' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ከበዓሉም በታላቁ በኋለኛው ቀን ኢየሱስ ቆሞ፦ ማንም የተጠማ ቢኖር ወደ እኔ ይምጣና ይጠጣ።”
ዮሐንስ 7፥37
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ከበዓሉም በታላቁ በኋለኛው ቀን ኢየሱስ ቆሞ፦ ማንም የተጠማ ቢኖር ወደ እኔ ይምጣና ይጠጣ።”
ዮሐንስ 7፥37
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤6👍4
#የእግዚአብሔር_ቃል_ምን_ይላል?
ሐዋርያት 12
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ በዚያም ዘመን ንጉሡ ሄሮድስ መከራ ያጸናባቸው ዘንድ ከቤተ ክርስቲያኑ በአንዳንዶቹ ላይ እጁን ጫነባቸው።
² የዮሐንስንም ወንድም ያዕቆብን በሰይፍ ገደለው።
³ አይሁድንም ደስ እንዳሰኛቸው አይቶ ጨምሮ ጴጥሮስን ደግሞ ያዘው። የቂጣ በዓልም ወራት ነበረ።
⁴ በያዘውም ጊዜ ወደ ወኅኒ አገባው ከፋሲካም በኋላ ወደ ሕዝብ ያወጣው ዘንድ አስቦ እያንዳንዱ አራት ወታደሮች ሆነው እንዲጠብቁት ለአራት ጭፍራ ክፍል አሳልፎ ሰጠው።
⁵ ጴጥሮስም በወኅኒ ይጠበቅ ነበር፤ ነገር ግን በቤተ ክርስቲያን ስለ እርሱ ወደ እግዚአብሔር ጸሎት አጥብቆ ይደረግ ነበር።
⁶ ሄሮድስም ሊያወጣው ባሰበ ጊዜ፥ በዚያች ሌሊት ጴጥሮስ በሁለት ሰንሰለት ታስሮ ከሁለት ወታደሮች መካከል ተኝቶ ነበር፤ ጠባቂዎችም በደጁ ፊት ሆነው ወኅኒውን ይጠብቁ ነበር።
⁷ እነሆም፥ የጌታ መልአክ ቀረበ በቤትም ውስጥ ብርሃን በራ፤ ጴጥሮስንም ጎድኑን መትቶ አነቃውና፦ ፈጥነህ ተነሣ አለው። ሰንሰለቶቹም ከእጁ ወደቁ።
⁸ መልአኩም፦ ታጠቅና ጫማህን አግባ አለው፥ እንዲሁም አደረገ።
⁹ ልብስህንም ልበስና ተከተለኝ አለው። ወጥቶም ተከተለው፤ ራእይንም የሚያይ ይመስለው ነበር እንጂ በመልአኩ የሚደረገው ነገር እውነት እንደ ሆነ አላወቀም።
¹⁰ የመጀመሪያውንና የሁለተኛውንም ዘብ አልፈው ወደ ከተማ ወደሚያወጣው ወደ ብረቱ መዝጊያ ደረሱ፤ እርሱም አውቆ ተከፈተላቸው፤ ወጥተውም አንዲት ስላች አለፉ ወዲያውም መልአኩ ከእርሱ ተለየ።
¹¹ ጴጥሮስም ወደ ልቡ ተመልሶ፦ ጌታ መልአኩን ልኮ ከሄሮድስ እጅና የአይሁድ ሕዝብ ይጠብቁት ከነበረው ሁሉ እንደ አዳነኝ አሁን በእውነት አወቅሁ አለ።
¹² ባስተዋለም ጊዜ እጅግ ሰዎች ተከማችተው ይጸልዩበት ወደ ነበረው ማርቆስ ወደ ተባለው ወደ ዮሐንስ እናት ወደ ማርያም ቤት መጣ።
¹³ ጴጥሮስም የደጁን መዝጊያ ባንኳኳ ጊዜ ሮዴ የሚሉአት አንዲት ገረድ ትሰማ ዘንድ ቀረበች፤
¹⁴ የጴጥሮስ ድምፅ መሆኑንም ባወቀች ጊዜ ከደስታዋ የተነሣ ደጁን አልከፈተችም፥ ነገር ግን ወደ ውስጥ ሮጣ ጴጥሮስ በደጅ ፊት ቆሞ እንዳለ አወራች።
¹⁵ እነርሱም፦ አብደሻል አሉአት። እርስዋ ግን እንዲሁ እንደ ሆነ ታስረግጥ ነበር። እነርሱም፦ መልአኩ ነው አሉ።
¹⁶ ጴጥሮስ ግን ማንኳኳቱን አዘወተረ፤ ከፍተውም አዩትና ተገረሙ።
¹⁷ ግን ዝም እንዲሉ በእጁ ጠቅሶ ጌታ ከወኅኒ እንዴት እንዳወጣው ተረከላቸውና፦ ይህን ለያዕቆብና ለወንድሞች ንገሩ አላቸው። ወጥቶም ወደ ሌላ ስፍራ ሄደ።
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ሐዋርያት 12
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ በዚያም ዘመን ንጉሡ ሄሮድስ መከራ ያጸናባቸው ዘንድ ከቤተ ክርስቲያኑ በአንዳንዶቹ ላይ እጁን ጫነባቸው።
² የዮሐንስንም ወንድም ያዕቆብን በሰይፍ ገደለው።
³ አይሁድንም ደስ እንዳሰኛቸው አይቶ ጨምሮ ጴጥሮስን ደግሞ ያዘው። የቂጣ በዓልም ወራት ነበረ።
⁴ በያዘውም ጊዜ ወደ ወኅኒ አገባው ከፋሲካም በኋላ ወደ ሕዝብ ያወጣው ዘንድ አስቦ እያንዳንዱ አራት ወታደሮች ሆነው እንዲጠብቁት ለአራት ጭፍራ ክፍል አሳልፎ ሰጠው።
⁵ ጴጥሮስም በወኅኒ ይጠበቅ ነበር፤ ነገር ግን በቤተ ክርስቲያን ስለ እርሱ ወደ እግዚአብሔር ጸሎት አጥብቆ ይደረግ ነበር።
⁶ ሄሮድስም ሊያወጣው ባሰበ ጊዜ፥ በዚያች ሌሊት ጴጥሮስ በሁለት ሰንሰለት ታስሮ ከሁለት ወታደሮች መካከል ተኝቶ ነበር፤ ጠባቂዎችም በደጁ ፊት ሆነው ወኅኒውን ይጠብቁ ነበር።
⁷ እነሆም፥ የጌታ መልአክ ቀረበ በቤትም ውስጥ ብርሃን በራ፤ ጴጥሮስንም ጎድኑን መትቶ አነቃውና፦ ፈጥነህ ተነሣ አለው። ሰንሰለቶቹም ከእጁ ወደቁ።
