' ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“የእግዚአብሔርን ሥራ በቸልታ የሚያደግ ርጉም ይሁን፥ ሰይፉንም ከደም የሚከለክል ርጉም ይሁን።”
ኤርምያስ 48፥10
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“የእግዚአብሔርን ሥራ በቸልታ የሚያደግ ርጉም ይሁን፥ ሰይፉንም ከደም የሚከለክል ርጉም ይሁን።”
ኤርምያስ 48፥10
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍9❤1
#የሮሜ_መልእክት_ጥናት
የእግዚአብሔር ፍትሕ (9:19-29)
የእግዚአብሔር ሉዓላዊነት ሌላ ችግር የሚፈጥር ይመስላል፡፡ «እግዚአብሔር ሉዓላዊ ከሆነ፣ ማን ሊቋቋመው ይችላል? የሚቋቋመው ካለ ደግሞ እንዴት ሊዳኝ ይችላል?» ይህ እግዚአብሔር በሰው ዘር ታሪክ ውስጥ ስለ ፍትሐዊ አሠራሩ የሚጠየቅ የቆየ ጥያቄ ነው፡፡
በቺካጐ ጎዳና በራሪ መንፈሳዊ ወረቀቶችን ስበትን የሆነውን አስታውሳለሁ። አብዛኛዎቹ ሰዎች ትራክቶችን በምሥጋና የተቀበሉኝ ሲሆን፣ አንዱ ግን ጭምድድ አድርጎ የውኃ አሸንዳ ውስጥ ወረወረው። የትራክቱ ስም «እግዚአብሔር እንድታውቃቸው የሚፈልገው አራት ነገሮች» የሚል ነበር።
ሰውየው፣ «እግዚአብሔር እንዲያውቃቸው የምፈልገው ጥቂት ነገሮች አሉ» አለ፡፡ «በዚህ ዓለም ለምን ብዙ ኀዘንና ሰቆቃ ኖረ? ሀብታሞች በነጻነት ሲመላለሱ ምስኪኖች ለምን ይሠቃያሉ?» ብሎ በንቀት ገላመጠኝና፣ «እግዚአብሔር አለ ብለህ አትንገረኝ! እግዚአብሔር ካለ በዓለም ላይ ከኖሩ ኃጢአተኞች ትልቁ እርሱ ነው!» አለና በንቀት ጀርባውን ሰጥቶኝ ከሕዝቡ ጋር ተቀላቀለ፡፡
እግዚአብሔር በባሕርይው ፍጹም እንደሆነ እናውቃለን፡፡ «የምድር ሁሉ ፈራጅ በቅን ፍርድ አይፈርድምን?» (ዘፍጥ. 18:25) እግዚአብሔር ዓመፅን ሲያደርግ ወይም ዐመፀኛ ዓላማና ፈቃድ እንዳለው ፈጽሞ የማይታሰብ ነው፡፡ አንዳንድ ጊዜ ግን እንዲህ የሚያደርግ ይመስላል፡፡ ለሙሴ ምሕረትን አደረገ፣ በፈርዖን ላይ ግን ፈረደበት፡፡ ይህ ትክክል ነውን? እስራኤልን መረጠ፣ ሌሎቹን አሕዛብ ተዋቸው። ይህ ልክ ነውን? ጳውሎስ ለዚህ ክስ ሦስት መልሶችን ሰጥቷል::
ሀ) ለእግዚአብሔር የምንመልስ እኛ ማን ነን? (9:19-21)
ይህ ሥነ - አመክንዮአዊ ነው፡፡ እግዚአብሔር ሠሪያችን ከሆነ፣ እኛ ደግሞ ሸክላዎች ነን፡፡ እግዚአብሔር ከእኛ ይልቅ ጥበበኛ ስለሆነ፣ የእግዚአብሔርን ፈቃድ ልናርም ወይም ልንቋቋም መሞከራችን ሞኝነት ነው:: (የዚህ ምንባብ ማጣቃሻ ኢሳ. 45:9 ነው::) ሸክላ ሕይወት የለውም፣ በሠሪው እጅም ላይ ተጽዕኖ ማሳደር አይችልም:: ስሜት፣ እውቀትና ፈቃድ ስላለን ከፈለግን እግዚአብሔርን ልንቃወመው እንችላለን:: (ኤርምያስ 18ን አንብቡ)፡፡ ነገር ግን አንድ ሰው ሙሴን ወይም ፈርዖንን እንዲሆን የሚወስነው እግዚአብሔር ነው፡፡ ሙሴም ሆነ ፈርዖን እንዲሁም ማንኛውም ሰው ወላጆችን መምረጥ፣ የሚወለድበትን ቦታና ጊዜ መምረጥ ወይም ምን ዓይነት ቁመና እንደሚኖረው መምረጥ፣ አይችልም:: እነዚህ ነገሮች በእግዚአብሔር እጅ መሆናቸውን ማመን አለብን::
ነገር ግን፣ ይህ መሆኑ ከተጠያቂነት አያድነንም፡፡ ፈርዖን ስለ እውነተኛው አምላክ የመማር ትልቅ ዕድል ነበረው፡፡ ነገር ግን ማመፅ ፈለገ፡፡ ጳውሎስ ይህንን እውነት የጠቀሰው የሚያስተምረው ጭብጥ መለኮታዊ ሉዓላዊነት እንጂ የሰው ተጠያቂነት ስለሆነ አይደለም፡፡ ውስኑ አእምሮአችን ሁለቱንም በሙላት ባይረዳም፣ አንዱ ሌላኛውን አይክድም፡፡
ለ) እግዚአብሔር የራሱ ዓላማ አለው (9:22-24)
እግዚአብሔር እንደ ፈርዖን ያለውን ጨካኝ እያየ ይደሰታል ማለት አይደለም፡፡ እግዚአብሔር ለሙሴ «የሕዝቤን መከራ በእውነት አየሁ ጨኸታቸውን ሰማሁ ሥቃያቸውን አውቃለሁ» (ዘጸ. 3:7) አለው፡፡ ይህ የሚያመለክተው እግዚአብሔር ለፈርዖን ዕድል መስጠቱን ነው (2ኛ ጴጥ. 3፡9)። በቁጥር 22 ላይ እግዚአብሔር ፈርዖንን የቁጣ ዕቃ አድርጎ አልመረጠውም፡፡ እግዚአብሔር ሰዎችን የሚያዘጋጃቸው ለክብር ነው (ቁ. 23):: ነገር ግን ኃጢአተኞች ራሳቸውን ለፍርድ ያዘጋጃሉ፡፡ በሙሴና በእስራኤል እግዚአብሔር የምሕረቱን ባለጠግነት ገለጠ፡፡ በፈርዖንና በግብፅ ላይ ደግሞ ኃይሉንና ቁጣውን ገለጠ፡፡ ማናቸውም ምሕረት የተገባቸው ስላልሆኑ፣ እግዚአብሔር በዐመፅ ሊከሰስ አይችልም፡፡
በፍጻሜውም የእግዚአብሔር ዓላማው በቤተ ክርስቲያኑ አይሁድንና አሕዛብን (ቁ. 24) ለመፍጠር ነው:: ዛሬ አማኞች በእግዚአብሔር ጸጋ «የምሕረት ዕቃዎች» ሆነው ለክብር እየተዘጋጁ ሲሆን፣ ይህም እውነት ሮሜ 8:29-30 ያለውን ክፍል ያስታውሰናል፡፡
ይቀጥላል. . .
