዕለት፣ በዓለም ዙሪያ በሚገኙ አይሁድ ዘንድ፣ በአቢብ ወር በዘጠነኛው ቀን በሐዘን የሚታሰብ ሲሆን፣ በብሉይ ኪዳን ውስጥ በእስራኤል ላይ ከፍተኛው የእግዚአብሔር ፍርድ ነበር፡፡ ሴዴቅያስ ለማምለጥ ሲሞክር ተያዘ፤ ወንዶች ልጆቹም ዐይኑ እያየ በፊቱ ታረዱ፤ ዐይኑም ወጣ፤ ከዚያም ከተከታዮቹ ጋር ወደ ባቢሎን ተጋዘ፡፡
ከከተማዪቱና ከቤተ መቅደሱ ውድመት በኋላ የባቢሎን ንጉሥ፣ ጎዶልያስን የይሁዳ ገዥ አድርጎ ሾመው፡፡ ከጥቂት ጊዜ በኋላ (በቂ ማስረጃ በሌለበት ሦስት ወር ወይም ጥቂት ዓመታት ሊሆን ይችላል)፣ ጎዶልያስ ከዳዊት ቤት በሆነው ወገን ተገደለ፤ ይህም አፍቃሬ ግብፅ በሆኑት ሰዎች ቀስቃሽነት ሳይፈጸም አልቀረም፡፡ የብርቱው መከራ ሰለባዎች የሆኑት የባቢሎንን የዐመፅ ምላሽ በመፍራት ኤርምያስንና ባሮክን ዐብረዋቸው እንዲሸሹ በማስገደድ ወደ ግብፅ ወረዱ፡፡ ስለዚህ ከምእት ዓመታት በፊት በሙሴ አማካይነት ከፈርዖን ትድግና የተገኘበት ዑደት በዚህ ጊዜ ፍጻሜ ላይ ደረሰ፡፡ ሌላው የሚያስገርመው ጒዳይ ደግሞ በአገልግሎቱ ዘመን ሁሉ በግብፅ ላይ እንዳይታመኑ ሲመክር የነበረው ኤርምያስ ያለፈቃዱ የምድር ሕይወቱን በዚያ እንዲጨርስ መደረጉ ነው፡፡ ስለዚህ በእስራኤል ውስጥ ዐይነተኛ ዘመን የነበረው መለኮታዊ አገዛዝ አከተመ፡፡ በሴሎ የማደሪያው ድንኳን መውደሙም የመሳፍንትን ዘመን ደመደመው፡፡ የሰሎሞን ቤተ መቅደስ መውደም በእስራኤል ዘንድ የንጉሣዊ አገዛዝ ዘመን ማክተሙን አመለከተ፡፡ በቲቶ (ጥጦስ) ዘመን (70 ዓ.ም.) ሁለተኛው ቤተ መቅደስ መውደሙ እስከ ዐዲሱ ዘመን ድረስ እስራኤል በምድሯ ላይ የምትኖርበት ዘመን በአደገኛ ሁኔታ ማክተሙን አመላካች ነበር፡፡
ነገረ መለኮታዊ አጽንዖት
የኤርምያስ መልእክት ጒሉሓን ባሕርያት፣ ለእርሱ ዘመንና ለእኛ ዘመን ዐቢይ ፋይዳ አላቸው፡፡ ኤርምያስ በዕድሜ ዘመኑ ሁሉ የደረሰበትን ሐዘንና ተቃውሞ ለመዝለቅ የበቃው በእግዚአብሔርና እግዚአብሔር በሰጠው ተስፋ ጽኑ እምነት ስለ ነበረው ነው (18+7! 29:14: 32:1-5):: የሕይወቱም የአገልግሎቱም ሁለት ትኲረቶች እግዚአብሔር (ማለት ቸርነቱ፣ በሰው ዘር ላይ ያለው ባለቤትነቱ፣ ንስሓና እምነት እውን ይሆኑ ዘንድ ግድ መሰኘቱ) እና ተንከራታች ሕዝቡ ሲሆኑ፣ ይህም የሥጋዊና የመንፈሳዊ ሕይወታቸውን ደኅንነት ያካትታል፡፡
