' ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“ከያዕቆብም ቤት ፊቱን የመለሰውን እግዚአብሔርን እጠብቃለሁ፥ እተማመንበትማለሁ።”
ኢሳይያስ 8፥17
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“ከያዕቆብም ቤት ፊቱን የመለሰውን እግዚአብሔርን እጠብቃለሁ፥ እተማመንበትማለሁ።”
ኢሳይያስ 8፥17
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤8
ከቅዱሳት መጻሕፍት መካከል መጀመሪያ እና መጨረሻ እንደተጻፈ የሚገመተው የቱ ነው?
Anonymous Quiz
57%
ሀ. ዘፍጥረት እና የዮሐንስ ራእይ
36%
ለ. ኢዮብ እና ራእይ
4%
ሐ. መሳፍንት እና ራእይ
4%
መ. መዝሙረ ዳዊት እና ራእይ
❤2
ሰሞኑ በቻናላችን በለጠፍነው ጥያቄ ላይ ብዙዎቻችሁ ግራ ተጋብታችኋል። ጥያቄም ጠይቃችኋል። በነገራችን ላይ ብዙ ሰው ተሳትፎ ግር መሰኙቱን በስፋት ስለገለጸልን ምን ያህል ለጥያቄዎቻችን ትኩረት እንደሰጣችሁ አይተናል። ደስ ብሎናል እናመሰግናለን!🙏 ከዚህ በታች በመጽሐፍ ቅዱሳችን ውስጥ ረጃጅም መጻሕፍትን ከነቃላት ብዛታቸው (ማለትም በተጻፉበት ቋንቋ) እነሆ፦
1. ኤርምያስ (33,002 ቃላት)
2. ኦሪት ዘፍጥረት (32,046 ቃላት)
3. መዝሙረ ዳዊት (30,147 ቃላት)
4. ሕዝቅኤል (29,918 ቃላት)
5. ዘጸአት (25, 957 ቃላት)
6. ኢሳይያስ (25,608 ቃላት)
7. ኦሪት ዘኁልቁ (25,048 ቃላት)
8. ኦሪት ዘዳግም (23,008 ቃላት)
9. ሁለተኛ ዜና መዋዕል (21,349 ቃላት)
10. አንደኛ ሳሙኤል (20,361 ቃላት)
ከዚህ ጋር በተያያዘ ጥሩ ቅዱሳት መጻሕፍትን መሠረት ያደረገ ፕሮግራም ያለው ሰው ሊያናግረን ይችላል። በተረፈ ያቋረጥነውን የሮሜ መልእክት ጥናታችንን በቅርቡ እንቀጥላለን።
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
1. ኤርምያስ (33,002 ቃላት)
2. ኦሪት ዘፍጥረት (32,046 ቃላት)
3. መዝሙረ ዳዊት (30,147 ቃላት)
4. ሕዝቅኤል (29,918 ቃላት)
5. ዘጸአት (25, 957 ቃላት)
6. ኢሳይያስ (25,608 ቃላት)
7. ኦሪት ዘኁልቁ (25,048 ቃላት)
8. ኦሪት ዘዳግም (23,008 ቃላት)
9. ሁለተኛ ዜና መዋዕል (21,349 ቃላት)
10. አንደኛ ሳሙኤል (20,361 ቃላት)
ከዚህ ጋር በተያያዘ ጥሩ ቅዱሳት መጻሕፍትን መሠረት ያደረገ ፕሮግራም ያለው ሰው ሊያናግረን ይችላል። በተረፈ ያቋረጥነውን የሮሜ መልእክት ጥናታችንን በቅርቡ እንቀጥላለን።
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍11❤2
' ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“በውኑ በአሕዛብ ጣዖታት መካከል ያዘንብ ዘንድ የሚችል ይገኛልን? ወይስ ሰማይ ዝናብ ማፍሰስ ይችላልን? አቤቱ አምላካችን ሆይ፥ አንተ አይደለህምን? አንተ ይህን ነገር ሁሉ አድርገሃልና ስለዚህ አንተን በተስፋ እንጠባበቃለን።”
ኤርምያስ 14፥22
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“በውኑ በአሕዛብ ጣዖታት መካከል ያዘንብ ዘንድ የሚችል ይገኛልን? ወይስ ሰማይ ዝናብ ማፍሰስ ይችላልን? አቤቱ አምላካችን ሆይ፥ አንተ አይደለህምን? አንተ ይህን ነገር ሁሉ አድርገሃልና ስለዚህ አንተን በተስፋ እንጠባበቃለን።”
ኤርምያስ 14፥22
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍2
ነቢዩ ኤርምያስ
#ኤርምያስ በመጽሐፍ ቅዱሳችን ውስጥ ረጅሙን መጽሐፍ የጻፈ ነቢይ ነው። ለመሆኑ ነቢዩ ኤርምያስ ማን ነው? በአብዛኛው አማኝ ዘንድ የብሉይ ኪዳን ነቢይ ማለትም ትንቢታቸው ወጥ በሆነ መጽሐፍ ከተሰደሩ ሲባል አእምሮው ላይ የሚመጣው እና የሚወደደው ነቢይ፣ ነቢዩ ኢሳይያስ ነው። ነገር ግን በእስራኤላዊያን ዘንድ ነቢዩ ኤርምያስ ነው። "አልቃሻው ነቢይ" በመባልም ይታወቃል። በእስራኤላውያን ዘንድ ተወዳጅ እንደሆነ ማሳያው ጌታችን እና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ "ሰዎች የሰውን ልጅ ማን እንደ ሆነ ይሉታል?” (ማቴ. 16፥13) ብሎ ሲጠይቅ ከደቀ መዛሙርቱ ካገኘው አንዱ ምላሽ ኤርምያስ የሚል ነበር። ታዲያ ነቢዩ ኤርምያስ ማን ነው?
ኤርምያስ፤ ትርጕሙ «እግዚአብሔር ከፍ ያደርጋል» ማለት ነው። ከእስራኤል ታላላቅ ነቢያት አንዱ። በኢየሩሳሌም አቅራቢያ ካለው ከተማ ከዓናቶት፥ ከካህናትም ወገን ነበረ። አባቱ በኢዮስያስ ዘመን የሕጉን መጽሐፍ ያገኘው ኬልቅያስ መሆኑን ብዙ ሊቃውንት ያምናሉ። ለእስራኤል ብቻ ሳይሆን ለአሕዛብም ጭምር ነቢይ እንዲሆን በተጠራ ጊዜ ደነገጠ፤ «ብላቴና ነኝ» በማለት አመነታ። በኋላ ግን በተሰጠው ተስፋ መሠረት በረታ። የተጠራውም 626 ከክርስቶስ ልደት በፊት፥ የይሁዳ ንጉሥ ኢዮስያስ በነገሠ በ13ኛው ዓመት ነበር። በኢዮስያስም ልጆች ዘመን ትንቢት እየተናገረ ቆይቶ፥ ከተጠራ ከ40 ዓመት በኋላ የኢየሩሳሌምን መማረክ አየ፤ ኤር. 1፡1-10። በዚህም ዘመን አምስት ነገሥታት ነገሡ።
መጽሐፉ የተጻፈው ከሚከተሉት ዐላማ የተነሣ ነው፣
(1) የኤርምያስን ነቢያዊ አገልግሎትና መልእክት በዘላቂነት በሰነድነት ለመያዝ፤
(2) ሕዝቡ ኪዳን ሲተላለፉና በእግዚአብሔርና በቃሉ ላይ በዐመፀኝነት ሲቀጥሉ የእግዚአብሔርን የማይቀርንና የማያመልጡት ፍርድ ለማሳየት፣
(3) ነቢያዊ ቃሉ የቱን ያህል ሐቅና የቱን ያህልስ ሥልጣን እንዳለው ለማሳየት፡፡ ብዙዎቹ የኤርምያስ ተንቢቶች በሕይወት ዘመኑ ተፈጽመዋል (ለምሳሌ 16፥9፤ 20፥4፤ 25፥1-14፣ 27፥19-22፤ 28፥15-17፤ 32፥10-13፡ 34፥1-5)፤ በረጅም ዘመን ውስጥ የሚፈጸሙት ሌሎቹ ትንቢቶቹ ከጊዜ በኋላ ተፈጽመዋል፤ ወይም ገና ወደ ፊት ይፈጸማሉ (ለምሳሌ 23፥5-6፣ 30፥8-9፣ 31፥31-34፤ 33፥14-16)፡፡
ይቀጥል የሚል አስተያየት ከበዛ በስፋት ስለነቢዩ እና አገልግሎቱ እንመለስበታለን። በተለይም ልዩ ባህሪያቶቹ፣ ስለምርኮው፣ ስለደረሰበት መከራ፣ ተቃውሞ፣ አሟሟቱ. . . ወ.ዘ.ተ
ምንጭ፦ የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት፤ ገጽ 174፣ ምሉእ ሕይወት፤ ገጽ 1099-1100
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
#ኤርምያስ በመጽሐፍ ቅዱሳችን ውስጥ ረጅሙን መጽሐፍ የጻፈ ነቢይ ነው። ለመሆኑ ነቢዩ ኤርምያስ ማን ነው? በአብዛኛው አማኝ ዘንድ የብሉይ ኪዳን ነቢይ ማለትም ትንቢታቸው ወጥ በሆነ መጽሐፍ ከተሰደሩ ሲባል አእምሮው ላይ የሚመጣው እና የሚወደደው ነቢይ፣ ነቢዩ ኢሳይያስ ነው። ነገር ግን በእስራኤላዊያን ዘንድ ነቢዩ ኤርምያስ ነው። "አልቃሻው ነቢይ" በመባልም ይታወቃል። በእስራኤላውያን ዘንድ ተወዳጅ እንደሆነ ማሳያው ጌታችን እና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ "ሰዎች የሰውን ልጅ ማን እንደ ሆነ ይሉታል?” (ማቴ. 16፥13) ብሎ ሲጠይቅ ከደቀ መዛሙርቱ ካገኘው አንዱ ምላሽ ኤርምያስ የሚል ነበር። ታዲያ ነቢዩ ኤርምያስ ማን ነው?
ኤርምያስ፤ ትርጕሙ «እግዚአብሔር ከፍ ያደርጋል» ማለት ነው። ከእስራኤል ታላላቅ ነቢያት አንዱ። በኢየሩሳሌም አቅራቢያ ካለው ከተማ ከዓናቶት፥ ከካህናትም ወገን ነበረ። አባቱ በኢዮስያስ ዘመን የሕጉን መጽሐፍ ያገኘው ኬልቅያስ መሆኑን ብዙ ሊቃውንት ያምናሉ። ለእስራኤል ብቻ ሳይሆን ለአሕዛብም ጭምር ነቢይ እንዲሆን በተጠራ ጊዜ ደነገጠ፤ «ብላቴና ነኝ» በማለት አመነታ። በኋላ ግን በተሰጠው ተስፋ መሠረት በረታ። የተጠራውም 626 ከክርስቶስ ልደት በፊት፥ የይሁዳ ንጉሥ ኢዮስያስ በነገሠ በ13ኛው ዓመት ነበር። በኢዮስያስም ልጆች ዘመን ትንቢት እየተናገረ ቆይቶ፥ ከተጠራ ከ40 ዓመት በኋላ የኢየሩሳሌምን መማረክ አየ፤ ኤር. 1፡1-10። በዚህም ዘመን አምስት ነገሥታት ነገሡ።
መጽሐፉ የተጻፈው ከሚከተሉት ዐላማ የተነሣ ነው፣
(1) የኤርምያስን ነቢያዊ አገልግሎትና መልእክት በዘላቂነት በሰነድነት ለመያዝ፤
(2) ሕዝቡ ኪዳን ሲተላለፉና በእግዚአብሔርና በቃሉ ላይ በዐመፀኝነት ሲቀጥሉ የእግዚአብሔርን የማይቀርንና የማያመልጡት ፍርድ ለማሳየት፣
(3) ነቢያዊ ቃሉ የቱን ያህል ሐቅና የቱን ያህልስ ሥልጣን እንዳለው ለማሳየት፡፡ ብዙዎቹ የኤርምያስ ተንቢቶች በሕይወት ዘመኑ ተፈጽመዋል (ለምሳሌ 16፥9፤ 20፥4፤ 25፥1-14፣ 27፥19-22፤ 28፥15-17፤ 32፥10-13፡ 34፥1-5)፤ በረጅም ዘመን ውስጥ የሚፈጸሙት ሌሎቹ ትንቢቶቹ ከጊዜ በኋላ ተፈጽመዋል፤ ወይም ገና ወደ ፊት ይፈጸማሉ (ለምሳሌ 23፥5-6፣ 30፥8-9፣ 31፥31-34፤ 33፥14-16)፡፡
ይቀጥል የሚል አስተያየት ከበዛ በስፋት ስለነቢዩ እና አገልግሎቱ እንመለስበታለን። በተለይም ልዩ ባህሪያቶቹ፣ ስለምርኮው፣ ስለደረሰበት መከራ፣ ተቃውሞ፣ አሟሟቱ. . . ወ.ዘ.ተ
ምንጭ፦ የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት፤ ገጽ 174፣ ምሉእ ሕይወት፤ ገጽ 1099-1100
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍18👏2😁2❤1
' ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“እግዚአብሔርም ራሔልን አሰበ፥ እግዚአብሔርም ተለመናት፥ ማኅፀንዋንም ከፈተላት፤”
ዘፍጥረት 30፥22
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“እግዚአብሔርም ራሔልን አሰበ፥ እግዚአብሔርም ተለመናት፥ ማኅፀንዋንም ከፈተላት፤”
ዘፍጥረት 30፥22
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤9👍1
#የእግዚአብሔር_ቃል_ምን_ይላል?
ኤርምያስ 20
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ በእግዚአብሔርም ቤት የተሾመው አለቃ የካህኑ የኢሜር ልጅ ጳስኮር ኤርምያስ በዚህ ነገር ትንቢት ሲናገር ሰማ።
² ጳስኮርም ነቢዩን ኤርምያስን መታው፥ በእግዚአብሔርም ቤት በነበረው በላይኛው በብንያም በር ባለው በእግር ግንድ ውስጥ አኖረው።
³ በነጋውም ጳስኮር ኤርምያስን ከግንድ ውስጥ አወጣው። ኤርምያስም እንዲህ አለው፦ እግዚአብሔር ስምህን፦ ማጎርሚሳቢብ እንጂ ጳስኮር ብሎ አይጠራህም።
⁴ እግዚአብሔር እንዲህ ይላልና፦ እነሆ፥ ለራስህና ለወዳጆችህ ሁሉ ፍርሃት አደርግሃለሁ፤ እነርሱም በጠላቶቻቸው ሰይፍ ይወድቃሉ ዓይኖችህም ያያሉ፤ ይሁዳንም ሁሉ በባቢሎን ንጉሥ እጅ አሳልፌ እሰጣለሁ፥ እርሱም ወደ ባቢሎን ያፈልሳቸዋል በሰይፍም ይገድላቸዋል።
⁵ የዚህችንም ከተማ ባለጠግነት ሁሉ ጥሪትዋንም ሁሉ ክብርዋንም ሁሉ የይሁዳንም ነገሥታት መዝገብ ሁሉ በጠላቶቻቸው እጅ አሳልፌ እሰጣለሁ፥ እነርሱም ይበዘብዙአቸዋል ይዘውም ወደ ባቢሎን ያፈልሱአቸዋል።
⁶ አንተም፥ ጳስኮር ሆይ፥ በቤትህም የሚኖሩት ሁሉ ተማርካችሁ ትሄዳላችሁ፤ አንተም በሐሰትም ትንቢት የተናገርህላቸው ወዳጆችህ ሁሉ ወደ ባቢሎን ትገባላችሁ፥ በዚያም ትሞታላችሁ፥ በዚያም ትቀበራላችሁ።
⁷ አቤቱ፥ አታለልኸኝ እኔም ተታለልሁ፥ ከእኔም በረታህ አሸነፍህም፤ ቀኑን ሁሉ መሳቂያ ሆኛለሁ፥ ሁሉም ያላግጡብኛል።
⁸ በተናገርሁ ቍጥር እጮኻለሁ፤ ግፍና ጥፋት ብዬ እጮኻለሁ፤ የእግዚአብሔር ቃል ቀኑን ሁሉ ስድብና ዋዛ ሆኖብኛልና።
⁹ እኔም፦ የእግዚአብሔርን ስም አላነሣም፥ ከእንግዲህ ወዲህም በስሙ አልናገርም ብል፥ በአጥንቶቼ ውስጥ እንደ ገባ እንደሚነድድ እሳት ያለ በልቤ ሆነብኝ፤ ደከምሁ፥ መሸከምም አልቻልሁም።
¹⁰ የብዙ ሰዎችን ስድብ ሰምቻለሁ፥ ማስፈራራትም ከብቦኛል። መውደቄን የሚጠብቁ የሰላሜ ሰዎች ሁሉ፦ ምናልባት ይታለል እንደ ሆነ፥ እናሸንፈውም እንደ ሆነ፥ እርሱንም እንበቀል እንደ ሆነ፥ ክሰሱት እኛም እንከስሰዋለን ይላሉ።
¹¹ እግዚአብሔር ግን እንደ ኃያልና እንደ ጨካኝ ከእኔ ጋር ነው፤ ስለዚህ አሳዳጆቼ ይሰናከላሉ አያሸንፉም፤ አይከናወንላቸውምና በጽኑ እፍረት ያፍራሉ፥ ለዘላለምም በማይረሳ ጕስቍልና ይጐሰቍላሉ።
¹² አቤቱ፥ ጻድቅን የምትመረምር ኵላሊትንና ልብን የምትመለከት የሠራዊት ጌታ ሆይ፥ ክርክሬን ገልጬልሃለሁና በቀልህን በላያቸው ለይ።
¹³ ለእግዚአብሔር ዘምሩ እግዚአብሔርንም አመስግኑ፤ የችግረኛውን ነፍስ ከክፉ አድራጊዎች እጅ አድኖአልና።
¹⁴ የተወለድሁባት ቀን የተረገመች ትሁን፤ እናቴ እኔን የወለደችባት ቀን የተባረከች አትሁን።
¹⁵ ወንድ ልጅ ተወልዶልሃል ብሎ ለአባቴ የምሥራች ነግሮ ደስ ያሰኘው ሰው የተረገመ ይሁን።
¹⁶ ያም ሰው እግዚአብሔር ሳይጸጸት እንደ ገለበጣቸው ከተሞች ይሁን፥ በማለዳም ልቅሶን በቀትርም ጩኸትን ይስማ፤
¹⁷ እናቴ መቃብር ትሆነኝ ዘንድ ማኅፀንዋም ዘወትር ይዞኝ ያቆይ ዘንድ በማኅፀን ውስጥ አልገደለኝምና።
¹⁸ ድካምንና ጣርን አይ ዘንድ ዘመኔም በእፍረት ታልቅ ዘንድ ስለ ምን ከማኅፀን ወጣሁ?
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ኤርምያስ 20
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ በእግዚአብሔርም ቤት የተሾመው አለቃ የካህኑ የኢሜር ልጅ ጳስኮር ኤርምያስ በዚህ ነገር ትንቢት ሲናገር ሰማ።
² ጳስኮርም ነቢዩን ኤርምያስን መታው፥ በእግዚአብሔርም ቤት በነበረው በላይኛው በብንያም በር ባለው በእግር ግንድ ውስጥ አኖረው።
³ በነጋውም ጳስኮር ኤርምያስን ከግንድ ውስጥ አወጣው። ኤርምያስም እንዲህ አለው፦ እግዚአብሔር ስምህን፦ ማጎርሚሳቢብ እንጂ ጳስኮር ብሎ አይጠራህም።
⁴ እግዚአብሔር እንዲህ ይላልና፦ እነሆ፥ ለራስህና ለወዳጆችህ ሁሉ ፍርሃት አደርግሃለሁ፤ እነርሱም በጠላቶቻቸው ሰይፍ ይወድቃሉ ዓይኖችህም ያያሉ፤ ይሁዳንም ሁሉ በባቢሎን ንጉሥ እጅ አሳልፌ እሰጣለሁ፥ እርሱም ወደ ባቢሎን ያፈልሳቸዋል በሰይፍም ይገድላቸዋል።
⁵ የዚህችንም ከተማ ባለጠግነት ሁሉ ጥሪትዋንም ሁሉ ክብርዋንም ሁሉ የይሁዳንም ነገሥታት መዝገብ ሁሉ በጠላቶቻቸው እጅ አሳልፌ እሰጣለሁ፥ እነርሱም ይበዘብዙአቸዋል ይዘውም ወደ ባቢሎን ያፈልሱአቸዋል።
⁶ አንተም፥ ጳስኮር ሆይ፥ በቤትህም የሚኖሩት ሁሉ ተማርካችሁ ትሄዳላችሁ፤ አንተም በሐሰትም ትንቢት የተናገርህላቸው ወዳጆችህ ሁሉ ወደ ባቢሎን ትገባላችሁ፥ በዚያም ትሞታላችሁ፥ በዚያም ትቀበራላችሁ።
⁷ አቤቱ፥ አታለልኸኝ እኔም ተታለልሁ፥ ከእኔም በረታህ አሸነፍህም፤ ቀኑን ሁሉ መሳቂያ ሆኛለሁ፥ ሁሉም ያላግጡብኛል።
⁸ በተናገርሁ ቍጥር እጮኻለሁ፤ ግፍና ጥፋት ብዬ እጮኻለሁ፤ የእግዚአብሔር ቃል ቀኑን ሁሉ ስድብና ዋዛ ሆኖብኛልና።
⁹ እኔም፦ የእግዚአብሔርን ስም አላነሣም፥ ከእንግዲህ ወዲህም በስሙ አልናገርም ብል፥ በአጥንቶቼ ውስጥ እንደ ገባ እንደሚነድድ እሳት ያለ በልቤ ሆነብኝ፤ ደከምሁ፥ መሸከምም አልቻልሁም።
¹⁰ የብዙ ሰዎችን ስድብ ሰምቻለሁ፥ ማስፈራራትም ከብቦኛል። መውደቄን የሚጠብቁ የሰላሜ ሰዎች ሁሉ፦ ምናልባት ይታለል እንደ ሆነ፥ እናሸንፈውም እንደ ሆነ፥ እርሱንም እንበቀል እንደ ሆነ፥ ክሰሱት እኛም እንከስሰዋለን ይላሉ።
¹¹ እግዚአብሔር ግን እንደ ኃያልና እንደ ጨካኝ ከእኔ ጋር ነው፤ ስለዚህ አሳዳጆቼ ይሰናከላሉ አያሸንፉም፤ አይከናወንላቸውምና በጽኑ እፍረት ያፍራሉ፥ ለዘላለምም በማይረሳ ጕስቍልና ይጐሰቍላሉ።
¹² አቤቱ፥ ጻድቅን የምትመረምር ኵላሊትንና ልብን የምትመለከት የሠራዊት ጌታ ሆይ፥ ክርክሬን ገልጬልሃለሁና በቀልህን በላያቸው ለይ።
¹³ ለእግዚአብሔር ዘምሩ እግዚአብሔርንም አመስግኑ፤ የችግረኛውን ነፍስ ከክፉ አድራጊዎች እጅ አድኖአልና።
¹⁴ የተወለድሁባት ቀን የተረገመች ትሁን፤ እናቴ እኔን የወለደችባት ቀን የተባረከች አትሁን።
¹⁵ ወንድ ልጅ ተወልዶልሃል ብሎ ለአባቴ የምሥራች ነግሮ ደስ ያሰኘው ሰው የተረገመ ይሁን።
¹⁶ ያም ሰው እግዚአብሔር ሳይጸጸት እንደ ገለበጣቸው ከተሞች ይሁን፥ በማለዳም ልቅሶን በቀትርም ጩኸትን ይስማ፤
¹⁷ እናቴ መቃብር ትሆነኝ ዘንድ ማኅፀንዋም ዘወትር ይዞኝ ያቆይ ዘንድ በማኅፀን ውስጥ አልገደለኝምና።
¹⁸ ድካምንና ጣርን አይ ዘንድ ዘመኔም በእፍረት ታልቅ ዘንድ ስለ ምን ከማኅፀን ወጣሁ?
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍2
' ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“እርሱ ግን እባቢቱን ወደ እሳት አራገፋት አንዳችም አልጐዳችውም፤”
ሐዋርያት 28፥5
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“እርሱ ግን እባቢቱን ወደ እሳት አራገፋት አንዳችም አልጐዳችውም፤”
ሐዋርያት 28፥5
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍4
ቅዱሳት መጻሕፍት
#የሮሜ_መልእክት_ጥናት የእግዚአብሔር ፍትሕ (9:19-29) የእግዚአብሔር ሉዓላዊነት ሌላ ችግር የሚፈጥር ይመስላል፡፡ «እግዚአብሔር ሉዓላዊ ከሆነ፣ ማን ሊቋቋመው ይችላል? የሚቋቋመው ካለ ደግሞ እንዴት ሊዳኝ ይችላል?» ይህ እግዚአብሔር በሰው ዘር ታሪክ ውስጥ ስለ ፍትሐዊ አሠራሩ የሚጠየቅ የቆየ ጥያቄ ነው፡፡ በቺካጐ ጎዳና በራሪ መንፈሳዊ ወረቀቶችን ስበትን የሆነውን አስታውሳለሁ። አብዛኛዎቹ…
#የሮሜ_መልእክት_ጥናት
የእግዚአብሔር ፍትሕ (9:19-29)
ሐ) ይህ ሁሉ በትንቢት ተነግሯል (9:25-29)
በመጀመሪያ ጳውሎስ ሆሴዕ 2:23ን ጠቅሶ፣ እግዚአብሔር አይሁድን ትቶ አሕዛብን እንደሚጠራ ያውጃል፡፡ ቀጥሎ ሆሴዕ 1፡10ን አጣቅሶ፣ እነዚህ አዲስ ሕዝቦች የእግዚአብሔር ሕዝብ እና «የሕያው እግዚአብሔር ልጆች›› ተብለው እንደሚጠሩ ያረጋግጣል:: ኢሳይያስ 10:22-23ን ጠቅሶ፣ አብዛኛው እስራኤላዊ ፍርድን እንደሚቀበል ቅሬታዎቹ ግን እንደሚድኑ ያሳያል፡፡ ቁጥር 28 ምናልባትም የሚናገረው እግዚአብሔር በእስራኤል ላይ ስደትንና ፍርድን ስለሚፈጸምበት ስለ መከራው ዘመን ይመስላል፡፡ ቅሬታዎች ብቻ ናቸው ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ምድር ሲመለስ ወደ መንግሥቱ የሚገቡት፡፡ ነገር ግን ዛሬ ከዚህ የምንማረው ነገር ግልጽ ነው፡፡ የሚያምኑት በጣም ጥቂት አይሁድ ብቻ ሲሆኑ፣ እነርሱም ከአሕዛብ ጋር «በእግዚአብሔር የተጠሩ» (ቁ. 24) ይባላሉ፡፡
የመጨረሻው ጥቅስ ከኢሳይያስ 1፡9 የሚያወሳ ሲሆን፣ አጽንኦት የሚሰጠው የሚያምኑትን ቅሬታዎች በሚያድነው እግዚአብሔር ጸጋ ላይ ነው፡፡
አሁን ታዲያ፣ ይህ ሁሉ የሚያስረግጠው ምንድን ነው? እግዚአብሔር አንዳንዶቹን አድኖ በሌሎቹ ላይ መፍረዱ ዐመፀኛ አያደርገውም፤ በብሉይ ኪዳን ከዘመናት በፊት የተነገሩትን ትንቢቶች ወደ ፍጻሜ እያመጣ ነውና፡፡ ቃሉን ባይጠብቅ ኖሮ ዐመፀኛ ይሆን ነበር፡፡ እነዚህ ትንቢቶች እንደሚያሳዩት የእግዚአብሔር ምርጫ አሕዛብ እንዲድኑ አስችሎአቸዋል፡፡ ይህ የእግዚአብሔር ጸጋ ነው፡፡ ከግብጽ ባርነት ነፃ በወጡበት ጊዜ እግዚአብሔር አሕዛብን ትቶ አይሁድን የመረጠው፣ በአይሁድ በኩል አሕዛብን ለማዳን ነው፡፡ የእስራኤል ሕዝብ ፈቃዱን ተቃወሙ፣ ይህ ግን ዓላማውን እንዲያጥፍ አላደረገም:: የአይሁድ ቅሬታዎች አመኑ፣ የእግዚአብሔም ቃል ተፈጸመ፡፡
እስካሁን፣ ጳውሎስ የእግዚአብሔርን ታማኝነት፣ ጽድቅና ፍትሐዊነት በማሳየት የእግዚአብሔርን ባሕርይ ትክክለኝነቱን እንደሚገልጽ እያስረዳ ነው፡፡ እስራኤላውያን ባይቀበሉም፣ የእግዚአብሔርን ምርጫ ሊገቱት አልቻሉም፡፡ ነገር ግን እርሱ ለባሕርይውና ለዓላማው እውነተኛ መሆኑን አረጋገጠ እንጂ፡፡
ይቀጥላል. . .
ምንጭ፦ ዋረን ደብልዩ ዌርዝ ቢ፤ ተስማማ፤ ገጽ 100-101
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የእግዚአብሔር ፍትሕ (9:19-29)
ሐ) ይህ ሁሉ በትንቢት ተነግሯል (9:25-29)
በመጀመሪያ ጳውሎስ ሆሴዕ 2:23ን ጠቅሶ፣ እግዚአብሔር አይሁድን ትቶ አሕዛብን እንደሚጠራ ያውጃል፡፡ ቀጥሎ ሆሴዕ 1፡10ን አጣቅሶ፣ እነዚህ አዲስ ሕዝቦች የእግዚአብሔር ሕዝብ እና «የሕያው እግዚአብሔር ልጆች›› ተብለው እንደሚጠሩ ያረጋግጣል:: ኢሳይያስ 10:22-23ን ጠቅሶ፣ አብዛኛው እስራኤላዊ ፍርድን እንደሚቀበል ቅሬታዎቹ ግን እንደሚድኑ ያሳያል፡፡ ቁጥር 28 ምናልባትም የሚናገረው እግዚአብሔር በእስራኤል ላይ ስደትንና ፍርድን ስለሚፈጸምበት ስለ መከራው ዘመን ይመስላል፡፡ ቅሬታዎች ብቻ ናቸው ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ምድር ሲመለስ ወደ መንግሥቱ የሚገቡት፡፡ ነገር ግን ዛሬ ከዚህ የምንማረው ነገር ግልጽ ነው፡፡ የሚያምኑት በጣም ጥቂት አይሁድ ብቻ ሲሆኑ፣ እነርሱም ከአሕዛብ ጋር «በእግዚአብሔር የተጠሩ» (ቁ. 24) ይባላሉ፡፡
የመጨረሻው ጥቅስ ከኢሳይያስ 1፡9 የሚያወሳ ሲሆን፣ አጽንኦት የሚሰጠው የሚያምኑትን ቅሬታዎች በሚያድነው እግዚአብሔር ጸጋ ላይ ነው፡፡
አሁን ታዲያ፣ ይህ ሁሉ የሚያስረግጠው ምንድን ነው? እግዚአብሔር አንዳንዶቹን አድኖ በሌሎቹ ላይ መፍረዱ ዐመፀኛ አያደርገውም፤ በብሉይ ኪዳን ከዘመናት በፊት የተነገሩትን ትንቢቶች ወደ ፍጻሜ እያመጣ ነውና፡፡ ቃሉን ባይጠብቅ ኖሮ ዐመፀኛ ይሆን ነበር፡፡ እነዚህ ትንቢቶች እንደሚያሳዩት የእግዚአብሔር ምርጫ አሕዛብ እንዲድኑ አስችሎአቸዋል፡፡ ይህ የእግዚአብሔር ጸጋ ነው፡፡ ከግብጽ ባርነት ነፃ በወጡበት ጊዜ እግዚአብሔር አሕዛብን ትቶ አይሁድን የመረጠው፣ በአይሁድ በኩል አሕዛብን ለማዳን ነው፡፡ የእስራኤል ሕዝብ ፈቃዱን ተቃወሙ፣ ይህ ግን ዓላማውን እንዲያጥፍ አላደረገም:: የአይሁድ ቅሬታዎች አመኑ፣ የእግዚአብሔም ቃል ተፈጸመ፡፡
እስካሁን፣ ጳውሎስ የእግዚአብሔርን ታማኝነት፣ ጽድቅና ፍትሐዊነት በማሳየት የእግዚአብሔርን ባሕርይ ትክክለኝነቱን እንደሚገልጽ እያስረዳ ነው፡፡ እስራኤላውያን ባይቀበሉም፣ የእግዚአብሔርን ምርጫ ሊገቱት አልቻሉም፡፡ ነገር ግን እርሱ ለባሕርይውና ለዓላማው እውነተኛ መሆኑን አረጋገጠ እንጂ፡፡
ይቀጥላል. . .
ምንጭ፦ ዋረን ደብልዩ ዌርዝ ቢ፤ ተስማማ፤ ገጽ 100-101
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤4👍1
' ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“ዓለም እናንተን ሊጠላ አይቻለውም፤ እኔ ግን ሥራው ክፉ መሆኑን እመሰክርበታለሁና እኔን ይጠላኛል።”
ዮሐንስ 7፥7
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“ዓለም እናንተን ሊጠላ አይቻለውም፤ እኔ ግን ሥራው ክፉ መሆኑን እመሰክርበታለሁና እኔን ይጠላኛል።”
ዮሐንስ 7፥7
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍5❤1
ከሚከተሉት ስሞች መካከል ተመሳሳይ ወይም ተዛማጅ ትርጉም ያለው የቱ ነው?
Anonymous Quiz
6%
ሀ. ኢየሱስ
3%
ለ. ኢያሱ
3%
ሐ. ኤልሳዕ
67%
መ. ሀ እና ለ
8%
ሠ. ሁሉም
13%
ረ. መልስ የለም
👍10❤1
' ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“ከኤልያስም የወደቀውን መጎናጸፊያ ወስዶ ውኃውን መታና፦ የኤልያስ አምላክ እግዚአብሔር ወዴት ነው? አለ፤ ውኃውንም በመታ ጊዜ ወዲህና ወዲያ ተከፈለ፤ ኤልሳዕም ተሻገረ።”
2ኛ ነገሥት 2፥14
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“ከኤልያስም የወደቀውን መጎናጸፊያ ወስዶ ውኃውን መታና፦ የኤልያስ አምላክ እግዚአብሔር ወዴት ነው? አለ፤ ውኃውንም በመታ ጊዜ ወዲህና ወዲያ ተከፈለ፤ ኤልሳዕም ተሻገረ።”
2ኛ ነገሥት 2፥14
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍8❤1
#ከተማ_ወይም_ቦታ_በቅዱሳት_መጻሕፍት
#ቤተ_ሳይዳ፤
ቤተ ሳይዳ የዓሣ አጥማጅ ቤት ማለት
1. ከገሊላ ባሕር በስተሰሜን የዮርዳኖስ ወንዝ ወደሚገባበት አቅራቢያ ያለ ከተማ፤ የጴጥሮስና የእንድርያስ የፊልጶስም አገር፤ ዮሐ. 1፥44-50፤ 12፥21። ክርስቶስ በቤተ ሳይዳ ዐይነ ስውሩን ፈወሰ፤ ማር. 8፥22-26። ነገር ግን ከተማው ትምህርቱን አልተቀበለም፤ ሉቃ. 1፥13።
2. ሄሮድስ ፊልጶስ ምናልባት ይህን ከተማ፥ ወይም ቤተ ሳይዳ የተባለ ሌላውን ከተማ እንደገና በስተምሥራቅ ሠራ፤ ክርስቶስ በዚህ ከተማ አቅራቢያ ባለው በምድረ በዳ አምስት ሺህ ሰው መገብ፤ ሉቃ. 9፥10-17።
3. በኢየሩሳሌም ውስጥ ደግሞ ቤተ ሳይዳ የምትባል የበሽተኞች መጠመቂያ ቦታ ነበረች፤ ዮሐ. 5፥2። ግን ስምዋ ቤተ ሳይዳ ሳይሆን፥ ቤተ ሔሰዳ፥ ወይም ቤተ ዛታ የነበረ ይመስላል፤ ትርጕሙም «የምሕረት ቤት» ማለት ነው።
ምንጭ፦የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት፣ ገጽ 113-114
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
#ቤተ_ሳይዳ፤
ቤተ ሳይዳ የዓሣ አጥማጅ ቤት ማለት
1. ከገሊላ ባሕር በስተሰሜን የዮርዳኖስ ወንዝ ወደሚገባበት አቅራቢያ ያለ ከተማ፤ የጴጥሮስና የእንድርያስ የፊልጶስም አገር፤ ዮሐ. 1፥44-50፤ 12፥21። ክርስቶስ በቤተ ሳይዳ ዐይነ ስውሩን ፈወሰ፤ ማር. 8፥22-26። ነገር ግን ከተማው ትምህርቱን አልተቀበለም፤ ሉቃ. 1፥13።
2. ሄሮድስ ፊልጶስ ምናልባት ይህን ከተማ፥ ወይም ቤተ ሳይዳ የተባለ ሌላውን ከተማ እንደገና በስተምሥራቅ ሠራ፤ ክርስቶስ በዚህ ከተማ አቅራቢያ ባለው በምድረ በዳ አምስት ሺህ ሰው መገብ፤ ሉቃ. 9፥10-17።
3. በኢየሩሳሌም ውስጥ ደግሞ ቤተ ሳይዳ የምትባል የበሽተኞች መጠመቂያ ቦታ ነበረች፤ ዮሐ. 5፥2። ግን ስምዋ ቤተ ሳይዳ ሳይሆን፥ ቤተ ሔሰዳ፥ ወይም ቤተ ዛታ የነበረ ይመስላል፤ ትርጕሙም «የምሕረት ቤት» ማለት ነው።
ምንጭ፦የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት፣ ገጽ 113-114
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍3❤1👏1
' ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“ጠላቴም ታያለች፥ እኔንም፦ አምላክህ እግዚአብሔር ወዴት ነው? ያለች በእፍረት ትከደናለች።”
ሚክያስ 7፥10
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“ጠላቴም ታያለች፥ እኔንም፦ አምላክህ እግዚአብሔር ወዴት ነው? ያለች በእፍረት ትከደናለች።”
ሚክያስ 7፥10
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍6❤2
#እራሳችንን_እንመርምር
በሕይወት ውጣ ውረድ እና ስንክሳር ውስጥ ስንገባ እግዚአብሔር እንደሚያየን እና እኛ ለመርዳት መፍጠኑን መጠራጠር እንጀምራለን። ግን እውነታው እንደዛ ነው? እግዚአብሔር የማይገደው ሰው አለ? እሺ እሱ እንዳለ ሆኖ እኛስ በሕይወት ጉዞአችን ዓይኖቻችን ወደ እግዚአብሔር ወይስ ወደ ሁኔታ ናቸው?
“እርስዋም ይናገራት የነበረውን የእግዚአብሔርን ስም ኤልሮኢ ብላ ጠራች የሚያየኝን በውኑ እዚህ ደግሞ አየሁትን? ብላለችና።”
ዘፍጥረት 16፥13
“እርሱ እግሮቼን ከወጥመድ ያወጣቸዋልና ዓይኖቼ ሁልጊዜ ወደ እግዚአብሔር ናቸው።”
መዝሙር 25፥15
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
በሕይወት ውጣ ውረድ እና ስንክሳር ውስጥ ስንገባ እግዚአብሔር እንደሚያየን እና እኛ ለመርዳት መፍጠኑን መጠራጠር እንጀምራለን። ግን እውነታው እንደዛ ነው? እግዚአብሔር የማይገደው ሰው አለ? እሺ እሱ እንዳለ ሆኖ እኛስ በሕይወት ጉዞአችን ዓይኖቻችን ወደ እግዚአብሔር ወይስ ወደ ሁኔታ ናቸው?
“እርስዋም ይናገራት የነበረውን የእግዚአብሔርን ስም ኤልሮኢ ብላ ጠራች የሚያየኝን በውኑ እዚህ ደግሞ አየሁትን? ብላለችና።”
ዘፍጥረት 16፥13
“እርሱ እግሮቼን ከወጥመድ ያወጣቸዋልና ዓይኖቼ ሁልጊዜ ወደ እግዚአብሔር ናቸው።”
መዝሙር 25፥15
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍6❤1
' ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“እነሆም እኔ ከአንተ ጋር ነኝ፥ በምትሄድባትም መንገድ ሁሉ እጠብቅሃለሁ፥ ወደዚችም ምድር እመልስሃለሁ፤ የነገርሁህን ሁሉ እስካደርግልህ ድረስ አልተውህምና።”
ዘፍጥረት 28፥15
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“እነሆም እኔ ከአንተ ጋር ነኝ፥ በምትሄድባትም መንገድ ሁሉ እጠብቅሃለሁ፥ ወደዚችም ምድር እመልስሃለሁ፤ የነገርሁህን ሁሉ እስካደርግልህ ድረስ አልተውህምና።”
ዘፍጥረት 28፥15
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍9❤1
በብሉይ ኪዳን ካሉት መጻሕፍት ውስጥ እንደ ዮሐንስ ራእይ አቡቀለምሲሳዊ የሥነ ጹሑፍ መንገድ የሚከተለው የቱ ነው?
Anonymous Quiz
21%
ሀ. ትንቢተ ሕዝቅኤል
14%
ለ. ትንቢተ ኢሳይያስ
57%
ሐ. ትንቢተ ዳንኤል
2%
መ. ትንቢተ ኤርምያስ
3%
ሠ. መዝሙረ ዳዊት
2%
ረ. መጽሐፈ ኢዮብ
❤2