mason-4-cr.pdf
2.3 MB
👉ርዕስ፦ የመንፈስ ቅዱስ ስጦታዎችን ማውቅና በአግባቡ መጠቀም
✍️ጸሐፊ፦ ዶ/ር መለሰ ወጉ
📑የገጽ ብዛት፦ 384
🖨 የታተመበት ዓመት፦1993 ዓመት/ 2000 እ. ኤ.አ
💡መጽሐፉ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የተጠቀሱትን የጸጋ ስጦታዎችን ከሞላ ጎደል አንድ በአንድ በዝርዝር ለመዳሰስ የሚሞክር ነው።
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
✍️ጸሐፊ፦ ዶ/ር መለሰ ወጉ
📑የገጽ ብዛት፦ 384
🖨 የታተመበት ዓመት፦1993 ዓመት/ 2000 እ. ኤ.አ
💡መጽሐፉ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የተጠቀሱትን የጸጋ ስጦታዎችን ከሞላ ጎደል አንድ በአንድ በዝርዝር ለመዳሰስ የሚሞክር ነው።
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤9👍2🔥2
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“እንግዲያስ ሰላም የሚቆምበትን እርስ በርሳችንም የምንታነጽበትን እንከተል።”
ሮሜ 14፥19
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“እንግዲያስ ሰላም የሚቆምበትን እርስ በርሳችንም የምንታነጽበትን እንከተል።”
ሮሜ 14፥19
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤3👍2
ቅዱሳት መጻሕፍት
መጽሐፍ ቅዱስ የእግዚአብሔር ቃል የተለየ ትኩረት ሳይሰጥ የሚያነብ አንባቢ እንኳን መጽሐፍ ቅዱስን በሚያነብበት ጊዜ መጽሐፉ ፍጹም ልዩ መሆኑን ይገነዘባል። መጽሐፍ ቅዱስ የሰውን ልጅ የብዙ ሺህ ዓመታት ታሪክ የሚያጠቃልል ሲሆን ፥ ከአርባ በሚበልጡ በተለያዩ ዘመናትና፥ የኑሮ ሁኔታዎች ውስጥ ባለፉ ጸሐፊዎች የተጻፈ ነው። ይሁን እንጂ የማይገናኙ ልዩ ልዩ ጽሑፎች ስብስብ ሳይሆን፥ አስደናቂ ተከታታይነትና…
የቀጠለ...
መጽሐፍ ቅዱስ የእግዚአብሔር ቃል
ለ. ውጫዊ ማረጋገጫ
መጽሐፍ ቅዱስ የእግዚአብሔር ቃል መሆኑን በራሱ የሚያስረግጥ ብቻ ሳይሆን፥ ተጠራጣሪዎችን እንኳን ለማሳመን በሚችሉ ብዙ መረጃዎች የተሞላ ነው።
1. የመጽሐፍ ቅዱስ ተከታታይነት ወይም ወጥነት።
ስለ መጽሐፍ ቅዱስ ከተገለጡት እጅግ አስገራሚ እውነቶች አንዱ፥ ወደ 1600 ዓመታት በሚጠጋ ጊዜ ውስጥ በኖሩና ከአርባ በላይ በሚሆኑ የተለያዩ ሰዎች የተጻፈ መሆኑ ነው። ይሁን እንጂ መጽሐፉ የስድሳ ስድስት መጻሕፍት ስብስብ ሳይሆን፥ አንድና ወጥ ነው። ጸሐፊዎቹ ከተለያየ ማኅበራዊ መሠረት የመጡ ናቸው፤ ነገሥታት፥ ጭሰኞች፥ ፈላስፋዎች፥ ዓሣ አጥማጆች፥ ሐኪሞች፥ የመንግሥት ባለሥልጣናት፥ ምሁራን፥ ባለቅኔዎች እና ገበሬዎች ነበሩ። እነዚህ ሰዎች በተለያዩ ባህሎችና ልምዶች መኖር ብቻ ሳይሆን፥ የተለያዩ ባህርያትም ነበሯቸው። ቢሆንም መጽሐፍ ቅዱስ ከዘፍጥረት እስከ ራእይ በግልጥ የሚታይ ተከታታይነትና ወጥነት አለው።
የመጽሐፉ ተከታታይነት ከአሁኑ ዓለም አፈጣጠር እስከ አዲሱ ሰማይና ምድር መፈጠር ድረስ ባለው ታሪካዊ ቅደም ተከተል ሥርዓት ሊታይ ይችላል። ብሉይ ኪዳን ስለ እግዚኣብሔር ባህርይ ፥ ስለ ኃጢአት፥ ስለ ድነት፥ እንዲሁም እግዚአብሔር ስለ መላው ዓለም፥ ስለ እስራኤልና ስለ ቤተ ክርስቲያን ያለውን ዓላማና ዕቅድ ይገልጣል። መለኮታዊ ትምህርት ከዝቅተኛው፥ ማለት ቀለል ካለ መግቢያ ተነሥቶ እስከተወሳሰበ ትምህርትነት ደረጃ በደረጃ ይቀርባል። መጽሐፍ ቅዱስ ምሳሌያዊ አገላለጦችን በቀጥተኛ ትርጉማቸው፥ ትንቢቶችን ደግሞ በተወሰነ ጊዜ ክንውናቸው ያሳያል። ከመጽሐፍ ቅዱስ ዐበይት ጉዳዮች አንዱ፥ በሰማይና በምድር እጅግ ስለከበረውና ፍጹም ስለሆነው ኢየሱስ ክርስቶስ በቅድሚያ መተንበይ፥ የትንቢቱን እውንነት ማመልከትና ኢየሱስን ከፍ ማድረግ ነው። ይህ አስደናቂ መጽሐፍ በሰዎች ተጻፈ ብሉ ከማመን ይልቅ፥ በእግዚአብሔር ገላጭነት ተጻፈ የሚለውን መቀበሉ ይቀልላል። ስለሆነም፥ በመጽሐፍ ቅዱስ የሚያምኑ ሁሉ፥ የተለያዩት የመጽሐፍ ቅዱስ መልእክቶች በተለያዩ ሰዎች የተጻፉ መሆናቸውን በመቀበል፥ የመልእክቶቹን አንድ ወጥነት በመንፈስ ቅዱስ ምሪትና አነሳሽነት ይረዳሉ።
2. የመጽሐፍ ቅዱሳዊ መገለጥ ጥልቅነት።