⁸ መልአኩም፦ ታጠቅና ጫማህን አግባ አለው፥ እንዲሁም አደረገ።
⁹ ልብስህንም ልበስና ተከተለኝ አለው። ወጥቶም ተከተለው፤ ራእይንም የሚያይ ይመስለው ነበር እንጂ በመልአኩ የሚደረገው ነገር እውነት እንደ ሆነ አላወቀም።
¹⁰ የመጀመሪያውንና የሁለተኛውንም ዘብ አልፈው ወደ ከተማ ወደሚያወጣው ወደ ብረቱ መዝጊያ ደረሱ፤ እርሱም አውቆ ተከፈተላቸው፤ ወጥተውም አንዲት ስላች አለፉ ወዲያውም መልአኩ ከእርሱ ተለየ።
¹¹ ጴጥሮስም ወደ ልቡ ተመልሶ፦ ጌታ መልአኩን ልኮ ከሄሮድስ እጅና የአይሁድ ሕዝብ ይጠብቁት ከነበረው ሁሉ እንደ አዳነኝ አሁን በእውነት አወቅሁ አለ።
¹² ባስተዋለም ጊዜ እጅግ ሰዎች ተከማችተው ይጸልዩበት ወደ ነበረው ማርቆስ ወደ ተባለው ወደ ዮሐንስ እናት ወደ ማርያም ቤት መጣ።
¹³ ጴጥሮስም የደጁን መዝጊያ ባንኳኳ ጊዜ ሮዴ የሚሉአት አንዲት ገረድ ትሰማ ዘንድ ቀረበች፤
¹⁴ የጴጥሮስ ድምፅ መሆኑንም ባወቀች ጊዜ ከደስታዋ የተነሣ ደጁን አልከፈተችም፥ ነገር ግን ወደ ውስጥ ሮጣ ጴጥሮስ በደጅ ፊት ቆሞ እንዳለ አወራች።
¹⁵ እነርሱም፦ አብደሻል አሉአት። እርስዋ ግን እንዲሁ እንደ ሆነ ታስረግጥ ነበር። እነርሱም፦ መልአኩ ነው አሉ።
¹⁶ ጴጥሮስ ግን ማንኳኳቱን አዘወተረ፤ ከፍተውም አዩትና ተገረሙ።
¹⁷ ግን ዝም እንዲሉ በእጁ ጠቅሶ ጌታ ከወኅኒ እንዴት እንዳወጣው ተረከላቸውና፦ ይህን ለያዕቆብና ለወንድሞች ንገሩ አላቸው። ወጥቶም ወደ ሌላ ስፍራ ሄደ።
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤2👍2
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ናቡከደነፆርም መልሶ፦ መልአኩን የላከ፥ ከአምላካቸውም በቀር ማንንም አምላክ እንዳያመልኩ ለእርሱም እንዳይሰግዱ ሰውነታቸውን አሳልፈው የሰጡትን የንጉሡንም ቃል የተላለፉትን በእርሱ የታመኑትን ባሪያዎቹን ያዳነ፥ የሲድራቅና የሚሳቅ የአብደናጎም አምላክ ይባረክ።”
ዳንኤል 3፥28
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ናቡከደነፆርም መልሶ፦ መልአኩን የላከ፥ ከአምላካቸውም በቀር ማንንም አምላክ እንዳያመልኩ ለእርሱም እንዳይሰግዱ ሰውነታቸውን አሳልፈው የሰጡትን የንጉሡንም ቃል የተላለፉትን በእርሱ የታመኑትን ባሪያዎቹን ያዳነ፥ የሲድራቅና የሚሳቅ የአብደናጎም አምላክ ይባረክ።”
ዳንኤል 3፥28
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤3👍1
የመከራ ወይም የፈተና ጊዜ ከሌሎች ጊዜያት ለየት የሚሉት ምን ማድረግ እንዳለብን እና እንደሌለብን ለማወቅ ግራ መጋባታችን ነው። ለዚህ ደግሞ መፍትሄው በልግስና ከሚሰጠው ከእግዚአብሔር ዘንድ ጥበብን መለመን ነው።
“ከእናንተ ግን ማንም ጥበብ ቢጎድለው፥ ሳይነቅፍ በልግስና ለሁሉ የሚሰጠውን እግዚአብሔርን ይለምን፥ ለእርሱም ይሰጠዋል።”
ያዕቆብ 1፥5
“If you need wisdom—if you want to know what God wants you to do—ask him, and he will gladly tell you. He will not resent your asking.”
Jam 1:5 (NLT)
"If you don't know what you're doing, pray to the Father. He loves to help. You'll get his help, and won't be condescended to when you ask for it."
James 1:5 (The Message )
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
“ከእናንተ ግን ማንም ጥበብ ቢጎድለው፥ ሳይነቅፍ በልግስና ለሁሉ የሚሰጠውን እግዚአብሔርን ይለምን፥ ለእርሱም ይሰጠዋል።”
ያዕቆብ 1፥5
“If you need wisdom—if you want to know what God wants you to do—ask him, and he will gladly tell you. He will not resent your asking.”
Jam 1:5 (NLT)
"If you don't know what you're doing, pray to the Father. He loves to help. You'll get his help, and won't be condescended to when you ask for it."
