ቅዱሳት መጻሕፍት
7.45K subscribers
1.36K photos
61 videos
332 files
807 links
በዚህ ቻናል

👉ቅዱሳት መጻሕፍት ይጠናሉ::
👉መጽሐፍ ቅዱሳዊ ትምህርቶች ይቀርባሉ::
👉 ለቅዱሳት መጽሐፍት ጥናት የሚያግዙ መጻሕፍት ይለቀቃሉ።

⭐️⭐️⭐️⭐️⭐️

@Holy_scriptures
Download Telegram
#የእግዚአብሔር_ቃል_ምን_ይላል?



1ኛ ጢሞቴዎስ 3
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ ማንም ኤጲስ ቆጶስነትን ቢፈልግ መልካምን ሥራ ይመኛል የሚለው ቃል የታመነ ነው።
² እንግዲህ ኤጲስ ቆጶስ እንዲህ ሊሆን ይገባዋል፤ የማይነቀፍ፥ የአንዲት ሚስት ባል፥ ልከኛ፥ ራሱን የሚገዛ፥ እንደሚገባው የሚሰራ፥ እንግዳ ተቀባይ፥ ለማስተማር የሚበቃ፥
³ የማይሰክር፥ የማይጨቃጨቅ ነገር ግን ገር የሆነ፥ የማይከራከር፥ ገንዘብን የማይወድ፥
⁴ ልጆቹን በጭምትነት ሁሉ እየገዛ የራሱን ቤት በመልካም የሚያስተዳድር፤
⁵ ሰው ግን የራሱን ቤት እንዲያስተዳድር ባያውቅ፥ የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያን እንዴት ይጠብቃታል?
⁶ በትዕቢት ተነፍቶ በዲያብሎስ ፍርድ እንዳይወድቅ፥ አዲስ ክርስቲያን አይሁን።
⁷ በዲያብሎስ ነቀፋና ወጥመድም እንዳይወድቅ፥ በውጭ ካሉት ሰዎች ደግሞ መልካም ምስክር ሊኖረው ይገባዋል።
⁸ እንዲሁም ዲያቆናት ጭምቶች፥ በሁለት ቃል የማይናገሩ፥ ለብዙ ወይን ጠጅ የማይጎመጁ፥
⁹ ነውረኛ ረብ የማይወዱ፥ በንጹሕ ሕሊና የሃይማኖትን ምሥጢር የሚይዙ ሊሆኑ ይገባቸዋል።
¹⁰ እነዚህም ደግሞ አስቀድሞ ይፈተኑ፥ ከዚያም በኋላ ያለ ነቀፋ ቢሆኑ በዲቁና ሥራ ያገልግሉ።
¹¹ እንዲሁም ሴቶች ጭምቶች፥ የማያሙ፥ ልከኞች፥ በነገር ሁሉ የታመኑ ሊሆኑ ይገባቸዋል።
¹² ዲያቆናት ልጆቻቸውንና የራሳቸውን ቤቶች በመልካም እየገዙ እያንዳንዳቸው የአንዲት ሴት ባሎች ይሁኑ።
¹³ በዲቁና ሥራ በመልካም ያገለገሉ ለራሳቸው ትልቅ ማዕርግና በክርስቶስ ኢየሱስ ባለው እምነት ብዙ ድፍረት ያገኛሉ።
¹⁴ ፈጥኜ ወደ አንተ እንድመጣ ተስፋ አድርጌ ይህን እጽፍልሃለሁ።
¹⁵ ብዘገይ ግን፥ በእግዚአብሔር ማደሪያ ቤት መኖር እንዴት እንደሚገባ ታውቅ ዘንድ እጽፍልሃለሁ፤ ቤቱም የእውነት ዓምድና መሠረት፥ የሕያው እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያን ነው።
¹⁶ እግዚአብሔርንም የመምሰል ምሥጢር ያለ ጥርጥር ታላቅ ነው፤ በሥጋ የተገለጠ፥ በመንፈስ የጸደቀ፥ ለመላእክት የታየ፥ በአሕዛብ የተሰበከ፥ በዓለም የታመነ፥ በክብር ያረገ።




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
4👏3👍2
.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“ለእናንተም የምነግራችሁ ለሁሉ እላለሁ፤ ትጉ።”
ማርቆስ 13፥37



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍64
የሚከተለው ጥቅስ የየትኛው የቅዱሳት መጻሕፍት መግቢያ ነው? “...በእግዚአብሔር ለተመረጡት እምነት እንዲሆንላቸው በዘላለምም ሕይወት ተስፋ እንደ አምልኮት ያለውን እውነት እንዲያውቁ የተላከ፤ ”
Anonymous Quiz
33%
ሀ. 2ኛ ዮሐንስ
8%
ለ. ፊልሞና
11%
ሐ. ፊልጵስዩስ
25%
መ. ቲቶ
24%
ሠ. 2ኛ ተሰሎንቄ
👏8
ቅዱሳት መጻሕፍት
ነቢዩ ኤርምያስ                         ክፍል-፬ ኤርምያስ በነበረበት ዘመን ገዦች እነማን ነበሩ? ኢዮስያስ ወደ ዙፋን የመጣው ገና የስምንት ዓመት ልጅ እያለ ነው፡፡ በፖለቲካ ረገድ ህልውናዋን ለመጠበቅ እየተከለከለች ሳለ፣ አሦር በባቢሎን ብርቱ ፍጥጫ ሥር ወድቃ ነበር፡፡ ይህም ሁኔታ ለይሁዳ ከአምልኮዋ ውስጥ የአሦርን ቅይጥ ነገሮች ለማስወገድ የላቀ ነጻነት አመጣለት፡፡ በ633…
ነቢዩ ኤርምያስ




                        ክፍል-


በኢዮአቄም የዐሥራ አንድ ዓመት ዘመነ መንግሥት ውስጥ የከርከሚሽ ጦርነት ተካሄደ (ከ46 ፥ 2 ጋር ያነጻ)፡፡ በመካከለኛው ምሥራቅ የኀይል ሚዛን ከግብፅ ወደ ባቢሎን መተላለፉን ያመላከተ ስለ ሆነ፣ ዘላቂ ፋይዳ ያለው ሁኔታ (ክሥተት) ነበር፡፡ ይህ ሽንፈት በግብፅ የመስፋፋት ምኞት ላይ የመጨረሻ በትር ሲሆን፤ ከለዳውያን በምዕራቡ ዓለም ላይ የበላይነት እንዲኖራቸው ዋስትናን ሰጠ፡፡ ይህ ሁኔታ ለዘመኑ ወደ ዐዲስ ምዕራፍ መሸጋገሪያ ነበር፤ ለእስራኤልም የወደፊት ዕጣ ፈንታ ዐቢይ ሚና ነበረው፡፡ ባቢሎናውያን ኢዮአቄምን በሥልጣናቸው ሥር ገዥ (መስፍን) አልባ አደረጉት፤ ጥቂት የማይባሉትን የአይሁድ መሳፍንት ያጋዙ ሲሆን (2ነገ 24 ፥ 1)፣ ከእነዚህ ከተጋዙት መካከል ዳንኤል አንዱ ነበር (ዳን 1፥1)፡፡

አንዳንድ ሊቃውንት በናቡደነፆር ይህ የኢየሩሳሌም ለመጀመሪያ ጊዜ መወሰድ የአይሁድ የሰባ ዓመት፣ የባቢሎን ግዞት መጀመሪያ ነው ይላሉ (25፥11)፤ ከዚህም ጋር የዳዊት ሥርወ መንግሥት መፍረስ ጀምሮ ነበር፡፡

ኢዮአቄም የጣዖት አምልኮን ደገፈ፤ በመንግሥቱ በሰፊው ይካሄድ ለነበረው ማኅበራዊ ኢፍትሓዊነትም ደንታ አልነበረውም (22 ፥ 13-19 2ነገ23፥37)፡፡ ኤርምያስ በዘመነ ንግሣቸው ትንቢቱን መናገር ከቀጠለባቸው ነገሥታት መካከል ኢዮአቄም የእግዚአብሔር መልእክትና የእግዚአብሔር መልእክተኛ ደመኛ ጠላት ነበር (ከ26 ፥ 20-23 ፤ ከ36 ፥ 20-26)፡፡ በ598-597 በባቢሎን ላይ ዐመፀ፤ ነገር ግን አልተሳካለትም፤ ከዚህም የተነሣ የይሁዳን መከራ አባባሰው (2ነገ 24 ፥ 1-5)፡፡ በኢዮአቄም ዘመነ መንግሥት ኤርምያስ ሥቃይ ደረሰበት፤ አሤሩበት፤ በከንቱ ስሙ ጠፋበት፤ ታሰረም፡፡ ንጉሡ የተጻፈውን ትንቢት አወደመበት፤ ነቢዩ ግን ከመለኮታዊ ተልእኮው አልተነቃነቀም (ከ11፥ 18-23 ፤ ከ12 ፥ 6፤ ከ15፥15-18፤ ከ18፥18፤ ከ20 ፥ 2 ፤ ከ26፥ 10-11:24፤ ከ36፥ 23)፡፡ ኤርምያስ እንደ ተነበየው (22 ፥ 18-19) ኢዮአቄም በዐሥራ አንደኛው ዓመት የሥልጣን ዘመኑ 598-597 በኢየሩሳሌም በዐመፅ ሞተ፡፡ ኢዮአቄም በናቡከደነፆር ሥልጣን ዘመን ወደ ባቢሎን መጋዙን የዜና መዋዕል ጸሓፊ አስፍሮአል (2ዜና 36፥6-7፤ እንዲሁም ዳን 1፥1)፡፡

(መ) ኢዮአኪን፤

የኢዮአቄምን ዙፋን የወረሰው ልጅ ኢዮአኪን ነው እንዲሁም ኢኮንያንና ኮንያ ይባላል [አዲሱ መደበኛ ትርጉም በ22 ፥ 24፤ በ24፥1 ላይ ያለውን ይመልከቱ]፤ በዙፋን ላይ የቈየውም ሦስት ወር ብቻ ነው (ከ2ነገ 24፥8)፡፡ ነገር ግን ይህ በዐሥራዎቹ የዕድሜ ዘመኑ መግዛት የጀመረው ንጉሥ ጨካኝ ንጉሥነቱን ጒልሕ አስኪያደርግ ድረስ በሥልጣን ላይ ቈየ፤ ይህንኑ ጨካኝ ንጉሥም ኤርምያስ በብርቱ አወገዘው (22፥24-30)፡፡ በባቢሎን ላይ የኢዮአኪን አባት ያካሄደው ዐመፅም በ597 ናቡከደነፆር ኢየሩሳሌምን እንዲወርር አስገደደው፤ ይህም ኢዮአኪን መሸነፉን አምኖ በተቀበለ ጊዜ ነበር (2ነገ 24፥17)፡፡ እርሱም ከብዙ የይሁዳ ገዥ መደቦች ጋር (ከእነርሱ መካከል ነቢዩ ሕዝቅኤል ይገኝ ነበር [ሕዝ 1፥2] ወደ ባቢሎን ተጋዘ፤ ቤተ መቅደሱም ተመዘበረ (2ነገ 24 ፥ 10-16)፡፡ ኢዮአኪን ሠላሳ ሰባት ዓመት ሙሉ በባቢሎን እስረኛ ነበር፡፡ በክፉው በአልጋ ወራሹ፤ በናቡከደነፆር ልጅ በዮርማሮዴቅ ከእስራት ነጻ ሆነ (2ነገ 25 ፥ 27-30)፡፡ አይሁድ እርሱ በዳዊት ዙፋን ላይ ተመልሶ ይነግሣል ብለው ለረዥም ዘመናት ባልተለመደ ሁኔታ ተስፋ ያደርጉ ነበር፡፡ ሕዝቅያስም ንጉሥ ሆኖ በእግሬ ይተካል ያለው ሴዴቅያስን ሳይሆን ኢዮአኪንን ነበር፡፡

(ሠ) ሴዴቅያስ፤

ታላቁ ናቡከደነፆር ካከናወናቸው አያሌ ተግባሮች መካከል ንጉሥ አድርጎ መሾምና ስም መለወጥ ይገኛ ሉ፡፡ ናቡከደነፆር ኢዮአኪንን ካጋዘ በኋላ የኢዮስያስን ልጅ ፤ የኢዮአኪንም አጎት የሆነውን ማታንያንን በይሁዳ ዙፋን ላይ አስቀመጠው፤ ስሙንም ሴዴቅያስ ብሎ ለወጠው (2ነገ 23 ፥ 34 ፤ 24 17: 2ዜና 36 10 ኤር 13) ይህም ሐቅ በባቢሎናውያን ዜና መዋዕል የተረጋገጠ ነው፡፡ የሴዴቅያስ ዘመነ መንግሥት ገና እንደ ተጀመረ፣ ይሁዳ ተከታታይ ወረራና ግዞት የደረሰበት ሲሆን፣ ገዦች በተለዋወጡ ቊጥር ተሸራርፎ የቀረው መንግሥት የሊቃውንት መኻን ሆኖአል፡፡ ሲዴቅያስ ደካማ፣ ወላዋይ፣ መልካም ሰብእናም የጐደለው ሰው ነበርና ውጤታማ አስተዳደርን እውን ለማድረግ ከዐቅሙ በላይ ሆኖ አገኘው፡፡ የባቢሎን አሻንጉሊት ሆኖ ለንጉሡ ታጥቆ ለመኖር በእስራኤል አምላክ ስም የማለ ሲሆን፣ በማንኛውም ውሳኔው ላይ አፍቃሬ ግብፅ በሆኑት ሹሞቹ ተጽዕኖ ሥር የሚገኝ ሰው ነበር፡፡

የእግዚአብሔር ሰው የነበረውን ኢዮስያስን አቈይተን፣ ሴዴቅያስ ከኤርምያስ ጋር የነበረው ግንኙነት ቀደም ካሉት የይሁዳ ነገሥታት ይልቅ በጣም የጠበቀ ነበር፡፡ ሆኖም ኤርምያስን ከመሳፍንቱ ተንኰለኛ ዕቅድ ለመጠበቅና ለናቡከደነፆር ይገዙ ዘንድ ኤርምያስ በተደጋጋሚ ይፋ ያደረገውን ከእግዚአብሔር የተቀበለውን ምክር ለመከተል ዐቅም የነበረው ሰው አልነበረም፡፡ ሴዴቅያስ በነገሠ በአራተኛው ዓመት ከኤዶም፣ ከሞዓብ፣ ከአሞን፣ ከጢሮስና ከሲዶን ነገሥታት ጋር ግምባር በመግጠም (27-3-11): በባቢሎን ላይ ዐመፀ:: ተወካዮችን ወደ ኢየሩሳሌም ሲልኩም ዐላማቸው ይህ ነበር፡፡ ይህን ሤራ ኤርምያስ አወገዘው፤ በመጨረሻም ይኸው ሤራ ከንቱ ሆኖ ቀረ:: በዚያው ዓመት ሴዴቅያስ ባቢሎንን የጐበኘበት ምክንያት፣ ታማኝነቱን ለናቡከደነፆር ለመግለጽ ታልሞ ሳይሆን አይቀርም (51፥ 59)፡፡


ይቀጥላል...


🚨ማሳሰቢያ የጊዜ አቆጣጠር ካልተጠቀሰ በቀር ዓመተ ቅድመ ክርስቶስ ነው።



ምንጭ፦ የብሉይ ኪዳን ማብራሪያ፤ ገጽ 825-826




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍5
.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“በክርስቶስ ኢየሱስ ወደ ዘላለም ክብሩ የጠራችሁ የጸጋ ሁሉ አምላክ ለጥቂት ጊዜ መከራን ከተቀበላችሁ በኋላ ራሱ ፍጹማን ያደርጋችኋል ያጸናችሁማል ያበረታችሁማል።”
1ኛ ጴጥሮስ 5፥10



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
7
በሚከተለው በሮሜ መልእክት ውስጥ በተጠቀሰው መሠረት በባዶ ቦታ የሚገባው ስም የማን ነው? "ይህንን መልእክት የጻፍሁ እኔ __ በጌታ ሰላምታ አቀርብላችኋለሁ።"
Anonymous Quiz
69%
ሀ. ሐዋርያው ጳውሎስ
5%
ለ. ጢሞቴዎስ
23%
ሐ. ጤርጥዮስ
2%
መ. በርናባስ
0%
ሠ. ሲላስ
👍41
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍61
የትንቢተ_ኢሳይያስ_የጥናት_መምሪያና_ማብራሪያ.pdf
36.3 MB
👉ርዕስ፦ የትንቢተ ኢሳይያስ የጥናት መምሪያ እና ማብራሪያ በትምህርተ መለኮት ማስፋፊያ (ት.መ.ማ) መልክ የተዘጋጀ
ጸሐፊ፦ ቲም ፌሎውስ
🗣ትርጉም፦ ግርማዊ ቡሾ
🖨አሳታሚ፦ ኤስ አይ ኤም (SIM Publishing)



ይህ በጣም ሰፊ የሆነ በትንቢተ ኢሳይያስ ላይ የሚያተኩረው የጥናት መምሪያ በቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ላይ በተሰማሩ ሰዎች ላይ ሲሆን የጥናት መምሪያውን በብዙ የተለያዩ መንገዶች መጠቀም ይቻላል።

👉በግል የእግዚአብሔርን ቃል ለማጥናት
👉በአዋቂዎች የሰንበት ትምህርት ቤት ወይም
👉በመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ቤት መጠቀም ይቻላል።



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
🔥31
.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“ከአፉም ሕጉን ተቀበል፥ በልብህም ቃሉን አኑር፤”
ኢዮብ 22፥22




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
7🔥6👍3
“በኢየሱስ ክርስቶስ ከሙታንም ባነሣው በእግዚአብሔር አብ ሐዋርያ የሆነ እንጂ ከሰዎች ወይም በሰው ያልሆነ ጳውሎስ...” ይህ ከቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ የየትኛው መጽሐፍ መግቢያ ነው?
Anonymous Quiz
31%
ሀ. ሮሜ
46%
ለ. ገላትያ
8%
ሐ. ፊልጵስዩስ
6%
መ. ቆላስይስ
2%
ሠ. ፊልሞና
6%
ረ. 1ኛ ጢሞቴዎስ
👍4
#እራሳችንን_እንመርምር

በሕይወታችን የሚያደናቅፍ ነገር በሞላበት አልፎም ተርፎ ስንፍገመገም የሚያቆም እና የሚያጸና በሚፈለግበት ጊዜ ረድኤት እና መድኃኒት ከየት ይገኛል?

"ሕግህን የሚወዱ ፍጹም ሰላም ያገኛሉ፤ ሊያደናቅፋቸውም የሚችል አንዳች ነገር የለም።"
መዝሙር 119፥165 (ሕያው ቃል)




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍32
.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“ክፉ ከሆነ ከአሁኑ ዓለም ያድነን ዘንድ እንደ አምላካችንና እንደ አባታችን ፈቃድ ስለ ኃጢአታችን ራሱን ሰጠ።”
ገላትያ 1፥4



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍54
የእግዚአብሔር ቃል እውቀት




ዛሬ በዓለማችን በሃይማኖት ሽፋን ሕሊናን በመሸንገል ለሚመጣው መራራ ቅጣት ራስን የማዘጋጀት ዝንባሌ የሚታየው በእውቀትና በመረዳት ሳይሆን ከእግዚአብሔር ቃል ውጭ በሆነ ከንቱ ሐሳብ በመመራት እንደሆነ ይታያል፡፡ አንዳንድ ጊዜም የተሳሳተ የሃይማኖት ትምህርትን በእግዚአብሔር ቃል ለመደገፍ የሚደረገው ጥረትም ቃሉን ካለመረዳት የመነጨ መሆኑን እናስተውላለን፡፡

ብዙ ዓመታት ያስቆጠረ ውሸት እውነት ሊመስል ቢችል እንኳ ውሸትነቱ መገለጡ አይቀሬ ነው፤ ለዚህም ደግሞ እውነት የሚመስለውን ነገር ሁሉ መርምሮ ለማረጋገጥ ብቸኛው መሣሪያ ጊዜ የማይለውጠው ሕያው የእግዚአብሔር ቃል ብቻ ነው፤ እርሱ ለእኛ እንደ ወንፊት ነው፤ እንክርዳድ የሞላበትን የፈጠራ ትምህርት እንለይበታለን፤ እግዚአብሔር ይመስገን፡፡

መጽሐፍ ቅዱስ የእግዚአብሔርን ቃል የያዘ ብቸኛና ታላቅ መጽሐፍ ነው፤ ይኸም መጽሐፍ የአባቶቻቸውን የቆየና የተሳሳተ መንገድ እንደ ጽድቅ ቆጥረው በመመካት ይጓዙ ለነበሩት የእስራኤል አዲስ ትውልድ ሲናገር «በአባቶቻችሁ ሥርዓት አትሂዱ፣ ወጋቸውንም አትጠብቁ፣ በጣዖቶቻቸውም አትርከሱ» በማለት ያስጠነቅቃል (ሕዝ.20፡18)፡፡

ጌታችን ኢየሱስ የእግዚአብሔርን ቃል ዕውቀት ወደ ጐን በመተው የሰውን ሥርዓት በመጠበቅ ለእርሱ የሚቀኑ የሚመስላቸውን ሰዎች ደጋግሞ ገሥጿል፤ ባሕልና ወግን የሚሰብኩትን የሕግ መምህራንንም «የሰውም ሥርዓት የሆነ ትምህርት እያስተማሩ በከንቱ ያመልኩኛል» (ማቴ.15፡9፣ ማር.7፡1-3) በማለት ተናግሯል፡፡ ይህም ንግግሩ እግዚአብሔርን እንደሚገባ ሳያውቁ የሚቀርብ አምልኮ ከንቱ መሆኑን ያስረዳል፡፡

እርግጥ ነው ለሰዎች ዓይን «መልካም የምትመስል መንገድ አለች፤ ፍጻሜዋ ግን ሞት ነው» እንደተባለው ከጥንት የኖረም ቢሆን እንደ እግዚአብሔር ቃል ያልሆነ መንገድ ሁሉ ፍጻሜው «ሞት» ብቻ ነው (ምሳ.16፡25)፡፡ ነገር ግን ሰው በጌታ በኢየሱስ ብቸኛ አዳኝነት ካመነ ከቀድሞ አባቶቹ ከወረሰው ከንቱ ኑሮ ይድናል፤ ጴጥሮስ ስለዚህ ነገር ሲጽፍ «ከአባቶቻችሁ ከወረሳችሁት ከከንቱ ኑሮአችሁ በሚያልፍ ነገር በብር ወይም በወርቅ ሳይሆን ነውርና እድፍ እንደሌለው እንደ በግ ደም በክቡር የክርስቶስ ደም እንደተዋጃችሁ ታውቃላችሁ» (1ጴጥ.1፡19) ብሏል፡፡

የእግዚአብሔር ቃል እውቀት ጥቅሞች

የእግዚአብሔር ቃል በሰው አንደበት ተነግረው የማያልቁ ብዙ ጥቅሞች እንዳሉት ቃሉን የሚጠቀሙበት ሁሉ ያውቁታል፡፡
የእግዚአብሔር ቃል፦

👉አስተዋይ ለመሆን (መዝ.118፡98፣104)፣
👉ጌታን ላለመበደል (መዝ.118፡11)፣
👉በሥራችን መከናወንን ለማግኘት (ኢያ.1፡7-9)፣

👉የልብ ደስታን ለማግኘት (ኤር.15፡16)፣
👉ለበጎ ሥራ ለመዘጋጀት (2ጢሞ.3፡15)፣
👉ለትምህርታችን (ሮሜ.15፡3-4)፣
👉የክፋት መንፈሳዊ ሠራዊትን ለመዋጋት (ኤፌ.6፡10)፣ ይጠቅማል፡፡ እንደዚሁም የእግዚአብሔር ቃል እውቀት በዚህ ጽሑፍ ውስጥ ቀጥሎ በዝርዝር የምንመለከታቸው ሌሎች ጥቅሞችም አሉት፡፡

1. ላለመሳሳት ይጠቅማል

ሁላችንም የሔዋን መሳሳት እንዴት እንደነበረ እናውቃለን፤ የሔዋንም የመጀመርያ ጥፋቷ ፍሬ ቆርጣ መብላቷ አልነበረም፤ ቀዳሚው ጥፋቷ ከፈጣሪ ቃል ይልቅ የፍጥረትን ድምፅ ማዳመጧ ነበር፡፡ ይህም ድምፅ ፍጹም ወዳጅና ተቆርቋሪ ከሚመስል ጠላት የመጣ ነበር፡፡ ማስጠንቀቂያ ከታከለበት የጌታ ቃል ይልቅ ማባበያ የተሞላው የፍጥረት ድምፅ አሳታት፡፡ ዛሬም ጠላት በምንም ዓይነት ጽድቅን ፊት ለፊት ተቃውሞ አይሰብክም፡፡ ግማሽ እውነት ግማሽ ውሸት በዘመኑ የሚሠራበት የሰይጣን ብልሃት መሆኑ ከታወቀ ውሎ አድሮአል፤ አንድ የቲያትር ተዋናይ(አርቲስት) ገጸ ባሕርይውን መስሎ ለመታየት ብዙ ነገሮችን ሊያደርግ ይችላል፤ ለምሣሌ ሰው ሰራሽ ፂም ሊያደርግ ረዥም ቀሚስ ሊለብስ ይችላል፤ አስመስሎም ይናገራል፤ ነገር ግን ያንን የወከለውን ነገር መሆን አይችልም፤ ከለበሳቸው አልባሳት ውስጥ ያለው ራሱ ነውና፡፡ በመሆኑም እንዲህ ካለው የሰይጣን ማታለል ለመዳን የሚቻልበት ብቸኛው መሣሪያ የእግዚአብሔር ቃል እውቀት ነው፡፡ ሰዎችም ቢሆኑ በተመሣሣይ መንገድ የክርስትናን መልክ ተላብሰው ሊያታልሉ ሲሞክሩ አሁንም መፍትሔው ያው የእግዚአብሔር ቃል እውቀት ነው፡፡


ይቀጥላል...



ምንጭ:- ewnetone.com




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
8👍4
.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“አሁን እኔ ጐሽ ለመባል የምሻው በሰዎች ዘንድ ነው ወይስ በእግዚአብሔር ዘንድ? ወይስ ሰዎችን ደስ ለማሰኘት እየተጣጣርሁ ነው? ሰዎችን ደስ ለማሰኘት የምጥር ብሆን ኖሮ፣ የክርስቶስ አገልጋይ ባልሆንሁ ነበር።”
ገላትያ 1፥10 (አዲሱ መ.ት)




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍5
ቅዱሳት መጻሕፍት
የእግዚአብሔር ቃል እውቀት ዛሬ በዓለማችን በሃይማኖት ሽፋን ሕሊናን በመሸንገል ለሚመጣው መራራ ቅጣት ራስን የማዘጋጀት ዝንባሌ የሚታየው በእውቀትና በመረዳት ሳይሆን ከእግዚአብሔር ቃል ውጭ በሆነ ከንቱ ሐሳብ በመመራት እንደሆነ ይታያል፡፡ አንዳንድ ጊዜም የተሳሳተ የሃይማኖት ትምህርትን በእግዚአብሔር ቃል ለመደገፍ የሚደረገው ጥረትም ቃሉን ካለመረዳት የመነጨ መሆኑን እናስተውላለን፡፡ ብዙ ዓመታት ያስቆጠረ…
የቀጠለ ...

የእግዚአብሔር ቃል እውቀት



የእግዚአብሔር ቃል እውቀት የሌላቸው ሰዎች ትክክለኛው መንገድ (ሃይማኖት) የቱ እንደሆነ መጠየቃቸው የተለመደ ነው፤ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥም የየትኛውም የሃይማኖት ድርጅት ስም ባለመጻፉ የትኛው ሃይማኖት ትክክል እንደሆነ ለማወቅ በመፈለግ ግራ ይጋባሉ፡፡ ነገር ግን ይህ ጥያቄም ሆነ ግራ መጋባት ሊመጣ የሚችለው የእግዚአብሔርን ቃል በጥልቀት ካለመረዳት ነው፤ ምክንያቱም እንደ እግዚአብሔር ቃል ስናስብ እግዚአብሔር ሰዎችን ሁሉ የሚጠራው ልጁን አምኖ ወደመከተል እንጂ ወደ የትኛውም የሃይማኖት ጎራ አይደለምና፡፡

ሰው ላለመሳሳት ከፈለገ ዛሬም ያለው አማራጭ የእግዚአብሔርን ቃል ማወቅና የተጻፈውን ሁሉ አንድም ሳይቀር አምኖ መቀበል ብቻ ነው፤ ይህ ካልሆነ ግን «መጽሐፍ ቅዱስ አለኝ፤ ከቤቴም አኑሬዋለሁ» ማለቱ ብቻውን ከስህተት አያድንም፤ ክብር ይግባውና ጌታ ኢየሱስም መጻሕፍቱ እያሏቸው በእምነት ነገር የሳቱ ፈሪሳውያንን «መጻሕፍትንና የእግዚአብሔርን ኃይል አታውቁምና ትስታላችሁ» ብሎአቸው ነበር፤ (ማቴ.22፡29፣ ማር.12፡24)፡፡

በዕለታዊ ኑሮም ቢሆን ከስህተት የምንጠበቀው የእግዚአብሔር ቃል እውቀት ሲኖረን ነው፤ መዝሙረኛው ዳዊት ስለዚህ ሲናገር «ጐልማሳ መንገዱን በምን ያነፃል? ቃልህን በመጠበቅ ነው» (መዝ.118፡9)፣ «አንተን እንዳልበድል ቃልህን በልቤ ሰወርኩ (ቊ.11)፣ «ሕግህ ለእግሬ መብራት ለመንገዴ ብርሃን ነው» (ቊ.105) «ከቃልህ የተነሣ አስተዋልሁ፣ ስለዚህ የሐሰትን መንገድ ጠላሁ»(ቊ.104) ብሏል፡፡

2. ላለመጥፋት ይጠቅማል

በጥንት ዘመን እንደነበረ በመጽሐፍ የተመዘገበለት ነገር ግን በአሁን ጊዜ የሌለ የቀደመው ዓለም የጠፋው የእግዚአብሔር ቃል እውቀት ስላልነበረው ነው፤ ከጥፋት ውኃ በፊት የነበረው ያ ዓለም ከሌሎች ሰባት ጋር ጽድቅን የሚሰብከውን ኖኅን ሊሰማው አልቻለም ነበር (2ጴጥ.2፡5)፤ «በዚህም ምክንያት ያን ጊዜ የነበረው ዓለም በውኃ ሰጥሞ ጠፋ» (2ጴጥ.3፡6)፤ ምክንያቱም አላዋቂነትን ወደው ነበርና (ምሳ.1፡22)፡፡ ግለሰብም ሆነ ሕዝብ እንዲሁም አገር የሚጠፉበት ዋነኛው ምክንያት የእግዚአብሔርን ቃል ካለማወቅ የተነሣ በሚፈጸሙ መንፈሳዊና ሥጋዊ በደሎች ነው፡፡ ሰው የጌታን ቃል ካላወቀ መጥፋቱ አይቀሬ ነው፡፡ በዚህ መልኩ ከበደሉ የተነሣ በእግዚአብሔር ፍርድ የሚጠፋ ሁሉ አስቀድሞውኑ የእግዚአብሔር ቃል እውቀት ማጣቱ ከእግዚአብሔር ፊት ያጠፋው(ያራቀው) መሆኑ ግልጥ ነው፤ ከዚህም አንጻር ስለጠፉት ቤተ እስራኤል «ሕዝቤ ዕውቀት ከማጣቱ የተነሣ ጠፍቶአልና» ተብሎ ተነግሯል (ሆሴ.4፡6)፡፡ እዚህ ላይ ሕዝበ እስራኤልን የሚያስተምር ሰው አልነበረምን? ብሎ መጠየቁ መልካም ነው፤ እስራኤል የሚያስተምሯቸው መምህራን፣ መሥዋዕት የሚያቀርቡላቸው ካህናት፣ ትንቢት የሚናገሩላቸው ነቢያት እንደዚሁም የሚያነቧቸው ቅዱሳት መጻሕፍት ነበሯቸው፡፡ ችግሩ ግን ነቢያት የሚናገሩትንና መጻሕፍት የሚመሰክሩትን የእግዚአብሔርን ቃል አውቀው አለመታዘዛቸው ነው፡፡ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስም ስለ አንድ ባለጠጋ ሰውና ስለደሃው አልዓዛር የተናገረው ታሪክ ሰው በእጁ ያሉትን መጻሕፍት በመጠቀም ከፍርድ የሚድንበትን የእግዚአብሔር ቃል እውቀት መያዝ እንደሚኖርበት ያስረዳል (ሉቃ.16፡27-31)፡፡ እንግዲህ ላለመጥፋት ከተፈለገ መፍትሔው የእግዚአብሔርን ቃል አውቆ መገኘት ብቻ ነው፡፡

3. ለሚጠይቁን ለመመለስ ይጠቅማል

ብዙውን ጊዜ የእግዚአብሔር ቃል እውቀት በሚገባ ሳይኖር ሲቀር በእምነት ነገር አላዋቂ ከሆኑ ወይም ከማያምኑ ሰዎች ለሚቀርቡ ጥያቄዎች አጥጋቢ መልስ መስጠት አይቻልም፡፡ ማንኛውም አማኝ ስለሚያምነው ነገር በተጠየቀ ጊዜ መልስ መስጠት ይችል ዘንድ የእግዚአብሔር ቃል ዕውቀት በሙላት ሊኖረው ይገባል፤ ስለዚህም መጽሐፍ ቅዱስ ሲናገር «የእግዚአብሔር ቃል በሙላት ይኑርባችሁ» ይላል (ቈላ.3፡16)፤ እንደዚሁም በሌላ ስፍራ «በእናንተ ስላለ ተስፋ ምክንያት ለሚጠይቋችሁ ሁሉ መልስ ለመስጠት የተዘጋጃችሁ ሁኑ» ይላል (1ጴጥ.3፡15)፤ ዳግመኛም «ለሚጠይቅህም እውነትን ቃል መመለስ ይቻልህ ዘንድ በምክርና በዕውቀት የከበረን ነገር አልፃፍሁልህምን?» የሚል እናነባለን (ምሳ.22፡21)፡፡

የቃሉ እውቀት አስተማሪ

ብዙዎች እንደሚያስቡትና እንደሚናገሩት መጽሐፍ ቅዱስ የተደበቀና የተሸሸገ ምሥጢር አይደለም፤ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ «የአፌ ቃላት ሁሉ ጽድቅ ናቸው፤ ጠማማ ዘወርዋራም አይደሉም፤ እነርሱ በሚያስተውሉ ዘንድ የቀኑ ናቸው፤ ዕውቀትንም ካገኙአት ሰዎች ጋር የተስማሙ ናቸው» ተብሎ ተነግሮአል (ምሳ.8፡8)፤ ስለዚህ እያንዳንዱ ሰው እግዚአብሔርን በሚፈልግ እውነተኛ ልብ ሆኖ ቢያነበው የቃሉን እውቀት በመንፈስ ቅዱስ አስተማሪነት ይማራል (ዮሐ.14፡26)፤ ይህ አስተማሪም ሁሌ ከተማሪው አይለይም፤ በየትኛውም ሰዓትና ጊዜ እንዲሁም ቦታ ይህ አስተማሪ መጽሐፍ ቅዱስን የሚያነቡትን ሁሉ ሲረዳ ይኖራል፤ እርሱ የሚመጣና የሚሄድ አይደለም፤ ስለእርሱም «አስተማሪህ ከአንተ ከእንግዲህ አይሰወርም ... ጆሮችህ በኋላህ መንገድህ ይህች ናት በእርስዋም ሂድ የሚለውን ቃል ይሰማሉ» ተብሏል (ኢሳ.30፡21)፡፡ አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝም ለጃንደረባው እንዳደረገው መንፈስ ቅዱስ ለአንባቢው መጻሕፍትን በማብራራት የሚመራውን ሰው ይልክለታል (ሐዋ.ሥራ8፡29-35)፡፡

ምንም እንኳ መታዘዝ ስለማንችል አእምሮአችን እንዳይወቅሰን መጽሐፍ ቅዱስን ባናነብ ይሻለናል የሚሉ ሰዎች ቢኖሩም ያለእግዚአብሔር እውቀት መኖራቸው ከተጠያቂነት ስለማያድናቸው መልካም አይሆንላቸውም፤ ምክንያቱም «ነፍስ ዕውቀት የሌላት ትሆን ዘንድ መልካም አይደለም» ተብሎአልና (ምሳ.19፡2)፡፡


ምንጭ:- ewnetone.com




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍42
.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“እግዚአብሔርን እንወቀው፤ የበለጠ እናውቀውም ዘንድ እንትጋ፤ እንደ ንጋት ብርሃን፣ በእርግጥ ይገለጣል፤ ምድርን እንደሚያረሰርስ የበልግ ዝናብ፣ እንደ ክረምትም ዝናብ ወደ እኛ ይመጣል።”
ሆሴዕ 6፥3 (አዲሱ መ.ት)




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
6🥰4👍1😁1
ራስን መግዛት - ትልቁ ስልጣን


"የመንፈስ ፍሬ ግን . . .  ራስን መግዛት ነው፡፡" ገላ. 5:22፣ 23

የመንፈስ ቅዱስ ፍሬ የክርስትና ሕይወት እውነተኛ ባህሪ ነው፡፡ ሐዋርያው ጳውሎስ በገላ. 5:22-23 ዘጠኝ የተለያየ ገጽታ ያሏቸውን ፍሬዎች ጠቅሷል፡፡ አንድ ሰው የሚሰጡትን መንፈሳዊ ስጦታዎችና መክሊቶች ተጠቅሞ ለእግዚአብሔር ስለሚሠራው ሥራ የመንፈስ ፍሬ በቀጥታ የሚነግረን ነገር ባይኖረውም ነገር ግን ግለሰቡ እንዴት ለእግዚአብሔር ሊኖር እንደሚገባ በግልጽ ያሳየናል፡፡ ስለ ግለሰቡ ማንነት ፍንጭ ይሰጠናል፡፡ በገላ. 5፡22-23 የተጠቀሱት ሁሉም መልካም ምግባሮች በኢየሱስ ውስጥ ተገልጠው መታየት ችለዋል፡፡ በመሆኑም የመንፈስ ፍሬ በመንፈስ ቅዱስ አማካይነት እውን መሆን የቻለው በእኛ ውስጥ በሚኖረው የኢየሱስ ክርስቶስ ሕይወት ነው፡፡ የመንፈስ ፍሬ በእኛ ውስጥ በሚከናወነው የመንፈስ ቅዱስ ስራ አማካኝነት የሚታይ የጸባይና የሕይወት ለውጥ ጭምር ነው፡፡ በእራሳችን የእግዚአብሔር ልጆች መሆን እንዳልቻልን ሁሉ በእራሳችን የባህርይ ለውጥ ወይም መንፈሳዊ ፍሬዎችን ማምጣት አንችልም፡፡

የመንፈስ ፍሬ ሙሉ ለሙሉ ሰብዓዊ በሆነ ጥረት ብቻ ልናገኘው የምንችለው ነገር አይደለም፡፡ “ስለ በጎ ፈቃዱ መፈለግንም ማድረግንም በእናንተ የሚሠራ እግዚአብሔር ነውና።” (ፊል. 2፡13)  እኛ የእግዚአብሔር ልጆች የምናደርጋቸው ማንኛውም አይነት መልካም ነገሮች ሁሉ መንፈስ ቅዱስ በእኛ ውስጥ የሚሠራው ስራ ውጤት ናቸው፡፡

በክርስትና ሕይወት እውነተኛ ፍሬ የምናፈራበት ቀዳሚ ምስጢር በክርስቶስ መኖር ነው፡፡ እርሱ በእኛ፤ እኛ በእርሱ፡፡ ከክርስቶስ ውጪ እውነተኛ የመንፈስ ፍሬ ማፍራት አንችልም፡፡ የመንፈስ ፍሬ ከውጪ የሚጫንብን ነገር ሳይሆን በውስጣችን የሚኖረው የክርስቶስ ሕይወት ውጤት ነው፡፡ የመንፈስ ፍሬ--የወይኑ ግንድ ከሆነው ክርስቶስ፤ ቅርንጫፍ ወደ ሆኑት አማኞች የሚፈስ የእርሱ ሕይወት ውጤት መሆኑን ኢየሱስ በዮሐ. 15፡1-11 ይነግረናል፡፡ ፍሬውን የሚያሳድገው በኢየሱስ የሚሠራው አምላካዊ ሥራ ነው፡፡ የአማኙ ኃላፊነት በክርስቶስ መኖር ነው፡፡ ክርስቶስ ሃሳባችንን ሲሞላው በድርጊቶቻችን የሚገለጥ ይሆናል፡፡ ኢየሱስ በእኛ ውስጥ ሕያው ሆኖ ይኖራል፡፡ ክርስቶስ በእኛ ውስጥ የኖረው ህይወት በውስጣችን  ፍሬ ስለሚያፈራ በምላሹ የእርሱን ባህርይ የምናንጸባርቅና የምናሳይ እንሆናለን፡፡

ራስን መግዛት በገላትያ 5:22 ከተጠቀሱ የመንፈስ ቅዱስ ፍሬዎች አንዱ መሆኑን ብዙዎቻችን እናውቃለን። ሁላችንም ባንሆን አንዳንድ ጊዜ ራሳችንን መግዛት  አቅቶን  መሆን  የማይገባንን  ሆነን  ራሳችንን አሳዛኝና አላስፈላጊ ሁኔታዎች ውስጥ እናገኘዋለን።  ብዙ ጥፋትም አድርሰን እናውቃለን። ራስን መግዛት እንደየሰው ዓላማ የተለያየ ቢሆንም በሁሉም የሥራ እና የኃይማኖት መስክ የተወደደ ነገር ነው። ራስን ስለ መግዛት መማርና ኑሮውን መለማማድ ከባድ ቢሆንም ወደ እምነት ብስለት ይመራናል። መድኃኒት ይመራል ነገር ግን ጤንነትን ይሰጣል።

በአሁኑ ወቅት፣ ራስን ስለ መግዛት መወያታቸን አስፈላጊ የሆነው ለምንድን ነው?

በዛሬው ጊዜ በሰዎች ላይ የሚደርሱት አብዛኞቹ ችግሮች የሚመነጩት ራስን ካለመግዛት ነው። አንዳንዶች ራሳቸውን መግዛት ስለሚያቅታቸው ከትምህርት ወይም ከሥራ ጋር በተያያዘ ዛሬ ነገ የማለት ልማድ የሚታይባቸው ከመሆኑም ሌላ የሚጠበቅባቸውን ነገር በትጋት ለማከናወን ይቸገራሉ። በተጨማሪም ራሳቸውን የማይገዙ ሰዎች ተሳዳቢዎች፣ ሰካራሞችና ዓመፀኞች ሲሆኑ፣ አላስፈላጊ ዕዳ ውስጥም ሊዘፈቁ እንዲሁም ለፍቺ፣ ለሱስ፣ ለእስር፣ ለስሜት ቀውስና ለዝሙት ተጋላጮች ናቸው፡፡ እነዚህ ችግሮች ራስን አለመግዛት ከሚያስከትላቸው መዘዞች መካከል ጥቂቶቹ ናቸው። በግልጽ ማየት እንደሚቻለው ራሳቸውን መግዛት የሚያቅታቸው ሰዎች በራሳቸውም ሆነ በሌሎች ላይ ጉዳት ያስከትላሉ። የሚያሳዝነው ራስን የመግዛት ችግር ከዕለት ወደ ዕለት እየተባባሰ መምጣቱ ነው። አውቀውም ይሁን ሳያውቁ ድርጊታቸው በራሳቸውም ሆነ በሌሎች ላይ የሚያስከትለውን መዘዝ ሳያገናዝቡ ፍጹም ባልሆነው ሥጋቸው ምኞት እየተነዱ ሕይወታቸውን እንዳሻቸው የሚመሩ ብዙዎች አሉ። ሰዎች ክፉ ነገር እንዲያደርጉ ለሚቀርብላቸው ጥያቄ እምቢ ለማለት አቅሙም ፍላጎቱም እንደሌላቸው ከመቼውም ጊዜ በበለጠ በዘመናችን ጎልቶ ይታያል።

በዘመናችን ያለውም ባሕል ራስን መግዛትን አያበረታታም። እንደፈለጉ መሆንን በሚያበረታታው ባሕላችን አዋቂዎችም ሆንን ልጆች የፈለግነውን እንድናደርግ የሚያነሳሳ መልእክት ሁልጊዜ ይዥጎደጎድብናል። በቅን ልቦና ተነሳስተው ምክር የሚለግሱንም ሆኑ ለገንዘብ ሲሉ የማይረባ ምክር የሚሰጡን ሰዎች ምንጊዜም ስሜታችንን ማስተናገድ እንዳለብን ሲናገሩም እንሰማለን። በመጨረሻዎቹ "ቀናት” ውስጥ እንደምንኖር ከሚያሳዩት ምልክቶች መካከል አንደኛው ሰዎች “ራሳቸውን የማይገዙ” መሆናቸው ነው (2ኛ ጢሞ 3፥3)፡፡ በዚህ በመጨረሻው ዘመን ውስጥ ክርስቲያኖች እራሳቸውን ከሌሎች የሚለዩበትን አንዱን የሆነውን ራስን የመግዛት ባህሪን እያሳዩና እያንፀባረቁ መኖር አለባቸው፡፡

ራስን መግዛት ስንል ምን ማለታችን ነው?

ራስን መግዛት ከውስጣችን ሊወጣ የሚታገለንን ማናቸውንም የስጋ ፍላጎትና ምኞትን መቆጣጠርና መግዛት ራስን መግዛት ይባላል፡፡ ራስን መግዛት  ማለት ስሜትን መቆጣጠር፤ መሻትን ማሸነፍ፤ ሁለንተናን ለእግዚአብሔር ፈቃድና ክብር ማስገዛት ማለት ነው፡፡ ራስን መግዛት ከውስጥ የሚመነጩ እና ከውጭ የሚመጡ ግፊቶችን መቋቋም መቻል ነው፡፡ ራስን መግዛት ለቁጣ፣ ለቂም በቀልና ለጥላቻ፣ ለሥጋዊ ጥቅም፣ ለስካር . . .  ወዘተ በአምሮአችንና በልባችን ግፊት ከሚመጣ ፈተና ራስን ማዳን እና ለሌሌችም ምስክር መሆን ነው። ራስን መግዛት ብዙ የሥጋ  እና  የዓለም  ክብር  ግብዣዎችን እምቢ ማለት ነው፡፡ ራስን  መግዛት  በሀሳብ፣በቃላትና  በተግባር የሚገለጥ ነገር ነው።


ምንጭ፦ habtamumeressa.blogspot.com




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍95
.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“አንተ ግን በተማርህበትና በተረዳህበት ነገር ጸንተህ ኑር፥ ከማን እንደ ተማርኸው ታውቃለህና፤”
2ኛ ጢሞቴዎስ 3፥14



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍10
#የእግዚአብሔር_ቃል_ምን_ይላል?



2ኛ ጢሞቴዎስ 3
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁰ አንተ ግን ትምህርቴንና አካሄዴን አሳቤንም እምነቴንም ትዕግሥቴንም ፍቅሬንም መጽናቴንም ስደቴንም መከራዬንም ተከተልህ፤
¹¹ በአንጾኪያና በኢቆንዮን በልስጥራንም የሆነብኝን የታገሥሁትንም ስደት ታውቃለህ፤ ጌታም ከሁሉ አዳነኝ።
¹² በእውነትም በክርስቶስ ኢየሱስ እግዚአብሔርን እየመሰሉ ሊኖሩ የሚወዱ ሁሉ ይሰደዳሉ።
¹³ ነገር ግን ክፉዎች ሰዎችና አታላዮች፥ እያሳቱና እየሳቱ፥ በክፋት እየባሱ ይሄዳሉ።
¹⁴ አንተ ግን በተማርህበትና በተረዳህበት ነገር ጸንተህ ኑር፥ ከማን እንደ ተማርኸው ታውቃለህና፤
¹⁵ ከሕፃንነትህም ጀምረህ ክርስቶስ ኢየሱስን በማመን፥ መዳን የሚገኝበትን ጥበብ ሊሰጡህ የሚችሉትን ቅዱሳን መጻሕፍትን አውቀሃል።
¹⁶-¹⁷ የእግዚአብሔር ሰው ፍጹምና ለበጎ ሥራ ሁሉ የተዘጋጀ ይሆን ዘንድ፥ የእግዚአብሔር መንፈስ ያለበት መጽሐፍ ሁሉ ለትምህርትና ለተግሣጽ ልብንም ለማቅናት በጽድቅም ላለው ምክር ደግሞ ይጠቅማል።



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍83
.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“ስለዚህ የተወደዳችሁ ወንድሞቼ ሆይ፤ ጸንታችሁ ቁሙ፤ በምንም ነገር አትናወጡ። ለጌታ ሥራ ዘወትር የምትተጉ ሁኑ፤ ምክንያቱም ለጌታ የምትደክሙት በከንቱ እንዳልሆነ ታውቃላችሁ።”
1ኛ ቆሮንቶስ 15፥58 (አዲሱ መ.ት)




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍42
#እንወያይ


የፕሮቴስታን ተሐድሶ ከፈነዳ 500 ዓመታትን ከዘለቀ ሰነበተ። ኦክቶበር 31፣ 1517 እ. ኤ.አ ማርቲን ሉተር 95ቱን መከራከሪያ ነጥቡን ሲለጥፍ ጅማሮውን አገኘ። ይህ መሠረት በማድረግ የቻናላችን ቤተሰቦች የሆናችሁ ፕሮቴስታንት፣ ኦርቶዶክስ፣ ካቶሊክ ወይም የሌላ ወገን የሆናችሁ ይህ ተሐድሶ ምን አመጣ? ጠቀመን ወይስ ጎዳን? ጠንካራ እና ደካማ ጎኖቹን በቅንነት እና በጨዋነት ከመጽሐፍ ቅዱስ አንጻር እየገለጽን እንወያይ።




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍143