' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“አብርሃም የተባለው ርስት አድርጎ ሊቀበለው ወዳለው ስፍራ ለመውጣት በእምነት ታዘዘ፥ ወዴትም እንደሚሄድ ሳያውቅ ወጣ።”
ዕብራውያን 11፥8
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“አብርሃም የተባለው ርስት አድርጎ ሊቀበለው ወዳለው ስፍራ ለመውጣት በእምነት ታዘዘ፥ ወዴትም እንደሚሄድ ሳያውቅ ወጣ።”
ዕብራውያን 11፥8
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤5👍1
#እራሳችንን_እንመርምር
መቼስ በእውነት እግዚአብሔርን የሚፈልግ እና የሚወድ በዘመኑም እግዚአብሔር ፈቃዱን እንዲፈጽም የሚሻ ሰው መሆንን እንፈልጋለን። እግዚአብሔር በታላቅ እጁ በዘመናችን ሁሉ ከእኛ ጋር እንዲሆንስ? ተገኝቶ ነው? የሚያስብል ነው። ታዲያ ይህ እንዲሆን ምን እናድርግ? ምንስ ከሕይወታችን ይወገድ?
“እነዚህም ጌታን ሲያመልኩና ሲጦሙ መንፈስ ቅዱስ፦ በርናባስንና ሳውልን ለጠራኋቸው ሥራ ለዩልኝ አለ።”
ሐዋርያት 13፥2
“ስለዚህ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ብትመለስ እመልስሃለሁ በፊቴም ትቆማለህ፤ የከበረውንም ከተዋረደው ብትለይ እንደ አፌ ትሆናለህ፤ እነርሱ ወደ አንተ ይመለሳሉ፥ አንተ ግን ወደ እነርሱ አትመለስም።”
ኤርምያስ 15፥19
“የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ በመንገዴ ብትሄድ ትእዛዜንም ብትጠብቅ፥ በቤቴ ላይ ትፈርዳለህ፥ አደባባዮቼንም ትጠብቃለህ፥ በዚህም ከቆሙት ከእነዚህ ጋር መግባትን እሰጣለሁ።”
ዘካርያስ 3፥7
“እንግዲህ ማንም ራሱን ከእነዚህ ከጠቀስኋቸው ነገሮች ቢያነጻ ለክቡር አገልግሎት የሚውል፣ የተቀደሰ፣ ለጌታው የሚጠቅም፣ ለመልካም ሥራም ሁሉ የተሰናዳ ዕቃ ይሆናል።”
2ኛ ጢሞቴዎስ 2፥21 (አዲሱ መ.ት)
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
መቼስ በእውነት እግዚአብሔርን የሚፈልግ እና የሚወድ በዘመኑም እግዚአብሔር ፈቃዱን እንዲፈጽም የሚሻ ሰው መሆንን እንፈልጋለን። እግዚአብሔር በታላቅ እጁ በዘመናችን ሁሉ ከእኛ ጋር እንዲሆንስ? ተገኝቶ ነው? የሚያስብል ነው። ታዲያ ይህ እንዲሆን ምን እናድርግ? ምንስ ከሕይወታችን ይወገድ?
“እነዚህም ጌታን ሲያመልኩና ሲጦሙ መንፈስ ቅዱስ፦ በርናባስንና ሳውልን ለጠራኋቸው ሥራ ለዩልኝ አለ።”
ሐዋርያት 13፥2
“ስለዚህ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ብትመለስ እመልስሃለሁ በፊቴም ትቆማለህ፤ የከበረውንም ከተዋረደው ብትለይ እንደ አፌ ትሆናለህ፤ እነርሱ ወደ አንተ ይመለሳሉ፥ አንተ ግን ወደ እነርሱ አትመለስም።”
ኤርምያስ 15፥19
“የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ በመንገዴ ብትሄድ ትእዛዜንም ብትጠብቅ፥ በቤቴ ላይ ትፈርዳለህ፥ አደባባዮቼንም ትጠብቃለህ፥ በዚህም ከቆሙት ከእነዚህ ጋር መግባትን እሰጣለሁ።”
ዘካርያስ 3፥7
“እንግዲህ ማንም ራሱን ከእነዚህ ከጠቀስኋቸው ነገሮች ቢያነጻ ለክቡር አገልግሎት የሚውል፣ የተቀደሰ፣ ለጌታው የሚጠቅም፣ ለመልካም ሥራም ሁሉ የተሰናዳ ዕቃ ይሆናል።”
2ኛ ጢሞቴዎስ 2፥21 (አዲሱ መ.ት)
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤6👍6
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ ቃሌን የሚጠብቅ ቢኖር ለዘላለም ሞትን አያይም።”
ዮሐንስ 8፥51
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ ቃሌን የሚጠብቅ ቢኖር ለዘላለም ሞትን አያይም።”
ዮሐንስ 8፥51
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤8👍3
የመጽሐፉ የገላትያ መልእክት ማብራሪያ ሲሆን መግቢያው እንደሚከተለው ይላል፦
