#እራሳችንን_እንመርምር
በምን ወይም በማን እንታመን? እንዴታ በእግዚአብሔር እንጂ! ይህን እውነት አምኖ ለመተግበር ቀላል ይመስላል ግን ከባድ እንደሆነ ሁላችንም እናውቀዋለን። ግን በዚህ እውነት ጸንቶ ከመኖር ወጪ ምን ምርጫ አለ? የትኛዎቹስ ልንመካባቸው የከጀልናቸው አዘለቁን?
“ወደ አንቺ የሰበሰብሻቸው በጮኽሽ ጊዜ ይታደጉሽ፤ ንፋስ ግን ይወስዳቸዋል ሽውሽውታም ሁሉን ያስወግዳቸዋል። በእኔ የታመነ ግን ምድሪቱን ይገዛል፥ የተቀደሰውንም ተራራዬን ይወርሳል።”
ኢሳይያስ 57፥13
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
በምን ወይም በማን እንታመን? እንዴታ በእግዚአብሔር እንጂ! ይህን እውነት አምኖ ለመተግበር ቀላል ይመስላል ግን ከባድ እንደሆነ ሁላችንም እናውቀዋለን። ግን በዚህ እውነት ጸንቶ ከመኖር ወጪ ምን ምርጫ አለ? የትኛዎቹስ ልንመካባቸው የከጀልናቸው አዘለቁን?
“ወደ አንቺ የሰበሰብሻቸው በጮኽሽ ጊዜ ይታደጉሽ፤ ንፋስ ግን ይወስዳቸዋል ሽውሽውታም ሁሉን ያስወግዳቸዋል። በእኔ የታመነ ግን ምድሪቱን ይገዛል፥ የተቀደሰውንም ተራራዬን ይወርሳል።”
ኢሳይያስ 57፥13
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍6❤1
' ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“አቤቱ፥ አንተ መብራቴ ነህና፤ እግዚአብሔርም ጨለማዬን ያበራል።”
2ኛ ሳሙኤል 22፥29
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“አቤቱ፥ አንተ መብራቴ ነህና፤ እግዚአብሔርም ጨለማዬን ያበራል።”
2ኛ ሳሙኤል 22፥29
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍5❤2
ከብሉይ ኪዳን ነቢያት መካከል በነቢዩ ኢሳይያስ ዘመን እንደነበረ የሚነገርለት፣ የትንቢቶቹ ወይም የመልዕክቱ ዋና ትኩረት ደግሞ ከላይ ያሉ መሪዎችን እና አስተዳዳሪዎችን የሆነው የቱ ነው?
Anonymous Quiz
21%
ሀ. ሚልክያስ
28%
ለ. ሆሴዕ
23%
ሐ. ኢዩኤል
23%
መ. ሚክያስ
6%
ሠ. ናሆም
❤6👍2
' ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“ዓይናቸውም ተከፈተ፥ አወቁትም፤ እርሱም ከእነርሱ ተሰወረ።”
ሉቃስ 24፥31
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“ዓይናቸውም ተከፈተ፥ አወቁትም፤ እርሱም ከእነርሱ ተሰወረ።”
ሉቃስ 24፥31
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤9
#ከተማ_ወይም_ቦታ_በቅዱሳት_መጻሕፍት
#ራማ፤ ከፍታ ማለት ነው። አንዳንድ ከተማዎች ራማ ተብለዋል፤ ከእነርሱም የታወቀው በገባዖንና በጊብዓ አጠገብ የነበረ ከተማ ነው፤ ኢያሱ 18፥25፤ መሳ. 19፥13። ይህ የዲቦራ አገር ነበር፤ መሳ. 4፥5። ኤርምያስ ታስሮ ከኢየሩሳሌም ከተወሰደ በኋላ ከራማ ተለቀቀ። ግን ይህ ራማ የትኛው እንደሆነ አልታወቀም፤ ኤር. 40፥1። ራሔል በራማ አጠገብ ተቀበረች፤ ስለዚህም የሐዘን ቦታ ሆነ፤ ኤር. 31፥15፤ ማቴ. 2፥18።
ምንጭ፦ የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት፤ ገጽ 67
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
#ራማ፤ ከፍታ ማለት ነው። አንዳንድ ከተማዎች ራማ ተብለዋል፤ ከእነርሱም የታወቀው በገባዖንና በጊብዓ አጠገብ የነበረ ከተማ ነው፤ ኢያሱ 18፥25፤ መሳ. 19፥13። ይህ የዲቦራ አገር ነበር፤ መሳ. 4፥5። ኤርምያስ ታስሮ ከኢየሩሳሌም ከተወሰደ በኋላ ከራማ ተለቀቀ። ግን ይህ ራማ የትኛው እንደሆነ አልታወቀም፤ ኤር. 40፥1። ራሔል በራማ አጠገብ ተቀበረች፤ ስለዚህም የሐዘን ቦታ ሆነ፤ ኤር. 31፥15፤ ማቴ. 2፥18።
ምንጭ፦ የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት፤ ገጽ 67
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍1
' ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“አሁን ግን ወንድሞች ከሚባሉት አንዱ ሴሰኛ ወይም ገንዘብን የሚመኝ ወይም ጣዖትን የሚያመልክ ወይም ተሳዳቢ ወይም ሰካር ወይም ነጣቂ ቢሆን ከእርሱ ጋር እንዳትተባበሩ እጽፍላችኋለሁ፤ እንደነዚህ ካለው ጋር መብል እንኳን አትብሉ።”
1ኛ ቆሮንቶስ 5፥11
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“አሁን ግን ወንድሞች ከሚባሉት አንዱ ሴሰኛ ወይም ገንዘብን የሚመኝ ወይም ጣዖትን የሚያመልክ ወይም ተሳዳቢ ወይም ሰካር ወይም ነጣቂ ቢሆን ከእርሱ ጋር እንዳትተባበሩ እጽፍላችኋለሁ፤ እንደነዚህ ካለው ጋር መብል እንኳን አትብሉ።”
1ኛ ቆሮንቶስ 5፥11
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍7❤3
' ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“ለኵነኔ አልልም፤ በአንድነት ለመሞትና በአንድነት ለመኖር በልባችን እንዳላችሁ አስቀድሜ ብዬአለሁና።”
2ኛ ቆሮ 7፥3