ምንጭ፦ ዋረን ደብልዩ ዌርዝ ቢ፤ ተስማማ፤ ገጽ 98-100
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የእግዚአብሔር ፍትሕ (9:19-29)
የእግዚአብሔር ሉዓላዊነት ሌላ ችግር የሚፈጥር ይመስላል፡፡ «እግዚአብሔር ሉዓላዊ ከሆነ፣ ማን ሊቋቋመው ይችላል? የሚቋቋመው ካለ ደግሞ እንዴት ሊዳኝ ይችላል?» ይህ እግዚአብሔር በሰው ዘር ታሪክ ውስጥ ስለ ፍትሐዊ አሠራሩ የሚጠየቅ የቆየ ጥያቄ ነው፡፡
በቺካጐ ጎዳና በራሪ መንፈሳዊ ወረቀቶችን ስበትን የሆነውን አስታውሳለሁ። አብዛኛዎቹ ሰዎች ትራክቶችን በምሥጋና የተቀበሉኝ ሲሆን፣ አንዱ ግን ጭምድድ አድርጎ የውኃ አሸንዳ ውስጥ ወረወረው። የትራክቱ ስም «እግዚአብሔር እንድታውቃቸው የሚፈልገው አራት ነገሮች» የሚል ነበር።
ሰውየው፣ «እግዚአብሔር እንዲያውቃቸው የምፈልገው ጥቂት ነገሮች አሉ» አለ፡፡ «በዚህ ዓለም ለምን ብዙ ኀዘንና ሰቆቃ ኖረ? ሀብታሞች በነጻነት ሲመላለሱ ምስኪኖች ለምን ይሠቃያሉ?» ብሎ በንቀት ገላመጠኝና፣ «እግዚአብሔር አለ ብለህ አትንገረኝ! እግዚአብሔር ካለ በዓለም ላይ ከኖሩ ኃጢአተኞች ትልቁ እርሱ ነው!» አለና በንቀት ጀርባውን ሰጥቶኝ ከሕዝቡ ጋር ተቀላቀለ፡፡
እግዚአብሔር በባሕርይው ፍጹም እንደሆነ እናውቃለን፡፡ «የምድር ሁሉ ፈራጅ በቅን ፍርድ አይፈርድምን?» (ዘፍጥ. 18:25) እግዚአብሔር ዓመፅን ሲያደርግ ወይም ዐመፀኛ ዓላማና ፈቃድ እንዳለው ፈጽሞ የማይታሰብ ነው፡፡ አንዳንድ ጊዜ ግን እንዲህ የሚያደርግ ይመስላል፡፡ ለሙሴ ምሕረትን አደረገ፣ በፈርዖን ላይ ግን ፈረደበት፡፡ ይህ ትክክል ነውን? እስራኤልን መረጠ፣ ሌሎቹን አሕዛብ ተዋቸው። ይህ ልክ ነውን? ጳውሎስ ለዚህ ክስ ሦስት መልሶችን ሰጥቷል::
ሀ) ለእግዚአብሔር የምንመልስ እኛ ማን ነን? (9:19-21)
ይህ ሥነ - አመክንዮአዊ ነው፡፡ እግዚአብሔር ሠሪያችን ከሆነ፣ እኛ ደግሞ ሸክላዎች ነን፡፡ እግዚአብሔር ከእኛ ይልቅ ጥበበኛ ስለሆነ፣ የእግዚአብሔርን ፈቃድ ልናርም ወይም ልንቋቋም መሞከራችን ሞኝነት ነው:: (የዚህ ምንባብ ማጣቃሻ ኢሳ. 45:9 ነው::) ሸክላ ሕይወት የለውም፣ በሠሪው እጅም ላይ ተጽዕኖ ማሳደር አይችልም:: ስሜት፣ እውቀትና ፈቃድ ስላለን ከፈለግን እግዚአብሔርን ልንቃወመው እንችላለን:: (ኤርምያስ 18ን አንብቡ)፡፡ ነገር ግን አንድ ሰው ሙሴን ወይም ፈርዖንን እንዲሆን የሚወስነው እግዚአብሔር ነው፡፡ ሙሴም ሆነ ፈርዖን እንዲሁም ማንኛውም ሰው ወላጆችን መምረጥ፣ የሚወለድበትን ቦታና ጊዜ መምረጥ ወይም ምን ዓይነት ቁመና እንደሚኖረው መምረጥ፣ አይችልም:: እነዚህ ነገሮች በእግዚአብሔር እጅ መሆናቸውን ማመን አለብን::
ነገር ግን፣ ይህ መሆኑ ከተጠያቂነት አያድነንም፡፡ ፈርዖን ስለ እውነተኛው አምላክ የመማር ትልቅ ዕድል ነበረው፡፡ ነገር ግን ማመፅ ፈለገ፡፡ ጳውሎስ ይህንን እውነት የጠቀሰው የሚያስተምረው ጭብጥ መለኮታዊ ሉዓላዊነት እንጂ የሰው ተጠያቂነት ስለሆነ አይደለም፡፡ ውስኑ አእምሮአችን ሁለቱንም በሙላት ባይረዳም፣ አንዱ ሌላኛውን አይክድም፡፡