የገላትያ መልእክት መግቢያ አደገኛ መጽሐፍ ነው። ይህ መጽሐፍ በዘመናችን ባሉት አብያተ ክርስቲያናት ዘንድ እውነተኛውን መንፈሳዊ ሕይወት በመተካት ላይ የሚገኘውን የሕግ አክራሪነት ዝንባሌ የሚያጋልጥ ነው። «በሐሰተኛ ትምህርቶች መካከል ያለ» ከማለት ይልቅ «በአብያተ ክርስቲያናት ዘንድ» ውስጥ ያልኩበት ዋናው ምክንያት በዚህ ዘመን ሕግ አክራሪነት የበለጠ የሰፈነው በቤተክርስቲያን ውስጥ ስለሆነ ነው።
በሚሊየን የሚቆጠሩ አማኞች አንዳንድ ድርጊቶችን ከመፈጸም በመቆጠባቸው ወይም አንድ የሃይማኖት መሪ በመከተላቸው ወይም የአንድ ቡድን አባል በመሆናቸው ብቻ «መንፈሳዊ» እንደሆኑ ያስባሉ። ዳሩ ግን ይህ ስሕተት መሆኑንና ወደ ትክክለኛው ሕይወት መምጣት የምንችለው ራሳችንን መንፈስ ቅዱስ እንዲቆጣጠረን በፈቀድንለት መጠን መሆኑን ጌታ በገላትያ መልእክት ውስጥ በግልፅ አሳይቶናል።
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የገላትያ መልእክት መግቢያ አደገኛ መጽሐፍ ነው። ይህ መጽሐፍ በዘመናችን ባሉት አብያተ ክርስቲያናት ዘንድ እውነተኛውን መንፈሳዊ ሕይወት በመተካት ላይ የሚገኘውን የሕግ አክራሪነት ዝንባሌ የሚያጋልጥ ነው። «በሐሰተኛ ትምህርቶች መካከል ያለ» ከማለት ይልቅ «በአብያተ ክርስቲያናት ዘንድ» ውስጥ ያልኩበት ዋናው ምክንያት በዚህ ዘመን ሕግ አክራሪነት የበለጠ የሰፈነው በቤተክርስቲያን ውስጥ ስለሆነ ነው።
በሚሊየን የሚቆጠሩ አማኞች አንዳንድ ድርጊቶችን ከመፈጸም በመቆጠባቸው ወይም አንድ የሃይማኖት መሪ በመከተላቸው ወይም የአንድ ቡድን አባል በመሆናቸው ብቻ «መንፈሳዊ» እንደሆኑ ያስባሉ። ዳሩ ግን ይህ ስሕተት መሆኑንና ወደ ትክክለኛው ሕይወት መምጣት የምንችለው ራሳችንን መንፈስ ቅዱስ እንዲቆጣጠረን በፈቀድንለት መጠን መሆኑን ጌታ በገላትያ መልእክት ውስጥ በግልፅ አሳይቶናል።
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍7
arnet-1-cr.pdf
1.8 MB
የገላትያ መልእክት
📔ርዕስ፦ አርነት መውጣት
👤ጸሐፊ፦ዋረን ደብልዩ ዌርዝቢ
🗣ተርጓሚ፦ጌቱ ግዛው
📑የገጽ ብዛት፦140
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📔ርዕስ፦ አርነት መውጣት
👤ጸሐፊ፦ዋረን ደብልዩ ዌርዝቢ
🗣ተርጓሚ፦ጌቱ ግዛው
📑የገጽ ብዛት፦140
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍6
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“እነርሱም ወዲያው ታንኳይቱንና አባታቸውን ትተው ተከተሉት።”
ማቴዎስ 4፥22
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“እነርሱም ወዲያው ታንኳይቱንና አባታቸውን ትተው ተከተሉት።”
ማቴዎስ 4፥22
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤3👍1👏1
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ወዳጅ ሆይ፥ በጎ የሆነውን እንጂ ክፉን አትምሰል። በጎ የሚያደርግ ከእግዚአብሔር ነው፤ ክፉን የሚያደርግ ግን እግዚአብሔርን አላየውም።”
3ኛ ዮሐንስ 1፥11
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ወዳጅ ሆይ፥ በጎ የሆነውን እንጂ ክፉን አትምሰል። በጎ የሚያደርግ ከእግዚአብሔር ነው፤ ክፉን የሚያደርግ ግን እግዚአብሔርን አላየውም።”
3ኛ ዮሐንስ 1፥11
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤3👍3
1ኛ ሳሙኤል 3
ይህ ምዕራፍ እንደሚከተለው ይጀምራል፦
“ብላቴናውም ሳሙኤል በዔሊ ፊት እግዚአብሔርን ያገለግል ነበር፤ በዚያም ዘመን የእግዚአብሔር ቃል ብርቅ ነበረ፤ ራእይም አይገለጥም ነበር።” (ቁ. 1)
ሲደመድም፦
“እግዚአብሔርም ደግሞ በሴሎ ተገለጠ፤ እግዚአብሔርም በእግዚአብሔር ቃል ለሳሙኤል በሴሎ ይገለጥ ነበር። የሳሙኤልም ቃል ለእስራኤል ሁሉ ደረሰ።” (ቁ. 21)
ለመሆኑ በእነዚህ ቁጥሮች መካከል ምን ለውጥ እንመለከታለን?
1. የእግዚአብሔር ቃል ብርቅ ነበረ(ቁ.1) እና ለሳሙኤል የእግዚአብሔር ቃል ይገለጥ ነበር (ቁ. 21)
2. ራእይም አይገለጥም ነበር (ቁ. 1) እና እግዚአብሔር ደግሞ በሴሎ ተገለጠ (ቁ. 21)
ታዲያ ይህ ለውጥ እንዴት ተከሰተ? ከሳሙኤል ሕይወት ምን እንማራለን?
1. ምንም የሚታይ ነገር በሌለበት እግዚአብሔርን በታማኝነት ያገለግል ነበር። (ቁ.1)
2. ሳሙኤል እግዚአብሔር ባለበት ይገኛል(ቁ. 3)
3. ቅን ነበር። ኤሊ ምንም ያህል ለእግዚአብሔር ቤት የሚቀና ባይሆንም ይታዘዘው፣ ይሰማው እና እግዚአብሔር ላስቀመጠው ታላቅን የማክበር ትእዛዝ ተገዢ ነበር። (ቁ. 5-9)
4. የኤሊ ልጆች በክፋት የተሞሉ ቢሆኑም ሳሙኤል እራሱን በቅድስና የጠበቀ ሰው ነው። (ቁ. 13)
5. የእግዚአብሔርን እውነት ያለፍርሃት የሚናገር ሰው ነው። (ቁ. 18)
ውጤቱስ
1. እግዚአብሔር እና ቃሉ ተገለጠ። (ቁ. 21)
2. የሳሙኤል ቃል በምድር ላይ አይወድቅም ነበር (ቁ. 19)
3. ሕዝቡ ከእስራኤል ጫፍ እስከ ጫፍ ድረስ ለእግዚአብሔር ነቢይ ለመሆን የታመነ እንደሆነ አወቀ (ቁ. 20)
ነቢይ እንደሆነ እያወጀ አልሄደም። ነገር ግን ሕዝቡ ነቢይ ለመሆን የታመነ እንደሆነ መሰከሩለት።
✍በዘመናችን እግዚአብሔር እንዲገለጥ እንፈልጋለን? ከፈለግን በግል ሕይወታችን ይህን የሳሙኤልን ፈለግ እንከተል!
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ይህ ምዕራፍ እንደሚከተለው ይጀምራል፦
“ብላቴናውም ሳሙኤል በዔሊ ፊት እግዚአብሔርን ያገለግል ነበር፤ በዚያም ዘመን የእግዚአብሔር ቃል ብርቅ ነበረ፤ ራእይም አይገለጥም ነበር።” (ቁ. 1)
ሲደመድም፦
“እግዚአብሔርም ደግሞ በሴሎ ተገለጠ፤ እግዚአብሔርም በእግዚአብሔር ቃል ለሳሙኤል በሴሎ ይገለጥ ነበር። የሳሙኤልም ቃል ለእስራኤል ሁሉ ደረሰ።” (ቁ. 21)
ለመሆኑ በእነዚህ ቁጥሮች መካከል ምን ለውጥ እንመለከታለን?
1. የእግዚአብሔር ቃል ብርቅ ነበረ(ቁ.1) እና ለሳሙኤል የእግዚአብሔር ቃል ይገለጥ ነበር (ቁ. 21)
2. ራእይም አይገለጥም ነበር (ቁ. 1) እና እግዚአብሔር ደግሞ በሴሎ ተገለጠ (ቁ. 21)
ታዲያ ይህ ለውጥ እንዴት ተከሰተ? ከሳሙኤል ሕይወት ምን እንማራለን?
1. ምንም የሚታይ ነገር በሌለበት እግዚአብሔርን በታማኝነት ያገለግል ነበር። (ቁ.1)
2. ሳሙኤል እግዚአብሔር ባለበት ይገኛል(ቁ. 3)
3. ቅን ነበር። ኤሊ ምንም ያህል ለእግዚአብሔር ቤት የሚቀና ባይሆንም ይታዘዘው፣ ይሰማው እና እግዚአብሔር ላስቀመጠው ታላቅን የማክበር ትእዛዝ ተገዢ ነበር። (ቁ. 5-9)
4. የኤሊ ልጆች በክፋት የተሞሉ ቢሆኑም ሳሙኤል እራሱን በቅድስና የጠበቀ ሰው ነው። (ቁ. 13)
5. የእግዚአብሔርን እውነት ያለፍርሃት የሚናገር ሰው ነው። (ቁ. 18)
ውጤቱስ
1. እግዚአብሔር እና ቃሉ ተገለጠ። (ቁ. 21)
2. የሳሙኤል ቃል በምድር ላይ አይወድቅም ነበር (ቁ. 19)
3. ሕዝቡ ከእስራኤል ጫፍ እስከ ጫፍ ድረስ ለእግዚአብሔር ነቢይ ለመሆን የታመነ እንደሆነ አወቀ (ቁ. 20)
ነቢይ እንደሆነ እያወጀ አልሄደም። ነገር ግን ሕዝቡ ነቢይ ለመሆን የታመነ እንደሆነ መሰከሩለት።
✍በዘመናችን እግዚአብሔር እንዲገለጥ እንፈልጋለን? ከፈለግን በግል ሕይወታችን ይህን የሳሙኤልን ፈለግ እንከተል!
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍15❤4
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“እኔ ለእግዚአብሔር ሕያው ሆኜ እኖር ዘንድ በሕግ በኩል ለሕግ ሞቼ ነበርና።”
ገላትያ 2፥19
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“እኔ ለእግዚአብሔር ሕያው ሆኜ እኖር ዘንድ በሕግ በኩል ለሕግ ሞቼ ነበርና።”
ገላትያ 2፥19
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤6
bereket-1.pdf
1.9 MB
👉ርዕስ፦ በረከት ወይስ መርገም አንዱን ምረጥ!
✍️ደራሲ፦ ዴሬክ ፕሪንስ
📑የገጽ ብዛት፦ 200
✍️ደራሲ፦ ዴሬክ ፕሪንስ
📑የገጽ ብዛት፦ 200
bereket-2.pdf
2.1 MB
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤1
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ዕውሮችንም በማያውቋት መንገድ አመጣቸዋለሁ፥ በማያውቋትም ጎዳና እመራቸዋለሁ፤ በፊታቸውም ጨለማውን ብርሃን አደርጋለሁ፥ ጠማማውንም አቀናለሁ። ይህን አደርግላቸዋለሁ፥ አልተዋቸውምም።”
ኢሳይያስ 42፥16
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ዕውሮችንም በማያውቋት መንገድ አመጣቸዋለሁ፥ በማያውቋትም ጎዳና እመራቸዋለሁ፤ በፊታቸውም ጨለማውን ብርሃን አደርጋለሁ፥ ጠማማውንም አቀናለሁ። ይህን አደርግላቸዋለሁ፥ አልተዋቸውምም።”
ኢሳይያስ 42፥16
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤3👍2
ጌታችን እና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በምድር ላይ በነበረበት ወቅት ያስተዳድሩ የነበሩ ሄሮድሶች የምን ወገን ነበሩ?
Anonymous Quiz
38%
ሀ. ይሁዳ
5%
ለ. ኤሳው
3%
ሐ. ኤፍሬም
11%
መ. ኤዶም
13%
ሠ. ለ እና መ
12%
ረ. ሀ እና መ
18%
ሰ. መልስ የለም
👍4
ጌታችን እና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በየትኛው አውራጃ ተወልዶ በየትኛው አውራጃ አደገ?
Anonymous Quiz
59%
ሀ. ቤተልሔም እና ናዝሬት
7%
ለ. ይሁዳ እና ናዝሬት
8%
ሐ. ይሁዳ እና ገሊላ
27%
መ. ቤተልሔም እና ገሊላ
👍5
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“እርሱንና ቤቱን በዙሪያውም ያሉትን ሁሉ አላጠርህለትምን? የእጁን ሥራ ባርከህለታል፥ ከብቱም በምድር ላይ በዝቶአል።”
ኢዮብ 1፥10
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“እርሱንና ቤቱን በዙሪያውም ያሉትን ሁሉ አላጠርህለትምን? የእጁን ሥራ ባርከህለታል፥ ከብቱም በምድር ላይ በዝቶአል።”
ኢዮብ 1፥10
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤3👍2
#የሮሜ_መልእክት_ጥናት
ሮሜ 9፥6-13
6. እንግዲህ እስራኤል በመጀመሪያ ይህን ያህል የተባረከ ሕዝብ ከነበረ፥ በኋላ ምን ነካው? አይሁዳውያን ለምን ደኅንነትን ሳያገኙ ቀሩ? የእግዚአብሔር የተስፋ ቃል ማለትም የእግዚአብሔር ቃል ተሻረባቸው ወይስ ተሰበረ? ይህ ሁሉ በጭራሽ አልሆነባቸውም! እግዚአብሔር ለእስራኤል የሰጠውን ተስፋ አላጠፈውም። ነገር ግን እነዚያ ሁሉ ተስፋዎች፥ ማለትም አዳኝ የመላክ ተስፋ፥ የደኅንነት ተስፋ፥ ለእውነተኞች አይሁዳውያን ተሰጥተዋል። ጳውሎስ ራሳቸውን አይሁዳውያን ብለው የሚጠሩ ሁሉ እውነተኞች አይሁዳውያን አይደሉም ብሎአል (ሮሜ 2፥28-29 ይመለከቷል)። የእስራኤል ዝርያዎች ሁሉ በትውልድ አይሁዳዊ የሆኑት) እስራኤላዊ (እውነተኞች አይሁዳውያን) አይደሉም።
ስለዚህ እግዚኣብሔር ለአይሁዳውያን የሰጠው ተስፋ አልተሻረም። ምክንያቱም ከአይሁዳውያን ብዙዎቹ «እውነተኞች አይሁዳውያን» አልነበሩም። እውነተኞች አይሁዳውያን በኢየሱስ የሚያምኑ አይሁዳውያን ብቻ ናቸው። በቁ. 8 ላይ ጳውሎስ በተፈጥሮ አይሁዳውያንና (በትውልድ የአብርሃም ዘር የሆኑ) የተስፋው ልጆች በሆኑ አይሁዳውያን (በተስፋው ማለት በኢየሱስ ያመኑ አይሁዳውያን) መካከል ያለውን ልዩነት ይናገራል። «የተስፋው ልጆች» የሆኑት ማለትም በክርስቶስስ ኢየሱስ ያመኑ እውነተኛ አይሁዳውያን፥ የእግዚአብሔር ተስፋ የተፈጸመላቸው ለእነርሱ ብቻ ነው (ሮሜ 4፥11-17)፡፡
«የተስፋው ልጆች» በእምነት ጻድቃን ለመሆን የሚፈልጉ ናቸው። «በሥጋ የተወለዱት» ደግሞ በራሳቸው ጥረትና በመልካም ሥራ ጻድቃን ለመሆን የሚፈልጉት ናቸው (ሮሜ 9፥32፤ ገላ. 3፥6-9)፡፡
7-9. በሥጋ የተወለዱ ልጆች (በመወለድ ዝርያዎች) የሆኑ ሁሉ የውርስ ተስፋ መቀበል እንደሌለባቸው ለማሳየት ጳውሎስ የአብርሃምን ምሳሌነት ይጠቅሳል። አብርሃም ሁለት «ከእርሱ የተወለዱ ልጆች» ነበሩት። እነርሱም ይስሐቅና እስማኤል ናቸው። ነገር ግን ከሁለቱ አንዱ ማለትም ይስሐቅ ብቻ ነው የአብርሃም እውነተኛ ልጅ፤ ውርስ ያገኘውም ይስሐቅ ብቻ ነበር። አብርሃም በመጀመሪያ ከሚስቱ ገረድ የወለደው እስማኤልን ቢሆንም (ዘፍ. 16፥1-4፥ 15-16) የእስማኤል ዝርያዎች ግን አይሁዳውያን አልነበሩም። አይሁዳውያን የመጡት አብርሃም ከሚስቱ ከሳራ ካገኘው ከሁለተኛ ልጁ ክይስሐቅ ነው። ይህ ልጅ እግዚአብሔር ለአብርሃም እስጥሃለሁ ብሎ ተስፋ የገባለት ነበር (ዘፍ. 18:14 ፤ 2፥1-13፤ ገላ. 4፥22-23)። እግዚአብሔር እውነተኛ ዝርያዎችን በመወለድ ብቻ አይቆጥርም። በእግዚአብሔር ፊት እውነተኛ ዝርያዎች በእግዚአብሔር ተስፋ መሠረት የሚመጡት ናቸው። ይህም በእምነት በኩል የሚመጡት ማለት ነው። አብርሃም በእግዚአብሔር ተስፋ በማመኑ ምክንያት ነበር እግዚአብሔር አብርሃምንና ሳራን በልጅ የባረካቸው።
እዚህ ላይ የጳውሎስ ዋና ነጥብ በመወለድ የአብርሃም የሥጋ ልጆች በመሆናቸው ብቻ አይሁዳውያን የእግዚአብሔር ልጆች ነን ሊሉ አለመቻላቸውን ነው። የእግዚአብሔር እውነተኛ ልጆች የተስፋው ልጆች ብቻ ናቸው። የአብርሃም ዝርያዎች ተብለው የሚታወቁት ወይም በሌላ መንገድ ለማየት፥ እውነተኛ አይሁዳውያን የሚባሉት የእምነት ልጆች እንጂ የሥጋ ልጆች አይደሉም። ስለሆነም እውነተኞቹ የአብርሃም ዝርያዎች በክርስቶስ ያመኑት ብቻ ናቸው። አይሁዳውያን (በትውልድ) ክርስቶስን አንቀበለውም ባሉት ጊዜ፥ ራሳቸውን ናቁ፥ ውርሳቸውንም አጠፉ፥ በእግዚአብሔር ቤተሰብ ውስጥ የነበራቸውንም ክቡር ቦታ አጡ።
10-12. በእነዚህ ጥቅሶች ውስጥ እግዚአብሔር በሥጋ ትውልድ ብቻ እውነተኛ ወራሾቹን እንደማይመርጥ፥ ጳውሎስ ሁለተኛ ምሳሌውን ይሰጣል። የይስሐቅ ሚስት ርብቃ መንትያ ልጆችን ወለደች። በአይሁድ ባሕል መሠረት ከመንትዮቹ በመጀመሪያ የተወለደው ኤሳው የቤተሰቡን ውርስ የመቀበል መብት ነበረው። እግዚአብሔር ግን በራሱ ፈቃድ ውርሱ ከመንትያዎቹ ሁለተኛ ሆኖ ለተወለደው ለያዕቆብ እንዲሆን አደረገ(ዘፍ. 25፥20-26፤ 27፥1-35)።
እዚህ ላይ እግዚአብሔር ውርስን ከልደት የተነሣ እንደማይሰጥ እናያለን። ነገር ግን የሚሰጠው በራሱ ፈቃድ ነው። ይህም በመምረጥ ያለው ዓላማ ጸንቶ እንዲቆምለት ነው (ቁ. 11)። ገና ከመወለዱ በፊት እንኳ እግዚአብሔር ያዕቆብን መረጠው፤ ወይም የውርሱ ወራሽ እንዲሆን ሾመው። ያዕቆብ ለዚህ የተገባ ሆኖ እንዲገኝ መልካም ሥራን ለመሥራት ምንም ዓይነት አጋጣሚ አልነበረውም፤ ጨርሶም ገና አልተወለደም ነበር። የእግዚአብሔር ምርጫ በሥራ ላይ የተመሠረተ አይደለም፤ ነገር ግን በራሱ በእግዚአብሔር የበላይነት ፈቃዱ ላይ ብቻ የተመሠረተ ነው። እግዚአብሔር የተገባን ስለሆንን አይመርጠንም፤ እርሱ የሚመርጠን ከጸጋው የተነሣ ብቻ ነው።
13. በዚህ መንገድ እግዚአብሔር ያዕቆብንና ዝርያዎቹን ወደደ (መረጠ)። ኤሳውንና ዝርያዎቹንም ጠላ (ናቀ) (ሚል. 1፥2-3)። ያዕቆብና ኤሳው ሁለቱም የይስሐቅ ልጆች ነበሩ፤ ነገር ግን ያዕቆብ ብቻ ውርስ ተቀበለ። እውነተኞቹ አይሁዳውያን ወይም እውነተኞቹ እስራኤላውያን የሚፈልቁት ከያዕቆብ ብቻ ሆነ።
ስለዚህ በዚህ ክፍል የጳውሎስ ዋና ትምህርት ይህ ነው፥ በልደት ብቻ አይሁዳውያን የሆኑትን ወይም በመልካም ሥራቸው ጻድቃን ለመሆን የሚፈልጉትን እግዚአብሔር አልመርጣቸውም፥ ልጆቹም አላደርጋቸውም። ይልቁንም እርሱ የመረጣቸው ጥሪውን ሰምተው እምነታቸውን በልጁ በኢየሱስ ላይ ያደረጉትን ብቻ ነው።
ምንጭ፦ የአዲስ ኪዳን ማብራሪያ፤ ገጽ 371-372
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ሮሜ 9፥6-13
6. እንግዲህ እስራኤል በመጀመሪያ ይህን ያህል የተባረከ ሕዝብ ከነበረ፥ በኋላ ምን ነካው? አይሁዳውያን ለምን ደኅንነትን ሳያገኙ ቀሩ? የእግዚአብሔር የተስፋ ቃል ማለትም የእግዚአብሔር ቃል ተሻረባቸው ወይስ ተሰበረ? ይህ ሁሉ በጭራሽ አልሆነባቸውም! እግዚአብሔር ለእስራኤል የሰጠውን ተስፋ አላጠፈውም። ነገር ግን እነዚያ ሁሉ ተስፋዎች፥ ማለትም አዳኝ የመላክ ተስፋ፥ የደኅንነት ተስፋ፥ ለእውነተኞች አይሁዳውያን ተሰጥተዋል። ጳውሎስ ራሳቸውን አይሁዳውያን ብለው የሚጠሩ ሁሉ እውነተኞች አይሁዳውያን አይደሉም ብሎአል (ሮሜ 2፥28-29 ይመለከቷል)። የእስራኤል ዝርያዎች ሁሉ በትውልድ አይሁዳዊ የሆኑት) እስራኤላዊ (እውነተኞች አይሁዳውያን) አይደሉም።
ስለዚህ እግዚኣብሔር ለአይሁዳውያን የሰጠው ተስፋ አልተሻረም። ምክንያቱም ከአይሁዳውያን ብዙዎቹ «እውነተኞች አይሁዳውያን» አልነበሩም። እውነተኞች አይሁዳውያን በኢየሱስ የሚያምኑ አይሁዳውያን ብቻ ናቸው። በቁ. 8 ላይ ጳውሎስ በተፈጥሮ አይሁዳውያንና (በትውልድ የአብርሃም ዘር የሆኑ) የተስፋው ልጆች በሆኑ አይሁዳውያን (በተስፋው ማለት በኢየሱስ ያመኑ አይሁዳውያን) መካከል ያለውን ልዩነት ይናገራል። «የተስፋው ልጆች» የሆኑት ማለትም በክርስቶስስ ኢየሱስ ያመኑ እውነተኛ አይሁዳውያን፥ የእግዚአብሔር ተስፋ የተፈጸመላቸው ለእነርሱ ብቻ ነው (ሮሜ 4፥11-17)፡፡
«የተስፋው ልጆች» በእምነት ጻድቃን ለመሆን የሚፈልጉ ናቸው። «በሥጋ የተወለዱት» ደግሞ በራሳቸው ጥረትና በመልካም ሥራ ጻድቃን ለመሆን የሚፈልጉት ናቸው (ሮሜ 9፥32፤ ገላ. 3፥6-9)፡፡
7-9. በሥጋ የተወለዱ ልጆች (በመወለድ ዝርያዎች) የሆኑ ሁሉ የውርስ ተስፋ መቀበል እንደሌለባቸው ለማሳየት ጳውሎስ የአብርሃምን ምሳሌነት ይጠቅሳል። አብርሃም ሁለት «ከእርሱ የተወለዱ ልጆች» ነበሩት። እነርሱም ይስሐቅና እስማኤል ናቸው። ነገር ግን ከሁለቱ አንዱ ማለትም ይስሐቅ ብቻ ነው የአብርሃም እውነተኛ ልጅ፤ ውርስ ያገኘውም ይስሐቅ ብቻ ነበር። አብርሃም በመጀመሪያ ከሚስቱ ገረድ የወለደው እስማኤልን ቢሆንም (ዘፍ. 16፥1-4፥ 15-16) የእስማኤል ዝርያዎች ግን አይሁዳውያን አልነበሩም። አይሁዳውያን የመጡት አብርሃም ከሚስቱ ከሳራ ካገኘው ከሁለተኛ ልጁ ክይስሐቅ ነው። ይህ ልጅ እግዚአብሔር ለአብርሃም እስጥሃለሁ ብሎ ተስፋ የገባለት ነበር (ዘፍ. 18:14 ፤ 2፥1-13፤ ገላ. 4፥22-23)። እግዚአብሔር እውነተኛ ዝርያዎችን በመወለድ ብቻ አይቆጥርም። በእግዚአብሔር ፊት እውነተኛ ዝርያዎች በእግዚአብሔር ተስፋ መሠረት የሚመጡት ናቸው። ይህም በእምነት በኩል የሚመጡት ማለት ነው። አብርሃም በእግዚአብሔር ተስፋ በማመኑ ምክንያት ነበር እግዚአብሔር አብርሃምንና ሳራን በልጅ የባረካቸው።
እዚህ ላይ የጳውሎስ ዋና ነጥብ በመወለድ የአብርሃም የሥጋ ልጆች በመሆናቸው ብቻ አይሁዳውያን የእግዚአብሔር ልጆች ነን ሊሉ አለመቻላቸውን ነው። የእግዚአብሔር እውነተኛ ልጆች የተስፋው ልጆች ብቻ ናቸው። የአብርሃም ዝርያዎች ተብለው የሚታወቁት ወይም በሌላ መንገድ ለማየት፥ እውነተኛ አይሁዳውያን የሚባሉት የእምነት ልጆች እንጂ የሥጋ ልጆች አይደሉም። ስለሆነም እውነተኞቹ የአብርሃም ዝርያዎች በክርስቶስ ያመኑት ብቻ ናቸው። አይሁዳውያን (በትውልድ) ክርስቶስን አንቀበለውም ባሉት ጊዜ፥ ራሳቸውን ናቁ፥ ውርሳቸውንም አጠፉ፥ በእግዚአብሔር ቤተሰብ ውስጥ የነበራቸውንም ክቡር ቦታ አጡ።
10-12. በእነዚህ ጥቅሶች ውስጥ እግዚአብሔር በሥጋ ትውልድ ብቻ እውነተኛ ወራሾቹን እንደማይመርጥ፥ ጳውሎስ ሁለተኛ ምሳሌውን ይሰጣል። የይስሐቅ ሚስት ርብቃ መንትያ ልጆችን ወለደች። በአይሁድ ባሕል መሠረት ከመንትዮቹ በመጀመሪያ የተወለደው ኤሳው የቤተሰቡን ውርስ የመቀበል መብት ነበረው። እግዚአብሔር ግን በራሱ ፈቃድ ውርሱ ከመንትያዎቹ ሁለተኛ ሆኖ ለተወለደው ለያዕቆብ እንዲሆን አደረገ(ዘፍ. 25፥20-26፤ 27፥1-35)።
እዚህ ላይ እግዚአብሔር ውርስን ከልደት የተነሣ እንደማይሰጥ እናያለን። ነገር ግን የሚሰጠው በራሱ ፈቃድ ነው። ይህም በመምረጥ ያለው ዓላማ ጸንቶ እንዲቆምለት ነው (ቁ. 11)። ገና ከመወለዱ በፊት እንኳ እግዚአብሔር ያዕቆብን መረጠው፤ ወይም የውርሱ ወራሽ እንዲሆን ሾመው። ያዕቆብ ለዚህ የተገባ ሆኖ እንዲገኝ መልካም ሥራን ለመሥራት ምንም ዓይነት አጋጣሚ አልነበረውም፤ ጨርሶም ገና አልተወለደም ነበር። የእግዚአብሔር ምርጫ በሥራ ላይ የተመሠረተ አይደለም፤ ነገር ግን በራሱ በእግዚአብሔር የበላይነት ፈቃዱ ላይ ብቻ የተመሠረተ ነው። እግዚአብሔር የተገባን ስለሆንን አይመርጠንም፤ እርሱ የሚመርጠን ከጸጋው የተነሣ ብቻ ነው።
13. በዚህ መንገድ እግዚአብሔር ያዕቆብንና ዝርያዎቹን ወደደ (መረጠ)። ኤሳውንና ዝርያዎቹንም ጠላ (ናቀ) (ሚል. 1፥2-3)። ያዕቆብና ኤሳው ሁለቱም የይስሐቅ ልጆች ነበሩ፤ ነገር ግን ያዕቆብ ብቻ ውርስ ተቀበለ። እውነተኞቹ አይሁዳውያን ወይም እውነተኞቹ እስራኤላውያን የሚፈልቁት ከያዕቆብ ብቻ ሆነ።
ስለዚህ በዚህ ክፍል የጳውሎስ ዋና ትምህርት ይህ ነው፥ በልደት ብቻ አይሁዳውያን የሆኑትን ወይም በመልካም ሥራቸው ጻድቃን ለመሆን የሚፈልጉትን እግዚአብሔር አልመርጣቸውም፥ ልጆቹም አላደርጋቸውም። ይልቁንም እርሱ የመረጣቸው ጥሪውን ሰምተው እምነታቸውን በልጁ በኢየሱስ ላይ ያደረጉትን ብቻ ነው።
ምንጭ፦ የአዲስ ኪዳን ማብራሪያ፤ ገጽ 371-372
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍4❤1
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“እንዲህም ሆነ ፈርዖን ሕዝቡን በለቀቀ ጊዜ፥ ምንም ቅርብ ቢሆን እግዚአብሔር በፍልስጥኤማውያን ምድር መንገድ አልመራቸውም፤ እግዚአብሔር፦ ሕዝቡ ሰልፉን ባየ ጊዜ እንዳይጸጽተው ወደ ግብፅም እንዳይመለስ ብሎአልና።”
ዘጸአት 13፥17
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“እንዲህም ሆነ ፈርዖን ሕዝቡን በለቀቀ ጊዜ፥ ምንም ቅርብ ቢሆን እግዚአብሔር በፍልስጥኤማውያን ምድር መንገድ አልመራቸውም፤ እግዚአብሔር፦ ሕዝቡ ሰልፉን ባየ ጊዜ እንዳይጸጽተው ወደ ግብፅም እንዳይመለስ ብሎአልና።”
ዘጸአት 13፥17
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤2👍1
#እራሳችንን_እንመርምር
ዘመናችን ምን ያህል እየሄደ ነው? ምን ያክል ዘመናችንን ቀድመን ወይም ዘግይተን እንዳለን እናውቃለን ወይ? ከዘመን መቅደም ወይም ከዘመን መዘግየት ምን ማለት ነው?
“አቤቱ፥ ፍጻሜዬን አስታውቀኝ፥ የዘመኔ ቍጥሮች ምን ያህል እንደ ሆኑ፥ እኔ ምን ያህል ወደ ኋላ እንደምቀር አውቅ ዘንድ።”
መዝሙር 39፥4
“እግዚአብሔር ሆይ፤ የሕይወቴን ፍጻሜ፣ የዘመኔንም ቍጥር አስታውቀኝ፤ አላፊ ጠፊ መሆኑንም ልረዳ።”
መዝሙር 39፥4 (አዲሱ መ.ት)
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ዘመናችን ምን ያህል እየሄደ ነው? ምን ያክል ዘመናችንን ቀድመን ወይም ዘግይተን እንዳለን እናውቃለን ወይ? ከዘመን መቅደም ወይም ከዘመን መዘግየት ምን ማለት ነው?
“አቤቱ፥ ፍጻሜዬን አስታውቀኝ፥ የዘመኔ ቍጥሮች ምን ያህል እንደ ሆኑ፥ እኔ ምን ያህል ወደ ኋላ እንደምቀር አውቅ ዘንድ።”
መዝሙር 39፥4
“እግዚአብሔር ሆይ፤ የሕይወቴን ፍጻሜ፣ የዘመኔንም ቍጥር አስታውቀኝ፤ አላፊ ጠፊ መሆኑንም ልረዳ።”
መዝሙር 39፥4 (አዲሱ መ.ት)
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍6