የቀጠለ...
#የሮሜ_መልእክት_ጥናት
ከአሸናፊዎች እንበልጣለን (8:31-39)
ቁ. 31 እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ከሆነ፥ ማን ሊቃወመን ይችላል? ሰይጣን ይቃወመናል፤ በመጨረሻ ግን እውነተኛን አማኝ ተቃውሞ ሊያሸንፈው አይችልም።
ቁ. 32 እግዚአብሔር ብዙ አስደናቂ ስጦታዎችን ሰጥቶናል። ጸጋ፥ ፍቅር፥ ደስታ፥ ይቅርታ፥ ደኅንነት፥ በሰማይ ያለን ውርስ፥ ከስጦታዎች ሁሉ ታላቅ ስጦታ የሆነው ግን ልጁ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። ገና የእግዚአብሔር ጠላቶች በነበርንበት ጊዜ ተወዳጅ ልጁን የሰጠን ከሆነ፥ አሁን ልጆቹ ከሆንን በኋላ እነዚህን ታናናሽ ስጦታዎችንስ ጨምሮ አይሰጠንምን?
እነዚህ ሌሎች ስጦታዎች ሁሉ በክርስቶስ የተሰጡን ናቸው። መንፈሳዊ በረከት ሁሉ የሚገኘው በክርስቶስ ነው (ኤፌ. 1፥3)። ከእነዚህ መንፈሳዊ ስጦታዎች ለአንዱ እንኳ ዋጋ መክፈል ይኖርብናልን? በጭራሽ አንከፍልም፤ በክርስቶስ ላመኑ ሁሉ እነዚህ ሁሉ በረከቶች በነፃ የሚሰጡ ናቸው።
ጳውሎስ እንደሚለው እግዚአብሔር ለሚወዱና እንደፈቃዱ ለተጠሩ ሁሉ፤ ክርስቶስን ለእኛ አሳልፎ ሰጠው (ቁ 28)።
እግዚአብሔር ለራሱ ልጅ አልራራም እግዚአብሔር ከእኛ ሰውሮ ሊያስቀር የፈለገው ነገር አልነበረምና ክቡር ስጦታውን ልጁን ሰጥቶናል። ከስጦታዎቹም ጋር ብዙ መንፈሳዊ በረከቶችንም ሰጥቶናል። እግዚአብሔር ከእኛ የሰወረው ምንም ነገር ስለሌለው እኛም ከእርሱ ሰውረን የምናስቀረው ምንም ነገር እንዳይኖር ይጠበቅብናል። ክርስቶስን ለእኛ አሳልፎ እንደሰጠው፥ እኛም ራሳችንንና ያለንን ነገር ሁሉ ለእርሱ አሳልፈን ልንሰጥ ይገባናል።
ይህ ታላቅ እውነት በብሉይ ኪዳን ከተገለጡት በጣም ጠቃሚ ድርጊቶች በአንዱ ምሳሌነት ይቀርባል። ይህም ድርጊት አብርሃም ልጁን ይስሐቅን መሥዋዕት አድርጎ ማቅረቡ ነው (ዘፍ. 22፥1-14)። አብርሃም ልጅ ለማግኘት ብዙ ዓመት ጠበቀ፤ በመጨረሻ ልጁ ይስሐቅ በተወለደ ጊዜ የመቶ ዓመት ሰው ነበር። ከዚህ በኋላ እግዚአብሔር አብርሃምን ልጅህን ይስሐቅን መሥዋዕት አድርገህ አቅርብልኝ ብሎ አዘዘው። እስከ ዛሬ ሲጠብቀው የነበረውን ልጁን እንዲገድል ተናገረው ማለት ነው። ይሁን እንጂ፥ አብርሃም እግዚአብሔርን ታዘዘ፣ ይስሐቅንም ለመሠዋት ተዘጋጀ። አብርሃም ልክ ልጁን ሊገድል ሲል እግዚአብሔር አቆመው፤ በይስሐቅም ምትክ አንድ የበግ ሙክት አዘጋጀ። እግዚአብሔር አብርሃምን እንዲህ አለው፤ "አንተ እግዚአብሔርን የምትፈራ ሰው መሆንህን አውቄአለሁ፤ አንዱን የገዛ ልጅህን ከእኔ ሰውረህ ለማስቀረት አላሰብክም» (ዘፍ. 22፥12)። እግዚአብሔር ልጁን እንዲሠዋለት አብርሃምን የጠየቀው የአብርሃምን እምነትና ታዛዥነት ለመፈተን ነበር። ጥቂት ቆይቶም እግዚአብሔር አብርሃምን እንዲህ አለው:- ". አንተ ይህን ስላደረግህና ልጅህንም መሥዋዕት ከማድረግ ስላልተቆጠብህ በእርግጥ እኔ እባርክሃለሁ» (ዘፍ. 22፥15-18)።
እስቲ ራሳችንን እንፈትን፤ እስከ ዛሬ ከእግዚአብሔር የሰወርነው ነገር አለን? ለእግዚአብሔር አንሰጥም ብለን የያዝነው በጣም የምንወደውና እጅግ የከበረ ነገር ይኖራልን? ከእግዚአብሔር ይበልጥ እወደዋለሁ የምንለውስ ነገር ይኖረን ይሆን? ለምሳሌ እንደ ሀብት፥ እንደ ቤተሰብ፥ እንደ ዝና የመሰለ ነገር ይኖር ይሆን? እግዚአብሔር በስተጀርባው ያስቀረብን ነገር ምንም የለውም፤ እኛም የአብርሃምን ምሳሌ በመከተል ከእግዚአብሔር ምንም የምንሰውረው ነገር አይኑር (ዕብ. 11፥17-19)፡፡
በጣም የምንወደውን ነገር ለእግዚአብሔር በምናቀርብበት ጊዜ ምን ይሆናል? ብዙውን ጊዜ እግዚአብሔር መልሶ ይሰጠናል። እኛ አሳልፈን መስጠታችንን ካየ በኋላ ልክ አብርሃም ይስሐቅን ይዞት እንደቀረ ሁሉ እኛንም ይዘናቸው እንድንቀር ያደርገናል።
ቁ. 33 ሰይጣን በእኛ ላይ የፈለገውን ክስ ማቅረብ ይችላል፤ ይሁን እንጂ ሊፈርድብን አይችልም። ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር ኅብረት ያላቸው አሁን ኩነኔ (ፍርድ) የለባቸውም (ቁ. 1)። እውነት ነው፥ በዚህ ዓለም ሰዎች ሊፈርዱብን ይችላሉ፤ ነገር ግን በክርስቶስ ላሉት ሁሉ በሰማይ ያ ፍርድ ይሰረዛል። ጳውሎስ ፍርድ የለባቸውም ሲል እርሱ የሚናገረው ስለሰማይ ነው እንጂ ስለ ምድር አይደለም።
ቁ. 34 የሚፈርድስ ማን ነው? በመጨረሻ ማንም አይደለም። ምክንያቱም ሰይጣን በእኛ ላይ የሚያቀርበውን ክስ እግዚአብሔር አይሰማውም። እግዚአብሔር የሚሰማው ኢየሱስ ክርስቶስን ብቻ ሲሆን፤ እርሱ በእግዚአብሔር ቀኝ ሆኖ ለእኛ የሚማልድልንና ጠበቃችን ነው (ኤፌ. 1፥20-23)።
ቁ. 35 ከክርስቶስ ፍቅር ሊለየን የሚችል ማን ነው? ማንም የለም! ከኃጢአት በቀር (ቁ. 38-39)። በዚህ ሕይወታችን ከሚያጋጥመን ነገር ሁሉ በክርስቶስ ኢየሱስ ያለነውን ከእግዚአብሔር ፍቅር ሊለየን የሚችል ምንም የለም። በዚህ ጥቅስ ላይ ጳውሎስ ችግርና ስደት ጨርሰው አይደርሱብንም አይደለም የሚለው። የእርሱ አባባል እነዚህ ሁሉ ነገሮች ክእግዚአብሔር ፍቅር ሊለዩን አይችሉም ነው።
ይቀጥላል...