እውነትን በመግለጥ ረገድ መጽሐፍ ቅዱስ ተመርምሮ አያልቅም። ቴሌስኮፕ የሰማይን ከፍታ እንደሚያሳይ፥ መጽሐፍ ቅዱስም የእግዚአብሔርን የእጅ ሥራዎች ከመነሻ እስከ ፍጻሜ፥ ከሰማያት ከፍታ፥ እስከ ሲኦል ጥልቀት ያመለክታል። ማይክሮስኮፕ ረቂቅ ነገሮችን እንደሚያሳይ ሁሉ፥ ረቂቁ የእግዚአብሔር ሥራ፥ ዕቅድና ዓላማው እንዲሁም የፍጥረቱ ፍጹምነት በመጽሐፍ ቅዱስ ተገልጧል። ምንም እንኳን መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የተካተቱት ብዙ መጻሕፍት የተጻፉት፥ ጸሐፊዎቹ ስለዘመናዊው ግኝት ግምት ባልነበራቸው ጊዜና በጥንታዊው የሰው ልጅ እውቀት ደረጃ ቢሆንም፥ በቅርቡ የተገኙት የሥነ-ምድር ምርምር ጥናቶች መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ያሉትን እውነቶች ከመቃረን ይልቅ ይደግፋሉ። ጥንታዊዎቹ ቅዱሳት መጻሕፍት በሚያስደንቅ አኳኋን ከዘመናዊው የሥነ-ምድር ምርምር ግኝቶች ጋር ይስማማሉ። መጽሐፍ ቅዱስ ዘላለማዊነት ያላቸውንና በእግዚአብሔር ብቻ የሚታወቁትን እውነቶች ስለሚገልጥ፥ ከሰው ምርምርና ግኝት በላይ የሆኑ እውነቶችን ይዟል። መጽሐፍ ቅዱስ እውነትን በሙላትና በረቂቅነት የሚያሳየንን ያህል የሚያሳይ ሌላ መጽሐፍ በዓለም የለም።
3. የመጽሐፍ ቅዱስ የመለወጥ ኃይልና ኅትመቱ።
በዓለማችን የመጽሐፍ ቅዱስን ያህል ለተለያዩ ሕዝቦችና ባህሎች በተለያዩ አያሌ ቋንቋዎች የታተመ ሌላ መጽሐፍ የለም። የማተሚያ መኪና እንደተፈለሰፈም ለመጀመሪያ ጊዜ የታተመው መጽሐፍ ቅዱስ ነው። በዓለም ታላላቅ ቋንቋዎች ሁሉ በብዙ ሚሊዮን ቅጂዎች ታትሟል። ጽሑፍ ያለው እያንዳንዱ ቋንቋ ከመጽሐፍ ቅዱስ ቢያንስ ጥቂት ክፍሎች የታተመ ነገር አለው። ምንም እንኳን እንደ ፈረንሳዊው ቮልቴር ያሉ ሃይማኖት የለሾች መጽሐፍ ቅዱስ ከአንድ ትውልድ ዕድሜ በኋላ ከአገልግሎት ውጪ ይሆናል ቢሉም፥ የሀያኛው ክፍለ-ዘመን ደራሲያንም መጽሐፉ ይረሳል ወይም ፈላጊ አይኖረውም ቢሉም፥ ካለፈው ይበልጥ በብዙ ቋንቋዎች በመታተም ላይ ነው። በተከታዮች ብዛት ከክርስትና የሚበልጡ ሌሎች ሃይማኖቶች፥ ከመጽሐፍ ቅዱስ ጋር ሊወዳደር የሚችልና መገለጥ ያለው ጽሑፍ ሊያቀርቡ አልቻሉም። የመጽሐፍ ቅዱስ ሕይወትን የመለወጥ ኃይል በዘመናችንም ቀጥሏል። ላልዳነ ሰው መጽሐፍ ቅዱስ “የመንፈስ ሰይፍ” ነው (ኤፌ. 6፡17)፤ ለዳነው የሚያነጻ፥ የቅድስናና ድል አድራጊነት ኃይል ነው (ዮሐ. 17፡17፤ 2ኛ ቆሮ. 3፡ 17፥ 18፤ ኤፌ. 5፡25-26)። መጽሐፍ ቅዱስ የሕግና የሥነ-ምግባር ብቸኛው መለኮታዊ መሠረት እንደሆነ ይኖራል።
ይቀጥላል. . .
ምንጭ፡- “ዋና ዋና የመጽሐፍ ቅዱስ ጭብጦች” መጽሐፍ በዶክተር ሉዊስ ስፔሪ ቼፈር የተጻፈ እና በተክሉ መንገሻ የተተረጎመ ነው፡፡
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
መጽሐፍ ቅዱስ የእግዚአብሔር ቃል
ለ. ውጫዊ ማረጋገጫ
መጽሐፍ ቅዱስ የእግዚአብሔር ቃል መሆኑን በራሱ የሚያስረግጥ ብቻ ሳይሆን፥ ተጠራጣሪዎችን እንኳን ለማሳመን በሚችሉ ብዙ መረጃዎች የተሞላ ነው።
1. የመጽሐፍ ቅዱስ ተከታታይነት ወይም ወጥነት።
ስለ መጽሐፍ ቅዱስ ከተገለጡት እጅግ አስገራሚ እውነቶች አንዱ፥ ወደ 1600 ዓመታት በሚጠጋ ጊዜ ውስጥ በኖሩና ከአርባ በላይ በሚሆኑ የተለያዩ ሰዎች የተጻፈ መሆኑ ነው። ይሁን እንጂ መጽሐፉ የስድሳ ስድስት መጻሕፍት ስብስብ ሳይሆን፥ አንድና ወጥ ነው። ጸሐፊዎቹ ከተለያየ ማኅበራዊ መሠረት የመጡ ናቸው፤ ነገሥታት፥ ጭሰኞች፥ ፈላስፋዎች፥ ዓሣ አጥማጆች፥ ሐኪሞች፥ የመንግሥት ባለሥልጣናት፥ ምሁራን፥ ባለቅኔዎች እና ገበሬዎች ነበሩ። እነዚህ ሰዎች በተለያዩ ባህሎችና ልምዶች መኖር ብቻ ሳይሆን፥ የተለያዩ ባህርያትም ነበሯቸው። ቢሆንም መጽሐፍ ቅዱስ ከዘፍጥረት እስከ ራእይ በግልጥ የሚታይ ተከታታይነትና ወጥነት አለው።
የመጽሐፉ ተከታታይነት ከአሁኑ ዓለም አፈጣጠር እስከ አዲሱ ሰማይና ምድር መፈጠር ድረስ ባለው ታሪካዊ ቅደም ተከተል ሥርዓት ሊታይ ይችላል። ብሉይ ኪዳን ስለ እግዚኣብሔር ባህርይ ፥ ስለ ኃጢአት፥ ስለ ድነት፥ እንዲሁም እግዚአብሔር ስለ መላው ዓለም፥ ስለ እስራኤልና ስለ ቤተ ክርስቲያን ያለውን ዓላማና ዕቅድ ይገልጣል። መለኮታዊ ትምህርት ከዝቅተኛው፥ ማለት ቀለል ካለ መግቢያ ተነሥቶ እስከተወሳሰበ ትምህርትነት ደረጃ በደረጃ ይቀርባል። መጽሐፍ ቅዱስ ምሳሌያዊ አገላለጦችን በቀጥተኛ ትርጉማቸው፥ ትንቢቶችን ደግሞ በተወሰነ ጊዜ ክንውናቸው ያሳያል። ከመጽሐፍ ቅዱስ ዐበይት ጉዳዮች አንዱ፥ በሰማይና በምድር እጅግ ስለከበረውና ፍጹም ስለሆነው ኢየሱስ ክርስቶስ በቅድሚያ መተንበይ፥ የትንቢቱን እውንነት ማመልከትና ኢየሱስን ከፍ ማድረግ ነው። ይህ አስደናቂ መጽሐፍ በሰዎች ተጻፈ ብሉ ከማመን ይልቅ፥ በእግዚአብሔር ገላጭነት ተጻፈ የሚለውን መቀበሉ ይቀልላል። ስለሆነም፥ በመጽሐፍ ቅዱስ የሚያምኑ ሁሉ፥ የተለያዩት የመጽሐፍ ቅዱስ መልእክቶች በተለያዩ ሰዎች የተጻፉ መሆናቸውን በመቀበል፥ የመልእክቶቹን አንድ ወጥነት በመንፈስ ቅዱስ ምሪትና አነሳሽነት ይረዳሉ።
2. የመጽሐፍ ቅዱሳዊ መገለጥ ጥልቅነት።