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“ለኵነኔ አልልም፤ በአንድነት ለመሞትና በአንድነት ለመኖር በልባችን እንዳላችሁ አስቀድሜ ብዬአለሁና።”
2ኛ ቆሮ 7፥3
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍3❤1😁1
' ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“በውኑ እኔን አትፈሩምን? ከፊቴስ አትደነግጡምን? ይላል እግዚአብሔር፤ እንዳያልፍ አሸዋን በዘላለም ትእዛዝ ለባሕር ዳርቻ አድርጌአለሁ፤ ሞገዱም ቢናወጥ አያሸንፍም፥ ቢጮኽም አያልፍበትም።”
ኤርምያስ 5፥22
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“በውኑ እኔን አትፈሩምን? ከፊቴስ አትደነግጡምን? ይላል እግዚአብሔር፤ እንዳያልፍ አሸዋን በዘላለም ትእዛዝ ለባሕር ዳርቻ አድርጌአለሁ፤ ሞገዱም ቢናወጥ አያሸንፍም፥ ቢጮኽም አያልፍበትም።”
ኤርምያስ 5፥22
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍6❤1
ከትንሳኤ ማግስት፡ መጽሐፍ ቅዱሳዊ መንፈሳዊነት
ቤተክርስቲያን ስላለችበት ሁኔታ እንዲሁም በውስጧ እየሆኑ ስለሉት ስብራቶችና ግራ የሚያጋቡ ነገሮች ስታስቡ “ኧረ መንፈሳዊነት ምን ማለት ነው?” የሚል ጥያቄ አይፈጠርባችሁም? ክርስቶስ የሞተውና የተነሳው “ለዚህ ነው?” አያስብላችሁም? ወይም ይህንን ጥያቄ እንደገና አንስተን እንደገና መመለስ እንዳለብን የዘነጋነው የቤት ሥራ አይመስላችሁም? ስለ ችግሩ እየተወያየንና አስተያየቶቻችንም እየቸርን የቤት-ሥራችን ግን ተቆለለ አይደል? እኔ ተቆልሎብኛል። ልክ የትዳር ሕይወት ከሠርግ ማግስት እንዲጀምር መጽሐፍ ቅዱሳዊውም “እውነተኛ ሕይወት” [ያ ጳውሎስ ለጢሞቴዎስ እየደጋገመ እንደ አዝማች ያሳሰበው ጉዳይ] እንዲሁ ከትንሳኤ ማግስት ይመስለኛል። መቼም ሞቱንና ትንሳኤውን አክብረን ስናበቃ ራሳችንን ማሳሰብ ያለብን ብዙ ነገሮች እንዳሉን ይሰማኛል። ከእነዚህ አንዱና ዋነኛ ግን “መንፈሳዊነት ምን ማለት ነው?” የሚለው መሆን አለበት። ይህ ወቅት ሞቱንና ትንሳኤውን ይዘን ሳናሰልስ ወደ ሥራ የምንሔድበት እንጂ፤ ወደ ሌላ ርእሰ-ጉዳይ የምንሸጋገርበት እንዳልሆነ ሁላችንም እናውቃለን። ይህ የሰሞኑ የመስቀልና የትንሳኤ ጉዳይ፣ ሌሎች አንገባጋቢ ጉዳዮቻችንን ወደ ጎን የሚያደርግ ሳይሆን፤ በእያንዳንዱ ጉዳዮቻችን ውስጥ ግን እንደ ጅማት ሊዘረጋ፤ እንደ ደም ስር ሊቀጣጠል፤ እንደ ደም በመላ የክርስትና ሕይወታችንና የቤተክርስቲያን ጉዳዮቻችንን ሊሰራጭ ይገባል። ጭንቅላት የሰውነት ብልቶች ተግባሮቻቸውን እንዲያከናውኑ ሁሉን እንደሚቆጣጠር፣ ይህ የሰሞኑ እውነታ የተግዳሮታችን ሁሉ ዓውድ ይሆን ዘንድ ልባዊ ጸሎቴ ነው። ስለዚህ መንፈሳዊ ሕይወት የመስቀልና የትንሳኤውን እውነታ የሚያንጸባርቅ መሆን አለበት። እንዲህ ከሆነ መንፈሳዊ ህይወት መስቀሉንና ክርስቶስን እንዲሁም በመስቀሉ ሥራ ላይ የተሳተፉት ስሉስ መለኮታዊ አካላትን የሚገልጥ መሆን አለበት። ትዝ አይላችሁም በቆሮንቶስ የነበረው የጸጋ-ሥጦታን አጠቃቀም ያለማወቅ ችግር? ምክኒያቱ? ስሉሱን አምላክ ያለማወቅ ችግር እንደሆነ ጽፎልናል “ስለ መንፈሳዊ ነገርም፥ ወንድሞች ሆይ፥ ታውቁ ዘንድ እወዳለሁ…መንፈስ አንድ ነው…ጌታም አንድ ነው…እግዚኢብሔር [አብ] አንድ ነው” (1 ቆሮ 12፥1-6). ” መንፈሳዊ ስጦታ የእግዚአብሔርን ክብርና ማንነት የሚገልጥ ነው እንጂ፣ ይለናል ጳውሎስ፤ የራሳችን እውነታ የምገልጥበት መንፈሳዊ-ልዕልና አይደለም። ይህም ከመንፈሳዊ ህይወት ጀርባ ጥልቅ ነገረ መለኮታዊ እውነታ አለ ማለት ነው፡፡ እናም አሁን የሰነበትንበት መንፈስ (የሰሞኑ መስቀል ተኮር ስብከት፤ መዝሙር፤ ጸሎት ምሥጋና፤ ይህ በትንሳኤው ሀይል ላይ የተደገፈ የሰሞኑ መታመናችን፤ ይህ ክርስቶስ ራሱን ለብዙዎች እስኪሰጥ ድረስ የወደደበት መውደድ ላይ የተመሰረተው ፍቅራችን) እንዴት ሳያቋርጥ ይቀጥል የሚለው ጥያቄ መታሰብ ያለበት ነው። መቼም ብዙ የሚያሳስበኝና የምጸልይበት ጉዳይ የዚህ የመንፈሳዊነት ጉዳይ ነው። “መንፈሳዊነት ምን ማለት ነው?” በየግል ሕይወታችን ውስጥ ለሚንጸባረቀው እንዲሁም በህብረት በየአብያተ-ክርስቲያናት በየእሑዱ ለምናካሒደው ስብሰባ ምን ፋይዳ አለው? ይህ ጥያቄ በአንድ ወገን በጣም ቀላል የሆነ፣ በክርስቶስ አምኖ የዳነ ሁሉ የቀመሰው እውነታ ነው። ነገር ግን በዚያው ልክ ጥልቅም ጥያቄ ነው። መንፈሳዊነት ትናንት ወደ መንግሥቱ የተጨመረ ሕጻን ሊዋኝበት የሚችል ገንዳ ነገር ግን ደግሞ ታላላቅ መርከቦችንም የሚያስተናግድ ባሕር ነው። በሕይወታችን የተለማመድነውን በቃላት ማስቀመጥ አንዳንዴ ትልቅ ጥበብን ይጠይቃል። ለምሳሌ ያህል የገላትያ ቤተክርስቲያን “ይህን ብቻ ከእናንተ እንድማር እወዳለሁ፤ [እንዴት] መንፈስን ተቀበላችሁን? (ገላ 3:2)” ሲል እነዚህ ሰዎች ጥልቅ የወንጌልን እውነት ሳይረዱ እንኳ ሕያው የሆነው መንፈስ ትልቅ መንፈሳዊ ሐይልን እንዲለማመዱ አብቅቷቸዋል። እዚህ ጋር ማብቃት ግን ትልቅ አደጋ ነው። ብስለት ባለው በጥበብ ቃል ይህንን ልምምድ መጽሐፍ ቅዱሳዊና ነገረ-መለኮታዊ በሆነ መንገድ መግለጥ እስካልቻልን ሲወሰድብንም፤ ከዚያም ስተን ስንወጣም (በሌላ መንፈስ) አናውቅም። ስለዚህ “መንፈሳዊነት ምንድር ነው?” የሚለውን አስፍተንና አጥልቀን እንደገና ማሰብ ያለብን ጉዳይ ይመስለኛል።
ይቀጥላል. . .
ምንጭ፦ semayawithought.org
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ቤተክርስቲያን ስላለችበት ሁኔታ እንዲሁም በውስጧ እየሆኑ ስለሉት ስብራቶችና ግራ የሚያጋቡ ነገሮች ስታስቡ “ኧረ መንፈሳዊነት ምን ማለት ነው?” የሚል ጥያቄ አይፈጠርባችሁም? ክርስቶስ የሞተውና የተነሳው “ለዚህ ነው?” አያስብላችሁም? ወይም ይህንን ጥያቄ እንደገና አንስተን እንደገና መመለስ እንዳለብን የዘነጋነው የቤት ሥራ አይመስላችሁም? ስለ ችግሩ እየተወያየንና አስተያየቶቻችንም እየቸርን የቤት-ሥራችን ግን ተቆለለ አይደል? እኔ ተቆልሎብኛል። ልክ የትዳር ሕይወት ከሠርግ ማግስት እንዲጀምር መጽሐፍ ቅዱሳዊውም “እውነተኛ ሕይወት” [ያ ጳውሎስ ለጢሞቴዎስ እየደጋገመ እንደ አዝማች ያሳሰበው ጉዳይ] እንዲሁ ከትንሳኤ ማግስት ይመስለኛል። መቼም ሞቱንና ትንሳኤውን አክብረን ስናበቃ ራሳችንን ማሳሰብ ያለብን ብዙ ነገሮች እንዳሉን ይሰማኛል። ከእነዚህ አንዱና ዋነኛ ግን “መንፈሳዊነት ምን ማለት ነው?” የሚለው መሆን አለበት። ይህ ወቅት ሞቱንና ትንሳኤውን ይዘን ሳናሰልስ ወደ ሥራ የምንሔድበት እንጂ፤ ወደ ሌላ ርእሰ-ጉዳይ የምንሸጋገርበት እንዳልሆነ ሁላችንም እናውቃለን። ይህ የሰሞኑ የመስቀልና የትንሳኤ ጉዳይ፣ ሌሎች አንገባጋቢ ጉዳዮቻችንን ወደ ጎን የሚያደርግ ሳይሆን፤ በእያንዳንዱ ጉዳዮቻችን ውስጥ ግን እንደ ጅማት ሊዘረጋ፤ እንደ ደም ስር ሊቀጣጠል፤ እንደ ደም በመላ የክርስትና ሕይወታችንና የቤተክርስቲያን ጉዳዮቻችንን ሊሰራጭ ይገባል። ጭንቅላት የሰውነት ብልቶች ተግባሮቻቸውን እንዲያከናውኑ ሁሉን እንደሚቆጣጠር፣ ይህ የሰሞኑ እውነታ የተግዳሮታችን ሁሉ ዓውድ ይሆን ዘንድ ልባዊ ጸሎቴ ነው። ስለዚህ መንፈሳዊ ሕይወት የመስቀልና የትንሳኤውን እውነታ የሚያንጸባርቅ መሆን አለበት። እንዲህ ከሆነ መንፈሳዊ ህይወት መስቀሉንና ክርስቶስን እንዲሁም በመስቀሉ ሥራ ላይ የተሳተፉት ስሉስ መለኮታዊ አካላትን የሚገልጥ መሆን አለበት። ትዝ አይላችሁም በቆሮንቶስ የነበረው የጸጋ-ሥጦታን አጠቃቀም ያለማወቅ ችግር? ምክኒያቱ? ስሉሱን አምላክ ያለማወቅ ችግር እንደሆነ ጽፎልናል “ስለ መንፈሳዊ ነገርም፥ ወንድሞች ሆይ፥ ታውቁ ዘንድ እወዳለሁ…መንፈስ አንድ ነው…ጌታም አንድ ነው…እግዚኢብሔር [አብ] አንድ ነው” (1 ቆሮ 12፥1-6). ” መንፈሳዊ ስጦታ የእግዚአብሔርን ክብርና ማንነት የሚገልጥ ነው እንጂ፣ ይለናል ጳውሎስ፤ የራሳችን እውነታ የምገልጥበት መንፈሳዊ-ልዕልና አይደለም። ይህም ከመንፈሳዊ ህይወት ጀርባ ጥልቅ ነገረ መለኮታዊ እውነታ አለ ማለት ነው፡፡ እናም አሁን የሰነበትንበት መንፈስ (የሰሞኑ መስቀል ተኮር ስብከት፤ መዝሙር፤ ጸሎት ምሥጋና፤ ይህ በትንሳኤው ሀይል ላይ የተደገፈ የሰሞኑ መታመናችን፤ ይህ ክርስቶስ ራሱን ለብዙዎች እስኪሰጥ ድረስ የወደደበት መውደድ ላይ የተመሰረተው ፍቅራችን) እንዴት ሳያቋርጥ ይቀጥል የሚለው ጥያቄ መታሰብ ያለበት ነው። መቼም ብዙ የሚያሳስበኝና የምጸልይበት ጉዳይ የዚህ የመንፈሳዊነት ጉዳይ ነው። “መንፈሳዊነት ምን ማለት ነው?” በየግል ሕይወታችን ውስጥ ለሚንጸባረቀው እንዲሁም በህብረት በየአብያተ-ክርስቲያናት በየእሑዱ ለምናካሒደው ስብሰባ ምን ፋይዳ አለው? ይህ ጥያቄ በአንድ ወገን በጣም ቀላል የሆነ፣ በክርስቶስ አምኖ የዳነ ሁሉ የቀመሰው እውነታ ነው። ነገር ግን በዚያው ልክ ጥልቅም ጥያቄ ነው። መንፈሳዊነት ትናንት ወደ መንግሥቱ የተጨመረ ሕጻን ሊዋኝበት የሚችል ገንዳ ነገር ግን ደግሞ ታላላቅ መርከቦችንም የሚያስተናግድ ባሕር ነው። በሕይወታችን የተለማመድነውን በቃላት ማስቀመጥ አንዳንዴ ትልቅ ጥበብን ይጠይቃል። ለምሳሌ ያህል የገላትያ ቤተክርስቲያን “ይህን ብቻ ከእናንተ እንድማር እወዳለሁ፤ [እንዴት] መንፈስን ተቀበላችሁን? (ገላ 3:2)” ሲል እነዚህ ሰዎች ጥልቅ የወንጌልን እውነት ሳይረዱ እንኳ ሕያው የሆነው መንፈስ ትልቅ መንፈሳዊ ሐይልን እንዲለማመዱ አብቅቷቸዋል። እዚህ ጋር ማብቃት ግን ትልቅ አደጋ ነው። ብስለት ባለው በጥበብ ቃል ይህንን ልምምድ መጽሐፍ ቅዱሳዊና ነገረ-መለኮታዊ በሆነ መንገድ መግለጥ እስካልቻልን ሲወሰድብንም፤ ከዚያም ስተን ስንወጣም (በሌላ መንፈስ) አናውቅም። ስለዚህ “መንፈሳዊነት ምንድር ነው?” የሚለውን አስፍተንና አጥልቀን እንደገና ማሰብ ያለብን ጉዳይ ይመስለኛል።
ይቀጥላል. . .
