' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ልዩ ልዩን የእግዚአብሔርን ጸጋ ደጋግ መጋቢዎች እንደ መሆናችሁ፥ እያንዳንዳችሁ የጸጋን ስጦታ እንደ ተቀበላችሁ መጠን በዚያው ጸጋ እርስ በርሳችሁ አገልግሉ፤”
1ኛ ጴጥሮስ 4፥10
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ልዩ ልዩን የእግዚአብሔርን ጸጋ ደጋግ መጋቢዎች እንደ መሆናችሁ፥ እያንዳንዳችሁ የጸጋን ስጦታ እንደ ተቀበላችሁ መጠን በዚያው ጸጋ እርስ በርሳችሁ አገልግሉ፤”
1ኛ ጴጥሮስ 4፥10
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤2
ቅዱሳት መጻሕፍት
#የሮሜ_መልእክት_ጥናት ከፍርሃት ነፃ ወጥተናል- መለየት የለም (8:31-39) ኩነኔ የማይኖርብን ከእግዚአብሔር ጽድቅ ስለምንካፈል እና ሕግ ሊኮንነን ስለማይችል ነው፡፡ ሥጋን አሸንፈን ለእግዚአብሔር እንድንኖር የእግዚአብሔር መንፈስ ስላለን ዕዳ የለብንም፡፡ ተስፋ መቁረጥም የለም፡፡ ምክንያቱም የተባረከ ተስፋችን በሆነው በክርስቶስ መመለስ የእግዚአብሔርን ክብር እንካፈላለንና፡፡ የእግዚአብሔርን ፍቅር…
የቀጠለ...
#የሮሜ_መልእክት_ጥናት
ከፍርሃት ነፃ ወጥተናል- መለየት የለም (8:31-39)
መ) ክርስቶስ ስለ እኛ ይማልዳል (8:34)
እጥፍ ምልጃ አማኝን በክርስቶስ ዋስትና ይሰጠዋል፡፡ መንፈስ ይማልዳል (8:26-27)፣ የእግዚአብሔር ልጅም ይማልድልናል (8:34):: ለእኛ የሞተልን ያው ጌታ አሁን በሰማያት ይማልድልናል፡፡ ሊቀ ካህናችን በመሆኑ ፈተናን መወጣት የምንችልበትን ጸጋና ጠላትን የምንረታበትን ጉልበት ይሰጠናል (ዕብ. 4:14-16)። ጠበቃችን ስለሆነና፣ ኃጢአታችንን ይቅር ብሎ ከእግዚአብሔር ጋር ያለንን ኅብረት ያድሳል (1ኛ ዮሐ. 1:9-2፡2)። ምልጃ ማለት ኢየሱስ ክርስቶስ በእግዚአብሔር ዙፋን ፊት እኛን ወክሎ ስላለ ራሳችንን መወከል አያሻንም ማለት ነው፡፡
በሮሜ 5:9-10 ባለው ክፍል ጳውሎስ የምልጃን አገልግሎት ጠቁሟል፡፡ የዳንነው በሞቱ ብቻ ሳይሆን በሕይወቱም ነው፡፡ «ስለ እነርሱም ሊማልድ ዘወትር በሕይወት ይኖራልና ስለዚህ ደግሞ በእርሱ ወደ እግዚአብሔር የሚመጡትን ፈጽሞ ሊያድናቸው ይችላል» (ዕብ. 7፡25)፡፡ ጴጥሮስ በጌታ ላይ ኃጢአት ሠርቶ ነበር፣ ነገር ግን በኢየሱስ ክርስቶስ ኃጢአቱ ተፋቀለት ኅብረቱም ታደሰለት፡፡ «ስምዖን ስምዖን ሆይ፣ እነሆ፣ ሰይጣን እንደ ስንዴ ሊያበጥራችሁ ለመነ፤ እኔ ግን እምነትህ እንዳይጠፋ ስለ አንተ አማለድሁ» (ሉቃስ 22፥31-32)። ስለ እያንዳንዳችን ይማልዳል ይህም አገልግሎቱ እያንዳንዳችን ዋስትና ያለን ስለመሆኑ ያረጋግጥልናል፡፡
ሠ) ክርስቶስ ይወድደናል (8:35-39)
ከቁጥር 31-34 ጳውሎስ እግዚአብሔር እንደማይተወን አረጋግጧል:: ነገር ግን እኛ ልንተወው እንችላለን? ከዚያስ? ጳውሎስ ይህንን ችግር በዚህ በመጨረሻው ክፍል ከክርስቶስ ፍቅር ሊለየን የሚችል ነገር እንደ ሌለ ያብራራል፡፡
ለመንፈሳዊ ዕድገታችን የሚያስፈልጉን ስለሆነ ብሎ (ሮሜ 5:3-5) እግዚአብሔር ከሕይወት ውጣ ውረዶች አያስጠልለንም፡፡ በሮሜ 8:28 እንደተናገረው የሕይወት ውጣ ውረዶች ለበጎ እንደሚሆኑልን እንጂ እንደማያጠፉን አረጋግጦልናል፡፡ ለራሳችን በጎነትና ለራሱ ክብር ሲል እግዚአብሔር ፈተናን ይፈቅዳል፡፡ ስለ እርሱ ብለን ፈተናን እንታገሳለን (8:36):: ይህንን በማድረጋችን እግዚአብሔር የሚተወን ይመስላችኋል? በፍጹም! ይልቁንም በሕይወት ፈተና ስናልፍ የበለጠ ይጠጋናል፡፡
በተጨማሪም፣ የምናሸንፍበትን ኃይል ይሰጠናል (ቁ. 37)። በክርስቶስ «ከአሸናፊዎች እንበልጣለን::» በድል ላይ ድልን ይሰጠናል፡፡ ሕይወትንም፣ ሞትንም፣ ያለውንም፣ የሚመጣውንም አንፈራም። ምክንያቱም ኢየሱስ ክርስቶስ ይወድደናል፣ ድልንም ይሰጠናል:: ይህ የተስፋ ቃል በእኛ ጥረት ላይ የተመሠረተ አይደለም፣ «እንዲህ ብታደርጉ፣ እንዲህ አደርጋለሁ» አላለም፡፡ ይህ ዋስትናችን የጸና እውነት ነው፡፡ እኛ የክርስቶስ ስለሆንን ዋስትናው የራሳችን መሆኑን እናውጃለን፡፡ ከእርሱ ፍቅር ምንም ሊለያችሁ አይችልም:: እመኑና በእርሱ ሐሴት አድርጉ!
የዚህ አስደናቂ ምዕራፍ ግምገማ ክርስቲያን ሙሉ በሙሉ ባለድል መሆኑን ያሳያል፡፡ ክርስቶስ ስለሞተልን ከፍርድ ነፃ ነን፡፡ የእርሱም ጽድቅ አለን፡፡ ክርስቶስ በመንፈሱ በእኛ ውስጥ ስለሚኖርና በሕይወቱ ስለምንካፈል፣ ከሽንፈት ነፃ ነን፡፡ ክርስቶስ ስለሚመጣና በክብሩ ስለምንካፈል ከተስፋ መቁረጥ አርነት ወጥተናል፡፡ ክርስቶስ ስለሚማልድልንና ከእርሱ ፍቅር ሊለየን የሚችል ማንም ስለሌለ፣ ከፍርሃት ነፃ ነን፡፡
ኩነኔ የለብንም! ዕዳ የለብንም! ተስፋ አንቆርጥም! ከእርሱ አንለይም!
እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ከሆነ፣ ማን ይቃወመናል?
ይቀጥላል...
