ቅዱሳት መጻሕፍት
7.45K subscribers
1.36K photos
61 videos
332 files
807 links
በዚህ ቻናል

👉ቅዱሳት መጻሕፍት ይጠናሉ::
👉መጽሐፍ ቅዱሳዊ ትምህርቶች ይቀርባሉ::
👉 ለቅዱሳት መጽሐፍት ጥናት የሚያግዙ መጻሕፍት ይለቀቃሉ።

⭐️⭐️⭐️⭐️⭐️

@Holy_scriptures
Download Telegram
finote-1.pdf
1.5 MB
👉ርዕስ፦ ፍኖተ መንግሥት
ከመጀመሪያ እስከ መጨረሻ አንድ መስመር አለ!
✍️ጸሐፊ፦ መርዓዊሥላሴ ንጉሤ (መጋቢ)
📑የገጽ ብዛት፦ 466
📆የታተመበት ዓመት፦ 2004 ዓ.ም



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍3
'    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“እስራኤል ደግነትን ጥሎአል፤ ጠላትም ያሳድዱታል።”
                 ሆሴዕ 8፥3



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
2
#የእግዚአብሔር_ቃል_ምን_ይላል?


መዝሙር 119
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁶⁵ አቤቱ፥ እንደ ቃልህ ለባሪያህ መልካም አደረግህ።
⁶⁶ በትእዛዛትህ ታምኛለሁና መልካም ምክርና እውቀትን አስተምረኝ።
⁶⁷ እኔ ሳልጨነቅ ሳትሁ፤ አሁን ግን ቃልህን ጠበቅሁ።
⁶⁸ አቤቱ፥ አንተ ቸር ነህ፥ በቸርነትህም ሥርዓትህን አስተምረኝ።
⁶⁹ የትዕቢተኞች ዓመፅ በላዬ በዛ፤ እኔ ግን በፍጹም ልቤ ትእዛዛትህን እፈልጋለሁ።
⁷⁰ ልባቸው እንደ ወተት ረጋ፤ እኔ ግን በሕግህ ደስ ይለኛል።
⁷¹ ሥርዓትህን እማር ዘንድ ያስጨነቅኸኝ መልካም ሆነልኝ።
⁷² ከአእላፋት ወርቅና ብር ይልቅ የአፍህ ሕግ ይሻለኛል።
⁷³ እጆችህ ሠሩኝ አበጃጁኝም፤ እንዳስተውል አድርገኝ፥ ትእዛዛትህንም እማራለሁ።
⁷⁴ በቃልህ ታምኛለሁና የሚፈሩህ እኔን አይተው ደስ ይላቸዋል።
⁷⁵ አቤቱ፥ ፍርድህ ጽድቅ እንደ ሆነች፥ በእውነትህም እንዳስቸገርኸኝ አወቅሁ።
⁷⁶ ምሕረትህ ለመጽናናቴ ትሁነኝ፥ እንደ ቃልህም ለባሪያህ ይሁነው።
⁷⁷ ሕግህ ተድላዬ ናትና ቸርነትህ ትምጣልኝ፥ በሕይወትም ልኑር።
⁷⁸ ትዕቢተኞች በዓመፅ ጠምመውብኛልና ይፈሩ፤ እኔ ግን በትእዛዝህ እጫወታለሁ።
⁷⁹ የሚፈሩህና ምስክሮችህን የሚያውቁ ወደ እኔ ይመለሱ።
⁸⁰ እንዳላፍር ልቤ በሥርዓትህ የቀና ይሁን።



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
4👍1
'    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“ነገር ግን ጥበብ የምትገኘው ወዴት ነው? የማስተዋልስ ስፍራ ወዴት ነው?”
               ኢዮብ 28፥12



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍41
የአማኝ ሕይወት በእድገት መቀጠል ሲገባው ለምን ወደ ኋላ ይላል?

በመንፈሳዊ ሕይወት ውስጥ ከማደግ ይልቅ ወደ ኋላ ማፈግፈግ ብዙ ጊዜ ይስተዋላል። ከእነዚህ ምክንያቶች ውስጥ ዛሬ አንዱን እንመለከታለን።

1. "ተንኰልን የሙጥኝ " ብሎ ሲይዝ

2. "ሊመለስም እንቢ" ሲል

“እንግዲህ ይህ የኢየሩሳሌም ሕዝብ ዘወትር ስለ ምን ወደ ኋላው ይመለሳል? ተንኰልን ይዞአል ሊመለስም እንቢ ብሎአል።”
(ኤርምያስ 8፥5)

“ታዲያ፣ ይህ ሕዝብ ለምን ፊቱን አዙሮ ወደ ኋላ ይሄዳል? ለምንስ ኢየሩሳሌም ዘወትር ወደ ኋላ ትመለሳለች? ተንኰልን የሙጥኝ ብለው ይዘዋል፤ ሊመለሱም ፈቃደኛ አይደሉም።”
ኤርምያስ 8፥5 (አዲሱ መ.ት)


"እንግዲህ ክፋትን ሁሉ ተንኰልንም ሁሉ ግብዝነትንም ቅንዓትንም ሐሜትንም ሁሉ አስወግዳችሁ፥ ጌታ ቸር መሆኑን ቀምሳችሁ እንደ ሆነ፥ ለመዳን በእርሱ እንድታድጉ አሁን እንደ ተወለዱ ሕፃናት ተንኰል የሌለበትን የቃልን ወተት ተመኙ።"
(1ኛ ጴጥሮስ 2፥1-3)

ለመሆኑ "ተንኮል" ማለት ምን ማለት ነው? እስቲ በዚህ ነገር በአሳብ መስጫው ላይ አሳብ ስጡበት፤ ተወያዩበትም።



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍112
'    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“ለራስህ ታላቅን ነገር ትፈልጋለህን? በሥጋ ለባሽ ሁሉ ላይ፥ እነሆ፥ ክፉ ነገርን አመጣለሁና አትፈልገው፥ ይላል እግዚአብሔር፤ ነገር ግን በሄድህበት ስፍራ ሁሉ ነፍስህን እንደ ምርኮ አድርጌ እሰጥሃለሁ።”
              ኤርምያስ 45፥5




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍41
#ከተማ_ወይም_ቦታ_በቅዱሳት_መጻሕፍት


#ናዝሬት

ናዝሬት፤ ከገሊላ ባሕር በስተምዕራብ 25 ኪ.ሜ. ርቆ በዛብሎን ነገድ ድርሻ ውስጥ በተራራማ አገር ላይ የተመሠረተ ከተማ ናት። ናዝሬት በብሉይ ኪዳን አልተጠቀሰም፤ በአዲስ ኪዳን ዘመንም ቦታው ወደ አገሩ ጠረፍ ስለሆነ ዝቅተኛ ግምት ይሰጠው ነበር፤ ዮሐ. 1፥47። ናዝሬት የዮሴፍና የማርያም መኖሪያ ከተማ ነበረ። ኢየሱስ በዚህ ተፀነሰ፤ በኋላም አደገበት፤ ሉቃ. 1፥26:27፤ 2፥39:40:51። ኢየሱስ የማስተማር ሥራውን ከጀመረ በኋላ አንድ ጊዜ ወደ ናዝሬት መጣ፤ ሕዝቡ ግን አልተቀበሉትም፤ ሉቃ. 4፥16-30። ዛሬ 30 ሺህ ያህል ሰዎች በናዝሬት ይኖራሉ።



ምንጭ፦የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት፣ ገጽ 140-141




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
5👍4👎1
'    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“ጥበብም ለልጆችዋ ሁሉ ጸደቀች።”
               ሉቃስ 7፥35



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
1👍1
ውድ የቻናላችን ቤተሰቦች ከ #4_ሺህ በላይ "subscribers" ስላገኘን ከልብ እናመሰግናለን! በዚህ ቻናል የሚመቻችሁን ነገር እና ይስተካከል፣ ይታረም፣ ይጨመር፣ ይቀነስ የምትሉትን ነገር በአሳብ መስጫው ላይ እንድታካፍሉን ስንል በትህትና እንጠይቃለን።



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍1
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
👍6
'    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“ኃጢአተኛ መቶ ጊዜ ክፉን ቢሠራ ዘመኑም ረጅም ቢሆን፥ እግዚአብሔርን ለሚፈሩት በፊቱም ለሚፈሩት ደኅንነት እንዲሆን አውቃለሁ፤”
              መክብብ 8፥12



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
5
#እራሳችንን_እንመርምር


ለምንድነው የምንጸልየው? ጸሎታችን በእርግጥ እንደሚመለስ እናምናለን? የምንቀበለው የጸለይነውን ወይስ ከዚያ በላይ?


“እንግዲህ በእኛ እንደሚሠራው ኃይል መጠን ከምንለምነው ወይም ከምናስበው ሁሉ ይልቅ እጅግ አብልጦ ሊያደርግ ለሚቻለው፥”
ኤፌሶን 3፥20



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍52
'    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“የእስራኤልም ልጆች በባሕሩ መካከል በየብስ ገቡ፥ ውኃውም በቀኛቸውና በግራቸው እንደ ግድግዳ ሆነላቸው።”
               ዘጸአት 14፥22



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍4🔥21
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍2
ጰራቅሊጦስ-2.pdf
752.5 KB
👉ርዕስ፦ ጰርቅሊጦስ
መንፈስ ቅዱስና ሥራው
✍️ጸሐፊ፦ ሰይፉ ከበደ
📑የገጽ ብዛት፦ 181


ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
'    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“መልካሙን የእምነት ገድል ተጋደል፥ የተጠራህለትንም በብዙም ምስክሮች ፊት በመልካም መታመን የታመንህለትን የዘላለምን ሕይወት ያዝ።”
              1ኛ ጢሞቴዎስ 6፥12



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍73🥰3
በዓለ ጰራቅሊጦስ


ዲያቆን ልሳነጽድቅ ኪዳነ



መንፈስ ቅዱስ ከሚጠራባቸው ስሞች አንዱ ጰራቅሊጦስ ናዛዚ መጽንዒ መስተፍሥሒ፤ የሚያጽናና፣ የሚመክር፣ የሚረዳ፣ የሚታደግ የሚል ትርጉም አለው፡፡ አጽናኝም የተባለው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። ‹‹አብ በስሜ የሚልከው ግን መንፈስ ቅዱስ የሆነው አጽናኝ እርሱ ሁሉን ያስተምራችኋል፤ እኔም የነገርኋችሁን ሁሉ ያሳስባችኋ›› ብሎ ተናግሯል፡፡ በሌላም በኩል ደግሞ ‹‹እኔ ከአብ ዘንድ የምልክላችሁ ጰራቅሊጦስ እርሱም ከአብ የሚወጣ የእውነት መንፈስ በመጣ ጊዜ፥ እርሱ ስለ እኔ ይመሰክራል›› እንዲል። (ዮሐ.፲፬፥፳፮፤ ፲፭፥፲፮)

ጰራቅሊጦስ የሚለው የመንፈስ ቅዱስ ስም የሚያጽናና፣ የሚመክር፣ የሚረዳ፣ የሚታደግ መሆኑም ከማሳየት በላይ፤ ፍጹም አካል ያለው አምላክ እንደሆነ አመልካች ነው። ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ጰራቅሊጦስ ማለት መሪ፣ አጽናኝ፣ ረጂ ማለት መሆኑን በስፋት ካስተማሩ ሊቃውንት በቀዳሚነት ይነሳል። ጰራቅሊጦሰ የተባለው መንፈስ ቅዱስ እግዚአብሔር ነው። ሐዋርያዊት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በመንፈስ ቅዱስ ያላትን እምነቷን ስትገልጥ ‹‹ወነአምን በመንፈስ ቅዱስ እግዚእ ማኅየዊ ዘሠረፀ እም አብ ንሰግድ ሎቱ ወንሰብሖ ምስለ አብ ወወልድ››፤ በመንፈስ ቅዱስ እናምናለን እርሱም ጌታ ሕይወትን የሚሰጥ ከአብ የሠረፀ ከአብ ከወልድ ጋራ በአንድነት እንሰግድለታለን፣ እናመሰግነዋለን፤›› የሚል ነው።

እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ቅዱስ፤ የቅድስናም ምንጭ ነው። አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ‹‹ወስመ መንፈስ ቅዱስ ነቅዐ ቅድሳትየ፤ የመንፈስ ቅዱስም ስም የቅድስናየ መገኛ ነው›› በማለት ገልጾታል። (መጽሐፈ ምሥጢር)

ቅዱስ ባስልዮስም በቅዳሴው ‹‹ሃሌ ሉያ ቅዱስ መንፈስ ቅዱስ ጰራቅሊጦስ መጽንዒ ቅድመ ዓለም የነበረ ዓለምን አሳልፎ የሚኖር መንፈስ ቅዱስ ንጹሕ ክቡር ልዩ ነው›› በማለት አምላካዊ ስሙን ጠርቶ አመስግኖታል። ቅድስት ቤተ ክርስቲያንም ዕለት ዕለት በምታከናውነው ሥርዓተ ቅዳሴ ‹‹መንጽሒ ወመጽንዒ የሚሆን መንፈስ ቅዱስ ክቡር ምስጉን ነው›› እያለች የአምላክነት ስሙን ጠርታ ታመሰግነዋለች።

ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ሃይማኖት ሊያጸኑ ከሓድያንን ሊለዩ (ሊያወግዙ) ሲሰባሰቡ በመካከላቸው ተገኝቶ ውሳኔ ያስወስናቸው የነበረው እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ እንደሆነ ሲገልጹ ጰራቅሊጦስ የተባለ ስሙን ጠርተው እንዲህ ብለዋል፣ ‹‹ወሀሎ ምስሌሆሙ ኅብረ መንፈስ ቅዱስ …. ጰራቅሊጦስ የሚያነጻና የሚያጸና መንፈስ ቅዱስም በጉባኤያቸው ነበረ፡፡›› (መጽሐፈ ምሥጢር)

ጌታችን አምላካችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ካረገ በኋላ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም፣ ዐሥራ ሁለቱ ደቀ መዛሙርት፣ ሰባ ሁለቱ አርድእት እና ሠላሳ ስድስቱ ቅዱሳት አንስት በኢየሩሳሌም ከተማ በአንድነት ሆነው በጸሎት ይተጉ ነበር፡፡ ጌታችን በሚያርግበት ጊዜ ‹‹እነሆ አባቴ የሰጠውን ተስፋ እኔ እልክላችኋለሁ፤ እናንተ ግን ከላይ ኃይል እስክትለብሱ ድረስ በኢየሩሳሌም ከተማ ቆዩ፤›› ሲል ለሐዋርያቱ በሰጣቸው የተስፋ ቃል መሠረት በዐረገ በዐሥረኛው ቀን መንፈስ ቅዱስን ልኮላቸዋል (ሉቃ. ፳፬፥፵፱)፡፡ ሁሉም በአንድ ቦታ ተሰባስበው ሳሉ እንደ ዐውሎ ነፋስ ያለ ድምፅ ድንገት ከሰማይ ወርዶ የነበሩበትን ቤት ሞላው፡፡ ከዚያም የተከፋፈሉ የእሳት ላንቃዎች በሁሉም ላይ አረፉባቸው፡፡ በዚህ ጊዜ ሁላቸውም መንፈስ ቅዱስ ባደላቸው መጠን በየሀገሩ ቋንቋዎች ሁሉ ተናገሩ፡፡ (ሐዋ.፪፥፩-፬)

ይቀጥላል. . .


ምንጭ፦ https://eotcmk.org



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍6
'    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“ብትወዱኝ ትእዛዜን ጠብቁ። እኔም አብን እለምናለሁ ለዘላለምም ከእናንተ ጋር እንዲኖር ሌላ አጽናኝ ይሰጣችኋል፤”
                 ዮሐንስ 14፥15-16



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
9