ኤርምያስ እግዚአብሔር የፍጥረት ሁሉ አምላክ መሆኑን በማመን (27፥5)፣ ስለ እግዚአብሔር ከፍ ያለ ሐሳብ አለው፡፡ የአሕዛብ አማልክት ህልውና የላቸውም (10፥11 (በአራማይስጥ ቋንቋ መጽሐፍ ውስጥ ብቸኛ ጥቅስ ነው)፤ 14 14፥ 22)፡፡ እግዚአብሔር የሰውን ልብ ክፋት ያውቃል (17፥9-10)፤ ይሁን እንጂ በእርሱ ላይ የሚታመኑትን ለመባረክ በመናፈቅ (17 ፥ 7) ሕዝቡን በጥልቅ ይወዳል (31፥1-3)፡፡ የጣዖት አምልኮና ልበ ደንዳናነት እንዲሁም ንስሓ አልባ አገልግሎት በእርሱ ፊት አስጸያፊዎች ናቸው (19:4-6 14፥12)፡፡ እግዚአብሔርን ሕይወት በሌላቸው ጣዖታት ከመወከል የበለጠ በእርሱ ላይ የሚሰነዘር ስድብ የለም፡፡ ኤርምያስ ያለመታከት በመቃወም ስብከት ያቀረበበት ልዩ ኀጢአት የጣዖት አምልኮ ነበር፡፡ ሦስት ዐይነት ሐሰት አስቈጣው፡-
(1) ንስሓ ይገባ ዘንድ የተደረገውን ጥሪ ሁሉ አልቀበልም እያለ ምንም አልሆንም የሚል ዐመፀኛ የሆነ ከንቱ ዋስትና፣
(2) ሕዝቡን በአደገኛ አስተማማኝነት እንዲሸፈኑ ያደረጉ የሐሰት ነቢያት፣
(3) ጣዖታትን በከንቱ ማምለክ፡፡ አምልኮ ለበኣል፣ ለሞሎክና ለሰማይ ንግሥት (ለኢሽታር) ይደረግ ነበር፡፡ የእነዚህ አማልክት ምስል በቤተ መቅደስ ውስጥ ሳይቀር ተቀምጦ ነበር (32፥34፤ ከ7፥31 ፤ ከ19፥5፤ ከ32 ፥ 35፤ ከ44፥18-19)፡፡
ይቀጥላል...
🚨ማሳሰቢያ የጊዜ አቆጣጠር ካልተጠቀሰ በቀር ዓመተ ቅድመ ክርስቶስ ነው።
ምንጭ፦ የብሉይ ኪዳን ማብራሪያ፤ ገጽ 826
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ክፍል-፮
ነገር ግን መጨረሻው ሩቅ አልነበረም:: በዘጠነኛው የአገዛዝ ዘመኑ (588)፣ ሴዴቅያስ ከፈርዖን ኡፍራ ጋር ግምባር በመግጠም በናቡከደነፆር ላይ ዐመፀ:: ባቢሎን ይሁዳን በመውረር ምላሽ ሰጥታ በ586 ከተማዋ በእጇ ስትወድቅ ወረራው ፍጻሜ ላይ ደረሰ (2ነገ 36፥17፤ ኤር 38 ፥ 28-39፥ 10)፡፡ በወረራው ዘመን ሁሉ ሴዴቅያስ እጁን ይሰጥ ዘንድ ኤርምያስ አደፋፈረው (21 ፥ 1-10 ፤ 34፥ 1-5፤ 17-22 37 ፥ 3-10፤ 16-17 ፤ 38፥ 14-23)፡፡ በአንድ ወቅት የግብፅ ሰራዊት እየገፋ መምጣት፣ የባቢሎንን ተዋጊ ሰራዊት ያፈገፍግ ዘንድ አስገደደው፤ ይሁን እንጂ ወረራው ተመልሶ ቀጠለ (37 ፥ 1-10)፡፡ በዚህም ጊዜ ሴዴቅያስ ፍርሀት ያደረበት ሰው ስለ ነበር፣ ኤርምያስ በይሁዳ በሚገኙት ጠላቶቹ ግፍ ደረሰበት (37 ፥ 11-21፤ ምዕ 38)፡፡ በዚህ ወቅት ኢየሩሳሌም የወደቀችበት ዕለት፣ በዓለም ዙሪያ በሚገኙ አይሁድ ዘንድ፣ በአቢብ ወር በዘጠነኛው ቀን በሐዘን የሚታሰብ ሲሆን፣ በብሉይ ኪዳን ውስጥ በእስራኤል ላይ ከፍተኛው የእግዚአብሔር ፍርድ ነበር፡፡ ሴዴቅያስ ለማምለጥ ሲሞክር ተያዘ፤ ወንዶች ልጆቹም ዐይኑ እያየ በፊቱ ታረዱ፤ ዐይኑም ወጣ፤ ከዚያም ከተከታዮቹ ጋር ወደ ባቢሎን ተጋዘ፡፡