ምንጭ፦ ዋረን ደብልዩ ዌርዝ ቢ፤ ተስማማ፤ ገጽ 90-91
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
#የሮሜ_መልእክት_ጥናት
ከፍርሃት ነፃ ወጥተናል- መለየት የለም (8:31-39)
መ) ክርስቶስ ስለ እኛ ይማልዳል (8:34)
እጥፍ ምልጃ አማኝን በክርስቶስ ዋስትና ይሰጠዋል፡፡ መንፈስ ይማልዳል (8:26-27)፣ የእግዚአብሔር ልጅም ይማልድልናል (8:34):: ለእኛ የሞተልን ያው ጌታ አሁን በሰማያት ይማልድልናል፡፡ ሊቀ ካህናችን በመሆኑ ፈተናን መወጣት የምንችልበትን ጸጋና ጠላትን የምንረታበትን ጉልበት ይሰጠናል (ዕብ. 4:14-16)። ጠበቃችን ስለሆነና፣ ኃጢአታችንን ይቅር ብሎ ከእግዚአብሔር ጋር ያለንን ኅብረት ያድሳል (1ኛ ዮሐ. 1:9-2፡2)። ምልጃ ማለት ኢየሱስ ክርስቶስ በእግዚአብሔር ዙፋን ፊት እኛን ወክሎ ስላለ ራሳችንን መወከል አያሻንም ማለት ነው፡፡
በሮሜ 5:9-10 ባለው ክፍል ጳውሎስ የምልጃን አገልግሎት ጠቁሟል፡፡ የዳንነው በሞቱ ብቻ ሳይሆን በሕይወቱም ነው፡፡ «ስለ እነርሱም ሊማልድ ዘወትር በሕይወት ይኖራልና ስለዚህ ደግሞ በእርሱ ወደ እግዚአብሔር የሚመጡትን ፈጽሞ ሊያድናቸው ይችላል» (ዕብ. 7፡25)፡፡ ጴጥሮስ በጌታ ላይ ኃጢአት ሠርቶ ነበር፣ ነገር ግን በኢየሱስ ክርስቶስ ኃጢአቱ ተፋቀለት ኅብረቱም ታደሰለት፡፡ «ስምዖን ስምዖን ሆይ፣ እነሆ፣ ሰይጣን እንደ ስንዴ ሊያበጥራችሁ ለመነ፤ እኔ ግን እምነትህ እንዳይጠፋ ስለ አንተ አማለድሁ» (ሉቃስ 22፥31-32)። ስለ እያንዳንዳችን ይማልዳል ይህም አገልግሎቱ እያንዳንዳችን ዋስትና ያለን ስለመሆኑ ያረጋግጥልናል፡፡
ሠ) ክርስቶስ ይወድደናል (8:35-39)
ከቁጥር 31-34 ጳውሎስ እግዚአብሔር እንደማይተወን አረጋግጧል:: ነገር ግን እኛ ልንተወው እንችላለን? ከዚያስ? ጳውሎስ ይህንን ችግር በዚህ በመጨረሻው ክፍል ከክርስቶስ ፍቅር ሊለየን የሚችል ነገር እንደ ሌለ ያብራራል፡፡
ለመንፈሳዊ ዕድገታችን የሚያስፈልጉን ስለሆነ ብሎ (ሮሜ 5:3-5) እግዚአብሔር ከሕይወት ውጣ ውረዶች አያስጠልለንም፡፡ በሮሜ 8:28 እንደተናገረው የሕይወት ውጣ ውረዶች ለበጎ እንደሚሆኑልን እንጂ እንደማያጠፉን አረጋግጦልናል፡፡ ለራሳችን በጎነትና ለራሱ ክብር ሲል እግዚአብሔር ፈተናን ይፈቅዳል፡፡ ስለ እርሱ ብለን ፈተናን እንታገሳለን (8:36):: ይህንን በማድረጋችን እግዚአብሔር የሚተወን ይመስላችኋል? በፍጹም! ይልቁንም በሕይወት ፈተና ስናልፍ የበለጠ ይጠጋናል፡፡
በተጨማሪም፣ የምናሸንፍበትን ኃይል ይሰጠናል (ቁ. 37)። በክርስቶስ «ከአሸናፊዎች እንበልጣለን::» በድል ላይ ድልን ይሰጠናል፡፡ ሕይወትንም፣ ሞትንም፣ ያለውንም፣ የሚመጣውንም አንፈራም። ምክንያቱም ኢየሱስ ክርስቶስ ይወድደናል፣ ድልንም ይሰጠናል:: ይህ የተስፋ ቃል በእኛ ጥረት ላይ የተመሠረተ አይደለም፣ «እንዲህ ብታደርጉ፣ እንዲህ አደርጋለሁ» አላለም፡፡ ይህ ዋስትናችን የጸና እውነት ነው፡፡ እኛ የክርስቶስ ስለሆንን ዋስትናው የራሳችን መሆኑን እናውጃለን፡፡ ከእርሱ ፍቅር ምንም ሊለያችሁ አይችልም:: እመኑና በእርሱ ሐሴት አድርጉ!
የዚህ አስደናቂ ምዕራፍ ግምገማ ክርስቲያን ሙሉ በሙሉ ባለድል መሆኑን ያሳያል፡፡ ክርስቶስ ስለሞተልን ከፍርድ ነፃ ነን፡፡ የእርሱም ጽድቅ አለን፡፡ ክርስቶስ በመንፈሱ በእኛ ውስጥ ስለሚኖርና በሕይወቱ ስለምንካፈል፣ ከሽንፈት ነፃ ነን፡፡ ክርስቶስ ስለሚመጣና በክብሩ ስለምንካፈል ከተስፋ መቁረጥ አርነት ወጥተናል፡፡ ክርስቶስ ስለሚማልድልንና ከእርሱ ፍቅር ሊለየን የሚችል ማንም ስለሌለ፣ ከፍርሃት ነፃ ነን፡፡
ኩነኔ የለብንም! ዕዳ የለብንም! ተስፋ አንቆርጥም! ከእርሱ አንለይም!
እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ከሆነ፣ ማን ይቃወመናል?
ይቀጥላል...
ምንጭ፦ ዋረን ደብልዩ ዌርዝ ቢ፤ ተስማማ፤ ገጽ 90-91
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍5
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ቅጥር እንደሌላት እንደ ፈረሰች ከተማ፥ መንፈሱን የማይከለክል ሰው እንዲሁ ነው።”
ምሳሌ 25፥28
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ቅጥር እንደሌላት እንደ ፈረሰች ከተማ፥ መንፈሱን የማይከለክል ሰው እንዲሁ ነው።”
ምሳሌ 25፥28
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍2❤1
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ሁሉንም ፍርሃት ያዛቸውና፦ ታላቅ ነቢይ በእኛ መካከል ተነሥቶአል፥ ደግሞ፦ እግዚአብሔር ሕዝቡን ጐበኘ እያሉ እግዚአብሔርን አመሰገኑ።”
ሉቃስ 7፥16
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ሁሉንም ፍርሃት ያዛቸውና፦ ታላቅ ነቢይ በእኛ መካከል ተነሥቶአል፥ ደግሞ፦ እግዚአብሔር ሕዝቡን ጐበኘ እያሉ እግዚአብሔርን አመሰገኑ።”
ሉቃስ 7፥16
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤2
#እራሳችንን_እንመርምር
እግዚአብሔር የመረጠልንን መንገድ ለመከተል እውቀት ለማግኘት ምን ማድረግ አለብን?
"እንግዲህ እግዚአብሔርን የሚፈራ ሰው ማነው? ለእርሱ የተመረጠለትን መንገድ እንዲከተል እግዚአብሔር ዕውቀቱን ይሰጠዋል፤"
መዝሙር 25፥12 (ሕያው ቃል)
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
እግዚአብሔር የመረጠልንን መንገድ ለመከተል እውቀት ለማግኘት ምን ማድረግ አለብን?
"እንግዲህ እግዚአብሔርን የሚፈራ ሰው ማነው? ለእርሱ የተመረጠለትን መንገድ እንዲከተል እግዚአብሔር ዕውቀቱን ይሰጠዋል፤"
መዝሙር 25፥12 (ሕያው ቃል)
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤3
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ስለ ምን ሕመሜ አዘወተረኝ? ቍስሌስ ስለ ምን የማይፈወስ ሆነ? ስለ ምንስ። አልሽርም አለ? በውኑ እንደ ሐሰተኛ ምንጭ፥ እንዳልታመነች ውኃ ትሆነኛለህን?”
ኤርምያስ 15፥18
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ስለ ምን ሕመሜ አዘወተረኝ? ቍስሌስ ስለ ምን የማይፈወስ ሆነ? ስለ ምንስ። አልሽርም አለ? በውኑ እንደ ሐሰተኛ ምንጭ፥ እንዳልታመነች ውኃ ትሆነኛለህን?”
ኤርምያስ 15፥18
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤1👍1
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
እንደ አውሮፓውያን ዘመን አቆጣጠር የጊዜ ስሌት ለምትጠቀሙ የቻናላችን ቤተሰቦች መልካም አዲስ ዓመት ይሁንላችሁ!
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍7❤1
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“አንተን በሚረዳህ በአባትህ አምላክ፣ በሚባርክህ፣ ሁሉን ማድረግ በሚችል አምላክ፣ ከላይ ከሰማይ በሚገኝ ረድኤት፣ ከምድር ጥልቅ በሚገኝ በረከት፣ ከማሕፀንና ከጡት በሚገኝ ምርቃት ይባርክሃል።”
ዘፍጥረት 49፥25 (አዲሱ መ.ት)
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“አንተን በሚረዳህ በአባትህ አምላክ፣ በሚባርክህ፣ ሁሉን ማድረግ በሚችል አምላክ፣ ከላይ ከሰማይ በሚገኝ ረድኤት፣ ከምድር ጥልቅ በሚገኝ በረከት፣ ከማሕፀንና ከጡት በሚገኝ ምርቃት ይባርክሃል።”
ዘፍጥረት 49፥25 (አዲሱ መ.ት)
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤7👍4
#የእግዚአብሔር_ቃል_ምን_ይላል?
መዝሙር 84
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ የሠራዊት አምላክ ሆይ፥ ማደሪያዎችህ እንደምን የተወደዱ ናቸው!
² ነፍሴ የእግዚአብሔርን አደባባዮች ትወድዳለች ትናፍቅማለች፤ ልቤም ሥጋዬም በሕያው አምላክ ደስ ተሰኘ።
³ ወፍ ለእርስዋ ቤትን አገኘች፥ ዋኖስም ጫጩቶችዋን የምታኖርበት ቤት አገኘች፤ የሠራዊት አምላክ ንጉሤም አምላኬም ሆይ፥ እርሱ መሠዊያህ ነው።
⁴ በቤትህ የሚኖሩ ሁሉ የተመሰገኑ ናቸው፤ ለዓለምና ለዘላለምም ያመሰግኑሃል።
⁵ አቤቱ፥ እርዳታው ከአንተ ዘንድ የሆነለት፥ በልቡም የላይኛውን መንገድ የሚያስብ ሰው ምስጉን ነው።
⁶ በልቅሶ ሸለቆ ውስጥ በወሰነው ስፍራ የሕግ መምህር በረከትን ይሰጣልና።
⁷ ከኃይል ወደ ኃይል ይሄዳሉ፤ የአማልክት አምላክ በጽዮን ይታያል።
⁸ የሠራዊት አምላክ አቤቱ፥ ጸሎቴን ስማ፤ የያዕቆብ አምላክ ሆይ፥ አድምጥ።
⁹ አቤቱ፥ መታመናችንን እይልን፥ ወደ ቀባኸውም ፊት ተመልከት።
¹⁰ ከአእላፍ ይልቅ በአደባባዮችህ አንዲት ቀን ትሻላለች፤ በኃጥኣን ድንኳኖች ከመቀመጥ ይልቅ፥ በእግዚአብሔር ቤት እጣል ዘንድ መረጥሁ።
¹¹ እግዚአብሔር አምላክ ምሕረትንና እውነትን ስለ ወደደ፥ ሞገስንና ክብርን ይሰጣል፤ እግዚአብሔር በቅንነት የሚሄዱትን ከመልካም ነገር አያሳጣቸውም።
¹² የሠራዊት አምላክ ሆይ፥ በአንተ የታመነ ሰው ምስጉን ነው።
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
መዝሙር 84
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ የሠራዊት አምላክ ሆይ፥ ማደሪያዎችህ እንደምን የተወደዱ ናቸው!
² ነፍሴ የእግዚአብሔርን አደባባዮች ትወድዳለች ትናፍቅማለች፤ ልቤም ሥጋዬም በሕያው አምላክ ደስ ተሰኘ።
³ ወፍ ለእርስዋ ቤትን አገኘች፥ ዋኖስም ጫጩቶችዋን የምታኖርበት ቤት አገኘች፤ የሠራዊት አምላክ ንጉሤም አምላኬም ሆይ፥ እርሱ መሠዊያህ ነው።
⁴ በቤትህ የሚኖሩ ሁሉ የተመሰገኑ ናቸው፤ ለዓለምና ለዘላለምም ያመሰግኑሃል።
⁵ አቤቱ፥ እርዳታው ከአንተ ዘንድ የሆነለት፥ በልቡም የላይኛውን መንገድ የሚያስብ ሰው ምስጉን ነው።
⁶ በልቅሶ ሸለቆ ውስጥ በወሰነው ስፍራ የሕግ መምህር በረከትን ይሰጣልና።
⁷ ከኃይል ወደ ኃይል ይሄዳሉ፤ የአማልክት አምላክ በጽዮን ይታያል።
⁸ የሠራዊት አምላክ አቤቱ፥ ጸሎቴን ስማ፤ የያዕቆብ አምላክ ሆይ፥ አድምጥ።
⁹ አቤቱ፥ መታመናችንን እይልን፥ ወደ ቀባኸውም ፊት ተመልከት።
¹⁰ ከአእላፍ ይልቅ በአደባባዮችህ አንዲት ቀን ትሻላለች፤ በኃጥኣን ድንኳኖች ከመቀመጥ ይልቅ፥ በእግዚአብሔር ቤት እጣል ዘንድ መረጥሁ።
¹¹ እግዚአብሔር አምላክ ምሕረትንና እውነትን ስለ ወደደ፥ ሞገስንና ክብርን ይሰጣል፤ እግዚአብሔር በቅንነት የሚሄዱትን ከመልካም ነገር አያሳጣቸውም።
¹² የሠራዊት አምላክ ሆይ፥ በአንተ የታመነ ሰው ምስጉን ነው።
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍4❤2
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“በእኔ ደስ ተሰኝተህ ከሆነ፣ አንተን ዐውቅህና ያለ ማቋረጥ በፊትህ ሞገስ አገኝ ዘንድ መንገድህን አስተምረኝ፤ ይህ ሕዝብ የአንተ ሕዝብ መሆኑን አስታውስ።”
ዘጸአት 33፥13 (አዲሱ መ.ት)
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“በእኔ ደስ ተሰኝተህ ከሆነ፣ አንተን ዐውቅህና ያለ ማቋረጥ በፊትህ ሞገስ አገኝ ዘንድ መንገድህን አስተምረኝ፤ ይህ ሕዝብ የአንተ ሕዝብ መሆኑን አስታውስ።”
ዘጸአት 33፥13 (አዲሱ መ.ት)
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤4
🌟የገና በዓል ታሪካዊ አመጣጥ
ክፍል-፩
በጳውሎስ ካሱ
የክርስትና ሃይማኖት ተከታዮች በየዓመቱ በደማቅ (በተለየ የአሜሪካና አውሮፓ) ሁኔታ ከሚያከብሯቸው በዓላት አንዱ ገና ነው፡፡የገና በዓል አከባበር በየአገሩ መጠነኛ ልዩነት ቢኖረውም በየዓመቱ አዳዲስ መሻሻሎች እየተደረገበት ደማቅነቱ እንደቀጠለ መጥቷል፡፡
ይህንኑ ተከትሎም የበዓሉን አጀማመርና ታሪክ ለማግኘት ብዙ ጥናቶች ተደርገዋል:: የጥናቶቹ ግኝትም ብዙዎቹን እርግጥ ይህ በዓል መጽሐፍ ቅዱሳዊ ነውን? ብለው እንዲጠይቁ ሲያደርግ ብዙዎቹን ግን በዓሉን መጽሐፍ ቅዱሳዊ ለማድረግ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶችን በመጥቀስ ትክክለኛነቱን ለማሳየት ይሞክራሉ፡፡የተቀሩት ደግሞ ትኩረታቸውን ከበዓሉ በሚገኘው ደስታ ላይ ብቻ በማድረግ የአያገባኝም አቋም ወስደዋል፡፡ እርግጥ የገና በዓል መጽሐፍ ቅዱሳዊ ነው? መልሱ በሚከተሉት የጥናት ግኝቶች ውስጥ ይገኛል፡፡
ኢየሱስ ክርስቶስ የተወለደው በእርግጥ በፈረንጆቹ ዲሴምበር 25 ወይም በኢትዮጵያዊያን ታኅሣሥ 29 ነውን? አዲስ ኪዳን ኢየሱሰ ክርስቶስ የተወለደበትን ቀን በትክክል አይናገርም::
ከወንጌላቱ ሁሉ መጀመርያ እንደተጻፈ የሚታመነው የማርቆስ ወንጌል ከክርስቶስ ልደት በኋላ በ65 ዓ.ም. የተጻፈ ሲሆን፣ ታሪኩን የሚጀምረው ከኢየሱስ ክርስቶስ ጥምቀት ነው። ይህም የሚጠቁመው የመጀመርያዎቹ ክርስቲያኖች የክርስቶስን የልደት ቀን እንደማያውቁ ለማወቅም ፍላጎት እንዳልነበራቸው ነው፡፡ ይህም አንድ ጥያቄ ማስነሳቱ አልቀረም፤ ክርስቶስ በዲሴምበር 25 ወይም ታኅሣሥ 29 ተወለደ ብሎ የጻፈው ማነው? እንዴትስ አወቀ? ታሪክ እንደሚናገረው ጌታ ተወለደ ተብሎ የሚታመንበትን ዓመት የወሰነው ዲዮኒሲየስ ኤግዚገስ (Dionysisus Exiguus) የተባለ የካቶሊክ መነኩሴ ነው፡፡
ክርስቶስ የተወለደበትን ዓመት ለመወሰን የተጠቀመው ቀመርም የሚከተለውን ይመስላል፡-
በቅድመ ክርስትና ሮም ዓመታት የሚቆጠሩት "ከአበ አርበ ኮንዲታ" (ab Urbe Condita) ማለትም ሮም ከተመሠረተችበት ቀን ጀምሮ ነው፤ ይህም AUC ይባላል እንደኛ ዓ.ም. ማለት ነው፡፡ ስለዚህ 1 AUC ሮም የተመሠረተችበትን ቀን ይወክላል፡፡ 5 AUC የሮምን ግዛት አምስተኛ ዓመት ይወክላል ወዘተ.
ዲዮኒሲየስ የሮማው ቄሳር አውግስጦስ ለ43 ዓመታት ከገዛ በኋላ በቄሳር ጢባርዩስ ተተካ የሚለውን ታሪክ አምኖ በመቀበል ቀመሩን በዚህ ላይ መሥርቷል፡፡
በሉቃስ ውንጌል ምዕራፍ 3 ቁጥር 1 እና 2 ላይ ኢየሱስ ክርስቶስ 30 ዓመት ሲሞላው የጢባርዩስ 15ኛ የንግሥ ዓመት እንደሆነ ተመልክቷል፡፡
ኢየሱስ ክርስቶስ በጢባርዮስ ዘመነ መንግሥት 30 ዓመቱ ከሆነ በቄሳር አውግስጦስ አገዛዝ ሥር 15 ዓመት ኖሯል ማለት ነው (ይህም የኢየሱስን ልደት በአውግስጦስ 28ኛ የሥልጣን ዓመት ላይ ያደረገዋል)፡፡
አውግስጦስ የነገሠው በ727 AUC ነው::እዚህ ላይ ተመሥርቶ ዲዮኒሲየስ የክርስቶስ ልደት በ754 AUC ነው ብሎ ደመደመ፡፡
መጽሐፍ ቅዱስ በሉቃስ 1፥5 ላይ ክርስቶስ የተወለደው በሄሮድስ ዘመነ መንግሥት እንደሆነ ይናገራል፡፡ ታሪክ እንደሚናገረው ደግሞ ሄርድስ የሞተው በ750 AUC ነው፡፡ ይህም ዲዮኒሲየስ ክርስቶስ ተወለደ ካለበት አራት ዓመታት ቀደም ብሎ ማለት ነው፡፡ ዮሴፍ ፊትዝመየር የተባሉ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት ፕሮፌሰር ይህ የዲዮኒሲየስ ቀመር የተሳሳተ እንደሆነና በዚሁ ቀመር ላይ የተመሠረተው ክርስቶስ የተወለደው በ1 ዓ.ም. (የክርስቲያኖች ዓመት መጀመርያ ተብሎ ከሚታመንበት ዓመት) ነው የሚለው እምነትም የተሳሳተ እንደሆነ ያስረዳሉ፡፡ እንደ ፕሮፌሰሩ ጥናት ክርስቶስ የተወለደው ሰፕቴምበር(መስከረም) 11 ክርስቶስ ተወለደ ተብሎ ከሚታመንበት ዓመት 3 ዓመት ቀደም ብሎ ነው፡፡ በማን እንደተጻፈ የማይታወቀውና Depaschg Computus በመባል የሚታወቅና ከክርስቶስ ልደት በኋላ በ243 ዓ.ም. በሰሜን አፍሪካ እንደተጻፈ የሚታመን ጽሑፍ ክርስቶስ በፈረንጆቹ ማርች 28 እንደ ተወለደ ይናገራል፡፡
ከሊመንት የተባለ የአሌክሳንደሪያ ሊቀ ጳጳስ ደግሞ በ215 ዓ.ም. በጻፈው ጽሑፍ ውስጥ ክርስቶስ ኖቨምበር(ኅዳር) 18 አንደተወለደ እንደሚያምን ገልጿል፡፡
ከተደረጉ ጥናቶች አንዱም እንኳን ክርስቶስ ዲሴምበር 25 ወይም ታኅሣሥ 29 ተወለደ የሚል የለም፡፡ ይህም እነዚህ ቀናት የክርስቶስ ልደት ነው የሚለው እምነት ከየት መጣ የሚለውን ጥያቄ ያስነሳሉ፡፡ የገና በዓል፣ የገና ዛፍና የገና አባት ወዘተ. አንድ ላይ የነበሩና በአንድ ጊዜ የመጡ ጉዳዮች ሳይሆኑ በየዘመናቱ የተጨመሩ ነገሮች ናቸው፡፡
ይቀጥላል...
ምንጭ:- ethiopianreporter.com
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ክፍል-፩
በጳውሎስ ካሱ
የክርስትና ሃይማኖት ተከታዮች በየዓመቱ በደማቅ (በተለየ የአሜሪካና አውሮፓ) ሁኔታ ከሚያከብሯቸው በዓላት አንዱ ገና ነው፡፡የገና በዓል አከባበር በየአገሩ መጠነኛ ልዩነት ቢኖረውም በየዓመቱ አዳዲስ መሻሻሎች እየተደረገበት ደማቅነቱ እንደቀጠለ መጥቷል፡፡
ይህንኑ ተከትሎም የበዓሉን አጀማመርና ታሪክ ለማግኘት ብዙ ጥናቶች ተደርገዋል:: የጥናቶቹ ግኝትም ብዙዎቹን እርግጥ ይህ በዓል መጽሐፍ ቅዱሳዊ ነውን? ብለው እንዲጠይቁ ሲያደርግ ብዙዎቹን ግን በዓሉን መጽሐፍ ቅዱሳዊ ለማድረግ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶችን በመጥቀስ ትክክለኛነቱን ለማሳየት ይሞክራሉ፡፡የተቀሩት ደግሞ ትኩረታቸውን ከበዓሉ በሚገኘው ደስታ ላይ ብቻ በማድረግ የአያገባኝም አቋም ወስደዋል፡፡ እርግጥ የገና በዓል መጽሐፍ ቅዱሳዊ ነው? መልሱ በሚከተሉት የጥናት ግኝቶች ውስጥ ይገኛል፡፡
ኢየሱስ ክርስቶስ የተወለደው በእርግጥ በፈረንጆቹ ዲሴምበር 25 ወይም በኢትዮጵያዊያን ታኅሣሥ 29 ነውን? አዲስ ኪዳን ኢየሱሰ ክርስቶስ የተወለደበትን ቀን በትክክል አይናገርም::
ከወንጌላቱ ሁሉ መጀመርያ እንደተጻፈ የሚታመነው የማርቆስ ወንጌል ከክርስቶስ ልደት በኋላ በ65 ዓ.ም. የተጻፈ ሲሆን፣ ታሪኩን የሚጀምረው ከኢየሱስ ክርስቶስ ጥምቀት ነው። ይህም የሚጠቁመው የመጀመርያዎቹ ክርስቲያኖች የክርስቶስን የልደት ቀን እንደማያውቁ ለማወቅም ፍላጎት እንዳልነበራቸው ነው፡፡ ይህም አንድ ጥያቄ ማስነሳቱ አልቀረም፤ ክርስቶስ በዲሴምበር 25 ወይም ታኅሣሥ 29 ተወለደ ብሎ የጻፈው ማነው? እንዴትስ አወቀ? ታሪክ እንደሚናገረው ጌታ ተወለደ ተብሎ የሚታመንበትን ዓመት የወሰነው ዲዮኒሲየስ ኤግዚገስ (Dionysisus Exiguus) የተባለ የካቶሊክ መነኩሴ ነው፡፡
ክርስቶስ የተወለደበትን ዓመት ለመወሰን የተጠቀመው ቀመርም የሚከተለውን ይመስላል፡-
በቅድመ ክርስትና ሮም ዓመታት የሚቆጠሩት "ከአበ አርበ ኮንዲታ" (ab Urbe Condita) ማለትም ሮም ከተመሠረተችበት ቀን ጀምሮ ነው፤ ይህም AUC ይባላል እንደኛ ዓ.ም. ማለት ነው፡፡ ስለዚህ 1 AUC ሮም የተመሠረተችበትን ቀን ይወክላል፡፡ 5 AUC የሮምን ግዛት አምስተኛ ዓመት ይወክላል ወዘተ.
ዲዮኒሲየስ የሮማው ቄሳር አውግስጦስ ለ43 ዓመታት ከገዛ በኋላ በቄሳር ጢባርዩስ ተተካ የሚለውን ታሪክ አምኖ በመቀበል ቀመሩን በዚህ ላይ መሥርቷል፡፡
በሉቃስ ውንጌል ምዕራፍ 3 ቁጥር 1 እና 2 ላይ ኢየሱስ ክርስቶስ 30 ዓመት ሲሞላው የጢባርዩስ 15ኛ የንግሥ ዓመት እንደሆነ ተመልክቷል፡፡
ኢየሱስ ክርስቶስ በጢባርዮስ ዘመነ መንግሥት 30 ዓመቱ ከሆነ በቄሳር አውግስጦስ አገዛዝ ሥር 15 ዓመት ኖሯል ማለት ነው (ይህም የኢየሱስን ልደት በአውግስጦስ 28ኛ የሥልጣን ዓመት ላይ ያደረገዋል)፡፡
አውግስጦስ የነገሠው በ727 AUC ነው::እዚህ ላይ ተመሥርቶ ዲዮኒሲየስ የክርስቶስ ልደት በ754 AUC ነው ብሎ ደመደመ፡፡
መጽሐፍ ቅዱስ በሉቃስ 1፥5 ላይ ክርስቶስ የተወለደው በሄሮድስ ዘመነ መንግሥት እንደሆነ ይናገራል፡፡ ታሪክ እንደሚናገረው ደግሞ ሄርድስ የሞተው በ750 AUC ነው፡፡ ይህም ዲዮኒሲየስ ክርስቶስ ተወለደ ካለበት አራት ዓመታት ቀደም ብሎ ማለት ነው፡፡ ዮሴፍ ፊትዝመየር የተባሉ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት ፕሮፌሰር ይህ የዲዮኒሲየስ ቀመር የተሳሳተ እንደሆነና በዚሁ ቀመር ላይ የተመሠረተው ክርስቶስ የተወለደው በ1 ዓ.ም. (የክርስቲያኖች ዓመት መጀመርያ ተብሎ ከሚታመንበት ዓመት) ነው የሚለው እምነትም የተሳሳተ እንደሆነ ያስረዳሉ፡፡ እንደ ፕሮፌሰሩ ጥናት ክርስቶስ የተወለደው ሰፕቴምበር(መስከረም) 11 ክርስቶስ ተወለደ ተብሎ ከሚታመንበት ዓመት 3 ዓመት ቀደም ብሎ ነው፡፡ በማን እንደተጻፈ የማይታወቀውና Depaschg Computus በመባል የሚታወቅና ከክርስቶስ ልደት በኋላ በ243 ዓ.ም. በሰሜን አፍሪካ እንደተጻፈ የሚታመን ጽሑፍ ክርስቶስ በፈረንጆቹ ማርች 28 እንደ ተወለደ ይናገራል፡፡
ከሊመንት የተባለ የአሌክሳንደሪያ ሊቀ ጳጳስ ደግሞ በ215 ዓ.ም. በጻፈው ጽሑፍ ውስጥ ክርስቶስ ኖቨምበር(ኅዳር) 18 አንደተወለደ እንደሚያምን ገልጿል፡፡
ከተደረጉ ጥናቶች አንዱም እንኳን ክርስቶስ ዲሴምበር 25 ወይም ታኅሣሥ 29 ተወለደ የሚል የለም፡፡ ይህም እነዚህ ቀናት የክርስቶስ ልደት ነው የሚለው እምነት ከየት መጣ የሚለውን ጥያቄ ያስነሳሉ፡፡ የገና በዓል፣ የገና ዛፍና የገና አባት ወዘተ. አንድ ላይ የነበሩና በአንድ ጊዜ የመጡ ጉዳዮች ሳይሆኑ በየዘመናቱ የተጨመሩ ነገሮች ናቸው፡፡
ይቀጥላል...
ምንጭ:- ethiopianreporter.com
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍3
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ጌታን ኢየሱስን ያስነሣው እኛን ደግሞ ከኢየሱስ ጋር እንዲያስነሣን ከእናንተም ጋር እንዲያቀርበን እናውቃለንና።”
2ኛ ቆሮ 4፥14
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ጌታን ኢየሱስን ያስነሣው እኛን ደግሞ ከኢየሱስ ጋር እንዲያስነሣን ከእናንተም ጋር እንዲያቀርበን እናውቃለንና።”
2ኛ ቆሮ 4፥14
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤2👍1
ለምን ተወለደ?
በሳምሶን ጥላሁን
‘ለምን ተወለደ?’ የሚለው ጥያቄ የሕይወት ጥያቄ ነው። ሆኖም ግን በአዲስ ኪዳን “ተወለደ” የሚለው ቃል፣ ወልድ ፍጹም ሰው ስለ መሆኑ (ስለ ነገረ ትሥጉት/incarnation) ከሚነግሩን ገለጻዎች አንዱና ዋነኛው ይሁን እንጂ፣ “ብቸኛው” ግን አይደለም። በአዲስ ኪዳን የትሥጉት ነገረ መለኮት በብዙ ቃላት ያሸበረቀ ነው። “ተወለደ” ከሚለው ዕሳቤ በተጨማሪ፣ በአዲስ ኪዳን እኩል አጽንዖት ተሰጥቷቸው የምናገኛቸው ተጨማሪ ነገረ መለኮታዊና ሙያዊ የሆኑ ገለጻዎች አሉ። በእነዚህ ገለጻዎች የነገረ ትሥጉት ግንዛቤያችን ሊዳብር ይገባዋል።
የዚህ ዐጭር ጽሑፍ ዐላማ፣ ስለ ልደቱ (ስለ ገና) በግል በአምልኮ ጊዜ ስናሰላስል ይሁን፣ በኅብረት ስንዘምረው፣ በስብከታችን ስናውጅ ወይም በአስተምህሮ ስናብራራ፣ የዳበረና የፋፋ የነገረ ትሥጉት መረዳት እንዲኖረን ይረዳን ሐሳብ ለማቀበል ነው።
የአዲስ ኪዳን የነገረ ትሥጉት ትርክት በሚከተሉት ቃላት/ሐረጎች ያሸበረቀ ነው፦
👉“ተወለደ” (ሉቃ 2፥10)
👉“ሥጋ ሆነ” (ዮሐ 1፥14)
👉“በመካከላችን ዐደረ” (ዮሐ 1፥14)
👉“ራሱን ባዶ አደረገ”
👉“ተገለጠ” (1ዮሐ 3፥8)
👉“ከሰማይ ወረደ” (ዮሐ 3፥11–13)
👉“ተላከ” (ገላ 4፥4፤ ሮሜ 8፥3)
👉“የባሪያን መልክ ያዘ” (ፊል 2፥5–7)
👉“መጣ” (1ጢሞ 1፥15)
👉“በሥጋና በደም ተካፈለ” (ዕብ 2፥24–25)
👉“በኀጢአተኛ ሥጋ ምሳሌ” (ሮሜ 8፥3) ወዘተ.
እነዚህን ቃላት/ሐረጎች በሦስት መደብ እናስቀምጣቸው፦
✍የመጀመሪያው መደብ ተጸንሶ ከመወለዱ አንጻርና እና የሰውን ባሕርይ ሙሉ ገንዘቡ አድርጎ መውሰዱን የሚያስገነዝቡን ናቸው (ተወለደ፣ ሥጋ ሆነ፣ የባሪያን መልክ ያዘ፣ በሰው አምሳል ሆነ፣ በኀጢአተኛ ሥጋ ምሳሌ…)።
✍ሁለተኛው መደብ ከሞላ ጎደል፣ ሰው ከመሆኑ በፊት ስለ ነበረው ቅድመ ሕላዌ የሚያስገነዝቡን ናቸው (ከሰማይ ወረደ፣ ራሱን ባዶ አደረገ፣ ተገለጠ፣ በመካከላችን ዐደረ…)።
✍ሦስተኛው መደብ ደግሞ የመወለዱን ዐላማ ያሳዩናል (ተላከ፣ መጣ…)።
እነዚህ መደቦች “ለምን ተወለደ?” የሚለውን ጥያቄ የሚመልሱ ሲሆን፣ ነገረ ትሥጉትን እና ነገረ ድነት የተያያዙ መሆናቸውን ያመለክቱናል።
ተወለደ (τίκτω, γεννάω)
“መልአኩም እንዲህ አላቸው፦ እነሆ፤ ለሕዝቡ ሁሉ የሚሆን ታላቅ ደስታ የምሥራች እነግራችኋለሁና አትፍሩ፤ ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኃኒት እርሱም ክርስቶስ ጌታ የሆነ ተወልዶላችኋልና።” (ሉቃ 2፥10–11)።
የገና በዓል በደረሰ ጊዜ፣ ስለ ሕፃኑ ኢየሱስ ከሚመጡልን ምስሎች የተለመደ ሆኖ የሚነገረው፣ “በግርግም የተኛ” ሕፃን የሚለው ነው። ይህ በርግጥ አስደናቂ እውነት ነው። ለዘመናት የሚጠበቀው የምሥራች ቃል አሁን ታወጀ። ምድር ደስ ይበልሽ፤ የዓለም መድኃኒት የሆነ “ሕፃን”፣ እርሱም የዳዊት ልጅ ክርስቶስ ተወልዷልና። የንጋት ጎህ ቀደደ። ተስፋው ተገለጠ።
በመጀመሪያ ይህ “ተወለደ” የሚለው ቃል አስረግጦ የሚያሳየን፣ የሕፃኑ መወለድ በአንድ እጅ አስቀድሞ እግዚአብሔር ከሰጠው የድነት ታሪክ ፍጻሜ ጋር መያያዙን ነው። ለዚህ ነው በሉቃስ ወንጌል ላይ ከክርስቶስ መወለድ ጋር ተያይዞ “ተስፋው ተፈጸመ” የሚለው ዕሳቤ እንደ አዝማች የሚደረደረው።
• የማርያም መዝሙር፤ "ለአባቶቻችን እንደ ተናገረ፣ ለአብርሃምና ለዘሩ ያለውን ለዘላለም ለመጠበቅ ነው።” (ሉቃ 1፥55)፤
• የዘካርያስ ትንቢት፤ “ጥንት በቅዱሳን ነቢያቱ አፍ እንደ ተናገረው … ይህንም ያደረገው ለአባቶቻችን ምሕረቱን ለማሳየት፣ ቅዱስ ኪዳኑን ለማስታወስ፣ ለአባታችን ለአብርሃም የማለውን መሓላ ለማሰብ ...” (1፥72–73)፤
• የስምዖን ባርኮት፤ “ዐይኖቼ በሰዎች ሁሉ ፊት ያዘጋጀኸውን ማዳንህን አይተዋልና”፤
የነቢዪቱ ሐና ስብከት፤ “የኢየሩሳሌምንም መቤዠት ለሚጠባበቁ” ሁሉ ስለ ሕፃኑ ተናገረች፤
በሁለተኛ ደረጃ ደግሞ “ተወለደ” የሚለው ቃል ኢየሱስ ፍጹም ሕፃን ልጅ መሆኑን ያሳየናል፤ “በጥበብና በቁመት፣ በሞገስም በእግዚአብሔርና በሰው ፊት” ማደግ ያስፈልገው ነበር። በሰው ስም “ኢየሱስ” ተብሎ ተሰይሟል። ትውልዱ በዳዊትም ቤት ተቆጥሯል። እንደ ማኛውም ሕፃን ጡት ጠብቷል፤ ፊደል ቆጥሯል፤ ተርቧል፤ አልቅሷል...። ሕፃኑ ለዐደጋ ግሉጥ ከመሆኑ የተነሣ፣ ዮሴፍ ወደ ግብፅ ይዞት ሊሰደድ የተገባ ነበር።
የማይወሰነው አምላክ ተወሰነ። ይህ ሕፃን በአንድ እጅ እንደ ማንም ሕፃን እንደ ነበር፣ ደግሞም በሌላ እጅ ‘ልዩ ሕፃን’ ይህም “መለኮታዊ” መሆኑን ማቴዎስ ሲያሳየን፣ “የተፀነሰው ከመንፈስ ቅዱስ ነው … እርሱ ሕዝቡን ከኀጢአታቸው ያድናቸዋል” ይላል። ይህ ሕፃን ሰው ብቻ ሳይሆን፣ “አዳኝም” ጭምር ነው።
ሉቃስ ደግሞ ይህንን ውጥረት፣ “መንፈስ ቅዱስ በአንቺ ላይ ይመጣል፤ ከአንቺ የሚወለደው ቅዱስ የእግዚአብሔር ልጅ ይባላል” በማለት ሕፃኑን “የእግዚአብሔር ልጅ” ይለዋል (ከመሲሓዊ ስያሜው ባለፈ)። እንዴት ሁለቱ በአንድ ጊዜ እውነት ሆኑ? “ምሥጢር! ምሥጢር!” ብለን ከመጮህ የዘለለ እውቀት የለንም።
ይቀጥላል ...
ምንጭ:- hintset.com
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
በሳምሶን ጥላሁን
‘ለምን ተወለደ?’ የሚለው ጥያቄ የሕይወት ጥያቄ ነው። ሆኖም ግን በአዲስ ኪዳን “ተወለደ” የሚለው ቃል፣ ወልድ ፍጹም ሰው ስለ መሆኑ (ስለ ነገረ ትሥጉት/incarnation) ከሚነግሩን ገለጻዎች አንዱና ዋነኛው ይሁን እንጂ፣ “ብቸኛው” ግን አይደለም። በአዲስ ኪዳን የትሥጉት ነገረ መለኮት በብዙ ቃላት ያሸበረቀ ነው። “ተወለደ” ከሚለው ዕሳቤ በተጨማሪ፣ በአዲስ ኪዳን እኩል አጽንዖት ተሰጥቷቸው የምናገኛቸው ተጨማሪ ነገረ መለኮታዊና ሙያዊ የሆኑ ገለጻዎች አሉ። በእነዚህ ገለጻዎች የነገረ ትሥጉት ግንዛቤያችን ሊዳብር ይገባዋል።
የዚህ ዐጭር ጽሑፍ ዐላማ፣ ስለ ልደቱ (ስለ ገና) በግል በአምልኮ ጊዜ ስናሰላስል ይሁን፣ በኅብረት ስንዘምረው፣ በስብከታችን ስናውጅ ወይም በአስተምህሮ ስናብራራ፣ የዳበረና የፋፋ የነገረ ትሥጉት መረዳት እንዲኖረን ይረዳን ሐሳብ ለማቀበል ነው።
የአዲስ ኪዳን የነገረ ትሥጉት ትርክት በሚከተሉት ቃላት/ሐረጎች ያሸበረቀ ነው፦
👉“ተወለደ” (ሉቃ 2፥10)
👉“ሥጋ ሆነ” (ዮሐ 1፥14)
👉“በመካከላችን ዐደረ” (ዮሐ 1፥14)
👉“ራሱን ባዶ አደረገ”
👉“ተገለጠ” (1ዮሐ 3፥8)
👉“ከሰማይ ወረደ” (ዮሐ 3፥11–13)
👉“ተላከ” (ገላ 4፥4፤ ሮሜ 8፥3)
👉“የባሪያን መልክ ያዘ” (ፊል 2፥5–7)
👉“መጣ” (1ጢሞ 1፥15)
👉“በሥጋና በደም ተካፈለ” (ዕብ 2፥24–25)
👉“በኀጢአተኛ ሥጋ ምሳሌ” (ሮሜ 8፥3) ወዘተ.
እነዚህን ቃላት/ሐረጎች በሦስት መደብ እናስቀምጣቸው፦
✍የመጀመሪያው መደብ ተጸንሶ ከመወለዱ አንጻርና እና የሰውን ባሕርይ ሙሉ ገንዘቡ አድርጎ መውሰዱን የሚያስገነዝቡን ናቸው (ተወለደ፣ ሥጋ ሆነ፣ የባሪያን መልክ ያዘ፣ በሰው አምሳል ሆነ፣ በኀጢአተኛ ሥጋ ምሳሌ…)።
✍ሁለተኛው መደብ ከሞላ ጎደል፣ ሰው ከመሆኑ በፊት ስለ ነበረው ቅድመ ሕላዌ የሚያስገነዝቡን ናቸው (ከሰማይ ወረደ፣ ራሱን ባዶ አደረገ፣ ተገለጠ፣ በመካከላችን ዐደረ…)።
✍ሦስተኛው መደብ ደግሞ የመወለዱን ዐላማ ያሳዩናል (ተላከ፣ መጣ…)።
እነዚህ መደቦች “ለምን ተወለደ?” የሚለውን ጥያቄ የሚመልሱ ሲሆን፣ ነገረ ትሥጉትን እና ነገረ ድነት የተያያዙ መሆናቸውን ያመለክቱናል።
ተወለደ (τίκτω, γεννάω)
“መልአኩም እንዲህ አላቸው፦ እነሆ፤ ለሕዝቡ ሁሉ የሚሆን ታላቅ ደስታ የምሥራች እነግራችኋለሁና አትፍሩ፤ ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኃኒት እርሱም ክርስቶስ ጌታ የሆነ ተወልዶላችኋልና።” (ሉቃ 2፥10–11)።
የገና በዓል በደረሰ ጊዜ፣ ስለ ሕፃኑ ኢየሱስ ከሚመጡልን ምስሎች የተለመደ ሆኖ የሚነገረው፣ “በግርግም የተኛ” ሕፃን የሚለው ነው። ይህ በርግጥ አስደናቂ እውነት ነው። ለዘመናት የሚጠበቀው የምሥራች ቃል አሁን ታወጀ። ምድር ደስ ይበልሽ፤ የዓለም መድኃኒት የሆነ “ሕፃን”፣ እርሱም የዳዊት ልጅ ክርስቶስ ተወልዷልና። የንጋት ጎህ ቀደደ። ተስፋው ተገለጠ።
በመጀመሪያ ይህ “ተወለደ” የሚለው ቃል አስረግጦ የሚያሳየን፣ የሕፃኑ መወለድ በአንድ እጅ አስቀድሞ እግዚአብሔር ከሰጠው የድነት ታሪክ ፍጻሜ ጋር መያያዙን ነው። ለዚህ ነው በሉቃስ ወንጌል ላይ ከክርስቶስ መወለድ ጋር ተያይዞ “ተስፋው ተፈጸመ” የሚለው ዕሳቤ እንደ አዝማች የሚደረደረው።
• የማርያም መዝሙር፤ "ለአባቶቻችን እንደ ተናገረ፣ ለአብርሃምና ለዘሩ ያለውን ለዘላለም ለመጠበቅ ነው።” (ሉቃ 1፥55)፤
• የዘካርያስ ትንቢት፤ “ጥንት በቅዱሳን ነቢያቱ አፍ እንደ ተናገረው … ይህንም ያደረገው ለአባቶቻችን ምሕረቱን ለማሳየት፣ ቅዱስ ኪዳኑን ለማስታወስ፣ ለአባታችን ለአብርሃም የማለውን መሓላ ለማሰብ ...” (1፥72–73)፤
• የስምዖን ባርኮት፤ “ዐይኖቼ በሰዎች ሁሉ ፊት ያዘጋጀኸውን ማዳንህን አይተዋልና”፤
የነቢዪቱ ሐና ስብከት፤ “የኢየሩሳሌምንም መቤዠት ለሚጠባበቁ” ሁሉ ስለ ሕፃኑ ተናገረች፤
በሁለተኛ ደረጃ ደግሞ “ተወለደ” የሚለው ቃል ኢየሱስ ፍጹም ሕፃን ልጅ መሆኑን ያሳየናል፤ “በጥበብና በቁመት፣ በሞገስም በእግዚአብሔርና በሰው ፊት” ማደግ ያስፈልገው ነበር። በሰው ስም “ኢየሱስ” ተብሎ ተሰይሟል። ትውልዱ በዳዊትም ቤት ተቆጥሯል። እንደ ማኛውም ሕፃን ጡት ጠብቷል፤ ፊደል ቆጥሯል፤ ተርቧል፤ አልቅሷል...። ሕፃኑ ለዐደጋ ግሉጥ ከመሆኑ የተነሣ፣ ዮሴፍ ወደ ግብፅ ይዞት ሊሰደድ የተገባ ነበር።
የማይወሰነው አምላክ ተወሰነ። ይህ ሕፃን በአንድ እጅ እንደ ማንም ሕፃን እንደ ነበር፣ ደግሞም በሌላ እጅ ‘ልዩ ሕፃን’ ይህም “መለኮታዊ” መሆኑን ማቴዎስ ሲያሳየን፣ “የተፀነሰው ከመንፈስ ቅዱስ ነው … እርሱ ሕዝቡን ከኀጢአታቸው ያድናቸዋል” ይላል። ይህ ሕፃን ሰው ብቻ ሳይሆን፣ “አዳኝም” ጭምር ነው።
ሉቃስ ደግሞ ይህንን ውጥረት፣ “መንፈስ ቅዱስ በአንቺ ላይ ይመጣል፤ ከአንቺ የሚወለደው ቅዱስ የእግዚአብሔር ልጅ ይባላል” በማለት ሕፃኑን “የእግዚአብሔር ልጅ” ይለዋል (ከመሲሓዊ ስያሜው ባለፈ)። እንዴት ሁለቱ በአንድ ጊዜ እውነት ሆኑ? “ምሥጢር! ምሥጢር!” ብለን ከመጮህ የዘለለ እውቀት የለንም።
ይቀጥላል ...
ምንጭ:- hintset.com
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍6
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“በዚህ የእግዚአብሔር ፍቅር በእኛ ዘንድ ተገለጠ፥ በእርሱ በኩል በሕይወት እንኖር ዘንድ እግዚአብሔር አንድ ልጁን ወደ ዓለም ልኮታልና።”
1ኛ ዮሐንስ 4፥9
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“በዚህ የእግዚአብሔር ፍቅር በእኛ ዘንድ ተገለጠ፥ በእርሱ በኩል በሕይወት እንኖር ዘንድ እግዚአብሔር አንድ ልጁን ወደ ዓለም ልኮታልና።”
1ኛ ዮሐንስ 4፥9
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤2
ቅዱሳት መጻሕፍት
ለምን ተወለደ? በሳምሶን ጥላሁን ‘ለምን ተወለደ?’ የሚለው ጥያቄ የሕይወት ጥያቄ ነው። ሆኖም ግን በአዲስ ኪዳን “ተወለደ” የሚለው ቃል፣ ወልድ ፍጹም ሰው ስለ መሆኑ (ስለ ነገረ ትሥጉት/incarnation) ከሚነግሩን ገለጻዎች አንዱና ዋነኛው ይሁን እንጂ፣ “ብቸኛው” ግን አይደለም። በአዲስ ኪዳን የትሥጉት ነገረ መለኮት በብዙ ቃላት ያሸበረቀ ነው። “ተወለደ” ከሚለው…
...የቀጠለ
ለምን ተወለደ?
በሳምሶን ጥላሁን
ሥጋ ሆነ (γίνομαι)
“ቃልም ሥጋ ሆነ…”። የዮሐንስ ወንጌል፣ እንደ ማቴዎስ፣ አሊያም እንደ ሉቃስ በውስጡ “የልደት” ትረካን አያካትትም። በዮሐንስ ሕፃን ሲወልድ አናይም። የምናገኘው “ቃል” ከተሰኘና ቅድመ ሕላዌ ካለው አካል ጀምሮ፣ ወደ ነገረ ትሥጉቱ የሚሄድ እንቅስቃሴ ነው። ይህ ከላይ ወደታች የሚሄድ የአተራረክ ዘዬ፣ ዮሐንስን ከሌሎቹ ወንጌላውያን ይለየዋል። በቅድመ ትሥጉት ማንነቱ፣ ቃል “ነበረ” ይለናል። የሚጠቀመው “ሆነ” የሚለውን የመሆን ግሥ ሲሆን፣ ይህም ‘በመጀመሪያ ቃል የሆነ፤ እግዚአብሔር የሆነ…'፣ ሳይሆን “ነበር” የሚለውን የመሆን ግሥ በመጠቀም ነው። ይኸውም፣ “በመጀመሪያ ቃል ነበረ … ቃልም ከእግዚአብሔርም ጋር ነበረ … ቃልም እግዚአብሔርም ነበረ።” “ነበር”፣ “ነበር”፣ “ነበር”! ሆኖም ግን ቁጥር 14 ላይ ሲደርስ፣ ዮሐንስ የመሆን ግሡን ከ“ነበረ” ወደ “ሆነ” ይለውጠዋል፤ ‘ቃልም ሥጋ ነበረ' ከማለት ይልቅ፣ “ቃልም ሥጋ ሆነ” በማለት። “ሆነ … ዐደረ”።
ይህ ገለጻ አስረግጦ የሚያመለክተን ቁም ነገር፣ “ቃል” በሁለት መደብ በአንድ ጊዜ የሚመደብ መሆኑን ነው። በአንድ በኩል ቃል በመለኮት መደብ ይኖራል። እርሱ አማክሎተ ፍጥረት ነው (Agent of Creation)፤ አማክሎተ ድነት ነው (Agent of Redemption)፤ ቃል አማክሎተ አስተርዮ ነው (Agent of Revelation)። በሌላ በኩል ደግሞ ቃል ከዚህ ቀደም “ያልነበረውን” ነገር ወሰደ፤ “ሥጋ ሆነ”።
በቁጥር 1 ላይ፣ “እግዚአብሔር” የሚለውን ቃል ዮሐንስ በሁለት ዐይነት መንገድ ይጠቀመዋል። አንድኛው አብን የሚወክል የመለኮት አካል ስም ሆኖ ጥቅም ላይ ሲውል፣ “ቃልም ከእግዚአብሔር ጋር ነበር” እርሱም አብ ነው። ሁለተኛው ደግሞ፣ “እግዚአብሔር” የሚለው ቃል የመለኮት ባሕርይን ገላጭ ሆኖ ጥቅም ላይ ውሏል፤ “ቃልም እግዚአብሔር ነበረ”። ስለዚህ ይህ መለኮታዊ ባሕርይ ገንዘቡ ሆኖ ይኖር የነበረው፣ እንዲሁም መለኮታዊ ከሆነው ከሌላኛው አካል ፊት ለፊት ሕልው ሆኖ ይኖር የነበረው ቃል፣ መለኮታዊ ባሕርይውን ሳይለቅቅ፣ ከዚህ ቀደም ያልነበረውን “ሰብዓዊ ባሕርይ” ገንዘቡ አደረገ።
እንቅስቃሴው ከላይ ከምጡቅ ሕልውናው ይጀምርና ወደ ምድር ሰብዓዊ ማንነቱ ይዘልቃል።
ቃል “ሥጋ” አልመሰለም፤ ቃል ሥጋ ሆነ እንጂ!
ይህ አቅጣጫ በዮሐንስ ትረካ ኋላ እየዳበረ ይመጣል። ይህ ሕይወትና ብርሃን የሆነው ቃል (ዮሐ 1፥4-5)፣ ሥጋ ሆኖ ተገልጦ (1፥14)፣ የእግዚአብሔርን ፍቅር በተለይ በመስቀል ሞቱ ተርኮልን (3፥16) ወደ ነበረበት በክብር ይመለሳል።
እግዚአብሔር ሕይወት፣ ብርሃን፣ ፍቅር ነው። የፍቅሩ፣ የሕይወቱና የብርሃኑ መገለጫ ሞገድ፣ የክብሩም መንጸባረቂያ ሥፍራ ‘ትሥጉቱ’ ነው። ኢየሱስ የእግዚአብሔር ክብር መገለጫ ነው። ዮሐንስ የክርስቶን ልደት “ተወለደ” በሚለው ቃል ሳይሆን፣ “ሆነ” በሚለው ስለተረከልን፣ ነገረ ትሥጉቱን ከሌላና ከምጡቅ ገጽታው አንጻር እንድናይ ረድቶናል።
መልካም በዓል!
ምንጭ:- hintset.com
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ለምን ተወለደ?
በሳምሶን ጥላሁን
ሥጋ ሆነ (γίνομαι)
“ቃልም ሥጋ ሆነ…”። የዮሐንስ ወንጌል፣ እንደ ማቴዎስ፣ አሊያም እንደ ሉቃስ በውስጡ “የልደት” ትረካን አያካትትም። በዮሐንስ ሕፃን ሲወልድ አናይም። የምናገኘው “ቃል” ከተሰኘና ቅድመ ሕላዌ ካለው አካል ጀምሮ፣ ወደ ነገረ ትሥጉቱ የሚሄድ እንቅስቃሴ ነው። ይህ ከላይ ወደታች የሚሄድ የአተራረክ ዘዬ፣ ዮሐንስን ከሌሎቹ ወንጌላውያን ይለየዋል። በቅድመ ትሥጉት ማንነቱ፣ ቃል “ነበረ” ይለናል። የሚጠቀመው “ሆነ” የሚለውን የመሆን ግሥ ሲሆን፣ ይህም ‘በመጀመሪያ ቃል የሆነ፤ እግዚአብሔር የሆነ…'፣ ሳይሆን “ነበር” የሚለውን የመሆን ግሥ በመጠቀም ነው። ይኸውም፣ “በመጀመሪያ ቃል ነበረ … ቃልም ከእግዚአብሔርም ጋር ነበረ … ቃልም እግዚአብሔርም ነበረ።” “ነበር”፣ “ነበር”፣ “ነበር”! ሆኖም ግን ቁጥር 14 ላይ ሲደርስ፣ ዮሐንስ የመሆን ግሡን ከ“ነበረ” ወደ “ሆነ” ይለውጠዋል፤ ‘ቃልም ሥጋ ነበረ' ከማለት ይልቅ፣ “ቃልም ሥጋ ሆነ” በማለት። “ሆነ … ዐደረ”።
ይህ ገለጻ አስረግጦ የሚያመለክተን ቁም ነገር፣ “ቃል” በሁለት መደብ በአንድ ጊዜ የሚመደብ መሆኑን ነው። በአንድ በኩል ቃል በመለኮት መደብ ይኖራል። እርሱ አማክሎተ ፍጥረት ነው (Agent of Creation)፤ አማክሎተ ድነት ነው (Agent of Redemption)፤ ቃል አማክሎተ አስተርዮ ነው (Agent of Revelation)። በሌላ በኩል ደግሞ ቃል ከዚህ ቀደም “ያልነበረውን” ነገር ወሰደ፤ “ሥጋ ሆነ”።
በቁጥር 1 ላይ፣ “እግዚአብሔር” የሚለውን ቃል ዮሐንስ በሁለት ዐይነት መንገድ ይጠቀመዋል። አንድኛው አብን የሚወክል የመለኮት አካል ስም ሆኖ ጥቅም ላይ ሲውል፣ “ቃልም ከእግዚአብሔር ጋር ነበር” እርሱም አብ ነው። ሁለተኛው ደግሞ፣ “እግዚአብሔር” የሚለው ቃል የመለኮት ባሕርይን ገላጭ ሆኖ ጥቅም ላይ ውሏል፤ “ቃልም እግዚአብሔር ነበረ”። ስለዚህ ይህ መለኮታዊ ባሕርይ ገንዘቡ ሆኖ ይኖር የነበረው፣ እንዲሁም መለኮታዊ ከሆነው ከሌላኛው አካል ፊት ለፊት ሕልው ሆኖ ይኖር የነበረው ቃል፣ መለኮታዊ ባሕርይውን ሳይለቅቅ፣ ከዚህ ቀደም ያልነበረውን “ሰብዓዊ ባሕርይ” ገንዘቡ አደረገ።
እንቅስቃሴው ከላይ ከምጡቅ ሕልውናው ይጀምርና ወደ ምድር ሰብዓዊ ማንነቱ ይዘልቃል።
ቃል “ሥጋ” አልመሰለም፤ ቃል ሥጋ ሆነ እንጂ!
ይህ አቅጣጫ በዮሐንስ ትረካ ኋላ እየዳበረ ይመጣል። ይህ ሕይወትና ብርሃን የሆነው ቃል (ዮሐ 1፥4-5)፣ ሥጋ ሆኖ ተገልጦ (1፥14)፣ የእግዚአብሔርን ፍቅር በተለይ በመስቀል ሞቱ ተርኮልን (3፥16) ወደ ነበረበት በክብር ይመለሳል።
እግዚአብሔር ሕይወት፣ ብርሃን፣ ፍቅር ነው። የፍቅሩ፣ የሕይወቱና የብርሃኑ መገለጫ ሞገድ፣ የክብሩም መንጸባረቂያ ሥፍራ ‘ትሥጉቱ’ ነው። ኢየሱስ የእግዚአብሔር ክብር መገለጫ ነው። ዮሐንስ የክርስቶን ልደት “ተወለደ” በሚለው ቃል ሳይሆን፣ “ሆነ” በሚለው ስለተረከልን፣ ነገረ ትሥጉቱን ከሌላና ከምጡቅ ገጽታው አንጻር እንድናይ ረድቶናል።
መልካም በዓል!
ምንጭ:- hintset.com
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤1
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ከሥጋ የተነሣ ስለ ደከመ ለሕግ ያልተቻለውን፥ እግዚአብሔር የገዛ ልጁን በኃጢአተኛ ሥጋ ምሳሌ በኃጢአትም ምክንያት ልኮ አድርጎአልና፤ እንደ መንፈስ ፈቃድ እንጂ እንደ ሥጋ ፈቃድ በማንመላለስ በእኛ የሕግ ትእዛዝ ይፈጸም ዘንድ ኃጢአትን በሥጋ ኰነነ።”
ሮሜ 8፥3-4
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ከሥጋ የተነሣ ስለ ደከመ ለሕግ ያልተቻለውን፥ እግዚአብሔር የገዛ ልጁን በኃጢአተኛ ሥጋ ምሳሌ በኃጢአትም ምክንያት ልኮ አድርጎአልና፤ እንደ መንፈስ ፈቃድ እንጂ እንደ ሥጋ ፈቃድ በማንመላለስ በእኛ የሕግ ትእዛዝ ይፈጸም ዘንድ ኃጢአትን በሥጋ ኰነነ።”
ሮሜ 8፥3-4
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍2❤1