ለ) እግዚአብሔር የራሱ ዓላማ አለው (9:22-24)
እግዚአብሔር እንደ ፈርዖን ያለውን ጨካኝ እያየ ይደሰታል ማለት አይደለም፡፡ እግዚአብሔር ለሙሴ «የሕዝቤን መከራ በእውነት አየሁ ጨኸታቸውን ሰማሁ ሥቃያቸውን አውቃለሁ» (ዘጸ. 3:7) አለው፡፡ ይህ የሚያመለክተው እግዚአብሔር ለፈርዖን ዕድል መስጠቱን ነው (2ኛ ጴጥ. 3፡9)። በቁጥር 22 ላይ እግዚአብሔር ፈርዖንን የቁጣ ዕቃ አድርጎ አልመረጠውም፡፡ እግዚአብሔር ሰዎችን የሚያዘጋጃቸው ለክብር ነው (ቁ. 23):: ነገር ግን ኃጢአተኞች ራሳቸውን ለፍርድ ያዘጋጃሉ፡፡ በሙሴና በእስራኤል እግዚአብሔር የምሕረቱን ባለጠግነት ገለጠ፡፡ በፈርዖንና በግብፅ ላይ ደግሞ ኃይሉንና ቁጣውን ገለጠ፡፡ ማናቸውም ምሕረት የተገባቸው ስላልሆኑ፣ እግዚአብሔር በዐመፅ ሊከሰስ አይችልም፡፡
በፍጻሜውም የእግዚአብሔር ዓላማው በቤተ ክርስቲያኑ አይሁድንና አሕዛብን (ቁ. 24) ለመፍጠር ነው:: ዛሬ አማኞች በእግዚአብሔር ጸጋ «የምሕረት ዕቃዎች» ሆነው ለክብር እየተዘጋጁ ሲሆን፣ ይህም እውነት ሮሜ 8:29-30 ያለውን ክፍል ያስታውሰናል፡፡
ይቀጥላል. . .
ምንጭ፦ ዋረን ደብልዩ ዌርዝ ቢ፤ ተስማማ፤ ገጽ 98-100
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍8
' ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“ቈዳዬ ቢጠፋም፣ ከሥጋዬ ብለይም፣ እግዚአብሔርን አየዋለሁ፤”
ኢዮብ 19፥26 (አዲሱ መ.ት)
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“ቈዳዬ ቢጠፋም፣ ከሥጋዬ ብለይም፣ እግዚአብሔርን አየዋለሁ፤”
ኢዮብ 19፥26 (አዲሱ መ.ት)
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤5
ቅዱሳት መጻሕፍት
የቀጠለ... አራቱ ደስታችንን ሊጠብቁ የሚችሉ አመለካከቶች 2. የሚገዛ አሳብ - ፊልጵስዩስ 2 ይህ ምዕራፍ የሚያተኩረው በሰዎች ላይ ነው፥ መሪ ጥቅሱም «ለወገኔ ይጠቅማል በማለት ወይም በከንቱ ውዳሴ ምክንያት አንድ እንኳ አታድርጉ፥ ነገር ግን እያንዳንዱ ባልንጀራው ከራሱ ይልቅ እንዲሻል በትሕትና ይቁጠር» (2፡3)። በምዕራፍ 1 ላይ ጳውሎስ ክርስቶስን የመጀመሪያው መሻቱ ሲያደርግ፥ በዚህ ምዕራፍ፥…
የቀጠለ...
አራቱ ደስታችንን ሊጠብቁ የሚችሉ አመለካከቶች
3. መንፈሳዊ አሳብ - ፊልጵስዩስ 3
በዚህ ምዕራፍ ውስጥ ጳውሎስ ወደ አሥራ አንድ ጊዜ ያህል «ነገር» የሚለውን ቃል ሲጠቀም ታገኛላችሁ። የአብዛኛዎቹ ሰዎች «አሳባቸው ምድራዊ» (3፡19) ለሆኑ ነገሮች ሲሆን፥ መንፈሳዊ ልብ ያላቸው ክርስቲያኖች ግን የሚጨነቁት ስለ ሰማያዊ ነገሮች መሆኑን ያሳየናል። «እኛ አገራችን በሰማይ ነውና፥ ከዚያም ደግሞ የሚመጣ መድኃኒት እርሱም ጌታን ኢየሱስ ክርስቶስን እንጠባበቃለን» (3፡20)። መንፈሳዊ ልብ ያለው ሰው የዚህን ዓለም ነገሮች የሚያያቸው በሰማያዊ አመለካከት አንፃር ነው - ታዲያ ይህ ምን ያህል ትልቅ ልዩነት ያመጣል!
በኢኳዶር ኡካስ ውስጥ አምስት ሚሲዮናዊያን በተገደሉበት ጊዜ አሳዛኝ የሆነው አሟሟታቸውን አንዳንድ ጋዜጦችና መጽሔቶች ታላቅ የሕይወት ጥፋት በማለት ገልጸውታል። በዚያን ጊዜ ለጓደኞቻቸውና ለወዳጆቻቸው ታላቅ ሀዘንና ቁጭት ቢያደርስባቸውም የኋላ ኋላ ግን ሞታቸው ለእነርሱም ሆነ ለዓለም «ጥፋት» እንዳልሆነ ተረጋገጠ። ጅም እልይት የተባለው ሰባኪ፥ «ሰው መያዝ የማይችለውን በመስጠት፥ ማጣት የማይችለውን ካገኘ ሞኝ አያሰኘውም» ሲል የተናገረው በእውነትም ትክክለኛ ነበር።
«ምድራዊ ነገርን» ፍለጋ መሮጥ የሰዎችን ደስታ ይሰርቃል፥ እና ይህ ደግሞ ክርስቲያኖችንም ይጨምራል። እኛ አንድን ነገር ለመያዝ እንፈልጋለን፥ በኋላ ግን እርሱ እኛን ተቆጣጥሮን እናገኘዋለን። ለዕድልና ለደስታ ብቸኛው መንገድ መንፈሳዊ ልብ መኖርና ነገሮችን ከእግዚአብሔር ወገን ሆኖ ማየት ነው። እንደ ጳውሎስ፥ ለነገሮች ትክክለኛ ሚዛን ያለን ሰዎች (3፡1-11)፥ ትክክለኛ ወኔ ያለን ሯጮች (3፡12-16) ወገናዊነት የማያጠቃን ትክክለኛ ራእይ ያለን ተቆርቋሪዎች (3፡17-21) መሆን አለብን። «እቆጥራለሁ ... እፈጥናለሁ ... እመለከታለሁ» የሚሉት ግሦች መንፈሳዊ ልብ (አስተሳሰብ) ያለውን ሰው ይገልጻሉ።
ይቀጥላል...
ምንጭ፦ ዋረን ደብልዩ ዌርዝ ቢ፤ ደስተኛ ሁን፤ የፊልጵስዩስ መልእክት ፤ ገጽ 8
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
አራቱ ደስታችንን ሊጠብቁ የሚችሉ አመለካከቶች
3. መንፈሳዊ አሳብ - ፊልጵስዩስ 3
በዚህ ምዕራፍ ውስጥ ጳውሎስ ወደ አሥራ አንድ ጊዜ ያህል «ነገር» የሚለውን ቃል ሲጠቀም ታገኛላችሁ። የአብዛኛዎቹ ሰዎች «አሳባቸው ምድራዊ» (3፡19) ለሆኑ ነገሮች ሲሆን፥ መንፈሳዊ ልብ ያላቸው ክርስቲያኖች ግን የሚጨነቁት ስለ ሰማያዊ ነገሮች መሆኑን ያሳየናል። «እኛ አገራችን በሰማይ ነውና፥ ከዚያም ደግሞ የሚመጣ መድኃኒት እርሱም ጌታን ኢየሱስ ክርስቶስን እንጠባበቃለን» (3፡20)። መንፈሳዊ ልብ ያለው ሰው የዚህን ዓለም ነገሮች የሚያያቸው በሰማያዊ አመለካከት አንፃር ነው - ታዲያ ይህ ምን ያህል ትልቅ ልዩነት ያመጣል!
በኢኳዶር ኡካስ ውስጥ አምስት ሚሲዮናዊያን በተገደሉበት ጊዜ አሳዛኝ የሆነው አሟሟታቸውን አንዳንድ ጋዜጦችና መጽሔቶች ታላቅ የሕይወት ጥፋት በማለት ገልጸውታል። በዚያን ጊዜ ለጓደኞቻቸውና ለወዳጆቻቸው ታላቅ ሀዘንና ቁጭት ቢያደርስባቸውም የኋላ ኋላ ግን ሞታቸው ለእነርሱም ሆነ ለዓለም «ጥፋት» እንዳልሆነ ተረጋገጠ። ጅም እልይት የተባለው ሰባኪ፥ «ሰው መያዝ የማይችለውን በመስጠት፥ ማጣት የማይችለውን ካገኘ ሞኝ አያሰኘውም» ሲል የተናገረው በእውነትም ትክክለኛ ነበር።
«ምድራዊ ነገርን» ፍለጋ መሮጥ የሰዎችን ደስታ ይሰርቃል፥ እና ይህ ደግሞ ክርስቲያኖችንም ይጨምራል። እኛ አንድን ነገር ለመያዝ እንፈልጋለን፥ በኋላ ግን እርሱ እኛን ተቆጣጥሮን እናገኘዋለን። ለዕድልና ለደስታ ብቸኛው መንገድ መንፈሳዊ ልብ መኖርና ነገሮችን ከእግዚአብሔር ወገን ሆኖ ማየት ነው። እንደ ጳውሎስ፥ ለነገሮች ትክክለኛ ሚዛን ያለን ሰዎች (3፡1-11)፥ ትክክለኛ ወኔ ያለን ሯጮች (3፡12-16) ወገናዊነት የማያጠቃን ትክክለኛ ራእይ ያለን ተቆርቋሪዎች (3፡17-21) መሆን አለብን። «እቆጥራለሁ ... እፈጥናለሁ ... እመለከታለሁ» የሚሉት ግሦች መንፈሳዊ ልብ (አስተሳሰብ) ያለውን ሰው ይገልጻሉ።
ይቀጥላል...
ምንጭ፦ ዋረን ደብልዩ ዌርዝ ቢ፤ ደስተኛ ሁን፤ የፊልጵስዩስ መልእክት ፤ ገጽ 8
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍3
' ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“በቍጣ ቀን ሀብት አትረባም፤ ጽድቅ ግን ከሞት ታድናለች።”
ምሳሌ 11፥4
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“በቍጣ ቀን ሀብት አትረባም፤ ጽድቅ ግን ከሞት ታድናለች።”
ምሳሌ 11፥4
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍4❤1
#እራሳችንን_እንመርምር
እስቲ እራሳችንን እንጠይቅ። እግዚአብሔር ስለ እኛ ክፉ አስቦ ያውቃል? በእውነት እርሱ እኛን በማሰቃየት የሚረካ አምላክ ነው? እርሱን የምንፈራ ከሆንን ከወዳጅነቱ ይልቅ ለእኛ ክፉ አሳቢ አድርገን ብንቆጥረው ያዋጣናል?
“ለእነርሱም መልካምን በማድረግ ደስ ይለኛል በእውነትም በፍጹም ልቤና በፍጹም ነፍሴ በዚህች ምድር እተክላቸዋለሁ።”
ኤርምያስ 32፥41
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
እስቲ እራሳችንን እንጠይቅ። እግዚአብሔር ስለ እኛ ክፉ አስቦ ያውቃል? በእውነት እርሱ እኛን በማሰቃየት የሚረካ አምላክ ነው? እርሱን የምንፈራ ከሆንን ከወዳጅነቱ ይልቅ ለእኛ ክፉ አሳቢ አድርገን ብንቆጥረው ያዋጣናል?
“ለእነርሱም መልካምን በማድረግ ደስ ይለኛል በእውነትም በፍጹም ልቤና በፍጹም ነፍሴ በዚህች ምድር እተክላቸዋለሁ።”
ኤርምያስ 32፥41
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤6
' ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“በአንድ አካልም የተጠራችሁለት ደግሞ የክርስቶስ ሰላም በልባችሁ ይግዛ፤ የምታመሰግኑም ሁኑ።”
ቆላስይስ 3፥15
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“በአንድ አካልም የተጠራችሁለት ደግሞ የክርስቶስ ሰላም በልባችሁ ይግዛ፤ የምታመሰግኑም ሁኑ።”
ቆላስይስ 3፥15
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍3❤1
ቅዱሳት መጻሕፍት
የቀጠለ... አራቱ ደስታችንን ሊጠብቁ የሚችሉ አመለካከቶች 3. መንፈሳዊ አሳብ - ፊልጵስዩስ 3 በዚህ ምዕራፍ ውስጥ ጳውሎስ ወደ አሥራ አንድ ጊዜ ያህል «ነገር» የሚለውን ቃል ሲጠቀም ታገኛላችሁ። የአብዛኛዎቹ ሰዎች «አሳባቸው ምድራዊ» (3፡19) ለሆኑ ነገሮች ሲሆን፥ መንፈሳዊ ልብ ያላቸው ክርስቲያኖች ግን የሚጨነቁት ስለ ሰማያዊ ነገሮች መሆኑን ያሳየናል። «እኛ አገራችን በሰማይ ነውና፥ ከዚያም…
የቀጠለ...
አራቱ ደስታችንን ሊጠብቁ የሚችሉ አመለካከቶች
4. የተጠበቀ ልብ - ፊልጵስዩስ 4
በእውነቱ ጭንቀት ስለአጋጣሚዎች፥ ስለሰዎች እንዲሁም ስለነገሮች የተሳሳተ አመለካከት (በአእምሮአችን) ሲጸነስ እና ትክክለኛ ያልሆነ ስሜት (በልባችን) ሲሰርፅ የሚፈጠር ነው። ስለዚህ፥ አንድ አሳብ፥ ማለትም በትሕትና ላይ የተመሠረተ አሳብ፥ እና መንፈሳዊ አሳብ ካለን፥ ለጭንቀት ያን ያህል ክብደት ልንሰጠው አይገባም። የሚያስፈልገን ነገር ቢኖር ጭንቀት ወደውስጣችን እንዳይገባ አእምሮአችንንና ልባችንን የሚጠብቅ መከላከያ ማግኘት ነው። ጳውሎስ ስለተጠበቀ አሳብ ሲያስረዳ
«አእምሮን ሁሉ የሚያልፍ የእግዚአብሔር ሰላም ልባችሁንና አሳባችሁን በክርስቶስ ኢየሱስ ይጠብቃል» (4፡7) ብሏል።
ጠበቀ የሚለው ወታደራዊ ቃል ነው፤ ይኸውም «ምሽግን ከአደጋ ለመከላከል ዘብ መቆምን» የሚያመለክት ነው። (እንደምናስታውሰው ጳውሎስ በታሠረበት ጊዜ ከአንድ ወታደር ጋር በሰንሰለት ተቆራኝቶ ነበር)።
ምዕራፍ 4 አማኝ በክርስቶስ ስላለው መንፈሳዊ ሀብቶች የሚያስረዳ ነው፤ እነርሱም የእግዚአብሔር ሰላም (4፡1-9)፥ የእግዚአብሔር ኃይል (4፡10-13)፥ እና የእግዚአብሔር እርዳታ (4፡14-23) ናቸው። እነዚህ ሁሉ ሀብቶች ካሉን ታዲያ ለምን እንጨነቃለን? የሚጠብቀን የእግዚአብሔር ሰላም (4፡7) እንዲሁም የሚመራን የሰላም አምላክ (4፡9) አለን። የእግዚአብሔር ሰላም ወደ እኛ የሚመጣው ትክክለኛ የሆነ ጸሎት ስንለማመድ (4፡6-7)፥ ትክክለኛ የሆነ አስተሳሰብ ስናራምድ (4፡8)፥ እና ትክክለኛ የሆነ ኑሮን ስንኖር (4፡9) ነው። ይህም በጭንቀት ሁሉ ላይ ድል የሚሰጠን የእግዚአብሔር ምሥጢር ነው።
ምንጭ፦ ዋረን ደብልዩ ዌርዝ ቢ፤ ደስተኛ ሁን፤ የፊልጵስዩስ መልእክት ፤ ገጽ 8-9
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
አራቱ ደስታችንን ሊጠብቁ የሚችሉ አመለካከቶች
4. የተጠበቀ ልብ - ፊልጵስዩስ 4
በእውነቱ ጭንቀት ስለአጋጣሚዎች፥ ስለሰዎች እንዲሁም ስለነገሮች የተሳሳተ አመለካከት (በአእምሮአችን) ሲጸነስ እና ትክክለኛ ያልሆነ ስሜት (በልባችን) ሲሰርፅ የሚፈጠር ነው። ስለዚህ፥ አንድ አሳብ፥ ማለትም በትሕትና ላይ የተመሠረተ አሳብ፥ እና መንፈሳዊ አሳብ ካለን፥ ለጭንቀት ያን ያህል ክብደት ልንሰጠው አይገባም። የሚያስፈልገን ነገር ቢኖር ጭንቀት ወደውስጣችን እንዳይገባ አእምሮአችንንና ልባችንን የሚጠብቅ መከላከያ ማግኘት ነው። ጳውሎስ ስለተጠበቀ አሳብ ሲያስረዳ
«አእምሮን ሁሉ የሚያልፍ የእግዚአብሔር ሰላም ልባችሁንና አሳባችሁን በክርስቶስ ኢየሱስ ይጠብቃል» (4፡7) ብሏል።
ጠበቀ የሚለው ወታደራዊ ቃል ነው፤ ይኸውም «ምሽግን ከአደጋ ለመከላከል ዘብ መቆምን» የሚያመለክት ነው። (እንደምናስታውሰው ጳውሎስ በታሠረበት ጊዜ ከአንድ ወታደር ጋር በሰንሰለት ተቆራኝቶ ነበር)።
ምዕራፍ 4 አማኝ በክርስቶስ ስላለው መንፈሳዊ ሀብቶች የሚያስረዳ ነው፤ እነርሱም የእግዚአብሔር ሰላም (4፡1-9)፥ የእግዚአብሔር ኃይል (4፡10-13)፥ እና የእግዚአብሔር እርዳታ (4፡14-23) ናቸው። እነዚህ ሁሉ ሀብቶች ካሉን ታዲያ ለምን እንጨነቃለን? የሚጠብቀን የእግዚአብሔር ሰላም (4፡7) እንዲሁም የሚመራን የሰላም አምላክ (4፡9) አለን። የእግዚአብሔር ሰላም ወደ እኛ የሚመጣው ትክክለኛ የሆነ ጸሎት ስንለማመድ (4፡6-7)፥ ትክክለኛ የሆነ አስተሳሰብ ስናራምድ (4፡8)፥ እና ትክክለኛ የሆነ ኑሮን ስንኖር (4፡9) ነው። ይህም በጭንቀት ሁሉ ላይ ድል የሚሰጠን የእግዚአብሔር ምሥጢር ነው።
ምንጭ፦ ዋረን ደብልዩ ዌርዝ ቢ፤ ደስተኛ ሁን፤ የፊልጵስዩስ መልእክት ፤ ገጽ 8-9
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍2❤1
' ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“ጌታ እግዚአብሔር ኃይሌ ነው፤ እግሮቼን እንደ ዋላ እግሮች ያደርጋል፤ በከፍታዎችም ላይ ያስሄደኛል።”
ዕንባቆም 3፥19
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“ጌታ እግዚአብሔር ኃይሌ ነው፤ እግሮቼን እንደ ዋላ እግሮች ያደርጋል፤ በከፍታዎችም ላይ ያስሄደኛል።”
ዕንባቆም 3፥19
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤4👍1
finote-1.pdf
1.5 MB
👉ርዕስ፦ ፍኖተ መንግሥት፣
ከመጀመሪያ እስከ መጨረሻ አንድ መስመር አለ!
✍️ጸሐፊ፦ መርዓዊሥላሴ ንጉሤ (መጋቢ)
📑የገጽ ብዛት፦ 466
📆የታተመበት ዓመት፦ 2004 ዓ.ም
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ከመጀመሪያ እስከ መጨረሻ አንድ መስመር አለ!
✍️ጸሐፊ፦ መርዓዊሥላሴ ንጉሤ (መጋቢ)
📑የገጽ ብዛት፦ 466
📆የታተመበት ዓመት፦ 2004 ዓ.ም
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍3
' ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“እስራኤል ደግነትን ጥሎአል፤ ጠላትም ያሳድዱታል።”
ሆሴዕ 8፥3
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“እስራኤል ደግነትን ጥሎአል፤ ጠላትም ያሳድዱታል።”
ሆሴዕ 8፥3
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤2
#የእግዚአብሔር_ቃል_ምን_ይላል?
መዝሙር 119
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁶⁵ አቤቱ፥ እንደ ቃልህ ለባሪያህ መልካም አደረግህ።
⁶⁶ በትእዛዛትህ ታምኛለሁና መልካም ምክርና እውቀትን አስተምረኝ።
⁶⁷ እኔ ሳልጨነቅ ሳትሁ፤ አሁን ግን ቃልህን ጠበቅሁ።
⁶⁸ አቤቱ፥ አንተ ቸር ነህ፥ በቸርነትህም ሥርዓትህን አስተምረኝ።
⁶⁹ የትዕቢተኞች ዓመፅ በላዬ በዛ፤ እኔ ግን በፍጹም ልቤ ትእዛዛትህን እፈልጋለሁ።
⁷⁰ ልባቸው እንደ ወተት ረጋ፤ እኔ ግን በሕግህ ደስ ይለኛል።
⁷¹ ሥርዓትህን እማር ዘንድ ያስጨነቅኸኝ መልካም ሆነልኝ።
⁷² ከአእላፋት ወርቅና ብር ይልቅ የአፍህ ሕግ ይሻለኛል።
⁷³ እጆችህ ሠሩኝ አበጃጁኝም፤ እንዳስተውል አድርገኝ፥ ትእዛዛትህንም እማራለሁ።
⁷⁴ በቃልህ ታምኛለሁና የሚፈሩህ እኔን አይተው ደስ ይላቸዋል።
⁷⁵ አቤቱ፥ ፍርድህ ጽድቅ እንደ ሆነች፥ በእውነትህም እንዳስቸገርኸኝ አወቅሁ።
⁷⁶ ምሕረትህ ለመጽናናቴ ትሁነኝ፥ እንደ ቃልህም ለባሪያህ ይሁነው።
⁷⁷ ሕግህ ተድላዬ ናትና ቸርነትህ ትምጣልኝ፥ በሕይወትም ልኑር።
⁷⁸ ትዕቢተኞች በዓመፅ ጠምመውብኛልና ይፈሩ፤ እኔ ግን በትእዛዝህ እጫወታለሁ።
⁷⁹ የሚፈሩህና ምስክሮችህን የሚያውቁ ወደ እኔ ይመለሱ።
⁸⁰ እንዳላፍር ልቤ በሥርዓትህ የቀና ይሁን።
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
መዝሙር 119
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁶⁵ አቤቱ፥ እንደ ቃልህ ለባሪያህ መልካም አደረግህ።
⁶⁶ በትእዛዛትህ ታምኛለሁና መልካም ምክርና እውቀትን አስተምረኝ።
⁶⁷ እኔ ሳልጨነቅ ሳትሁ፤ አሁን ግን ቃልህን ጠበቅሁ።
⁶⁸ አቤቱ፥ አንተ ቸር ነህ፥ በቸርነትህም ሥርዓትህን አስተምረኝ።
⁶⁹ የትዕቢተኞች ዓመፅ በላዬ በዛ፤ እኔ ግን በፍጹም ልቤ ትእዛዛትህን እፈልጋለሁ።
⁷⁰ ልባቸው እንደ ወተት ረጋ፤ እኔ ግን በሕግህ ደስ ይለኛል።
⁷¹ ሥርዓትህን እማር ዘንድ ያስጨነቅኸኝ መልካም ሆነልኝ።
⁷² ከአእላፋት ወርቅና ብር ይልቅ የአፍህ ሕግ ይሻለኛል።
⁷³ እጆችህ ሠሩኝ አበጃጁኝም፤ እንዳስተውል አድርገኝ፥ ትእዛዛትህንም እማራለሁ።
⁷⁴ በቃልህ ታምኛለሁና የሚፈሩህ እኔን አይተው ደስ ይላቸዋል።
⁷⁵ አቤቱ፥ ፍርድህ ጽድቅ እንደ ሆነች፥ በእውነትህም እንዳስቸገርኸኝ አወቅሁ።
⁷⁶ ምሕረትህ ለመጽናናቴ ትሁነኝ፥ እንደ ቃልህም ለባሪያህ ይሁነው።
⁷⁷ ሕግህ ተድላዬ ናትና ቸርነትህ ትምጣልኝ፥ በሕይወትም ልኑር።
⁷⁸ ትዕቢተኞች በዓመፅ ጠምመውብኛልና ይፈሩ፤ እኔ ግን በትእዛዝህ እጫወታለሁ።
⁷⁹ የሚፈሩህና ምስክሮችህን የሚያውቁ ወደ እኔ ይመለሱ።
⁸⁰ እንዳላፍር ልቤ በሥርዓትህ የቀና ይሁን።
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤4👍1
' ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“ነገር ግን ጥበብ የምትገኘው ወዴት ነው? የማስተዋልስ ስፍራ ወዴት ነው?”
ኢዮብ 28፥12
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“ነገር ግን ጥበብ የምትገኘው ወዴት ነው? የማስተዋልስ ስፍራ ወዴት ነው?”
ኢዮብ 28፥12
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍4❤1
የአማኝ ሕይወት በእድገት መቀጠል ሲገባው ለምን ወደ ኋላ ይላል?
በመንፈሳዊ ሕይወት ውስጥ ከማደግ ይልቅ ወደ ኋላ ማፈግፈግ ብዙ ጊዜ ይስተዋላል። ከእነዚህ ምክንያቶች ውስጥ ዛሬ አንዱን እንመለከታለን።
1. "ተንኰልን የሙጥኝ " ብሎ ሲይዝ
2. "ሊመለስም እንቢ" ሲል
“እንግዲህ ይህ የኢየሩሳሌም ሕዝብ ዘወትር ስለ ምን ወደ ኋላው ይመለሳል? ተንኰልን ይዞአል ሊመለስም እንቢ ብሎአል።”
(ኤርምያስ 8፥5)
“ታዲያ፣ ይህ ሕዝብ ለምን ፊቱን አዙሮ ወደ ኋላ ይሄዳል? ለምንስ ኢየሩሳሌም ዘወትር ወደ ኋላ ትመለሳለች? ተንኰልን የሙጥኝ ብለው ይዘዋል፤ ሊመለሱም ፈቃደኛ አይደሉም።”
ኤርምያስ 8፥5 (አዲሱ መ.ት)
"እንግዲህ ክፋትን ሁሉ ተንኰልንም ሁሉ ግብዝነትንም ቅንዓትንም ሐሜትንም ሁሉ አስወግዳችሁ፥ ጌታ ቸር መሆኑን ቀምሳችሁ እንደ ሆነ፥ ለመዳን በእርሱ እንድታድጉ አሁን እንደ ተወለዱ ሕፃናት ተንኰል የሌለበትን የቃልን ወተት ተመኙ።"
(1ኛ ጴጥሮስ 2፥1-3)
ለመሆኑ "ተንኮል" ማለት ምን ማለት ነው? እስቲ በዚህ ነገር በአሳብ መስጫው ላይ አሳብ ስጡበት፤ ተወያዩበትም።
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
በመንፈሳዊ ሕይወት ውስጥ ከማደግ ይልቅ ወደ ኋላ ማፈግፈግ ብዙ ጊዜ ይስተዋላል። ከእነዚህ ምክንያቶች ውስጥ ዛሬ አንዱን እንመለከታለን።
1. "ተንኰልን የሙጥኝ " ብሎ ሲይዝ
2. "ሊመለስም እንቢ" ሲል
“እንግዲህ ይህ የኢየሩሳሌም ሕዝብ ዘወትር ስለ ምን ወደ ኋላው ይመለሳል? ተንኰልን ይዞአል ሊመለስም እንቢ ብሎአል።”
(ኤርምያስ 8፥5)
“ታዲያ፣ ይህ ሕዝብ ለምን ፊቱን አዙሮ ወደ ኋላ ይሄዳል? ለምንስ ኢየሩሳሌም ዘወትር ወደ ኋላ ትመለሳለች? ተንኰልን የሙጥኝ ብለው ይዘዋል፤ ሊመለሱም ፈቃደኛ አይደሉም።”
ኤርምያስ 8፥5 (አዲሱ መ.ት)
"እንግዲህ ክፋትን ሁሉ ተንኰልንም ሁሉ ግብዝነትንም ቅንዓትንም ሐሜትንም ሁሉ አስወግዳችሁ፥ ጌታ ቸር መሆኑን ቀምሳችሁ እንደ ሆነ፥ ለመዳን በእርሱ እንድታድጉ አሁን እንደ ተወለዱ ሕፃናት ተንኰል የሌለበትን የቃልን ወተት ተመኙ።"
(1ኛ ጴጥሮስ 2፥1-3)
ለመሆኑ "ተንኮል" ማለት ምን ማለት ነው? እስቲ በዚህ ነገር በአሳብ መስጫው ላይ አሳብ ስጡበት፤ ተወያዩበትም።
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍11❤2
' ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“ለራስህ ታላቅን ነገር ትፈልጋለህን? በሥጋ ለባሽ ሁሉ ላይ፥ እነሆ፥ ክፉ ነገርን አመጣለሁና አትፈልገው፥ ይላል እግዚአብሔር፤ ነገር ግን በሄድህበት ስፍራ ሁሉ ነፍስህን እንደ ምርኮ አድርጌ እሰጥሃለሁ።”
ኤርምያስ 45፥5
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“ለራስህ ታላቅን ነገር ትፈልጋለህን? በሥጋ ለባሽ ሁሉ ላይ፥ እነሆ፥ ክፉ ነገርን አመጣለሁና አትፈልገው፥ ይላል እግዚአብሔር፤ ነገር ግን በሄድህበት ስፍራ ሁሉ ነፍስህን እንደ ምርኮ አድርጌ እሰጥሃለሁ።”
ኤርምያስ 45፥5
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍4❤1
#ከተማ_ወይም_ቦታ_በቅዱሳት_መጻሕፍት
#ናዝሬት
ናዝሬት፤ ከገሊላ ባሕር በስተምዕራብ 25 ኪ.ሜ. ርቆ በዛብሎን ነገድ ድርሻ ውስጥ በተራራማ አገር ላይ የተመሠረተ ከተማ ናት። ናዝሬት በብሉይ ኪዳን አልተጠቀሰም፤ በአዲስ ኪዳን ዘመንም ቦታው ወደ አገሩ ጠረፍ ስለሆነ ዝቅተኛ ግምት ይሰጠው ነበር፤ ዮሐ. 1፥47። ናዝሬት የዮሴፍና የማርያም መኖሪያ ከተማ ነበረ። ኢየሱስ በዚህ ተፀነሰ፤ በኋላም አደገበት፤ ሉቃ. 1፥26:27፤ 2፥39:40:51። ኢየሱስ የማስተማር ሥራውን ከጀመረ በኋላ አንድ ጊዜ ወደ ናዝሬት መጣ፤ ሕዝቡ ግን አልተቀበሉትም፤ ሉቃ. 4፥16-30። ዛሬ 30 ሺህ ያህል ሰዎች በናዝሬት ይኖራሉ።
ምንጭ፦የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት፣ ገጽ 140-141
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
#ናዝሬት
ናዝሬት፤ ከገሊላ ባሕር በስተምዕራብ 25 ኪ.ሜ. ርቆ በዛብሎን ነገድ ድርሻ ውስጥ በተራራማ አገር ላይ የተመሠረተ ከተማ ናት። ናዝሬት በብሉይ ኪዳን አልተጠቀሰም፤ በአዲስ ኪዳን ዘመንም ቦታው ወደ አገሩ ጠረፍ ስለሆነ ዝቅተኛ ግምት ይሰጠው ነበር፤ ዮሐ. 1፥47። ናዝሬት የዮሴፍና የማርያም መኖሪያ ከተማ ነበረ። ኢየሱስ በዚህ ተፀነሰ፤ በኋላም አደገበት፤ ሉቃ. 1፥26:27፤ 2፥39:40:51። ኢየሱስ የማስተማር ሥራውን ከጀመረ በኋላ አንድ ጊዜ ወደ ናዝሬት መጣ፤ ሕዝቡ ግን አልተቀበሉትም፤ ሉቃ. 4፥16-30። ዛሬ 30 ሺህ ያህል ሰዎች በናዝሬት ይኖራሉ።
ምንጭ፦የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት፣ ገጽ 140-141
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤5👍4👎1