James 1:5 (The Message )
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍4❤1
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ልጄ ሆይ፤ ትክክለኛ ፍርድንና አስተውሎ መለየትን ጠብቅ፤ እነዚህ ከእይታህ አይራቁ፤”
ምሳሌ 3፥21 (አዲሱ መ.ት)
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ልጄ ሆይ፤ ትክክለኛ ፍርድንና አስተውሎ መለየትን ጠብቅ፤ እነዚህ ከእይታህ አይራቁ፤”
ምሳሌ 3፥21 (አዲሱ መ.ት)
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍2❤1
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ዳዊትም ሳኦል ክፉን እንዳሰበበት አወቀ፤ ካሁኑን አብያታርንም፦ ኤፉዱን ወደዚህ አምጣ አለው።”
1ኛ ሳሙኤል 23፥9
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ዳዊትም ሳኦል ክፉን እንዳሰበበት አወቀ፤ ካሁኑን አብያታርንም፦ ኤፉዱን ወደዚህ አምጣ አለው።”
1ኛ ሳሙኤል 23፥9
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤3👍1
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ከዚህም በኋላ ከእነርሱ ለሁለቱ ወደ ባላገር ሲሄዱ በመንገድ በሌላ መልክ ተገለጠ፤”
ማርቆስ 16፥12
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ከዚህም በኋላ ከእነርሱ ለሁለቱ ወደ ባላገር ሲሄዱ በመንገድ በሌላ መልክ ተገለጠ፤”
ማርቆስ 16፥12
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤1👍1
መጽሐፍ ቅዱስን ለማጥናት ትክክለኛው መንገድ ምንድነው?
የቅዱስ ቃሉን ትርጉም መወሰን አማኝ በዚህ ሕይወት ካሉት እጅግ ጠቃሚ ተግባራት መካከል አንደኛው ነው። እግዚአብሔር መጽሐፍ ቅዱስን የግድ እንድናነብ አይነግረንም። እኛ የግድ ማጥናትና ባግባቡ መያዝ አለብን (2 ጢሞቴዎስ 2፡15)። ቅዱሳን መጻሕፍትን ማጥናት ከባድ ሥራ ነው። ቅዱስ ቃሉን በግልብ ወይም አጭር ቅኝት መመልከት አንዳንዴ በጣም የተሳሳተ ድምዳሜ ያመጣል። ስለዚህ፣ የቅዱስ ቃሉን ትክክለኛ ፍቺ ለመወሰን በርካታ መርሖዎችን መረዳት ወሳኝ ነው።
#አንደኛ፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ተማሪ የግድ መጸለይና መንፈስ ቅዱስን መጠየቅ አለበት፣ መረዳትን እንዲሰጠው፣ ይህ አንደኛው ተግባሩ ስለሆነ። “ግን እርሱ የእውነት መንፈስ በመጣ ጊዜ ወደ እውነት ሁሉ ይመራችኋል፤ የሚሰማውን ሁሉ ይናገራል እንጂ ከራሱ አይነግርምና፤ የሚመጣውንም ይነግራችኋል” (ዮሐንስ 16፡13)። መንፈስ ቅዱስ፣ ሐዋርያት አዲስ ኪዳንን ሲጽፉ እንደመራቸው ሁሉ፣ ቅዱስ ቃሉን አንድንረዳ ይመራናል። አስታውሱ፣ መጽሐፍ ቅዱስ የእግዚአብሔር መጽሐፍ ነው፣ እናም ምን ማለት አንደሆነ ልንጠይቀው ያስፈልጋል። ክርስቲያን ከሆናችሁ፣ የቅዱስ ቃሉ ደራሲ —መንፈስ ቅዱስ—በውስጣችሁ ያድራል፣ እናም እሱ የጻፈውን እንድትረዱለት ይሻል።
#ሁለተኛ፣ የቅዱስ ቃሉን ቁጥሮች የከበቡትን መዘን ልናወጣና የቁጥሩን ፍች ከዐውደ-ጽሑፉ ውጭ ለመወሰን መሞከር አይገባንም። በዙሪያው ያሉትን ቁጥሮችና ምዕራፎች ዘወትር ማንበብ አለብን ዐውደ-ጽሑፉን ለመገንዘብ። ሁሉም ቅዱስ ቃል ከእግዚአብሔር ሲመጣ (2 ጢሞቴዎስ 3:16፤ 2 ጴጥሮስ 1:21)፣ እግዚአብሔር ሰዎችን ተጠቅሟል፣ እሱን ይጽፉት ዘንድ። እነዚህ ሰዎች በአእምሯቸው ጭብጥ አለ፣ ለመጻፍም ዓላማ አላቸው፣ እንዲሁም የተወሰነ ጉዳይ የሚያስተላልፉት። የምናጠናውን የመጽሐፍ ቅዱስን መጽሐፍ ዳራ ማንበብ ይኖርብናል፣ ማን እንደ ጻፈው፣ ለማን እንደ ተጻፈ፣ መቼ እንደ ተጻፈ፣ እና ለምን እንደተጻፈ ለመረዳት። ደግሞም፣ ጽሑፉ ለራሱ እንዲናገር በመፍቀድ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርብናል። አንዳንዴ ሰዎች የገዛ ራሳቸውን ፍች ከቃሉ ጋር ያያይዛሉ፣ ራሳቸው የሚፈልጉትን ትርጓሜ ለማግኘት።
#ሦስተኛ፣ እኛ ባጠቃላይ ነጻ ለመሆን መሞከር አይኖርብንም፣ በእኛ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት ላይ። ከሌሎች፣ ቅዱስ ቃሉን ለረዥም ጊዜ ካጠኑት ሰዎች በኩል መረዳትን ልናገኝ አንችልም ብሎ ማሰብ ትዕቢተኝነት ነው። አንዳንድ ሰዎች በስሕተት መጽሐፍ ቅዱስን የሚቀርቡት በመንፈስ ቅዱስ ላይ ብቻ ነው የምንጠጋው በሚል ሐሳብ ሁሉንም የተሸሸጉ የቅዱስ ቃሉን እውነቶች የደረሱበት ይመስላቸዋል። ክርስቶስ፣ መንፈስ ቅዱስን በመስጠት፣ ለሰዎች መንፈሳዊ ስጦታ ይሰጣቸዋል፣ ለክርስቶስ አካል። ከእነዚህ መንፈሳዊ ስጦታዎች አንደኛው ማስተማር ነው (ኤፌሶን 4:11-12፤ 1 ቆሮንቶስ 12:28)። እነዚህ መምህራን የተሰጡን በጌታ ነው፣ ቅዱስ ቃሉን በትክክል እንድንገነዘብና እንድንታዘዝ እንዲረዱን። ዘወትር ከሌሎች አማኞች ጋር መጽሐፍ ቅዱስን ማጥናት ብልህነት ነው፣ የእግዚአብሔርን ቃል እውነት ለመረዳትና ለመተግበር እርስ በርስ ለመደጋገፍ።
ስለዚህ፣ በማጠቃለያ፣ መጽሐፍ ቅዱስን ለማጥናት ተገቢ የሆነው መንገድ ምንድነው? አንደኛ፣ በጸሎትና በትሕትና፣ በመንፈስ ቅዱስ ላይ ልንታመን ይገባል፣ መረዳትን አንዲሰጠን። ሁለተኛ፣ ዘወትር ቅዱስ ቃሉን ማጥናት ያለብን በዐውደ-ጽሑፉ አኳያ ነው፣ መጽሐፍ ቅዱስ ራሱ እንደሚገልጽ በመገንዘብ። ሦስተኛ፣ የሌሎችን ክርስቲያኖች ጥረት ልናከብር ይገባል፣ ያለፉትንም ሆነ ያሁኖቹን፣ እነሱም የመጽሐፍ ቅዱስን ተገቢ የሆነ የአጠናን ዘዴ ያመላከቱትን። አስታውሱ፣ እግዚአብሔር የመጽሐፍ ቅዱስ ደራሲ ነው፣ እናም እሱ አንድንገነዘበው ይፈልጋል።
ምንጭ፦ www.gotquestions.org
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የቅዱስ ቃሉን ትርጉም መወሰን አማኝ በዚህ ሕይወት ካሉት እጅግ ጠቃሚ ተግባራት መካከል አንደኛው ነው። እግዚአብሔር መጽሐፍ ቅዱስን የግድ እንድናነብ አይነግረንም። እኛ የግድ ማጥናትና ባግባቡ መያዝ አለብን (2 ጢሞቴዎስ 2፡15)። ቅዱሳን መጻሕፍትን ማጥናት ከባድ ሥራ ነው። ቅዱስ ቃሉን በግልብ ወይም አጭር ቅኝት መመልከት አንዳንዴ በጣም የተሳሳተ ድምዳሜ ያመጣል። ስለዚህ፣ የቅዱስ ቃሉን ትክክለኛ ፍቺ ለመወሰን በርካታ መርሖዎችን መረዳት ወሳኝ ነው።
#አንደኛ፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ተማሪ የግድ መጸለይና መንፈስ ቅዱስን መጠየቅ አለበት፣ መረዳትን እንዲሰጠው፣ ይህ አንደኛው ተግባሩ ስለሆነ። “ግን እርሱ የእውነት መንፈስ በመጣ ጊዜ ወደ እውነት ሁሉ ይመራችኋል፤ የሚሰማውን ሁሉ ይናገራል እንጂ ከራሱ አይነግርምና፤ የሚመጣውንም ይነግራችኋል” (ዮሐንስ 16፡13)። መንፈስ ቅዱስ፣ ሐዋርያት አዲስ ኪዳንን ሲጽፉ እንደመራቸው ሁሉ፣ ቅዱስ ቃሉን አንድንረዳ ይመራናል። አስታውሱ፣ መጽሐፍ ቅዱስ የእግዚአብሔር መጽሐፍ ነው፣ እናም ምን ማለት አንደሆነ ልንጠይቀው ያስፈልጋል። ክርስቲያን ከሆናችሁ፣ የቅዱስ ቃሉ ደራሲ —መንፈስ ቅዱስ—በውስጣችሁ ያድራል፣ እናም እሱ የጻፈውን እንድትረዱለት ይሻል።
#ሁለተኛ፣ የቅዱስ ቃሉን ቁጥሮች የከበቡትን መዘን ልናወጣና የቁጥሩን ፍች ከዐውደ-ጽሑፉ ውጭ ለመወሰን መሞከር አይገባንም። በዙሪያው ያሉትን ቁጥሮችና ምዕራፎች ዘወትር ማንበብ አለብን ዐውደ-ጽሑፉን ለመገንዘብ። ሁሉም ቅዱስ ቃል ከእግዚአብሔር ሲመጣ (2 ጢሞቴዎስ 3:16፤ 2 ጴጥሮስ 1:21)፣ እግዚአብሔር ሰዎችን ተጠቅሟል፣ እሱን ይጽፉት ዘንድ። እነዚህ ሰዎች በአእምሯቸው ጭብጥ አለ፣ ለመጻፍም ዓላማ አላቸው፣ እንዲሁም የተወሰነ ጉዳይ የሚያስተላልፉት። የምናጠናውን የመጽሐፍ ቅዱስን መጽሐፍ ዳራ ማንበብ ይኖርብናል፣ ማን እንደ ጻፈው፣ ለማን እንደ ተጻፈ፣ መቼ እንደ ተጻፈ፣ እና ለምን እንደተጻፈ ለመረዳት። ደግሞም፣ ጽሑፉ ለራሱ እንዲናገር በመፍቀድ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርብናል። አንዳንዴ ሰዎች የገዛ ራሳቸውን ፍች ከቃሉ ጋር ያያይዛሉ፣ ራሳቸው የሚፈልጉትን ትርጓሜ ለማግኘት።
#ሦስተኛ፣ እኛ ባጠቃላይ ነጻ ለመሆን መሞከር አይኖርብንም፣ በእኛ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት ላይ። ከሌሎች፣ ቅዱስ ቃሉን ለረዥም ጊዜ ካጠኑት ሰዎች በኩል መረዳትን ልናገኝ አንችልም ብሎ ማሰብ ትዕቢተኝነት ነው። አንዳንድ ሰዎች በስሕተት መጽሐፍ ቅዱስን የሚቀርቡት በመንፈስ ቅዱስ ላይ ብቻ ነው የምንጠጋው በሚል ሐሳብ ሁሉንም የተሸሸጉ የቅዱስ ቃሉን እውነቶች የደረሱበት ይመስላቸዋል። ክርስቶስ፣ መንፈስ ቅዱስን በመስጠት፣ ለሰዎች መንፈሳዊ ስጦታ ይሰጣቸዋል፣ ለክርስቶስ አካል። ከእነዚህ መንፈሳዊ ስጦታዎች አንደኛው ማስተማር ነው (ኤፌሶን 4:11-12፤ 1 ቆሮንቶስ 12:28)። እነዚህ መምህራን የተሰጡን በጌታ ነው፣ ቅዱስ ቃሉን በትክክል እንድንገነዘብና እንድንታዘዝ እንዲረዱን። ዘወትር ከሌሎች አማኞች ጋር መጽሐፍ ቅዱስን ማጥናት ብልህነት ነው፣ የእግዚአብሔርን ቃል እውነት ለመረዳትና ለመተግበር እርስ በርስ ለመደጋገፍ።
ስለዚህ፣ በማጠቃለያ፣ መጽሐፍ ቅዱስን ለማጥናት ተገቢ የሆነው መንገድ ምንድነው? አንደኛ፣ በጸሎትና በትሕትና፣ በመንፈስ ቅዱስ ላይ ልንታመን ይገባል፣ መረዳትን አንዲሰጠን። ሁለተኛ፣ ዘወትር ቅዱስ ቃሉን ማጥናት ያለብን በዐውደ-ጽሑፉ አኳያ ነው፣ መጽሐፍ ቅዱስ ራሱ እንደሚገልጽ በመገንዘብ። ሦስተኛ፣ የሌሎችን ክርስቲያኖች ጥረት ልናከብር ይገባል፣ ያለፉትንም ሆነ ያሁኖቹን፣ እነሱም የመጽሐፍ ቅዱስን ተገቢ የሆነ የአጠናን ዘዴ ያመላከቱትን። አስታውሱ፣ እግዚአብሔር የመጽሐፍ ቅዱስ ደራሲ ነው፣ እናም እሱ አንድንገነዘበው ይፈልጋል።
ምንጭ፦ www.gotquestions.org
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍3
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“እንደዚህ ከእምነት የሆኑት ካመነው ከአብርሃም ጋር ይባረካሉ።”
ገላትያ 3፥9
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“እንደዚህ ከእምነት የሆኑት ካመነው ከአብርሃም ጋር ይባረካሉ።”
ገላትያ 3፥9
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤5👍2
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ስለዚህ፥ ወዳጆቼ ሆይ፥ ሁልጊዜ እንደ ታዘዛችሁ፥ በእናንተ ዘንድ በመኖሬ ብቻ ሳይሆን ይልቁን አሁን ስርቅ፥ በፍርሃትና በመንቀጥቀጥ የራሳችሁን መዳን ፈጽሙ፤”
ፊልጵስዩስ 2፥12
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ስለዚህ፥ ወዳጆቼ ሆይ፥ ሁልጊዜ እንደ ታዘዛችሁ፥ በእናንተ ዘንድ በመኖሬ ብቻ ሳይሆን ይልቁን አሁን ስርቅ፥ በፍርሃትና በመንቀጥቀጥ የራሳችሁን መዳን ፈጽሙ፤”
ፊልጵስዩስ 2፥12
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤4👍2
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“እግዚአብሔርም ደግሞ በሴሎ ተገለጠ፤ እግዚአብሔርም በእግዚአብሔር ቃል ለሳሙኤል በሴሎ ይገለጥ ነበር። የሳሙኤልም ቃል ለእስራኤል ሁሉ ደረሰ።”
1ኛ ሳሙኤል 3፥21
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“እግዚአብሔርም ደግሞ በሴሎ ተገለጠ፤ እግዚአብሔርም በእግዚአብሔር ቃል ለሳሙኤል በሴሎ ይገለጥ ነበር። የሳሙኤልም ቃል ለእስራኤል ሁሉ ደረሰ።”
1ኛ ሳሙኤል 3፥21
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤2👍2
#የእግዚአብሔር_ቃል_ምን_ይላል?
ሐዋርያት 2
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁴² በሐዋርያትም ትምህርትና በኅብረት እንጀራውንም በመቍረስ በየጸሎቱም ይተጉ ነበር።
⁴³ ነገር ግን በሰው ሁሉ ፍርሀት ሆነ፤ በሐዋርያትም እጅ ብዙ ድንቅና ምልክት ተደረገ።
⁴⁴ ያመኑትም ሁሉ አብረው ነበሩ፤
⁴⁵ ያላቸውንም ሁሉ አንድነት አደረጉ። መሬታቸውንና ጥሪታቸውንም እየሸጡ፥ ማንኛውም እንደሚፈልግ ለሁሉ ያካፍሉት ነበር።
⁴⁶ በየቀኑም በአንድ ልብ ሆነው በመቅደስ እየተጉ በቤታቸውም እንጀራ እየቈረሱ፥ በደስታና በጥሩ ልብ ምግባቸውን ይመገቡ ነበር፤
⁴⁷ እግዚአብሔርንም እያመሰገኑ በሕዝብ ሁሉ ፊት ሞገስ ነበራቸው። ጌታም የሚድኑትን ዕለት ዕለት በእነርሱ ላይ ይጨምር ነበር።
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ሐዋርያት 2
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁴² በሐዋርያትም ትምህርትና በኅብረት እንጀራውንም በመቍረስ በየጸሎቱም ይተጉ ነበር።
⁴³ ነገር ግን በሰው ሁሉ ፍርሀት ሆነ፤ በሐዋርያትም እጅ ብዙ ድንቅና ምልክት ተደረገ።
⁴⁴ ያመኑትም ሁሉ አብረው ነበሩ፤
⁴⁵ ያላቸውንም ሁሉ አንድነት አደረጉ። መሬታቸውንና ጥሪታቸውንም እየሸጡ፥ ማንኛውም እንደሚፈልግ ለሁሉ ያካፍሉት ነበር።
⁴⁶ በየቀኑም በአንድ ልብ ሆነው በመቅደስ እየተጉ በቤታቸውም እንጀራ እየቈረሱ፥ በደስታና በጥሩ ልብ ምግባቸውን ይመገቡ ነበር፤
⁴⁷ እግዚአብሔርንም እያመሰገኑ በሕዝብ ሁሉ ፊት ሞገስ ነበራቸው። ጌታም የሚድኑትን ዕለት ዕለት በእነርሱ ላይ ይጨምር ነበር።
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤5
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“አቤቱ፥ ጸሎቴ ወደ ፊትህ ትቅረብ፤ እንደ ቃልህም አስተዋይ አድርገኝ።”
መዝሙር 119፥169
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“አቤቱ፥ ጸሎቴ ወደ ፊትህ ትቅረብ፤ እንደ ቃልህም አስተዋይ አድርገኝ።”
መዝሙር 119፥169
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤4👍1
#የሮሜ_መልእክት_ጥናት
ሮሜ 9፥6-13
ጳውሎስ ከሚያስደስተው ከምዕራፍ 8 ኀዘን ወደ ተሞላው ወደ ምዕራፍ 9 መራመዱ ግልጽ ነው፡፡ ክርስቶስን ሲያይ ተደሰተ፤ የጠፉትን እስራኤላውያንን ሲያይ ደግሞ አለቀሰ፡፡ እንደ ሙሴ (ዘጸ. 32:30-35) ስለ እስራኤል መዳን ራሱ የተረገመ ይሆን ዘንድ ፈቃደኛ ነበር:: ይሄ ጳውሎስ ምን ዓይነት ሰው ነው? ስላልዳኑት ከመንግሥተ ሰማይ መጉደልን እንኳ መረጠ (9፡3)፤ ስለጠፉትም ሲል ሲዖል መውረድን ፈቀደ፡፡
ጭብጡ እግዚአብሔር እስራኤልን የመምረጡ ጉዳይ ሲሆን፣ በመጀመሪያ የዳሰሰው የመመረጣቸውን በረከት ነው (ቁ. 4-5)። እግዚአብሔር እስራኤላውያንን ልጆቹ አድርጎ መርጦአቸዋል (ዘጸ. 4:22-23)። በመገናኛ ድንኳንና በቤተ መቅደስ ክብሩን አሳይቶአቸዋል (ዘጸ. 40:34-38፣ 1ኛ ነገ. 8:10-11):: ሙሴ በሲና ተራራ ላይ ያየው ክብር በእስራኤል መካከል ኖረ (ዘጸ. 24:16-17):: እግዚአብሔር ቃል ኪዳኑን ለእስራኤል ሰጠ፣ በመጀመሪያ ለአብርሃም፣ ከዚያም ተጨማሪ ቃል ኪዳኖችን ለሙሴና ለዳዊት ሰጠ፡፡ ፖለቲካዊ፤ ማኅበራዊና ሃይማኖታዊ ሕይወት የሚያስተዳድር ሕግ የሰጣቸው ሲሆን፣ በታዘዙት መሠረት እንደሚባርካቸው ዋስትና ነበራቸው፡፡ በመገናኛው ድንኳንና በቤተ መቅደስ እንዲያገለግሉት «የእግዚአብሔርን አገልግሎት» ሰጣቸው፡፡ የተስፋ ቃልንና አባቶችን ሰጣቸው፡፡ የዚህ ሁሉ በረከት ዓላማ ኢየሱስ ክርስቶስ በእነርሱ በኩል ወደ ዓለም እንዲመጣ ነው:: (ቁ. 5 ኢየሱስ አምላክ መሆኑን እንደሚያስረግጥ አስታውሉ፡፡) እነዚህ ሁሉ በረከቶች ለእስራኤል በነፃ የተሰጡ ሲሆን፣ ለሌሎች አሕዛብ ግን አልተሰጡም ነበር፡፡
እነዚህ ሁሉ በረከቶች ቢኖሩም እስራኤል ግን አልተሳካላትም፡፡ መሢሑ በመጣ ጊዜ እስራኤላውያን ገፉት፣ ሰቀሉትም፡፡ ጳውሎስ ራሱ አሳዳጅ ስለነበረ፣ ይህን ከእርሱ በተሻለ መልኩ የሚያውቅ አይኖርም፡፡ የእስራኤል መውደቅ የእግዚአብሔርን ቃል ይሽራልን? መልሱ «በፍጹም! የሚል ነው:: ሰዎች በቃሉ ላይ የፈለጋቸውን ቢያደርጉም፣ እግዚአብሔር ግን ታማኝ ነው»፡፡ በዚህ ስፍራ ጳውሎስ የእስራኤልን የመመረጥ ምክንያት ያብራራል፡፡
ሀ) በሥጋ የዘር ሐረግ አልነበረም (9:6-10)
በሮሜ 2፡25-29 እንዳየነው፣ በሥጋ የአብርሃም ዘር በሆኑና በመንፈስ የአብርሃም ልጆች በሆኑት መካከል ልዩነት እንዳለ አይተናል፡፡ አብርሃም ሁለት ልጆች ነበሩት፣ እስማኤልና (ከአጋር) ይስሐቅ (ከሣራ)፡፡ እስማኤል የበኩር ልጅ ስለሆነ፣ መመረጥ ነበረበት፡፡ ነገር ግን እግዚአብሔር የመረጠው ይስሐቅን ነበረ፡፡ ይስሐቅና ርብቃ ዔሣውና ያዕቆብ የተባሉ ሁለት መንትያ ልጆች ነበሯት፡፡ የመጀመሪያ ልጅ በመሆኑ ዔሣው መመረጥ ሲገባው ፣ እግዚአብሔር የመረጠው ግን ያዕቆብን ነበረ፡፡ በተለይ ዔሣውና ያዕቆብ እንደ ይስሐቅና እስማኤል የተወለዱት ከሁለት እናቶች ሳይሆን፣ የአንድ እናት የአንድ አባት ልጆች ነበሩ፡፡ የእግዚአብሔር ምርጫ በሚታይ ነገር ላይ የተመሠረተ አይደለም፡፡ ስለዚህ የአብርሃም የሥጋ ዘር የሆኑት እስራኤላውያን የእግዚአብሐርን ቃል ቢገፉ፣ የእግዚአብሔርን ምርጫ ከንቱ አያደርገውም፡፡
ለ) በሰው ጥረት አይደለም (9:11-13)
ሕፃናቱ ከመወለዳቸው አስቀድሞ እግዚአብሔር ያዕቆብን መረጠ፡፡ ልጆቹ በጎ ወይም ክፉ አላደረጉም፣ የእግዚአብሔር ምርጫ በባሕርያቸው ወይም በፀባያቸው ላይ የተመረኮዘ አልነበረም:: ቁጥር 13 ከሚልክያስ 1:2-3 የተወሰደ ሲሆን፣ የሚያወሳውም ስለ እስራኤልና ስለ ኤዶም ነው እንጂ ስለ ኃጢአተኛ ግለሰቦች አይደለም:: ዮሐ. 3:16 እንደሚያመለክተው እርሱ ኃጢአተኞችን ይወዳል፡፡ ምንባቡ የሚናገረው ስለ አንድ አገር መመረጥ እንጂ ስለ ግለሰቦች አይደለም፡፡ እግዚአብሔር እስራኤልን የመረጠው በሰው ጥረት ላይ ተመሥርቶ ስላልነበረ፣ አለመታዘዛቸው የእግዚአብሔርን የምርጫ ዓላማ ከንቱ አያደርገውም፡፡ ሕዝቡ ታማኞች ባይሆኑም እንኳ እግዚአብሔር ታማኝ ነው፡፡
ይቀጥላል...
ምንጭ፦ ዋረን ደብልዩ ዌርዝ ቢ፤ ተስማማ፤ ገጽ 94-96
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ሮሜ 9፥6-13
ጳውሎስ ከሚያስደስተው ከምዕራፍ 8 ኀዘን ወደ ተሞላው ወደ ምዕራፍ 9 መራመዱ ግልጽ ነው፡፡ ክርስቶስን ሲያይ ተደሰተ፤ የጠፉትን እስራኤላውያንን ሲያይ ደግሞ አለቀሰ፡፡ እንደ ሙሴ (ዘጸ. 32:30-35) ስለ እስራኤል መዳን ራሱ የተረገመ ይሆን ዘንድ ፈቃደኛ ነበር:: ይሄ ጳውሎስ ምን ዓይነት ሰው ነው? ስላልዳኑት ከመንግሥተ ሰማይ መጉደልን እንኳ መረጠ (9፡3)፤ ስለጠፉትም ሲል ሲዖል መውረድን ፈቀደ፡፡
ጭብጡ እግዚአብሔር እስራኤልን የመምረጡ ጉዳይ ሲሆን፣ በመጀመሪያ የዳሰሰው የመመረጣቸውን በረከት ነው (ቁ. 4-5)። እግዚአብሔር እስራኤላውያንን ልጆቹ አድርጎ መርጦአቸዋል (ዘጸ. 4:22-23)። በመገናኛ ድንኳንና በቤተ መቅደስ ክብሩን አሳይቶአቸዋል (ዘጸ. 40:34-38፣ 1ኛ ነገ. 8:10-11):: ሙሴ በሲና ተራራ ላይ ያየው ክብር በእስራኤል መካከል ኖረ (ዘጸ. 24:16-17):: እግዚአብሔር ቃል ኪዳኑን ለእስራኤል ሰጠ፣ በመጀመሪያ ለአብርሃም፣ ከዚያም ተጨማሪ ቃል ኪዳኖችን ለሙሴና ለዳዊት ሰጠ፡፡ ፖለቲካዊ፤ ማኅበራዊና ሃይማኖታዊ ሕይወት የሚያስተዳድር ሕግ የሰጣቸው ሲሆን፣ በታዘዙት መሠረት እንደሚባርካቸው ዋስትና ነበራቸው፡፡ በመገናኛው ድንኳንና በቤተ መቅደስ እንዲያገለግሉት «የእግዚአብሔርን አገልግሎት» ሰጣቸው፡፡ የተስፋ ቃልንና አባቶችን ሰጣቸው፡፡ የዚህ ሁሉ በረከት ዓላማ ኢየሱስ ክርስቶስ በእነርሱ በኩል ወደ ዓለም እንዲመጣ ነው:: (ቁ. 5 ኢየሱስ አምላክ መሆኑን እንደሚያስረግጥ አስታውሉ፡፡) እነዚህ ሁሉ በረከቶች ለእስራኤል በነፃ የተሰጡ ሲሆን፣ ለሌሎች አሕዛብ ግን አልተሰጡም ነበር፡፡
እነዚህ ሁሉ በረከቶች ቢኖሩም እስራኤል ግን አልተሳካላትም፡፡ መሢሑ በመጣ ጊዜ እስራኤላውያን ገፉት፣ ሰቀሉትም፡፡ ጳውሎስ ራሱ አሳዳጅ ስለነበረ፣ ይህን ከእርሱ በተሻለ መልኩ የሚያውቅ አይኖርም፡፡ የእስራኤል መውደቅ የእግዚአብሔርን ቃል ይሽራልን? መልሱ «በፍጹም! የሚል ነው:: ሰዎች በቃሉ ላይ የፈለጋቸውን ቢያደርጉም፣ እግዚአብሔር ግን ታማኝ ነው»፡፡ በዚህ ስፍራ ጳውሎስ የእስራኤልን የመመረጥ ምክንያት ያብራራል፡፡
ሀ) በሥጋ የዘር ሐረግ አልነበረም (9:6-10)
በሮሜ 2፡25-29 እንዳየነው፣ በሥጋ የአብርሃም ዘር በሆኑና በመንፈስ የአብርሃም ልጆች በሆኑት መካከል ልዩነት እንዳለ አይተናል፡፡ አብርሃም ሁለት ልጆች ነበሩት፣ እስማኤልና (ከአጋር) ይስሐቅ (ከሣራ)፡፡ እስማኤል የበኩር ልጅ ስለሆነ፣ መመረጥ ነበረበት፡፡ ነገር ግን እግዚአብሔር የመረጠው ይስሐቅን ነበረ፡፡ ይስሐቅና ርብቃ ዔሣውና ያዕቆብ የተባሉ ሁለት መንትያ ልጆች ነበሯት፡፡ የመጀመሪያ ልጅ በመሆኑ ዔሣው መመረጥ ሲገባው ፣ እግዚአብሔር የመረጠው ግን ያዕቆብን ነበረ፡፡ በተለይ ዔሣውና ያዕቆብ እንደ ይስሐቅና እስማኤል የተወለዱት ከሁለት እናቶች ሳይሆን፣ የአንድ እናት የአንድ አባት ልጆች ነበሩ፡፡ የእግዚአብሔር ምርጫ በሚታይ ነገር ላይ የተመሠረተ አይደለም፡፡ ስለዚህ የአብርሃም የሥጋ ዘር የሆኑት እስራኤላውያን የእግዚአብሐርን ቃል ቢገፉ፣ የእግዚአብሔርን ምርጫ ከንቱ አያደርገውም፡፡
ለ) በሰው ጥረት አይደለም (9:11-13)
ሕፃናቱ ከመወለዳቸው አስቀድሞ እግዚአብሔር ያዕቆብን መረጠ፡፡ ልጆቹ በጎ ወይም ክፉ አላደረጉም፣ የእግዚአብሔር ምርጫ በባሕርያቸው ወይም በፀባያቸው ላይ የተመረኮዘ አልነበረም:: ቁጥር 13 ከሚልክያስ 1:2-3 የተወሰደ ሲሆን፣ የሚያወሳውም ስለ እስራኤልና ስለ ኤዶም ነው እንጂ ስለ ኃጢአተኛ ግለሰቦች አይደለም:: ዮሐ. 3:16 እንደሚያመለክተው እርሱ ኃጢአተኞችን ይወዳል፡፡ ምንባቡ የሚናገረው ስለ አንድ አገር መመረጥ እንጂ ስለ ግለሰቦች አይደለም፡፡ እግዚአብሔር እስራኤልን የመረጠው በሰው ጥረት ላይ ተመሥርቶ ስላልነበረ፣ አለመታዘዛቸው የእግዚአብሔርን የምርጫ ዓላማ ከንቱ አያደርገውም፡፡ ሕዝቡ ታማኞች ባይሆኑም እንኳ እግዚአብሔር ታማኝ ነው፡፡
ይቀጥላል...
ምንጭ፦ ዋረን ደብልዩ ዌርዝ ቢ፤ ተስማማ፤ ገጽ 94-96
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤2👍1👏1
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ከእኛ አንድ ስንኳ ለራሱ የሚኖር የለምና፥ ለራሱም የሚሞት የለም፤”
ሮሜ 14፥7
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ከእኛ አንድ ስንኳ ለራሱ የሚኖር የለምና፥ ለራሱም የሚሞት የለም፤”
ሮሜ 14፥7
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤4
#ከተማ_ወይም_ቦታ_በቅዱሳት_መጻሕፍት
#ተሰሎንቄ፤ ሐዋርያው ጳውሎስ በ2ኛ የስብከት ጕዞው ከሲላስና ከጢሞቴዎስ ጋር ወደ ተሰሎንቄ ሄደ። ከተማይቱ በግሪክ አገር የመቄዶንያ አውራጃ ዋና ከተማና ታላቅ ወደብ ስትሆን፥ ወደ ምሥራቅ በሚወስደው በታላቁ የሮም መንገድ ላይ ትገኝ ነበር። ጳውሎስ በፊልጵስዩስ ከተማ ስደት ከደረሰበት በኋላ ወደ ተሰሎንቄ ደረሰ፤ እዚያም 3 ሳምንት ያህል አስተማረ፤ ሐ.ሥ. 17፥1-10፤ 1ተሰ. 2፥2።
ምንጭ፦ የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት፤ ገጽ 121
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
#ተሰሎንቄ፤ ሐዋርያው ጳውሎስ በ2ኛ የስብከት ጕዞው ከሲላስና ከጢሞቴዎስ ጋር ወደ ተሰሎንቄ ሄደ። ከተማይቱ በግሪክ አገር የመቄዶንያ አውራጃ ዋና ከተማና ታላቅ ወደብ ስትሆን፥ ወደ ምሥራቅ በሚወስደው በታላቁ የሮም መንገድ ላይ ትገኝ ነበር። ጳውሎስ በፊልጵስዩስ ከተማ ስደት ከደረሰበት በኋላ ወደ ተሰሎንቄ ደረሰ፤ እዚያም 3 ሳምንት ያህል አስተማረ፤ ሐ.ሥ. 17፥1-10፤ 1ተሰ. 2፥2።
ምንጭ፦ የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት፤ ገጽ 121
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍4
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ስንት ጊዜ ሐዋርያዊ ጉዞ አደረገ ተብሎ ይታመናል!
Anonymous Quiz
8%
ሀ. ሁለት
26%
ለ. አራት
18%
ሐ. ሰባት
37%
መ. ሶስት
9%
ሠ. አምስት
2%
ረ. አንድ
👍8