እውነትን በመግለጥ ረገድ መጽሐፍ ቅዱስ ተመርምሮ አያልቅም። ቴሌስኮፕ የሰማይን ከፍታ እንደሚያሳይ፥ መጽሐፍ ቅዱስም የእግዚአብሔርን የእጅ ሥራዎች ከመነሻ እስከ ፍጻሜ፥ ከሰማያት ከፍታ፥ እስከ ሲኦል ጥልቀት ያመለክታል። ማይክሮስኮፕ ረቂቅ ነገሮችን እንደሚያሳይ ሁሉ፥ ረቂቁ የእግዚአብሔር ሥራ፥ ዕቅድና ዓላማው እንዲሁም የፍጥረቱ ፍጹምነት በመጽሐፍ ቅዱስ ተገልጧል። ምንም እንኳን መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የተካተቱት ብዙ መጻሕፍት የተጻፉት፥ ጸሐፊዎቹ ስለዘመናዊው ግኝት ግምት ባልነበራቸው ጊዜና በጥንታዊው የሰው ልጅ እውቀት ደረጃ ቢሆንም፥ በቅርቡ የተገኙት የሥነ-ምድር ምርምር ጥናቶች መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ያሉትን እውነቶች ከመቃረን ይልቅ ይደግፋሉ። ጥንታዊዎቹ ቅዱሳት መጻሕፍት በሚያስደንቅ አኳኋን ከዘመናዊው የሥነ-ምድር ምርምር ግኝቶች ጋር ይስማማሉ። መጽሐፍ ቅዱስ ዘላለማዊነት ያላቸውንና በእግዚአብሔር ብቻ የሚታወቁትን እውነቶች ስለሚገልጥ፥ ከሰው ምርምርና ግኝት በላይ የሆኑ እውነቶችን ይዟል። መጽሐፍ ቅዱስ እውነትን በሙላትና በረቂቅነት የሚያሳየንን ያህል የሚያሳይ ሌላ መጽሐፍ በዓለም የለም።
3. የመጽሐፍ ቅዱስ የመለወጥ ኃይልና ኅትመቱ።
በዓለማችን የመጽሐፍ ቅዱስን ያህል ለተለያዩ ሕዝቦችና ባህሎች በተለያዩ አያሌ ቋንቋዎች የታተመ ሌላ መጽሐፍ የለም። የማተሚያ መኪና እንደተፈለሰፈም ለመጀመሪያ ጊዜ የታተመው መጽሐፍ ቅዱስ ነው። በዓለም ታላላቅ ቋንቋዎች ሁሉ በብዙ ሚሊዮን ቅጂዎች ታትሟል። ጽሑፍ ያለው እያንዳንዱ ቋንቋ ከመጽሐፍ ቅዱስ ቢያንስ ጥቂት ክፍሎች የታተመ ነገር አለው። ምንም እንኳን እንደ ፈረንሳዊው ቮልቴር ያሉ ሃይማኖት የለሾች መጽሐፍ ቅዱስ ከአንድ ትውልድ ዕድሜ በኋላ ከአገልግሎት ውጪ ይሆናል ቢሉም፥ የሀያኛው ክፍለ-ዘመን ደራሲያንም መጽሐፉ ይረሳል ወይም ፈላጊ አይኖረውም ቢሉም፥ ካለፈው ይበልጥ በብዙ ቋንቋዎች በመታተም ላይ ነው። በተከታዮች ብዛት ከክርስትና የሚበልጡ ሌሎች ሃይማኖቶች፥ ከመጽሐፍ ቅዱስ ጋር ሊወዳደር የሚችልና መገለጥ ያለው ጽሑፍ ሊያቀርቡ አልቻሉም። የመጽሐፍ ቅዱስ ሕይወትን የመለወጥ ኃይል በዘመናችንም ቀጥሏል። ላልዳነ ሰው መጽሐፍ ቅዱስ “የመንፈስ ሰይፍ” ነው (ኤፌ. 6፡17)፤ ለዳነው የሚያነጻ፥ የቅድስናና ድል አድራጊነት ኃይል ነው (ዮሐ. 17፡17፤ 2ኛ ቆሮ. 3፡ 17፥ 18፤ ኤፌ. 5፡25-26)። መጽሐፍ ቅዱስ የሕግና የሥነ-ምግባር ብቸኛው መለኮታዊ መሠረት እንደሆነ ይኖራል።
ይቀጥላል. . .
ምንጭ፡- “ዋና ዋና የመጽሐፍ ቅዱስ ጭብጦች” መጽሐፍ በዶክተር ሉዊስ ስፔሪ ቼፈር የተጻፈ እና በተክሉ መንገሻ የተተረጎመ ነው፡፡
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍3❤2
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ምሕረትህን በሚያውቁህ ላይ፥ ጽድቅህንም ልባቸው በቀና ላይ ዘርጋ።”
መዝሙር 36፥10
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ምሕረትህን በሚያውቁህ ላይ፥ ጽድቅህንም ልባቸው በቀና ላይ ዘርጋ።”
መዝሙር 36፥10
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤5👍2
#የሮሜ_መልእክት_ጥናት
የእግዚአብሔር ጽድቅ (9:14-18)
እግዚአብሔር አንዱን መርጦ ሌላውን መተዉ ዐመፀኛ መሆኑን የሚያመለክት ይመስላል፡፡ «በእግዚአብሔር ዘንድ ዐመፃ አለ ወይ?» ብሎ ጳውሎስ ጠይቋል:: ራሱ «አይደለም» ብሎ መልስ ይሰጣል፡፡ ቅዱስ እግዚአብሔር ዐመፅ ያደርጋል ማለት የማይታሰብ ነገር ነው:: ምርጫ የጸጋ ጉዳይ ነው፡፡ እግዚአብሔር ነገርን ሁሉ እንደ ጽድቃችን ቢሰጠን ኖሮ፣ ማንም አይድንም ነበር፡፡ ጳውሎስ ዘጸአት 33:19 ጠቅሶ የእግዚአብሔር ምሕረትና ርኅራኄ የሚቀጥሉት እንደ ሰው ፈቃድ ሳይሆን፣ እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ መሆኑን አሳይቷል:: ሁላችንም ምሕረት ሳይሆን፣ ፍርድ የተገባን ነበርን፡፡ ዘጸአት 33 የሚናገረው ሙሴ በተራራው ላይ ሕግጋተ እግዚአብሔርን ሲቀበል እስራኤላውያን ስለማመንዘራቸው ነው፡፡ ሕዝብ ሁሉ መሞት ሲገባቸው፣ እግዚአብሔር የቀሰፈው ግን 3,000 ሰዎችን ብቻ ነው:: ያልሞቱት ቅዱሳን ስለሆኑ ወይም የሞቱት ከእነርሱ የባሱ ክፉና ርኩሳን ስለሆኑ ሳይሆን፣ በምሕረቱና በጸጋው ነው::
ጳውሎስ ዘጸአት 9:16 በመጥቀስ ፈርዖንን እንደ ምሳሌ አቅርቧል:: ሙሴ አይሁድ ነበር፣ ፈርዖን ደግሞ አረማዊ፣ ነገር ግን ሁለቱም ኃጢአተኞች ነበሩ፡፡ ሁለቱም ነፍሰ ገዳዮች ነበሩ፡፡ ሁለቱም የእግዚአብሔርን ተአምራት አይተዋል፡፡ ሙሴ ሲድን፣ ፈርዖን ግን ጠፋ፡፡ እግዚአብሔር ፈርዖንን ያስነሣው ክብሩንና ኃይሉን ሊገልጥ ነው:: ሙሴን ደግሞ የማረው ሕዝቡን እስራኤልን ነፃ እንዲያወጣ ነው፡፡ ፈርዖን ገዥ ነው፣ ሙሴ ደግሞ ባሪያ ነበር፡፡ ነገር ግን የእግዚአብሔርን ምሕረትና ርኅራኄ የተለማመደው ሙሴ ነው ምክንያቱም እግዚአብሔር እንዲህ እንዲሆን ፈቀደ፡፡ እግዚአብሔር ሉዓላዊ ስለሆነ በሥራውና በአደራረጉ እንደ ፈቀዱና እንደ ዓላማው ያደርጋል፡፡ ነገሩ የጽድቅ ጉዳይ ሳይሆን፣ ልዑል የሆነው የእግዚአብሔር ፈቃድ ጉዳይ ነው፡፡
እግዚአብሔር ቅዱስ ነውና ኃጢአትን ሊቀጣ ይገባዋል፡፡ ነገር ግን እግዚአብሔር አፍቃሪና ኃጢአተኞችን ለማዳን መሻት ያለው አምላክ ነው:: ሰው ሁሉ ቢድን፣ ቅድስናውን መካዱ ነው፤ ሰው ሁሉ ቢጠፋ ደግሞ፣ ፍቅሩን ሊክድ ነው፡፡ መፍትሔው የእግዚአብሔር ሉዓላዊ ምርጫ ነው፡፡
እግዚአብሔር እስራኤልን መርጦ ግብፅን ኮነነ፣ ሉዓላዊ፣ ዓላማው ይህ ነበርና፡፡ እግዚአብሔር ጻድቅ ስለሆነ፣ ምሕረቱን በምን መንገድ እንደሚሰጥ ማንም ሊጠይቅ አይችልም፡፡
ይህን ክፍል ስንጨርስ ስለ ፈርዖን ልብ «መደንደን» እንነጋገራለን (ቁ. 18)። «የልብ መደንደን» ሂደት ከዘጸአት 7-14 ድረስ 15 ጊዜ ተጠቅሷል፡፡ አንዳንድ ጊዜ ፈርዖን ልቡን እንዳደነደነ ተነግሮናል (ዘጸ. 8:15፣19፣32)፣ በሌላ ጊዜ ደግሞ እግዚአብሔር የፈርዖንን ልብ እንዳደነደነ ተጽፎአል (ዘጸ. 9:12፤10:1፣20፣27)፡፡ ቃሉን በማወጅና ኃይሉን በመግለጥ ፈርዖን ንስሐ እንዲገባ ዕድል ቢሰጠውም፣ እርሱ ግን እግዚአብሔርን በመቋቋም ልቡን አደነደነ:: ችግሩ ያለው በእግዚአብሔር ዘንድ ሳይሆን፣ በፈርዖን ላይ ነው:: በረዶን የሚያቀልጥ የፀሐይ ብርሃን ሽክላን ያደርቃል፡፡ እግዚአብሔር ፈርዖንን በንስሐ ገብቶ እንዲያምን ዕድል ስለሰጠው፣ እግዚአብሔር ዐመፀኛ አልነበረም፡፡
ይቀጥላል...
ምንጭ፦ ዋረን ደብልዩ ዌርዝ ቢ፤ ተስማማ፤ ገጽ 96-98
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የእግዚአብሔር ጽድቅ (9:14-18)
እግዚአብሔር አንዱን መርጦ ሌላውን መተዉ ዐመፀኛ መሆኑን የሚያመለክት ይመስላል፡፡ «በእግዚአብሔር ዘንድ ዐመፃ አለ ወይ?» ብሎ ጳውሎስ ጠይቋል:: ራሱ «አይደለም» ብሎ መልስ ይሰጣል፡፡ ቅዱስ እግዚአብሔር ዐመፅ ያደርጋል ማለት የማይታሰብ ነገር ነው:: ምርጫ የጸጋ ጉዳይ ነው፡፡ እግዚአብሔር ነገርን ሁሉ እንደ ጽድቃችን ቢሰጠን ኖሮ፣ ማንም አይድንም ነበር፡፡ ጳውሎስ ዘጸአት 33:19 ጠቅሶ የእግዚአብሔር ምሕረትና ርኅራኄ የሚቀጥሉት እንደ ሰው ፈቃድ ሳይሆን፣ እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ መሆኑን አሳይቷል:: ሁላችንም ምሕረት ሳይሆን፣ ፍርድ የተገባን ነበርን፡፡ ዘጸአት 33 የሚናገረው ሙሴ በተራራው ላይ ሕግጋተ እግዚአብሔርን ሲቀበል እስራኤላውያን ስለማመንዘራቸው ነው፡፡ ሕዝብ ሁሉ መሞት ሲገባቸው፣ እግዚአብሔር የቀሰፈው ግን 3,000 ሰዎችን ብቻ ነው:: ያልሞቱት ቅዱሳን ስለሆኑ ወይም የሞቱት ከእነርሱ የባሱ ክፉና ርኩሳን ስለሆኑ ሳይሆን፣ በምሕረቱና በጸጋው ነው::
ጳውሎስ ዘጸአት 9:16 በመጥቀስ ፈርዖንን እንደ ምሳሌ አቅርቧል:: ሙሴ አይሁድ ነበር፣ ፈርዖን ደግሞ አረማዊ፣ ነገር ግን ሁለቱም ኃጢአተኞች ነበሩ፡፡ ሁለቱም ነፍሰ ገዳዮች ነበሩ፡፡ ሁለቱም የእግዚአብሔርን ተአምራት አይተዋል፡፡ ሙሴ ሲድን፣ ፈርዖን ግን ጠፋ፡፡ እግዚአብሔር ፈርዖንን ያስነሣው ክብሩንና ኃይሉን ሊገልጥ ነው:: ሙሴን ደግሞ የማረው ሕዝቡን እስራኤልን ነፃ እንዲያወጣ ነው፡፡ ፈርዖን ገዥ ነው፣ ሙሴ ደግሞ ባሪያ ነበር፡፡ ነገር ግን የእግዚአብሔርን ምሕረትና ርኅራኄ የተለማመደው ሙሴ ነው ምክንያቱም እግዚአብሔር እንዲህ እንዲሆን ፈቀደ፡፡ እግዚአብሔር ሉዓላዊ ስለሆነ በሥራውና በአደራረጉ እንደ ፈቀዱና እንደ ዓላማው ያደርጋል፡፡ ነገሩ የጽድቅ ጉዳይ ሳይሆን፣ ልዑል የሆነው የእግዚአብሔር ፈቃድ ጉዳይ ነው፡፡
እግዚአብሔር ቅዱስ ነውና ኃጢአትን ሊቀጣ ይገባዋል፡፡ ነገር ግን እግዚአብሔር አፍቃሪና ኃጢአተኞችን ለማዳን መሻት ያለው አምላክ ነው:: ሰው ሁሉ ቢድን፣ ቅድስናውን መካዱ ነው፤ ሰው ሁሉ ቢጠፋ ደግሞ፣ ፍቅሩን ሊክድ ነው፡፡ መፍትሔው የእግዚአብሔር ሉዓላዊ ምርጫ ነው፡፡
እግዚአብሔር እስራኤልን መርጦ ግብፅን ኮነነ፣ ሉዓላዊ፣ ዓላማው ይህ ነበርና፡፡ እግዚአብሔር ጻድቅ ስለሆነ፣ ምሕረቱን በምን መንገድ እንደሚሰጥ ማንም ሊጠይቅ አይችልም፡፡
ይህን ክፍል ስንጨርስ ስለ ፈርዖን ልብ «መደንደን» እንነጋገራለን (ቁ. 18)። «የልብ መደንደን» ሂደት ከዘጸአት 7-14 ድረስ 15 ጊዜ ተጠቅሷል፡፡ አንዳንድ ጊዜ ፈርዖን ልቡን እንዳደነደነ ተነግሮናል (ዘጸ. 8:15፣19፣32)፣ በሌላ ጊዜ ደግሞ እግዚአብሔር የፈርዖንን ልብ እንዳደነደነ ተጽፎአል (ዘጸ. 9:12፤10:1፣20፣27)፡፡ ቃሉን በማወጅና ኃይሉን በመግለጥ ፈርዖን ንስሐ እንዲገባ ዕድል ቢሰጠውም፣ እርሱ ግን እግዚአብሔርን በመቋቋም ልቡን አደነደነ:: ችግሩ ያለው በእግዚአብሔር ዘንድ ሳይሆን፣ በፈርዖን ላይ ነው:: በረዶን የሚያቀልጥ የፀሐይ ብርሃን ሽክላን ያደርቃል፡፡ እግዚአብሔር ፈርዖንን በንስሐ ገብቶ እንዲያምን ዕድል ስለሰጠው፣ እግዚአብሔር ዐመፀኛ አልነበረም፡፡
ይቀጥላል...
ምንጭ፦ ዋረን ደብልዩ ዌርዝ ቢ፤ ተስማማ፤ ገጽ 96-98
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤4👍1
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ስለ ንፍታሌምም እንዲህ አለ፦ ንፍታሌም በሞገስ ጠግቦአል፥ የእግዚአብሔርንም በረከት ተሞልቶአል፤ ባሕሩንና ደቡቡን ይወርሳል።”
ዘዳግም 33፥23
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ስለ ንፍታሌምም እንዲህ አለ፦ ንፍታሌም በሞገስ ጠግቦአል፥ የእግዚአብሔርንም በረከት ተሞልቶአል፤ ባሕሩንና ደቡቡን ይወርሳል።”
ዘዳግም 33፥23
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤6🔥1
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ለጢሞቴዎስ እና ለቲቶ መልእክታተ ምጋቤ ሲልክ፣ ሁለቱ መጋቢዎች የት ከተማ ነበሩ?
Anonymous Quiz
12%
ሀ. ጢሞቴዎስ፦ ሮም፣ ቲቶ፦ ቆሮንቶስ
21%
ለ. ጢሞቴዎስ፦ ኤፌሶን፣ ቲቶ፦ ቆሮንቶስ
41%
ሐ. ጢሞቴዎስ፦ ኤፌሶን፣ ቲቶ፦ ቀርጤስ
8%
መ. ጢሞቴዎስ፦ ቆሮንቶስ ፣ ቲቶ፦ ሮም
18%
ሠ. ጢሞቴዎስ፦ መቄዶንያ ፣ ቲቶ፦ ቆሮንቶስ
👍6🔥2
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“የዔሊም ልጆች ምናምንቴዎች ነበሩ፤ እግዚአብሔርንም አያውቁም ነበር።”
1ኛ ሳሙኤል 2፥12
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“የዔሊም ልጆች ምናምንቴዎች ነበሩ፤ እግዚአብሔርንም አያውቁም ነበር።”
1ኛ ሳሙኤል 2፥12
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍3❤2
#የእግዚአብሔር_ቃል_ምን_ይላል?
ገላትያ 2
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ ከዚያ ወዲያ ከአሥራ አራት ዓመት በኋላ ከበርናባስ ጋር ቲቶን ደግሞ ይዤ ወደ ኢየሩሳሌም ሁለተኛ ወጣሁ፤
² እንደ ተገለጠልኝም ወጣሁ፤ ምናልባትም በከንቱ እንዳልሮጥ ወይም በከንቱ ሮጬ እንዳልሆን በአሕዛብ መካከል የምሰብከውን ወንጌል አስታወቅኋቸው፤ ዋኖች ግን መስለው ለሚታዩ ለብቻቸው አስታወቅኋቸው።
³ ነገር ግን ከእኔ ጋር የነበረ ቲቶ እንኳ የግሪክ ሰው ሲሆን ይገረዝ ዘንድ ግድ አላሉትም፤
⁴ ነገር ግን ባሪያዎች ሊያደርጉን በክርስቶስ ኢየሱስ ያለንን አርነታችንን ይሰልሉ ዘንድ ሾልከው በስውር ስለ ገቡ ስለ ሐሰተኞች ወንድሞች ነበረ።
⁵ የወንጌልም እውነት በእናንተ ዘንድ ጸንቶ እንዲኖር ለአንድ ሰዓት እንኳ ለቅቀን አልተገዛንላቸውም።
⁶ አለቆች የመሰሉት ግን፥ በፊት ማን እንደ ነበሩ አይገደኝም፤ እግዚአብሔር የሰውን ፊት አይቶ አያደላም፤ አለቆች የመሰሉት አንዳች እንኳ አልጨመሩልኝምና፥
⁷ ተመልሰው ግን ጴጥሮስ ለተገረዙት የሆነው ወንጌል አደራ እንደ ተሰጠው እንዲሁ ለእኔ ላልተገረዙት የሆነው ወንጌል አደራ እንደ ተሰጠኝ አዩ፤
⁸ ለተገረዙት ሐዋርያ እንዲሆን ለጴጥሮስ የሠራለት፥ ለእኔ ደግሞ ለአሕዛብ ሐዋርያ እንድሆን ሠርቶአልና።
⁹ ደግሞ የተሰጠኝን ጸጋ አውቀው፥ አዕማድ መስለው የሚታዩ ያዕቆብና ኬፋ ዮሐንስም እኛ ወደ አሕዛብ እነርሱም ወደ ተገረዙት ይሄዱ ዘንድ ለእኔና ለበርናባስ ቀኝ እጃቸውን ሰጡን፤
¹⁰ ድሆችን እናስብ ዘንድ ብቻ ለመኑን፥ ይህንም ደግሞ ላደርግ ተጋሁ።
¹¹ ነገር ግን ኬፋ ወደ አንጾኪያ በመጣ ጊዜ ፊት ለፊት ተቃወምሁት፥ ይፈረድበት ዘንድ ይገባ ነበርና።
¹² አንዳንድ ከያዕቆብ ዘንድ ሳይመጡ ከአሕዛብ ጋር አብሮ ይበላ ነበርና፤ በመጡ ጊዜ ግን ከተገረዙት ወገን ያሉትን ፈርቶ ያፈገፍግ ነበርና ከእነርሱ ተለየ።
¹³ የቀሩትም አይሁድ ደግሞ፥ በርናባስ ስንኳ በግብዝነታቸው እስከ ተሳበ ድረስ፥ ከእርሱ ጋር አብረው ግብዞች ሆኑ።
¹⁴ ነገር ግን እንደ ወንጌል እውነት በቅንነት እንዳልሄዱ ባየሁ ጊዜ በሁሉ ፊት ኬፋን፦ አንተ አይሁዳዊ ሳለህ በአይሁድ ኑሮ ያይደለ በአሕዛብ ኑሮ ብትኖር፥ አሕዛብ በአይሁድ ኑሮ ሊኖሩ እንዴት ግድ አልሃቸው? አልሁት።
¹⁵ እኛ በፍጥረት አይሁድ ነን ኃጢአተኞችም የሆኑ አሕዛብ አይደለንም፤
¹⁶ ነገር ግን ሰው በኢየሱስ ክርስቶስ በማመን እንዲጸድቅ እንጂ በሕግ ሥራ እንዳይሆን አውቀን፥ ሥጋን የለበሰ ሁሉ በሕግ ሥራ ስለማይጸድቅ፥ እኛ ራሳችን በሕግ ሥራ ሳይሆን በክርስቶስ እምነት እንጸድቅ ዘንድ በክርስቶስ ኢየሱስ አምነናል።
¹⁷ ነገር ግን በክርስቶስ ልንጸድቅ የምንፈልግ ስንሆን ራሳችን ደግሞ ኃጢአተኞች ሆነን ከተገኘን፥ እንግዲያስ ክርስቶስ የኃጢአት አገልጋይ ነዋ? አይደለም።
¹⁸ ያፈረስሁትን ይህን እንደ ገና የማንጽ ከሆንሁ ራሴ ሕግ ተላላፊ እንድሆን አስረዳለሁና።
¹⁹ እኔ ለእግዚአብሔር ሕያው ሆኜ እኖር ዘንድ በሕግ በኩል ለሕግ ሞቼ ነበርና።
²⁰ ከክርስቶስ ጋር ተሰቅዬአለሁ፤ እኔም አሁን ሕያው ሆኜ አልኖርም ክርስቶስ ግን በእኔ ይኖራል፤ አሁንም በሥጋ የምኖርበት ኑሮ በወደደኝና ስለ እኔ ራሱን በሰጠው በእግዚአብሔር ልጅ ላይ ባለ እምነት የምኖረው ነው።
²¹ የእግዚአብሔርን ጸጋ አልጥልም፤ ጽድቅስ በሕግ በኩል ከሆነ እንኪያስ ክርስቶስ በከንቱ ሞተ።
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ገላትያ 2
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ ከዚያ ወዲያ ከአሥራ አራት ዓመት በኋላ ከበርናባስ ጋር ቲቶን ደግሞ ይዤ ወደ ኢየሩሳሌም ሁለተኛ ወጣሁ፤
² እንደ ተገለጠልኝም ወጣሁ፤ ምናልባትም በከንቱ እንዳልሮጥ ወይም በከንቱ ሮጬ እንዳልሆን በአሕዛብ መካከል የምሰብከውን ወንጌል አስታወቅኋቸው፤ ዋኖች ግን መስለው ለሚታዩ ለብቻቸው አስታወቅኋቸው።
³ ነገር ግን ከእኔ ጋር የነበረ ቲቶ እንኳ የግሪክ ሰው ሲሆን ይገረዝ ዘንድ ግድ አላሉትም፤
⁴ ነገር ግን ባሪያዎች ሊያደርጉን በክርስቶስ ኢየሱስ ያለንን አርነታችንን ይሰልሉ ዘንድ ሾልከው በስውር ስለ ገቡ ስለ ሐሰተኞች ወንድሞች ነበረ።
⁵ የወንጌልም እውነት በእናንተ ዘንድ ጸንቶ እንዲኖር ለአንድ ሰዓት እንኳ ለቅቀን አልተገዛንላቸውም።
⁶ አለቆች የመሰሉት ግን፥ በፊት ማን እንደ ነበሩ አይገደኝም፤ እግዚአብሔር የሰውን ፊት አይቶ አያደላም፤ አለቆች የመሰሉት አንዳች እንኳ አልጨመሩልኝምና፥
⁷ ተመልሰው ግን ጴጥሮስ ለተገረዙት የሆነው ወንጌል አደራ እንደ ተሰጠው እንዲሁ ለእኔ ላልተገረዙት የሆነው ወንጌል አደራ እንደ ተሰጠኝ አዩ፤
⁸ ለተገረዙት ሐዋርያ እንዲሆን ለጴጥሮስ የሠራለት፥ ለእኔ ደግሞ ለአሕዛብ ሐዋርያ እንድሆን ሠርቶአልና።
⁹ ደግሞ የተሰጠኝን ጸጋ አውቀው፥ አዕማድ መስለው የሚታዩ ያዕቆብና ኬፋ ዮሐንስም እኛ ወደ አሕዛብ እነርሱም ወደ ተገረዙት ይሄዱ ዘንድ ለእኔና ለበርናባስ ቀኝ እጃቸውን ሰጡን፤
¹⁰ ድሆችን እናስብ ዘንድ ብቻ ለመኑን፥ ይህንም ደግሞ ላደርግ ተጋሁ።
¹¹ ነገር ግን ኬፋ ወደ አንጾኪያ በመጣ ጊዜ ፊት ለፊት ተቃወምሁት፥ ይፈረድበት ዘንድ ይገባ ነበርና።
¹² አንዳንድ ከያዕቆብ ዘንድ ሳይመጡ ከአሕዛብ ጋር አብሮ ይበላ ነበርና፤ በመጡ ጊዜ ግን ከተገረዙት ወገን ያሉትን ፈርቶ ያፈገፍግ ነበርና ከእነርሱ ተለየ።
¹³ የቀሩትም አይሁድ ደግሞ፥ በርናባስ ስንኳ በግብዝነታቸው እስከ ተሳበ ድረስ፥ ከእርሱ ጋር አብረው ግብዞች ሆኑ።
¹⁴ ነገር ግን እንደ ወንጌል እውነት በቅንነት እንዳልሄዱ ባየሁ ጊዜ በሁሉ ፊት ኬፋን፦ አንተ አይሁዳዊ ሳለህ በአይሁድ ኑሮ ያይደለ በአሕዛብ ኑሮ ብትኖር፥ አሕዛብ በአይሁድ ኑሮ ሊኖሩ እንዴት ግድ አልሃቸው? አልሁት።
¹⁵ እኛ በፍጥረት አይሁድ ነን ኃጢአተኞችም የሆኑ አሕዛብ አይደለንም፤
¹⁶ ነገር ግን ሰው በኢየሱስ ክርስቶስ በማመን እንዲጸድቅ እንጂ በሕግ ሥራ እንዳይሆን አውቀን፥ ሥጋን የለበሰ ሁሉ በሕግ ሥራ ስለማይጸድቅ፥ እኛ ራሳችን በሕግ ሥራ ሳይሆን በክርስቶስ እምነት እንጸድቅ ዘንድ በክርስቶስ ኢየሱስ አምነናል።
¹⁷ ነገር ግን በክርስቶስ ልንጸድቅ የምንፈልግ ስንሆን ራሳችን ደግሞ ኃጢአተኞች ሆነን ከተገኘን፥ እንግዲያስ ክርስቶስ የኃጢአት አገልጋይ ነዋ? አይደለም።
¹⁸ ያፈረስሁትን ይህን እንደ ገና የማንጽ ከሆንሁ ራሴ ሕግ ተላላፊ እንድሆን አስረዳለሁና።
¹⁹ እኔ ለእግዚአብሔር ሕያው ሆኜ እኖር ዘንድ በሕግ በኩል ለሕግ ሞቼ ነበርና።
²⁰ ከክርስቶስ ጋር ተሰቅዬአለሁ፤ እኔም አሁን ሕያው ሆኜ አልኖርም ክርስቶስ ግን በእኔ ይኖራል፤ አሁንም በሥጋ የምኖርበት ኑሮ በወደደኝና ስለ እኔ ራሱን በሰጠው በእግዚአብሔር ልጅ ላይ ባለ እምነት የምኖረው ነው።
²¹ የእግዚአብሔርን ጸጋ አልጥልም፤ ጽድቅስ በሕግ በኩል ከሆነ እንኪያስ ክርስቶስ በከንቱ ሞተ።
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍3
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ልጆችም ስለ ሆናችሁ እግዚአብሔር አባ አባት ብሎ የሚጮኽ የልጁን መንፈስ በልባችሁ ውስጥ ላከ።”
ገላትያ 4፥6
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ልጆችም ስለ ሆናችሁ እግዚአብሔር አባ አባት ብሎ የሚጮኽ የልጁን መንፈስ በልባችሁ ውስጥ ላከ።”
ገላትያ 4፥6
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍4❤3
#እራሳችንን_እንመርምር
እግዚአብሔርን እንፈራዋለን? እናውቀዋለንስ? እግዚአብሔርን የሚፈራው ሰው ማን ነው? የሚያውቀዉስ? የማይፈሩት ምን አይነት ሰዎች ይሆናሉ?
“የዔሊም ልጆች ምናምንቴዎች ነበሩ፤ እግዚአብሔርንም አያውቁም ነበር።”
1ኛ ሳሙኤል 2፥12
“የዔሊ ልጆች ምናምንቴዎች ነበሩ፤ እግዚአብሔርንም አይፈሩም ነበር።”
1ኛ ሳሙኤል 2፥12 (አዲሱ መ.ት)
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
እግዚአብሔርን እንፈራዋለን? እናውቀዋለንስ? እግዚአብሔርን የሚፈራው ሰው ማን ነው? የሚያውቀዉስ? የማይፈሩት ምን አይነት ሰዎች ይሆናሉ?
“የዔሊም ልጆች ምናምንቴዎች ነበሩ፤ እግዚአብሔርንም አያውቁም ነበር።”
1ኛ ሳሙኤል 2፥12
“የዔሊ ልጆች ምናምንቴዎች ነበሩ፤ እግዚአብሔርንም አይፈሩም ነበር።”
1ኛ ሳሙኤል 2፥12 (አዲሱ መ.ት)
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍4❤2
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ባሪያዬ ሙሴ ሞቶአል፤ አሁንም አንተና ይህ ሕዝብ ሁሉ ተነሥታችሁ ለእስራኤል ልጆች ወደምሰጣቸው ምድር ይህን ዮርዳኖስ ተሻገሩ።”
ኢያሱ 1፥2
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ባሪያዬ ሙሴ ሞቶአል፤ አሁንም አንተና ይህ ሕዝብ ሁሉ ተነሥታችሁ ለእስራኤል ልጆች ወደምሰጣቸው ምድር ይህን ዮርዳኖስ ተሻገሩ።”
ኢያሱ 1፥2
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍5❤3
shoes-2.pdf
1.5 MB
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
shoes-1.pdf
1.4 MB
👉ርዕስ፦ ካርቦን-ኮፒ ክርስትና፣ ሌላውን ከመምሰል ኢየሱስን እንምሰል
✍️ጸሐፊ፦ ዶ/ር መለሰ ወጉ
📑የገጽ ብዛት፦ 299
📆የታተመበት ዓ.ም፦ 2005 ዓ.ም/ 2013 እ.ኤ.አ
✍️ጸሐፊ፦ ዶ/ር መለሰ ወጉ
📑የገጽ ብዛት፦ 299
📆የታተመበት ዓ.ም፦ 2005 ዓ.ም/ 2013 እ.ኤ.አ
❤10👍4
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ነገር ግን ኢየሱስ እርሱ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆነ ታምኑ ዘንድ፥ አምናችሁም በስሙ ሕይወት ይሆንላችሁ ዘንድ ይህ ተጽፎአል።”
ዮሐንስ 20፥31
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ነገር ግን ኢየሱስ እርሱ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆነ ታምኑ ዘንድ፥ አምናችሁም በስሙ ሕይወት ይሆንላችሁ ዘንድ ይህ ተጽፎአል።”
ዮሐንስ 20፥31
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤4👍2
የቀጠለ...
መጽሐፍ ቅዱስ የእግዚአብሔር ቃል
4. የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት።
የመጽሐፍ ቅዱስ ከሰው እውቀት በላይ የሆነ ባሕርይ የሚታየው፥ ሊታወቅ የማይቻልን እውነት ግልጥና እንዲታወቅ አድርጎ ማቅረቡ ነው። ዘላለምን ማለት ሰው ከመፈጠሩ በፊት የነበረውን ተፈጥሮ ሳይቀር ይገልጣል። የእግዚኣብሔር ባሕርይና ሥራዎቹም ተገልጠውበታል፡፡ እግዚኣብሔር ለዓለም፥ ለእስራኤልና ቤተ ክርስቲያን ያለው አሳብና ዘላለማዊ ዕቅዱ፥ መጽሐፍ ቅዱሳዊው ትንቢት ውስጥ ተጠቃሏል። በማንኛውም ጉዳይ ላይ የሚሰጠው ገለጣ የመጨረሻ፥ ትክክልና ጊዜ የማይገድበው ነው። ሁለንተናዊ ባሕርይው አንባቢዎቹን ከጊዜና ከዘላለም ጋር በተዛመደ ነገር ብልሆች አድርጓቸዋል።
5. መጽሐፍ ቅዱስ ስነ-ጽሑፍነቱ።
በሥነ-ጽሑፍነቱ ሲታይ፥ መጽሐፍ ቅዱስ ምጡቅ ነው። ታሪካዊ ዘገባዎችን ብቻ ሳይሆን፥ ዝርዝር ትንቢቶችን፥ ውብ የሆኑ ቅኔዎችን፥ ልዩ ውበት ያለው ተውኔትን፥ የፍቅርና የጦርነት ታሪኮችን፥ በመጽሐፍ ቅዱሳዊው እውነት ላይ የሚነሡ ፍልስፍናዎችን ያጠቃልላል። የጸሐፊዎቹ መለያየት ከያዛቸው ጉዳዮች ስብጥር ብዛት ጋር ይስማማል። እንደ መጽሐፍ ቅዱስ በዘመናት የኖሩትንና በሁሉም የእውቀት ደረጃ ላይ የነበሩትን ሰዎች የማረከ ጽሑፍ የለም።
6. የማያዳላው የመጽሐፍ ቅዱስ ሥልጣን።
መጽሐፍ ቅዱስ በሰዎች መጻፉ ለሰዎች እንዲያደላ አላደረገውም። ያለማመንታት የማንንም ኃጢአት እና ደካማነት ይገልጣል። ይህ ብቻ አይደለም፥ በራሳቸው በጎ ምግባር የሚታመኑ ፍጻሜያቸው ጥፋት መሆኑንም ያስገነዝባል። በሰዎች ብዕር ቢጻፍም፥ ከሰው ወደ ሰው ሳይሆን፥ ከእግዚአብሔር ወደ ሰው የተላለፈ መልእክት ነው። ስለ ምድራዊ ነገሮችና ስለ ሰዎች ልምምድ ቢገልጥም፥ የሰማይና የምድርን፥ የሚታዩና የማይታዩ ነገሮችን፥ ስለ እግዚአብሔር የሚገልጡ እውነቶችን፥ ስለ መላእክት፥ ስለ ሰው፥ ስለ ጊዜና ዘላለም፥ ስለ ሞትና ሕይወት፥ ስለ ኃጢአትና ድነት፥ ስለ መንግሥተ ሰማያትና ሲኦልም በግልጥነትና በሥልጣን ያብራራል። እንዲህ ያላን መጽሐፍ ሰው መጻፍ ቢፈልግ እንኳን፥ ያለመለኮታዊ ምሪት ሊጽፈው አይችልም ነበር። ስለዚህ መጽሐፍ ቅዱስ፥ ሰሰው ቢጻፍም፥ እግዚአብሔር ብቻ ከሚሰጠው እርግጠኛነት፥ ዋስትና እና ሠላም ጋር ከርሱ የተላከ ነው።
7. የመጽሐፍ ቅዱስ ሉዓላዊ ባሕርይ።
መጽሐፍ ቅዱስ፥ ከሁሉም ይልቅ እግዚአብሔር በልጁ በኩል እራሱን መግለጡን ያመለከተ፥ አካልነቱንና ክብሩን ያስገነዘበ ታላቅ መጽሐፍ ነው። እንደ ኢየሱስ ያለው ሰብእና የሟች ሰው ፈጠራ ሊሆን አይችልም፤ ምክንያቱም ፍጹምነቱ ከሁሉ የላቀ እንዲሁም ቅድስናና ጥበብ ያለው በመሆኑ የዚህ ምድር ሰው የሚገነዘበው አልነበረም። የመጽሐፍ ቅዱስ ዋና ባሕርይ የኢየሱስ ክርስቶስን ታላቅ ታሪክ በመግለጥ ተረጋግጧል።
መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ከተካተቱት ሰብአዊና ከሰብአዊነት በላይ በሆኑ ባሕርያት ኅብረት የተነሣ፥ የተጻፈ ቃል በሆነው መጽሐፍ ቅዱስና፥ ሕያው ቃል በሆነው ኢየሱስ ክርስቶስ መካከል ተመሳሳይነት ይታይ ይሆናል። ሁለቱም ከመሠረታቸው መለኮታዊ ናቸው። በመሆናቸውም የመለኮትንና የሰውን ምስጢራዊና ፍጹም ግንኙነት ይገልጣሉ። ሁለቱም በሚያምኑ ሰዎች ሕይወት ውስጥ የሚሠራ የመለወጥ ኃይል ያላቸው ሲሆን፥ የማያምኑ ሰዎችን ደግሞ እንዳይቀበሷቸው በሚፈልግ ፈቃዳቸው እንዲቀጥሉ እግዚአብሔር ትቷቸዋል። በሁለቱም ውስጥ የማይበከለውና የማይሻረው መለኮታዊ ፍጹምነት አለ። የሚገልጿቸው እውነቶች የሕፃን አእምሮ በሚገነዘበው ደረጃ ቀላል ናቸው። ያንኑ ያህል፥ ፍጻሜ የሌለው የመለኮታዊው ጥበብ እንዲሁም እውቀት ሀብቶች ሲሆኑ፥ እንደፈጠራቸው እንደ እግዚአብሔር ዘላለማዊ ናቸው።
ምንጭ፡- “ዋና ዋና የመጽሐፍ ቅዱስ ጭብጦች” መጽሐፍ በዶክተር ሉዊስ ስፔሪ ቼፈር የተጻፈ እና በተክሉ መንገሻ የተተረጎመ ነው፡፡
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
መጽሐፍ ቅዱስ የእግዚአብሔር ቃል
4. የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት።
የመጽሐፍ ቅዱስ ከሰው እውቀት በላይ የሆነ ባሕርይ የሚታየው፥ ሊታወቅ የማይቻልን እውነት ግልጥና እንዲታወቅ አድርጎ ማቅረቡ ነው። ዘላለምን ማለት ሰው ከመፈጠሩ በፊት የነበረውን ተፈጥሮ ሳይቀር ይገልጣል። የእግዚኣብሔር ባሕርይና ሥራዎቹም ተገልጠውበታል፡፡ እግዚኣብሔር ለዓለም፥ ለእስራኤልና ቤተ ክርስቲያን ያለው አሳብና ዘላለማዊ ዕቅዱ፥ መጽሐፍ ቅዱሳዊው ትንቢት ውስጥ ተጠቃሏል። በማንኛውም ጉዳይ ላይ የሚሰጠው ገለጣ የመጨረሻ፥ ትክክልና ጊዜ የማይገድበው ነው። ሁለንተናዊ ባሕርይው አንባቢዎቹን ከጊዜና ከዘላለም ጋር በተዛመደ ነገር ብልሆች አድርጓቸዋል።
5. መጽሐፍ ቅዱስ ስነ-ጽሑፍነቱ።
በሥነ-ጽሑፍነቱ ሲታይ፥ መጽሐፍ ቅዱስ ምጡቅ ነው። ታሪካዊ ዘገባዎችን ብቻ ሳይሆን፥ ዝርዝር ትንቢቶችን፥ ውብ የሆኑ ቅኔዎችን፥ ልዩ ውበት ያለው ተውኔትን፥ የፍቅርና የጦርነት ታሪኮችን፥ በመጽሐፍ ቅዱሳዊው እውነት ላይ የሚነሡ ፍልስፍናዎችን ያጠቃልላል። የጸሐፊዎቹ መለያየት ከያዛቸው ጉዳዮች ስብጥር ብዛት ጋር ይስማማል። እንደ መጽሐፍ ቅዱስ በዘመናት የኖሩትንና በሁሉም የእውቀት ደረጃ ላይ የነበሩትን ሰዎች የማረከ ጽሑፍ የለም።
6. የማያዳላው የመጽሐፍ ቅዱስ ሥልጣን።
መጽሐፍ ቅዱስ በሰዎች መጻፉ ለሰዎች እንዲያደላ አላደረገውም። ያለማመንታት የማንንም ኃጢአት እና ደካማነት ይገልጣል። ይህ ብቻ አይደለም፥ በራሳቸው በጎ ምግባር የሚታመኑ ፍጻሜያቸው ጥፋት መሆኑንም ያስገነዝባል። በሰዎች ብዕር ቢጻፍም፥ ከሰው ወደ ሰው ሳይሆን፥ ከእግዚአብሔር ወደ ሰው የተላለፈ መልእክት ነው። ስለ ምድራዊ ነገሮችና ስለ ሰዎች ልምምድ ቢገልጥም፥ የሰማይና የምድርን፥ የሚታዩና የማይታዩ ነገሮችን፥ ስለ እግዚአብሔር የሚገልጡ እውነቶችን፥ ስለ መላእክት፥ ስለ ሰው፥ ስለ ጊዜና ዘላለም፥ ስለ ሞትና ሕይወት፥ ስለ ኃጢአትና ድነት፥ ስለ መንግሥተ ሰማያትና ሲኦልም በግልጥነትና በሥልጣን ያብራራል። እንዲህ ያላን መጽሐፍ ሰው መጻፍ ቢፈልግ እንኳን፥ ያለመለኮታዊ ምሪት ሊጽፈው አይችልም ነበር። ስለዚህ መጽሐፍ ቅዱስ፥ ሰሰው ቢጻፍም፥ እግዚአብሔር ብቻ ከሚሰጠው እርግጠኛነት፥ ዋስትና እና ሠላም ጋር ከርሱ የተላከ ነው።
7. የመጽሐፍ ቅዱስ ሉዓላዊ ባሕርይ።
መጽሐፍ ቅዱስ፥ ከሁሉም ይልቅ እግዚአብሔር በልጁ በኩል እራሱን መግለጡን ያመለከተ፥ አካልነቱንና ክብሩን ያስገነዘበ ታላቅ መጽሐፍ ነው። እንደ ኢየሱስ ያለው ሰብእና የሟች ሰው ፈጠራ ሊሆን አይችልም፤ ምክንያቱም ፍጹምነቱ ከሁሉ የላቀ እንዲሁም ቅድስናና ጥበብ ያለው በመሆኑ የዚህ ምድር ሰው የሚገነዘበው አልነበረም። የመጽሐፍ ቅዱስ ዋና ባሕርይ የኢየሱስ ክርስቶስን ታላቅ ታሪክ በመግለጥ ተረጋግጧል።
መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ከተካተቱት ሰብአዊና ከሰብአዊነት በላይ በሆኑ ባሕርያት ኅብረት የተነሣ፥ የተጻፈ ቃል በሆነው መጽሐፍ ቅዱስና፥ ሕያው ቃል በሆነው ኢየሱስ ክርስቶስ መካከል ተመሳሳይነት ይታይ ይሆናል። ሁለቱም ከመሠረታቸው መለኮታዊ ናቸው። በመሆናቸውም የመለኮትንና የሰውን ምስጢራዊና ፍጹም ግንኙነት ይገልጣሉ። ሁለቱም በሚያምኑ ሰዎች ሕይወት ውስጥ የሚሠራ የመለወጥ ኃይል ያላቸው ሲሆን፥ የማያምኑ ሰዎችን ደግሞ እንዳይቀበሷቸው በሚፈልግ ፈቃዳቸው እንዲቀጥሉ እግዚአብሔር ትቷቸዋል። በሁለቱም ውስጥ የማይበከለውና የማይሻረው መለኮታዊ ፍጹምነት አለ። የሚገልጿቸው እውነቶች የሕፃን አእምሮ በሚገነዘበው ደረጃ ቀላል ናቸው። ያንኑ ያህል፥ ፍጻሜ የሌለው የመለኮታዊው ጥበብ እንዲሁም እውቀት ሀብቶች ሲሆኑ፥ እንደፈጠራቸው እንደ እግዚአብሔር ዘላለማዊ ናቸው።
ምንጭ፡- “ዋና ዋና የመጽሐፍ ቅዱስ ጭብጦች” መጽሐፍ በዶክተር ሉዊስ ስፔሪ ቼፈር የተጻፈ እና በተክሉ መንገሻ የተተረጎመ ነው፡፡
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤3👍2