ምንጭ፦ የአዲስ ኪዳን ማብራሪያ ፤ ገጽ 370
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
#የሮሜ_መልእክት_ጥናት
ከአሸናፊዎች እንበልጣለን (8:31-39)
ቁ. 31 እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ከሆነ፥ ማን ሊቃወመን ይችላል? ሰይጣን ይቃወመናል፤ በመጨረሻ ግን እውነተኛን አማኝ ተቃውሞ ሊያሸንፈው አይችልም።
ቁ. 32 እግዚአብሔር ብዙ አስደናቂ ስጦታዎችን ሰጥቶናል። ጸጋ፥ ፍቅር፥ ደስታ፥ ይቅርታ፥ ደኅንነት፥ በሰማይ ያለን ውርስ፥ ከስጦታዎች ሁሉ ታላቅ ስጦታ የሆነው ግን ልጁ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። ገና የእግዚአብሔር ጠላቶች በነበርንበት ጊዜ ተወዳጅ ልጁን የሰጠን ከሆነ፥ አሁን ልጆቹ ከሆንን በኋላ እነዚህን ታናናሽ ስጦታዎችንስ ጨምሮ አይሰጠንምን?
እነዚህ ሌሎች ስጦታዎች ሁሉ በክርስቶስ የተሰጡን ናቸው። መንፈሳዊ በረከት ሁሉ የሚገኘው በክርስቶስ ነው (ኤፌ. 1፥3)። ከእነዚህ መንፈሳዊ ስጦታዎች ለአንዱ እንኳ ዋጋ መክፈል ይኖርብናልን? በጭራሽ አንከፍልም፤ በክርስቶስ ላመኑ ሁሉ እነዚህ ሁሉ በረከቶች በነፃ የሚሰጡ ናቸው።
ጳውሎስ እንደሚለው እግዚአብሔር ለሚወዱና እንደፈቃዱ ለተጠሩ ሁሉ፤ ክርስቶስን ለእኛ አሳልፎ ሰጠው (ቁ 28)።
እግዚአብሔር ለራሱ ልጅ አልራራም እግዚአብሔር ከእኛ ሰውሮ ሊያስቀር የፈለገው ነገር አልነበረምና ክቡር ስጦታውን ልጁን ሰጥቶናል። ከስጦታዎቹም ጋር ብዙ መንፈሳዊ በረከቶችንም ሰጥቶናል። እግዚአብሔር ከእኛ የሰወረው ምንም ነገር ስለሌለው እኛም ከእርሱ ሰውረን የምናስቀረው ምንም ነገር እንዳይኖር ይጠበቅብናል። ክርስቶስን ለእኛ አሳልፎ እንደሰጠው፥ እኛም ራሳችንንና ያለንን ነገር ሁሉ ለእርሱ አሳልፈን ልንሰጥ ይገባናል።
ይህ ታላቅ እውነት በብሉይ ኪዳን ከተገለጡት በጣም ጠቃሚ ድርጊቶች በአንዱ ምሳሌነት ይቀርባል። ይህም ድርጊት አብርሃም ልጁን ይስሐቅን መሥዋዕት አድርጎ ማቅረቡ ነው (ዘፍ. 22፥1-14)። አብርሃም ልጅ ለማግኘት ብዙ ዓመት ጠበቀ፤ በመጨረሻ ልጁ ይስሐቅ በተወለደ ጊዜ የመቶ ዓመት ሰው ነበር። ከዚህ በኋላ እግዚአብሔር አብርሃምን ልጅህን ይስሐቅን መሥዋዕት አድርገህ አቅርብልኝ ብሎ አዘዘው። እስከ ዛሬ ሲጠብቀው የነበረውን ልጁን እንዲገድል ተናገረው ማለት ነው። ይሁን እንጂ፥ አብርሃም እግዚአብሔርን ታዘዘ፣ ይስሐቅንም ለመሠዋት ተዘጋጀ። አብርሃም ልክ ልጁን ሊገድል ሲል እግዚአብሔር አቆመው፤ በይስሐቅም ምትክ አንድ የበግ ሙክት አዘጋጀ። እግዚአብሔር አብርሃምን እንዲህ አለው፤ "አንተ እግዚአብሔርን የምትፈራ ሰው መሆንህን አውቄአለሁ፤ አንዱን የገዛ ልጅህን ከእኔ ሰውረህ ለማስቀረት አላሰብክም» (ዘፍ. 22፥12)። እግዚአብሔር ልጁን እንዲሠዋለት አብርሃምን የጠየቀው የአብርሃምን እምነትና ታዛዥነት ለመፈተን ነበር። ጥቂት ቆይቶም እግዚአብሔር አብርሃምን እንዲህ አለው:- ". አንተ ይህን ስላደረግህና ልጅህንም መሥዋዕት ከማድረግ ስላልተቆጠብህ በእርግጥ እኔ እባርክሃለሁ» (ዘፍ. 22፥15-18)።
እስቲ ራሳችንን እንፈትን፤ እስከ ዛሬ ከእግዚአብሔር የሰወርነው ነገር አለን? ለእግዚአብሔር አንሰጥም ብለን የያዝነው በጣም የምንወደውና እጅግ የከበረ ነገር ይኖራልን? ከእግዚአብሔር ይበልጥ እወደዋለሁ የምንለውስ ነገር ይኖረን ይሆን? ለምሳሌ እንደ ሀብት፥ እንደ ቤተሰብ፥ እንደ ዝና የመሰለ ነገር ይኖር ይሆን? እግዚአብሔር በስተጀርባው ያስቀረብን ነገር ምንም የለውም፤ እኛም የአብርሃምን ምሳሌ በመከተል ከእግዚአብሔር ምንም የምንሰውረው ነገር አይኑር (ዕብ. 11፥17-19)፡፡
በጣም የምንወደውን ነገር ለእግዚአብሔር በምናቀርብበት ጊዜ ምን ይሆናል? ብዙውን ጊዜ እግዚአብሔር መልሶ ይሰጠናል። እኛ አሳልፈን መስጠታችንን ካየ በኋላ ልክ አብርሃም ይስሐቅን ይዞት እንደቀረ ሁሉ እኛንም ይዘናቸው እንድንቀር ያደርገናል።
ቁ. 33 ሰይጣን በእኛ ላይ የፈለገውን ክስ ማቅረብ ይችላል፤ ይሁን እንጂ ሊፈርድብን አይችልም። ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር ኅብረት ያላቸው አሁን ኩነኔ (ፍርድ) የለባቸውም (ቁ. 1)። እውነት ነው፥ በዚህ ዓለም ሰዎች ሊፈርዱብን ይችላሉ፤ ነገር ግን በክርስቶስ ላሉት ሁሉ በሰማይ ያ ፍርድ ይሰረዛል። ጳውሎስ ፍርድ የለባቸውም ሲል እርሱ የሚናገረው ስለሰማይ ነው እንጂ ስለ ምድር አይደለም።
ቁ. 34 የሚፈርድስ ማን ነው? በመጨረሻ ማንም አይደለም። ምክንያቱም ሰይጣን በእኛ ላይ የሚያቀርበውን ክስ እግዚአብሔር አይሰማውም። እግዚአብሔር የሚሰማው ኢየሱስ ክርስቶስን ብቻ ሲሆን፤ እርሱ በእግዚአብሔር ቀኝ ሆኖ ለእኛ የሚማልድልንና ጠበቃችን ነው (ኤፌ. 1፥20-23)።
ቁ. 35 ከክርስቶስ ፍቅር ሊለየን የሚችል ማን ነው? ማንም የለም! ከኃጢአት በቀር (ቁ. 38-39)። በዚህ ሕይወታችን ከሚያጋጥመን ነገር ሁሉ በክርስቶስ ኢየሱስ ያለነውን ከእግዚአብሔር ፍቅር ሊለየን የሚችል ምንም የለም። በዚህ ጥቅስ ላይ ጳውሎስ ችግርና ስደት ጨርሰው አይደርሱብንም አይደለም የሚለው። የእርሱ አባባል እነዚህ ሁሉ ነገሮች ክእግዚአብሔር ፍቅር ሊለዩን አይችሉም ነው።
ይቀጥላል...
ምንጭ፦ የአዲስ ኪዳን ማብራሪያ ፤ ገጽ 370
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍8❤1
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ጌታ እግዚአብሔር ኃይሌ ነው፤ እግሮቼን እንደ ዋላ እግሮች ያደርጋል፤ በከፍታዎችም ላይ ያስሄደኛል።”
ዕንባቆም 3፥19
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ጌታ እግዚአብሔር ኃይሌ ነው፤ እግሮቼን እንደ ዋላ እግሮች ያደርጋል፤ በከፍታዎችም ላይ ያስሄደኛል።”
ዕንባቆም 3፥19
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤3
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ያመለጠው የይሁዳ ቤት ቅሬታ ሥሩን ወደ ታች ይሰድዳል፥ ወደ ላይም ያፈራል።”
2ኛ ነገሥት 19፥30
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ያመለጠው የይሁዳ ቤት ቅሬታ ሥሩን ወደ ታች ይሰድዳል፥ ወደ ላይም ያፈራል።”
2ኛ ነገሥት 19፥30
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤1👍1
ከሐሰተኛ ነቢያት፣ ሐዋርያት. . . አስተማሪዎች ለመጠበቅ ምን እናድርግ? (ከይሁዳ መልእክት)
👉የእግዚአብሔርን ቃል ማሰብ፣ ማስታወስ
"እናንተ ግን፥ ወዳጆች ሆይ፥ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ሐዋርያት ቀድሞ የተነገረውን ቃል አስቡ፤" (ቁ. 17)
👉በሃይማኖት ለማደግ፣ ለመጠንከር፣ ለመጎልበት፣ ለመታነጽ መትጋት
"እናንተ ግን፥ ወዳጆች ሆይ፥ ከሁሉ ይልቅ በተቀደሰ ሃይማኖታችሁ ራሳችሁን ለማነጽ እየተጋችሁ" (ቁ. 20)
👉 በመንፈስ ቅዱስ የሚመራን ጸሎት መጸለይ
"በመንፈስ ቅዱስም እየጸለያችሁ" (ቁ. 20)
👉 በእግዚአብሔር ምሕረት እየተደገፍን የዘላለምን ሕይወት ለመውረስ መጠባበቅ
"ወደ ዘላለም ሕይወት የሚወስደውን የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ምሕረት ስትጠባበቁ" (ቁ. 21)
👉 በእግዚአብሔር ፍቅር ራስን መጠበቅ
"በእግዚአብሔር ፍቅር ራሳችሁን ጠብቁ" (ቁ. 21)
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👉የእግዚአብሔርን ቃል ማሰብ፣ ማስታወስ
"እናንተ ግን፥ ወዳጆች ሆይ፥ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ሐዋርያት ቀድሞ የተነገረውን ቃል አስቡ፤" (ቁ. 17)
👉በሃይማኖት ለማደግ፣ ለመጠንከር፣ ለመጎልበት፣ ለመታነጽ መትጋት
"እናንተ ግን፥ ወዳጆች ሆይ፥ ከሁሉ ይልቅ በተቀደሰ ሃይማኖታችሁ ራሳችሁን ለማነጽ እየተጋችሁ" (ቁ. 20)
👉 በመንፈስ ቅዱስ የሚመራን ጸሎት መጸለይ
"በመንፈስ ቅዱስም እየጸለያችሁ" (ቁ. 20)
👉 በእግዚአብሔር ምሕረት እየተደገፍን የዘላለምን ሕይወት ለመውረስ መጠባበቅ
"ወደ ዘላለም ሕይወት የሚወስደውን የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ምሕረት ስትጠባበቁ" (ቁ. 21)
👉 በእግዚአብሔር ፍቅር ራስን መጠበቅ
"በእግዚአብሔር ፍቅር ራሳችሁን ጠብቁ" (ቁ. 21)
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍6❤2
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ለእስራኤል ሁሉ ሥርዓትንና ፍርድን አድርጌ በኮሬብ ያዘዝሁትን የባሪያዬን የሙሴን ሕግ አስቡ።”
ሚልክያስ 4፥4
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ለእስራኤል ሁሉ ሥርዓትንና ፍርድን አድርጌ በኮሬብ ያዘዝሁትን የባሪያዬን የሙሴን ሕግ አስቡ።”
ሚልክያስ 4፥4
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤1
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ነገር ግን ባስጨነቋቸው መጠን የእስራኤላውያን ቍጥር በዛ፤ በምድሪቱም እየተስፋፉ ሄዱ፤ ከዚህም የተነሣ ግብፃውያኑ እስራኤላውያንን እጅግ ፈሯቸው፤”
ዘጸአት 1፥12 (አዲሱ መ.ት)
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ነገር ግን ባስጨነቋቸው መጠን የእስራኤላውያን ቍጥር በዛ፤ በምድሪቱም እየተስፋፉ ሄዱ፤ ከዚህም የተነሣ ግብፃውያኑ እስራኤላውያንን እጅግ ፈሯቸው፤”
ዘጸአት 1፥12 (አዲሱ መ.ት)
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤6
የዘንባባ ባህርያት
“ጻድቅ እንደ ዘንባባ ያፈራል፥ እንደ ሊባኖስ ዝግባም ያድጋል።”
መዝሙር 92፥12
👉 በአውሎንፋስ አይሰበርም። ንፋስን ዝቅ ብሎ ያሳልፋል
👉 ስሩን ወደታች በጥልቀት ይሰዳል
👉 ቀጥ ብሎ ነው የሚያድገው
👉 በድርቅ አይጠቃም
👉 ቅጠሉ ዓመቱን በሙሉ አረንጓዴ ነው
👉 ከሌሎች ዘንባባዎች ጋር መዳቀል አይችልም
👉 የማያቋርጥ እድገት አለው
👉 ፍሬው አይበላሽም
ምንጭ፦ https://www.faithwriters.com/article-details.php?id=120686
https://www.tblfaithnews.com/faith-religion/palm-trees-do-you-have-the-character-that-they-do
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
“ጻድቅ እንደ ዘንባባ ያፈራል፥ እንደ ሊባኖስ ዝግባም ያድጋል።”
መዝሙር 92፥12
👉 በአውሎንፋስ አይሰበርም። ንፋስን ዝቅ ብሎ ያሳልፋል
👉 ስሩን ወደታች በጥልቀት ይሰዳል
👉 ቀጥ ብሎ ነው የሚያድገው
👉 በድርቅ አይጠቃም
👉 ቅጠሉ ዓመቱን በሙሉ አረንጓዴ ነው
👉 ከሌሎች ዘንባባዎች ጋር መዳቀል አይችልም
👉 የማያቋርጥ እድገት አለው
👉 ፍሬው አይበላሽም
ምንጭ፦ https://www.faithwriters.com/article-details.php?id=120686
https://www.tblfaithnews.com/faith-religion/palm-trees-do-you-have-the-character-that-they-do
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍5🔥2
የጥምቀት በዓልን ለምታከብሩ የቻናላችን ቤተሰቦች እንኳን ለጌታችን እና ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የጥምቀት በዓል በሰላም አደረሳችሁ!
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤3
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ፊትህን ከእኔ አትሰውር፥ ተቈጥተህ ከባሪያህ ፈቀቅ አትበል፤ ረዳት ሁነኝ፥ አትጣለኝም፥ የመድኃኒቴም አምላክ ሆይ፥ አትተውኝ።”
መዝሙር 27፥9
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ፊትህን ከእኔ አትሰውር፥ ተቈጥተህ ከባሪያህ ፈቀቅ አትበል፤ ረዳት ሁነኝ፥ አትጣለኝም፥ የመድኃኒቴም አምላክ ሆይ፥ አትተውኝ።”
መዝሙር 27፥9
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍3❤1
#እራሳችንን_እንመርምር
በእግዚአብሔር ፊት በጸሎት ቀርበን እየለመንን እና እየጸለይን ነው ወይስ እኛ በጉልበታችን ምኞቶቻችንን ለማሳካት እየተጋደልን? እግዚአብሔር ጸሎትን ስለማይሰማ ነው ወይስ ፈቃዳችን ከእርሱ ፈቃድ በልጦብን ይሆን መጸለይ ያቆምነው?
"አንድ ነገር ለማግኘት ትጓጓላችሁ። ያንን የጓጓችሁለትን ነገር ለማግኘት ነፍስ እስከ ማጥፋት ትደርሳላችሁ። የእናንተ ያልሆነውን ትመኛላችሁ። የተመኛችሁትን ለማግኘት ጠብ ትፈጥራላችሁ ፤ ትጋደላላችሁ። ይህን ሁሉ አድርጋችሁም የምትመኙትን አታገኙም። የምትፈልጉትን ነገር የማታገኙትም እግዚአብሔርን በጸሎት ስላልጠየቃችሁት ነው።"
ያዕቆብ 4፥2 (ሕያው ቃል)
“በስውር ወይም በጨለማ ምድር ስፍራ አልተናገርሁም፤ ለያዕቆብ ዘር፦ በከንቱ ፈልጉኝ አላልሁም እኔ እግዚአብሔር ጽድቅን እናገራለሁ ቅንንም አወራለሁ።”
ኢሳይያስ 45፥19
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
በእግዚአብሔር ፊት በጸሎት ቀርበን እየለመንን እና እየጸለይን ነው ወይስ እኛ በጉልበታችን ምኞቶቻችንን ለማሳካት እየተጋደልን? እግዚአብሔር ጸሎትን ስለማይሰማ ነው ወይስ ፈቃዳችን ከእርሱ ፈቃድ በልጦብን ይሆን መጸለይ ያቆምነው?
"አንድ ነገር ለማግኘት ትጓጓላችሁ። ያንን የጓጓችሁለትን ነገር ለማግኘት ነፍስ እስከ ማጥፋት ትደርሳላችሁ። የእናንተ ያልሆነውን ትመኛላችሁ። የተመኛችሁትን ለማግኘት ጠብ ትፈጥራላችሁ ፤ ትጋደላላችሁ። ይህን ሁሉ አድርጋችሁም የምትመኙትን አታገኙም። የምትፈልጉትን ነገር የማታገኙትም እግዚአብሔርን በጸሎት ስላልጠየቃችሁት ነው።"
ያዕቆብ 4፥2 (ሕያው ቃል)
“በስውር ወይም በጨለማ ምድር ስፍራ አልተናገርሁም፤ ለያዕቆብ ዘር፦ በከንቱ ፈልጉኝ አላልሁም እኔ እግዚአብሔር ጽድቅን እናገራለሁ ቅንንም አወራለሁ።”
ኢሳይያስ 45፥19
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍6❤3
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“እግዚአብሔርም በሌሒ ያለውን አዘቅት ሰነጠቀ፥ ከእርሱም ውኃ ወጣ፤ እርሱም ጠጣ፥ ነፍሱም ተመለሰች፥ ተጠናከረም። ስለዚህም የዚያን ቦታ ስም ዓይንሀቆሬ ብሎ ጠራው፤ ይህም እስከ ዛሬ ድረስ በሌሒ አለ።”
መሳፍንት 15፥19
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“እግዚአብሔርም በሌሒ ያለውን አዘቅት ሰነጠቀ፥ ከእርሱም ውኃ ወጣ፤ እርሱም ጠጣ፥ ነፍሱም ተመለሰች፥ ተጠናከረም። ስለዚህም የዚያን ቦታ ስም ዓይንሀቆሬ ብሎ ጠራው፤ ይህም እስከ ዛሬ ድረስ በሌሒ አለ።”
መሳፍንት 15፥19
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍4❤2