ከከተማዪቱና ከቤተ መቅደሱ ውድመት በኋላ የባቢሎን ንጉሥ፣ ጎዶልያስን የይሁዳ ገዥ አድርጎ ሾመው፡፡ ከጥቂት ጊዜ በኋላ (በቂ ማስረጃ በሌለበት ሦስት ወር ወይም ጥቂት ዓመታት ሊሆን ይችላል)፣ ጎዶልያስ ከዳዊት ቤት በሆነው ወገን ተገደለ፤ ይህም አፍቃሬ ግብፅ በሆኑት ሰዎች ቀስቃሽነት ሳይፈጸም አልቀረም፡፡ የብርቱው መከራ ሰለባዎች የሆኑት የባቢሎንን የዐመፅ ምላሽ በመፍራት ኤርምያስንና ባሮክን ዐብረዋቸው እንዲሸሹ በማስገደድ ወደ ግብፅ ወረዱ፡፡ ስለዚህ ከምእት ዓመታት በፊት በሙሴ አማካይነት ከፈርዖን ትድግና የተገኘበት ዑደት በዚህ ጊዜ ፍጻሜ ላይ ደረሰ፡፡ ሌላው የሚያስገርመው ጒዳይ ደግሞ በአገልግሎቱ ዘመን ሁሉ በግብፅ ላይ እንዳይታመኑ ሲመክር የነበረው ኤርምያስ ያለፈቃዱ የምድር ሕይወቱን በዚያ እንዲጨርስ መደረጉ ነው፡፡ ስለዚህ በእስራኤል ውስጥ ዐይነተኛ ዘመን የነበረው መለኮታዊ አገዛዝ አከተመ፡፡ በሴሎ የማደሪያው ድንኳን መውደሙም የመሳፍንትን ዘመን ደመደመው፡፡ የሰሎሞን ቤተ መቅደስ መውደም በእስራኤል ዘንድ የንጉሣዊ አገዛዝ ዘመን ማክተሙን አመለከተ፡፡ በቲቶ (ጥጦስ) ዘመን (70 ዓ.ም.) ሁለተኛው ቤተ መቅደስ መውደሙ እስከ ዐዲሱ ዘመን ድረስ እስራኤል በምድሯ ላይ የምትኖርበት ዘመን በአደገኛ ሁኔታ ማክተሙን አመላካች ነበር፡፡
ነገረ መለኮታዊ አጽንዖት
የኤርምያስ መልእክት ጒሉሓን ባሕርያት፣ ለእርሱ ዘመንና ለእኛ ዘመን ዐቢይ ፋይዳ አላቸው፡፡ ኤርምያስ በዕድሜ ዘመኑ ሁሉ የደረሰበትን ሐዘንና ተቃውሞ ለመዝለቅ የበቃው በእግዚአብሔርና እግዚአብሔር በሰጠው ተስፋ ጽኑ እምነት ስለ ነበረው ነው (18+7! 29:14: 32:1-5):: የሕይወቱም የአገልግሎቱም ሁለት ትኲረቶች እግዚአብሔር (ማለት ቸርነቱ፣ በሰው ዘር ላይ ያለው ባለቤትነቱ፣ ንስሓና እምነት እውን ይሆኑ ዘንድ ግድ መሰኘቱ) እና ተንከራታች ሕዝቡ ሲሆኑ፣ ይህም የሥጋዊና የመንፈሳዊ ሕይወታቸውን ደኅንነት ያካትታል፡፡
ኤርምያስ እግዚአብሔር የፍጥረት ሁሉ አምላክ መሆኑን በማመን (27፥5)፣ ስለ እግዚአብሔር ከፍ ያለ ሐሳብ አለው፡፡ የአሕዛብ አማልክት ህልውና የላቸውም (10፥11 (በአራማይስጥ ቋንቋ መጽሐፍ ውስጥ ብቸኛ ጥቅስ ነው)፤ 14 14፥ 22)፡፡ እግዚአብሔር የሰውን ልብ ክፋት ያውቃል (17፥9-10)፤ ይሁን እንጂ በእርሱ ላይ የሚታመኑትን ለመባረክ በመናፈቅ (17 ፥ 7) ሕዝቡን በጥልቅ ይወዳል (31፥1-3)፡፡ የጣዖት አምልኮና ልበ ደንዳናነት እንዲሁም ንስሓ አልባ አገልግሎት በእርሱ ፊት አስጸያፊዎች ናቸው (19:4-6 14፥12)፡፡ እግዚአብሔርን ሕይወት በሌላቸው ጣዖታት ከመወከል የበለጠ በእርሱ ላይ የሚሰነዘር ስድብ የለም፡፡ ኤርምያስ ያለመታከት በመቃወም ስብከት ያቀረበበት ልዩ ኀጢአት የጣዖት አምልኮ ነበር፡፡ ሦስት ዐይነት ሐሰት አስቈጣው፡-
(1) ንስሓ ይገባ ዘንድ የተደረገውን ጥሪ ሁሉ አልቀበልም እያለ ምንም አልሆንም የሚል ዐመፀኛ የሆነ ከንቱ ዋስትና፣
(2) ሕዝቡን በአደገኛ አስተማማኝነት እንዲሸፈኑ ያደረጉ የሐሰት ነቢያት፣
(3) ጣዖታትን በከንቱ ማምለክ፡፡ አምልኮ ለበኣል፣ ለሞሎክና ለሰማይ ንግሥት (ለኢሽታር) ይደረግ ነበር፡፡ የእነዚህ አማልክት ምስል በቤተ መቅደስ ውስጥ ሳይቀር ተቀምጦ ነበር (32፥34፤ ከ7፥31 ፤ ከ19፥5፤ ከ32 ፥ 35፤ ከ44፥18-19)፡፡
ይቀጥላል...
🚨ማሳሰቢያ የጊዜ አቆጣጠር ካልተጠቀሰ በቀር ዓመተ ቅድመ ክርስቶስ ነው።
ምንጭ፦ የብሉይ ኪዳን ማብራሪያ፤ ገጽ 826
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤3👍3👏1
በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ "ነቢይ" ተብሎ የተጠራው ሰው ማን?
Anonymous Quiz
15%
ሀ. ኤልያስ
31%
ለ. አብርሃም
8%
ሐ. ኖኅ
36%
መ. ሙሴ
8%
ሠ. ኢሳይያስ
2%
ረ. ዳዊት
👍7
. ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“እርሱ ግን ስለ ኃጢአት አንድን መሥዋዕት ለዘላለም አቅርቦ በእግዚአብሔር ቀኝ ተቀመጠ፥”
ዕብራውያን 10፥12
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“እርሱ ግን ስለ ኃጢአት አንድን መሥዋዕት ለዘላለም አቅርቦ በእግዚአብሔር ቀኝ ተቀመጠ፥”
ዕብራውያን 10፥12
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍4
በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ ንጉሡ ዳዊት ሲነግስ ለመጀመሪያ ጊዜ የነገሰው የት ነበር?
