' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ያዕቆብ ሆይ፥ እስራኤልም ሆይ፦ መንገዴ ከእግዚአብሔር ተሰውራለች ፍርዴም ከአምላኬ አልፋለች ለምን ትላለህ? ለምንስ እንዲህ ትናገራለህ?”
ኢሳይያስ 40፥27
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ያዕቆብ ሆይ፥ እስራኤልም ሆይ፦ መንገዴ ከእግዚአብሔር ተሰውራለች ፍርዴም ከአምላኬ አልፋለች ለምን ትላለህ? ለምንስ እንዲህ ትናገራለህ?”
ኢሳይያስ 40፥27
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍5❤2😁1
የያዕቆብ ልጆች እና በረከቶቻቸው
ክፍል - ፩
፩. ሮቤል
ዘፍ. 49፥3-4፤ ዘዳ. 33፥6
ሮቤል የያዕቆብ የመጀመሪያ ልጅ ነው፡፡ ሮቤል የተወለደው ከልያ ሲሆን እግዚእብሔር መከራዋን እንዳየላትና ከዚህም በኋላ ያዕቆብ ይወደኛል ስትል ስሙን ሮቤል ብላ ጠራችው (ዘፍ. 29፥31-32)። ያዕቆብ ድብቅ ያልሆነ በገሃድ የመውደድ ፍቅሩን የገለጸው ለራሔል ስለ ነበር ልያ አስቀድማ ልጅ በመውለዷ የያዕቆብን የፍቅር ልብ እንደምታገኝ በመገመቷ የማህጸኗን መክፈቻና የመጀመሪያዋን ወንድ ልጅ ስም ከዚህ የተነሳ ሰየመችው፡፡ የስሙም ትርጓሜ እነሆ ወንድ ልጅ ማለት ነው፡፡ ወንድ ልጅ ሰጥቼሃለሁ፣ አንተም የፍቅር ልብህን አትንፈገኝ በማለት ልያ ለያዕቆብ ፍቅር መለመኛ እንዲሆናት ሮቤል መጠሪያውን አገኘ፡፡
ሮቤል ዮሴፍን ወንድሞቹ ሊያጠፉት በተነሱ ጊዜ ደም እንዳያፈሱ ነገር ግን በጉድጓድ እንዲጥሉት አደረገ (ዘፍ. 37፥22 )። በኋላም ወንድሞቹ ከጉድጓድ አውጥተው ሲሸጡት በአጠገባቸው እንዳልነበረና ከወንድሞቹም ተለይቶ ብቻውን ወደ ጉድጓዱ በተመለሰ ጊዜ ዮሴፍን እንዳጣው የእግዚአብሔር ቃል ይመስክራል (ዘፍ. 37፥29 ) ፡፡ ሮቤል በልቡ ያለውን ሰውሮ ሌሎቹ ከሚያደርጉት ጋር ይሄድ ስለ ነበር በኋላ በእንባ ቢጮህም ዮሴፍን ማዳን አልቻለም፡፡ እውነት ሊያስከፍል የሚችለውን ዋጋ ፊት ለፊት ከመክፈል ተሰውሮ በድብቅ በልቡ ያሰበውን መፈጸምን መረጠ፡፡ ብቻውንም በስውር ዮሴፍን አድናለሁ ብሎ ላሰበው ድርጊቱ ግን ሰዓት ስላለፈበት ጅብ ከሄደ ውሻ ጮኸ እንደሚሉት እንደ አገራችን ተረት ሆነበት፡፡ የወንድሞቹንም ክፋት ልክ ባለ ማወቁ ሊያደርግ ባስበው የልቡ ውሳኔ ላይ ፀሐይ ጠለቀችበት፡፡ ጊዜም አመለጠው፡፡
ብዙ ጊዜ ስናመነታ፤ ቀን ስላለ በሌላ ጊዜ እደርሳለሁ እያልን በምናስተላልፋቸው ብዙ ነገሮቻችን ላይ ሳናስብና ሳናውቅ ጊዜ አምልጦን ሁኔታዎችም ተለውጠው ራሳችንን እናገኛለን፡፡ በዚያን ሰዓት የጸጸት እንባ፣ የምሬት ጩኸት፣ የፀጉር መንጨት፤ የደረት መድቃት ባዶ እሪታ ብቻ ይሆናል፡፡ ቀን ሳለ ወይም ጊዜ ሳለ ማድረግ የሚገባንን ለማድረግ የታጠቅንና የቆረጥን ልንሆን ያስፈልጋል (ዮሐ.9፥4)::
ያዕቆብ ስለ ሮቤል ሲናገር እንዲህ አለ (ዘፍ. 49፥4)፦
1ኛ. ሮቤል አንተ የበኩር ልጄና ኃይሌ፥ የጉብዝናዬም መጀመሪያ ነህ
እግዚእብሔር ለአብርሃም፥ ለይስሐቅና በኋላም ለያዕቆብ በሰጠው የኪዳን ሐረግ የተስፋውን ቃል ለመሙላት ከያዕቆብ ልጆች ሮቤል በኩር ሆኖ ተወለደ፡፡ የነገድ መጀመሪያ፤ የበረከት መጀመሪያ፤ የአባቱ መተኪያና የአባቱ መጠሪያ እንዲሆን እነሆ ወንድ ልጅ ተወለደ፡፡ የበኩር ልጅ የአባትንና የእናትን ፍቅር ያለምንም ተሻሚ የሚጠግብ ልጅ ነው:: ከዚህም የተነሳ ያዕቆብ እነዚያን ቀናቶች እያስታወሰ ወንድ ልጅ ተወለደልህ የተባለለትን ቀን እያሰበ ኃይሌና የጉብዝናዬ መጀመሪያ ነህ እያለ የትዝታውን ማህደር ይፈትሻል፡፡ ከሮቤል መወለድ ጋር የያዕቆብ ትዝታ እርሱን ተክቶ በአብርሃም የተጀመረውን አዲስ ወገን የሚቀጥል ተኪ ሰው መገኘቱን አይቶ ልቡ በደስታ ይፍለቀለቅ እንደ ነበር መገመት አያስቸግርም፡፡ ትውልድን መተካት እንኳን በሰው ዘር በእንስሳትም ያለ ትልቅ የተፈጥሮ ግፈት ስለሆነ የመጀመሪያ የበኩር ልጁን ማግኘቱ የትውልድ ሐረጉ የመቀጠል ምልክቱ ስለሆነ ለደስታው መጠን አልነበረውም ነበር፡፡
2ኛ. የክብር አለቃና የኃይል አለቃ
የበኩር ልጅ በአባቱ እግር ተተክቶ አባቱ በነበረው ክብርና ኃይል የሚንቀሳቀስ፤ የሚገባና የሚወጣም ነው:: መጀመሪያ መወለድ በሚስጠው እድል ተጠቃሚ ስለሆነ የበኩር ልጅ የቤተስብ ድርሻው ሁልጊዜ ትልቅ ነው፡፡ በተለይ አባቱ በውርስ ሊያስተላልፍ የሚችለው የክብርና የኃይል ስፍራ ካለ በዚያ ስፍራ የመጀመሪያው ተተኪ ሆኖ የሚቀርበው የበኩር ልጅ ነው፡፡ በቀድሞው ዘመንና አሁንም በምድር ላይ የቀሩት ጥቂት ነገሥታት የመግዛት ዘመናቸው ሲያበቃ የግዛት በትራቸውንና ዙፋናቸውን የሚያስረክቡት ለመጀመሪያ ልጃቸው ነው::
ይህ ታላቅ መታደል ግን ለሁሉም የበኩር ልጅ በታሪክ ውስጥ ተከናውኗል ባይባልም የመጀመሪያ ልጆች ለዚህ መታደም አስቀድመው መታስባቸው የማይቀር የብኩርና ክብራቸው ነው::
ይቀጥላል...
ምንጭ፦ አበራ ጌታሁን (ዶ/ር)፤ የያዕቆብ ልጆች እና በረከቶቻቸው፤ ገጽ 4-6
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ክፍል - ፩
፩. ሮቤል
ዘፍ. 49፥3-4፤ ዘዳ. 33፥6
ሮቤል የያዕቆብ የመጀመሪያ ልጅ ነው፡፡ ሮቤል የተወለደው ከልያ ሲሆን እግዚእብሔር መከራዋን እንዳየላትና ከዚህም በኋላ ያዕቆብ ይወደኛል ስትል ስሙን ሮቤል ብላ ጠራችው (ዘፍ. 29፥31-32)። ያዕቆብ ድብቅ ያልሆነ በገሃድ የመውደድ ፍቅሩን የገለጸው ለራሔል ስለ ነበር ልያ አስቀድማ ልጅ በመውለዷ የያዕቆብን የፍቅር ልብ እንደምታገኝ በመገመቷ የማህጸኗን መክፈቻና የመጀመሪያዋን ወንድ ልጅ ስም ከዚህ የተነሳ ሰየመችው፡፡ የስሙም ትርጓሜ እነሆ ወንድ ልጅ ማለት ነው፡፡ ወንድ ልጅ ሰጥቼሃለሁ፣ አንተም የፍቅር ልብህን አትንፈገኝ በማለት ልያ ለያዕቆብ ፍቅር መለመኛ እንዲሆናት ሮቤል መጠሪያውን አገኘ፡፡
ሮቤል ዮሴፍን ወንድሞቹ ሊያጠፉት በተነሱ ጊዜ ደም እንዳያፈሱ ነገር ግን በጉድጓድ እንዲጥሉት አደረገ (ዘፍ. 37፥22 )። በኋላም ወንድሞቹ ከጉድጓድ አውጥተው ሲሸጡት በአጠገባቸው እንዳልነበረና ከወንድሞቹም ተለይቶ ብቻውን ወደ ጉድጓዱ በተመለሰ ጊዜ ዮሴፍን እንዳጣው የእግዚአብሔር ቃል ይመስክራል (ዘፍ. 37፥29 ) ፡፡ ሮቤል በልቡ ያለውን ሰውሮ ሌሎቹ ከሚያደርጉት ጋር ይሄድ ስለ ነበር በኋላ በእንባ ቢጮህም ዮሴፍን ማዳን አልቻለም፡፡ እውነት ሊያስከፍል የሚችለውን ዋጋ ፊት ለፊት ከመክፈል ተሰውሮ በድብቅ በልቡ ያሰበውን መፈጸምን መረጠ፡፡ ብቻውንም በስውር ዮሴፍን አድናለሁ ብሎ ላሰበው ድርጊቱ ግን ሰዓት ስላለፈበት ጅብ ከሄደ ውሻ ጮኸ እንደሚሉት እንደ አገራችን ተረት ሆነበት፡፡ የወንድሞቹንም ክፋት ልክ ባለ ማወቁ ሊያደርግ ባስበው የልቡ ውሳኔ ላይ ፀሐይ ጠለቀችበት፡፡ ጊዜም አመለጠው፡፡
ብዙ ጊዜ ስናመነታ፤ ቀን ስላለ በሌላ ጊዜ እደርሳለሁ እያልን በምናስተላልፋቸው ብዙ ነገሮቻችን ላይ ሳናስብና ሳናውቅ ጊዜ አምልጦን ሁኔታዎችም ተለውጠው ራሳችንን እናገኛለን፡፡ በዚያን ሰዓት የጸጸት እንባ፣ የምሬት ጩኸት፣ የፀጉር መንጨት፤ የደረት መድቃት ባዶ እሪታ ብቻ ይሆናል፡፡ ቀን ሳለ ወይም ጊዜ ሳለ ማድረግ የሚገባንን ለማድረግ የታጠቅንና የቆረጥን ልንሆን ያስፈልጋል (ዮሐ.9፥4)::
ያዕቆብ ስለ ሮቤል ሲናገር እንዲህ አለ (ዘፍ. 49፥4)፦
1ኛ. ሮቤል አንተ የበኩር ልጄና ኃይሌ፥ የጉብዝናዬም መጀመሪያ ነህ
እግዚእብሔር ለአብርሃም፥ ለይስሐቅና በኋላም ለያዕቆብ በሰጠው የኪዳን ሐረግ የተስፋውን ቃል ለመሙላት ከያዕቆብ ልጆች ሮቤል በኩር ሆኖ ተወለደ፡፡ የነገድ መጀመሪያ፤ የበረከት መጀመሪያ፤ የአባቱ መተኪያና የአባቱ መጠሪያ እንዲሆን እነሆ ወንድ ልጅ ተወለደ፡፡ የበኩር ልጅ የአባትንና የእናትን ፍቅር ያለምንም ተሻሚ የሚጠግብ ልጅ ነው:: ከዚህም የተነሳ ያዕቆብ እነዚያን ቀናቶች እያስታወሰ ወንድ ልጅ ተወለደልህ የተባለለትን ቀን እያሰበ ኃይሌና የጉብዝናዬ መጀመሪያ ነህ እያለ የትዝታውን ማህደር ይፈትሻል፡፡ ከሮቤል መወለድ ጋር የያዕቆብ ትዝታ እርሱን ተክቶ በአብርሃም የተጀመረውን አዲስ ወገን የሚቀጥል ተኪ ሰው መገኘቱን አይቶ ልቡ በደስታ ይፍለቀለቅ እንደ ነበር መገመት አያስቸግርም፡፡ ትውልድን መተካት እንኳን በሰው ዘር በእንስሳትም ያለ ትልቅ የተፈጥሮ ግፈት ስለሆነ የመጀመሪያ የበኩር ልጁን ማግኘቱ የትውልድ ሐረጉ የመቀጠል ምልክቱ ስለሆነ ለደስታው መጠን አልነበረውም ነበር፡፡
2ኛ. የክብር አለቃና የኃይል አለቃ
የበኩር ልጅ በአባቱ እግር ተተክቶ አባቱ በነበረው ክብርና ኃይል የሚንቀሳቀስ፤ የሚገባና የሚወጣም ነው:: መጀመሪያ መወለድ በሚስጠው እድል ተጠቃሚ ስለሆነ የበኩር ልጅ የቤተስብ ድርሻው ሁልጊዜ ትልቅ ነው፡፡ በተለይ አባቱ በውርስ ሊያስተላልፍ የሚችለው የክብርና የኃይል ስፍራ ካለ በዚያ ስፍራ የመጀመሪያው ተተኪ ሆኖ የሚቀርበው የበኩር ልጅ ነው፡፡ በቀድሞው ዘመንና አሁንም በምድር ላይ የቀሩት ጥቂት ነገሥታት የመግዛት ዘመናቸው ሲያበቃ የግዛት በትራቸውንና ዙፋናቸውን የሚያስረክቡት ለመጀመሪያ ልጃቸው ነው::
ይህ ታላቅ መታደል ግን ለሁሉም የበኩር ልጅ በታሪክ ውስጥ ተከናውኗል ባይባልም የመጀመሪያ ልጆች ለዚህ መታደም አስቀድመው መታስባቸው የማይቀር የብኩርና ክብራቸው ነው::
ይቀጥላል...
ምንጭ፦ አበራ ጌታሁን (ዶ/ር)፤ የያዕቆብ ልጆች እና በረከቶቻቸው፤ ገጽ 4-6
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍4❤3
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ከክፉ ሰዎችም እጅ እታደግሃለሁ፥ ከጨካኞችም ጡጫ እቤዥሃለሁ።”
ኤርምያስ 15፥21
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ከክፉ ሰዎችም እጅ እታደግሃለሁ፥ ከጨካኞችም ጡጫ እቤዥሃለሁ።”
ኤርምያስ 15፥21
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤6👍5
❤8👍3👏1
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“የሚታገልም ሁሉ በነገር ሁሉ ሰውነቱን ይገዛል፤ እነዚያም የሚጠፋውን አክሊል ሊያገኙ ነው፥ እኛ ግን የማይጠፋውን።”
1ኛ ቆሮንቶስ 9፥25
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“የሚታገልም ሁሉ በነገር ሁሉ ሰውነቱን ይገዛል፤ እነዚያም የሚጠፋውን አክሊል ሊያገኙ ነው፥ እኛ ግን የማይጠፋውን።”
1ኛ ቆሮንቶስ 9፥25
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤3👍2
#እራሳችንን_እንመርምር
በዘመናችን ምን ማድረግ እንዳለብን እናውቃለን ወይስ በደመነፍስ ነው የምንኖረው? እሺ በዘመናችን ምን ማድረግ እንዳለብን ካወቅንስ፣ ላወቅነው ነገር እየታዘዝን ነው?
“እስራኤልም የሚገባውን ያደርግ ዘንድ ዘመኑን የሚያውቁ ጥበበኞች ሰዎች የይሳኮር ልጆች አለቆች ሁለት መቶ ነበሩ፤ ወንድሞቻቸውም ሁሉ ይታዘዙአቸው ነበር።”
1 ዜና 12፥32
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
በዘመናችን ምን ማድረግ እንዳለብን እናውቃለን ወይስ በደመነፍስ ነው የምንኖረው? እሺ በዘመናችን ምን ማድረግ እንዳለብን ካወቅንስ፣ ላወቅነው ነገር እየታዘዝን ነው?
“እስራኤልም የሚገባውን ያደርግ ዘንድ ዘመኑን የሚያውቁ ጥበበኞች ሰዎች የይሳኮር ልጆች አለቆች ሁለት መቶ ነበሩ፤ ወንድሞቻቸውም ሁሉ ይታዘዙአቸው ነበር።”
1 ዜና 12፥32
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤5
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ንጋትም በሆነ ጊዜ እግዚአብሔር በእሳትና በደመና ዓምድ ሆኖ የግብፃውያንን ሠራዊት ተመለከተ፥ የግብፃውያንንም ሠራዊት አወከ።”
ዘጸአት 14፥24
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ንጋትም በሆነ ጊዜ እግዚአብሔር በእሳትና በደመና ዓምድ ሆኖ የግብፃውያንን ሠራዊት ተመለከተ፥ የግብፃውያንንም ሠራዊት አወከ።”
ዘጸአት 14፥24
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍3❤2
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ነገር ግን እግዚአብሔር ስለ ወደዳችሁ ለአባቶቻችሁም የማለላቸውን መሐላ ስለ ጠበቀ፥ ስለዚህ እግዚአብሔር በጽኑ እጅ አወጣችሁ፥ ከባርነትም ቤት ከግብፅ ንጉሥ ከፈርዖን እጅ አዳናችሁ።”
ዘዳግም 7፥8
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ነገር ግን እግዚአብሔር ስለ ወደዳችሁ ለአባቶቻችሁም የማለላቸውን መሐላ ስለ ጠበቀ፥ ስለዚህ እግዚአብሔር በጽኑ እጅ አወጣችሁ፥ ከባርነትም ቤት ከግብፅ ንጉሥ ከፈርዖን እጅ አዳናችሁ።”
ዘዳግም 7፥8
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤3👍2
#የእግዚአብሔር_ቃል_ምን_ይላል?
2ኛ ጴጥሮስ 1
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
²-³ የመለኮቱ ኃይል፥ በገዛ ክብሩና በበጎነቱ የጠራንን በማወቅ፥ ለሕይወትና እግዚአብሔርን ለመምሰል የሚሆነውን ነገር ሁሉ ስለ ሰጠን፥ በእግዚአብሔርና በጌታችን በኢየሱስ እውቀት ጸጋና ሰላም ይብዛላችሁ።
⁴ ስለ ክፉ ምኞት በዓለም ካለው ጥፋት አምልጣችሁ ከመለኮት ባሕርይ ተካፋዮች በተስፋ ቃል እንድትሆኑ፥ በእነዚያ ክብርና በጎነት የተከበረና እጅግ ታላቅ የሆነ ተስፋን ሰጠን።
⁵ ስለዚህም ምክንያት ትጋትን ሁሉ እያሳያችሁ በእምነታችሁ በጎነትን ጨምሩ፥
⁶ በበጎነትም እውቀትን፥ በእውቀትም ራስን መግዛት፥ ራስንም በመግዛት መጽናትን፥ በመጽናትም እግዚአብሔርን መምሰል፥
⁷ እግዚአብሔርንም በመምሰል የወንድማማችን መዋደድ፥ በወንድማማችም መዋደድ ፍቅርን ጨምሩ።
⁸ እነዚህ ነገሮች ለእናንተ ሆነው ቢበዙ፥ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ እውቀት ሥራ ፈቶችና ፍሬ ቢሶች እንዳትሆኑ ያደርጉአችኋልና፤
⁹ እነዚህ ነገሮች የሌሉት ዕውር ነውና፥ በቅርብም ያለውን ብቻ ያያል፥ የቀደመውንም ኃጢአቱን መንጻት ረስቶአል።
¹⁰ ስለዚህ፥ ወንድሞች ሆይ፥ መጠራታችሁንና መመረጣችሁን ታጸኑ ዘንድ ከፊት ይልቅ ትጉ፤ እነዚህን ብታደርጉ ከቶ አትሰናከሉምና።
¹¹ እንዲሁ ወደ ዘላለሙ ወደ ጌታችንና መድኃኒታችን ወደ ኢየሱስ ክርስቶስ መንግሥት መግባት በሙላት ይሰጣችኋልና።
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
2ኛ ጴጥሮስ 1
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
²-³ የመለኮቱ ኃይል፥ በገዛ ክብሩና በበጎነቱ የጠራንን በማወቅ፥ ለሕይወትና እግዚአብሔርን ለመምሰል የሚሆነውን ነገር ሁሉ ስለ ሰጠን፥ በእግዚአብሔርና በጌታችን በኢየሱስ እውቀት ጸጋና ሰላም ይብዛላችሁ።
⁴ ስለ ክፉ ምኞት በዓለም ካለው ጥፋት አምልጣችሁ ከመለኮት ባሕርይ ተካፋዮች በተስፋ ቃል እንድትሆኑ፥ በእነዚያ ክብርና በጎነት የተከበረና እጅግ ታላቅ የሆነ ተስፋን ሰጠን።
⁵ ስለዚህም ምክንያት ትጋትን ሁሉ እያሳያችሁ በእምነታችሁ በጎነትን ጨምሩ፥
⁶ በበጎነትም እውቀትን፥ በእውቀትም ራስን መግዛት፥ ራስንም በመግዛት መጽናትን፥ በመጽናትም እግዚአብሔርን መምሰል፥
⁷ እግዚአብሔርንም በመምሰል የወንድማማችን መዋደድ፥ በወንድማማችም መዋደድ ፍቅርን ጨምሩ።
⁸ እነዚህ ነገሮች ለእናንተ ሆነው ቢበዙ፥ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ እውቀት ሥራ ፈቶችና ፍሬ ቢሶች እንዳትሆኑ ያደርጉአችኋልና፤
⁹ እነዚህ ነገሮች የሌሉት ዕውር ነውና፥ በቅርብም ያለውን ብቻ ያያል፥ የቀደመውንም ኃጢአቱን መንጻት ረስቶአል።
¹⁰ ስለዚህ፥ ወንድሞች ሆይ፥ መጠራታችሁንና መመረጣችሁን ታጸኑ ዘንድ ከፊት ይልቅ ትጉ፤ እነዚህን ብታደርጉ ከቶ አትሰናከሉምና።
¹¹ እንዲሁ ወደ ዘላለሙ ወደ ጌታችንና መድኃኒታችን ወደ ኢየሱስ ክርስቶስ መንግሥት መግባት በሙላት ይሰጣችኋልና።
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍7❤2
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ወድጃቸዋለሁና የይሁዳን ቤት አበረታለሁ፥ የዮሴፍንም ቤት አድናለሁ፤ አደላድላቸዋለሁም፤ እመልሳቸዋለሁ፤ እኔም አምላካቸው እግዚአብሔር ነኝና፥ እኔም እሰማቸዋለሁና እንዳልጣልኋቸው ይሆናሉ።”
ዘካርያስ 10፥6
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ወድጃቸዋለሁና የይሁዳን ቤት አበረታለሁ፥ የዮሴፍንም ቤት አድናለሁ፤ አደላድላቸዋለሁም፤ እመልሳቸዋለሁ፤ እኔም አምላካቸው እግዚአብሔር ነኝና፥ እኔም እሰማቸዋለሁና እንዳልጣልኋቸው ይሆናሉ።”
ዘካርያስ 10፥6
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍5❤1👏1
#የሮሜ_መልእክት_ጥናት
ሮሜ 9፥1-5
1-3. ስለምን ጳውሎስ ይህን የሚያህል ታላቅ ሐዘንና የማያቋርጥ ጭንቀት ሊኖረው ቻለ? ምክንያቱም የራሱ ዘር ከሆኑት ከአይሁዳውያን ብዙዎቹ ገና በኢየሱስ ክርስቶስ አላመኑም ነበር። ምንም እንኳ፥ አይሁዳውያን ልዩና የእግዚአብሔር ምርጥ ሕዝብ ቢሆኑም፤ ባለማመናቸው ምክንያት የደኅንነትን ምቹ ጊዜ አጥተዋል። ክርስቶስ የመጣው በመጀመሪያ ለአይሁዳውያን አዳኝ በመሆን ነበር (ማቴ. 15፥24፤ ሮሜ 1፥16)፤ ነገር ግን ብዙዎቹ አልተቀበሉትም፤ ስለሆነም ወንጌል ለአረማውያን ተሰበከ። ጳውሎስ ራሱ ለአረማውያን ሐዋርያ እንዲሆን እግዚአብሔር በተለየ ሁኔታ መረጠው (የሐዋ. 9፥15፤ ገላ. 2፥8)። በዚህ ሁኔታ አረማውያን በክርስቶስ ማመን ጀመሩ፤ በጥቂት ዓመታት ውስጥ ከአይሁዳውያን ክርስቲያኖች ይልቅ በጣም ብዙ አረማውያን ክርስቲያኖች ነበሩ።
ጳውሎስ የተረገመ እስከሚሆን በመመኘት በጣም ታላቅ ሐዘን በልቡ ነበር። ይህም አይሁዳውያን ወንድሞቹ የሚድኑ ቢሆን፥ በአንፃሩ ማለት እርሱ የተረገመ መሆንን ይመርጥ ነበር። ጳውሎስ ለሌሎች ሰዎች የነበረው ፍቅርና የሃላፊነት ስሜት በጣም ታላቅ ከመሆኑ የተነሣ ለእነርሱ ሲል የዘላለም ደኅንነትን ቢያጣ ይወድ ነበር። በብሉይ ኪዳን ታላቁ የአይሁድ መሪ ሙሴ ተመሳሳይ ነገር ለማድረግ ራሱን አሳልፎ ሰጥቷል፤ ይኸውም የአይሁድን ሕዝብ ከእግዚአብሔር ቁጣ ለማዳን ሲል ራሱ ቢጠፋ ፈልጎ ነበር (ዘጸ. 32፥30-32)።
4. ጳውሎስ እዚህ ላይ አይሁዳውያንን የእስራኤል ሕዝብ ይላቸዋል። እስራኤል የአይሁድ ሕዝብ የመጀመሪያ ስም ነው፤ አይሁዳውያንም እስራኤላውያን ይባሉ ነበር (ሮሜ 10፥1)። እግዚአብሔር የራሱ ልዩ ሕዝብ እንዲሆኑ እስራኤልን መረጠ፤ እንደ ልጅ አድርጎም ተቀበላቸው፤ መብትም ሰጣቸው። መለኮታዊ ክብር፥ የልጅነትን ማለትም የእግዚአብሔር መገኘት ከእነርሱ ጋር ነበር። እግዚአብሔር የራሱን ቃል ኪዳን ለአይሁዳውያን ሰጥቷቸዋል። በተለይም ከመጀመሪያው አይሁዳዊ ከአብርሃም ጋር ቃል ኪዳን ገብቶ ነበር (ዘፍ. 17፥3-8)። እግዚአብሔር የራሱንም ሕግ ለአይሁዳውያን ሰጥቷቸዋል በዚህም ሕግ የራሱን ፈቃድ ገልጦላቸው ነበር። ክርስቶስ የሚባል አዳኝ እንደሚልክላቸው የሚያስረዱ ተስፋዎችንም ሰጥቶአቸው ነበር። ልክ አብርሃም በእምነቱ ምክንያት ጻድቅ ተብሎ እንደተጠራ ሁሉ (ዘፍ. 15፥6) አይሁዳውያንም እምነታቸውን በክርስቶስ ላይ ቢያደርጉ ጻድቃን ተብለው ይጠራሉ፤ ደኅንነትንም ይቀበላሉ።
5. ክርስቶስ ራሱ ከአይሁድ አባቶች ማለትም ከአብርሃም፥ ከይስሐቅ፥ ከያዕቆብና ከይሁዳ ሲወርድ ሲዋረድ የመጣ አይሁዳዊ ነበር (ማቴ. 1፥1-2)። በእርግጥ እስራኤል በእግዚአብሔር የተባረከ ነገድ ነው።
እዚህ ላይ ጳውሎስ ስለ ክርስቶስ አንድ ቃል መጨመር ተገድዶአል፤ ይኸውም ክርስቶስ በሁሉም ላይ አምላክ እንደሆነ ነው። ክርስቶስ አንድ ታላቅ ሰው ብቻ እንዳልሆነ ሁልጊዜ ማስታወስ ይገባናል፤ ነገር ግን ታላቅ መሪ፥ ነቢይና አስተማሪም ነበር። እንዲውም ራሱ አምላክ ነው፤ በሁሉም ላይ አምላክ ነው።
ምንጭ፦ የአዲስ ኪዳን ማብራሪያ ፤ ገጽ 371
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ሮሜ 9፥1-5
1-3. ስለምን ጳውሎስ ይህን የሚያህል ታላቅ ሐዘንና የማያቋርጥ ጭንቀት ሊኖረው ቻለ? ምክንያቱም የራሱ ዘር ከሆኑት ከአይሁዳውያን ብዙዎቹ ገና በኢየሱስ ክርስቶስ አላመኑም ነበር። ምንም እንኳ፥ አይሁዳውያን ልዩና የእግዚአብሔር ምርጥ ሕዝብ ቢሆኑም፤ ባለማመናቸው ምክንያት የደኅንነትን ምቹ ጊዜ አጥተዋል። ክርስቶስ የመጣው በመጀመሪያ ለአይሁዳውያን አዳኝ በመሆን ነበር (ማቴ. 15፥24፤ ሮሜ 1፥16)፤ ነገር ግን ብዙዎቹ አልተቀበሉትም፤ ስለሆነም ወንጌል ለአረማውያን ተሰበከ። ጳውሎስ ራሱ ለአረማውያን ሐዋርያ እንዲሆን እግዚአብሔር በተለየ ሁኔታ መረጠው (የሐዋ. 9፥15፤ ገላ. 2፥8)። በዚህ ሁኔታ አረማውያን በክርስቶስ ማመን ጀመሩ፤ በጥቂት ዓመታት ውስጥ ከአይሁዳውያን ክርስቲያኖች ይልቅ በጣም ብዙ አረማውያን ክርስቲያኖች ነበሩ።
ጳውሎስ የተረገመ እስከሚሆን በመመኘት በጣም ታላቅ ሐዘን በልቡ ነበር። ይህም አይሁዳውያን ወንድሞቹ የሚድኑ ቢሆን፥ በአንፃሩ ማለት እርሱ የተረገመ መሆንን ይመርጥ ነበር። ጳውሎስ ለሌሎች ሰዎች የነበረው ፍቅርና የሃላፊነት ስሜት በጣም ታላቅ ከመሆኑ የተነሣ ለእነርሱ ሲል የዘላለም ደኅንነትን ቢያጣ ይወድ ነበር። በብሉይ ኪዳን ታላቁ የአይሁድ መሪ ሙሴ ተመሳሳይ ነገር ለማድረግ ራሱን አሳልፎ ሰጥቷል፤ ይኸውም የአይሁድን ሕዝብ ከእግዚአብሔር ቁጣ ለማዳን ሲል ራሱ ቢጠፋ ፈልጎ ነበር (ዘጸ. 32፥30-32)።
4. ጳውሎስ እዚህ ላይ አይሁዳውያንን የእስራኤል ሕዝብ ይላቸዋል። እስራኤል የአይሁድ ሕዝብ የመጀመሪያ ስም ነው፤ አይሁዳውያንም እስራኤላውያን ይባሉ ነበር (ሮሜ 10፥1)። እግዚአብሔር የራሱ ልዩ ሕዝብ እንዲሆኑ እስራኤልን መረጠ፤ እንደ ልጅ አድርጎም ተቀበላቸው፤ መብትም ሰጣቸው። መለኮታዊ ክብር፥ የልጅነትን ማለትም የእግዚአብሔር መገኘት ከእነርሱ ጋር ነበር። እግዚአብሔር የራሱን ቃል ኪዳን ለአይሁዳውያን ሰጥቷቸዋል። በተለይም ከመጀመሪያው አይሁዳዊ ከአብርሃም ጋር ቃል ኪዳን ገብቶ ነበር (ዘፍ. 17፥3-8)። እግዚአብሔር የራሱንም ሕግ ለአይሁዳውያን ሰጥቷቸዋል በዚህም ሕግ የራሱን ፈቃድ ገልጦላቸው ነበር። ክርስቶስ የሚባል አዳኝ እንደሚልክላቸው የሚያስረዱ ተስፋዎችንም ሰጥቶአቸው ነበር። ልክ አብርሃም በእምነቱ ምክንያት ጻድቅ ተብሎ እንደተጠራ ሁሉ (ዘፍ. 15፥6) አይሁዳውያንም እምነታቸውን በክርስቶስ ላይ ቢያደርጉ ጻድቃን ተብለው ይጠራሉ፤ ደኅንነትንም ይቀበላሉ።
5. ክርስቶስ ራሱ ከአይሁድ አባቶች ማለትም ከአብርሃም፥ ከይስሐቅ፥ ከያዕቆብና ከይሁዳ ሲወርድ ሲዋረድ የመጣ አይሁዳዊ ነበር (ማቴ. 1፥1-2)። በእርግጥ እስራኤል በእግዚአብሔር የተባረከ ነገድ ነው።
እዚህ ላይ ጳውሎስ ስለ ክርስቶስ አንድ ቃል መጨመር ተገድዶአል፤ ይኸውም ክርስቶስ በሁሉም ላይ አምላክ እንደሆነ ነው። ክርስቶስ አንድ ታላቅ ሰው ብቻ እንዳልሆነ ሁልጊዜ ማስታወስ ይገባናል፤ ነገር ግን ታላቅ መሪ፥ ነቢይና አስተማሪም ነበር። እንዲውም ራሱ አምላክ ነው፤ በሁሉም ላይ አምላክ ነው።
ምንጭ፦ የአዲስ ኪዳን ማብራሪያ ፤ ገጽ 371
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍1
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ሕዝቡም ወጥቶ የሶርያውያንን ሰፈር በዘበዘ፤ እንደ እግዚአብሔርም ቃል አንድ መስፈሪያ መልካም ዱቄት በአንድ ሰቅል፥ ሁለትም መስፈሪያ ገብስ በአንድ ሰቅል ተሸመተ።”
2ኛ ነገሥት 7፥16
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ሕዝቡም ወጥቶ የሶርያውያንን ሰፈር በዘበዘ፤ እንደ እግዚአብሔርም ቃል አንድ መስፈሪያ መልካም ዱቄት በአንድ ሰቅል፥ ሁለትም መስፈሪያ ገብስ በአንድ ሰቅል ተሸመተ።”
2ኛ ነገሥት 7፥16
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤1👍1
የመፅሐፍ_ቅዱስ_ማጥኛ_እቅድ_bible_reading.pdf
182.9 KB
መጽሐፍ ቅዱስን በአንድ ዓመት ውስጥ አጥንቶ ለመጨረስ የሚረዳ የጥናት እቅድ
👉 እያንዳንዱ ወር 25 የማጥኛ ቀናቶች አሉት:: ቀሪዎቹ 5 ቀናት ምናልባትም
የተዘለለ ቀን ካለ ወይም ለክለሳ የሚሆን ነው::
👉 እያንዳንዱ ቀን ከ ብሉይ ኪዳን እና ከ አዲስ ኪዳን ሁለቱንም ያጠቃለለ ሲሆን
የመፅሐፍ ቅዱስ ውህደቱንም በሚገባ እንድንረዳ ይረዳናል::
👉ይሄ pdf የተዘጋጀው ከ JUNE - M A Y /ሰኔ-ግንቦት) ግን ከማንኛውም ወር መጀመር ይቻላል::
በአክሊሉ ተፈራ
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👉 እያንዳንዱ ወር 25 የማጥኛ ቀናቶች አሉት:: ቀሪዎቹ 5 ቀናት ምናልባትም
የተዘለለ ቀን ካለ ወይም ለክለሳ የሚሆን ነው::
👉 እያንዳንዱ ቀን ከ ብሉይ ኪዳን እና ከ አዲስ ኪዳን ሁለቱንም ያጠቃለለ ሲሆን
የመፅሐፍ ቅዱስ ውህደቱንም በሚገባ እንድንረዳ ይረዳናል::
👉ይሄ pdf የተዘጋጀው ከ JUNE - M A Y /ሰኔ-ግንቦት) ግን ከማንኛውም ወር መጀመር ይቻላል::
በአክሊሉ ተፈራ
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍5
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ኢዮአታምም በአምላኩ በእግዚአብሔር ፊት መንገዱን አቅንቶአልና በረታ።”
2 ዜና 27፥6
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ኢዮአታምም በአምላኩ በእግዚአብሔር ፊት መንገዱን አቅንቶአልና በረታ።”
2 ዜና 27፥6
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤1
የስሙ ትርጉም "እግዚአብሔር አምላኬ ነው" የሆነው የቱ ነው?
Anonymous Quiz
33%
ሀ. ኤልያስ
11%
ለ. ኤርምያስ
15%
ሐ. ኢሳይያስ
23%
መ. ዳንኤል
18%
ሠ. ሕዝቅኤል
❤3👍2😁1
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“አብርሃምም በግምባሩ ወደቀ፥ ሳቀም፥ በልቡም አለ፦ የመቶ ዓመት ሰው በውኑ ልጅ ይወልዳልን? ዘጠና ዓመት የሆናትም ሣራ ትወልዳለችን?”
ዘፍጥረት 17፥17
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“አብርሃምም በግምባሩ ወደቀ፥ ሳቀም፥ በልቡም አለ፦ የመቶ ዓመት ሰው በውኑ ልጅ ይወልዳልን? ዘጠና ዓመት የሆናትም ሣራ ትወልዳለችን?”
ዘፍጥረት 17፥17
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍6❤1
የያዕቆብ ልጆች እና በረከቶቻቸው
ክፍል - ፪
3ኛ. እንደ ውኃ የምትዋልል ነህ፤ አለቅነት ለአንተ አይሁን፤ ወደ አባትህ መኝታ ወጥተሃልና አረከሰኸው፣ ወደ አልጋዬም ወጣ
በበኩርነት መብቱ ተገብቶት የነበረውን የክብርና የኃይል አለቅነት፤ በኃይልና በብርታት በአባቱ እግር ተተክቶ ወገኑን የመምራት ሥልጣኑን ሮቤል እዚህ ስፍራ ይነጠቃል፡፡ የበኩርነቱን ስፍራ የማጣቱን ምክንያት ያዕቆብ በሁለት ነገሮች ይጠቀልለዋል፡፡ እነዚህም ሁለት ነገሮች አንዱ ባህሪውን ሌላው ደግሞ ድርጊቱን የሚያካትቱ ናቸው::
ሀ. እንደ ውኃ የምትዋልል ነህ
ውኃ ፈሳሽ ስለሆነ ቁልቁለት ወዳለበትና ወደ ተመቸው ይፈሳል፡፡ የነፋስም ጉልበት ያንቀሳቅሰዋል፡፡ ወዲያና ወዲህም ያፈሰዋል፡፡ ውኃ በፈሳሽነት ባህሪው ምክንያት የራሱ የሆነ ቅርጽ የለውም፡፡ ውኃ ሊኖረው የሚችለው ቅርጽ ውኃው የተቀመጠበት ዕቃ ቅርጽ ነው፡፡ በብርጭቆ ውስጥ ያለ ውኃ የብርጭቆውን ቅርጽ ይይዛል፡፡ በኮካ ኮላና በአንቦ ውኃ ጠርሙሶች ውስጥ የተቀመጡ ፈሳሾች የጠርሙሱን ቅርጽ ይዘው ይቀመጣሉ፡፡ ከየጠርሙሶቻቸው ውስጥ ግን ሊወጡ የመሬትን ስበት እየተከተሉ ቁልቁል ወዳለበት ለመፍስስ ይፈጥናሉ፡፡ ስለዚህ ውኃ የርሱ የሆነና የኔ ነው የሚለው፤ የሚታወቅበትና የሚጠራበትም ቅርጽ የሌለው ፈሳች ስለሆነ በቅርጽ ባህሪ ስለሚገለጥ መልክ ስለ ውኃ መናገር አይቻልም፡፡
እንደ ውኃ የሚዋልል ልብ ያለው፥ በልቡም ባለ አሳብ መቆምና መቁረጥ የማይችል ሰው ብርቱ መሪና አለቃ ሆኖ መገኘት ያስቸግረዋል፡፡ ዮሴፍን እንኳ ከጨከኑበት ወንድሞቹ እጅ ለማዳን ሮቤል የልቡን አሳብ ደብቆ በሽፋን ቋንቋ ወንድሞቹን ሲናገር ተመልክተናል (ዘፍ.37፥22-29)፡፡ እንደ ውኃ የሚዋልል ልብ ያለውን መደገፍና ማመን አይቻልም፡፡ ደግፎ የመሸከም ጉልበቱ ቶሎ ስለሚከዳው የተደገፈበትን ሁሉ ይጎዳል፡፡ የራሳቸው አሳብ የሌላቸው፤ የሚሠሩትንና የሚያደርጉትን ሁሉ ሌሎች የሚያቀርቡላቸው፤ እንደ ነገሩአቸው ብቻ እንጂ ተጨማሪን ነገር የማያሰቡ፥ የመምራት አቅም ስለማይኖራቸው የመሪነት ቦታ ላይ እንኳ ቢቀመጡ ጊዜያቸው አጭር ይሆናል፡፡ ሮብዓም የሚባል የእስራኤል ንጉሥ መንገሥ በጀመረ ጊዜ ከሕዝቡ ለገጠመው ጥያቄ ምክርን ከሁለት ወገን ጠየቀ፡፡ ሁለቱም ወገኖች የሰጡት ምክር አንዱ ከሌላው አጅግ የተለያየ ሆነ፡፡ በእንዲህ ያለ ጊዜ ጥሩ መሪና የራሱም አሳብ ያለው አሰተዳዳሪ ከሁለቱም ወገኖች የተሰጡትን ምክሮች መርምሮ፤ ለምንም እንዲህ ሊለያዩ እንደቻሉ አጢኖ ዳኝነት መሰጠት ሲገባው ያልሆነውን ምክር በመሰማቱ የሕዝቡን ልብ አሳዘነ፡፡ በኋላም ከዚህ ክፉ ምክር የተነሳ የመንግሥቱ ግዛትና የእሰራኤልም ሕዝብ በእጠቃላይ ለሁለት እንዲከፈል ምክንያት ሆነ (1ኛ ነገ. 12፥1 - 15 )።
እንዲህም ባለ የልብ መዋለል ባህሪው ምክንያት የክብርና የኃይል አለቅነት የተገባው ሮቤል ብኩርናው ተወሰደበት፡፡ ብኩርናውም ለዮሴፍ ልጆመች እንደተሰጠ የእግዚአብሔር ቃል ይመሰከራል (1ኛ ዜና. 5፥1፡ ዘፍ. 48፥5)፡፡ የበኩር ልጅን በረከት ማጣት ምንነት ለሮቤል አዲስ ነገር አይመስለኝም፡፡ ወይም ደግሞ የሩቅ ዘመን ጨዋታና ትውስታ ብቻ አይደለም፡፡ አጎቱ የሆነው የአባቱ ታላቅ ወንድም እንዴት አድርጎ ብኩርናውን በትንሽ ነገርና ጥቂት ቢታገሰ ሊያልፍ በሚችል ነገር አንደ ለወጠው ለእርሱ ድብቅ ምሥጢር አይደለም (ዘፍ. 25፥27-34)፡፡ ነገር ካለፈና የሆዱ ረሃብም ከታገሰለት በኋሳ ዔሳው ብኩርናውን በብዙ እንባም ቢፈልገው መልሶ ሊያገኘው አልቻለም (ዕብ. 12፥16-17)፡፡ ሊመለስ በማይችል ነገር ላይ እንባና ጩኸት ትርፉ ጉዳት ብቻ በመሆኑ የዔሳውም ጸጸት ዘመኑን ሁሉ ሊከተለው ኖረ።
ዲቦራና ባርቅ በዝማሬ ቅኔያቸው ስለ እስራኤል ነገዶች በተቀኙ ጊዜ ስለ ሮቤል ልብ መዋለልና እንደ ውኃ መፍሰስ እንዲህ በማለት ገለጹ፦ “በሮቤል ፈሳሾች አጠገብ ብዙ የልብ ማመንታት ነበረ...በሮቤል ፈሳሾች አጠገብ ታላቅ የልብ ምርምር ነበረ” (መሳ. 5፥15-16)::
ይቀጥላል...
ምንጭ፦ አበራ ጌታሁን (ዶ/ር)፤ የያዕቆብ ልጆች እና በረከቶቻቸው፤ ገጽ 6-8
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ክፍል - ፪
3ኛ. እንደ ውኃ የምትዋልል ነህ፤ አለቅነት ለአንተ አይሁን፤ ወደ አባትህ መኝታ ወጥተሃልና አረከሰኸው፣ ወደ አልጋዬም ወጣ
በበኩርነት መብቱ ተገብቶት የነበረውን የክብርና የኃይል አለቅነት፤ በኃይልና በብርታት በአባቱ እግር ተተክቶ ወገኑን የመምራት ሥልጣኑን ሮቤል እዚህ ስፍራ ይነጠቃል፡፡ የበኩርነቱን ስፍራ የማጣቱን ምክንያት ያዕቆብ በሁለት ነገሮች ይጠቀልለዋል፡፡ እነዚህም ሁለት ነገሮች አንዱ ባህሪውን ሌላው ደግሞ ድርጊቱን የሚያካትቱ ናቸው::
ሀ. እንደ ውኃ የምትዋልል ነህ
ውኃ ፈሳሽ ስለሆነ ቁልቁለት ወዳለበትና ወደ ተመቸው ይፈሳል፡፡ የነፋስም ጉልበት ያንቀሳቅሰዋል፡፡ ወዲያና ወዲህም ያፈሰዋል፡፡ ውኃ በፈሳሽነት ባህሪው ምክንያት የራሱ የሆነ ቅርጽ የለውም፡፡ ውኃ ሊኖረው የሚችለው ቅርጽ ውኃው የተቀመጠበት ዕቃ ቅርጽ ነው፡፡ በብርጭቆ ውስጥ ያለ ውኃ የብርጭቆውን ቅርጽ ይይዛል፡፡ በኮካ ኮላና በአንቦ ውኃ ጠርሙሶች ውስጥ የተቀመጡ ፈሳሾች የጠርሙሱን ቅርጽ ይዘው ይቀመጣሉ፡፡ ከየጠርሙሶቻቸው ውስጥ ግን ሊወጡ የመሬትን ስበት እየተከተሉ ቁልቁል ወዳለበት ለመፍስስ ይፈጥናሉ፡፡ ስለዚህ ውኃ የርሱ የሆነና የኔ ነው የሚለው፤ የሚታወቅበትና የሚጠራበትም ቅርጽ የሌለው ፈሳች ስለሆነ በቅርጽ ባህሪ ስለሚገለጥ መልክ ስለ ውኃ መናገር አይቻልም፡፡
እንደ ውኃ የሚዋልል ልብ ያለው፥ በልቡም ባለ አሳብ መቆምና መቁረጥ የማይችል ሰው ብርቱ መሪና አለቃ ሆኖ መገኘት ያስቸግረዋል፡፡ ዮሴፍን እንኳ ከጨከኑበት ወንድሞቹ እጅ ለማዳን ሮቤል የልቡን አሳብ ደብቆ በሽፋን ቋንቋ ወንድሞቹን ሲናገር ተመልክተናል (ዘፍ.37፥22-29)፡፡ እንደ ውኃ የሚዋልል ልብ ያለውን መደገፍና ማመን አይቻልም፡፡ ደግፎ የመሸከም ጉልበቱ ቶሎ ስለሚከዳው የተደገፈበትን ሁሉ ይጎዳል፡፡ የራሳቸው አሳብ የሌላቸው፤ የሚሠሩትንና የሚያደርጉትን ሁሉ ሌሎች የሚያቀርቡላቸው፤ እንደ ነገሩአቸው ብቻ እንጂ ተጨማሪን ነገር የማያሰቡ፥ የመምራት አቅም ስለማይኖራቸው የመሪነት ቦታ ላይ እንኳ ቢቀመጡ ጊዜያቸው አጭር ይሆናል፡፡ ሮብዓም የሚባል የእስራኤል ንጉሥ መንገሥ በጀመረ ጊዜ ከሕዝቡ ለገጠመው ጥያቄ ምክርን ከሁለት ወገን ጠየቀ፡፡ ሁለቱም ወገኖች የሰጡት ምክር አንዱ ከሌላው አጅግ የተለያየ ሆነ፡፡ በእንዲህ ያለ ጊዜ ጥሩ መሪና የራሱም አሳብ ያለው አሰተዳዳሪ ከሁለቱም ወገኖች የተሰጡትን ምክሮች መርምሮ፤ ለምንም እንዲህ ሊለያዩ እንደቻሉ አጢኖ ዳኝነት መሰጠት ሲገባው ያልሆነውን ምክር በመሰማቱ የሕዝቡን ልብ አሳዘነ፡፡ በኋላም ከዚህ ክፉ ምክር የተነሳ የመንግሥቱ ግዛትና የእሰራኤልም ሕዝብ በእጠቃላይ ለሁለት እንዲከፈል ምክንያት ሆነ (1ኛ ነገ. 12፥1 - 15 )።
እንዲህም ባለ የልብ መዋለል ባህሪው ምክንያት የክብርና የኃይል አለቅነት የተገባው ሮቤል ብኩርናው ተወሰደበት፡፡ ብኩርናውም ለዮሴፍ ልጆመች እንደተሰጠ የእግዚአብሔር ቃል ይመሰከራል (1ኛ ዜና. 5፥1፡ ዘፍ. 48፥5)፡፡ የበኩር ልጅን በረከት ማጣት ምንነት ለሮቤል አዲስ ነገር አይመስለኝም፡፡ ወይም ደግሞ የሩቅ ዘመን ጨዋታና ትውስታ ብቻ አይደለም፡፡ አጎቱ የሆነው የአባቱ ታላቅ ወንድም እንዴት አድርጎ ብኩርናውን በትንሽ ነገርና ጥቂት ቢታገሰ ሊያልፍ በሚችል ነገር አንደ ለወጠው ለእርሱ ድብቅ ምሥጢር አይደለም (ዘፍ. 25፥27-34)፡፡ ነገር ካለፈና የሆዱ ረሃብም ከታገሰለት በኋሳ ዔሳው ብኩርናውን በብዙ እንባም ቢፈልገው መልሶ ሊያገኘው አልቻለም (ዕብ. 12፥16-17)፡፡ ሊመለስ በማይችል ነገር ላይ እንባና ጩኸት ትርፉ ጉዳት ብቻ በመሆኑ የዔሳውም ጸጸት ዘመኑን ሁሉ ሊከተለው ኖረ።
ዲቦራና ባርቅ በዝማሬ ቅኔያቸው ስለ እስራኤል ነገዶች በተቀኙ ጊዜ ስለ ሮቤል ልብ መዋለልና እንደ ውኃ መፍሰስ እንዲህ በማለት ገለጹ፦ “በሮቤል ፈሳሾች አጠገብ ብዙ የልብ ማመንታት ነበረ...በሮቤል ፈሳሾች አጠገብ ታላቅ የልብ ምርምር ነበረ” (መሳ. 5፥15-16)::
ይቀጥላል...
ምንጭ፦ አበራ ጌታሁን (ዶ/ር)፤ የያዕቆብ ልጆች እና በረከቶቻቸው፤ ገጽ 6-8
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤2👎1
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ስምዖንም መልሶ፦ አቤቱ፥ ሌሊቱን ሁሉ አድረን ስንደክም ምንም አልያዝንም፤ ነገር ግን በቃልህ መረቦቹን እጥላለሁ አለው።”
ሉቃስ 5፥5
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ስምዖንም መልሶ፦ አቤቱ፥ ሌሊቱን ሁሉ አድረን ስንደክም ምንም አልያዝንም፤ ነገር ግን በቃልህ መረቦቹን እጥላለሁ አለው።”
ሉቃስ 5፥5
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤3👍3
#እራሳችንን_እንመርምር
የነገሮች ቅለት እና ክብደት የሚወሰነው እግዚአብሔር ፈቅዷል ወይስ አልፈቀደም? ወይም ወዷል ወይስ አልወደደም በሚለው እንደሆነ በሚገባ የተረዳን ይመስላችኋል? ስንት ጊዜ በነገሮች ፊት ቆመን የእግዚአብሔርን ፈቃድ አጣርጠን በዚያ ከመንቀሳቀስ ይልቅ፣ በእግዚአብሔር ላይ በማመጽ ተንቀሳቀስን? ብቻ እግዚአብሔር ይውደደን!
"እግዚአብሔርስ ከወደደን ወተትና ማር ወደምታፈስሰው ወደዚች ምድር ያገባናል እርስዋንም ይሰጠናል። ነገር ግን በእግዚአብሔር ላይ አታምፁ፤ እንደ እንጀራ ይሆኑልናልና የምድሪቱን ሰዎች አትፍሩ፤ ጥላቸው ከላያቸው ተገፍፎአል፥ እግዚአብሔርም ከእኛ ጋር ነው፤ አትፍሩአቸው ብለው ተናገሩአቸው።"
ዘኍልቁ 14፥8-9
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የነገሮች ቅለት እና ክብደት የሚወሰነው እግዚአብሔር ፈቅዷል ወይስ አልፈቀደም? ወይም ወዷል ወይስ አልወደደም በሚለው እንደሆነ በሚገባ የተረዳን ይመስላችኋል? ስንት ጊዜ በነገሮች ፊት ቆመን የእግዚአብሔርን ፈቃድ አጣርጠን በዚያ ከመንቀሳቀስ ይልቅ፣ በእግዚአብሔር ላይ በማመጽ ተንቀሳቀስን? ብቻ እግዚአብሔር ይውደደን!
"እግዚአብሔርስ ከወደደን ወተትና ማር ወደምታፈስሰው ወደዚች ምድር ያገባናል እርስዋንም ይሰጠናል። ነገር ግን በእግዚአብሔር ላይ አታምፁ፤ እንደ እንጀራ ይሆኑልናልና የምድሪቱን ሰዎች አትፍሩ፤ ጥላቸው ከላያቸው ተገፍፎአል፥ እግዚአብሔርም ከእኛ ጋር ነው፤ አትፍሩአቸው ብለው ተናገሩአቸው።"
ዘኍልቁ 14፥8-9
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤2👍2
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“እግዚአብሔርም ለሙሴ እንደ ነገረው ሁሉ ኢያሱ ምድሪቱን ሁሉ ያዘ፤ ኢያሱም ለእስራኤል እንደ ክፍላቸውና እንደ ነገዳቸው ርስት አድርጎ ምድሪቱን ሰጣቸው፤ ምድሪቱም ከሰልፍ ዐረፈች።”
ኢያሱ 11፥23
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“እግዚአብሔርም ለሙሴ እንደ ነገረው ሁሉ ኢያሱ ምድሪቱን ሁሉ ያዘ፤ ኢያሱም ለእስራኤል እንደ ክፍላቸውና እንደ ነገዳቸው ርስት አድርጎ ምድሪቱን ሰጣቸው፤ ምድሪቱም ከሰልፍ ዐረፈች።”
ኢያሱ 11፥23
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤5👍4
#የሮሜ_መልእክት_ጥናት
ሮሜ 9
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁶ ነገር ግን የእግዚአብሔር ቃል የተሻረ አይደለም። እነዚህ ከእስራኤል የሚወለዱ ሁሉ እስራኤል አይደሉምና፤ የአብርሃምም ዘር ስለሆኑ ሁላቸው ልጆች አይደሉም፥
⁷ ነገር ግን፦ በይስሐቅ ዘር ይጠራልሃል ተባለ።
⁸ ይህም፥ የተስፋ ቃል ልጆች ዘር ሆነው ይቆጠራሉ እንጂ እነዚህ የሥጋ ልጆች የሆኑ የእግዚአብሔር ልጆች አይደሉም ማለት ነው።
⁹ ይህ፦ በዚህ ጊዜ እመጣለሁ ለሳራም ልጅ ይሆንላታል የሚል የተስፋ ቃል ነውና።
¹⁰ ይህ ብቻ አይደለም፥ ነገር ግን ርብቃ ደግሞ ከአንዱ ከአባታችን ከይስሐቅ በፀነሰች ጊዜ፥
¹¹ ልጆቹ ገና ሳይወለዱ፥ በጎ ወይም ክፉ ምንም ሳያደርጉ፥ ከጠሪው እንጂ ከሥራ ሳይሆን በምርጫ የሚሆን የእግዚአብሔር አሳብ ይጸና ዘንድ፥
¹² ለእርስዋ፦ ታላቁ ለታናሹ ይገዛል ተባለላት።
¹³ ያዕቆብን ወደድሁ ኤሳውን ግን ጠላሁ ተብሎ እንደ ተጻፈ ነው።
ሮሜ 9 (አዲሱ መ.ት)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁶ ነገር ግን የእግዚአብሔር ቃል ተሽሮአል ማለት አይደለም፤ ከእስራኤል የተወለደ ሁሉ እስራኤላዊ አይደለምና።
⁷ ከአብርሃም ዘርም ስለሆኑ፣ ሁሉም ልጆቹ አይደሉም፤ ይልቁንስ፣ “ትውልድህ በይሥሐቅ በኩል ይጠራልሃል” እንደ ተባለው ነው።
⁸ ይህም ማለት የእግዚአብሔር ልጆች የተባሉት የሥጋ ልጆች አይደሉም፤ ነገር ግን የአብርሃም ልጆች የተባሉት የተስፋው ልጆች ናቸው።
⁹ “ጊዜው ሲደርስ እመለሳለሁ፤ ሳራም ወንድ ልጅ ትወልዳለች” ተብሎ ተስፋው ተሰጥቶአልና።
¹⁰ ይህም ብቻ ሳይሆን፣ የርብቃ ልጆች አንድ አባት አላቸው፤ እርሱም አባታችን ይሥሐቅ ነው።
¹¹ መንትዮቹ ገና ሳይወለዱ፣ ወይም በጎም ሆነ ክፉ ሳያደርጉ፣ የእግዚአብሔር ሐሳብ በምርጫ ይጸና ዘንድ፣
¹² በሥራ ሳይሆን ከጠሪው በመሆኑ፣ “ታላቁ ታናሹን ያገለግላል” ተብሎ ተነገራት።
¹³ ይህም፣ “ያዕቆብን ወደድሁ፤ ዔሳውን ግን ጠላሁ” ተብሎ እንደ ተጻፈው ነው።
ሮሜ 9 (ሕያው ቃል)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁶ ይህ ከሆነ፥ ታዲያ እግዚአብሔር ለአይሁድ ሕዝብ የሰጠውን ተስፋ ሽሮታል ማለት ነው? ይህን ማለት አይቻልም። ምክንያቱም ከእሥራኤል ዘር የተወለዱ ሁሉ እሥራኤላውያን ናቸው ማለት አይደለም።
⁷ በልደተ ሥጋ ከአብርሃም ዘር ስለተገኙ ብቻ የአብርሃም ልጆች ናቸው ማለት አይቻልም። አብርሃም ሌሎች ልጆች እንዳሉት ቢታወቅም፥ ተስፋ የተነገረለት ለልጁ ለይስሐቅና ከእርሱም ለሚገኘው ልጅ ለያዕቆብ ዘር መሆኑ በቅዱሳት መጻሕፍት ተጽፏል።
⁸ ይህም ማለት በሥጋ ከአብርሃም ተወለዱና ሁሉም የእግዚአብሔር ልጆች ናቸው ማለት አይደለም። የእግዚአብሔር ልጆች ተብለው የሚቆጠሩት፥ እግዚአብሔር ለአብርሃም በገባለት የተስፋ ቃል መሠረት የተወለዱለት ብቻ ናቸው።
⁹ እግዚአብሔር ፥ «የዛሬ ዓመት መጥቼ እጐበኛችኋለሁ። ሚስትህ ሣራም ወንድ ልጅ ትወልድልሃለች» የሚል የተስፋ ቃል ለአብርሃም ሰጥቶት ነበር።
¹⁰ ይህም ብቻ አይደለም። ርብቃ ከአባታችን ከይስሐቅ መንታ ልጆች በፀነሰች ጊዜ፥
¹¹ ልጆቹ ተወልደው አድገው ክፉ ወይም ደግ ከመሥራ ታቸው በፊት ገና በእናታቸው ማሕፀን ሳሉ እግዚአብሔር ለርብቃ፥
¹² «ታላቁ ለታናሹ ይገዛል» ብሏታል። ይህም
¹³ «ያዕቆብን ወደድኩ፤ ዔሳውን ግን ጠላሁ» ተብሎ በቅዱሳት መጻሕፍት የተጻፈው ቃል እግዚአብሔር የሰውን ድርጊት ተከትሎ ሳይሆን፥ ማንኛውንም ነገር በራሱ የምርጫ እቅድ የሚሠራ መሆኑን ያስገነዝበናል።
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ሮሜ 9
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁶ ነገር ግን የእግዚአብሔር ቃል የተሻረ አይደለም። እነዚህ ከእስራኤል የሚወለዱ ሁሉ እስራኤል አይደሉምና፤ የአብርሃምም ዘር ስለሆኑ ሁላቸው ልጆች አይደሉም፥
⁷ ነገር ግን፦ በይስሐቅ ዘር ይጠራልሃል ተባለ።
⁸ ይህም፥ የተስፋ ቃል ልጆች ዘር ሆነው ይቆጠራሉ እንጂ እነዚህ የሥጋ ልጆች የሆኑ የእግዚአብሔር ልጆች አይደሉም ማለት ነው።
⁹ ይህ፦ በዚህ ጊዜ እመጣለሁ ለሳራም ልጅ ይሆንላታል የሚል የተስፋ ቃል ነውና።
¹⁰ ይህ ብቻ አይደለም፥ ነገር ግን ርብቃ ደግሞ ከአንዱ ከአባታችን ከይስሐቅ በፀነሰች ጊዜ፥
¹¹ ልጆቹ ገና ሳይወለዱ፥ በጎ ወይም ክፉ ምንም ሳያደርጉ፥ ከጠሪው እንጂ ከሥራ ሳይሆን በምርጫ የሚሆን የእግዚአብሔር አሳብ ይጸና ዘንድ፥
¹² ለእርስዋ፦ ታላቁ ለታናሹ ይገዛል ተባለላት።
¹³ ያዕቆብን ወደድሁ ኤሳውን ግን ጠላሁ ተብሎ እንደ ተጻፈ ነው።
ሮሜ 9 (አዲሱ መ.ት)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁶ ነገር ግን የእግዚአብሔር ቃል ተሽሮአል ማለት አይደለም፤ ከእስራኤል የተወለደ ሁሉ እስራኤላዊ አይደለምና።
⁷ ከአብርሃም ዘርም ስለሆኑ፣ ሁሉም ልጆቹ አይደሉም፤ ይልቁንስ፣ “ትውልድህ በይሥሐቅ በኩል ይጠራልሃል” እንደ ተባለው ነው።
⁸ ይህም ማለት የእግዚአብሔር ልጆች የተባሉት የሥጋ ልጆች አይደሉም፤ ነገር ግን የአብርሃም ልጆች የተባሉት የተስፋው ልጆች ናቸው።
⁹ “ጊዜው ሲደርስ እመለሳለሁ፤ ሳራም ወንድ ልጅ ትወልዳለች” ተብሎ ተስፋው ተሰጥቶአልና።
¹⁰ ይህም ብቻ ሳይሆን፣ የርብቃ ልጆች አንድ አባት አላቸው፤ እርሱም አባታችን ይሥሐቅ ነው።
¹¹ መንትዮቹ ገና ሳይወለዱ፣ ወይም በጎም ሆነ ክፉ ሳያደርጉ፣ የእግዚአብሔር ሐሳብ በምርጫ ይጸና ዘንድ፣
¹² በሥራ ሳይሆን ከጠሪው በመሆኑ፣ “ታላቁ ታናሹን ያገለግላል” ተብሎ ተነገራት።
¹³ ይህም፣ “ያዕቆብን ወደድሁ፤ ዔሳውን ግን ጠላሁ” ተብሎ እንደ ተጻፈው ነው።
ሮሜ 9 (ሕያው ቃል)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁶ ይህ ከሆነ፥ ታዲያ እግዚአብሔር ለአይሁድ ሕዝብ የሰጠውን ተስፋ ሽሮታል ማለት ነው? ይህን ማለት አይቻልም። ምክንያቱም ከእሥራኤል ዘር የተወለዱ ሁሉ እሥራኤላውያን ናቸው ማለት አይደለም።
⁷ በልደተ ሥጋ ከአብርሃም ዘር ስለተገኙ ብቻ የአብርሃም ልጆች ናቸው ማለት አይቻልም። አብርሃም ሌሎች ልጆች እንዳሉት ቢታወቅም፥ ተስፋ የተነገረለት ለልጁ ለይስሐቅና ከእርሱም ለሚገኘው ልጅ ለያዕቆብ ዘር መሆኑ በቅዱሳት መጻሕፍት ተጽፏል።
⁸ ይህም ማለት በሥጋ ከአብርሃም ተወለዱና ሁሉም የእግዚአብሔር ልጆች ናቸው ማለት አይደለም። የእግዚአብሔር ልጆች ተብለው የሚቆጠሩት፥ እግዚአብሔር ለአብርሃም በገባለት የተስፋ ቃል መሠረት የተወለዱለት ብቻ ናቸው።
⁹ እግዚአብሔር ፥ «የዛሬ ዓመት መጥቼ እጐበኛችኋለሁ። ሚስትህ ሣራም ወንድ ልጅ ትወልድልሃለች» የሚል የተስፋ ቃል ለአብርሃም ሰጥቶት ነበር።
¹⁰ ይህም ብቻ አይደለም። ርብቃ ከአባታችን ከይስሐቅ መንታ ልጆች በፀነሰች ጊዜ፥
¹¹ ልጆቹ ተወልደው አድገው ክፉ ወይም ደግ ከመሥራ ታቸው በፊት ገና በእናታቸው ማሕፀን ሳሉ እግዚአብሔር ለርብቃ፥
¹² «ታላቁ ለታናሹ ይገዛል» ብሏታል። ይህም
¹³ «ያዕቆብን ወደድኩ፤ ዔሳውን ግን ጠላሁ» ተብሎ በቅዱሳት መጻሕፍት የተጻፈው ቃል እግዚአብሔር የሰውን ድርጊት ተከትሎ ሳይሆን፥ ማንኛውንም ነገር በራሱ የምርጫ እቅድ የሚሠራ መሆኑን ያስገነዝበናል።
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍4❤2