ምንጭ፦ semayawithought.org
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍8❤4
' ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“ስለዚህ እስራኤል ብቻውን በሰላም ይኖራል፤ የሰማያት ጠል በሚወርድበት፣ እህልና የወይን ጠጅ ባለበት ምድር፣ የያዕቆብ ምንጭ የሚነካው የለም።”
ዘዳግም 33፥28 (አዲሱ መ.ት)
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“ስለዚህ እስራኤል ብቻውን በሰላም ይኖራል፤ የሰማያት ጠል በሚወርድበት፣ እህልና የወይን ጠጅ ባለበት ምድር፣ የያዕቆብ ምንጭ የሚነካው የለም።”
ዘዳግም 33፥28 (አዲሱ መ.ት)
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍5❤2
“ለሞት እንዳልተኛ አይኖቼን አብራ”
አለመታደስ አንድም መደምሰስ ነው። ድምሳሴው፣ በሰላ ምሳር ዛፍ ተቆርጦ ሲገነደስ አይነት የአፍታ መዓት ባይመስልም፣ ክፉ ደዌ ውስጥ ውስጡን እየበላው የሰራ አካላቱን ያሟሰሰው መጻጉዕ ተስለምልሞ ፀጥ እንደሚለው ዓይነት በለሆሳስ ነው።
ሰው ብቻውን የተተወ እንደሆነ ግስገሳው ወደ ውድመት ነው፤ ጥረቱ ሁሉ ይሟጠጣል፣ ማንነቱ ይሟጠጣል፣ አፈር አፈር ይሸተዋል። ራሱን በራሱ ማዳን የማይችል የሕይወት ውሃ ፈላጊ፣ የደረቅ መሬት እንቡጥ ነው። የመኖርና የመስራት ሰርቶም ውጤት የማምጣት አቅሙ ሕያው እግዚአብሄር ብቻ ነው። የሁልጊዜ ተደጋፊነታችን ምስጢሩም ይኸው ነው። እኛ ዘንድ ሕይወት አይመነጭም፣ እርሱ ዘንድ ግን ሕይወት አይቋረጥም።
“ማንም የተጠማ ቢኖር ወደ እኔ ይምጣና ይጠጣ፤ በእኔ የሚያምን፣ መጽሐፍ እንዳለ የሕይወት ውሃ ምንጭ ከውስጡ ይፈልቃል።” ያለው፣ “በእርሱ ሕይወት ነበረች” የተባለለት ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።
ለመሞት ብንፈልግ ይህን ያህል ብዙ መራቀቅ አይጠይቀንም፤ ሕይወት አለምላሚዎቹን ዋና ዋና ነገሮች፣ አየር፣ ውሃና ምግብ ላይ የምናሳየውን ያላሰለሰ ትጋት መቀነስና ማቋረጥ ብቻ ነው። በመንፈሳዊው አለምም ቢሆን ጉልበት የሚሻው ነገር ሕያውነት ነው። ለዚህ ነው ከሕያው አምላክ ጋር የሚደረገው ግንኙነት የክት ሳይሆን የወትሮ መሆን ያለበት። እየታደስን፣ እየለመለምን፣ አንገታችን ቀና የሚል ፍጡራን ነን። በተፈጥሮ አካሄድ ሲርበን ጉልበታችን እንደሚጥመለመል፣ ሲጠማን ምላሳችን ከትናጋችን እንደሚጣበቅ፣ ስንታፈን አየር ፍለጋ እንደምንወራጭ ሁሉ የውስጣዊ ሕይወት ተሃድሶ እንደሚያሻን ለማወቅም በቂ ምልክቶች አሉ።
ከብዙ በጥቂቱ እነሆ፡ ጸሎት፣ አምልኮና አገልግሎት አውቶማቲክ ይሆናል፤ በልቦና ታስቦ በውስጣዊ ጉጉት ተፈልጎ እያወቁ የሚያደርጉት ሳይሆን ቁልፉ ሲነካ እንደሚሽከረከር የግዱን በዘልማዳዊ ህግ ይከናወናል፤ ስለዚህም ይታክታል ፍችውም ይደበዝዛል። የባሰም እንደሆነ ከናካቴው ይቀራል።
መኖር ማለት የየዕለቱን ጉሮሮ የመድፈን ተግባር ለማከናወን የሚደረግ አድካሚ አዙሪት ብቻ ይሆናል። ይኸው የኑሮ ገበያ ቱማታና የስጋ ፍላጎት ከበሮ ድምድምታ በእውቀትም በደመነፍስም የምንከተለው ዜማ ምት ይሆናል። “አዳሜው ሁሉ የሚሮጥለት እንዲያውም ሌላ መሮጫ ምክንያት ባይኖር ነው።”
በክፉና በደግ፣ በንጹህና በርኩስ፣ በጥበብና በጅልነት፣ በእግዚአብሄር መልአክና በጋኔን፣ በእውነትና በሃሰት መሀከል ያለው የልዩነት መስመር እየወየበ ከአንዱ ወደ ሌላው ዘው እያሉ መመለስ እንዲያም ድንበሩን የሽርሽር መስክ ማድረግ እየተለመደ ይመጣል።
“ለካ ልቤን ንፁህ ያደረኩት በከንቱ ነው፤ እጄንም በየዋህነት የታጠብኩት በከንቱ ኖሮአል!” የሚል ውስጣዊ ማልጎምጎም እየበረታ ይመጣል።
ከሰዎች ጋር በተለይ ደግሞ ቅርብ ከሆኑት ወንድሞቻችን እህቶቻችን ጋር ያለን ፍቅራዊ ትኩሳት እየበረደ ይመጣል። ቢኖሩም ባይኖሩም አብረን ብንሆንም ባንሆንም ደንታ ቢስ እየሆንን ስንቀጥል አልፎ አልፎ እንዲያውም አጠገባችን ባይሆኑ እንመርጣለን። ክርስቲያናዊ ህብረት ይጎፈንነናል፤ “እስቲ ተውኝ” የስልቹነታችን ዜማ ይሆናል።
በምንኖርበት አካባቢ ከአፈር ከቅጠሉ ጋር ተዋህደን ቀለማችን ሳይለይ ብንረሳ እንመርጣለን። ለውጥ የማምጣት ፍላጎታችን ይነቅዛል፤ የማይለማ የማይሰማ ዱልዱም መሆን ጣጣ የሌለበት ሕይወት ይመስለናል።
በአፋችን “እሰይ በሰማይ ቤት አለኝ” እያልን እየዘመርን በልባችን “እስቲ እዚህ ያለውን ቤት ባሳመረልኝ” እንላለን። ያኛው ሩቅ የማይደረስበት ምናልባት ስለርሱ ማሰብ ጅል የሚያድርግ እንደሆነ የሚቆጠር፣ ተጨባጩን ቁሳዊ ዓለምን ግን በትኩስ ስግብግብነት የሚያፈቅር አውሬ ልብ ይረባብናል።
ተሐድሶ ማለት ከዘልማድ እስር ቤት፣ ከሞት እስራት በመንፈስ ቅዱስ ሃይል ተመንጥቆ መውጣት ነው፤ ሰባት ጊዜ ከተነጠረ ብር ይልቅ በጠራው በእግዚአብሄር ቃል እንጀራ መበርታት ነው። በእግዚአብሄር ደስታና እርካታ ማግኘት ነው፤ በወገኖች ፍቅር መለምለም ነው፤ በፅድቅ ሕይወት እርምጃ የሚገኝ አንበሳዊ ድፍረት ነው፤ በተልዕኮ እርግጥኝነት ምክንያት የሚደረግ ግሥገሳ ነው። ተሐድሶ የቦዘ ዓይን ፍንትው የሚልበት፣ ከሁለንታለም ፈጣሪ ጋር ፍቅር የሚያገረሽበት፣ እንቅስቃሴ ሁሉ ትርጉም የሚያገኝበት ደማቅ ኑሮ ነው። የኢየሱስ ክርስቶስ ወዳጅም ወታደርም የመሆን ብቃት ነው።
ይህ ሁሉ እንዴት ሊሆን ይችላል?
ከሁሉ በፊትና በላይ ልዑል እግዚአብሄር አዳሽ አምላክ ነው። በፈጣሪነቱ የሚታወቀው ይህ አምላክ፣ በአዳሽነቱም ወደር የለውም። የደረቁ አጥንቶችን ተንቀሳቃሽ ሠራዊት ለማድረግ አራት ነፋሳት የሚጠራ፣ መቃብር ከፋች ብርቱ ጌታ ነው። ያሁን ዘመን ዋናው ስራው ሙታንን መቀስቀስ ነው።
በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል የግንኙነት እድሳት፣ በቅዱስ መንፈሱ በኩል የንጽህናና የሀይል እድሳት እያደረገ ነው።
መንገዱ የተወላከፈ እንግድግድ የሰው ልጅ የሞት ሽረቱን መንከላወስ ትቶ ለምርመራ መቆም አለበት።
“እንግዲህ ከወዴት እንደወደክ አስብ፣ ንስሀም ግባ፣ የቀደመውንም ስራህን አድርግ” የተባለው በብዙ መስመር ብርቱ የነበረው ፍቅሩ ግን ያረጀበት የቤ/ክርስቲያን መሪና ህዝቡ ናቸው።
እስኪ ነገሮችን ላይ ላይ የመነካካት ግልብነታችንን ትተን ስለሕይወታችን አምርረን እናስብ፤ “አስብ” ተብለናላ! እስኪ ጎምዛዛውን ፍሬ ከአፋችን እንትፋው፣ መንፈሳዊ ጭካኔ እንልመድ። “ንስሀ ግባ” ማለት ሌላ ምንድን ነው? እስኪ ደግሞ በመፅሀፉም በልምድም የምናውቀውን ተገቢ ስራ እንደገና እንቀጥል፤ “የቀደመውን ስራህን አድርግ” ማለቱ ቋሚ የኑሮ መልክ ያለ መሆኑን ያመለክታል።
በፍቅረ እግዚአብሄር በፍቅረ ሰብዕ እንታደስ
በእውነት ትምህርት በንፁህ ሃይማኖት እንታደስ
በሰላም ናፍቆት በእርቅ አስተናጋጅነት እንታደስ
በቅዱስ ኑሮ በቅዱስ ሃሳብ እንታደስ
መንፈስ ቅዱስ ለእኔና ለወገኖቼ አዲስ ነፋስ ላክልን፣ ሕያውነት ወደ አጥንቶቻችን ውስጥ ይዝለቅ፣ የምድሪቱም ገጽ ይፍካ።
ንጉሤ ቡልቻ
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
አለመታደስ አንድም መደምሰስ ነው። ድምሳሴው፣ በሰላ ምሳር ዛፍ ተቆርጦ ሲገነደስ አይነት የአፍታ መዓት ባይመስልም፣ ክፉ ደዌ ውስጥ ውስጡን እየበላው የሰራ አካላቱን ያሟሰሰው መጻጉዕ ተስለምልሞ ፀጥ እንደሚለው ዓይነት በለሆሳስ ነው።
ሰው ብቻውን የተተወ እንደሆነ ግስገሳው ወደ ውድመት ነው፤ ጥረቱ ሁሉ ይሟጠጣል፣ ማንነቱ ይሟጠጣል፣ አፈር አፈር ይሸተዋል። ራሱን በራሱ ማዳን የማይችል የሕይወት ውሃ ፈላጊ፣ የደረቅ መሬት እንቡጥ ነው። የመኖርና የመስራት ሰርቶም ውጤት የማምጣት አቅሙ ሕያው እግዚአብሄር ብቻ ነው። የሁልጊዜ ተደጋፊነታችን ምስጢሩም ይኸው ነው። እኛ ዘንድ ሕይወት አይመነጭም፣ እርሱ ዘንድ ግን ሕይወት አይቋረጥም።
“ማንም የተጠማ ቢኖር ወደ እኔ ይምጣና ይጠጣ፤ በእኔ የሚያምን፣ መጽሐፍ እንዳለ የሕይወት ውሃ ምንጭ ከውስጡ ይፈልቃል።” ያለው፣ “በእርሱ ሕይወት ነበረች” የተባለለት ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።
ለመሞት ብንፈልግ ይህን ያህል ብዙ መራቀቅ አይጠይቀንም፤ ሕይወት አለምላሚዎቹን ዋና ዋና ነገሮች፣ አየር፣ ውሃና ምግብ ላይ የምናሳየውን ያላሰለሰ ትጋት መቀነስና ማቋረጥ ብቻ ነው። በመንፈሳዊው አለምም ቢሆን ጉልበት የሚሻው ነገር ሕያውነት ነው። ለዚህ ነው ከሕያው አምላክ ጋር የሚደረገው ግንኙነት የክት ሳይሆን የወትሮ መሆን ያለበት። እየታደስን፣ እየለመለምን፣ አንገታችን ቀና የሚል ፍጡራን ነን። በተፈጥሮ አካሄድ ሲርበን ጉልበታችን እንደሚጥመለመል፣ ሲጠማን ምላሳችን ከትናጋችን እንደሚጣበቅ፣ ስንታፈን አየር ፍለጋ እንደምንወራጭ ሁሉ የውስጣዊ ሕይወት ተሃድሶ እንደሚያሻን ለማወቅም በቂ ምልክቶች አሉ።
ከብዙ በጥቂቱ እነሆ፡ ጸሎት፣ አምልኮና አገልግሎት አውቶማቲክ ይሆናል፤ በልቦና ታስቦ በውስጣዊ ጉጉት ተፈልጎ እያወቁ የሚያደርጉት ሳይሆን ቁልፉ ሲነካ እንደሚሽከረከር የግዱን በዘልማዳዊ ህግ ይከናወናል፤ ስለዚህም ይታክታል ፍችውም ይደበዝዛል። የባሰም እንደሆነ ከናካቴው ይቀራል።
መኖር ማለት የየዕለቱን ጉሮሮ የመድፈን ተግባር ለማከናወን የሚደረግ አድካሚ አዙሪት ብቻ ይሆናል። ይኸው የኑሮ ገበያ ቱማታና የስጋ ፍላጎት ከበሮ ድምድምታ በእውቀትም በደመነፍስም የምንከተለው ዜማ ምት ይሆናል። “አዳሜው ሁሉ የሚሮጥለት እንዲያውም ሌላ መሮጫ ምክንያት ባይኖር ነው።”
በክፉና በደግ፣ በንጹህና በርኩስ፣ በጥበብና በጅልነት፣ በእግዚአብሄር መልአክና በጋኔን፣ በእውነትና በሃሰት መሀከል ያለው የልዩነት መስመር እየወየበ ከአንዱ ወደ ሌላው ዘው እያሉ መመለስ እንዲያም ድንበሩን የሽርሽር መስክ ማድረግ እየተለመደ ይመጣል።
“ለካ ልቤን ንፁህ ያደረኩት በከንቱ ነው፤ እጄንም በየዋህነት የታጠብኩት በከንቱ ኖሮአል!” የሚል ውስጣዊ ማልጎምጎም እየበረታ ይመጣል።
ከሰዎች ጋር በተለይ ደግሞ ቅርብ ከሆኑት ወንድሞቻችን እህቶቻችን ጋር ያለን ፍቅራዊ ትኩሳት እየበረደ ይመጣል። ቢኖሩም ባይኖሩም አብረን ብንሆንም ባንሆንም ደንታ ቢስ እየሆንን ስንቀጥል አልፎ አልፎ እንዲያውም አጠገባችን ባይሆኑ እንመርጣለን። ክርስቲያናዊ ህብረት ይጎፈንነናል፤ “እስቲ ተውኝ” የስልቹነታችን ዜማ ይሆናል።
በምንኖርበት አካባቢ ከአፈር ከቅጠሉ ጋር ተዋህደን ቀለማችን ሳይለይ ብንረሳ እንመርጣለን። ለውጥ የማምጣት ፍላጎታችን ይነቅዛል፤ የማይለማ የማይሰማ ዱልዱም መሆን ጣጣ የሌለበት ሕይወት ይመስለናል።
በአፋችን “እሰይ በሰማይ ቤት አለኝ” እያልን እየዘመርን በልባችን “እስቲ እዚህ ያለውን ቤት ባሳመረልኝ” እንላለን። ያኛው ሩቅ የማይደረስበት ምናልባት ስለርሱ ማሰብ ጅል የሚያድርግ እንደሆነ የሚቆጠር፣ ተጨባጩን ቁሳዊ ዓለምን ግን በትኩስ ስግብግብነት የሚያፈቅር አውሬ ልብ ይረባብናል።
ተሐድሶ ማለት ከዘልማድ እስር ቤት፣ ከሞት እስራት በመንፈስ ቅዱስ ሃይል ተመንጥቆ መውጣት ነው፤ ሰባት ጊዜ ከተነጠረ ብር ይልቅ በጠራው በእግዚአብሄር ቃል እንጀራ መበርታት ነው። በእግዚአብሄር ደስታና እርካታ ማግኘት ነው፤ በወገኖች ፍቅር መለምለም ነው፤ በፅድቅ ሕይወት እርምጃ የሚገኝ አንበሳዊ ድፍረት ነው፤ በተልዕኮ እርግጥኝነት ምክንያት የሚደረግ ግሥገሳ ነው። ተሐድሶ የቦዘ ዓይን ፍንትው የሚልበት፣ ከሁለንታለም ፈጣሪ ጋር ፍቅር የሚያገረሽበት፣ እንቅስቃሴ ሁሉ ትርጉም የሚያገኝበት ደማቅ ኑሮ ነው። የኢየሱስ ክርስቶስ ወዳጅም ወታደርም የመሆን ብቃት ነው።
ይህ ሁሉ እንዴት ሊሆን ይችላል?
ከሁሉ በፊትና በላይ ልዑል እግዚአብሄር አዳሽ አምላክ ነው። በፈጣሪነቱ የሚታወቀው ይህ አምላክ፣ በአዳሽነቱም ወደር የለውም። የደረቁ አጥንቶችን ተንቀሳቃሽ ሠራዊት ለማድረግ አራት ነፋሳት የሚጠራ፣ መቃብር ከፋች ብርቱ ጌታ ነው። ያሁን ዘመን ዋናው ስራው ሙታንን መቀስቀስ ነው።
በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል የግንኙነት እድሳት፣ በቅዱስ መንፈሱ በኩል የንጽህናና የሀይል እድሳት እያደረገ ነው።
መንገዱ የተወላከፈ እንግድግድ የሰው ልጅ የሞት ሽረቱን መንከላወስ ትቶ ለምርመራ መቆም አለበት።
“እንግዲህ ከወዴት እንደወደክ አስብ፣ ንስሀም ግባ፣ የቀደመውንም ስራህን አድርግ” የተባለው በብዙ መስመር ብርቱ የነበረው ፍቅሩ ግን ያረጀበት የቤ/ክርስቲያን መሪና ህዝቡ ናቸው።
እስኪ ነገሮችን ላይ ላይ የመነካካት ግልብነታችንን ትተን ስለሕይወታችን አምርረን እናስብ፤ “አስብ” ተብለናላ! እስኪ ጎምዛዛውን ፍሬ ከአፋችን እንትፋው፣ መንፈሳዊ ጭካኔ እንልመድ። “ንስሀ ግባ” ማለት ሌላ ምንድን ነው? እስኪ ደግሞ በመፅሀፉም በልምድም የምናውቀውን ተገቢ ስራ እንደገና እንቀጥል፤ “የቀደመውን ስራህን አድርግ” ማለቱ ቋሚ የኑሮ መልክ ያለ መሆኑን ያመለክታል።
በፍቅረ እግዚአብሄር በፍቅረ ሰብዕ እንታደስ
በእውነት ትምህርት በንፁህ ሃይማኖት እንታደስ
በሰላም ናፍቆት በእርቅ አስተናጋጅነት እንታደስ
በቅዱስ ኑሮ በቅዱስ ሃሳብ እንታደስ
መንፈስ ቅዱስ ለእኔና ለወገኖቼ አዲስ ነፋስ ላክልን፣ ሕያውነት ወደ አጥንቶቻችን ውስጥ ይዝለቅ፣ የምድሪቱም ገጽ ይፍካ።
ንጉሤ ቡልቻ
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤3👍3
' ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“በእግዚአብሔር ታመን፥ መልካምንም አድርግ፥ በምድርም ተቀመጥ፥ ታምነህም ተሰማራ።”
መዝሙር 37፥3
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“በእግዚአብሔር ታመን፥ መልካምንም አድርግ፥ በምድርም ተቀመጥ፥ ታምነህም ተሰማራ።”
መዝሙር 37፥3
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤3
#እራሳችንን_እንመርምር
በሕይወት መንገድ የሚጋፉንና የሚያስጨንቁን ብዙዎች ናቸው። ጥያቄ መሆን ያለበት ግን ጭንቅ ሲበዛብን ከእግዚአብሔር ቃል መንገድ ፈቀቅ አልን ወይስ ቃሉን ይዘን ጸንተን የሙጥኝ ብለን እንገኛለን?
“ያሳደዱኝና ያስጨነቁኝ ብዙዎች ናቸው፤ ከምስክር ግን ፈቀቅ አላልሁም።”
መዝሙር 119፥157
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
በሕይወት መንገድ የሚጋፉንና የሚያስጨንቁን ብዙዎች ናቸው። ጥያቄ መሆን ያለበት ግን ጭንቅ ሲበዛብን ከእግዚአብሔር ቃል መንገድ ፈቀቅ አልን ወይስ ቃሉን ይዘን ጸንተን የሙጥኝ ብለን እንገኛለን?
“ያሳደዱኝና ያስጨነቁኝ ብዙዎች ናቸው፤ ከምስክር ግን ፈቀቅ አላልሁም።”
መዝሙር 119፥157
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍2❤1
' ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“አቤቱ ጌታ እግዚአብሔር ሆይ፥ እነሆ፥ አንተ ሰማይንና ምድርን በታላቅ ኃይልህና በተዘረጋች ክንድህ ፈጥረሃል፥ ከአንተም የሚያቅት ነገር የለም።”
ኤርምያስ 32፥17
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“አቤቱ ጌታ እግዚአብሔር ሆይ፥ እነሆ፥ አንተ ሰማይንና ምድርን በታላቅ ኃይልህና በተዘረጋች ክንድህ ፈጥረሃል፥ ከአንተም የሚያቅት ነገር የለም።”
ኤርምያስ 32፥17
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤5
አትፍራ
"አትፍራ" የሚለው ቃል በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ ተደጋግሞ ይገኛል። እናላቹ አንድ ሰው ብድግ ብሎ ለምንድነው የማልፈራው ቢል ትፈርዱበታላችሁ? የሚፈራበትን ምክንያት ዘርዝር ካላችሁትም ስፍር ቁጥር የሌለውን ተራ በተራ ይሰድርላችኋል። ግን የእግዚአብሔር ቃል ለምን መፍራት እንደ ሌለብን ሲገልጽ አንድ አጭር መልስ አለው እርሱም፦ "#እኔ_ከአንተ_ጋር_ነኝ" የሚለው ነው። እንዴ? እንዴት ለእነዚህ ፍጻሜ ለማይገኝላቸው ለሚያስፈሩን ነገሮች አንድ ዓረፍተ ነገር ብቻውን መልስ ይሆናል? እንዴታ መልስማ ይሆናል! ምክንያት ጥቀስልኝ ካላችሁ፦
፩. እኔ ከአንተ ጋር ነኝ ያለው ሁሉን ቻዩና ሁሉን የሚገዛው እግዚአብሔር ነው።
፪. ከአንተ ጋር እሆናለሁ ሳይሆን ያለው እኔ ከአንተ ጋር ነኝ ነው። ወደፊት እሆናለሁ ካለማ እስከዛ እንዴት ይዘለቃል ይባል ይሆናል "ነኝ" ካለ ግን ፍርሃት ዘሎ እንዳይገባ መፈናፈኛ ያጣልና ዋስትናችን ሙሉ ነው።
ከእኔ ጋር ያለው እርሱ እግዚአብሔር ከሆነ፣ ዛሬዬም በእርሱ ቁጥጥር ስር ካለ ምን ይመጣል? ብቻ እግዚአብሔር ከእኔ ጋር እንዳለ እኔም ከእርሱ ጋር እንዳለው እርግጠኛ ልሁን እንጂ
“ከዚያም ወደ ቤርሳቤህ ወጣ። በዚያችም ሌሊት እግዚአብሔር ተገለጠለት፥ እንዲህም አለው፦ እኔ የአባትህ የአብርሃም አምላክ ነኝ አትፍራ፥ እኔ ከአንተ ጋር ነኝና እባርክሃለሁ ስለ ባሪያዬ ስለ አብርሃም ዘርህን አበዛለሁ።”
ዘፍጥረት 26፥23-24
“ጽኑ፥ አይዞአችሁ፥ አትፍሩ፥ ከፊታቸውም አትደንግጡ፤ አምላክህ እግዚአብሔር እርሱ ከአንተ ጋር ይሄዳል፤ አይጥልህም፥ አይተውህም።”
ዘዳግም 31፥6
“በምትሄድበት ሁሉ አምላክህ እግዚአብሔር ከአንተ ጋር ነውና ጽና፥ አይዞህ አትፍራ፥ አትደንግጥ ብዬ አላዘዝሁህምን?”
ኢያሱ 1፥9
“እኔ ከአንተ ጋር ነኝና አትፍራ፤ እኔ አምላክህ ነኝና አትደንግጥ፤ አበረታሃለሁ፥ እረዳህማለሁ፥ በጽድቄም ቀኝ ደግፌ እይዝሃለሁ።”
ኢሳይያስ 41፥10
“እኔ ከአንተ ጋር ነኝና አትፍራ፤ ዘርህንም ከምሥራቅ አመጣዋለሁ፥ ከምዕራብም እሰበስብሃለሁ።”
ኢሳይያስ 43፥5
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
"አትፍራ" የሚለው ቃል በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ ተደጋግሞ ይገኛል። እናላቹ አንድ ሰው ብድግ ብሎ ለምንድነው የማልፈራው ቢል ትፈርዱበታላችሁ? የሚፈራበትን ምክንያት ዘርዝር ካላችሁትም ስፍር ቁጥር የሌለውን ተራ በተራ ይሰድርላችኋል። ግን የእግዚአብሔር ቃል ለምን መፍራት እንደ ሌለብን ሲገልጽ አንድ አጭር መልስ አለው እርሱም፦ "#እኔ_ከአንተ_ጋር_ነኝ" የሚለው ነው። እንዴ? እንዴት ለእነዚህ ፍጻሜ ለማይገኝላቸው ለሚያስፈሩን ነገሮች አንድ ዓረፍተ ነገር ብቻውን መልስ ይሆናል? እንዴታ መልስማ ይሆናል! ምክንያት ጥቀስልኝ ካላችሁ፦
፩. እኔ ከአንተ ጋር ነኝ ያለው ሁሉን ቻዩና ሁሉን የሚገዛው እግዚአብሔር ነው።
፪. ከአንተ ጋር እሆናለሁ ሳይሆን ያለው እኔ ከአንተ ጋር ነኝ ነው። ወደፊት እሆናለሁ ካለማ እስከዛ እንዴት ይዘለቃል ይባል ይሆናል "ነኝ" ካለ ግን ፍርሃት ዘሎ እንዳይገባ መፈናፈኛ ያጣልና ዋስትናችን ሙሉ ነው።
ከእኔ ጋር ያለው እርሱ እግዚአብሔር ከሆነ፣ ዛሬዬም በእርሱ ቁጥጥር ስር ካለ ምን ይመጣል? ብቻ እግዚአብሔር ከእኔ ጋር እንዳለ እኔም ከእርሱ ጋር እንዳለው እርግጠኛ ልሁን እንጂ
“ከዚያም ወደ ቤርሳቤህ ወጣ። በዚያችም ሌሊት እግዚአብሔር ተገለጠለት፥ እንዲህም አለው፦ እኔ የአባትህ የአብርሃም አምላክ ነኝ አትፍራ፥ እኔ ከአንተ ጋር ነኝና እባርክሃለሁ ስለ ባሪያዬ ስለ አብርሃም ዘርህን አበዛለሁ።”
ዘፍጥረት 26፥23-24
“ጽኑ፥ አይዞአችሁ፥ አትፍሩ፥ ከፊታቸውም አትደንግጡ፤ አምላክህ እግዚአብሔር እርሱ ከአንተ ጋር ይሄዳል፤ አይጥልህም፥ አይተውህም።”
ዘዳግም 31፥6
“በምትሄድበት ሁሉ አምላክህ እግዚአብሔር ከአንተ ጋር ነውና ጽና፥ አይዞህ አትፍራ፥ አትደንግጥ ብዬ አላዘዝሁህምን?”
ኢያሱ 1፥9
“እኔ ከአንተ ጋር ነኝና አትፍራ፤ እኔ አምላክህ ነኝና አትደንግጥ፤ አበረታሃለሁ፥ እረዳህማለሁ፥ በጽድቄም ቀኝ ደግፌ እይዝሃለሁ።”
ኢሳይያስ 41፥10
“እኔ ከአንተ ጋር ነኝና አትፍራ፤ ዘርህንም ከምሥራቅ አመጣዋለሁ፥ ከምዕራብም እሰበስብሃለሁ።”
ኢሳይያስ 43፥5
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤6👍6
' ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“በጠራሁህ ቀን ቀርበህ፦ አትፍራ አልህ።”
ሰቆ. 3፥57
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“በጠራሁህ ቀን ቀርበህ፦ አትፍራ አልህ።”
ሰቆ. 3፥57
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤5👍4
ከሐዋርያት መካከል ኢየሱስ ክርስቶስ ያልመረጠው ሐዋርያ የቱ ነው?
Anonymous Quiz
1%
ሀ. ጴጥሮስ
3%
ለ. ይሁዳ
53%
ሐ. ማትያስ
12%
መ. በርተሎሜዎስ
31%
ሠ. ኢየሱስ ያልመረጠው ሐዋርያ የለም
👍7❤5
' ==❀❀❀===❀❀❀==
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“የአምላኬም እጅ በእኔ ላይ መልካም እንደሆነች፥ ንጉሡም የነገረኝን ቃል ነገርኋቸው። እነርሱም፦ እንነሣና እንሥራ አሉ። እጃቸውንም ለበጎ ሥራ አበረቱ።”
ነህምያ 2፥18
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የዕለቱ ጥቅስ
==❀❀❀===❀❀❀==
“የአምላኬም እጅ በእኔ ላይ መልካም እንደሆነች፥ ንጉሡም የነገረኝን ቃል ነገርኋቸው። እነርሱም፦ እንነሣና እንሥራ አሉ። እጃቸውንም ለበጎ ሥራ አበረቱ።”
ነህምያ 2፥18
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍6❤2