Anonymous Quiz
15%
ሀ. ኢየሩሳሌም
18%
ለ. ቤተልሔም
17%
ሐ. ሴሎ
41%
መ. ኬብሮን
9%
ሠ. ቤቴል
👍4
#እራሳችንን_እንመርምር
ነገ ስናስብ ተራራ የሚያሳክልብንና በጭንቅ የሚወረን ለነገ ያለን መመካት ነው። ዛሬ ነገ ላይ ይኖራሉ ያልናቸው ነገሮች ላይኖሩ እንደሚችሉ ምን ያክሎቻችን በእርግጥ እናውቀዋለን? ዛሬ ላይ ሆነን፣ ነገ አልታየኝም ማለት ነገ ይጨልማል ያለው ማን ነው?
“ቀን የሚያመጣውን ምን እንደ ሆነ አታውቅምና ነገ በሚሆነው አትመካ።”
ምሳሌ 27፥1
“ራሳችሁን ከፍቅረ ንዋይ ጠብቁ፤ ባላችሁ ነገር ረክታችሁ ኑሩ፤ ምክንያቱም እግዚአብሔር፣ “ከቶ አልተውህም፤ በፍጹም አልጥልህም” ብሎአል።”
ዕብራውያን 13፥5 (አዲሱ መ.ት)
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ነገ ስናስብ ተራራ የሚያሳክልብንና በጭንቅ የሚወረን ለነገ ያለን መመካት ነው። ዛሬ ነገ ላይ ይኖራሉ ያልናቸው ነገሮች ላይኖሩ እንደሚችሉ ምን ያክሎቻችን በእርግጥ እናውቀዋለን? ዛሬ ላይ ሆነን፣ ነገ አልታየኝም ማለት ነገ ይጨልማል ያለው ማን ነው?
“ቀን የሚያመጣውን ምን እንደ ሆነ አታውቅምና ነገ በሚሆነው አትመካ።”
ምሳሌ 27፥1
“ራሳችሁን ከፍቅረ ንዋይ ጠብቁ፤ ባላችሁ ነገር ረክታችሁ ኑሩ፤ ምክንያቱም እግዚአብሔር፣ “ከቶ አልተውህም፤ በፍጹም አልጥልህም” ብሎአል።”
ዕብራውያን 13፥5 (አዲሱ መ.ት)
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍4
. ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“ቅጥር እንደሌላት እንደ ፈረሰች ከተማ፥ መንፈሱን የማይከለክል ሰው እንዲሁ ነው።”
ምሳሌ 25፥28
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“ቅጥር እንደሌላት እንደ ፈረሰች ከተማ፥ መንፈሱን የማይከለክል ሰው እንዲሁ ነው።”
ምሳሌ 25፥28
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤2
የጠጣር ልብ አደገኛ ውጤቶች
የምንኖርበት ጊዜ ልባችንን ልያጠጥር ስለሚችል ከመቼውም ጊዜ በበለጠ ልባችንን በትኩረት መከታተል አለብን ፡፡
በአንድ ሌሊት አይከሰትም። አንድ ሰው ከእግዚአብሔር ጋር በንቁ ጉዞ ሊኖር ይችላል ከዚያም ቀስ በቀስ ወደ ደረቅነት ወደ ሚቀዘቅዘው ይሸጋገራል፡፡ ትክክል የሆነውን ያውቃሉ ፡፡ ግን ከእንግዲህ ግድ የላቸውም ፡፡ ግዴለሽነት ልባቸውን ይገዛል። የሌላውን ችግር እንደራስ በቀላሉ ማግኘት አይቻልም። በአንድ ወቅት እምነት ጠንካራ እና ንቁ ነበር ፣ መቀዝቀዝ ፣ ጥርጣሬ እና ነቀፋ ወረረዉ፡፡ ልጅ-መሰል እምነት ይቀልጣል እናም እንቅፋትን ይታገሱታል።
ልብን መለወጥ እንዴት ከባድ ነው ጠንካራ ልብን ማዳበር የምንችልባቸው የተለያዩ መንገዶች አሉ ፣ ግን ሁለት ዋናዎች መጥቀስ ተገቢ ነው-
1. እዉነትን መስማት ግን ተግባራዊ አለማድረግ፡፡
ጠንካራ ልብ በቀላሉ ሊያድግ ከሚችልበት አንድ ትልቁ መንገድ ምን ማድረግ እንዳለብን ስናውቅ እርምጃ ሳንወስድ ስንቀር ነው፡፡ የምንኖረው ከማንኛውም የበለጠ እውቀት እና ማስተዋል በሚገኝበት ትውልድ ውስጥ ነው። ሁልጊዜ እውነትን ለመስማት እድል አለን ፡፡ ችግሩ ፣ ብዙ እንሰማለን ፣ ግን በጣም ትንሽ ነገር ላይ እርምጃ እንወስዳለን፡፡
እኛ በታላላቅ አስተማሪዎች ተከብበናል ፣ ግን ብዙዎች ስለእሱ ምንም አያደርጉም ፣ ይህም ውሎ አድሮ ጠንካራ እና ቀዝቃዛ ወደ ሆነው ልብ እንዲያድጉ ያደርጋቸዋል ፡፡
ብዙዎች የሆነ ነገር በመስማታቸው ምክንያት “እናዉቃለን” ብለው በማሰብ ተታለዋል ። ግን ያ እውነት በዕለት ተዕለት ኑሯቸው ውስጥ ንቁ እውነታ አይደለም ፡፡እውነት በእዉነታዉ ላይ ተግባራዊ ካልተደረገ እና በውሳኔዎችም ውስጥ እንዲታይ እስካልተፈቀደ ድረስ እውነት ትርጉም የለውም። ሌሎች ትክክል የሆነውን ነገር በትክክል ያውቃሉ ፣ ግን እርምጃ ላለመውሰድ ይመርጣሉ። የክርስትና ሕይወት ግቡ የሰማችሁትን መውሰድ ነው ፣ ያዕቆብ 1፥22 እንደሚናገረው “ቃሉን የምታደርጉ እንጂ የምትሰሙ ብቻ አትሁኑ” ፡፡
በአንዳንድ መንገዶች ፣ አንድ ጠንካራ ልብ ለመጽሐፍ ቅዱስ እውነት የተጋለጠ ሰው ግን በነገሩ ምንም ባለማድረግ ሊገለፅ ይችላል፡፡
2. የልብዎ ችግር በጊዜ መፍትሄ አለማግኘቱ፡፡
ጠንካራ ልብ የሚያዳብርበት ዋነኛው ምክንያት የተሰበሩ ልምዶች እና የተሰበሩ ጉዳዮች ሁልጊዜ የሚያስፈልገውን ፈውስ የማይቀበሉ ከሆነ ነው። አሁን ሰዎች በብዛት ከባድ እየሆኑ ነው ምክንያቱም እግዚአብሔር የሕይወታቸውን ጥልቅ ሥቃይ እንዲፈውስ ስላልፈቀዱ ነው ፡፡
ቅሬታ፣ ለሌሎች አለማሰብ ጠንካራ ልብ ሊያዳብሩ ከሚችሉ ዋና ነገሮች ነገሮች አንዱ ነው፡፡ ጠንካራ ልብን ካሸናፊዎቹ የሚለየው ቅሬታን እንዴት መወጣት አለመቻሉ ነው፡፡
በስህተት የተያዘ እና ጥልቅ ቅሬታ የልብ ገዳይ ሊሆን ይችላል ፡፡ጥልቅ የህመማችን ቅሬታ ለማከም ካልሞከርን ወደ ቂም መያዝ ፣ መለያየት እና ወደ የከፋ መቀዝቀዝ ያመራናል፡፡ የልብ ጡንቻዎቻችን ያላቅቅብናል፡፡
ሁሉም ሰው ለብስጭት እና ለችግሮች የራሱ ድርሻ አለው። ብዙዎች በሥቃይ ውስጥ እግዚአብሔርን መጋበዝ ይመርጣሉ ፡፡ ምንም እንኳን እጅግ በጣም ከባድ ቢሆንም ፣ ከዚህ በፊት የማያውቋቸውን የእግዚአብሔር ተፈጥሮ ገጽታዎችን ያያሉ ፡፡ በመከራ ፣ በማጣት በብስጭት ጊዜያት ታላቅ ጥንካሬ እና ብስለት ያገኛሉ። ሆኖም በተመሳሳይ ጊዜ ፣ ብዙዎች በመንፈስ እና በስሜት ይወሰዳሉ፡፡
በተጎዳን ወይም በተቃጠልንባቸው ወቅቶች ውስጥ ማለፍ እንችላለን እናም እግዚአብሔር ጠንካራ ቦታዎችን በማለስለስ ልባችንን መፈወስ ይፈልጋል ፡፡ ለጥንካሬ ተስፋ አለ ፡፡ነገር ግን ያ ጥንካሬ የማይጣስበት ጊዜ ይመጣል ፡፡ እግዚአብሔር ራሱ በፊትህ ሊወጣ ይችላል እናም ምንም ነገር አይለውጠዉም ፡፡
ይቀጥላል...
ምንጭ:- www.hiyawkal.org
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የምንኖርበት ጊዜ ልባችንን ልያጠጥር ስለሚችል ከመቼውም ጊዜ በበለጠ ልባችንን በትኩረት መከታተል አለብን ፡፡
በአንድ ሌሊት አይከሰትም። አንድ ሰው ከእግዚአብሔር ጋር በንቁ ጉዞ ሊኖር ይችላል ከዚያም ቀስ በቀስ ወደ ደረቅነት ወደ ሚቀዘቅዘው ይሸጋገራል፡፡ ትክክል የሆነውን ያውቃሉ ፡፡ ግን ከእንግዲህ ግድ የላቸውም ፡፡ ግዴለሽነት ልባቸውን ይገዛል። የሌላውን ችግር እንደራስ በቀላሉ ማግኘት አይቻልም። በአንድ ወቅት እምነት ጠንካራ እና ንቁ ነበር ፣ መቀዝቀዝ ፣ ጥርጣሬ እና ነቀፋ ወረረዉ፡፡ ልጅ-መሰል እምነት ይቀልጣል እናም እንቅፋትን ይታገሱታል።
ልብን መለወጥ እንዴት ከባድ ነው ጠንካራ ልብን ማዳበር የምንችልባቸው የተለያዩ መንገዶች አሉ ፣ ግን ሁለት ዋናዎች መጥቀስ ተገቢ ነው-
1. እዉነትን መስማት ግን ተግባራዊ አለማድረግ፡፡
ጠንካራ ልብ በቀላሉ ሊያድግ ከሚችልበት አንድ ትልቁ መንገድ ምን ማድረግ እንዳለብን ስናውቅ እርምጃ ሳንወስድ ስንቀር ነው፡፡ የምንኖረው ከማንኛውም የበለጠ እውቀት እና ማስተዋል በሚገኝበት ትውልድ ውስጥ ነው። ሁልጊዜ እውነትን ለመስማት እድል አለን ፡፡ ችግሩ ፣ ብዙ እንሰማለን ፣ ግን በጣም ትንሽ ነገር ላይ እርምጃ እንወስዳለን፡፡
እኛ በታላላቅ አስተማሪዎች ተከብበናል ፣ ግን ብዙዎች ስለእሱ ምንም አያደርጉም ፣ ይህም ውሎ አድሮ ጠንካራ እና ቀዝቃዛ ወደ ሆነው ልብ እንዲያድጉ ያደርጋቸዋል ፡፡
ብዙዎች የሆነ ነገር በመስማታቸው ምክንያት “እናዉቃለን” ብለው በማሰብ ተታለዋል ። ግን ያ እውነት በዕለት ተዕለት ኑሯቸው ውስጥ ንቁ እውነታ አይደለም ፡፡እውነት በእዉነታዉ ላይ ተግባራዊ ካልተደረገ እና በውሳኔዎችም ውስጥ እንዲታይ እስካልተፈቀደ ድረስ እውነት ትርጉም የለውም። ሌሎች ትክክል የሆነውን ነገር በትክክል ያውቃሉ ፣ ግን እርምጃ ላለመውሰድ ይመርጣሉ። የክርስትና ሕይወት ግቡ የሰማችሁትን መውሰድ ነው ፣ ያዕቆብ 1፥22 እንደሚናገረው “ቃሉን የምታደርጉ እንጂ የምትሰሙ ብቻ አትሁኑ” ፡፡
በአንዳንድ መንገዶች ፣ አንድ ጠንካራ ልብ ለመጽሐፍ ቅዱስ እውነት የተጋለጠ ሰው ግን በነገሩ ምንም ባለማድረግ ሊገለፅ ይችላል፡፡
2. የልብዎ ችግር በጊዜ መፍትሄ አለማግኘቱ፡፡
ጠንካራ ልብ የሚያዳብርበት ዋነኛው ምክንያት የተሰበሩ ልምዶች እና የተሰበሩ ጉዳዮች ሁልጊዜ የሚያስፈልገውን ፈውስ የማይቀበሉ ከሆነ ነው። አሁን ሰዎች በብዛት ከባድ እየሆኑ ነው ምክንያቱም እግዚአብሔር የሕይወታቸውን ጥልቅ ሥቃይ እንዲፈውስ ስላልፈቀዱ ነው ፡፡
ቅሬታ፣ ለሌሎች አለማሰብ ጠንካራ ልብ ሊያዳብሩ ከሚችሉ ዋና ነገሮች ነገሮች አንዱ ነው፡፡ ጠንካራ ልብን ካሸናፊዎቹ የሚለየው ቅሬታን እንዴት መወጣት አለመቻሉ ነው፡፡
በስህተት የተያዘ እና ጥልቅ ቅሬታ የልብ ገዳይ ሊሆን ይችላል ፡፡ጥልቅ የህመማችን ቅሬታ ለማከም ካልሞከርን ወደ ቂም መያዝ ፣ መለያየት እና ወደ የከፋ መቀዝቀዝ ያመራናል፡፡ የልብ ጡንቻዎቻችን ያላቅቅብናል፡፡
ሁሉም ሰው ለብስጭት እና ለችግሮች የራሱ ድርሻ አለው። ብዙዎች በሥቃይ ውስጥ እግዚአብሔርን መጋበዝ ይመርጣሉ ፡፡ ምንም እንኳን እጅግ በጣም ከባድ ቢሆንም ፣ ከዚህ በፊት የማያውቋቸውን የእግዚአብሔር ተፈጥሮ ገጽታዎችን ያያሉ ፡፡ በመከራ ፣ በማጣት በብስጭት ጊዜያት ታላቅ ጥንካሬ እና ብስለት ያገኛሉ። ሆኖም በተመሳሳይ ጊዜ ፣ ብዙዎች በመንፈስ እና በስሜት ይወሰዳሉ፡፡
በተጎዳን ወይም በተቃጠልንባቸው ወቅቶች ውስጥ ማለፍ እንችላለን እናም እግዚአብሔር ጠንካራ ቦታዎችን በማለስለስ ልባችንን መፈወስ ይፈልጋል ፡፡ ለጥንካሬ ተስፋ አለ ፡፡ነገር ግን ያ ጥንካሬ የማይጣስበት ጊዜ ይመጣል ፡፡ እግዚአብሔር ራሱ በፊትህ ሊወጣ ይችላል እናም ምንም ነገር አይለውጠዉም ፡፡
ይቀጥላል...
ምንጭ:- www.hiyawkal.org
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍1
በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ በንጉሡ ዳዊት ዘመን ካህን ማን ነበር?
Anonymous Quiz
9%
ሀ. ሳዶቅ
28%
ለ. ሳሙኤል
21%
ሐ. አብያታር
9%
መ. ኢዮአብ
3%
ሠ. አኪጦፌል
30%
ረ. ሀ እና ሐ
. ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“በዚያም ኢየሱስ እንደ መልከ ጼዴቅ ሹመት ለዘላለም ሊቀ ካህናት የሆነው፥ ስለ እኛ ቀዳሚ ሆኖ ገባ።”
ዕብራውያን 6፥20
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“በዚያም ኢየሱስ እንደ መልከ ጼዴቅ ሹመት ለዘላለም ሊቀ ካህናት የሆነው፥ ስለ እኛ ቀዳሚ ሆኖ ገባ።”
ዕብራውያን 6፥20
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍9